Quantcast
Channel: ዘ-ሐበሻ – Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 8745 articles
Browse latest View live

ኢትዮጵያ የብሄራዊ እርቅ ኮሚሽን ማቋቋም የሚያስፈልጋት ጊዜ ላይ ናት (ገለታው ዘለቀ)

$
0
0

   ገለታው ዘለቀ  

reconciliatioባለፉት ጥቂት ተከታታይ ጽሁፎች ላይ እንደተወያየነው በስምምነት ላይ የተመሰረተ ባህላዊ ውህደት ውስጥ መግባት ኢትዮጵያን እንደገና ለማነጽ ኣማራጭ መፍትሄ ይሆናል። ታዲያ በስምምነት ላይ የተመሰረተ ባህላዊ ውህደት ላሉብን ውስብስብ ሁለንተናዊ ችግሮች ሁሉ መፍትሄ ይሆናል ማለት ሳይሆን ቅድሚያ ተሰጥቷቸው ሊፈቱ የሚገባቸውን ባህላዊ ማህበራዊ ችግሮች መስመር በማስያዝ በሂደት እየተፈቱ እንዲሄዱ ከማድረጉም በላይ ሌሎች ችግሮችን ለመፍታት ደግሞ ቀጥተኛ ያልሆነ ኣስተዋጾ ስላለው ነው።   በችግር ኣፈታት ጊዜ ከሚመጡት መፍትሄዎች መካከል የትኛውን ብናስቀድም ነው ሌላውን ችግርም ኣብሮ ሊፈታልን የሚችለው ብለንም እንጠይቃለንና በዚህ ረገድ በስምምነት ላይ የተመሰረተ ባህላዊ ውህደት ውስጥ መግባት ሌሎች መጋቢና ተለጣጣቂ ችግሮችን ለመፍታት ይጠቅማል ከሚል ነው።

ባለፉት ዘመናችን ያሉብንን ሃገራዊ ችግሮች ሁሉ ስንዘረዝር ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ ፣ ምናምን እያልን ለያይተን እንዘርዝራቸው እንጂ ሁሉንም ችግሮች ለመፍታት የምንሄድበት መንገድ ግን ፖለቲካዊ ይዘት ባለው መንገድ ነው። ፖለቲካዊ ችግሮቻችንን ፖለቲካዊ ይዘት ባለው መንገድ፣ ማህበራዊውን ደግሞ ማህበራዊ በሆነ መንገድ፣ ኢኮኖሚውንና ሌሎቹንም እንደ ተፈጥሯቸው ከመፍታት ይልቅ ለሁሉም ችግር ፖለቲካን የችግር መፍቻ ቁልፍ ኣድርገን መውሰዳችንና የፖለቲካው ጣልቃ ገብነት በማየሉ ችግሮቻችን መፍትሄ ሳያገኙ እንዲቆዩ ያደረገ ይመስላል። ለማህበራዊ ችግሮቻችን ሁሉ ፖለቲካዊ ይዘት ያለው መፍትሄ ከማምጣት ይልቅ ባህላዊና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዩችን ከባህርያቸው ኣንጻር ለመፍታት ብንጥር ችግሮቻችን ኣሁን ያሉትን ያህል ኣይበዙም ነበር። በኣሁኑ ሰዓት ፖለቲካው ማህበራዊውን ህይወታችንን የነካበት ምክንያት የማያገባው ውስጥ ገብቶ በመገኘቱ ነው።

በዛሬው ውይይታችን የምናነሳው ጉዳይ በስምምነት ላይ የተመሰረተ ባህላዊ ውህደት ስንል ኣንድ ቁልፍ ቃል በዚህ የመወያያ ርእስ ውስጥ ይሰመርበታል። ይህም  ስምምነት የሚለው ነው። ስምምነት ስንል ወይም እንዴት ኣድርገን ነው ወደ ስምምነት የምንመጣው ስንል  በዚህ ኣገባብ ሶስት ጉዳዩችን ይዳስሳል።

1. ያለፈውን ታሪካችንን እንዴት ኣድርገን ነው ወደ ስምምነት የምንመጣው? ታሪካዊ ግድፈቶችን እንዴት እንፍታቸው? እንዴትስ እንያቸው? በሚለው ዙሪያ ያጠነጥናል::

2. ችግሮቻችን ታሪካዊ ብቻ ሳይሆኑ ኣሁን ድረስ ስላሉ እነዚህን ችግሮች እንዴት እንያቸው?  እንዴትስ እንዳይቀጥሉ ማድረግ እንችላለን? የሚለውን ይይዛል

3. ሁላችን የምንፈልጋትን የወደፊት ኢትዮጵያን እንዴት ኣድርገን ነው በጋራ ጥሩ መሰረት ጥለን መጻኢ እድሏን የምናበጀው? የሚለውንም ይይዛል።

እንግዲህ በነዚህ ከፍ ብለን በዘረዘርናቸው ኣሳቦች ዙሪያ ስምምነት ላይ መድረስ ያስፈልጋል ስንል በምን መንገድ ነው የምንወያየውና የምንስማማው? የትና በማን ኣማካኝነት ይፈጸማል? የሚሉ በጣም ተግባር የናፈቃቸው ጥያቄዎች መነሳታቸው ኣይቀርም። ምክንያቱም ሃገራችን ውስጥ ላሉት ችግሮች የመፍትሄ ኣሳብ ኣይደለም የጠፋው:: በየጊዜው በቡድንም በግልም ጠቃሚና የሃገርን ችግር ሊያቃልል የሚችል ኣሳብ ይመጣል:: ነገር ግን እነዚህን የመፍትሄ ኣሳቦች የሚያደራጅና መልክ የሚያስይዝ ባለመኖሩ እንዲሁ ኣንዱን እያነሳን ኣንዱን እየጣልን እንኖራለን።

በዛሬው ውይይታችን ስምምነት የሚለውን ኣሳብ እንዴት ልናመጣው እንደምንችል ተግባራዊ ሃሳቦችን እናነሳለን። እንግዲህ ወደ ነጥባችን እንውረድና ስምምነትን ልናመጣበት ከምንችልባቸው ዘዴዎች ኣንዱ የብሄራዊ እርቅ ኮሚሽንን ኣቋቁሞ በመስራት ነው። ይህ ኮሚሽን ኣሁን በስልጣን ላይ ያለው መንግስት ቢደግፈውና ኣብሮ ቢሳተፍ እሰየው ካልሆነም ግን ከመንግስት እውቅና ውጭ መቋቋም ይችላል። መንግስት ደገፈው ኣልደገፈው የሚያመጣው ችግር ኣይኖርም። በዚህ ጉዳይ ላይ ወደ ሁዋላ እንወያያለን። ለኣሁኑ ስለ ብሄራዊ እርቅ መሰረታዊ ጉዳዮችን ኣንስተን እንወያይ።

ስለ ብሄራዊ እርቅ ምንነትና ይዘት እንዲሁም ኣፈጻጸም ስንወያይ ብሄራዊ እርቅን የምናየው  ባለፈው በተወያየንበት በስምምነት ላይ በተመሰረተ የባህል ውህደት ጽንሰ ሃሳብ ማእቀፍ (framework) ውስጥ ነው።

 

የብሄራዊእርቅምንነት ይዘትና ኣፈጻጸም

ከሁሉ ኣስቀድመን ብሄራዊ እርቅ የሚባለው ጽንሰ ሃሳብ በኢትዮጵያ ሁኔታ ምን ማለት እንደሆነ ልንበይነው ይገባል። ብሄራዊ እርቅ በኣለማችን ታሪክ ውስጥ በብዙ ኣገሮች የተፈጸመ ሲሆን የእርቁ ትርጓሜና ኣፈጻጸም እንዲሁም ግቦች ሁሉ ሊለያዩ ይችላሉ። እኛ ኢትዮጵያዊያን ወደ ብሄራዊ እርቅ ለመግባት መጀመሪያ ብሄራዊ እርቅ በኢትዮጵያ ሁኔታ (context) ምን ማለት እንደሆነ በሚገባ ካልተረዳን ብሄራዊ እርቁ ግቡን ላይመታ ይችላል። በመሆኑም ብሄራዊ እርቅ ማለት ምን ማለት ነው? የሚለውን ጉዳይ ኣንስተን በሚገባ እንወያይ። ሃሳባችንን ለማፋፋት ብሄራዊ እርቅን ከኣንዳንድ ሃገሮች ታሪክ ኣንጻር በመጀመሪያ እንመልከት። ለምሳሌ  ያህል በኣውስትራሊያ ውስጥ የብሄራዊ እርቅ ጉዳይ ተነስቷል። እንደሚታወቀው ከታላቋ ብሪታኒያ የኣስራ ስምንተኛው ክፍለዘመን ሰፈራ ፕሮግራም በፊት ኣውስትራሊያ በነባር(indiginious) ህዝቦች የተያዘች ኣገር እንደነበረች ይታወቃል። በሰፈራው ጊዜ በነባሮቹ ህዝቦች ላይ የመፈናቀል፣ የማንገላታት ወንጀሎች ተፈጽመዋል። ዛሬ የኣውስትራሊያ መንግስት ያን የተፈጸመ ታሪካዊ  ስህተት ኣመርቅዞ እንዳይቆይ የወሰደው ርምጃ ብሄራዊ እርቅ ማድረግ ሲሆን ከ 1998 ዓ.ም ጀምሮ መንግስት የብሄራዊ እርቅ ወይም (National sorry day) ኣውጆ በየዓመቱ እየታሰበ ይገኛል። የዚህ የይቅርታ ቀን ኣዋጅ የሚያሳየው ነገር ላለፉት ስህተቶች ሃላፊነት የሚወስድ ኣካል መገኘቱንና የነበረውን ግፍ እውቅና መስጠት መቻላቸውን ለወደፊቱም እንደዚያ ኣይነት ግፍ እንዳይፈጸም ዋስትና መስጠታቸውን ነው። የኣውስትራሊያ ችግር እንደኛ በሶስት መንገድ ላይታይ ይችላል። ይቅርታው ግን ለስንት ኣመት እንደሚደረግ ኣይታወቅም። ዋናው ግን በነባሩ ህዝብ ዘንድ የነፍስ ጽዳት ለማምጣት የታሰበ በመሆኑ ብሄራዊ እርቁ ለኣውስትራሊያውያን ከፍተኛ ጠቀሜታ ኣለው። የነበረውን ታሪካዊ ችግር እውቅና ሰጥቶ ይቅርታ ማወጁ የኣውስትራሊያን ህዝብና መንግስት ልበሰፊነትና ኣርቆ ኣሳቢነት ያሳያል። ነባር ህዝቦችም በዚህ የሚረኩ ይመስለኛል። ከዛ ውጭ ኣፈታሪክ እንደሚናገረው ራሳቸው ነባር ህዝቦችም ከሌላ ክፍለ ዓለም መጥተው የሰፈሩ ናቸው። ዋናው ጥያቄያቸው በሰፈራው ወቅት የነበረው ግፍና በደል ሲሆን እነሆ ዛሬ ተባብረው ዴሞክራሲያዊ መንግስት  በመመስረታቸው ታሪክን ወደ ሁዋላ ኣይቶ ለችግሮች እውቅና ለመስጠት ችለዋል።

ደቡብ ኣፍሪካን ደግሞ እንይ። በደቡብ ኣፍሪካም እንደዚሁ ታሪካዊ የሆነ ብሄራዊ እርቅ የተካሄደባት ኣገር ስትሆን ከኣፓርታይድ ኣገዛዝ ለመላቀቅም ሆነ ከተላቀቀች በሁዋላ ደቡብ ኣፍሪካን በከፍተኛ የመንፈስ ልእልና ሲመራ የነበረው የብሄራዊ እርቅ ስሜት ነው። በደቡብ ኣፍሪካ ብሄራዊ እርቅ ሂደት ውስጥ ከፍተኛ ሚና ከተጫወቱት መካከል Nelson Mandela ኣውራ ናቸው። በኔልሰን ማንዴላ የተመራው ደቡብ ኣፍሪካን እንደገና የማነጽ ስራ ሲጀመር ኣገሪቱ ያለፈችበትን መራራ ችግር ለመፍታት የተጠቀመችው ዘዴ በሪስቶሬቲቭ  ጀስቲስ (Restorative justice) እና ቀስ እያለ በሚያድግ ዴሞክራሲ ቁስልን ማከምና የወደፊቷን የሁሉም የምትሆንን ደቡብ ኣፍሪካን መገንባት ይመስላል።

ደቡብ ኣፍሪካ ከኣፓርታይድ እንደተላቀቀች ወደ ሪትሪቢዩቲቭ ጀስቲስ (Retributive juctice) ኣተኩራ ቢሆን ምናልባትም ውጤታማ ኣትሆንም ነበር። ዋናው ጉዳይ ግን ደቡብ ኣፍሪካ ውስጥ የኣፓርታይድ ገዢዎች ለነበረው ችግር ሃላፊነት የመውሰድና ብሄራዊ እርቅን በሪስቶሬቲቭ ጀስቲስና በዝግ እያለ በሚያድግ ዴሞክራሲ ለመፍታት ፈቃደኛ በመሆናቸው የጥፋትና የሞት መላእክን ከደቡብ ኣፍሪካ ሊያባርሩት ችለዋል። ታላቁ የብሄራዊ እርቅ መሪ ኔልሰን ማንዴላም በዚህ ረገድ የተጫወቱት ሚና ታሪክ ሁሌ ሲዘክረው ይኖራል።

የሩዋንዳን ጉዳይም እናንሳ። ሩዋንዳ በዚህኛው ክፍለ ዘመን የዓለምን ህዝብ ያስደነገጠ ወንጀልን ካስተናገደች በሁዋላ ወንጀሉ ጋብ ሲል የወደፊት ኣቅጣጫዋ ግራ ያጋባት ኣገር ነበረች። ለኣንድ መቶ ቀናት በየቀኑ ስምንት ሺህ ሰዎች፣ በየሰዓቱ ከሶስ መቶ ሰላሳ ሰዎች በላይ ያለቁባት ሃገር የወደፊት እጣ ፈንታዋን ለማሰብ በርግጥም እጅግ ከባድ ስራ ነበር።  በርግጥ ሩዋንዳ ያ ወንጀል ጋብ ሲል ለወደፊት እጣፈንታዋ ወዲያው ኣዋጭ መስመር መስሎ የታያት ብሄራዊ እርቅ ማውረድ ቢሆንም ብሄራዊ እርቁ በሩዋንዳ ሁኔታ ምን መልክ ይያዝ? በምን መልኩ ይፈጸም? የሚሉት ጥያቄዎች ግን በጣም ሊከብዷት የሚችሉ ጉዳዩች ነበሩ። በኣንዳንዶች ዘንድ ኣጥብቆ ይቀነቀን የነበረው ጉዳይ ብሄራዊ እርቁ በሪትሪቢዩቲቭ ጀስቲስ ኣማካኝነት ሊፈጸም ይገባዋል የሚል ነበር። ሁላችን እንደምናውቀው ሪትሪቢዩቲቭ ጀስቲስ ማለት ለወንጀለኛው ተገቢውን ቅጣት በመስጠት የተበዳይን ነፍስ ማጽዳት ወይም ማርካት ማለት ሲሆን ሪስቶሬቲቭ ጀስቲስ ደግሞ የሚያተኩረው ወንጀለኛውን በመቅጣት ላይ ሳይሆን ተበዳዩን በመካስ ላይ ያተኮረ የፍትህና የእርቅ ማውረጃ ዘዴ ነው። ታዲያ ኣንዳንድ  ሩዋንዳዊያን ሪትሪቢዩቲቭ ጀስቲስ ነው ፈውስ የሚያመጣልን ሲሉ በርግጥ በብዙዎች ዘንድ ተቀባይነት ሳያገኙ ኣልቀሩም። ምክንያቱም ወንጀሉ የተፈጸመው በኣጭር ጊዜ በመሆኑ፣ ወንጀሉ ግድያ በመሆኑ፣ ገዳይና የሟች ቤተሰብ ጎረቤት በመሆናቸው፣ ኣሰቃቂ ወንጀል በመሆኑ ሪትሪቢዮቲቭ ጀስቲስ ተገቢነው እንዲሉ የገፋፋቸው ይመስላል። ይሁን እንጂ በኣንድ መቶ ቀናት ላለቀው ስምንት መቶ ሺህ ህዝብ ገዳዩችና ለገዳዩቹ ተባባሪዎች ፍርድ ለመስጠት ሩዋንዳ ኣቅም ኣልነበራትም። ሩዋንዳ በዚያን ወቅት ላለቁት ስምንት መቶ ሺህ ቱትሲዎችና ለዘብተኞች ወደ ኣንድ መቶ ሺህ ወንጀለኞችን ለፍርድ ኣቅርባ መቅጣት ከፈለገች ኣጠቃላይ የፍርዱ ሂደት ወደ  ኣንድ መቶ ኣመት ይፈጅባት ነበር የሚሉ ወገኖች ኣሉ።  ሪስቶረቲቭ ጀስቲስን ተጠቅማ ችግሯን ለመፍታት ብትሞክር ደግሞ ገዳይና ሟች ጎረቤታም በመሆናቸው፣ የሟች ደም ገና ስላልደረቀ በርግጥ የሃገሪቱ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት ሌላ ችግር ውስጥ መውደቁ ሌላ ኣሳብን ያመጣባት ትመስላለች። ሩዋንዳ የነበረችበት መስቀለኛ መንገድ ኣስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የጣላት በመሆኑ ሁለቱንም የፍትህ ኣሰጣጥ ዘዴዎች ኣደባልቃ እንድትሄድ ሳያስገድዳት ኣልቀረም። በመሆኑም ባህላዊ የጋካካ ፍርድ ቤቶችን በማቋቋም የተወሰነውን ችግር በዚህ በሪትሪቢዩቲቭ ጀስቲስ የተወሰነውን ደግሞ ዝግ እያለ በሚያድግ ዴሞክራሲና በሪስቶሬቲቭ ጀስቲስ ይፈታል እያለች እየደለለች ማርገብ ችላለች። ከሁሉ በላይ ግን ሩዋንዳ ወደ ዘጠና በመቶ የሚሆነው ህዝብ ክርስቲያን በመሆኑና ኣብያተ ክርስቲያናት የሚሰብኩት የይቅርታና የምህረት ትምህርት የሩዋንዳን ችግር በሪስቶሬቲቭ ፍትህ ለመፍታት ከፍተኛ ኣስተዋጾ ሳያደርግ ኣልቀረም። በኣጠቃላይ የሩዋንዳ ችግር ውስብስብና ኣስቸጋሪ በመሆኑ ሁለቱም የፍትህ ኣሰጣጥ ዘዴዎች ተግባር ላይ የዋሉ ይመስላሉ።

ለኣብነት በየሃገሩ የተፈጸመውን ወንጀል እያነሳን የተወያየነው ችግር በየቤቱ ኣለ፣ ይሁን እንጂ ሁሉም ሃገር ችግሩን ለመፍታት ጥረት እያደረገ ነው ኣገር የቆመው ለማለት ነው። ወደኛው ኣገር እንመለስና ብሄራዊ እርቅ በኢትዮጵያ ምን ማለት እንደሆነ እንመልከት።

በኢትዮጵያ ውስጥ ሊኖር የሚችለውን የብሄራዊ እርቅ ይዘት ለማየት መጀመሪያ ስለ ኣለፈው ታሪካዊ ግድፈቶች ማንሳት ተገቢ ነው። ከፍ ሲል እንዳልነው በኣውስትራሊያ ውስጥ ለነበረው ግፍ ሃላፊነት የሚወስድ እውቅና የሚሰጥ ኣካል ተገኝቱዋል። ወደኛ ሃገር ስንመጣ ላለፉት በደሎች እውቅና ለመስጠትም ሆነ ኣንድ ኣካል ለጥፋቱ ሃላፊነት ለመውሰድ የምንችልበት ሁኔታ ጠፍቷል። ይህ የሆነበት ምክንያት ሁሉም የባህል ቡድን በየፊናው ባለፉት ስርዓቶች ተጎድቻለሁ ባይ በመሆኑ ነው።

በኣጼ ምኒልክ ጊዜ የጠፉ ጥፋቶች ካሉ ለነዚያ ጥፋቶች የኣማራውን ህዝብ ሃላፊነት ውሰድና ይቅርታ በል የሚል ኣካል ቢነሳ ኣማራው ለራሱ ተበድያለሁ ባይ ነው። በፊውዳሉ ስርዓት በጭሰኝነት፣ በባርነት መከራየን ኣይቻለሁ:: በወቅቱ የተጠቀሙት ጥቂት ፊውዳሎች ናቸው:: ተውኝ እባካችሁ ይላል። በኣጼ ሃይለስላሴ ዘመንም ቢሆን የወሎ ርሃብ ሲመጣ ሃይለስላሴ ዓለም እንዳይሰማ ኣድርገው በዚያ ደረጃ ጨክነው ኣስጨርሰውኝ የለም ወይ? ደርግ ኣማራ ነው ካላችሁ ደግሞ የጎንደርንና የወሎን ወላድ እምባ ኣታዩም ወይ? ወዘተ. እያለ እያነባ ባለፉት ስርዓቶች የተጎዳውን ይቆጥራል። ኦሮሞው በበኩሉ በዚህኛውም ባለፈውም መንግስት ተነጥየ ተጎዳሁ፣ ባህሌ፣  ማንነቴ ተጎዳ ብሎ እያነባ ይናገራል፣ ትግሬው በበኩሉ ባለፈውም ሆነ ኣሁን የተመቸኝ ነገር የለም፣ የውስጥ ችግሬን እኔ ነኝ የማውቀው ተለይቼ ተበድያለሁ እያለ ያነባል፣ የደቡብ ህዝቡ ተበድያለሁ የኔን መከራ ማን ባየው እያለ እያነባ ይናገራል፣ ሱማሌው የኔ መከራ መቼ ነው የሚያቆመው? መከራየን እያየሁ ነው እያለ ያነባል። ጋምቤላው፣ ኣፋሩ ሁሉም በተናጠልም በቡድንም ተጎድቻለሁ እያለ ያነባል። ታዲያ እንዲህ በሆነባት ኣገር ብሄራዊ እርቅ ምን መልክ ይኖረዋል የሚለው ጥያቄ ላይ ነው መወያየት ያለብን።

በመጀመሪያ ግን እኛ ኢትዮጵያዊያን ያለፉ ታሪካዊ ችግሮች ኣጥንተን መፍትሄ ለመስጠት የታሪክ ተዓማኒነትም ችግር ኣለብን። በተለይ በኣሁነ ወቅት ፖለቲካው ከፋፍሎ የመግዛት ዘዴን የሚጠቀም በመሆኑ ኣንዳንድ በፈጠራ የሚጻፉ ታሪኮች ያለፈውን ታሪካችንን በሚገባ ኣይተን ብሄራዊ እርቅ ለማምጣት እንቅፋት ነው። የሆነ ሆኖ ግን በኢትዮጵያ ውስጥ ላለፈውም ሆነ ኣሁን ላለው ግፍና በደል ኣንድ ቡድን እንደ ቡድን ሃላፊነት ወስዶ ይቅርታ የሚልበት ሁኔታ የለም። በደቡብ ኣፍሪካም ሆነ በኣውስትራሊያ ወይም በሌሎች ኣገሮች እንደተፈጠረው ኣይነት ሃላፊነት ወስዶ የቡድኖችን እንባ የሚያብስ ጠፋ። በመሆኑም የኢትዮጵያ ምሁራን በዚህ ኣስቸጋሪ ወቅት በኢትዮጵያ ውስጥ ብሄራዊ እርቅ ማለት ምን ማለት እንደሆነና ሁላችንን የሚፈውስ ኣሳብ በግድ ኣምጠው ሊወልዱ ይገባል።

በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ነባራዊ ሁኔታ የሚያሳየው ቡድኖች እንደቡድንም በጅምላም ባለፈው ጊዜ ለደረሰባቸው በደል ሁሉ ያለፈውንና ኣሁን ያለውን ስርዓት የታሪክ ተጠያቂ ማድረጉ ኣንዱ የስምምነቱ ኣሳብ ወለል ቢሆን መልካም ነው። ይሁን እንጂ ላለፉት ችግሮቻችን ቡድኖች እንደ ቡድን ተጎዳሁ የሚሉት ካለ ለዚያ ቡድን ጉዳት እውቅና መስጠት ኣንዱ የስምምነቱ ኣካል ሊሆን ይገባል። ኣንድ ቡድን ተጎዳሁ ተጎድቼ ነበር ሲል የለም ያንተ ጉዳት ትንሽ ነው የኔ ይበልጣል ማለቱ ብሄራዊ ፈውስን ኣያመጣም።ሰው ህመሙን የሚያውቀው ራሱ ነው። በመሆኑም ቡድኖች  የተጎዳነው ኣለ ሲሉ ማዳመጥና ሃዘንን መጋራት ለችግር እውቅና መስጠት ነው የኢትዮጵያ ብሄራዊ እርቅ መሰረቱ።  ኦሮሞው ኣጼ ምኒሊክ ጎድተውኛል ካለ ሌላው ብሄር ልክ ኣይደለም ኣልጎዱህም ማለቱ ለብሄራዊ እርቁ ኣይጠቅመንም። ኣንዱ ዜጋ ኣጼ ምኒሊክ  ካጠፉት ጥፋት ይልቅ የሰሩት ጀብዱ በተለይም ኢትዮጵያን ከውጭ ወራሪ ለመመከት ያደረጉት ተጋድሎ ከበለጠበት ቢወዳቸው ቢፎክርላቸው ሌላው ኢትዮጵያዊ መበሳጨትና ጥል ውስጥ መግባት የለበትም። ኣንድ መሪ ለኣንዱ ኢትዮጵያዊ ተወዶ ለሌላው የሚጠላ ቢሆንም ከዚህ ልዩነታችን ጋር ኣብረን መኖር እንችላለን። ኢትዮጵያዊ ለመሆን ሁሉ ሰው ኣጼ ምኒሊክን መውደድ ኣለበት ማለት ኣይደላም።ፕሬዚደንት ኦባማንና ፕሬዚደንት ቡሽን የሚወድም የሚጠላም በሰላም እንደሚኖረው እኛም ከልዩነት ጋር መኖርን መልመድ ያስፈልገናል።

ኣሁን እኛ ጋር ያለው የኮሙኒኬሽን ችግር ይመስላል። የኮሙኒኬሽን ችግሮች ምንጫቸው የእውነት መዛነፍ (distortion of truth) እንዲሁም የማንነት ፖለቲካ ውጤቶች ስለሆኑ ለነዚህ ችግሮች ራስን ሰለባ ኣለማድረግ ነው።በመሆኑም የኢትዮጵያ ብሄራዊ እርቅ ዋናው መሰረት እርስ በርስ መረዳዳት(understanding eachother) ነው ማለት ነው። ያለፈውን ህመማችንን በመደማመጥ ነው ልንፈታው የምንችለው። ችግራችንን ስንገልጥ የለም ያንተ ቁስል ትንሽ ነው የኔ ነው ትልቁና ኣንተ ስለ ብሶትህ ኣታንሳ ኣይባልም። ቢሆን ቢሆን ራስን ከውጭ ወደ ውስጥ ከውስጥ ወደ ውጭ የማየት ልብ ቢኖረን እሱ ነው ያለፈውንና ኣሁን ድረስ የቀጠለውን ችግራችንን የሚፈታው። በኣሁኑ ሰዓት እኔ ኦሮሞ መሆኔ ቀርቶ ትግራይ ሆኘ ብፈጠር ምን ይሰማኝ ነበር? ምን እሆን ነበር? ብሎ ቢያስብ በኣንጻሩ የትግራይ ህዝብ ኦሮሞው ኣማራው ተለይቼ ተጎዳሁ ሲል  በኣሁኑ ሰዓት እኔ ኦሮሞ ሆኘ ተፈጥሬ ቢሆን ምን ይሰማኝ ነበር? የሚል ከፍ ያለ መረዳት (understanding eachother’s pain and understanding each other’s feelings) በተለይ በሌሂቁ በኩል ቢታይ ነው የብሄራዊ እርቁ መሰረቱ የሚጠብቀው። ኣንድ ሰው ጉዳቴ ከፍተኛ ነው ሲል የለም ያንተ ትንሽ ነው የኔ ነው ትልቁ ጉዳት ወደ ማለት ማዘንበላችን የኮሙኒኬሽን ችግር ያመጣብናል። እውነቱን እንነጋግር ከተባለ እኛ ኢትዮጵያዊያን ያለፈውን ችግር  በብሄራዊ ይቅርታ ለመዝጋት የገጠመን ችግር ይሄው የኮሙኒኬሽን ችግር ነው። ያለመደማመጥና ህመምን ለመካፈል መድረክ ማጣት ትልቅ ችግሮች ሆነዋል። ሌላው ደግሞ ቅድም እንዳልኩት ያለፈውን ችግራችንን በብሄራዊ እርቅ ለመፍታት የነበሩትን በደሎች ወደ መድረክ ኣምጥቶ እውነትን ለመግለጥ ኣሁን ያለው መንግስት ታሪክን ስላቆራፈደውና ብርታትንም ሆነ ድካምን ከቡድን ማንነት ጋር እንድናያይዝ የሚገፋ ነገር በመኖሩ በከፍተኛ ሁኔታ እውነትን የማግኘትና የመዋጥ ችግር ይገጥመናል። በተጨማሪም  ኢትዮጵያዊያን ኣዳዲስ በሚወለዱ ታሪኮች ሳንደነብር ከስሜት በላይ ሆነን እርስ በርስ በመረዳዳትና ኣለ ለተባለው ችግር እውቅና በመስጠት ነገሩን ማርገብ ይጠበቅብናል።ከሁሉ በላይ ግን ኢትዮጵያ ያለፈውን ችግር ልታይበት የምትችልበት ኣንድ ሌላ ትልቅ ነገር የዛሬው ይዞታዋ ነው። በፊት የነበሩ ማህበራዊና ፓለቲካዊ እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ኣሁን ድረስ እየተንከባለሉ መጥተው ስለሚገኙ ኣሁን ያለውን በቡድኖች መካከል ያለውን ክፍተት በሪስቶሬቲቭ ፍትህ ልትፈታው ይገባታል።  በትምህርት፣ በፖለቲካ ተሳትፎ በባህልና በቋንቋ ኣካባቢ ያለውን ችግር ኢትዩጵያ ለመፍታት ስምምነት ውስጥ መግባት ኣለባት። ይህ ስምምነት ነው ኣንዱ የብሄራዊ እርቁ ይዘት።  ሪስቶሬቲቭ  ፍትህ ስንል በማህበራዊ ተቋማት ግንባታ ይሁን ከፍ ሲል በገለጽናቸው ሁኔታዎች የተጎዱ ኣካባቢዎችን በኣፌርማቲቭ ኣክሽን ዘዴዎች ለመፍታት ስምምነት ላይ መጀመሪያ መድረስ ኣለብን። ይህ የብሄራዊ እርቁ ሰነድ የሚይዘው ኣንዱ ጉዳይ መሆን ኣለበት።

በመሆኑም ኢትዮጵያ በስምምነቱዋ ወቅት የምታካትታቸው ጉዳዩች በግልጽ መጀመሪያ መቀመጥ ኣለባቸው። ቡድኖች እንደ ቡድን ሁሉም ተበድለዋልና ብሄራዊ እርቁ  ሁሉንም ሊክስ የሚችልና ኮሙኒኬሽንን የሚያዳብር መሆን ኣለበት። በዓለማችን የሚነሱ ጦርነቶች ኣብዛኛዎቹ ማለት ይቻላል ምክንያታዊነት ያላቸው ኣይደሉም ኣብዛኛዎቹ ከኮሙኒኬሽን ችግር ጋር የተያያዙ ናቸው። ኣንዳንዴ ቡድኖች የተጣሉበትን ሁኔታ በውል ሳያውቁት ብዙ ይዋጉና ብዙ ሰው ካለቀ በሁዋላ ይታረቃሉ። የሚገርመው ሲታረቁና ስሜታቸው ሲረጋ የከፈሉት ዋጋ እንዲሁ ሜዳ ላይ ሆኖ የሚያገኙበት ጊዜ ይኖራል። በመሆኑም ብሄራዊ እርቁ በቡድኖች መካከል ያለን ኮሙኒኬሽን ለማስተካከል መላ ሊወልድ ይገባዋል።

ከፍ ሲል እንዳልነው ብሄራዊ እርቅ በኢትዮጵያ የሚኖረው መልክ ሁሉንም በመካስ ላይ ሁሉንም ችግሮች እውቅና በመስጠት ላይ የተመሰረተ መሆን ይኖርበታል። በተለይ ያለፈውን ችግራችንን ለመፍታት ችግሩ ከኮሙኒኬሽንና ከስሜት ሃያልነት ጋር የተያያዘ በመሆኑ በረጋና በሰከነ መንፈስ ዜጎች ያለፈውን ችጋራቸውን በጋራ እውቅና ሰጥተው ሲንከባለል ለመጣው ችግር ደግሞ ኣፈርማቲቭ ኣክሽንስና ሌሎች የርስበርስ የመካካሻ ዘዴ ተጠቅመው  ፈውስን ማውረድ ኣለባቸው። እንዲህ ስናደርግ ብሄራዊ እርቁ ሁለቱን ርምጃዎች የሚራመድ ሲሆን ሌላ ሶስተኛ ጉዳይ ደግሞ በውስጡ ሊያቅፍ ይገባዋል :: ይህ ሌላው የእርቁ ፓኬጅ የሚይዘው ደግሞ ኣዲሲቷን  ኢትዮጵያን እንደገና ለማነጽ እንዴት ኣብረን እንውጣ? እንዴት የጋራ ቤታችንን ኣብረን እናጥብቅ የሚለውን ያካትታል:: በመሰረቱ ይሄ ጉዳይ ቀላልም ከባድም ነው። ቀላል የሆነበት መንገድ በኣብዛኛው ፖለቲከኛና ሌሂቅ ዘንድ ቅንነቱ ካለ መፍትሄው ቀላል ስለሆነ ሲሆን ጠማምነቱ ካለ ደግሞ   ፈተና ነው።

በስምምነት ላይ የተመሰረተ ባህላዊ ውህደት ብሄራዊ እርቅን በኢትዮጵያ የሚያየው እንደዚህ ነው። በዚህ ጽንሰ ሃሳብ መሰረት ብሄራዊ እርቁ ሪስቶሬቲቭ ጀስቲስን መሰረት ያደረገና  በሚያድግ ዴሞክራሲ ችግሮችን ሊፈታ የሚችል ስምምነት ማለት ነው። ይህ ማለት ግን ሪትሪቢዩቲቭ ጀስቲስ ቦታ የለውም ማለት ኣይደለም። በኣሁኑ ሰዓት በከፍተኛ ሙስናና ከፍተኛ ወንጀል እየፈጸሙ ያሉ ሰዎች ይህንን ኣሳባችንን እያዩ እንደ ጅልነት ኣይተው ከስልጣን እስኪወርዱ በግፋቸው እንዲቀጥሉ በር ኣይከፍትም።

የብሄራዊ እርቅ ሰነዱ እንደነዚህ ኣይነት ሰዎችን በቡድን እያየ ሳይሆን በግለሰብ ደረጃ ወደ ፍርድ ሊያመጣቸው መቻሉ ኣያጠያይቅም። እንደ ቡድን እንደ ሃገር ኢኮኖሚያዊ ችግሮቻችንን ዝግ እያለ ሊሰራጭ በሚችል የሪዲስትሪቢዩሽን ዘዴ ተመጣጣኝ እድገት ለማምጣት መስማማት፣ ፖለቲካዊ ተሳትፎን ከባህላዊ ውህደት ስምምነት ኣንጻር ኣይቶ ከብሄር ፖለቲካ ኣውጥቶ በኣንድ ብሄራዊ ማንነት ስር ለመገንባት መስማማት፣ ዋና የሃገሪቱን ቋንቋዎችን ቁጥር  መጨመር ኣጠቃላይ ፈውስን ለማምጣት ይጠቅማል።

ኢትዮጵያ ሪስቶሬቲቭ ጀስቲስ ላይ እንድታተኩር የሚያደርጋት ለዘላቂ ሰላምና ልማት ኣንድነት የሚረዳት ሲሆን ይህ የፍትህ  ኣሰጣጥ ዘዴ በኢትዮጵያ ቡድኖች ዘንድ የተባረከና የሚበረታታ ነው። የኦሮሞ ስርዓትን ብናይ ለሪስቶሬቲቭ ጀስቲስ ትልቅ ቦታ ኣለው። ይቅር ማለትን፣ በዳዩን ከመቅጣት ይልቅ ተበዳዩን መካስን ያበረታታል። ኣማራው ኣካባቢ ያለውን የሽምግልና ስርዓት ስናይ በኣብዛኛው ሪስቶሬቲቭ ጀስቲስ የሚበረታታበት ሁኔታ ኣለ። በደቡብ፣ በምስራቅ በተለይም በሶማሌ ክልል ይህ የፍትህ ስርዓት ከፍተኛ ተጽእኖ ኣለው።

የሃይማኖት ዳራችንም ቢሆን ወደ መቶ ፐርሰንት የሚጠጋው ህዝብ ሃይማኖተኛ በሆነበት ኣገርም ይህ የፍትህ ስርዓት ሊሸከመው የሚችል በተፈጥሮው የተደራጀ ተቋም በመኖሩ ተመራጭ እንዲሆን ያደርገዋል።

ሌላው ከዚህ በተጨማሪ ደግሞ ባለፈው ጊዜ በግድ በሆነ ኣሲምሌሽን ጠፉ የሚባሉ ባህሎች ካሉ እነሱን የማስመለስ (Restoration and revival) ስራ ለመስራት መስማማቱ ነው ኣንዱ የእርቁ ሰንድ የሚይዘው ጉዳይ። የጠፉና በመጥፋት ላይ ያሉ ጠቃሚ ባህሎች ካሉና ቡድኖች የሚቆጩባቸው ከሆነ የማስመለስ ፖሊሲ ኣውጥቶ ቡድኖችን ሁሉ ተባብሮ ለመካስ ኪዳን መግባት። ቡድኖች ኣጣናቸው የሚሉዋቸውን በሙሉ ለማስመለስ ባይቻልም ኣብዛኛውን በመመለስ የቡድኖችን ልብ ማሳረፍ ይቻላል።

ሌላው የብሄራዊ እርቁ ሰነድ ሊይዘው የሚገባው ጉዳይ ለወደፊቱዋ ኢትዮጵያ የሚሆን ኣስተዳደራዊ ባህልን የመገንባት ስምምነት ሲሆን ይህም ዴሞክራሲ ነው። ቡድኖች በመጀመሪያ ዴሞክራሲ ከኣሁን በሁዋላ ያስተዳድረን  መንግስታት ቢቀያየሩም ዴሞክራሲ ግን የጋራ ባህላችን ይሁን የሚል ስምምነት ውስጥ ሊገቡ ይገባል። ይህ ኣስተዳደራዊ ባህል የጋራ የሁላቸው በመሆኑ ወደፊት ለህይወታቸው መሪ ይሆናል ማለት ነው።

ሌላው መሰመር ያለበትና የስምምነቱ ኣንዱ ኣካል ሊሆን የሚገባው ለመልካም ታሪኮቻችንም እውቅና መስጠት ነው። ኢትዮጵያን የመከራ ቤት ብቻ ኣድርጎ ከማየት የኣፍሪካ መቀመጫ ያደረጋትን የነጻነት ታጋይነቱዋን ማስታወስና ለነዚህ ታሪኮቻችን ደግሞ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ኣስተዋጾ በማድረጋቸው እውቅና ሊሰጡት ይገባል። ይህ ኣይነቱ ስሜት ሚዛናዊ የሆነ ስሜትን ከመፍጠሩም በላይ ኣገር ኣለን ስንል የምንመካባቸው ብዙ ኣኩሪ ታሪኮች እንዳሉንም ስለሚያደርግ ነው።

በሌላ በኩል ደግሞ የስምምነታቸን ሰነድ ኣንዱ ሊይዘው የሚገባው ነገር የማትከፋፈል ኢትዮጵያን ለትውልድ ማሳለፍ ነው። መንግስት መጥቶ መንግስት ሲሄድ ቋሚ ዶግማ የሆነ ስምምነት ሆኖ ሊቀመጥ የሚገባው ጉዳይ ነው። የወደፊቷን ኢትዮጵያን እንደገና ማነጽ ማለት ይሄው ነው።

 

ማጠቃለያ

በቅርቡ ከኔልሰን ማንዴላ ሞት ጋር በተያያዘ ዓለም ያሳየችውን ስሜት ስናይ ያስደንቃል።በኔልሰን ማንዴላ ሞት ምክንያት የዛሬይቱ ዓለማችን በሚያስደንቅ መልኩ መነቃነቋ፣ ያ ሁሉ መሪ ወደ ደቡብ ኣፍሪካ መጉረፉ የሚያሳየው የሃያ ኣንደኛዋ ክፍለ ዘመን ዓለም ለብሄራዊ እርቅና ይቅርታ የሰጠችውን ታላቅ ክብርና ቦታ ነው።ኢትዮጵያዊያንም ከዚህ የምንማረው ኣለ:: ኢትዮጵያ ብህዙ በመሆኑዋ ይህ ተፈጥሮዋ በስምምነት ላይ የተመሰረተች  ኣገር እንድትሆን ያስገድዳታል:: በመሆኑም በስምምነት ላይ የተመሰረተ ባህላዊ ውህደት ያስፈልገናል የምንለው ኣንዱ መነሻ ይሄ ነው። እንዴት ወደ ስምምነት እንገባለን? በምን መንገድ ነው ወደዚያ መስመር የምንገባው? ተግባራዊ ሂደቱ ምንድነው? ካልን ኣንዱ መንገድ ብሄራዊ እርቅ ማምጣት ነው። ከፍ ሲል እንዳልነው ብሄራዊ እርቅ ማለት በኢትዮጵያ ኣንዱ በዳይ ሌላው ካሳ የሚሰጥ ሳይሆን ርስበርስ የሚረዳዱበትና ሁሉም የሚካሱበት የእርቅ ኣሳብ ነው። በዋናነት ብሄራዊ እርቁ ያለፈውን ችግር መፍታት ኣሁን የዘለቀውን ችግር ማቆም ሆኖ ከሁሉ በላይ ግን ኢትዮጵያን እንደገና ለማነጽ የስምምነት ነጥቦችን ኣውጥቶ በነዚያ ስምምነቶች ዙሪያ መስማማት ነው። እነዚህ የስምምነት ኣጀንዳዎች የሃገሪቱ ዶግማዎች ይሆኑና ዘላለማዊ ኪዳን ይሆናሉ። ይህ ኪዳን ከህገ መንግስቷም በላይ ሆኖ የሚኖር ይሆናል።። ህገ መንግስት የሚያረቁ መንግስታትም ከነዚህ ዶግማዎች ኣንጻር ህጎችን ሊያወጡ ይገባል። ይህ የእርቅ ሰነድ በሃይማኖት መሪዎች፣ በባህል መሪዎች በፖለቲካ ፓርቲዎችና በሲቪክ ማህበራት ዘንድ ሁሉ የሚቀመጥ የሚከበር ትልቅ ኪዳን መሆን ኣለበት።ኢትዮጵያ በእንደዚህ ኣይነት ለየት ባለ ቅርጽ ብትተዳደርስ? ከህገ-መንግስቷም በላይ ሌላ ዶግማ የሆነ ኣዲስ ኪዳን ቢኖራት ጥሩ ኣይሆንም ?

መቼም ይሄ ተግባር የናፈቀው ህሊናችን ጥያቄ ማንሳቱ ኣይቀርም። ይህ ብሄራዊ እርቅ የሚባለው ነገር መቼ ነው መካሄድ ያለበት? ተዋንያኑስ እነማን ይሆናሉ? የሚል ተግባራዊ ጉዳዮች ይመጣሉ። በኢትዮጵያ ብሄራዊ እርቅ ማለት የተጣሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች መታረቅ፣ ወይም ውህደት ማድረግ ማለት ኣይደለም። በርግጥ የነዚህ ፓርቲዎች ውህደትና ስምምነት ለብሄራዊ እርቁ ከፍተኛ ኣስተዋጾ ኣለው። ኣሁን የምናወራውን ሰፊ ኪዳን ለመፈጸም ነው። ዓለምን የሚያስደምም ስምምነት ተስማምተን ኢትዮጵያን እንደገና ልናቆም ነው። ተዋንያን የሚሆኑት የተለያዩ ፓርቲዎች፣ የሃይማኖት ቡድኖች፣ ሲቪክ ማህበራት፣ ባህላዊ ቡድኖች ዜጎች ሁሉ ናቸው። ከኣለማቀፉ ማህበረሰብም ታዛቢ ኣስገብታ ይህንን ስምምነቱዋን ለኣለም ማሳየት ኣለባት። ከዚያ በሁዋላ ኢትዮጵያ ታላቅ ድግስ ደግሳ ያን የተስማማችበትን ቀን ዘወትር የምታከብረው የኢትዮጵያ ዳግም ምስረታ (Foundation day) ቀን ብላ ያን ቀን ዘወትር በየዓመቱ ታከብረዋለች።ይሄ መሆን የሚችል ነው።

ኢትዮጵያ ይህን የእርቅ ኪዳን የምትገባው ኣሁን ያለው መንግስት ወደ እርቅ ከመጣ ብቻ ኣይደለም። ይህ መንግስት ለዚህ እርቅ ሁኔታዎችን ቢያመቻችና ኣብሮ ቢሳተፍ ታሪክ ያመሰግነዋል። ነገር ግን በነውጥም ሆነ በጠመንጃ ይህ መንግስት ከወደቀ በሁዋላም ኢትዮጵያ የግድ ወደዚህ ኪዳን ውስጥ መግባት ስላለባት ከወዲሁ መዘጋጀት ያስፈልጋል። ባለፈው ታሪካችን የጠፋው ይሄ ነው። ለውጦች ሲመጡ ብሄራዊ እርቅ ሳይደረግ ኣሸናፊው ተሽናፊውን እየረገመ የተሻልኩ ነኝ እያለ ስለመጣን ብሄራዊ ችግሮቻችን እየባሱ መጥተዋል። ኣሁን ግን በየትኛውም ሁኔታ ቢሆን ኢትዮጵያ በዚህ የእርቅ ኣሳብ ውስጥ ማለፍ ኣለባት። ይሄ የግድ ነው።የብሄራዊ እርቁን የሚመራውና የእርቅ ኣሳቦችን የሚያመጣውን ኮሚሽን ኣገር ወዳድ የሆኑ የፖለቲካ ፓርቲዎችና ሲቪክ ማህበራት ሚዲያዎችና ኮሚኒቲዎች ከፊታቸው ያለውን የልዩነት ተራራ በጎን በኩል ዞረው ኣልፈው ይህን ሰነድ የሚያዘጋጁና መላ የሚፈጥሩ ኣካላትን ሊፈጥሩ ይገባል።ይሄ ሰው የሚሰራው ኢትዮጵያዊያን ልንሸከመው የምችለው ሃላፊነት ነው። ኣሁን ባለው የፖለቲካ ኣሰላለፍ ኢትዮጵያ የጎደላት ይሄ ነው። ኣልፎ ኣልፎ የተለያዩ ፓርቲዎችን ኣገናኝቶ በማነጋገር የእርቅ ኣሳብን ለማዳበር የሚሰራ የለም ማለት ይቻላል። ከዚህም በተጨማሪ በየጊዜው የሚመጡ ለችግራችን የሚሆኑ የመፍትሄ  ኣሳቦችን የሚያጠናና የሚያደራጅ ባለመኖሩ ወርቅ የሆኑ ኣሳቦች ሁሉ ባከኑ። ለዚህም ኣንድ ጠርናፊ እውነትን የሚያፈላልግ የእርቅ ኣሳቦችን የሚያዳብር ተቋም ያስፈልገናልና በዚህ ላይ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ትኩረት ሰጥቶ መላ ሊለው መስሎኝ ነው።

እግዚኣብሄር ኢትዮጵያን ይባርክ!

ቸር እንሰንብት

geletawzeleke@gmail.com


ወደ ሃገር ለመሄድ እጃቸውን የሰጡ ኢትዮጵያውያን በሳዑዲ ዛሬም የብሶት ድምጻቸውን ያሰማሉ (የድምጽ ዘገባ)

$
0
0

(ፎቶ ፋይል)

(ፎቶ ፋይል)


ነቢዩ ሲራክ
ሁለተኛ ወር የያዘውን የሪያድ መንፉሃን ሁከት የኢትዮጵያውያንን መሞትና መቁሰል ብሎም መፈናቀል ተከትሎ የሳውዲ ሪያድ የኢንባሲና የጅዳ ቆንስል መስሪያ ቤት በባህር በሃጅና ኦምራ የመጡትን ጨምሮ ከአሰሪዎቻቸው ጋር የማይሰሩ ዜጎች በሳውዲ ህግ መሰረት ህገ ወጥ ናቸውና ወደ ሃገራቸው እንዲገቡ ተደጋጋሚ ማስታወቂያና ምክር ማስተላለፉ ይታወሳል። ይህንን ማስታወቂያ ተከትሎ ከ150 ሽህ በላይ ዜጎች ወደ ሃገር የገቡ ሲሆን ወደ ሃገር ለመግባት አቅማምተው የነበሩት ፍተሻው ጥንከር እያለ ሲመጣ ወደ ሃገር ለመግባት እጃቸውን በመስጠት ላይ ናቸው። ወደ ሃገር እንግባ ብለው በተደረገው ጥሪ እጃቸውን የሰጡት መኖሪያና የስራ ፈቃድ የነበራቸው ዜጎች ግን እዚህ በጅዳ ሽሜሲና በሪያድ እስር ቤቶች በደልና እንግልት እየደረሰብን ነው ሲሉ ምሬታቸውን ገልጸውልኛል።
በደል ብሶታቸውን አዘገጃጅቸዋለሁ ፣ በዛሬ የጀርመን ራዲዮ ዜና መጽሔት ይከታተሉ። ( የዜና መጽሔቱ 13ኛ ደቂቃ ላይ ይገኛል)
ሰላም

[jwplayer mediaid="11496"]

የመቀለ ወጣቶች ከህወሓት መሪዎች ጋር ተጋጩ

$
0
0
የመቀሌ ከተማ (ፎቶ ፋይል)

የመቀሌ ከተማ (ፎቶ ፋይል)

አብርሃ ደስታ በፌስቡክ ገጹ እንደዘገበው፦

ዛሬ ሐሙስ ታህሳስ 24, 2006 ዓም በኮብልስቶን ስራ የተሰማሩ (ና ለመሰማራት በማህበራት የተደራጁ) የመቀለ ወጣቶች በመቀለ ከተማ ማዘጋጃቤት አዳራሽ ተሰብስበው ነበር። የተሰበሰቡበት ምክንያት በጨረታ የተወዳደሩበት የኮብልስቶን ግንባታ መሰረዙ ሊነገራቸው ተብሎ ነበር።

ባለፈው ዓመት በኮብልስቶን ስራ የተሰማሩ ወጣቶች አብዛኞቹ መክሰራቸው ይታወሳል። የከሰሩበት ምክንያት ደግሞ ለኮብልስቶን ስራ ተብሎ ከዓለም ባንክ የተከኘ ገንዘብ በሐላፊዎች አለ አግባብ መመዝበሩ ነበር። የኮብልስቶን ገንዘብ የሰረቁ ባለስልጣናት መታሰራቸው ይታወሳል።

አሁን በወጣው ጨረታ መሰረት ግን ለስርቅ የሚሆን የሚተርፍ የኮብልስቶን ገንዘብ አይኖርም። በዚህ ምክንያት የህወሓት መሪዎች ጨረታው ለመሰረዝና ሌላ አዲስ ጨረታ ለመክፈት ወስነዋል። ወጣቶቹም የህወሓት መሪዎች የወሰዱት እርምጃ ክፉኛ ተቃውሞውታል። ወጣቶቹ ለጠየቁት ጥያቄ ተገቢ መልስ ባለመግኘታቸው ስብሰባው ረግጠው ወጥተዋል። የአደራሹ በር በመዝጋት ስብሰባው ረግጠው እንዳይወጡ ጥረት የተደረገ ቢሆንም አልተሳካም።

ወጣቶቹ ነገ ጠዋት (ዓርብ) ወደ ክልል ቢሮ ተሰባስበው ይሄዳሉ። የክልል መንግስት መፍትሔ ካልሰጣቸው የተቃውሞ ሰልፍ እስከማድረግ ይደርሳሉ።

ይህ የኮብልስቶን ጉዳይ ባብዛኞቹ የትግራይ ክልል ከተሞች ትልቅ አጀንዳ ሁኗል።

(ኮብልስቶንም … ንትርክ በዛባት)

ያለፉት ስህተቶች ትምህርት እንጂ ማነቆ አይሁኑ –ግርማ ካሳ

$
0
0

ግርማ ካሳ  

እንደ ፈረንጆች አቆጣጠር፣  ኖቬምበር 17 ቀን 1996 ነበር። በሰርቢያ (የቀድሞ ዩጎስላቪያ) ፣  የክልል ምርጫ ይደረጋል።  በቩክ ድራስኮቪች የሚመራዉ SPO ፣ በቬስና ፔሲች የሚመራዉ GSS እና ሌሎች ድርጅቶች በአንድ ላይ ሆነው አብላጫ ድምጽ ያገኛሉ። ነገር ግን  በወቅቱ የነበሩ አምባገነን ባለስልጣናት፣ እነ ስሎቦዳን ሚሎሶቪች አጭበረበሩ።  ከኖቬምበር 17 1996 እስከ ፌቡሩያሪ 11 1997 ድረስ፣ «ያጄድኖ» የሚል፣  ሕዝባዊ ተቃዉሞዎች በስፋት ተደረጉ። ባለስልጣናቱ፣  የሕዝቡ ሰላማዊ ተቃዉሞ አይሎ መምጣቱን ሲያዩ አፈገፈጉ። የተቃዋሚዎች ስብስብ በክልል ምርጫዉ ያገኙትን ምርጫ፣ ተቀበሉ። ሊበራል ዴሞክራቱ ዞራን ጂንጂች የአገሪቷ መዲና የቤል ግሬድ ከንቲባ ሆኑ።

 

ብዙም አልቆየም፣ በተቃዋሚዎች መካከል ችግር መታየት ጀመረ። በቩክ ድራስኮቪች የሚመራዉ ፓርቲና  በዞራን ጂንጂች በሚመራዉ ፓርቲ መካከል ልዩነቶች ተፈጠሩ። መካረር መጣ። የሕዝብን ጥያቄ አንግቦ በጋራ መቆም ተሳናቸው። በአደባባይ መወጋገዝ ጀመሩ። በአመቱ አገራዊ የፕሬዘዳንት ምርጫ ሲደረግ የሚሎሶቪች የሶሻሊስት ፓርቲ በቀላሉ ስልጣኑን ጨበጠ። የተለፋበት፣ የተደከመበት ሕዝባዊ እንቅስቃሴ ከሸፈ። አምባገነኖች አሸነፉ። በሕዝብ ትግል የተገኙ ዉጤት እንደገና ተቀለበሱ። ዞራን ጂንጂችም ከናካቴዉ ከተመረጡበት የቤልግሬድ ከንቲባነት ተነሱ።

 

በ1998 በየክልሉ ተማሪዎች «ኦትፖር» ( በሰርቢያን ቋንቋ እምቢተኝነት) በሚል ስም ከታች ወደ ላይ የሆነ እንቅስቃሴ ጀመሩ። የተከፋፈሉ የፖለቲካ ደርጅቶች በአንድ ላይ እንደገና ተሰባሰቡ። ካለፉት ስህተቶች በመማር፣ ፍጹም ሰላማዊና ሕጋዊ በሆነ መንገድ ለሚቀጥለው ምርጫ መዘጋጀት ጀመሩ። ከፍተኛ ጫና እየተደረገም ዝግጅቱ ተጧጧፈ። የገዥዉ ፓርቲ ደጋፊዎችን የመሳብ ሥራ በስፋት ተሰራ። በዚህም ምክንያት በርካታ የገዢዉ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ተቃዋሚዎችን መቀላቀል ጀመሩ። ኢቫን ስታምቦሊች ፣ የሚሎሶቪች አጋር የነበሩ ፖለቲከኛ ፣ ተቃዋሚዎች በመቀላቀላቸውም በሚሎሶቪሽ የደህንነት ሰራተኞች ታፍነው ተገደሉ።

 

ሴፕቴምበር 2000 ዓ.ም ምርጫ ተደረገ። የሚሎሶቪች ምርጫ ቦርድ፣ አሁንም የተጭበረበረ የምርጫ ዉጤት ይፋ አደረገ።  ያንን አስከትሎ  ኦክቶቦር  2000 ዓ.ም ፣ ትልቅ ተቃውሞ ሰልፍ ተደረገ። ምርጫ ቦርድ የምርጫዉን ዉጤት ወደ ነበረበት እንዲመልስ ተገደደ። የተቃዋሚዎች እጩ የሆኑት  ኮስቶኒሳ እንዳሸነፉ ተገለጸ። የሚሎሶቪች ስልጣን ፍጻሜ ሆነ። የሰርቢያ ሕዝብ የማይቀለበስ ድል ተቀዳጀ።

 

ይሄንን ያለ ምክንያት አይደለም ያመጣሁት። በሰርቢያ፣ በመጀመሪያዉ ምርጫ  የተከሰተው፣ በኢትዮጵያም በምርጫ ዘጠና ሰባት ከተከሰተው ብዙ የሚለይ አይደለም። ያኔ በቅንጅት ጊዜ የሕዝብ ጉልበት አያሎ የወጣበት ወቅት ነበር። ነገር ግን በተቃዋሚዎች መካከል በተፈጠሩ ልዩነቶች፣ በቀላሉ ሕወሃት/ኢሕአዴግ ስልጣን ላይ ለመቆየት ቻለ። (በገዢው ፓርቲ የደረሰው ወከባ፣ ግድያ፣ እሥር፣ እንግልትን ጫና ቢኖርም፣ በዋናነት የተቃዋሚዎች ችግር ነው አገዛዙን ያቆየው ብዬ ነዉ የማምነው)

 

ሰርቦች ጠመንጃ አላነሱም። ሰርቦች ለዉጥ ማምጣት አይቻልም ብለው አላወጁም። ሰርቦች ተስፋ አልቆረጡም። እኛ ኢትዮጵያዉያን ግን ተስፋ ቆረጥን። ፎጣችንን መሬት ላይ ጥለን፣ አምባገነንነትን አሜን ብሎ የመቀበል አዝማሚያ አሳየን። «ተቃዋሚዎች አይረቡም። ያኔ ደግፈናቸው ጉድ አላደረጉንም እንዴ ? አርፎ መቀመጥ ይሻላል፣ ሰላማዊ ትግል አይሰራም ….» የሚሉ ጨለምተኛና የሽንፈት አባባሎችን ማሰማት ጀመርን።

 

የገዢዉ ፓርቲ ሰዎችም፣ ስልጣን ላይ ለመቆት የሚያስችላቸው፣  ይሄዉ የተቃዋሚዎች መከፋፈልና የሕዝቡም ተስፋ መቁረጥ ስለነበረ፣  በሚቆጣጠሯቸው ሜዲያዎች፣ ሕዝቡ በተቃዋሚዎች ላይ የበለጠ ተስፋ እንዲቆርጥ፣ ከፍተኛና ሲስቴማቲክ፣  ተቃዋሚዎች የማጥላላትን የማሳነስ ዘመቻቸዉን አፋፋሙ። ጠንካራ የሚሏቸውን የተቃዋሚ መሪዎችና ጋዜጠኞች ያለ ርህራሄ አሰሩ። ብርቱካን ሚደቅሳን አሰቃይተውና ሰባብረው (ለስድስት ወራት ሁለት ሜትር በሁለት ሜትር ጨለማ ቤት ዉስጥ እንዳስቀመጧት) ለስደት ዳረጓት። «እነርሱን ያየህ ተቀጣ» በሚል፣  በአንዱዋለም አራጌ፣ በእስክንደር ነጋ፣ በርዪት አለሙ፣ በዉብሸት ታዬ፣ በበቀለ ገርባ እንዲሁም በሌሎች ..ሰላማዊ ወገኖቻችን ላይ፣ በተራ የዉሸት ሽብር ክስ፣  ኢፍትሃዊነትና ኢሰብአዊነት የተሞላበት ግፍ መፈጸማቸዉን ቀጠሉ። በሕዝቡ  አይምሮ ዉስጥ፣ እነርሱን ማንም ሊነካቸው የማይችሉ፣  ግዙፎች (ኢንቪሲብል) እንደሆኑ ለመሳል መሞከርና፣ ሕዝቡ እርስ በርስ ተፈራርቶ እንዳይደራጅ፣ እንዳይነጋገር፣ እንዳይተማመን፣ በዘር፣ በኃይማኖት በጥቅም እንዲከፋፈል፣  ማድረጉን ተያያዙት።

 

ነገር ግን ኢትዮጵያዉያን መንቃት ያለብን ይመስለኛል። ከሰርቦች መማር ያለብን ይመስለኛል። አምባገነኖች ኃይለኛ የሆኑ ይመስላሉ እንጂ ሁልጊዜ ባዶ መሆናቸዉን መረዳት አለብን። ሕወሃት/ኢሕአዴግ የሕዝብ ድጋፍ የሌለው፣ በሙስና የተዘፈቀ፣ ለሕዝብና ለዜጎች ከበሬታ የማያሳይ፣ ዜጎችን ሽብርተኞች እያለ የሚያሸብር፣ የበሰበሰ ድርጅት እንደሆነ በግልጽ እየታየ ነዉ።

 

እንግዲህ «ትላንት ወድቀናል ብለን፣ የትናንቱ ጠባሳችንን እያየን ወደፊት ከመራመድ መቆጠብ የለብንም» እላለሁ። ከስህተቶቻችን ተምረን፣ ያለፈው ታሪካችን በአይምሯችን እየፈጠረ ካለው ጎታች ጫና ተላቀን፣ ይሄንን ዘረኛና አምባገነን ስርዓት ለመቀየር በቁርጠኝነት መነሳት የግድ ነዉ። ቁልፉ በእጃችን ነዉ። በርግጥ ለዉጥ ማምጣት እንችላለን። ጥያቄው «ፍላጎቱ አለን ወይ?» የሚል ነዉ።

 

እያንዳንዳች ወደ ራሳችን እንመልከት። እራሳችንን እንጠይቅ። «እስከመቼ ነዉ፣  በአገራችን እንደ ባይተዋር ፈርተን እና አንገታችንን ደፍተን የምንቀመጠው ?» ማለት እንጀመር። በየወረዳችን፣ በየአካባቢያችን፣  ሰላማዊ የፖለቲካ እንቅስቃሴ የሚያደርጉ ድርጅቶችን እንቀላቀል። የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ፣ ጠንካራና አገር ሰፊ የኢትዮጵያዊትነትና የሰለጠነ ፖለቲካ የሚያራምድ ድርጅት ነዉ። በመቀሌ፣ አርባ ምንጭ፣ ጂንካ፣ አዳማ ፣ አሶሶ …በአገርቷ ክፍሎች ሁሉ ብትሄዱ አንድነት በዚያ አለ። አንድነትን እንቀላቀል። አንድነትን እንደግፍ። የሰማያዊ ፓርቲ ፣ መኢአድ፣ ኤዴፓ፣ አረና ..ሁሉም በፊናቸው የሕዝብን ጥያቄ እያሰተጋቡ ነው። እንቀላቀላቸው። እንደግፋቸው። ልዩነቶቻቸውንም አጣበው ፣ የበለጠ ኃይልና ጉልበት ኖሯቸው ሰላማዊ፣ የኢትዮጵያዊነት የሰለጠነን የፖለቲካ ትግል ይመሩ  ዘንድ፣ እንዲሰባሰቡ፣ እንዲዋሃዱ እናበረታታቸው።

 

ፈረንጆች ኒው ዪር ሬዞሉሽን (የአዲስ አመት ዉሳኔ) ይሉታል። እንግዲህ፣ በዚህ የ2014 አዲስ አመት፣ የሁላችንም ምኞት፣ ጥረትና ዉሳኔ፣  በአገራችን መልካም ለዉጥ እንዲመጣ፣ የድርሻችንን በሃሳብ፣ በገንዘብ፣ በጸሎት ለማገዝ ይሁን። የሌሎች ሕመምና ስቃይ ይሰማን። ዝምታን በቃ እንበል። እግዚአብሄር አምላክም ረድኤቱን ያብዛልን!

 

comment pic

የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ልዩ ጉባኤው የአቋም መግለጫ

$
0
0

UDJዛሬ በደረስንበት 21ኛው ክፍለዘመን በአለማችን የሚገኘው ሕዝብ ሰብአዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶቹ በተከበሩበት ሁኔታ መመራት ይሻል፡፡ በዚህ ዘመን አምባገነን መሪዎችና መንግስታት በየትኛውም መስፈርት ስልጣን ላይ የመቆየት እድል የላቸውም፡፡ በዚህ ረገድ በቅርብ አመታት ውስጥ የማይደፈሩና እንደ ፈርኦን ይመለኩ የነበሩ አምባገነን መንግስታት በህዝባዊ ማዕበል ተጥለቅልቀውና ተንጠው መቀመቅ ሲወርዱ የአለም ህዝብ ሁሉ አስተውሏል፡፡ በአሁኑ ወቅት የዲሞክራሲና የነፃነት ጥየቄ ከዳቦ ጥያቄ ይበልጥ አንገብጋቢ እየሆነ መጥቷል፡፡

የአለማችን አንድ አካል የሆነችው አገራችን ኢትዮጵያ የዘመናት የስልጣኔ ጉዞዋ የምድራችን ቁንጮ የታሪክ ባለቤት ያደርጋታል፡፡ በየዘመናቱ የተነሱ ገዢዎቻችን ሲጭኑብን የቆዩት የአገዛዝ ቀንበር ወገባችንን ቢያጎብጠውም የኢትዮጵያ አንድነትና ሉኣላዊነት ፍፁም ሳይሸራረፍ ተጠብቆ ዘመን እንዲሻገርና ለትውልድ እንዲተላለፍ የማይሻ ኢትዮጵያዊ የለም፡፡

ወታደራዊው ደርግ ከሥልጣን በተወገደ ማግስት ዲሞክራሲና ነፃነት የሰፈነበት የዜጎች ሰብአዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶች የሚከበሩባትን ኢትዮጵያ ለማየት ያልጓጓ ኢትዮጵያዊ አልነበረም፡፡ ህልማችን በእውነት ሳይፈታ ቀረ፣ ተስፋ ያደረግነው ነገር ከዓመት ዓመት እየጨለመ መጣ፡፡ ኢህአዴግ ባለፉት 23 ዓመታት የምኒሊክን ቤተመንግስት ቢቆጣጠርም የአገርን ህልውና ከመጠበቅና የህዝብ እንባን ከማበስ ይልቅ ዜጎችን መውጪያ መግቢያእያሳጣና የመከራን ገፈት እያስጨለጠ ጉዞውን ቀጥሏል፡፡ ስደቱ፣ እንግልቱ፣ ግርፋቱ፣ እስራቱ፣ ግድያው፣ አፈናው፣ ስቃዩ ከመቀነስ ይልቅ በየጊዜው እየከፋ ይገኛል፡፡

አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ይህን ቀንበር ለመስበር እንደ መርፌ ቀዳዳ በጠበበው የፖለቲካ ምህዳር ውስጥ እየተንቀሳቀሰ በመላው አገሪቱ ህዝብን ለትግል እያሰለፈ ይገኛል፡፡
ይህን እልህ አስጨራሽ ትግል ለመምራት ትልቁ የስልጣን አካል የሆነው ይህ ጠቅላላ ጉባኤ ታህሳስ 19 እና 20 / 2006 ዓ.ም ለሁለት ተከታታይ ቀናት ባደረገው ከፍተኛ ስብሰባ አያሌ አገራዊ ጉዳዮችን በማንሳት ተወያይቷል፡፡ የፓርቲውን ምክር ቤት ፣ የሥራ አስፈፃሚና የኦዲት ኮሚሽንን ሪፖርት በማድመጥ ጠንካራ ውይይት አካሂዷል፡፡

በመጨረሻም የአገልግሎት ዘመናቸውን ባጠናቀቁት የፓርቲው ፕሬዚደንት የተከበሩ ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ምትክ የተከበሩ ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራውን ፍፁም ግልፅና ዲሞክራሲያዊ በሆነ ምርጫ ተክቷል፡፡ የፓርቲውን ብሔራዊ ምክር ቤት እና የኦዲት ኮሚሽን አባላትንም በመምረጥ ጉባኤው ተጠናቋል፡፡

አባላቱ በጉባኤው ማጠናቀቂያ የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ የሚከተለውን የአቋም መግለጫና ውሳኔ በማሳለፍ ተጠናቋል፡፡

1ኛ. ገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ በአገሪቱ የሚደረገውን የሰላማዊ ትግል እንቅስቃሴ ሙሉ ለሙሉ ለማኮላሸት ነጋ ጠባ የሚያጠነጠነው እኩይ ሴራ የህዝቡን ስሜት ወደ ሌላ አቅጣጫ እና ጥግ እየገፋው ይገኛል፡፡ ይሁን እንጂ ፓርቲያችን አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ በጀመረው የሰላማዊ ትግል ጉዞ የኢትዮጵያን ህዝብ የስልጣን ባለመብት ለማድረግ እስከመጨረሻው እንጥፍጣፊ በጥብቅ መታገል እንደሚኖርበት ይታመናል፡፡ በመሆኑም እኛ ከመላው አገሪቱ በዚህ ጉባኤ ላይ የታደምን የፓርቲ አባላትና አመራሮች ከመቼውም ጊዜ በላቀ መልኩ ለሰላማዊ ትግሉ ቁርጠኛ መሆናችንን እናረጋግጣለን፡፡
2ኛ. አምባገነኑ የኢህአዴግ መንግስት የፓርቲያችንን እንቅስቃሴዎች እግር በእግር እየተከታተለና በሀሰት ውንጀላ በማጠልሸት በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት እንዳናገኝ ጠቅልሎ በያዘው የቴሌቪዥን ጣቢያ ሰፊ የሆነ አፍራሽ ተልዕኮን እያስተጋባ ይገኛል፡፡ይህ ጉዳይ ህገ መንግስቱ ለመድብለ ፓርቲ ሥርዓት ግንባታ ያመቻቸውን መንገድ ሙሉ ለሙሉ የሚጠቅም ነው፡፡ ከዚህ አንፃር አገር እየመራሁኝ ነው የሚለው ኢህአዴግ ፓርቲያችንን ከሽብር ድርጊት ከአሸባሪዎች ጋር ለማቆራኘት የሚያደርገውን እኩይ ሴራ አጥብቀን እናወግዛለን፡፡

3ኛ. በዚህ ልዩ ጉባኤ ወቅት በአካል በመቅረብ በገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ ካድሬዎችና ታጣቂዎች በሰሜን ጎንደር ዳባት ወረዳ አርቡር ቀበሌ ነዋሪ የሆነችው የ 8 ዓመቷ ህፃን ስለእናት ማስረሻ ጥላሁን የደረሰባትን እጅግ ዘግናኝና ሰቅጣጭ የአካል ጉዳትአሳይታለች፣ ሁኔታው የጉባኤውን አባላት ክፉኛ ያስቆጣ ሆኗል፡፡ አባቷን እና የቤት እንስሳትን በጥይት ገድለው ህፃን ስለእናትን በጥይት አረር እጇን የቆረጡ እኝህ እኩያን ወንጀለኞች በአስቸኳይ ለፍርድ እንዲቀርቡ እንጠይቃለን፡፡
4ኛ. የገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ የአመራር ዘመን አገራችን ኢትዮጵያ በታሪኳ እጅግ የተዋረደችበትና ሉኣላዊነቷ የተደፈረበት ወቅት መሆኑ ይታወቃል፡፡ ዜጎች የከፋ የሰብአዊ መብት ጥሰት ይደርስባቸዋል፣ይታሰራሉ፣ ይደበደባሉ፣ ይገደላሉ፣ ይሰደዳሉ ወዘተርፈ፡፡
ለስደት በተዳረጉባቸው አገራትም ዜጎቻችን በግፍ ሲገደሉና ሲደበደቡ እያን ነው፡፡ በቅርቡ በሳውዲ አረቢያና ሰሞኑን ደግሞ በደቡብ ሱዳን ኢትዮጵያዊያን ላይ የደረሰው ሞትና ስቃይ የእያንዳንዳችንን ልብ የሰበረ ጉዳይ ነው፡፡ ለዚህም ተጠያቂው ኢህአዴግ ነው፡፡
በመሆኑም ገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ በመላው ዓለም እንደ ወንዝ ዳር አሸዋ ተበትነው ለሚንገላቱ ዜጎች ጉዳይ በአፅንኦት እየተከታተለ እንዲታደግና የመንግስትነት ግዴታውን ባግባቡ እንዲወጣ አጥብቀን እንጠይቃለን፡፡
5ኛ. በአሁኑ ወቅት የገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ ጥቂት ሹማምንት እጆቻቸውን እያስረዘሙ የአገርን ሀብት እየዘረፉ ናቸው፣ ሥርዓቱ ሙሉ ለሙሉ በሚባል መልኩ በሙስና የተጨማለቀ መሆኑን እየተጋለጠ ነው፡፡ ዜጎች ዛሬ የዕለት ጉርሳቸውን አጥተው ሲራቡና ሲጠሙ፣ወጣቶች የሥራ ዕድል ተነፍጓቸው በአሳፋሪ ሁኔታ ከአገር ሲሰደዱ፣ የኑሮ ውድነቱ ትውልዱን ግራ እያጋባ ነው፣ ህዝቡ ፍትህና መልካም አስተዳደር በማጣት ነጋ ጠባ የዜግነቱ ጉዳይ ጥያቄ በፈጠረበት ሁኔታ የነገዋን ኃያልና የበለፀገች ኢትዮጵያን አይደለም ማየት ይቅርና የህልውናዋ ጉዳይም አጣብቂኝ ውስጥ የገባበት ሰዓት ላይ ደርሰናል፡፡ በአገሪቱም አስከፊ ብሔራዊ ቀውስ ይፈጠራል ብለን እንሰጋለን፡፡
ከዚህ አንፃር ገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ በአጭር ጊዜ ውስጥ ብሔራዊ መግባባትን የሚያሰፍን መድረክ እንዲያዘጋጅ አበክረን እንጠይቃለን፡፡
6ኛ. ኢቴቪ የኢትዮጵያ ሕዝብ ልሳንነቱን እርግፍ አድርጎ በመተው የገዢው ፓርቲ አገልጋይ መሆኑን የትኛውም ኢትዮጵዊ የሚያውቀው ጉዳይ ነው፡፡ አንድነት ፓርቲ የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት ፕሮግራም ላይ በመላው አገሪቱ ሰላማዊ ሰልፍ እና ስብሰባዎችን በጠራበት ወቅት ኢቴቪ ጅሃዳዊ ሃረካት ፊልምን አቀናብሮ ፓርቲያችንን ከአሸባሪዎች ተርታ ሲፈርጀው ቆይቷል፡፡ ሌላው ቀርቶ ጉባኤያችንን ባከናወንበት ታህሳስ 19 ምሽት ኢቴቪ ያንኑ ፊልም በድጋሚ በማቅረብ አንድነት ፓርቲ በደሴ፣ በጎንደር፣ በአርባምንጭ፣ በጂንካ፣ በባህርዳር ወዘተ ካደረጋቸው ሰላማዊ ሰልፎችና በፓርላማ የፓርቲያችን ብቸኛው ተወካይ ስለ ፀረ ሽብር ህጉ አፋኝነት ያነሱትን ሀሳብ ከሽብር ጋር በማያያዝ ከንቱ ዲስኩር ሲያቀርብ ተመልክተናል፡፡ ኢቴቪ የአንድ ድርጅት መሆኑ አብቅቶ የኢትዮጵያን ሕዝብ ዋይታና ብሶት የሚያስተጋባ ግዙፍ የብዙሃን መገናኛ ድርጅት እንዲሆን አጥብቀን እንጠይቃለን፡፡
7ኛ. ፓርቲያችን አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ከተመሠረተበት ዕለት ጀምሮ ከኢህአዴግ አምባገነናዊ አገዛዝ ጋር በብርቱ እየተናነቀ መሪዎቹ እየታሰሩበትና እየተደበደቡበት መዋቅሩን በመላው አገሪቱ ዘርግቶ አመርቂ የትግል ውጤት እያመጣ ቢሆንም የኢትዮጵያን ሕዝብ የሥልጣን ባለቤትነት ለማረጋገጥ የሚቀረው ጉዞ እጅግ ረጅም ነው፡፡ ከዚህ አንፃር ፓርቲያችን ይህ ታላቅ ጉባኤ የወሰናቸውን ውሳኔዎችና መርሃ ግብሮች በአግባቡ እየተወጣ ታሪክ ይሰራ ዘንድ አጥብቀን እናስገነዝባለን፡፡
በቀጣይ ዓመታት ፓርቲውን በበላይነት እንዲመሩ የተመረጡ አመራሮች ከመቼውም ግዜ በበለጠ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ከአደራ ጭምር እናሳስባለን፡፡

የለንደን ማርያም ቤ/ክ ጉዳይ፡ የሃሰተ መአትን በመርጨት እርስ በእርስ ለማጋጨት የሚጥሩ ካህናትን አሁንም ማርያም እያጋለጠቻቸው ትገኛለች

$
0
0

ቀን፡ 03/01/2014
በክህነት ካባ ተሸፍኖ እግዚአብሔን ሳይፈሩና ሰውን ሳያፍሩ የሃሰተ መአትን በሕዝበ ክርስቲያን ውስጥ በመርጨት እርስ በእርስ ለማጋጨት የሚጥሩ ካህናትን አሁንም ማርያም እያጋለጠቻቸው ትገኛለች።

አእምሮአቸውም በጠፋባቸው እውነትንም በተቀሙ እግዚአብሔርን መምሰል ማትረፊያ የሚሆን በመሰላቸው ሰዎች ይገኛሉ።እንደነዚህ ካሉት ራቅ።1ኛ ጤሞቲ.6፤4-6።

london
የቤተ ክርስቲያን አባላት፤ ካህናቱንና ምእመናኑን ወክለው ርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያንን በበላይነት እንዲያስተዳድሩ ሕዝብ መርጦ ሰይሟቸው የነበሩት 3 ካህናት፤ 4 ምእመናንና 1 የሰንበት ት/ቤት ተወካዮች የአገልግሎት ጊዜአቸውን ጨርሰው ለረጅም ጊዜ በኃላፊነት ላይ በመቆየታቸውና ከዛም ጋር ተያይዞ ብዙ የአስተዳደር ችግሮች በመከሰታቸው ምክንያት በ23 September 2012 ሁላችንም በገዛ ፍቃዳችን ከሥልጣናችን ለቀናል በማለት ለሕዝብ ይፋ አደረጉ።
ከዛም በመቀጠል አዲስ የሰበካ አስተዳደር ጉባኤ ምርጫ ይካሄዳል ሲባል የካህናቱ ተወካዮች በተለይም አባ ግርማ ከበደ ሥላጣናቸውን ዘለዓለማዊ ለማድረግ ሲሉ አዲስ ምርጫ የሚካሄደው በሕዝቡ ፍላጎትና ውሳኔ ሳይሆን እኛ ባልነውና በሚመቸን መንገድ ብቻ ነው በማለታቸው ከፍተኛ ሁከት ተፈጠረ።
በዚህ ጊዜ ይህንን ሁከትና መከፋፈል መቋቋም ያቃታቸው 4ቱ የምእመናን ተወካዮች ቃላቸውን በመጠበቅ ሥራቸውን ሙሉ በሙሉ አቆመው እቤታቸው ቀሩ።
ይህ በሆነበት ወቅት አባ ግርማን ጨምሮ ሦስቱ ካህናት በምእመኑ መልቀቅ ተደስተው ሥልጣኑን ሁሉ የግላቸው በማድረግ የማይፈልጓቸውን የቤተ ክርስቲያኑን አባላት ቤተ ክርስቲያኑ ቅጥር ግቢ ውስጥ እንዳትደርሱ በማለት በደብዳቤ ማገድና ማባረር በመጀመራቸው ቤተ ክርስቲያንን እስከማዘጋት የሚደርስ ሁከትና ረብሻ አስነሱ።

ከዛም በመቀጠል የቤተ ክርስቲያኑ መሰሶ፤ ጣሪያና ግድግዳ የሆኑትን አባላቱን ለማሸነፍ የሚችሉበትን ኃይል ለማግኘት ሲሉ የመረጣቸውንና የወከላቸውን ሕዝብ ከድተው ቤተ ክርስቲያኗ የሃገረ ስብከቱ ናት፤ ንብረቷም የቅዱስ ሲኖዶስ ነው የሚል ማጭበርበሪያን በመጠቀም የመንግሥት ተወካይ የሆኑ ጳጳሳትንና የኤምባሲ ባለሥልጣናትን ተጠቅመው ቤተ ክርስቲያኗን ከአባላቷ ነጥቀው በመውሰድ እጅ መንሺያና መሾሚያ መሸለሚያ ሊያደርጓት ጣሩ፤ ሆኖም ግን አባላት ባደረጉት ጠንካራ ትግልና በእግዚአብሔር ተራዳኢነት አንዱም ተንኮላቸውና ክህደታቸው ውጤት ሳያስገኝላቸው መክኖ ቀረ።
ከዛም በመቀጠል ቤተ ክርስቲያኗ የምትገኝበትን ሃገር አጠቃላይ ሕግና በተለይም ቤተ ክርስቲያኗ የተመዘገበችበትን የቻሪ ሕግ መከተልን አሻፈረኝ በማለት በማታለልና በመዋሸት የቤተ ክርስቲያንን ንብረት ከአባላቷ መንጠቅ እንችላለን በማለት የሃገርንም ሆነ የሕዝብ ንብረትን ሲዘርፉ ይሉኝታም ሆነ ሃፍረት ካልፈጠረባቸው የዘመናችን የቀን ጅቦች ጋር በመመሳጠር በቤተ ክርስቲያኑ አባላት ላይ የጥቃት ዘመቻ ከፍተው አሁንም በአባላቱ ጥንካሬና በእግዚአብሔር ተራዳኢነት የተኮል መረባቸው ሁሉ እንዳይሰራ ተደረገ፡፡
በመጨረሻ የቻሪቲ ኮሚሽን ጉዳዩን በመረዳት ምንም እንኳ ከሥልጣን አንለቅም ብለው ሥልጣንን የሙጥኝ ብለው ሕዝብንና ቤተ ክርስቲያንን የሁከት መድረክ ያደረጉት 4 የሰበካ አስተዳደር ጉባኤ አባላት (Trustees) ውስጥ አንድም ሥለ ምእመኑ የሚከራከርና ምእመኑን የሚወክል አባል ባይኖርም ከዚህ እነሱ የሙጥኝ ካሉት ሥልጣን እንደ ሰንኮፍ አውጥቶ በመጣል ቤተ ክርስቲያኗን እና አባላቷን ከፈጠሩባት ሕመም ለማዳን ያለው አማራጭ አዲስ ምርጫ ማካሄድ መሆኑን በመረዳት ባለ አደራዎች (Trustees) ነን ብላችሁ ከሆነ የምትንገታገቱት ኃላፊነት የሚሰማው ሥራ መሥራት አለባቸሁ በሚል በንፈስ መብታቸውን ለማስከበርና ቤተ ክርስቲያናቸውንና ሃይማኖታቸውን ጠብቀው ለማኖር ሕጋዊ መንገድ ይዘው ከሚታገሉ የቤተ ክርስቲያኑ አባላት ተወካዮችና የሕግ ጠበቃቸው ጋር ግንኙነት በመፍጠር ከቤተ ክርስቲያን መከፈት ጀምሮ አዲስ ምርጫ ስለሚካሄድበት ሁኔታ ታዛቢ ባለበትና፤ በፊርማ በሚረጋገጥ የውል ሰነድ መሰረት ስምምነትና መግባባት ላይ እንዲደርሱ ቀነ ገደብ ወስኖ መመሪያ ሰጣቸው።
ቻሪቲ ኮሚሽን ይህንን መመሪያ ሲያወጣ ግን እነሱ ብቻ ናቸው ትረስቲዎች ብሎ መወሰኑ ሳይሆን ማን ትረስቲ እንደሆነ የሚወስነው ፍርድ ቤት ነው በማለት ከችግሩ ለመውጣት ግን መፍትሔው ሁሉም ወገን የተስማማበት ምርጫ ማካሄድ ነው የሚለውን አበክሮ በመግለጽ ነበር።
ይህንንም ቻሪቲ ኮሚሽን በጻፈው ደብዳቤ በተራ ቁጥር 5 ላይ እንደሚከተለው በማለት ያብራራዋል።

“As part of our regulatory case we considered the question of who are the validly appointed trustees of the charity. This is a matter to which only the Courts can provide a definitive answer because the question centers on interpreting the governing document of the charity, which is under the jurisdiction of the Courts.”

ይህንን የመሰለ መመሪያና ማብራሪያ ቻሪቲ ኮሚሽን ለሁለቱም ወገን የሕግ ጠበቆች ልኮ እያለ የእውነትና የፍትሕ መንገድ ሁሉ ጨለማ መስሎ የሚታያቸው አባ ግርማና ተከታዮቻቸው ግን በተለመደው የቅጥፈት ተግባራቸው መሠረት ከመመሪያው ውስጥ ቻሪቲ ኮሚሽን ትረስቲዎች ናችሁ ብሎ ተቀብሎናል የሚል የተሳሳተ ትርጉም በማውጣት ከአሁን በኋላ የምንፈልገውን የፈላጭ ቆራጭነት ድርጊት ሁሉ የመፈጸም መብት ተሰጥቶናል የሚል አዋጅ አሰሙ።
ከዛም በመቀጠል
1. ረብሻና ሁከት በቤተ ክርስቲያን ውስጥ እየተከሰተ በHealth & Safety ችግር ምክንያት ተዘጋ ብለው ለ9 ወር ያሸጉትን ቤተ ክርስቲያን የኛ ሥልጣን ተረጋግጦልናልና የቤተ ክርስቲያን አባላት ቢፈልጉ ገብተው ይጫረሱ በሚል የአረመኔነት መንፈስ ቤተ ክርስቲያኑ በ29/12/2013 እንከፍታለን የሚል ማስታወቂያ አሰራጩ።
London church
3. ከቄሱ የጳጳሱ እንዲሉ አቡነ እንጦስ የሚባሉ በኢትዮጵያ መንግሥት የዲፕሎማሲ ፓስፖርት የሚንቀሳቀሱና መንበራቸው በሥላሴ ቤተ ክርስቲያን የሆነ፡ ራሷን ችላ ስትተድደር ከኖረችው ከንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት የሌላቸው በሥላሴ ቤተ ክርስቲያንና በገብረኤል ቤተ ክርስቲያን በመገኘት ቤተ ክርስቲያኑን እንድከፍት ቻሪቲ ኮሚሽን ስለፈቀደልኝና ከቅዱስ ሲኖዶስም ስለታዘዝሁ እኔ አቅመ ደካማ ነኝና በ29/12/13 እሑድ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ድረሥ ሁላችሁም መጥታችሁ እንድትረዱኝ በማለት ስብከት፤ ቅስቀሳና ጥሪ አደረጉ። ከዛም በማያያዝ ከለንደን ውጪ ያሉ ተንቀሳቃሽ አብያተ ክርስቲያናት የመጓጓዣ ኮች ተልኮላቸው በነጻ በመጓጓዝ ማርያም ቤተ ክርስቲያን መጥተው የእነ አባ እንጦስ ሠራዊት ሆነው እንዲዘምቱ መርሃ ግብር ተዘጋጀ።
አቡነ እንጦስ ከአሁን በፊትም እንኳንስ ብጹዕ ከተባለ ጳጳስ ቀርቶ ከማንኛውም የእግዚአብሔር አማኝ ሰው በማይጠበቅ ሁኔታ የቤተ ክርስቲያኑ አባላት የሚጸልዩበት ቦታ ድረሥ በመምጣት ሰላም አወርዳለሁ በማለት እኔ የሁለታችሁም አባት ነኝ፤ ለአንዳችሁም አላደላም በማለት እውነተኛ አባት መንፈሳዊ አባት መሆናቸውን ለማሳየት ጥረው ነበር። የሚገርመው ግን ይህንን የቅጥፈት ቃል የሚናገሩት በሌላ በኩል ከቤተ ክርስቲያኗ አባላት ጋር ለውነት ቆመው የእውነት ሥራን በመስራት ላይ ያሉትን ቄስ ብርሃኑን ከቤተ ክርስቲያኑ አባላት ጎራ ወጥተህ ከኔ ጎን ተሰልፈህ አባላቱ እንዲበተኑ ካላደረግህ አሳርህን አሳይሃለሁ በማለት በስማቸው እየፈረሙ የሚልኩትን ከአንድም ሁለት የማስጠንቀቂያ ደብዳቤና ከአባ ግርማ ጎን ቆመው ቀን ከሌሊት እንደሚሰሩ እግዚአብሔር ቀርቶ አባላትም የሚያቁት የአደባባይ ምሥጢር ስለነበር እኝህ ጳጳስ እንኳንስ ሰውን እግዚአብሔርንም አታልላለው ብለው በማሰብ የሚያደርጉት ጥረት በእጅጉ የሚያሳዝንና የሚያሳዝን ነበር።
ይህ አልበቃ ብሏቸው ነው ዛሬ ደግሞ ሌላ በሬ ወለደ ሃሰት ለሕዝበ ክርስቲያኑ የሚነግሩት። አቡነ እንጦስ ቻሪቲ ኮሚሽን ቤተ ክርስቲያን እንድከፍት ፈቅዶልኛል ያሉት ቻሪቲ ኮሚሽን ግን የእሳቸው ጣልቃ መግባት ተገቢ ያልሆነ መሰናክል ነው በማለት የገለጸው ባጭሩ እንደሚከተለው ነበር።
“We have pointed out that a role of the Archbishop of the Diocese of North West Europe is neither appropriate nor desirable for the trustees to create unnecessary barriers to an inclusive election process.”
በሌላ በኩል ደግሞ አቡነ እንጦስ ይህንን የሃሰት መረጃ መሠረት በማድረግ ለጸሎትና ለቅዳሴ የተሰበሰበውን ሕዝበ ክርስቲያን እኔ አቅመ ደካማ ነኝና መጥታችሁ እርዱኝ ማለታቸው የቤተ ክርስቲያኑን በር ለመክፈት የሚፈነቅል ድንጋይና የሚጎተት ገመድ ኖሮ ጉልበት አስፈልጎ ሳይሆን በብዛት መጥታችሁ በቤተ ክርስቲያኑ አባላት ላይ በመዝመት ቤተ ክርስቲያኗን እንድወርስ እርዱኝ ማለታቸው ነበር።
በዚህ ድርጊታቸው እኚህ ጳጳስ ምን ያህል እግዚአብሔርን ሳይፈሩና ሰውን ሳያፍሩ ውሸትን ከመንዛት አልፈው ዓላማቸውን ለማሳካት ሲሉ አንዱን ክርስቲያን በሌላው ላይ አዝምቶ ማፋጀት የማያሳስባቸውና የማይጸጽታቸው ሰው እንደሆኑ መረዳት ይቻላል።
4. ከዚሁ ጋራ አባ ግርማ ከበደና ተከታዮቻቸው፤ ከኢትዮጵያ ኤምባሲ ባለሥልጣናት፤ የወያኔ የደህንነት ሰዎች፤ የሃገረ ስብከቱና የሥላሴ ሹማምንቶች ጋር በመሆን ለአካባቢው ፖሊስ ሥለ ቤተ ክርስቲያኑ አባላት የሃሰት መረጃንና ማስፈራሪያ በማቅረብ የፖሊስ ኃይል በተጋነነው መረጃ ላይ በመመርኮዝ ከፍተኛ የደም መፋሰስና መበጣበጥ ሊመጣ ነው ብሎ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ልዩ የፖሊስ ኃይል እንዲያሰማራ አስደረጉ።
5. አባ ግርማና ተከታዮቻቸው የሚደገፉት እጅግ ጥቂት በሆኑ አባላት በመሆኑና 90% የሚሆነው የቤተ ክርስቲያኑ አባላት አንባ ገነናዊና ክርስቲያናዊ ያልሆነውን ድርጊታቸውን የሚቃወምና የሚኮንን በመሆኑ፤ ቤተ ክርስቲያኑ ሲከፈት የወያኔ መንግሥት ደጋፊ የሆኑ የሥላሴና የገብረኤል ቤተ ክርስቲያን አባላት በተለይም የሥላሴ ቤተ ክርስቲያን አባላት ከነካህናቱና የሰበካ አስተዳደር ጉባኤ አባላት (Trustees) ሳይቀሩ በዘመቻ መልክ መጥተው የቤተ ክርስቲያኑን አባላት በቁጥር በመብለጥ እንዲያጠቁላቸውና እንዲያባርሩላቸው በማሰብ የራሳቸውን ቤተ ክርስቲያን የቅዳሴ አገልግሎት በመጨረስ ተጓጉዘው እስኪደርሱላቸው ጊዜ እንደሚወስድ በማሰብ የቤተ ክርስቲያኑን መከፈቻ ሰዓት ከጠዋቱ 5 ሰዓት (1100) እንዲሆን አደረጉ።

የቤተ ክርስቲያኑ በሕገወጥ መንገድ መከፈት ከተረጋገጠ በኋላ የተፈጠሩ ክስተቶች።
1. የቤተ ክርስቲያኑ አባላት ቤተ ክርስቲያናቸው ከተዘጋችባቸው ጀምሮ ላለፉት 9 ወራት በብርድ፤ በዝናብና በቸነፈር ጸሎታቸውንና ልመናቸውን ሳያስተጓጉሉ በየዕለተ ሰንበቱ ከጠዋቱ አንድ ሰዓት ተኩል ጀምሮ ቤተ ክርስቲያናቸው በመድረስ በቅጥር ግቢ ውስጥ እስከ እኩለ ቀን ድረስ ጸሎትም ሆነ ሥርዓተ ቅዳሴ ያካሂዱ ሥለ ነበር በ29/12/13 በዛው መሠረት እቤተ ክርስቲያናቸው ቅጥር ግቢ ሲደርሱ አባ ግርማ ከበደና ተከታዮቻቸው ከወያኔ ወኪሎችና ደጋፊዎች በሚያገኙት የገንዘብ ፈሰስ በመጠቀም ከፍተኛ ክፍያ የሚጠይቁ ከ10 ያላነሱ Private Security ቀጥረው በማቆም አባላቱ ወደ ቅጥር ግቢ ውስጥ የሚገቡባቸውን በሮች በሰንሰለት በመቆለፉ እንዲከለከሉ አደረጉ። ይህ የተደረገበት ምክንያትም አባላቱ የሌሎች ቤተ ክርስቲያን አባላት የራሳቸውን አገልግሎት ጨርሰው ተጓጉዘው ማርያም ቤተ ክርስቲያን እስኪደርሱና የአባ ግርማ ጎራ በሰው ኃይል እስኪጠናከር ጊዜ ለመግዛትና ከዚህም በተጨማሪ አባላቱ ለምን ማምለኪያና መጸለያ ቦታችንን እንከለከላለን ብለው አንባ ጓሮ እንዲፈጥሩና ይህ ሁኔታ ሲፈጠርም ፖሊስ ጠርቶ አባላትን ለማስያዝና ለማስወንጀል ነበር።
2. በዚህም ምክንያት ቤተ ክርስቲያኗን ከመመሥረት ጀምሮ ለደረሰችበት ከፍተኛ የዕድገት ደረጃ ለማብቃት ላለፉት 40 ዓመታት በጽናት ቆመው ሃብትና ጉልበታቸውን በማፍሰስ፤ የለፉ የደከሙና ያገለገሉ ካህናትና ምእመናን ከ1 ዓመት ህፃን ጀምሮ እስከ 80 ዓመት ዕድሜ ያላቸው አዛውንቶች፤ አቅመ ደካሞችና ህመምተኞች ሳይቀሩ በከፋው የክረምት ብርድና ቁር እየተጠበሱ አውራ ጎዳና አስፋልት ጫፍ ላይ በመኮልኮል ከሦስት ሰዓታት የበለጠ ቢሰቃዩም የደረሰባቸውን በደል ሁሉ በጽናትና በትዕግሥት በማለፍ ከፓሊስ ኃላፊዎች ጋር በመነጋገር በመጨረሻ በፖሊስ ውሳኔና መመሪያ መሠረት የቤተ ክርስቲያኑ ቅጥር ግቢ በር ተከፍቶላቸው ሊገቡ ችለዋል።
3. እነዚህ በቁጥር ከ320 በላይ የሚሆኑ የቤተ ክርስቲያኑ አባላት ካህናትና ምእመናን ወደ ቅጥር ግቢው ሲገቡ አባ ግርማና ተከታዮቻቸው ተቻኩለው የቤተ ክርስቲያኑን ዋናና ትልቅ በር ብርግድ አድርገው ቢከፍቱም አባላቱ ግን የተከፈተው ቤተ ክርስቲያን መዝጊያ በር እንጂ የሰዎች በር እንደተዘጋና እንደተቆለፈ በመሆኑ በቤተ ክርስቲያን አባላት ላይ ቂምን ቋጥረው፤ ክርስቲያኑን ህብረተሰብ እርስ በእርሱ አጋጭተው በዛ መሃል ለመኖር ቀንና ሌሊት የዲያብሎስን ሥራ ከሚሰሩ ካህናት ጋር ሆዶ ሻክሮ ጥላቻን አዝሎ እርቅ ሳይወርድና ሰላም ሳይሰፍን ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ገብቶ መቀደስም ሆነ ማስቀደስ በእግዚአብሔር ማላገጥ ነው በሚል ወደ ቤተ ክርስቲያኑ መግባትን ትተው ወደ ተለመደው የመቀደሻ ሥፍራቸው እየተዥጎደጎዱ ገቡ። ከዛም በመቀጥል ምንም ምንም ሳይሉ የዕለቱን ጸሎታቸውንና ሥርዓተ ቅዳሴ ማካሄድ ጀመሩ።
4. አባ ግርማና ተከታዮቻቸው፤ ከሥላሴ ቤተ ክርስቲያንና ከወያኔ ባለሥልጣናት ጋር በመሆን ከሌላ ቤተ ክርስቲያናትና ከለንደን ውጪ ያስመጧቸውን የወያኔ ደጋፊዎች በማግተለትል ወደ ቤተ ክርስቲያኑ እንዲገቡ አደረጉ፤ እነዚህ አዋጅ ተነግሮና ነጋሪት ተጎስሞ የመጡ የወያኔ ደጋፊዎች ግን ሲበዙ ቢውሉ በቁጥር ከ120 የሚበልጡ አልነበሩም።
5. አቡነ እንጦስና የሃገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ የተባለው መጋቢ ተወልደና ሌሎች የሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ካህናትና ሹማምንቶች የቤተ ክርስቲያኗ አባላት በአንጡራ ገንዛባቸው ገዝተው ባቆሙት የቪካሬጅ ህንፃ ውስጥ ሌሊቱን ተደብቀው በማንጋት በጓሮ በር አድርገው ከሕዝብ ተሸሽገው እንደ ሌባ በጓሮ በር ቤተ ክርስቲያኑ ውስጥ ገቡ።
6. አባ ግርማና ተከታዮቻቸው ከቤተ ክርስቲያኑ መከፈት ጋር ያቀዱት ዕቅድና ያዘጋጁት ነገር ቢኖር በተቀደሰው የእግዚአብሔር ቤት፤ በጽላት ፊት ሕዝበ ክርስቲያንን ለማጋጨትና በሚነሳው ሁከት የቤተ ክርስቲያኑ አባላትን ወንጀለኛ አድርጎ በፓሊስ ለማስያዝ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በየ ጥጉ ካሜራና የድምጽ መቅጃ መሣሪያ አዘጋጅተው ልክ ወጥመድ ውስጥ እንደሚገባ አውሬ አባላትን መጠበቅ ነበር። እነሱ አባላትን ለማጥቃት ወጥመድ ቢያዘጋጁም በዛ ወጥመድ ውስጥ የሚገቡት ግን ከሌሎች አብያተ ክርስቲያናት ተጠርተው በማያገባቸው የሌላ ቤተ ክርስቲያን ጉዳይ ውስጥ ጣልቃ እንዲገቡ የተደረጉት ክርስቲያኖች ጭምር ሊሆኑ እንደሚችሉ ግን የእነ አባ ግርማ ጭንቅላት ታሳቢ እንደማያደርገው የታወቀ ነበር፤ ለዚህም ማረጋገጫው ከአሁን በፊት ወጣቶችን ከየቦታው ሰብስበው አባላትን ለጸብ እንዲያነሳሱና እንዲያስወነጅሉ፤ በመስደብና በድብቅ በመማታት እነሱ መልሰው እንዲመቷችሁ አድርጉ ብለው አሰማርተዋቸው አምስት ወጣቶች ሲታሰሩና ሲወነጀሉ እነ አባ ግርማን የተሰማቸው አንዳችም ፀፀት አልነበረም።
ይህንን ሁሉ ያገናዘቡትና አርቀው ያዩት የቤተ ክርስቲያኑ አባላት ቻሪቲ ኮሚሽን የሰጠው ሕጋዊና መመሪያ ተጥሶ ከአባላት ተወካዮችና ጠበቆች ጋር ፍጠሩ የተባሉትን line of communication ተግባራዊ ሳያደርጉ እነ አባ ግርማ ለሚፈጽሙት ሕገ ወጥ የተንኮል ተግባር ሰለባ ላለመሆንና ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በራሳቸውም ላይ ሆነ በሌሎች ክርስቲያን ወገኖቻቸው ላይ የሚደርሰውን ያልተገባ ነበር ለማስቀረት ሲሉ እነሱ እውጪ በብርድ እየተጠበሱ የሌላ ቤተ ክርስቲያን አባላት ቤተ ክርስቲያናቸውን ወረው ሲይዙ እያዩ ያቺን ቀን በታላቅ ትዕግሥትና ብልህነት አሳልፈዋታል፤ ነገም ቀን አለና የነገው ቀን ደግሞ ምን እንደሚሆን የሚያውቀው እግዚአብሔር ብቻ ነው።

በመጨረሻም አባ ግርማ ከበደም ሆኑ ቄስ ዳዊት አበበና ቄስ አባተ ጎበና ሕዝብ አምኖና መርጦ የሰጣቸውን ጊዚያዊ ኃላፊነት ዘለዓለማዊ ለማድረግ ሲሉና የራሳቸውን ዓላማ ለማሳካት ሲሉ አንድ ሆኖ በኖረው ሕዝበ ክርስቲያን መካከል የሃሰት ክምር በመሥራት ሕዝብ እርስ በእርሱ እንዲከፋፈልና በጥላቻ እንዲተያይ ከማድረግ አልፈው የቤተ ክርስቲያኑን ውስጣዊ የአስተዳደር ችግር ወደ ሌሎች አብያተ ክርስቲያናት በማዛመት በሚያገኙት ድጋፍ የአባላትን መብት ለመጣስ የሚያደርጉት ጥረት በመጨረሻ በሕግ የሚያስጠይቃቸውና ምድራዊም ሆነ ሰማያዊ ፍርዳቸውን ከማግኘት እንደማይድኑ ማመንና መረዳት ያስፈልጋል።
ውድ የርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አባላትና መላው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ተከታዮችና በ29/12/2013 በቤተ ክርስቲያናችሁ በመገኘት ቤተ ክርስቲያናችሁንና ሃይማኖታችሁን ለመጠበቅና መብታችሁን ለማስከበር በታላቅ ትዕግሥትና ችሎታ ዕለተ ቀኑ በሰላም እንዲያልፍ በማደረጋችሁ እግዚአብሔርም የሚወደው ሰላምና ትዕግሥትን ነውና የማያልቅበት አምላክ በረከቱን አብዝቶ ይሰጣችሁ! ያሰባችሁትን ሁሉ ያሳካላችሁ!!
ወደ ፊትም እንዲሁ በየ ዕለተ እሑዱና በአስፈላጊው ጊዜ ሁሉ ወደ ቤተ ክርስቲያናችሁ በመምጣት በዚህ የሕግ የበላይነት በሰፈነበትና የሰው ልጅ ነጻነት በተረጋገጠበት ሃገር የሃሰት ተግባርን፤ ተንኮልንና አንባ ገነንነትን በሕጋዊ መንገድ በመዋጋት ለቤተ ክርስቲያናችሁ፤ ለሃይማኖታችሁና ለመብታችሁ መከበር በጽናት በመቆም ሃሰትን በእውነት በማሸነፍ ሃይማኖታችሁንና ቤተ ክርስቲያናችሁን በመጠበቅ ለትውልድ የሚተላለፍ ስራ ታከናውኑ ዘንድ የእውነት አምላክና የእውነት መንገድ በሆነው በጌታችን በመድሐኒታችን በእየሱስ ክርስቶስ ሥም ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር! አሜን!!
ለንደን ደብረ ጽዮን ቤተ ክርስቲያንን ከነጣቂዎች እናድን!!

በሞያሌ ከተማ የኦነግ ታጣቂዎች የፈጸሙትን ጥቃት ተከትሎ ከተማዋ በመከላከያ ሰራዊት ስትታመስ ዋለች

$
0
0

oLF Militeryኢሳት ቲቪ በዛሬ ስርጭቱ እንደዘገበው በሞያሌ ከተማ የኦነግ ታጣቂዎች የፈጸሙትን ጥቃት ተከትሎ ከተማዋ በመከላከያ ሰራዊት ስትታመስ ዋለች። ባለፈው ረቡእ ታጣቂዎቹ ከቀኑ 10 ሰአት ገደማ ወደ ከተማዋ በመግባት 3 ጠባቂዎችን በመግደልና አንደኛውን ታጣቂ መሳሪያውን በመቀማትና ልብሱን በማስወለቅ ” ሂድና ለአለቆችህ ንገር” በማለት ጉዳት ሳያደርሱበት መልቀቃቸውን የከተማዋ ነዋሪዎች ገልጸዋል። ታጣቂዎቹ አንድ ድግን መትረጊስ፣ አንድ ላውንቸርና አንድ ባዙቃ ማርከው ወስደዋል። ይህንን ተከትሎ በአካባቢው የደረሱት የመከላከያ ሰራዊት አባላት አንዳንድ የከተማ ነዋሪዎችን እየደበደቡ ሲያሰቃዩ መቆየታቸውን ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ለኢሳት ገልጸዋል።

አንድ ሹፌር ለኢሳት እንደገለጹት የመከላከያ ሰራዊት አባላት ተሳፋሪዎችን ከመኪና ላይ በማስወረድ ድብደባ እንደፈጸሙባቸውና እርሳቸውም በጥፊ እንደተመቱ ተናግረዋል
“እኛ ለምን እንደተደበደብን አልገባንም” የሚሉት ነዋሪዎች፣ ሁኔታው እስከትናንት ድረስ ውጥረት የነበረበት እንደነበርና ፍተሻው በእየጫካው እየተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል።

ታጣቂዎቹ በነዋሪዎች ላይ ምንም አይነት ጉዳት አለማድረሳቸውም ተገልጿል። በጉዳዩ ዙሪያ የሞያሌን አስተዳደር ለማነጋገር ሙከራ ብናደርግም አልተሳካልንም። መንግስትም በጉዳዩ ላይ የሰጠው አስተያየት የለም።

ኦነግ ገዢውን ሀይል በትጥቅ ትግል ለማስወገድ ከሚንቀሳቀሱት ድርጅቶች መካከል አንዱ ነው። ይህ በእንዲህ እንዳለ የመንግስት ታጣቂዎች በኦጋዴን ውስጥ በሚኖሩ ዜጎች ላይ እርምጃ እየወሰደ መሆኑን ኦጋዴን ፕሬስ ዘግቧል።

ልዩ ሚሊሺያ የሚባሉት ሀይሎች ከመከላከያ ሰራዊት አባላት ጋር በወሰዱት እርምጃ ፍሪህ ደሃግ አዳር የተባለው ሰው ሲገደል ሌሎች ደግሞ ቆስለዋል።

አቶ አያሌው ጎበዜ ከአማራ ክልል ፕሬዝዳንትነታቸው ለምን ተነሱ?

$
0
0

ከአቡዛብር ተገኝ

ፋክት መፅሄት (በታህሳስ 2006፣ ቁጥር 26 እትሙ) የአማራ ክልል ፕሬዝዳንት የነበሩት አቶ አያሌው ጎበዜ በምን ምክንያት ከስልጣን እንደ ተነሱ ያሰፈራቸውን መላምቶች አንብቤያለሁ፡፡ ብዙዎቹ በግምትና በይሆናል ላይ የተመሰረቱ ከመሆናቸውም በላይ ለግለሰቡ ከፕሬዝዳንትነት መነሳት በዋና ምክንያትነት ሊመደቡ የሚችሉ አይደሉም፡፡ ለዚህም ነው ለመፃፍ መነሳቴ፡፡

አቶ አያሌው ከአማራ ክልል ፕሬዝዳንትነት የተነሱበት ዋና ምክንያት ምንድነው?

ከዜናው ሀሳብ በመነሳት በአንድምታ የምንረዳው እውነታ ስላለ፣ በኢቲቪ ከቀረበው የአቶ አያሌው ዱላ የማቀበል ዜና ልጀምር፡- በኢቲቪ ዜና መሰረት አቶ አያሌው ጎበዜ ከአማራ ክልል ፕሬዝዳንትነት ስልጣናቸው የተነሱት በፍቃዳቸው ነው፤ “በቃኝ፣ ዱላውን ላቀብል” ብለው፡፡ እንኳንስ ከክልል ፕሬዝዳንትነት ስልጣን ላይ ይቅርና ከተራው የሹመት ስልጣን (ለምሳሌ ምክትል ቢሮ ሀላፊ፣ ከዚያም ዝቅ ሲል “ፕሮሰስ ኦውነር”) ላይ በራሱ ፈቃድ “ልውረድ” ያለን የፖለቲካ ተሿሚ፣ ኢህአዴግ “‘በቃኝ’ ካልክማ እሰዬ” ብሎ ቶሎ የመልቀቅ ልምድ የለውም፤ ኢህአዴግ እንደ ገብስ ቆሎ ሳያሽ የማውረድ ባህል የለውም፡፡ ኢህአዴግ፣ አፍ አውጥቶ “ሹሙኝ-ሹሙኝ” ያለን ወይም በጣም “በሚያስበላ” ሁኔታ እንዲሾም የቋመጠን ሰው የስልጣን መንበሩ የማያቀምሰውን ያህል፣ “ስልጣን በቃኝ” ያለን አባል፣ ተንደርድሮ አያወርድም – ለዚያውም የክልል ፕሬዝዳንት ያህልን ሰው፣ ለዚያውም አስቸኳይ መደበኛ የምክር ቤት ስብሰባ ጠርቶ፡፡

አያሌው ጎበዜ

አያሌው ጎበዜ


ስለሆነም ኢቲቪ አቶ አያሌው ጎበዜ በራሳቸው ፈቃድ “የመተካካት መርሁ በ’ኔም ላይ ይተግበርልኝ” ብለው ከፕሬዝዳንትነታቸው ስለመልቀቃቸው የነገረን ዜና ታእማኒነት የሌለው፣ የተለመደ የኢህአዴግ ድራማ ለመሆኑ አንድ ማሳያ ነው፡፡ ሌላው ማሳያ ግለሰቡ አስቸኳይ መደበኛ የምክር ቤት ስብሰባ ከስልጣን በለለቁበት እለት፣ ሙሉ አምባሳደር ሆነው የመሾማቸው “ትንግርት” ነው፡፡ የአማራው ክልል የምክር ቤት አስቸኳይ መደበኛ ስብሰባ የተጠራው፣ በአቶ አያሌው የቀረበውን “የመተካካት መርሁ በ’ኔም ላይ ይተግበርልኝ” ጥያቄ አዳምጦ ካመነበት ከፕሬዝዳንትነታቸው ሊያነሳቸው፣ ካላመነበት ደግሞ ጥያቄውን ውድቅ ሊያደርግ ነው፡፡ ወይም ደግሞ ጥያቄያቸውን በመሰረታዊ ሀሳብነት ተቀብሎ ከፕሬዝዳንትነታቸው የሚያነሳበትን ወቅት ግን የተወሰነ ጊዜ ሊያራዝም ይችላል፡፡

ከአምባሳደርነት ሹመታቸው የምንረዳው ግን ሁሉም ነገር ቀድሞ ያለቀ መሆኑን ነው፡፡ ግለሰቡ መነሳታቸውም፣ መሾማቸውም ያለቀ ነገር ነበር፡፡ መቼም ምክር ቤት ተብዬው የመወሰን ሙሉ ቀርቶ እንጥፍጣፊ ስልጣን እንኳን ቢኖረው፣ በአምባሳደርነት የተሾመን ግለሰብ ከፕሬዝዳንትነት ስለማውረድ፣ አለማውረድ ጉዳይ እንዲወያይ ባልተደረገ ነበር፡፡ በሌላ አነጋገር አቶ አያሌ ጎበዜ ከፕሬዝዳንትነታቸው እንዲነሱ ለምክር ቤቱ ሀሳባቸውን ካቀረቡበት እለት በፊት አምባሳደር ሆነው ተሹመዋል፡፡ ስለሆነም ቢያንስ በዚያች እለት ግለሰቡ ሁለት ጥምር ስልጣን በትከሻቸው ላይ ነበር – የአማራ ክልል ፕሬዝዳንትም፣ በቱርክ የኢትዮጵያ ሙሉ አምባሳደርም ነበሩ፡፡ ስለዚህም የአማራው ክልል ም/ቤት አስቸኳይ መደበኛ ስብሰባ ተጠርቶ ሲወያይ የነበረው፣ ቀድሞውኑ ከፕሬዝዳንትነቱ በተነሳና አምባሳደር ሆኖ በተሸመ ግለሰብ (አቶ አያሌው) ጉዳይ ላይ ነበር፡፡ (የኢህአዴግ ድራማ እንዴት ደስ ይላል¡)
ድራማው ግን በዚህ አያበቃም፡፡ አቶ አያሌው ለምን ከፕሬዝዳንትነታቸው እንዲነሱ ተደረገ? ፋክት መፅሄት ከተወሰኑ መላምቶች አንፃር በማየት ስለግለሰቡ አነሳስ ምክንያት ለማቅረብ ሞክራለች፡፡ ሆኖም አንዳንዶቹ መላምቶች የተሳሳቱና እጅግ የተጋነኑ ስለሆነ፣ እኔ ለክልሉ ባለስልጣናት ካለኝ ቅርበት አንፃር የተወሰኑት ላይ ማስተካካያ ለመስጠትና ለግለሰቡ ከስልጣን መነሳት ዋናውን ምክንያት ለመጠቆም እፈልጋለሁ፡፡

አቶ አያሌው ከስልጣን የተነሱት ለሱዳን ከተሰጠ የወሰን አካባቢ ቦታ ጋር የተያያዘ መሆኑን አንዳንድ ሰዎች ይናገራሉ፡፡ ከዚህ በፊትም አቶ አያሌው “አልፈርምም አለ” ተብሎ መናፈሱ ይታወቃል፡፡ ይህ ግን ስህተት ነው፡፡ አቶ አያሌ በዙሪያቸው ያሰባሰቧቸው የወንዝ ልጆች በስፋት የለቀቁት ተራ ፕሮፓጋናዳ ነው፡፡ አንደኛ መለስን እንኳንስ “የቁርጥ ቀን ልጅ” በሚፈለግበት እንዲህ ባለው ሁኔታ ቀርቶ፣ ቀላል በሚባሉት ጉዳዮችም “ይህን እኔ አልሰራም” የሚል ባለስልጣን ኢትዮጵያ አልነበራትም (ያማ ቢሆን ኖሮ፣ የተሸከምነው መከራ በግማሽ እንኳን በቀነሰልን ነበር)፡፡ እንዲያውም አቶ መለስ በአንድ ወቅት አቶ አያሌውን “አንተ የማትጠቅም፣ የማትጎዳም ነህ” ብለው በመተቸታቸው በድርጅቱ ትልልቆቹ አባላት ውስጥ ዜናው በስፋት ተናፍሶ ነበር፡፡ ባጭሩ አቶ አያሌው “እምቢ” የማለት ወኔው የላቸውም፡፡ (በሱዳኑ ፊርማ ላይ አቶ ደመቀ መኮንን እንዲሳተፉ የተደረገው፣ ሙስሊም ስለሆኑ/ኢስላማዊ ዳራ ስላላቸው የሱዳኖችን ስነልቦና “ለመግዛት” ኢህአዴግ የቀየሰው ስልት ከመሆን አይዘልም፣ ወደ አንዳንድ አረብ አገራት ዲፕሎማቶችን ሲመድብ ተመሳሳይ መንገድ ስለሚከተል፡፡)

እና አቶ አያሌው ለምን ከፕሬዝዳንትነታቸው እንዲነሱ ተደረገ? የአቶ አያሌው ከፕሬዝዳንትነት መነሳት ለብዙዎች ድንገታዊ ሊመስል ይችላል፤ አንደኛ አቶ አያሌው “የመተካካት መርሁ በ’ኔም ላይ ይተግበርልኝ” ብለው እንዲጠይቁና ይቺው ቃላቸውም ሳትጨመር-ሳትቀነስ በኢቲቪ እንድትተላለፍ ተደርጓል፡፡ ሁለተኛ “ከስልጣን አውርዱኝ” ጥያቆያቸውን ያየው ም/ቤት ጉዳዩን የተወያየበት በ“አስቸኳይ መደበኛ ስብሰባ” ነው፡፡ ሆኖም ግን ሀቁ ሌላነው፡፡ (እነዚህ ግርግሮች ሌላው የድራማው አካል ናቸው)፡፡

አቶ አያሌውን ከፕሬዝዳንትነት የስልጣን ኮርቻ የማንሳቱ እቅድ የተዘረጋው ሟቹ ጠቅላይ ሚኒስትር (አቶ መለስ) በነበሩበት ወቅት ነው፡፡ አቶ መለስ በመሩትና ባህር ዳር ላይ በተካሄደ የኢህአዴግ ስብሰባ ላይ አቶ አያሌ ተገምግመዋል፡፡ በዋናነት የቀረበባቸውና የተቀበሉት ክስም በክልሉ ባሉ የተለያዩ የስልጣን/የሹመት እርከኖች ላይ የራሳቸውን አካባቢ ሰዎች እጅግ በተደራጀ መንገድ ማሰባሰባቸው ነው፡፡ አንዳንዶች ሂደቱን “ጎጃማይዜሽን” ይሉታል፤ ሌሎች ደግሞ “ማርቆሳይዜሽን” በማለት ይጠሩታል፡፡

አቶ አያሌው ሹመት የሚሰጡበት ቀመር በጣም ግልፅ ነው፡፡ እሳቸው ከመጡበት ከደብረ ማርቆስና አካባቢው የተማረ ከተገኘ ያለ ምንም ጥርጥር ይሾማል፡፡ ማርቆሴ እያለ ሌላ ሰው በምንም ሁኔታ አይሾምም፡፡ ማርቆሴ ከጠፋ፣ የአቶ አያሌው ሁለተኛው የሹመት ቀመር ስራ ላይ ይውላል፤ ጎጃሜ የሆነ ሰው ተፈልጎ ይሾማል፡፡ ማርቆሴ ሁሉ ጎጃሜ ቢሆንም፣ ጎጃሜ ሁሉ ግን ማርቆሴ አይደለም፡፡ ሆኖም ማርቆሴ ያልሆነ ጎጃሜን መሾም፣ ጎንደሬን፣ ወሎዬን ወይም የሰሜን ሸዋ ሰው ከመሾም እጅግ የተሻለ ነው፤ ምክንያቱም ጎንደሬም፣ የሸዋ ሰውም ሆነ ወሎዬ መቼም ቢሆን ጎጃሜ አይደለምና፡፡ ይህ የአቶ አያሌው የሹመት ቀመር ከስልጣን በሚወርዲት ላይም ስራ ላይ ይውላል፤ ባብዛኛው ከስልጣን የሚወርድ ተሿሚ ማርቆሴ ወይም ጎጃሜ አይደለም፤ ባጋጣሚ ነገሩ ከፍቶ ከስልጣን ከተነሳም ወይ የተሻለ ቦታ ይሰጠዋል፤ ካልሆነም በያዘው ደረጃና ደመወዝ የአቶ አያሌው አማካሪ ሆኖ ይሾማል (ፉገራ በሚወዱ ካድሬዎች አነጋገር Recycle Bin ውስጥ ይገባል፡፡ ይህ ማለት እንደ ገና የሚሾምበት ጊዜ አለ ማለት ነው፤ አቶ አያሌው ማዘናጋት የሚገባቸውን ካዘናጉ በኋላ፡፡ የቀመሩን ዘረኝነት (racist) ልብ ይሏል፡፡)

ይህም በመሆኑ አሁን በአማራ ክልል ርእሰ ከተማ -በባህር ዳር- ብዙዎቹን የመንግስት ተቋማት የሚመሩት ባለስልጣኖችና ምክትሎቻቸው፣ ዝቅ ሲልም የምክትሎቹ ምክትሎች (ፕሮሰስ ኦውነር፣ መምሪያ ሀላፊ፣ ወዘተ) በዚህ የአቶ አያሌው የሹመት አሰጣጥ ቀመር ወደ ስልጣን የመጡ ናቸው፡፡ ይህ የአቶ አያሌ የሹመት ቀመር በቀጥታ በማይመሩት በባህር ዩኒቨርስቲ ጭምር ስራ ላይ እየዋለ እንደ ሆነ ይነገራል፤ ዩኒቨርስቲው በፌደራል ትምህርት ሚኒስቴር የሚመራና ያሉት መምህራንም ከአገሪቱ ብሄር ብሄረሰቦች የተገኙ ሆነው እያለ፤ የፕሬዝዳንት፣ ምክትል ፕሬዝዳንቶችና ዲን ስልጣን (ወረድ ሲልም ከፕሮግራም ሀላፊ) በአብዛኛው በመጀመሪያ ደረጃ በማርቆሴዎች፣ ከዚያም በጎጃሜዎች “ቡድን” እንዲያዝ ተደርጓል፡፡ የአቶ አያሌው የጎጠኝነትና የዘረኝነት እጅ ይሄን ያህል ረጅም ነው፡፡

ይህ ድርጊታቸው ማለትም ክልሉን የጎጠኞች አምባ ማድረጋቸው አቶ አያሌውን ክፉኛ አስገምግሟቸዋል – በአቶ መለስና በሌሎቹም የኢህአዴግ ቁንጮ አባላት፡፡ ሆኖም አቶ መለስ በሀይል የወቀሷቸውን፣ የሰደቧቸውን፣ ያንቋሸሿቸውን ያህል አቶ አያሌውን ሮጥ ብለው ከስልጥን ማንሳት አልሆነላቸውም፡፡ በአቶ አያሌው ድርጊት “የበገኑትን” ያህል የይስሙላውን የአማራ ክልል ም/ቤት አስቸኳይ መደበኛ ስብሰባ አስጠርተው ግለሰቡን ከፕሬዝዳንትነታቸው በማስወረድ “የትምህን ግባ” ማለት አልቻሉም፡፡ ያን የመሰለ ባለ ራእይ መሪ ይህን ማድረግ ለምን ተሳነው?
ምክንያቱ ግልፅ ነው፡፡ አቶ አያሌው ዙሪያቸውን ያሰለፉት የጎጥ ሀይል ቀላል አይደለም፡፡ ከላይኛው የክልል ካቢኔ ጀምሮ፣ የቢሮ ሀላፊዎች፣ ምክትሎቻቸው፣ ከምክትሎቹ ስር ያሉ ሌሎች ሀላፊዎች ከ95 በመቶ በላይ ከፍ ሲል የተገለፀውን የአቶ አያሌውን የሹመት ቀመር ተከትለው የመጡ ናቸው፡፡ (እዚህ ላይ ከምክትል ቢሮ ሀላፊዎች በታች ባለ የስልጣን ሹመት ላይ አቶ አያሌ ቀጥተኛ ሚና የላቸውም፡፡ ሆኖም በሹመት ቀመራቸው ያመጧቸውን የራሳቸውን የወንዝ ልጆች በሳቸው ቀመር እንዲመሩ ማድረግ አይሳናቸውም፤ አድርገውታልም፤ ተገምግመውበታልም፡፡)
ስለሆነም አቶ አያሌውን በድንገት እንደ ሙጀሌ ፍንቅል ማድረግ አደጋ እንዳለው ኢህአዴግ አመነበት፡፡ እዚያ ክልል ላይ የሰፈረውን አብዛኛውን ባለስልጣን አስኮርፎ ክልሉን መምራት (እንደፈለጉ ማሽከርከር) እንደማይቻል ኢህአዴግ ልብ አለ፡፡ ምናልባት ቅሬታው ስር ሰዶ በተለይም ደብረ ማርቆስ ወደሚገኘው ህዝብ ሊደርስና ያልተፈለገ መነሳነሳት/ብጥብጥ ሊያስከትል እንደሚችል እነመለስ ሰጉ፡፡ ስለሆነም ግለሰቡን በረጅም ጊዜ ለማውረድ መስራት አማራጭ የሌለው ጉዳይ ሆነ፡፡

እናም በክልሉ መስተዳድር መዋቅር ውስጥ የሌለ አደረጃጀት ኢህአዴግ ፈጠረና ከፕሬዝዳንቱ ሰር ሁለት ምክትሎች እንዲኖሩ ተደረገ፡፡ ሁለቱ ምክትሎችም በአቶ አያሌው ዙሪያ ካሰፈሰፉት የጎጥ ቡድኖች ውጭ እንዲሆኑ ተደረገ፤ አቶ አህመድ አብተውና አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ሁለት ምክትል ፕሬዝዳንቶች ሆነው ተሸሙ፤ ሁለቱም ከወሎ፡፡ ስለሆነም አቶ አያሌው የነበራቸው ያሹትን የማድረግ ስልጣን በእጅጉ ተገድበ፤ ባጭሩ ተንሳፈፉ፡፡

የተዘረጋውን ጠንካራ የማርቆሴ መዋቅርና የአቶ አያሌውን ተፅእኖ የማዳከሙ ስራ እንደ ተሳካ ሲታወቅ የይስሙላው የአማራ ክልል ም/ቤት ተጠራ፤ የይስሙላውን የአቶ አያሌው ዱላ ላቀብል የሚል ምክንያት አዳመጠ፤ አፅድቅ የተባለውን አፀደቀ፡፡ በቃ- የሆነው ይኼው ነው፡፡
በነገራችን ላይ ኢቲቪ በአንድ የዜና ስርጭት ላይ፣ የአቶ አያሌውን ከስልጣን መውረድ “ካረዳ” በኋላ፣ ወዲያው በማስከተል በሙሉ አምባሳደርነት መሾማቸውን “ማብሰሩ” ሰውዬው ከፕሬዝዳንትነት በመነሳቱ ቅር የሚላቸውን መገኖች (የማርቆሴ ቡድን) ስሜት ለማከም መሆኑን ልብ ይሏል፤ ኢህአዴግ እንዲህ ነው መፍራት ሲጀምር ልክ የለውም፣ መድፈር ሲያበዛ ልክ እንደሌለው ሁሉ፡፡

ሌላው ለአቶ አያሌው ከስልጣን መሳነት እንደ ተጨማሪ ምክንያት ሊቀርብ የሚችለው፣ የምስራቅ ጎጃም በተለይም በሞጣ የአዲስ አበባ መንገድ አቅጣጫ ያለው ህዝብ ተደጋጋሚ ቅሬታና አቤቱታ ነው፡፡ የአዲስአበባ-ሞጣ-ባህር ዳር የጠጠር መንገድ በአስፋልት እንዲሰራ የአካባቢው ህዝብ ለዘመናት ጠያቄ ሲያቅርብ ኖሯል፡፡ ሟቹ ጠቅላይ ሚኒስትር – አቶ መለስ – ለህዝቡ ቃል የገቡ ቢሆነም እስካሁን ድረስ የመንገድ ስራው ሊጀመር አልቻለም፡፡ ለዚህ ደግሞ ዋናው ተጠያቂ፣ የአካባቢው ህዝብ እንደሚናገረው፣ አቶ አያሌው ናቸው፤ “አቶ አያሌው በስልጣን እያለ የኛ መንገድ አይሰራም” በማለት ቅሬታቸውን በምሬት ይናገራሉ፡፡ በቅርቡ ሰላማዊ ሰልፍ ሁሉ ወጥተዋል፡፡ ግን አቶ አያሌው ለምን ችክ ብለው መንገድ ግንባታውን ያሰናክላሉ?

የአካባቢው ተወላጅ ምሁራን እንደሚሉት የሞጣው መንገድ መሰራት ከአዲስ አበባ-ባህር ዳር ያለውን ርቀት ቢያንስ በ70 ኪሎ ሜትር ስለሚያሳጥረው፣ በነባሩ መስመር ማለትም በቡሬ በኩል ባሉት ከተሞች ላይ ከፍተኛ የሆነ አሉታዊ ተፅኖ ይኖረዋል፤ ያለ ጥርጥር ብዙዎቹ ተሸከርካሪዎች በሞጣው መስመር ስለሚሄዱ የቡሬ መስመር ነጋዴዎች በተለይም ሆቴሎች ገቢ ትርጉም ባለው ሁኔታ ማሽቆልቆሉ አይቀሬ ነው፡፡ ደብረ ማርቆስ ያለችው ደግሞ በዚሁ የቡሬ መስመር ነው፡፡ አቶ አያሌው ደግሞ ከዚህች አካባቢ ምሁራን ብቻ ሳይሆን ከከተማዋ ጋር ያላቸው ፍቅር ወደር የለውም፡፡ እናም ለጎጣቸው ሲሉ የጎረቤታቸውን ጎጥ መልማት ሲከላከሉ ነው የኖሩት፡፡
እና ኢህአዴግ እኒህን ሰው ከስልጣን ማንሳት ይነሰው?


የሰላማዊ ትግል እድገታችን –ግርማ ሞገስ

$
0
0
(ግርማ ሞገስ)

(ግርማ ሞገስ)

የዚህ ጽሑፍ ግብ የሰላማዊ ትግል እድገት ከኢትዮጵያ ውጭ እና በኢትዮጵያ ውስጥ ያደረጋቸውን እድገቶች ታሪክ ማጥናት ነው።
(ሀ) ከኢትዮጵያ ውጭ፥
(1) ከክርስቶስ መወለድ ቀደም ብሎ
ጥንታዊ ሮማውያን ከክርስቶስ ልደት 509 አመቶች ግድም ቀደም ብሎ የነበረውን ፍጹም አምባገነናዊ የዙፋን አገዛዝ አፍርሰው ረፓብሊክ የፖለቲካ ስርዓት መሰረቱ። ይህ አዲስ ህብረተሰብ ፓትሪሳን (Patrician) እና ፕሌቢያን (Plebeian) በሚባሉ ሁለት መደቦች የተከፈለ ነበር። ፓትሪሳን የሚባለው መደብ በቀድሞው ንጉሳዊ ስርዓት የነገስታት እና የባላባት ዝርያዎችን የነበሩትን ያካተተ የገዢዎች መደብ ነበር። ፕሌቢያን (Plebeian) የተባለው መደብ አናጺውን፣ ብረታ ብረት አቅላጩን፣ መንገድ እና ህንጻ ሰራተኛውን፣ አራሹን፣ ነጋዴውን፣ ምግብ አብሳዩን፣ በወታደርነት አገልጋዩን እና የመሳሰለውን የህብረተሰብ ክፍል ያካተተ መደብ ነበር። -–ቀጣዩን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ–-

 

እስር ላይ የሚገኘው አንዷለም አራጌ አዲሱን የአንድነት አመራር “ሕዝቡን ለመብቱ እንዲታገል አንቁት”አላቸው

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) በዘ-ሐበሻ አንባቢዎች ዘንድ የ2005 ዓ.ም የዓመቱ ምርጥ ሰው ሽልማትን ያገኘውና በ እድሜ ልክ እስራት በገዢው መንግስት ተበይኖበት ቃሊቲ የሚገኘው አንዷለም አራጌ ዛሬ ጠዋት ሊጠይቁት የሄዱትን አዳዲሶቹን የአንድነት ፓርቲ አመራሮች “ሕዝቡን ለመብቱ እንዲታገል አንቁት፤ ሕዝቡ መብቱን አውቆ ለመብቱ እንዲነሳ በማንቃት ለውጥ ለማምጣት ጠንክራችሁ ሥሩ፤ እንደምታደርጉትም ተስፋ አለኝ” ማለቱን ከአዲስ አበባ የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች ገልጸዋል።
Andualem aragie
ባሳለፍነው ሳምንት የፕሬዚዳንት ነጋሶ ጊዳዳን እና ካቢኔያቸውን በምርጫ አሰናብቶ በአዲስ የሾመው አንድነት ፓርቲ፤ አዳዲሶቹ ተሿሚዎች ስልጣናቸውን ከተቀበሉ በኋላ የመጀመሪያ ሥራቸውን ያደረጉት በ እስር ቤት የሚገኙትን የፓርቲዎቻቸውን አባላት መጠየቅ ነበር። በዚህም መሠረት አዳዲሱ አመራር እስር ቤት ከሚገኙት የድርጅቱ አመራሮችና አባላት የሚያበረታቱ ምክሮችን መቀበሉን ከዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች ዘገባ ለመረዳት ተችሏል።

አንዷለም አራጌ በአዲሱና በወጣት በተገነባው የአንድነት ፓርቲ አመራር ደስተኛ መሆኑን ገልጾ “ሕዝቡን ለመብቱ እንዲታገል አንቁት፤ ሕዝቡ መብቱን አውቆ ለመብቱ እንዲነሳ በማንቃት ለውጥ ለማምጣት ጠንክራችሁ ሥሩ፤ እንደምታደርጉትም ተስፋ አለኝ” ብሏቸዋል። ይኸው የአንድነት ፓርቲ አመራር እዛው ቃሊቲ የሚገኙትን እነ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋን ጨምሮ ሌሎች የሕሊና እስረኞችን ለመጠየቅ ጠይቆ መከልከሉ የታወቀ ሲሆን ወደ ዘዋይ ያመራው የአንድነት ፓርቲ ቡድን እዛው እስር ቤት የሚገኙትን ን የአንድነት የብሄራዊ ምክር ቤት አባል አቶ ናትናኤል መኮንንና በዚያ የሚገኙ ሌሎች እስረኞችን መጎብኘታቸውም ጨምሮ የደረሰን መረጃ ያመለክታል።

በሕወሓት/ ኢሕአዴግ አስተዳደር “በሽብርተኝነት ወንጀል” ተከሷል፤ በሌሎች ኢትዮጵያውያን ዘንድ ደግሞ የሕሊና እስረኛ ነው የሚባለው አንዷለም አራጌ ከዚህ ቀደም ከ እስር ቤት ተቃዋሚዎች የእኔን እስር ቤት መማቀቅ ልትጠቀሙበት አልቻላችሁም፤ ሕዝቡን ለማታገል ልትጠቀሙበት ትችሉ ነበር ሲሉ የነበረውን ድክመት መግለጹን ዘ-ሐበሻ መዘገቧ አይዘነጋም።

ዴሞክራሲያ ጋዜጣ (PDF)፡ ያልተቋረጠ ትግል፤ ያልተቆጠበ መሥዋዕት

$
0
0

eprp rt ዴሞክራሲያ ቅጽ 39 ቁጥር 3

መሠረትን በሕዝብ ፍቅርና በሃገር ጥቅም ላይ አድርጎ የሚታገል ድርጅት፤ ዓላማውን ከግብ ለማድረስ ያልተቆጠበ ትግልና ያልተቆጠበ መሥዋዕት ከመክፈል የተለየ ባህርይና ድርጊት አይኖረውም።
ሙሉውን በPDF ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

አንኳን ለብርሃነ በሰላም ልደቱ አደረሰዎ

“ለአፍሪካ ቀንድ ሠላም የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ መመለስ አለበት” –ረ/ፕሮፌሠር መድኅኔ ታደሠ

$
0
0

<strong>“ለአፍሪካ ቀንድ ሠላም የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ መመለስ አለበት”
“የመለስን ያህል ስልጣን የያዘ ሠው አለመኖር ብዙ ነገሮችን ሸግግርና ጥያቄ ውስጥ እንዲገቡ አድርጓቸዋል”
ረ/ፕሮፌሠር መድኅኔ ታደሠ</strong>

<em>ረዳት ፕሮፌሠር መድኅኔ ታደሠ በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በአፍሪካ ፖለቲካ ጉዳዮች በተለይ በግጭት አወጋገድ አጥኚና ተመራማሪ ናቸው፤ በመገናኛ ብዙሃን በመቅረብ በሚሰጡት ትንታኔም ይታወቃሉ፡፡ “Horn of African Veteran Political Analyst” በማለት የውጪ ሃገር መገናኛ ብዙሃን ይገልጿቸዋል፡፡ ረ/ፕ መድሃኔ ከሥራ ጉዳይ ጋር በተያያዘ አብላጫ ጊዜያቸውን በውጪ ሃገራት ነው የሚያሳልፉት፤ ባለፈው ሳምንት ከደቡብ ሱዳን እንደተመለሱ በወቅታዊ የሃገር ውስጥና የአፍሪካ ቀንድ ፖለቲካ ዙሪያ ከሎሚ አዘጋጅ ቶማስ አያሌው ጋር ያደረጉት ቆይታ እንደሚከተለው ቀርቧል፡-
</em>
ሎሚ፡- ረ/ፕ መድኅኔ እንኳን በሠላም ተመለሱ፤ ለመሆኑ በአሁኑ ወቅት ዋና ትኩረትዎን ምን ላይ አድርገው በመስራት ላይ ነዎት?
Medhane Tadesse 1
ረ/ፕ መድኅኔ፡- እንኳን ደሕና ቆያችሁኝ፡፡ በዋነኛነት በአፍሪካ የፀጥታ ችግሮችና ግጭት አፈታት ዙሪያ ከተለያዩ መንግስታትና ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር የማማከር ስራ ነው የምሠራው፡፡ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የተጠመድኩበት ስራ የአፍሪካ ህብረት የፀጥታ ዘርፍን ስትራቴጂ ማዳበር ነበር፡፡ ትኩረቱ የአፍሪካ መንግስታት የፀጥታ ተቋማትን ማሻሻል ነው፡፡ የአፍሪካ ሃገራት ካሉበት በጣም የወደቀ የማይመች አሠራር መለወጥ ያስፈልጋል፡፡ ቀደም ሲል አፍሪካ ለዚህ የሚሆን ዕቅድ አልነበራትም፡፡ የአፍሪካ ህብረትም ዕቅዱ ያስፈልገው ነበር፡፡
የአሕጉሪቱ መንግስታት የየሃገራቸውን የደህንነት፣ ፖሊስና መከላከያ ኃይል የመሳሰሉ የፀጥታ መዋቅሮቻቸውን ለህዝብ ተጠያቂ እንዲሆኑ ማድረግ አለባቸው፡፡ እነዚህ የግጭት መንስዔም የችግር ምንጮችም ናቸው፡፡ ስለሆነም አዋጁ ተረቆ ካልጸደቀ በቀር አፍሪካ ውስጥ ሠላምና ዲሞክራሲ ሊመጣ አይችልም በሚል እሳቤ ይሄንን ሃሳብ ከሚጋሩ ጓደኞቼ ጋር ሆነን አጀንዳውን ቀረጽን፡፡ የየሃገራቱን ነጣጥለን ከመመልከት በአሕጉር ደረጃ በተለይ የፀጥታና የደህንነት ተቋማት አወቃቀር እንዲሻሻል ማድረግ አለብን ብለን በመነሳት ባለፉት ሁለት ዓመታት ለዚህ የሚሆን መነሻ ሃሳብና ግብአት አስቀምጠን በአማካሪነት ስንሰራ ቆይተናል፡፡ ሥራው ተጠናቆም የመሪዎች ጉባዔ አፅድቆታል፡፡

ሎሚ፡- በኮተቤ መምህራን ኮሌጅ በሚያስተምሩበት ወቅት የአፍሪካ ግጭት ተመራማሪ እየተባሉ ነበር የሚጠሩት፤ በመፅሐፎችዎም ይኽ ተጠቅሷል፤ እነዚህን የጥናት ውጤቶች ጠቅለል አድርገው ቢገልጹልን?

ረ/ፕ መድኅኔ፡- አብዛኞቹ መፅሃፎቼ ከታተሙ ከ10 ዓመት በላይ ሆኗቸዋል፡፡ አንዱ የኢትዮ ኤርትራ ጉዳይ ነው፡፡ ሁለተኛው ትልቅ ተፅዕኖ የፈጠረው መፅሀፍ በአፍሪካ ቀንድ በማተኮር በ“አል ኢትሃድ አል ኢስላሚያ” ዙሪያ የፃፍኩት ነው፤ የሶማሊያ አክራሪ ቡድኖች ምንጭ፣ እድገት እና አፈጣጠር ላይ ያተኮረ ነው፤ ሶማሊያ በዚህ ከቀጠለች አክራሪዎቹ ወታደራዊ የበላይነት የሚጨብጡበት ሁኔታ ሊፈጠር እንደሚችል ከ10 ዓመት በፊት ነበር የፃፍኩት፤ የተባለው ሆኖ “ኢስላሚክ ፍርድ ቤቶች ሕብረት”፣ “አልሸባብ” መጡ፤ ይሕን እና ከምንጫቸው አንስቶ ወደ ዓለም አቀፍ ጂሃድ እንቅስቃሴ ምስረታ ድረስ የሚኖረውን ሂደት እንዲሁም በሶማሊያ ምን ሊፈጠር እንደሚችል የሚጠቁም መጽሐፍ ነው፡፡ የሆነው ሆኖ ኢትዮጵያም ጣልቃ እስከመግባት ደረሠች፡፡
ሌላኛው መጽሐፌ የናይል ጉዳይ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ውሃ እንዲሁም የሱዳንና ግብፅ ነዳጅ ዘይት ወሳኞቹ የትስስር ክንፎች ወይም የግጭት ምንጮች ይሆናሉ ነው የሚለው፡፡ ይሕም ረጅም ዓመት ሆኖታል፡፡ በአጠቃላይ ወሳኝ ናቸው የሚባሉ የአፍሪካ ቀንድ ዘመን ተሻጋሪ ግጭቶችን፣ መፍትሔዎችን፣ ምን ሊፈጠር እንደሚችል የሚጠቁሙ ስራዎች ላይ ነበር ያተኮርኩት፡፡

አሁንም ድረስ እዚያው ላይ ነው እየዳከርን ያለነው፡፡ ወይ መንግስታቱ አይሠሙም፤ አለያም ምንም አይነት እንቅስቃሴ ማድረግ ስላልቻሉ ችግሮቹ እንደቀጠሉ ናቸው፡፡ በርግጥ ችግሮቹ ዘመንና ትውልድ ተሻጋሪ በመሆናቸው እንኳንስ በአንድ መንግስት ቀርቶ በአራትና አምስት መንግስታት ላይቀረፉ ይችላሉ፡፡ የአባይ ጉዳይ፣ የኢትዮጵያ የባህር በር ጉዳይ… ለዘመናትና ለትውልዶች የሚቆዩ ይሆናሉ፡፡ ችግሮቹ በአንዴ ይፈታሉ ማለት ባይቻልም የመፍትሄ አቅጣጫውን ማስቀመጥ ግን ይቻላል፡፡ የኤርትራም ጉዳይ እንደዚያው ነው፡፡ በዚህ ዙሪያ ከአስር ዓመት በፊት ያደረግኩትን ጥናት በኢ.ሲ.ኤ መድረክ አቅርቤ ነበር፡፡

በጥናቱ የውሃ እንቅስቃሴ ኢትዮጵያ ውስጥ አደገኛ እየሆነ እንደሚሄድ፣ ብሔር፣ ሃይማኖት፣ ህዝብን ሊፈትን የሚችል ኃይል ሊኖረው እንደሚችል ጠቁሜያለሁ፡፡ በተለይ በሃይማኖት ረገድ የሳዑዲው “ዋህቢያ” ያለውን ጥንስስ፣ የሃይማኖት ግጭት በአምስት አመት ውስጥ ሊፈጥር እንደሚችል ነበር ያ ፅሁፍ የሚያብራራው፡፡ ያኔ መንግስት አልተቀበለውም ነበር፡፡ አሁን ደግሞ የሆነው እየታየ ነው፡፡ በአጠቃላይ የኢትዮጵያ ችግሮች ዙሪያ ያተኮረ ነበር፡፡ ችግሩ አሁንም በተለያየ መልኩ የሚታይበት ሁኔታ ነው ያው፡፡

ሎሚ፡- ገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ ከቀድሞው መሪ አቶ መለስ ዜናዊ ሕልፈት በኋላ የከፋ መሠነጣጠቅ ውስጥ እንደገባ በተለያዩ ወገኖች ይገለፃል፡፡ እርስዎ ስለዚህ ጉዳይ ምን መረጃ አለዎት?

ረ/ፕ መድኅኔ፡- የከፋ መሠነጣጠቅ ለማለት ያስቸግራል፡፡ ከመለስ ሞት በኋላ ኢህአዴግ ብቻ ሳይሆን ሃገሪቷም ሌላ ሽግግር ውስጥ ነው የገባችው፡፡ ኢትዮጵያ ሽግግር ላይ መሆኗን ያለመረዳት ችግር ያለ ይመስለኛል፡፡ ልክ ከደርግ በኋላ እንደነበረው ሽግግር ማለት ነው፡፡ ምክንያቱም የመለስን ያህል ከፍተኛ ስልጣን የነበረው ሰው አለመኖር ብዙ ነገሮችን ሽግግርና ጥያቄ ውስጥ እንዲገቡ አድርጓቸዋል፡፡ ስልጣን የማሸጋገሩና የማጠናከሩ ጉዳይ አሁንም እንደቀጠለ ነው፤ ፍፃሜ ላይ አልደረሠም፡፡ በዚህ ውስጥ በፓርቲው፣ በመከላከያው፣ በፀጥታ ተቋማትም ብዙ ሂደቶች ሊኖሩ ይችላሉ፡፡ ሂደቶቹ አንድ መልክና ቅርፅ አልያዙም፡፡ ይህ እንግዲህ የተለያዩ ኃይሎች ፍላጎቶች የሚንጸባረቅበት ስለሆነ እየተከታተሉ ማየት ነው የሚሻለው፡፡

ሎሚ፡- ኤርትራ (በተለይ ኢሳይያስ አፈወርቂ) ከኢትዮጵያ ጋር በኮንፌዴሬሽን የመዋሃድ ሃሳብ እንዳላቸው፣ ሆኖም ግን በኢህአዴግ በኩል ፈቃደኝነቱ እንደጠፋ አቶ አብርሃም ያየሕ በቅርቡ በበተኑት ሠፊ መጣጥፋችው ገልፀዋል፤ አሁንም ሆነ በቀደመው ጊዜ በኤርትራ በኩል እንዲህ ያለ ሃሳብ ቀርቦ ነበር?

ረ/ፕ መድኅኔ፡- ይሄ ሃሳብ የነበረው በነፃነት ትግሉ ወቅት ነው፡፡ እንዲያውም ህዝባዊ ግንባር ሃርነት ኤርትራ (ሻዕቢያ) የኢትዮጵያን ወይም የደርግን ሠራዊት የማሸነፍ ዕድሉ ብዙም የሚያስተማምን ስላልነበር፣ ጦርነቱ ረጅም ጊዜ ሲፈጅ ኮንፌዴሬሽንን እንደ አንድ አማራጭ በፖሊሲያቸው ውስጥ ያስገቡበት ሁኔታ ነበር፡፡ የጦርነቱ መልክ ከሽሬው ውጊያ በኋላ ስለተቀየረ ነበር ወደ ግልፅ የመገንጠል አቅጣጫ የገቡት፡፡ አፄ ኃ/ስላሴም ሆኑ የደርግ መንግስት ለድርድር ቀርበው ቢሆን ኖሮ ሻዕቢያ የኮንፌዴሬሽንን አማራጭ ሊቀበል የሚችልበት ዕድል ሠፊ ነበር፡፡ ሆኖም በተጠቀሰው ምክንያት አጀንዳው ተቀየረ፡፡

አሁን እንደገና ሃሳቡ ቀረበ ከተባለም ሌሎች ጉዳዮች መታየት አለባቸው፡፡ አንዳንዴ አቶ ኢሳይያስ የማያደርጉትን የመናገር ነገር ይታይባቸዋል፡፡ ሲያሻቸው ከኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል እንገዛለን ይላሉ፤ በሌላ ጊዜ ደግሞ ኢትዮጵያ ካልፈረሠች የኤርትራ የወደፊት ዕጣ ፈንታ ብሩህ አይሆንም ይላሉ፡፡ በሌላ መልኩ ደግሞ ከኢትዮጵያ ውጪ ኤርትራ ///// ናት ይላሉ፡፡ አሁን ወደተጠቀሰው ግንዛቤ መምጣታቸው ጥሩ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ትልቅ ሃገር ናት፡፡ ለትልቅ ሃገር ደግሞ ክብር ይገባል፡፡ ከዚህች ትልቅ ሃገር ጋር የተለያዩ ግንኙነቶችን ማጠናከር ለኤርትራ ጠቃሚ ነው፡፡ ቢዘገዩም ይሄን መገንዘባቸው በራሱ መልካም ነው፡፡

ከዚያ በፊት ግን በርካታ ነገሮች መደረግ ይኖርባቸዋል፡፡ ሁለቱ ሃገራት እርስ በርሳቸው የሚተነኳኮሡበትና የሚናቆሩበትን ማስቀረት፣ አንዳቸው የሌላኛውን ሃገር አማፂ ቡድን መደገፋቸውን ለማቆም ስምምነት ላይ መድረስ አለባቸው፡፡ በሁለቱ ሃገራት የመሬት ውዝግብ አለ፤ ኮንዴዴሬሽኑ በዋናው ጉዳይ መተማመን ላይ ከደረሱ በኋላ የሚመጣ ነው፡፡ ኤርትራ ለራሷም ለጎረቤቶቿም ስትል በወሳኝ መልኩ ትጥቅ ማስፈታት አለበት፡፡ ይሄ ባልሆነበት ሁኔታ ወደ ኮንዴዴሬሽኑ መግባት የሚሆን አይደለም፡፡ ከኢትዮጵያ ውጪ ኤርትራ ምን ልትሆን እንደምትችል መገመት አያዳግትም፡፡ ሃሳቡ መምጣቱ መልካም ነው ቢባልም የሚስተካከሉት ጉዳዮች ግን መቅደም ይኖርባቸዋል፡፡
Medhane Tadesse
ሎሚ፡- ኤርትራ የአፍሪካ ቀንድን እንደምታተራምስ የኢትዮጵያ መንግስት በተደጋጋሚ ገልጿል፤ እንደዚህ አይነት ድርጊት ውስጥ ለምን ገባች ይላሉ? የሚፈጠረውስ ትርምስ ራሷን አይጎዳትም?

ረ/ፕ መድኅኔ፡- ጎድቷታል እንጂ፡፡ የኤርትራ የውጪ ጉዳይ ፖሊሲ ጥላቻ እና በቀልን የሚያንጸባርቅ ነው፡፡ በኢትዮጵያ አንዳንድ ገጠራማ አካባቢዎች በደፈጣ ጥቃት የመገዳደል ባሕል አልተቀረፈም፤ የኤርትራ የውጪ ግንኙነትና የፀጥታ ፖሊሲም ከዚህ ጋር የሚመሳሰል እንጂ፣ ኃላፊነት የሚሠማውና ጥቅሙን ለማስከበር የሚንቀሳቀስ ሃገር የውጪ ፖሊሲ አይደለም፡፡ ቂም እና ጥላቻው የተፈጠረው ኤርትራ ለራሷ ከነበራት አስተሳሰብ የመነጨ ነው፡፡ ኤርትራ ስትፈጠር መሪዎቿ በአፍሪካ ቀንድና በቀጠናው ራሳቸውን አድራጊ ፈጣሪ አድርገው መመልከታቸው የፈጠረው ተጽዕኖ ነው፡፡ ደርግን በማሸነፋቸው ነፃ ሲወጡ ወታደራዊ የበላይነት መጨበጣቸውን እንደ ትልቅ እሴት ይዘው ነበር የተነሱት፡፡ ወታደራዊ የበላይነቱ ተሠሚነት፣ የኢኮኖሚ የበላይነትና የዲፕሎማሲ ድጋፍ ስለሚያመጣ የኤርትራን ተሰሚነት በዓለም ጭምር ከፍ ያደርግልናል ብለው አመኑ፡፡ ሆኖም ደርግን ያሸነፉት በኢትዮጵያውያን ትብብር እንጂ ለብቻቸው አልነበረም፡፡ ለራሳቸው የነበራቸው ገፅታ ግን የኤርትራን ፖሊሲና ወታደራዊ አቅጣጫ ለመወሰን የሚያበቃቸው አድርገው ወሰዱት፡፡ “አይበገሬነቱን፣ አሸናፊነቱን” የሰበኩለት ወታደራዊ አቅማቸው ግን በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ድምጥማጡ ጠፍቶ ዜሮ ገባ፡፡ ዋነኛ መመኪያቸውም በዚያ ጦርነት ተናደ፡፡ ይሕም በጣም ክፉኛ ጎዳቸው፡፡ አሁንም ግን ከዚያ መውጣት አልቻሉም፡፡ በዚህ የተነሳ የበቀልና የጥላቻ የውጪ ግንኙነት ፖሊሲን እያራመዱ ነው፤ በኢትዮ-ሶማሊያ ውጊያ የዚያድ ባሬ መንግስት የፈጠረው አይነት የበላይነት ስሜት ነበር ያደረባቸው፡፡ ይሕ አጀንዳቸውና ስነ ልቦናቸው ተሻሽሎ የሚታይ አይመስለኝም፡፡ ለዚህም ነው ከኢትዮጵያም ሆነ ከሌሎች ጎረቤት ሃገሮች ጋር ለመጋጨት የበቁት፡፡ የኤርትራ መሪዎች እድሜያቸው እየገፋ በመሆኑ አሁን መለወጥ ይችላሉ የሚሉ አሉ፡፡ ይለወጡ እንኳን ቢባል የፖለቲካ አደጋ አለው፡፡ በተለይ “ለህዝባዊ ግንባር ሃርነት ኤርትራ”፡፡

ኢሳይያስ አፈወርቂ ህዝቡን መሳሪያ በማስታጠቅና በወታደሩ በመተማመን ኤርትራ ውስጥ የዴሞክራሲን ለውጥ አፍነው ይዘዋል፡፡ የዴሞክራሲና የሕገ መንግስት ጥያቄ ሲነሳባቸው ይሕንን መግታት የቻሉት “ወረራ ላይ ነን፣ የኤርትራ ደሕንነት ለአደጋ ተጋልጧል፣ አሠብን ሊወስዱብን ነው፣ ነፃነታችንን ልናጣ ነው” የሚለውን ፕሮፓጋንዳ በመጠቀም ነው፡፡ ከጎረቤቶቻቸው ጋር ሠላም ከፈጠሩ በሃገራቸው የዴሞክራሲና የሕገ መንግስት ጥያቄ እንደሚነሳባቸው ያውቁታል፡፡ ይሕንን ደግሞ አይፈልጉትም፡፡ ከመጠን በላይ የታጠቀው የኤርትራ ሠራዊት ወደየቤቱ መመለስ አለበት፡፡ ያንን ለመመለስ አቅሙም የላቸውም፤ የፖለቲካም ስጋታቸው አይሎም በብሔራዊ ውትድርና እና በጦር ሠራዊት ውስጥ የከፋ ብዙ የሠብዓዊ መብት ጥሠት እንዲፈጸም ያደርጋሉ፡፡ ሕዝቡን እንደ ህብረተሠብ ገድለውታል፡፡ የኤርትራ ዴሞክራሲያዊ ለውጥ ጥያቄዎችን ማዘግየት የሚችሉት ደግሞ በዚህ በከበባና በጦርነት ስሜት ሲቀጥሉ ብቻ በመሆኑ በዚሁ ገፍተውበታል፡፡

ሎሚ፡- ከዕድሜ መግፋት ባሻገር የኢሳይያስ ጤንነት እንደተቃወሰ ይነገራል፡፡ እንዲያውም ስልጣናቸውን ለወታደራዊ መኮንኖች አለያም ለልጃቸው ለመስጠት እንዳሠቡም እየተገለጸ ነው፡፡ ከኢሳይያስ በኋላ ኤርትራ ምን ልትመስል ትችላለች?

ረ/ፕ መድኅኔ፡- እንደ ግብፅ እና ሌሎች የሠሜን አፍሪካ ሃገራት ጦር ሠራዊቱ ነው የተደራጀና የታጠቀውን ኃይል የያዘው፡፡ ሆኖም ግን ሠራዊቱንና ህዝቡን መነጠል አይቻልም፡፡ ምክንያቱም ሁሉም የሠራዊቱ አባል ከሕዝቡ የወጣና ህዝቡ ውስጥ ስለገባ ተቋሙን ብቻውን ነጥሎ ማቆም አይቻልም፡፡ ከአቶ ኢሳይያስ በኋላ ሠራዊቱ የኃይል የበላይነቱን ሊቆጣጠር ይችላል፡፡ ሆኖም ግን እርስ በርሱ የሚግባባ፣ መደበኛ አወቃቀር ያለው ወታደራዊ መንግስት መጠበቅ ይከብዳል፡፡ ከአቶ ኢሳይያስ በኋላ ቢያንስ አራት ከበዛም አምስት የጦር አበጋዞች የሚቆጣጠሩት፣ እርስ በርሱ የሚጋጭ የመሬትና የህዝብ ሽንሸና ይኖራል፡፡ አቶ ኢሳይያስም እያሉ ጄኔራሎች ናቸው ክልሎችን የሚቆጣጠሩትና የሚያስተዳድሩት፡፡ እነዚህ ጄኔራሎች እርስ በእርሳቸው አይስማሙም፤ በተጨማሪም በህገ ወጥና የወንጀል ዝንባሌ ውስጥ ከገቡ ቆይተዋል፡፡ ከአቶ ኢሳይያስ በኋላ እነዚህ እርስ በራሳቸው የማይስማሙ፣ የተለያዩ አካባቢዎችን የሚቆጣጠሩ፣ ህገወጥ ኢኮኖሚን የሚመሩ የጦር ጄኔራሎች የሚቆጣጠሩት ሃገር ስለሚሆን እንደ ሶማሊያ ባይሆን ተቀራራቢ ነገር የሚታይ ይመስለኛል፡፡ ጄኔራሎቹ እስከ ሲናይ በረሃ ድረስ ይሄዳሉ፡፡ ኤርትራዊያንን በ/// መልክ የሚቆጣጠሩ የጦር አበጋዞች ያሉበት ሃገር ነው፡፡ ወታደራዊ ተቋምን ይዘው የወንጀል ተግባር የሚያከናውኑ ናቸው፡፡ ስለዚህ አሁንም ወንጀለኞች ሆነው፣ ኢሳይያስ በማይኖርበት ጊዜ ደግሞ ነፃ ወንጀለኞች ይሆናሉ ማለት ነው፡፡

ሎሚ፡- ሽብርተኝነት የኢትዮጵያ ከፍተኛ ስጋት ስለመሆኑ ከመንግስት ወገን የሚሠጠውን መግለጫ እንዴት ተከታተሉት?

ረ/ፕ መድኅኔ፡- ሽብርተኝነት የሁሉም ሃገር ስጋት ነው፡፡ የኢትዮጵያ የተለየ አይደለም፡፡ ምናልባት ኢትዮጵያ ከነበራት ታሪካዊ ቦታ ለአካባቢው ካላት ተፅዕኖ እና የራሱዋን የሃይማኖት ጥንካሬዎች አንፃር ምናልባት አንዳንድ ፅንፈኛ ተመራማሪዎችና አስተማሪዎች አላማ ልትሆን ትችላለች፡፡ በአጠቃላይ ግን ኬንያ እንዳየነው ነው ለዚህ አይነት ነገር የተጋለጠች ነች፡፡ ኢትዮጵያ ጋር የተገናኘ የራሱ መልክ ቢኖረውም እንደዛም ሆኖ ግን ሽብርተኝነት ስንዋጋ መጀመሪያ ውስጣችንን ሠላም ፣ ዴሞክራሲ ቅድሚያ ሠጥተን ነው፡፡ ህዝቡን አሠባስቦ አስፈላጊውን ነፃነትና ፍትህ አስፍኖ፣ የዴሞክራሲ ሞዴ ሆኖ አጠቃላይ ህዝን አንቀሳቅሶ ፅንፈኞችን መዋጋት ደንብ ነው፡፡ ከዛ ውጭ እነዚህን ሁኔታዎች ሳያደርጉ ሽብርተኝነትን እንዋጋልን ማለት ጊዜያዊ ነው፡፡ እንጂ ዘላቂ አይደለም፡፡

ሎሚ፡- ከአመታት በፊት ከመንግስት ጋር (ከፌደራል ጉዳዮች) ጋር ስብሰባ ሲያደር የነበሩ የሙስሊም ማህበረሠብ ተወካዮች በፀረ- ሽብር በህጉ መከሠሳቸውን እንዴት ተከታተሉት?

ረ/ፕ መድኅኔ፡- እኔ ቀደም ብዬ ካልኩት ጋር ነው የማያይዘው የፀረ ሽብር ህግ የሃገሪቱ የውስጥ ሠላም አንድነት ዴሞክራሲ መንካት የፀረ ሽብር ህጉ የፖለቲካ ምህዳሩን ማጥበብ የለበትም፡፡ የፀረ ሽብር ህጉ የመናገር የመፃፍ የመንቀሳቀስ፣ የመጠይቅ መብቶችን መገደብ የለበትም ይሄ ከሆነ ለሌሎች የአፍሪካ ሃገሮች የፖለቲካ መጠቀሚያ ነው የሚሆነው ይሄ ላለመሆኑ እርግጠኝ መሆን አይቻልም፡፡ ስለዚህ ብዙ መሻሻል ያለባቸው ህጎች አሉ፡፡ ይቺ ሃር በሠላም፣ በአንድት፣ በዴሞክራሲ ጠንካራ ሆና የምትቀጥልበት መንገድ እነዚህ ሸብበው የያዙ ህጎችን ማፍረስና መለወጥ ይጠይቃል፡፡ ይሄ ለሃገሪቱ ለህዝብም ለመንግስትም አይጠቅምም ይቺ ሃገር የአካባቢውንና የአፍሪካ ጦርነትን ልትጎናፀፍ የምትችለው የራሱን ጤናማ የሆነ የፖለቲካ ሲስተም ልትገነባ ስትችል ብቻ ነው፡፡ በኢኮኖሚ በፓን አፍሪካኒዝም ብቻ መዝፈን አይደለም፡፡ ለኢትዮጵያ መሪነት ወሳኙ የዴሞክራሲ ተምሳሌት መሆን የዴሞክራሲ ተምሳሌት ለመሆን ሠላምን ለማስፈን ዋናው እንቅፋት እንደዚህ አይነት ህጎች ናቸው፡፡ እነዚህ ህጎች መቀየር አለባቸው፡፡ መንግስት ከዚህ ትንሽ አስተሳሰብ ወጥቶ ሠፋ ወዳለው መንገድ ለማሰብ እንደዚህ አይነት ነገሮችን እያሻሻሉ እንቅፋት የሆኑትን በሁደት እየጠረገ መሄድ አለበት፡፡

ሎሚ፡- የአሠብ ወደብ ለኢትዮጵያ የሚሠጥበት አለም አቀፍ ህግ እንዳለ የአለም አቀፍ ህግ ባለሞያዎች ይገልፃሉ፡፡ ገዥው ፓርቲ ደግሞ ይሄን ሃሳብ ለማንሳት የሚፈልግ አይመስልም፡፡ ኢትዮጵያ ወደብ ሊኖራት አይገባም? ከተቻለስ አሠብን የመመለስ እንቅስቃሴ ማድረግ ይቻላል?

ረ/ፕ መድኅኔ፡- ወደብ ሊኖራት አይገባም ብቻ ሳይሆንም ኢትዮጵያ የተወሰደባት ወደብ ማግኘት አለባት፡፡ ነበራት ወደም ብዬ ገልጨዋለሁ የአባ ተፋሠስ ጥያቄ የምስራቅ አፍሪካ የብሔርና ቋንቋዎች ስብጥር ጥያቄ፣ የኢትዮጵያ የወደብ መጠቀም የቀደብ ጥያቄ ዝም ብሎ አንድ መንግስት ስለመጣ የሚቀየር ነገር እንዳይመስልህ አይቀየርም ዘላለማዊ ነው ይሄ እስካልተፈታ ድረስ ሃሮች ሠላማዊ አይሆኑም አካባቢው ከግጭት አይወጣም፣እድገትም የለም፣ ለኢትዮጵያ ኮኖሚ ብቻ ሳይሆን ለአካባው ሠላምም ቢሆን የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ መመለስ አለበት፡፡ የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ በተለይ ቀይ ባህርን ከወሠድክ የኢትዮጵያን ነገስታት የኢትዮጵያን መሪዎች ጥያቄ ነው፡፡ የቀይ ባህር ጥያቄ የትግራ መሳፍንቶች እንጂ የኤርትራ መሳፍንቶች አያውቁትም ነበር፡፡ ስለሲህ አጀንዳው የኢትዮጵየን ጂኦግራፊው አሁን በወሠነላቸው ሁኔታ ባህሩን ተቆጣጠሩት ማለት የነሱ ሆኖ ይቀጥላል ማለት አይደለም፡፡ ሊሆን አይችልም፡፡ ይሄ ትልቅ ሃገር ነው፡፡ የባህር በር ጥያቄን ሳትመልስ የኢኮኖሚ እድገት፣ የኢኮኖሚ ትብብር፣አካባቢያዊ ትስስር፣ ሠላም አይገኝም፡፡ ኤርትራዊያንም መገንዘብ አለባቸው ይገነዘቡታል የሚል እነት አለኝ፡፡ አንድ ባህርን ለብቻህ ስለተቆጣጠርክ ጥቅም የለም፡፡ ሰላምም አያመጣም፣ እድገትም አያመጣም ፡፡ ኢትዮጵያ ካልተጠቀመችበት ለኤርትራዊያን ፍይዳ የለውም፣ የኢኮኖሚ ጠቀሜታውን አይደለም እየወራሁ ያለሁት ለኢትዮጵያ የባህር በር ተዘግቶባት ኤርትራ ለብቻዋ ልተበለፅግና፣ ሠላም ልታገኝ አትችል፡፡ ኃላፊነት የሚሠማው መንግስት እስካለ ድረስ ህዝቡ በዚህ ደረጃ የሚረዳው ነው፡፡ የሚመለስኝ ዝም ብሎ ሽርሽር ጥላቻና በቀል የፈጠፈው ስሜት ነው ጤናማነት ያለው አዕምሮ ለረጅም ጊዜ በትውዶች የሚመነዘር ፖሊሲ ሊሆን አይችልም፡፡

ሎሚ፡- በኢትዮጵያ በተለይ በመንግስት ባለስልጣናት ዘንድ የከፋ ደረጃ ላይ ደርሷል የሚባለው ሙስና እንዴት ተመለከቱት? ችግሩን ለማስወገድስ ምን መደረግ አለበት?

ረ/ፕ መድኅኔ፡- ያው እኔ ብዙ ጊዜ እዚህ ስለሌለሁ ይህንን ነገር አላውቀውም ግን ምንድነው አንድ የሚያስፈራኝ ነገር አለ፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ እኔ የማውቃቸው ብዙ የአፍሪካ ሃገሮች እንደ ናይጄሪያ፣ ኬንያ፣ ደቡብ አፍሪካ ሙስና ለረጅም ጊዜያት ከፍተኛ ደረጃ ላይ እንደነበር አውቃለሁ፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ግን በትንሽ ደረጃ ላይ ነበር፡፡ የእነርሱን የሙስናና የጉዳት ደረጃ ላይ ለመድረስ ግን የፈጀብን ጊዜ በጣም ፈጠነ፣ በዚህ ፍጥረነት ከተጓዝን ግን በጣም አደገኛ ነው፡፡ ናይጄሪያና ኬንያን የተመለከተ ኧረ የኢትዮጵያ የሙስና ደረጃ ኧረ በ7 አመት ከደረሰበት በጣም አደገኛ ነው እና እኛም ሃገር ያሠጋናል ማለት ነው፡፡ ከነእርሱ በላይ ሌላም ሙስና እንደስርዓት የበላይ ደረጃ ላይ እንዳይደርሰ መቆጣጠር ነው፡፡ እዚያ ደረጃ ላይ ከደረስን በጣም ከባድ ነው፡፡ የበላይነት ብቻ ሳይሆን ሙስና ከፖለቲካ ጋር ከተያያዘ ሌላው ሶስተኛ አደጋ ነው፡፡ አራተኛው ከተሣሠረም ከፍተኛ አደጋ ነው የሚሆነው፡፡ እነዚህ አራት ነገሮች ያሠጉኛል፡፡ ዝርዝሩን ግን አላውቀውም፡፡

Hiber Radio: ሳውዲ አረቢያ ለመኖሪያና ለስራ ፈቃድ እድሳት ተጨማሪ የሁለት ወር ጊዜ ሰጠች

$
0
0

የህብር ሬዲዮ ታህሳስ 27 ቀን 2006 ፕሮግራም

ለክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለብርሃነ ልደቱ አደረሳችሁ

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

<...ሰማያዊ ፓርቲ ሰላማዊ ተቃዋሚዎች ብቻ ሳይሆኑ ሰማያዊ ተጋዮች ናቸው... ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት እስካሁን በተጓዙባቸው ከተሞች ሁሉ አስቸጋሪ ጥያቄ አልተጠየቁም .....> አቶ ከባዱ በላቸው በሰሜን አሜሪካ የሰማያዊ ፓርቲ ድጋፍ ኮሚቴ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ለሕብር ሬዲዮ ከተናገሩት(ሙሉውን ያዳምጡ)

<... ኢትዮጵያዊያን ሳውዲ ባወጣችው የሁለት ወር የመኖሪያና የስራ ፈቃድ እድሳት እንዳይዘናጉ ..... በሳውዲ ያፈሩትን ንብረት አገራቸው ይዘው እንዲገቡ ሊፈቀድላቸው ይገባል ...> ከሳውዲ ያደረግነው ቃለመጠይቅ (ሙሉውን ያዳምጡ)

በኦባማ ኬር አንዱን ኢንሹራንሰ ከሌላው እንዴት ማበላለጥ እንችላለን? ምንን የሚአሟሉ ኢንሹራንሶችን ነው መግዛት ያለብን?

ዶ/ር ኤፍሬም መኮንን ለጥያቄዎቻችን የሰጡት ውይይት

የገና በዓልን አስመልክቶ ቃለ ምዕዳን ከብጹዕ አቡነ ዮሴፍ የኔቫዳና የአሪዞና ሊቀ ጳጳስ ጋር ቆይታ አድርገናል

ሌሎችም ዝግጅቶች

ዜናዎቻችን

- ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ በርካታ አፍሪካዊያን ስደተኞች ከመስጠም በጣሊያን በጠረፍ ጠባቂዎች ህይወታቸው ተረፈ

- የሙስሊሙ ሰላማዊ እንቅስቃሴ አራማጆች በእስር ላይ የሚያገኙ መሪዎቻቸውን ለመዘከር እየተንቀሳቀሱ መሆኑን ገለፁ

- አንዷለም አራጌ አዲሱ የአንድነት አመራር ለውጥ ለማምጣት እንዲችሉ መልእክት አስተላለፈ

- ከ63 ሚሊየን ሽልንግ በላይ የሚያወጣ አደንዛዥ እፅ በሆዱ ይዞ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ለመሄድ የሞከረው ተያዘ

- ሳውዲ አረቢያ ለመኖሪያና ለስራ ፈቃድ እድሳት ተጨማሪ የሁለት ወር ጊዜ ሰጠች

- የቀድሞው ፕሬዝዳንትና ልጃቸው ለደላላ ባለመክፈላቸው ተከሰሱ

ሌሎችም ዜናዎች አሉን

ዘመንን ለማሰር (በልጅግ ዓሊ)

$
0
0

Ethiopian Flag

ይህን 77 እስሩት በገመድ፣

ወደ 78 እንዳይረማመድ።

ይህች አነስተኛ ስንኝ የሰማኋት እንደ ሃገራቸን አቆጣጠር በ1978 ዓ.ም  ላይ ነበር። መቼም የማይረሳ የለም አሥረኛው የአብዮት በዓልም ተረሳ። ያኔ እነ “ጓድ መንግሥቱ“ ድርቁን ደብቀው አሥረኛውን የሥልጣን ዘመናቸውን ለማክበር ውስኪ በመርከብ ያስገቡበትና የተራጩበት ዘመን ነበር። ያኔ እነ “ብጻይ መለስ“ በድርቁ ስም በተገኘው ገንዘብ ጠብመንጃ የገዙበት ዘመን ነበር። የማይረሳ የለም በዚያ ዘመን በድርቅ ያለቀው ወገናችንም ተረሳ። የሕዝብ ገንዘብ ለውስኪና ለጠብመንጃ ያዋሉት ትንሽ ቆይተው ስልጣን ተቀያየሩ። 1977 ማሰር አቅቶን 1983 ከድጡ ወደ ማጡ አነጎደን።

በደርግ ዘመን የደረሰውን ድርቅ ለመከላከል በሰሜን የሚኖሩትን ዜጎቻችንን(ከሰሜን እየታፈሱ የመጡት ዜጎቻችን በድርቁ ምክንያት ይሁን በሌላ ወደፊት አዋቂዎች ይጽፉት ይሆናል)  ወደ ምዕራብ ማስፈር ተጀምሮ ነበር። ማስፈሩ ሁለት መልክ ነበረው። ሠፈራ የሚባለው ሰው ባልሰፈረበት አካባቢ ወስዶ ማስፈር ሲሆን ስግሰጋ የሚባለው ደግሞ በሕዝብ ቁጥር የሳሱትን ወረዳዎች በሰፋሪዎች መሰግሰግ ነበር። ሠፈራና ስግሰጋ የራሱ የሆነ በሰፊው የሚተረክለት ታሪክ አለው።

ከሰሜን ኢትዮጵያ ለሠፈራና ለስግሰጋ ወደ ኢሉባቡር የመጡ አንድ ሽማግሌ ገበሬ ነበሩ ይህችን ከላይ የሰፈረችውን ስንኝ ለመጀመሪያ ጊዜ  የነገሩኝ። ይህች ስንኝ ሁለት ትርጉም ይዛለች። አንደኛው 1978 ከ 1977 ይብሳልና አይሸጋገር የሚል ሲሆን ሁለተኛው 1977 ያየነው ችግር ወደ 1978 እንዳያልፍ የሚል ነው። ሽማግሌው እንዳስረዱኝ የመጀመሪው ነው ትክክሉ።   ከጊዜ በኋላም አንድ የምቀርበው የወረኢሉ ሰው ስለነ መንግሥቴ ደፋር ፣ ስለነ ብሩኬ ስንጫወት  ይህችን ግጥም አስተወሰኝና ማስታወሻ ላይ ጽፌ ይዣት ቆይቼ ለዛሬው መነሻ ሆነችኝ። (መንግሥቴ ደፋርና ብሩኬ በወረኢሉና ሰሜን ሸዋ ሃገር ያንቀጠቀጡ “ሽፍቶች“ ነበሩ። ቀን ሲሞላ የሚጻፍ ታላቅ ታሪክ አላቸው።)

ድርቅ ከሳይንስ በተቃረነ መልኩ በአገራቸን ሁል ጊዜ ዱብ እዳ ነው የሚሆነው። 1966 የደረሰውም ይሁን 1977 የተደገመው ድርቅ እንደው ሳንሰማው ነው በድንገት ያየነው። የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ 80ኛ ዓመት በተከበረ ማግሥት ድርቅ “ሳይታሰብ“ መጣ። ደርግም ሕዝብ ሲራብ የንጉሡ ባለሥልጣናት  ኬክ ይበሉ ነበር በማለት ቅስቀሳ አድርጎ ነበር ወደ ስልጣን የመጣው። ደርግ ይባስ ብሎ  የአሥረኛውን አብዮት በዓል እስከሚያልፍ ድርቁን ደብቆ፣ በዓሉ  ባለቀ ማግስት ድርቅ እንደ ዱብ እዳ፤  እንደ ተምች ከሰማይ እንደወደቀ ነገረን። በ1966 ዓ.ም. እንደ ሃገራችን አቆጣጠር የደረሰው ድርቅ  እንደ ወንጀል ተቆጥሮ 60ዎቹን ባለሥልጣናት የገደለው መንግሥቱ በእሱ ዘመን ለተደበቀው ድርቅ ራሱን ሳይገድል መቅረቱ ፍትህ አልባነት ነው ማለት ይቻል ይሆን?

በዛ ዘመን ካለ መንግሥቱ አመራር ምንም ነገር የሚሆን አልነበረምና በዓሉ ካለቀ በኋላ ሁላችንም ስለድርቁ ተነግሮን ዝግጅት እንድናደርግ ታዘዝን። ከግብርና ሚኒስቴር እስከ ታች እስከ ወረዳ ድረስ  ከግብርና ጋር ግንኙነት ያለን በሙሉ ክተቱ ተባልን። የኢሠፓ አባላት መሪዎቻችን ሆነው እኛ የእርሻ ኤክስፐርቶቹ ተመሪ ሆነን ሥራውን ጀመርን። ቀርፋፋዋ ኢሊባቡር ከአዝጋሚነት ወጥታ እንቅስቃሴ በእንቅስቃሴ ሆነች። በየመሥሪያ ቤቱ ያሉ መኪናዎች ከእኛ ተወስደው ለኢሠፓዎቹ መጓጓዣ ሆኑ። እኛ ወደ ሞተር ባይስክልና ወደ ትራክተር ተዘዋወርን።

በዚያ ወቅት ኢሊባቡር ነበርኩና እኔም ለዚህ “ሳይታሰብ በድንገት“ ከሰማይ የመጣብንን እዳ ለመቋቋም በየቦታው መራወጥ ጀመርን።  በጋምቤላ ለሰፋሪዎች ቦታ መዘጋጀት ጀመረ። በሌላ በኩል ደግሞ በሕዝብ ቁጥር የሳሱ የገበሬ ማህበራት ውስጥ ከሰፋሪዎቹ ውስጥ እየተወሰዱ ይሰገሰጉ ጀመር። እኔ ጎሬ አካባቢ በሚገኝ ወረዳ ለሚሰገሰጉት ገበሬዎች ጎጆ ለመስራት ተመደብኩ። ዛሬ ያገኘሁት ትንሽ የየቀኑን ሁኔታ የምዘግብበት ማስታወሻ አንዲት ጎሬ ለምትኖር አንዲት ወይዘሪት የተጻፈ ደብደቤ ላይ የደብዳቤውን ብዙው ዝባዝብኬ ተቀንሶለት እንዲህ የሚል የተጠቀሰ ጉዳይ ይገኝበታል። ።

 

 ውዷ

ጓጆ ቤት መሥራት ቀርቶ ጎጆ ቤት ውስጥ አድሬ አላውቅም። ይህ የምሰራው ጎጆ (ጎጆ ከተባለ) የሚገርም ነው። ከላይ ሳር ጣል ተደርጎ ይከደንና ግንድግዳው በዘንባባ ይሸፈናል። የኛን አዛዥ አላፊ ካድሬዎችን ለመሆኑ ይህ የምንሰራው ቤት ከምን ይከላከላል? ብዬ ጠይቄ ነበር። የተሰጠኝ መልስ ለጊዜው ማረፊያ ካገኙ  ሰፋሪዎቹ ሲመጡ ያሻሽሉታል የሚል ነበር። በድርቅ የተጎዳ ሰው እውን ቤት መስራት ይችል ይሆን? የሚገርም ነው። ለማንኛውም ሥራውን እያጣደፍነው ነው። ስራው አልቆ ጎሬ ለመምጣት ቸኩያለሁ።

ይላል። በዛ ወቅት የነበረውን ጥድፊያ አጉልቶ ነው። ከሁሉ የሚገርመው በትንሽ ቀን ያንን ሁሉ ሕዝብ ማጓጓዝ እንዴት አስከፊ ነበር። በችኮላውና በሕዝብ ብዛቱ ምክንያት ከአንድ አውቶቡስ ውስጥ የነበሩ ቤተሰቦች በምደባ ይለያዩና አንዱ ጎሬ ሌላው ጋምቤላ ይደርሰው ነበር። ማንም ጥንቃቄ የሚያደርግ አልነበረም። ብዙ ቤተሰቦች ሳይገኛኑ ይቀሩ ነበር። ልጆች በረሃብም ይሆን በጉዞው አድካሚነት ይረግፉ ነበር። ይህንን ያልተጠና ሰፈራ የመንግሥቱ መመሪያ ነውና ማንም ባለሥልጣን፣ ማንም የእርሻ ኤክስፐርት ሊቃወም አልሞከረም።

ሰፋሪዎቹ መጥተው በሰራው ቤት ከተመደቡ በኋላ እየተመላለስኩ እጠይቃቸው ነበር። ይህንን ግዜ ነው አንድ ሽማግሌ ስለዚህ አባባል ያጫወቱኝ። አዎ ገበሬዎቹ  ነገሩ ገብቷቸው ኑሮ በ1978 ከ 1977 እንደሚብስ ገምተው ነበር።

የፈረንጆቹ ዓመት ከ2013 ወደ 2014 ሲቀየር የተመኘሁት ይህንን ግጥም ነበር። የሃገራችንን ጉዳይ በጥሞና ሳስበው፣ በየቀኑ እየባሰ የሄደውን የወያኔን ግፍ ስንገምተው፣ የደሃውና የሃብታሙ ልዩነት እየገፋ መምጣቱን ስመለከተው፣ ችግርን በመሸሽ በየበርሃው በየባሕሩ የሚያልቀው ወጣት ዜጎችቻን ቁጥር መጨመርን ሳሰላው፣ በእየእስር ቤቱ የሚማቁትን ዜጎቻችንን ሳስታውሳቸው፣ ለሃያ ዓመት  በነጃዋር፣ በነ ተሰፋዬ ግብረ አብ፣ በእነ ብርሃኑ ዳምጤ መሰሎቹ የተዘራው የዘር ፖለቲካ ስሞኑን የደረሰበትን ደረጃ በጣም ያሳስበኛል።

ሃገራችን አንድነቷን ጠብቃ የመኖሩዋ ሁኔታ ጥርጣሬ ውስጥ ሲገባ፣  ጠንካራ የሆነ ተቃዋሚ ለመፍጠር ያለውን ችግር ስንገመግመው፣  በትግሉ ውስጥ ተስፋ የሚሰጥ ሁኔታ ሳጣበት 2014 ከ 2013፣ የሚብስ መሆኑን ስንረዳው ያኔ እንደ ገበሬዎቹ፡ -

ይህን 13ትን እሰሩት በገመድ

ወደ 14ቱ እንዳይረማመድ ።

ለማለት ተገደድኩ።

የሃገራችንን ሁኔታ ልብ ብለን ስንመከተው ይህ ዘመን ከመቼውን ጊዜ ይበልጥ የሚያስፈራ ሆኖ ይታሰበኛል። በተለይ 2013 መጨረሻ ላይ የተመለከትነው ሁኔታ ስንገመግመው፣ በተለይ እነዚህ በዘር የተለከፉ አጋንቶችን እዚህ ማን አደረሳቸው የሚለውን ስንመለከተው፣ በወያኔ ቀጥሎ ራሳችንን እንድንገመግም ይጠይቀናል። ሞኝ ብቻ ነው ቤቱ ሲቃጠል የሚስቀው። ለሚቃጠለው ቤቱ ቤንዚል የሚያቀብለው። ሞኝ ብቻ ነው ፎቅንና ጥልፍልፍ መንገድን ተመልክቶ እየፈረሰ ያለውን የሃገሩን አንድነት የሚዘነጋው። ሞኝ ብቻ ነው ሃገርን ለሚፈርሱ መድረክ እየሰጠ ሃገሩን የሚያፈርሰው። የአባትህ ቤት ሲዘረፍ አብረህ ዝረፍ የሚለው በሃገር አይሰራም።

የዘር ፖለቲካ የደረሰበትን ደረጃ ያልተረዱ ብዙ ናቸው። ክምር ፎቅ፣ ጥልፍፍ መንገድ፣ ዳንኪራ መደለቂያ ቡና ቤት ብቻ ለሃገር አንድነት የሚበቃ የሚመስላቸው የዋሆች እየበዙ ነው።  ዛሬ በድሎት የሚንደላቀቁ ዘመናዮች በየጥጉ በረሃብና በበሽታ የሚልቁት ዜጎቻችንን እንዳያዩ የየክለቡ አብለጭላጭ መብራት ዓይናቸውን ሽብቧቸዋል። በዓለም ታሪክ በቅርብ እንኳን ስንት የሚያምሩ ፎቆች በዘር ክፍፍል እንደፈረሱ የማይረዱ አሉ።ትንሽ ዘርን ተመርኩዛ የምትንሳ ሁኔታ የእርስ በእርስ መተላለቅን  እንደምታስከትል፣ የተከመሩ ፎቆችም ሆነ ፣ጥልፍለፍ መንገዶች በቀናት ሊፈርሱ እንደሚችሉ ያልተረዱ የዋሆች የአንድነት ኃይሎችን እየተዋጉ ጭንብል ላጠለቁ ዘረኞች መድረክ ፣ እውቅና እየሰጡ እንዳሉ ሊረዱት ይገባል።

ከወያኔ ተፋተናል ያሉን ሁሉ መለያየታቸው መልካም ነው። ለምን ከወያኔ እንደተፋቱ አሳማኝ ምክንያት ሳያቀርቡ ሰው እንደጠፋ በየቦታው የፖለቲካ ተንታኝ . . . የኮሚቴ አባል . . .  የመድረክ የክብር እንግዳ፣ . . .  ወዘተ. እያደረጉ መካብ በተሰፋዬ ገብረአብም ይሁን በጃዋር የከሸፈ ነው። ነገም በብርሃኑ ዳምጤ ቢደገም የሚያስደንቅ አይደለም። ከወያኔ ወጥተው ተቃዋሚ ሆንን ሲሉ ወያኔ ውስጥ ሆነው የሠሩትን ጥፋት ለሕዝብ እንኳን ይቅርታ እንዲጠይቁ አይደረግም። ብቻ የሰሞኑን ፖለቲካችንን ይደግፉልን እንጂ በሃገር ላይ የሚያመጡትን ጥፋት አይታየንም።

ለሃገራቸው የሠሩ፣ የሞቱ እየተወገዙ፣ ሃገራቸውን የገደሉ ወደፊትም ሊገድሉ የተዘጋጁ ትላንት የወያኔ አሽከር የነበሩ፣ አሁን ተቃዋሚ ነን የሚሉ  እነ ጃዋር፣ እነ ብርሃኑ ዳምጤ (ደቡር) ጀግና ተብለው እየተዘፈነላቸው ነው። ሲሞቅ ኦ.ፒ. ዲ. ኦ.(OPDO) ሲቀዘቅዝ ተቃዋሚ፣ ትላንት የወያኔን  ቀንደኛ ደጋፊ ሥልጣን ሲከለከል ተቃዋሚ መሆን የዘመኑ የፖለቲካ ገጽታ ነው።

እንደነ ጃዋር አይነት የዘር ፖለቲከኞች አቋም በቀየሩ ቁጥር አብረን ዳንኪራ የምንረግጠው ምን እንባል? አንድ ሰሞን ፓልቶኩም ፣ ራዲዮኑም ጃዋር ፣ ጃዋርና ሲልና የፖለቲካ ተንታኝ የሚል አዲስ ስም ተሰጥቶት በባልና ሚስት ጥል ላይ እንኳን ሳይቀር(እንደ ቀልድ ውሰዷት) ሃሳብ እንዲሰጥ ሲጠየቅ እንዴት ያላገባ ሰው የትዳር ሊቅ ሊባል ይቻላል የሚል ተቃውሞዬን አቅርቤ ነበር። ይኸው ዛሬ ጃዋርን ተቀምጠቀው የሰቀሉ  ካስቀመጡበት ቆመው ማውረድ አቃታቸው። ሕዝብን የሚከፋፍለውን ጥያቄ ይዞ ለኢትዮጵያ የሚመኝላትን የእርስ በእርስ ጦርነቱን ይቀሰቅስ ጀመር። ጃዋር ትንሽ ሲፍቁት ኦፒዲኦ(OPDO)፣ በጣም ከፋቁት ወያኔ(TPLF) መሆኑን አጥተነው ነው። አይመስለኝም ለሰሞነኛ ፖለቲካ ከጠቀመን ስለሃገራቸን ግድ ስለማይኖረን ይመስለኛል።

እነ ጃዋር  እኛን የሞቀው ላይ የምንጣደውን ሲፈለጉ  ደጋፊያቸው አድርገው ያጫጩናል፣ ሲደብራቸው ደግሞ የዘር ፖለቲካቸውን አምጥተው ያምሱናል። ዛሬ ወያኔ ፣ ነገ ተቃዋሚ ፣ ተነገ ወዲያ ደግሞ ተመልሰው ወያኔ እንደፈለጉ መሆን ይችላሉ። በተቃዋሚው መድረክ ላይ ከወያኔ ለተመለሱት ሁሉ እግራቸው ሥር እንድንነጠፍ የሚፈልጉ ብዙ ናቸው።

እድሜ “ለነጻ ሜዲያ ጋዜጠኞች“፣ እድሜ ለኛ በሞቀበት ለምንጣደው፣ ሃገራችንን ሊበትኗት ሲራወጡ አብረን  ልንበትናት እየሮጥን ነው። እንግዲህ ፍላጎታችን ይህ ከሆነ አሁን የምናየው ደስ ሊለን ይገባል።  ስለ ኦሮሞ ሕዝብ ስንት አንጋፋ አሮሞዎች እያሉ ይህ ስንዝሮ ፖለቲከኛ ጃዋር  ይጋበዛል። ስለ እስልምና ስንት የተማሩ የበሰሉ ሊቀ ሊቃውንቶች እያሉ ጃዋር ሁሉም ቦታ የሃይማኖት ተንታኝ ሆኖ ይቀርባል። ጥፋቱ ጃዋር ጋር አይደለም ጥፋቱ ለሃገራቸን አንድነት እንዋጋለን ብለን ግን ለክፍፍል በምንሰራው ላይ ነው። እነ ጃዋር በኛው መድረክ፣ በኛው ገንዘብ አላማቸውን ሲስፈጽሙ እንደሞኝ የሚቃጠለውን ቤታችንን እያየን እንስቃለን። በነጻ ፕረስ ስም እውቅና እንሰጣለን።

ትላንት የወያኔ ደጋፊ ሆኖ ዛሬ ከወያኔ ተጣላሁ ካለን ምራን ብለን እግሩ ሥር እንነጠፋለን። ይህ ደግሞ ለምዶብናል። 1997 ምርጫ ዋና የወያኔ አቀንቃኝ የነበረውና የነ ሽብሬን መገደል ትክክል ነው ብሎ ሲያቀነቅን የነበረው፣ አሁን  በግል ጥቅም ምክንያት ከወያኔ የተጣላው ብርሃኑ ዳምጤ (ደቡር፣ አባ መላ) ዛሬ በየሃገሩ የክብር እንግዳ፣ በመገናኛ ዘዴው ተንታኝ ከሆነ ሰነበተ። ለአንዲት የሰሙኑ የፖለቲካ ጥቅም ሲባል ብርሃኑ ደቡርን እላይ የሰቀላችሁት በኋላ እንደለመደው ሲክዳችሁ ስትንጫጩ መስማታችን አይቀርም። ትንቢት እንዳይመስላችሁ ደቡርን በደንብ አድርገን እናቀውቀዋለን። ቆዳችሁን ገፎ ይሸጠዋል፣ ደቡር ሃገሩን አይደለም እናቱንም ቢሆን ይደልላል። አታውቁት እንደሆን መርካቶ ላይ ሄዳችሁ የተሰራውን ግፍ ጠይቁ። እንኳን የቀይ ሽብሩን ፣ እነ ሽብሬን ረስተን የለም እንዴ !!  ምን ይደንቃል።

እድሜ ለኛ ብጻይ ብርሃኑ ዳምጤ ከወያኔ ጋር የምናደርገውን ትግል ይምሩልን ብለን  . . .  ሁሉንም እናስረክበው  . . .  እውነት፣ እውነት እላችኋለሁ ብርሃኑ ዳምጤ ደቡር ይክደናል። ከዛም አሁን ከሰማይ ሰማየት  የሰቀልነው እንደ ድመት እግሩ ስር እናለቅሳለን። ብርሃኑ ደቡር ቆዳችንን ገፎ ሥጋችንን ለአሞራ ይበትነዋል። በጨረታው አይገደድም ለበለጠው ይሸጠናል። ኢሕአፓ ነው ፣ ግንቦት 7 ነው ፣ መኢአድ ነው . . . እያለ እንደፈለገ ይከፍለናል። ምን እንሆናል ለመሸጥ የተዘጋጀን በጎች አይደለንም እንዴ? በሉ የዘመኑ ፖለቲከኞች ከጃዋር ፣ ከብርሃኑ ዳምጤ ጥፋት መፈለግ ትታችሁ ከነቴዲ አፍሮ ጥፈት ፈልጉ። መቼም፣ የምታሸንፉት አይደለም የምታጠቁ ወያኔን ከመቃወም ቴዲን መስደብ ይሻላል። ጃዋርን ከመቃወም ቴዲን መስደብ ለዝሙት ቱሪስቶች ፣ ለዘመኑ ኢንቨስተሮች ፣ የደደቦች ሸንጎ አባሎች የሚሻል ነው ።

2013 ተቀይሮ 2014 ሲገባ ተስፋ የሚሰጥ ራዕይ ያለው ፖለቲካ እያከተመ እንጂ እያበበ መሆኑ  አይታይም። ጠብ አጫሪ፣ እኔ እኔ በሚል የተቃኘ የግለሰቦች ፍላጎት የሕዝብን ራዕይ ሸፍኖ ጎልቶ ወጥቶ ስንመለከት የዴሞክራሲ ትግል የመጨረሻው ቀን ርቆ ይታየናል። ከነገ ደህና የሚጠብቅ ትንሽ ነው።

ዓመትን ማሰር ቢቻል የምናስራቸው ዓመታት ብዙ ይሆኑ ነበር። ከዛ በፊት ግን ሕዝብ ለክፍፍል የሚጠሩ ምክንያቶችና እነዚህ አጀንዳዎች ለግል ጥቅማቸው ከፍ የሚደርጉ ፖለቲከኞች ከፖለቲካው መድረክ ሊሸበቡ ይገባል። እነ ተስፋዬ ግብረ እባብ፣  እነ ጃዋር ፣  እነ ብርሃኑ ዳምጤ . . .  ነገም ብዙዎች ይመጣሉ። ተቃዋሚ መሆናቸውን መከልከል አይገባም ምሩን ማለት ግን ደደብነት ነው።

ወያኔዎች ሃገራችንን ለማፍረስ የማይጠቀሙበት መንገድ የለም። በማካከላችን አንቀላፊዎች(Sleepers) ያስቀምጡብናል። ቀኑ ሲደርስ ያነቋቸዋል። ሰሞኑን በእነ ጃዋር ያየነው ይህንን ነው።  እነ ጀዋር ሲነቃባቸው ሌሎች ይላካሉ። እኛም ምሩን ብለን እንቀበላቸዋለን። ለወራት ካመሱን በኋላ ያደረሱትን ጉዳት አድርሰው ተልዕኳቸው ተፈጽሟልና  ይሸሸጋሉ። ሌሎች በምትካቸው ይመደቡልናል . . .  እንዲህ እንዲህ እያልን ዓመት እንቆጥራለን . . .። መቼ ይሆን እያየን አለማየታችንን የምንገነዘበው? መቼ ይሆን ከተኛንበት የቁም እንቅልፍ የምንነቃው? መቼ ነው ሰው ነኝ ወይስ በሰው ምስል የቆምኩ “ሰው“ ብለን ራሳችንን የምንመረመረው። ብልህን አንዴ ያሞኙታል፤ ሞኝን ግን ዘንተለት እንዲሉ ነውና ከእንቅልፋችን እንንቃ።

በአዲሱ የፈረንጆች ዓመት ስለ ሃገራችን አንድነት የሚያስቡ ሁሉ በሰላም ይክረሙ!

ለንደን  ታህሳስ 2006

 

Beljig.ali@gmail.com

 


ኮካኮላ የቴዲ አፍሮ ውል እንዲሰርዝ ዘመቻ ተጀመረ (ከክንፉ አሰፋ) ጋዜጠኛ

$
0
0

በ 2014 ብራዚል ለሚካሄደው የአለም ዋንጫ ላይ ቴዲ አፍሮ የክብር እንግዳ እንዳይሆን አዲስ ዘመቻ በእነ ጃዋር መሃመድ መጀመሩ ተሰማ።

 በዓለም ዙርያ ያሉ ኢትዮጵያውያን በሳውዲ ለተፈናቀሉ ወገኖች እየተረባረቡ ባሉበት በዚህ ፈታኝ ወቅት፤  ጃዋር እና ሜንጫዎቹ ጸረ-ኢትዮጵያዊነት ዘመቻቸውን በስፋት ተያይዘውታል።  በዛሬው እለት ከአዲስ አበባ በደረሰን ዜና መሰረት ኮካኮላ የቴዲ አፍሮን የአለም ስፖርት ፌዴሬሽን (ፊፋ) ስፖንሰርነት እንዲያነሳ ጠይቀዋል።  አዲስ አድማ ለመጀመርም ዝግጅታቸውን አጠናቀዋል። በ 2014 ብራዚል ለሚካሄደው የአለም እግር ኳስ ዋንጫ አፍሪካን ወክሎ እንዲገኝ ኮካኮላ ቴዲን የመረጠው መሆኑ ይታወሳል። የአለም ስፖርት ፌዴሬሽን (ፊፋ) ወጣቱ ቴዲ አፍሮ አፍሪካን እንዲወክል መምረጡ ዘረኞቹን አስቆጥቶ እንደነበር የሚታወስ ነው።

ቴዲ አፍሮ በአለም መድረክ ላይ የሚያቀርበው ኢትዮጵያዊ የሙዚቃ ቃና ሀገራችንን እና መላው አፍሪካን የሚያስጠራ ነው።   የሄነከኑ አድማ በኦህዴድ ብርቱ ጥረት የተሳካላቸው እነኚህ ባለ አድማዎች፣ ሰሞኑን የደስታ መግለጫቸውን በየድረ-ገጾቻቸው ላይ  እየተለዋወጡ እንደሆነ ተገልጿል። ሄኒከን ኮንሰርቱን የሰረዘው ከኦህዴድበተላለፈ ቀጭን ትእዛዝ ስለመሆኑ ማስረጃው አሉ።

እነ ጃዋር በዚህ አላበቁም። በዲሴምበር 8፤ 2013 በተላለፈ የአቶ ቡልቻ ደመቅሳ እና ሌሎች ምሁራን ቃለ-ምልልስ ምክንያት የጀርመኑ (ዶቸ ቨለ) የአማርኛ ድምጽ ሬዲዮ ጋዜጠኛ ከስራ እንዲነሳም ከአቤቱታ ጋር ቀጭን ትእዛዝ ለቦርዱ አስተላልፎ ነበር።  የዶቸ ቨለ ቦርድ ላይ ኦህዴድ ተጽእኖ ስለሌለው ይህ ዘማቻ ሊሳካ አልቻለም።

tedddyየኮካኮላው ዘመቻ የተነጣጠረው በቴዲ አፍሮ ላይ ሳይሆን በአኢትዮጵያዊነት ላይ ስለሆነ በአለም ዙርያ ያሉ ኢትዮጵያውያን ዝምታውን በመስበር በነዚህ ሰዎች ላይ የሶሻል ሚድያ ዘመቻ መክፈት ይገባቸዋል።

 

ፓትርያርክ አቡነ መርቆሬዎስ የጌታን ልደት በማስመልከት ቃለ ምዕዳን ሰጡ

$
0
0

ከፓትርያርል አቡነ መርቆሬዎስ የጌታን ልደት በማስመልከት ቃለ ምዕዳን ሰጡ (በድምጽና በጽሁፍ)
አባ መርቆሬዎስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳስ ዘኢትዮጵያ
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤ አሜን!!

“ስብሃት ለእግዚአብሔር በሰማያት ወ ሰላም በምድር ሥምረቱ ለሰብእ”
“ክብር ለእግዚአብሔር በሰማያት፤ ሰላምም በምድር፤ ለሰውም በጎ ፈቃድ ይሁን።” (ሉቃ 2:14)

Read Full Story in PDF/ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

ቃለምዕዳኑን በድምጽ ለማድመጥ ይኸው

Health: በእንቅልፍ ልቤ ከብልቴ የሚወጣውን ፈሳሽ እንዴት መቆጣጠር እችላለሁ?

$
0
0

(በዘ-ሐበሻ ጋዜጣ ቁጥር 51 ላይ ታትሞ የወጣ)
ጂቲ እባላለሁ፡፡ የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ነኝ፡፡ ዋነኛ ችግሬ ምን መሰላችሁ? በእንቅልፍ ልቤ በተደጋጋሚ የዘር ፍሬዬ እየፈሰሰ ተቸግሬያለሁ፡፡ ይህ ችግር በተደጋጋሚ መከሰት ከጀመረ አንድ ዓመት ይሆነኛል፡፡ በሳምንት ቢያንስ ሶስት ቀን ይህ ችግር ይከሰትብኛል፡፡ ሁሌም ከእንቅልፌ ስነቃ በተደጋጋሚ የሌሊት ልብሴ፣ የውስጥ ሱሪዬ እና አንሶላዬ ረጥቦ እና አልጋዬ ባልተለመደ ጠረን ታውዶ አገኘዋለሁ፡፡ ይህ ነገር ደግሞ ለሀፍረት ስሜት ያጋልጠኛል፡፡ ለራስ ምታት ህመምም ይዳርገኛል፡፡ ገና ተማሪ ስሆንኩ እስካሁን የሴት ጓደኛ የለኝም፡፡ ወሲብም ፈፅሜ አላውቅም፡፡ አልፎ አልፎ ግን ማስተርቤት አደርጋለሁ፡፡ ስለዚህ ውድ የዘ-ሃበሻ አዘጋጅ ይሄ ነገር የሚከሰትብኝ ለምንድን ነው? ወሲብ ብጀምርስ ይህ ነገር ይጠፋል? ከዚህ ነገር መላቀቅ የምችለው እንዴት ነው? እባክህ ለችግሬ መልስ ፈልግልኝ፡፡ ጂቲ ነኝ
ask your doctor
የዶ/ር ዓብይ ዓይናለም ምላሽ፡- በተፈጠረብህ ነገር ብዙ አትደናገጥ፡፡ ምክንያቱም ይህ ችግር ያንተ ብቻ ሳይሆን የብዙ ወንድ እና ሴት ወጣቶች እንዲሁም ጎልማሶች ችግር ነው፡፡ እንደ የተለየ ጤና ችግር በመቁጠርም አትረበሽ፡፡
በእንግሊዝኛ ኖክቱርናል ኢሚሽን (Nocturnal Emission) በመባል የሚታወቀው በሌሊት የሚከሰት የዘር ፍሬ በዘፈቀደ መፍሰስ በአብዛኛው በወጣትነት ዕድሜ ላይ በሰውነት ውስጥ የሚከሰት ባይኮሎጂካል እና የሆርሞን ለውጦችን ተከትሎ በስፋት የሚከሰት ጤናማ የጉርምስና ምልክት ነው፡፡ በተደጋጋሚ የሚከሰት ከሆነ ግን ተጨማሪ ምርመራ ለማድረግ እንገደዳለን፡፡ ነገር ግን ይህ ችግር በአነስተኛ መጠንም ቢሆን በጎልማሶች እና በአረጋዊያን ላይም ሊከሰት ይችላል፡፡ ጥናቶች እንደሚጠቁሙት በእንቅልፍ ልብ የዘር ፍሬ የሚፈሰው በሁለት መልኩ ነው፡፡ የመጀመሪያው እና በአብዛኛው የሚከሰተው በእንቅልፍ ልብ የብልት መወጠርን (መቆምን) ተከትሎ ነው፡፡ ይህ ነገር በአብዛኛው ወሲባዊ ህልሞችን በመመልከት እና በወሲባዊ ሀሳብ መወጠርን ተከትሎ የሚከሰት ነው፡፡ በአንዳንድ ሰዎች ላይ ደግሞ ብልት ሳይወጠርም የዘር ፍሬ ሊፈስ ይችላል፡፡ ይህ ነገር ደግሞ ከወሲባዊ ሀሳቦች ጋር የተገናኘ አይደለም፡፡ ስለዚህ የአንተ ችግር ከሁለቱ በየትኛው ውስጥ እንደሚወድቅ ለራስህ መልስ ስጥ፡፡
ጥናቶች እንደሚያሳዩት በወጣትነት የዕድሜ ክልል ውስጥ ከሚገኙ ወንዶች 84 በመቶ የሚሆኑት ቢያንስ በወር አንድ ጊዜ ይህ ችግር ይከሰትባቸዋል፡፡ በተደጋጋሚ የማስተርቤሽን ተግባር የሚፈፅሙ ወጣቶች በእንቅልፍ ልብ የዘር ፈሳሽ ለመፍሰስ ችግር የተጋለጡ ናቸው፡፡ በመንስኤው ዙሪያ የተደረጉ ጥናቶች እንደሚገልፁት በእንቅልፍ ልብ የሚከሰተው የዘር ፍሬ መፍሰስ ወሲብ ካለመፈፀም ጋር እንደማይገናኝ ይጠቁማሉ፡፡ በእንቅልፍ ልብ ዘር ፍሬ የመፍሰስ አጋጣሚ የሚፈጠረው በተለያዩ ምክንያቶች ነው፡፡ በሰውነታችን ውስጥ በሚከሰት የሆርሞኖች ለውጥ የመጀመሪያው ሲሆን ከፍተኛ የሆነ የዘር ፍሬ ክምችት በሰውነታችን ውስጥ መኖር ደግሞ በሁለተኛነት ሊጠቀስ ይችላል፡፡ ከላይ ከተጠቀሱት ምክንያቶች በተጨማሪ ወሲብ እና ተያያዥ ጉዳዮችን ሲፈፅሙ ህልም ማየት እና ስለወሲብ ደጋግሞ ማሰብ እንዲሁም ከመኝታ በፊት ወሲብ ቀስቃሽ ፊልሞችን መመልከት እንዲሁም መጽሐፍትን ማንበብ በእንቅልፍ ወቅት ዘር ፍሬ የመፍሰስ ችግርን እንደሚያስከትል ይጠቁማሉ፡፡
ወድ ጠያቂያችን ጂቲ በወር አንድ ጊዜ እና ሁለት ጊዜ በእንቅልፍ ልብ የዘር ፍሬ የመፍሰስ ችግር ጤናማ እንዲሁም ተፈጥሯዊ እና ምንም አይነት ችግር የሌለው ነው፡፡ ነገር ግን በየቀኑ እና እንደ አንተ በሳምንት ሁለት ሶስቴ የሚከሰት ከሆነ እና እሱን ተከትሎ መደበርን፣ ራስ ምታትን፣ አቅም እንዲሁም እንቅልፍ ማጣትን የሚያስከትል ከሆነ ግን ጤናማ ስላልሆነ በፍጥነት ባለሞያን ማማከር ያስፈልግሃል፡፡ ምክንያቱም ይህ ነገር በሰውነታችን ወስጥ የሚኖረውን የቴስቴስትሮን መጠን በማሳነስ ለተለያዩ ሆርሞን ችግሮች ሊያጋልጥ ይችላል፡፡
ከዚህ በተጨማሪ የዘር ፍሬ በብዛት መፍሰስ በሰውነታችን ውስጥ ጤናማ ያልሆነ የዘር ፍሬ ፈሳሸ ምርት ምልክት ሊሆን ይችላል፡፡ ጤናማ ያልሆነ የዘር ፍሬ ምርት ደግሞ በተለይ ወንዶችን ለመሀንነት ችግር ሊያጋልጥ ይችላል፡፡ የዘር ፍሬ ብዛት በመመረቱ የተነሳ የዘር ፍሬ በብዛት የሚፈስ ከሆነ የሚፈሰው የዘር ፍሬ በአብዛኛው ትክክለኛ ቅርጽ እና መጠን ያለው ስለማይሆን ከሴት እንቁላል ጋር ተገናኝቶ ጽንስ የመፍጠር አቅሙ እጅግ አነስተኛ ይሆናል፡፡
በተመሳሳይ ይህ ነገር በሰውነታችን ውስጥ ያለው የዘር ፍሬ ክምችት አነሰተኛ እንዲሆን ያደርጋል፡፡ በአንድ ጊዜ በሚፈስ የዘር ፍሬ ውስጥ ከ20 ሚሊዮን በላይ ሴሎች ይገኛሉ፡፡ በአንድ ሚሊ ሊትር የዘር ፈሳሽ ውስጥ የሴሎች ብዛት ከ20 ሚሊዮን በታች ከሆነ ጽንሰ የመፍጠር አቅም አይኖረውም፡፡
ከዚህ በተጨማሪ በእንቅልፍ ልብ የዘር ፍሬን መፍሰሰ በወሲብ ወቅት ከሴቷ በፊት ቀድሞ የመርካት ችግርን እና ሌሎች ስንፈተ ወሲብ ችግሮችን ያስከትላል፡፡ የሰውነት ክብደት መቀነስን እና በራስ የመተማመን መንፈስንም ያሳጣል፡፡ ለራሳችን የምንሰጠውን ግምት በመሸርሸርም የፀፀት እና የጥፋተኝነት ስሜት እንዲሰማን ያደርጋል፡፡
ወደ መፍትሄው ስንመጣ የመጀመሪያው በጀርባ አለመተኛት ነው፡፡ ወደ መኝታ ከመሄድ በፊት ወተት አለመጠጣት እና ብዙ ምግብ አለመመገብም ይመከራል፡፡ በተለይ ደግሞ እራት ወደ መኝታ ከመሄዳችን ቢያንስ ከ3 ሰዓት በፊት መመገብ እና እራት ላይ ብዙ ቅመም የበዛበት ምግብን፣ ከመጠን በላይ ወይን ከመጠጣት፣ እንቁላል፣ ስጋ እና ሌሎች አነቃቂ ነገሮች የበዛባቸው ምግቦችን ከመመገብ መቆጠብ ቢቻል እራት ላይ አትክልት እና ፍራፍሬዎችን ማዘውተር ጠቃሚ ነው፡፡ ሌላው መፍትሄ ደግሞ ምግብን በደምብ አድቅቆ መመገብ እንዲሁም የፈሳሽ አወሳሰዳችንን ማስተካከል ነው፡፡ በተለይ ከእራት በኋላ ብዙ ፈሳሽ አለመውሰድ፣ ቀን ላይ ብዙ ውሃ መጠጣት፣ ከመኝታ በፊት ሽንትን መሽናት ጠቃሚ ነው፡፡ ብዙ ጊዜ የዘር ፍሬ የሚፈሰው ሊነጋጋ ሲል ስለሆነ በጠዋት የመነሳት ልማድን ማዳበርም ይመከራል፡፡
ውድ ጂቲ ፈረስ መጋለብን እና ሳይክል መንዳትን የመሳሰሉ ችግሮችንም ለዚህ ችግር ያጋልጣል፡፡ ስለዚህ መሰል ተግባራትን መቀነስም ጠቃሚ ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የእግር ጉዞ ማድረግ፣ ከመኝታ በፊት ወሲብ ቀስቃሸ ፊልሞችንም ሆነ ጽሁፎችን ከመመልከት እና ከማንበብ መቆጠብ፣ እለታዊ የአካል ብቃት እንቅስቃሴን ማዘውተር እንዲሁም ብልት እና አካባቢውን በየቀኑ በአግባቡ ማጽዳት እና የተመጣጠነ የአመጋገብ ስርዓትን ማዳበር ጠቃሚ ነው፡፡
በእንቅልፍ ልብ ካለፍቃድ እና ካለፍላጎት የዘር ፍሬ የመፍሰስ ችግርን ከላይ በመፍትሄነት የተዘረዘሩትን ነገሮች በአግባቡ እና ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ በማድረግ ካለብህ ችግር መላቀቅ ትችላለህ፡፡ በእነዚህ መንገዶች የምትፈልገውን ለውጥ ማምጣት ካልቻልክ ግን በአፋጣኝ ባለሞያዎችን ማማከር ይገባሃል፡፡ S
(በዘ-ሐበሻ ጋዜጣ ቁጥር 51 ላይ ታትሞ የወጣ)

Share and Enjoy

  • Facebook
  • Twitter
  • Delicious
  • LinkedIn
  • StumbleUpon
  • Add to favorites
  • Email
  • RSS

ሕዝባዊ ብሶት –የከተማ አብዮት? –ከተመስገን ደሳለኝ (ጋዜጠኛ)

$
0
0

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ

ባለፈው ሳምንት ኢህአዴግ በከተሞች ላይ የቋጠረውን ስር የሰደደ ጥላቻ ከነመግፍኤው ጨርፈን ከተመለክተን በኋላ፤ ለዛሬ፣ ታላላቅ ግድፈቶቹ ሕዝባዊ ተቃውሞ ለመቀስቀስ ሊኖራቸው የሚችለውን አስተዋፅኦና በአደባባዩ የሚነሱትን ዋና ዋና ጥያቄዎች ለመዘርዘር፤ እንዲሁም ‹‹ማኦኢዝም›› የሚበይነውን ከገጠር የሚነሳ ብረታዊ ትግል፣ ከሰላማዊው የከተማ አብዮት አንፃር ለመፈተሽ ቀጠሮ መያዛችን ይታወሳል፡፡ እናም እንዲህ እንቀጥላለን…

የኢህአዴግ ግድፈቶች

ፈረንጅኛው ‘Achilles Heels’ በሚል ስያሜ የሚገልፃቸው እና አማርኛው ደካማ ጎኖች ብሎ የሚሰይማቸው የስርዓቱ ታላላቅ ግድፈቶች ከዕለት ዕለት ራሳቸውን ማብዛታቸው ፍፃሜው የሚተነበይ አድርገውታል፤ ይኸውም ብሔር ተኮር ጥያቄዎች አለመመለሳቸው፣ ውጤት አልባው የገጠር ፖሊሲ፣ የድህረ-ደርግ የዴሞክራሲ ሽግግሩ መክሸፍ (ከፖለቲካ፣ ከሰብዓዊ እና ሀሳብን በነፃነት ከመግለፅ አንፃር)፣ የኢኮኖሚ እድገት አለመኖር፣ ድህነት ከቀድሞውም በበረታ መልኩ መስፋፋቱ፣ የትምህርት ፖሊሲው ክስረት፣ የስራ-አጥ ቁጥር አለቅጥ ማሻቀብ፣ የራስ አስተዳደር (Self-adminstration) ሙሉ ለሙሉ አለመተግበር (ከስልጤ እስከ ቁጫ ያሉ የማንነት ጥያቄዎች መቆሚያ ማጣታቸው)፣ የመሬት ፖሊሲው የአርሶ አደሩን የነፍስ ወከፍ የይዘት መጠን ከአንድ ሄክታር ማሳነሱ፣ የከተሞች ስራ-አጥነት በወጣት ከተሜ የተማሩ ልጆች ላይ መብዛቱ፣ በልማታዊ መንግስት ትግበራ እና በብሄር ፌደራሊዝም መሀከል የማይታረቁ ቅራኔዎች መኖራቸው፣ ከተሜነት እየተስፋፋ ሲመጣ በብሔር ፖለቲካ ሞት ላይ ግለሰባዊነት እንደሚነግስና ኢህአዴግም ይህንን ተቃርኖ ተከትሎ የርዕዮተ-ዓለም መሸጋሸግ ማድረግ የማይችል መሆኑ እና መሰል ተቋማዊ ክስረቶች በቀጣይ ሊያርማቸው የማይቻለው ታላላቅ ግድፈቶች በመሆናቸው እንደተለመደው ውጤቱ ቀድሞ የሚታወቀውን የይስሙላ ምርጫ ከመጠበቅ ይልቅ የአደባባይ ተቃውሞን ለማማተር ሥረ-ምክንያት ሊሆን መቻሉ አጠራጣሪ (አከራካሪ) አይደለም፡፡

ጉዳዩን በሚገባ ለማስረገጥ ከኢህአዴግ አጠቃላይ ህልውናዊ ባህሪ አኳያ ከላይ ከጠቀስኳቸው ነጥቦች ሊፈታቸው የማይቻላቸው ‹ብሎኖች› መሀከል ሶስቱን (ዋነኞቹ ናቸው ከሚል አረዳድ) በጨረፍታ በአዲስ መስመር እንያቸው፡፡

ያ ሁሉ ነጋሪት የተጎሰመለት የድህረ-ደርግ የዲሞክራሲ ሽግግር ‹ተስፋ› ሙሉ በሙሉ ሞት የታወጀበት አሁን በምንጠራው የ97ቱ ምርጫ ማግስት ነበር፡፡ ይህንንም ተከትሎ አቶ መለስ ‹ልማታዊ መንግስት› የሚል ሀልዮት ይዞ ብቅ ማለቱ ይታወሳል፤ በወቅቱ (1998 ዓ.ም ይመስለኛል) በማንችስተር ዩንቨርስቲ በመገኘት ቀጣዩ የስርዓቱ ማዋቀሪያ ምሶሶ አድርጎ ሃሳቡን ያብራራው የምርጫ ፖለቲካ፣ የሰብዓዊ መብቶችን እና መሰል ዲሞክራሲያዊ ዕሴቶችን ጨፍልቆ ‹በአብዮታዊ› መንገድ ልማት ማምጣትን ቀዳሚ ግቡ እንደሚያደርገው በመፎከር ጭምር ነበር፤ ይሁንና ፅንሰ-ሃሳቡን በቅርበት ስንመለከተው፣ በዛሬይቱ ኢትዮጵያ አውድ፤ በተለይም ስርዓቱ ካነበረው ቋንቋ ተኮር ፌደራሊዝም ጋር በማይታረቁ ቅራኔዎች መሞላቱን ለመረዳት አያዳግትም፡፡

ለዚህ ክርክር ማስረገጫ ይሆን ዘንድም ከተቃርኖዎቹ ውስጥ ሁለት ነጥቦችን ብቻ እናንሳ፤ የመጀመሪያው ልማታዊ መንግስት ‹የዜጎች የክሂል ልቀትን በመንተራስ ብቻ የተሳለጠ ቢሮክራሲን መገንባትና ተቋማዊነትን ማጎልበት ያስፈልጋል› ከሚለው መደምደሚያ አንፃር ነው፤ በርግጥ ይህ ሃሳብ ስኬታማነቱ የታየው በአንድ ቋንቋ ተናጋሪ ሀገራት ውስጥ ቢሆንም፣ በሙያ ብቻ ስርዓቱ ሲዋቀር ግን የተለየ የቡድን ጥቅሞችን ለማስፈፀም እንደማይመች ተግባራዊ ተሞክሮዎቹ ይናገራሉ፡፡ ከዚህ አኳያም የገዥው ፓርቲ የፌደራሊዝም ቅርፅ በግልባጩ የብሔር ማንነቶችን ተቀዳሚና ብቸኛ ተቋማዊነትን መገንቢያ አማራጭ ማድረጉ ከተጠቀሰው የልማታዊ መንግስት ጭብጥ ጋር በቀጥታ ያላትመዋል፡፡ እናም ከላይ እስከታች ያለው የስልጣን አወቃቀሩ የላቀ ክሂልን ረግጦ የብሔር ተዋፅኦን ለመጠበቅ በማለም ብቻ የተወሰነ ስርዓታዊ መልክ መያዙን ስንመለከት፣ ገዥዎቻችን ሀልዮቱን ለመተግበር ሲንቀሳቀሱ በሁለት ምርጫዎች ቅርቃር ውስጥ እንዲወድቁ መገደዳቸው የማይቀር ጉዳይ ሆኖ እናገኘዋለን፤ እነርሱም የፌደራሊዝሙን ቅርፅ ወደ መልከአ-ምድራዊ (Geographical) መቀየር፣ አሊያም ‹‹ልማታዊ መንግስት ነን›› የሚለውን አሰልቺ ፕሮፓጋንዳ አራግፎ መጣል የሚሉ ናቸው፡፡ ይህንን ደግሞ ኢህአዴግ
ከግትረኛነት ባህሪው አንፃር ይቀበለዋል ተብሎ አለመጠበቁ አንዱ ህልውናዊ ግድፈቱ ያደርገዋል፡፡

ሌላው ተጣራሽ ርዕሰ-ጉዳይ በስልጣን ኢ-ማዕከላዊነትና በማዕከላዊ መንግስት መጠናከር መካከል ያለው ነው፤ በሁለት አስርታቱ ስርዓታዊ ሙከራ፣ የበዛው ከወረቀት ላይ ባይዘልም፣ በጥቂቱም ቢሆን ኢ-ማዕከላዊ ለማድረግ ስለመጣሩ የምናውቀው እውነት ነው፡፡ ይሁንና የልማታዊ መንግስት ፅንሰ-ሀሳብ ማዕከላዊ አስተዳደሩ ሙሉ በሙሉ አጠቃላይ የስልጣን ገፆችን ጠቅልሎ እንዲይዝ ያስገድደዋል፡፡ ይህንንም ስልጣን በማከፋፈል ላይ የሚመሰረት ግጭት ህልውናዊ ድክመቱ አድርገን ልንወስደው እንችላለን፡፡

ሁለተኛው አስረጂ ጭብጥ የብሔር ማንነትን ዘላለማዊ የስርዓት መልክ ማድረጉ፣ ከከተሜነትና የከተሞች መስፋፋት ጋር አብሮ እየገነገነ ከሚመጣው ግለሰብኝነት (የግለሰብ መብትን ማስቀደም) ጋር ሊኖረው የሚችለው ግጭት ነው፡፡ በስነ-ማህበረሰብና ፖለቲካል ኢኮኖሚ አስተምህሮቶች መሰረት (በዋናነት በምዕራባዊ ሥልጣኔ)፣ የከተሜነት ዕድገት መገለጫ ኢህአዴግ ቀን-ከሌሊት እንደሚለፍፈው የፎቆች መደርደርና የመንገድ መስፋፋት ብቻ አይደለም፤ ይልቁንም ከተሜነት ማለት ከጋርዮሽ ማንነት እየተላቀቁ በመምጣት የግል የሆኑ አለማዊ ዕይታዎችን በማጎልበት፣ በመረጡት ማንነትን መተርጎሚያ ፈር ከሚተሳሰሩ ዜጎች ጋር ህብረት መፍጠር የሚለው አንድምታ ነው ብዬ አስባለሁ፡፡ ምክንያቱም በፆታ፣ በሙያ፣ በኃይማኖት አሊያም በተመረጠ ርዕዮተ-ዓለም ስር ምክንያተኝነትን ብቻ በመንተራስ ‹መደራጀት› የከተሜነት ቀዳሚ መለዮ ነውና፡፡ ይህንን ድምዳሜ በተለይም በአዲስ አበቤዎች ዘንድ እየመጣ ካለው የከተሜነት ባህሪ እና ከብሔር ፖለቲካው ጋር ስናስተያየው ‹‹የማይታረቀው ቅራኔ›› (በካርል ማርክስ አባባል) እነበረከት ስምዖን ፊት ይቆማል፡፡ ኢህአዴግ ይህ ተፈጥሮአዊ የማህበረሰብ ዕድገት እንኳ እንደሚገታው አለማሰቡ ከህልውናዊ ግድፈቶቹ አንዱ አድርገን ልንቆጥረው እንገደዳለን፡፡

ርዕሰ-ጉዳያችንን ለመጠቅለል የምጠቅሰው የመጨረሻው ማሳያ፣ ስርዓቱ የተነሳበትን የራስ ዕድል በራስ በመወሰን መብት ላይ ትገበራው የሚያሳየውን ሀሳዊነት ነው፤ ወታደራዊው ደርግ ይከተለው የነበረው ‹አሀዳዊ አስተዳደር›፣ ቋንቋን መሰረት ባደረገው ፌዴራሊዝም ከተተካ በኋላ ስለ ጉዳዩ ያጠኑ ምሁራኖች ‹‹የስልጤ ሞዴል›› እያሉ የሚጠሩትን ይህንን ጭብጥ፣ ግንባሩ እየመረጠ መስጠቱን የሚዘክሩ በዜጎች ደም የተፃፉ የዳጎሱ ታሪኮች ያረጋግጡልናል፡፡ እንደ ምሳሌም የሲዳማንና ሰሞኑን እየታዘብን ያለውን የቁጫን የማንነት ጥያቄዎች ብቻ መጥቀስ በቂ ይመስለኛል፤ ሲዳማ በሀገሪቱ ሕገ-መንግስት መሰረት ክልል ለመሆን የሚያስፈልጉትን መስፈርቶች ሁሉ ቢያሟላም የተሰጠው ምላሽ ለዓመታት ሞትና እስርን በጥያቄው አራማጆች ላይ እንደ ሐምሌ ዝናብ መዘርገፍ ሲሆን፣ ከሲዳማ ቁጥር በታች ያላቸው የማህበረሰብ ክፍሎች ደግሞ በክልል ደረጃ የመዋቀር መብታቸው ሲከበር ተመልክተናል፡፡ ይህንንም የተዛነፈ የመብት ትግበራን በመሰረታዊ የስርዓቱ ክሽፈትነት ልንቆጥረው እንደምንችል ይሰማኛል፡፡ የተቃውሞ መድረኩን ከውስጥም ከውጭም የሞሉት ኃይሎች ዋነኛ ጥያቄም፣ የብሔራችን መብት አልተከበረም የሚለው መሆኑ (በመጠኑ ላይ ባንስማማም፣ ቡድኖቹ ከየብሔራቸው ደጋፊ እንዳላቸው አይካድምና) ስርዓታዊ ሽንፈቱን ያበዛዋል፡፡ በአናቱም በስልጤው ሞዴል ግፊት ወደ አደባባይ የመጡት የወለኔና የቁጫ የማንነት ጥያቄዎች የሚጠቁሙት አንዳች ነገር ቢኖር፣ የስርዓቱ ቁንጮዎች የተጠቀሰውን ስታሊኒስታዊ የራስ ዕድል በራስ የመወሰን ጉዳይ በሕገ-መንግስታቸው ውስጥ ሲከቱት፣ ኢትዮጵያን በመሰለ ባለብዙ ቋንቋ ተናጋሪ ዜጎች ሀገር ጥያቄው ማቆሚያ እንደማይኖረው አለማሰባቸውን ነው፡፡

በእነዚህ የኢህአዴግ ታላለቅ ግድፈቶች ህላዊነት ከተስማማን የለውጥ መንገዱንም አንስቶ መነጋገሩ የግድ አስፈላጊ ነውና ወደዚያው እንለፍ፡፡

የከተማ አብዮት ሲባል…

በዚህ ተጠይቅ የምናየው አማራጭ የለውጥ መንገድ ያለንበት ሃያ አንደኛው ክፍለ ዘመን የሚበይነውን ሰላማዊ የከተማ አብዮት ብቻ ሳይሆን፣ ረዥም ዓመታትን ወደ ኋላ ተጉዘን በአማራጭነት ይተገበሩ የነበሩትንም ጭምር ነው፤ ምክንያቱም በኢትዮጵያችን ዛሬም ከተቃውሞ ስብስቡ መካከል ሁለቱንም ስልት የሚያቀነቅኑ የፖለቲካ ድርጅቶች መኖራቸው እውነት ነውና፡፡

ምንም እንኳ ጥያቄያቸው፣ አመሰራረታቸው እና የሚከተሉት ርዕዮተ-ዓለም ፍፁም የተለያየ ቢሆንም፣ ከኦነግ እስከ ኦብነግ፤ ከአርበኞች ግንባር እስከ ግንቦት ሰባት (ሁሉን አቀፍ የሚሉት ስልት እንደተጠበቀ ሆኖ) ድረስ የሚጠቀሱ ድርጅቶች ከከተማ አብዮት የ‹ማኦኢዝም›ን (ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረግ ጦርነት ላይ የሚያተኩር) የትግል ስልት እንደ ብቸኛ አማራጭ መውሰዳቸው የታወቀ ነው፡፡ ለዚህ ሁሉ ተቃውሞ መነሾ የሆነው ራሱ ኢህአዴግም ወደ ስልጣን የመጣበት መንገድ ሳይቀነስ ሳይጨመር ይኸው እንደነበረም አይዘነጋም፡፡

በኢትዮጵያ የፓርቲ ፖለቲካ መቀንቀን ከተጀመረበት 1960ዎቹ አጋማሽ አንስቶ የተመሰረቱ ግራ ዘመም ድርጅቶች በሙሉ ‹‹መንፈሳዊ አባት›› አድርገው የሚወስዱት የማኦ ዚዱንግ (Mao Zedong) የቻይና ኮምኒስት ፓርቲ (CCP) ለጥቂት ዓመታትም ቢሆን አራምዶት የነበረው የትግል ስልት ከከተማ ወደ ገጠር የሚነሳ እንደነበረ ይታወሳል፤ ይሁንና ሲሲፒ እ.ኤ.አ. በ1927 ዓ.ም. የፀደይ ወራት በሻንጋይ ሼክ (Chiang Kai-shek) ከሚመራው ‹‹Kuomintang›› (KMT)፣ የደረሰበትን ከባድ ወታደራዊ ጡጫ መቋቋም ተስኖት ከጠንካራ መሰረቶቹ ሻንጋይ እና ክንቶን (ዛሬ ስሟ ‹ጉዋንዡ› /Guangzhou/ በሚል ተቀይሯል) ከተሞች ወደ ገጠር ማፈግፈጉን ድርሳናቱ ይናገራሉ፡፡ ከዚህ በኋላም የእነ ማኦ ድርጅት ‹የሠራተኛ መደብ› የሚል አጀንዳውን አርቆ ሰቅሎ፣ እንደ አዲስ በገበሬ ሰራዊት በመዋቀር የትጥቅ ትግልን ከገጠር የመጀመር ጠቀሜታ ሰባኪ ብሎም የገበሬ አምባገንነት አቀንቃኝ ሆኖ ብቅ ማለቱን ከታሪክ ንባብ መረዳት ይቻላል፡፡ በነገራችን ላይ ሲሲፒ የስልት ለውጥ ከማድረጉ በፊት ከ11 ሺ ኪሎ ሜትር በላይ ርቀት የሚሸፍነውን ‹‹ረጅሙ-ጉዞ››ን (Long march) በፅናት መጨረሱ የዓላማ ፅናቱን ያሳያል፡፡

እነ ማኦ ለመስማት ከሚዘገንነው መስዋዕትነት በኋላ ለሥልጣን የበቁት ድርጅታቸው በተመሰረተ በሃያ ስምንተኛ አመት (እ.ኤ.አ. በ1949 ዓ.ም) ነበር፡፡ ከዚህ በኋላም በተለያዩ የዓለማችን ሀገራት የሚኖሩ ሕዝቦች ‹ጭቆናን ለማስወገድ› በሚል ‹ግራ ዘመም› ድርጅት መስርተው በእምቢተኝነት ሲያምፁ፣ ማኦኢዝም የትግል ስልት የሚበይነውን በገበሬዎች በተደራጀ ሰራዊት ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረግ ሽምቅ ውጊያን እንደሁነኛ አማራጭ መከተላቸውን ታሪክ ይነግረናል፡፡ በአናቱም የማኦ አስተምህሮ ‹በገበሬ አብዮት› የሚመሰረትን የ‹እርሻ መር ኢኮኖሚ ማህበረሰብ› (Agrarian society) መፍጠርን እና የከተሞችን ፖለቲካል ኢኮኖሚ በማፈራረስ የገበሬውን ሁለንተናዊ ከፍታ ማረጋገጥ ላይ ማተኮሩ በዚህ መንገድ ወደ ሥልጣን የወጡ ገዥዎቻችንን ባህሪ ለመዳኘት ይረዳናል፡፡

እነሆም በዚህ ትውልድ መቀመጫቸውን በሀገራችን የጠረፍ ከተሞች አሊያም በአውሮፓና አሜሪካ ያደረጉ ብረት ያነሱ ድርጅቶች ከላይ በተጠቀሰው የታሪክ ንባብ ከተመዘኑ፣ አንድም የመረጡት የትግል ስልት ዘመኑን የሚዋጅ ነው ብሎ ለመቀበል ያዳግታል፤ ሁለትም በለስ ቀንቷቸው ያሰቡት መሳካት ቢችል እንኳ፣ በእንዲህ አይነት መልኩ ባንክ ዘርፈው፣ መሰረተ ልማቶችን አውድመው፣ ንፁህን ዜጎችን ለህልፈት ዳርገው፣ የቅርብ ጓደኞቻቸውን ሰውተውና ጠብ-መንጃ ተሸክመው ወደ ቤተ-መንግስት የሚመጡበት መንገድ፣ ከዓመታት በፊት መለስና ጓዶቹ ‹ታግለናል፣ ሞተናል፣ ደምተናል… እናም ምርጥ ምርጡ ለእኛና ለቤተሰቦቻችን ብቻ› በሚል ድምዳሜ ካዘጋጁት ‹መፅሀፍ› አንድ ገፅ ገንጥለው ‹‹የሞትንም እኛ፤ ያለንም እኛ…›› ወደሚል የአምባገነኖች ጠርዝ መገፋታቸው አይቀሬ ይመስለኛል፡፡

በተጨማሪም ‹‹ጨቋኝ ጨቋኝን ሊተካው ይችላል›› እንዲል አርስቶትል ኢህአዴግ ለአስራ ሰባት ዓመታት በዱር-በገደል ወጥቶና ወርዶ፣ አስከፊ መስዋዕትነትን ከፍሎ፣ አራት ኪሎ ከደረሰ በኋላ፣ ያነበረው ስርዓት ካመፀበት የመንግስቱ ኃይለማርያም አስተዳደር ጋር ያለው ልዩነት የስም ብቻ መሆኑ መዘንጋት የለበትም፡፡ ይህ ሁኔታም ነው በብረት የታጠረ፣ ደም አፋሳሽና የተናጥል አሸናፊነትን በሚያውጅ ስብከት ላይ ብቻ የተገነባው የትግል ትርጓሜ ዛሬም እንደአዲስ የመከለሱ ዜና በስጋት ያነጠበን፡፡ በርግጥም የጭቆናን ሸክም ከትከሻ ለማውረድ ሲባል የተካሄዱ መራራ ትግሎች ውጤታቸው ጨቋኞችን መቀያየር መሆኑና የትንቅንቁ ወራቶች መርዘም ያስከተሉት ኪሳራዎች ከዘመኔ ቀድሞ የነበረውን የማኦን መንገድ የታሪክ መዛግብት ላይ ብቻ ተወስኖ እንዲቀር በመገደብ ለአማራጭነት እንኳ እንዳይበቃ አድርገውታል፡፡ የዚያን ዘመን የጨቋኞች አገዛዝ ውርስን ለመከተል ወቅቱ አመቺ አለመሆኑንና የሥልጣን ወንበርን ለጊዜውም ለማሰንበት ዘመን-ወለዱን አመቻማች አምባገነንትን መጠመቅ ማስፈለጉም የትግሉ ስያሜ በድጋሚ ለብይን እንዲቀርብ ተጨማሪ ኃይል ሆኗል፡፡ ርዕዮተ-ዓለማዊ ልዩነቶች እስኪዘነጉ ድረስ መጥበባቸው፣ ክስተቶች ከአንድ ሀገር ድንበር መዝለላቸው እንዲሁም ወቅታዊዎቹ የለውጥ ስኬቶች በጋራ የቀድሞውን የአብዮት መስመር በጥርጣሬ እንድንመለከተው ፈርደውበታል፡፡ ዛሬ ላይ አብዮት ቃሉ ብቻ እስኪቀር ድረስ ተነቅሎ ነባር የመዳረሻ መንገዶቹ ፈራርሰዋል፤ በፍርስራሹ ላይም አዲስ ትርጓሜ ተቸክችኮበታል፡፡

እነዚህና መሰል ሁነቶች የለውጡን መንገድ ለመቃረም ፊታችንን ወደ አውሮፓውያኖቹ የ‹ብርቱካናማ› እና የ‹ፅጌረዳ› አሊያም ወደ አረቡ የ‹ፀደይ› አብዮት እንመልስ ዘንድ ያስገድዱናል፡፡ ይህ ግን እነ ሌኒን ያራምዱትና ይመክሩት ከነበረው በከተሞች ውስጥ ከሚደረገው የትጥቅ ትግል ፍፁም የተለይ ይመስለኛል፡፡ በርግጥም እንዲህ አይነቱ አማራጭ በ1966ቱ አብዮት ማግስት በራሳችን ሰዎች ተሞክሮ ከመክሸፉም በላይ ሀገሪቱን ወደ ቀለም ሽብር ከቷት መቼም ሊተካ የማይችል ዋጋ ማስከፈሉ ሁሌም በቁጭት የምናስበው ታሪካችን ነው፡፡ እናም ለእኔ ትውልድ የለውጥ ጥያቄ ከሰላማዊው የከተማ አብዮት ውጪ ያሉ አማራጮች ከጠቀሜታቸው ይልቅ ጥፋታቸው አመዝኖ ነው የሚታየኝ፡፡ በተለይም ነባሩን የኢትዮጵያ የፖለቲካ ባህል (የ‹ጦር አርበኝነት›ን በ‹ሲቪል ጀግንነት›) ለመቀየርም ሆነ፣ ከእርስ በርስ እልቂት፣ ከደም መፋሰስ፣ ከደካማው ኢኮኖሚ መንኮታኮት፣ ካለመረጋጋት… ለመታደግ ብቸኛ መፍትሄ ይኸው ነው፡፡ በተጨማሪም ከከተማ መነሳቱ ለአገዛዙ ምሰሶ፤ ለሀገሪቱ ደግሞ ስጋት የሆኑትን የሃይማኖት እና ብሔር (ቋንቋ) ልዩነቶችን ተሻግሮ፣ በአንድ ሀገር በእኩል ማንነት ላይ የሚያሰባስብ ኃይል ይፈጥራል ብዬ አስባለሁ፡፡

በነገራችን ላይ ለእንዲህ አይነቱ አደገኛ ስጋት መቃረባችንን የሚያሳየው በይበልጥ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከተቃውሞ ስብስቡ አካባቢ የሚሰማው ከሀገር ይልቅ የትውልድ መንደርን የማስቀደም ድምፅ ነው፡፡ ይሁንና ይህ መንገድ የትም ሊያደርስ ካለመቻሉም በላይ ላለፉት ሃያ ዓመታት የጭቆና ቀንበርን ትከሻችን ላይ እንዲከርር አስተዋፅኦ አድርጓል፡፡ እናም ወደ ተናፋቂው የነፃነት ምኩራብ ሊያደርሰን የሚችለው ድምዳሜ ስርዓቱ ትግራይን ከኦሮሚያ፣ ወይም ከአማራ… የበላይ አድርጎ ያስተዳድራል ለሚሉ ከፋፋይ አሉባልታዎች ጆሮ መንፈግ ብቻ ነው፤ የአንዳንድ ብሔር ተኮር ድርጅት አፈ-ቀላጤዎችም ንጉሳዊውን ዘመን የአማርኛ ቋንቋ ተናጋሪዎች ወኪል ለማስመሰል መሞከራቸውም ሆነ ህወሓት የተሰኘው የማፍያ ቡድን የሚፈፅመውን ግፋአዊ አገዛዝ በየትኛውም መስፈርት ከትግራይ ህዝብ ጋር ለማያያዝ የሚያደርጉትን ጥረት ማክሸፉ ከአብዮቱ ቅድመ ዝግጅቶች አንዱ ይመስለኛል፡፡

የሆነው ሆኖ ‹አብዮት የራት ግብዣ አይደለም› እንዲል ማኦ፣ አሁን እየተናገርንለት ያለው ሰላማዊው የከተማ ተቃውሞ የጠብ-መንጃውን ያህል ባይሆንም እንኳ ዋጋ ማስከፈሉ አይቀሬ መሆኑ መዘንጋት የለበትም፡፡ በየትኛውም ሀገር ያሉ አምባገነን ገዥዎች በሕዝባዊ እምቢተኝነት አደባባይ የወጡ ተቃዋሚዎቻቸውን ወደ ቤተ-መንግስታቸው እንዲገቡ ሲፈቅዱ ታይቶም ተሰምቶም አይታወቅም፡፡

እንዲያውም በግልባጩ በጦር ሠራዊትና በደህንነት ኃይል ለማስፈራራት ሲሞክሩ፣ ከተቃዋሚዎቻቸው የተወሰኑትን በመቀጣጫነት በጥይት ሲያስደበድቡ፣ አስተባባሪዎቹን ሲያስሩ፣ የአገዛዛቸውን የብረት መዳፍ ይበልጥ ሲያጠነክሩ… ይስተዋላሉ፡፡ ይሁንና ይህ አይነቱ የጭካኔ እርምጃ አምባገነኖችን ከአብዮቱ ወላፈን ሊታደጋቸው አለመቻሉን ማረጋገጥ ካስፈለገ ቱኒዝያ ጥሩ ማሳያ ትመስለኛለች፡፡ አደባባዩን ከማማተር አስቀድሞ ግን አብዮቱ መያዝ ስለሚገባው ባህርያት ጥቂት ነጥቦችን ማንሳት ሳያስፈልግ አይቀርም፡፡

የለውጡ መስመር አንዱ መለዮ መሆን የሚኖርበት የትኞቹንም ጨቋኝ ህጎችን በአደባባይ መጣስ ነው፤ እዚህ ቦታ ለመሰለፍ ጠይቀን ተከለከልን፤ ደጋፊዎቻችንን እንዳንሰበስብ አዳራሽ አጣን… እና መሰል ቀልዶችን በመተው አዋጆቹን (እንደ ፀረ-ሽብር እና የፕሬስ አዋጅ ውስጥ ያደፈጡ ቀፍዳጅ አንቀፆችን) በግላጭ በመጣስ በገፍ ወደዘብጥያ ለመውረድ መወሰን የአብዮቱ ዋና አካሄድ መሆን የሚኖርበት ይመስለኛል (በዚህ አውድ አንድ የቢሆን ምሳሌ እናንሳ፤ አሁን ካሉት ህጋዊ ፓርቲዎች መካከል አንዱ በአንድ ክፉ ቀን የፓርቲው የህጋዊነት ማረጋገጫ በሎሌው የምርጫ ቦርድ ጽ/ቤት ቢሰረዝና እኛም አማራጭ አካሄዶችን ስለማሰላሰላቸው ብንጠይቅ፣ ‹‹ጨዋታው ፈረሰ…›› ብለው ወደየቤታቸው ገብተው ይቀመጡ ይሆናል ከሚለው ውጪ የምናገኘው ምላሽ ምን ሊሆን ይችላል?)

ሌላኛው ነጥብ ቡድናዊ መሰባሰቢያ መስፈርቶችን ይመለከታል፤ በአረቡ ፀደይ እንዳስተዋልነው (ስለአረቡ ዓለም አብዮት ባህሪያት ከፍትህ ጋዜጣ እስከ ፋክት መፅሄት ድረስ በተደጋጋሚ ሊብራራ ተሞክሯልና እዚህ መድገም አያስፈልግም) የፆታን፣ የኃይማኖትን፣ የመደብን፣ የአንድ ርዕዮተ-ዓለምን አሊያም የብሄር ልዩነቶችን በመሻገር ሁለንተናዊ የዜግነት ነፃነቶችን መሻትን ብቻ ማዕከል ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ ሁለንተናዊ የዜግነት ነፃነቶች ሲባል ደግሞ የኃይማኖት፣ የፖለቲካና የሲቪል መብቶች መከበር ማለት መሆኑ ግልፅ ነው፡፡ የትኞቹንም የቡድንም ሆነ ግለሰብ ተኮር ጥያቄዎች ይህንን ነፃነት በማስከበር ትግል ውስጥ ማስመለስ እንደሚቻል መታወቁ የአብዮቱን መሪ ቡድኖች መልከዓ-ባህሪ በዜግነት ላይ ብቻ እንዲቆም ያደርገዋል፤ ይህ ክንውንም፣ በአንድ በኩል የስርዓቱን የከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲ ሲያከሽፍ፣ በሌላ በኩል የተሻለች ሀገር ለማቆም የማይነቃነቅ ጠንካራ መሰረት ይጥላል (በነገራችን ላይ ከዚህ ቀደም ፋክትን ጨምሮ በአራቱም የህትመት ውጤቶች ያነሳኋቸው የፈራ ይመለስ፣ ሞት የማይፈሩ ወጣቶች፣ ለምን ትፈራለህ? የታህሪር ናፍቆት፣ የዘገየው አብዮት፣ የግፉአን ዕድሜ ምን ያህል ይረዝማል? አደባባዩ ምን ያህል ይርቃል? የመሳሰሉት ቀዳሚ ድምፆች በዚህ አይነቱ ሰላማዊ የከተማ
አብዮት የሚበየኑ መሆኑን ማስታወስ ያስፈልጋል)

የአብዮቱ ግቦች…

በጥቅሉ እዚህ ድረስ ስንነጋገርበት የነበረው የከተማ አብዮት እንደ ሊቢያ ወይም ሶርያ ለእርስ በእርስ እልቂት የሚዳርግ ደም አፋሳሽ አለመሆኑ ግልፅ ይመስለኛል፡፡ በዚህ አውድ ትኩረት ሊሰጥበት የሚገባው አንኳር ጉዳይ የአረቡን መነቃቃት ተከትሎ በሞሮኮ፣ የመን እና ኳታር እንደታየው አይነት፣ ከስር ነቀል ለውጥ ይልቅ የፖለቲካ ማሻሻያዎች እንዲደረጉ የአምባገነኑን አገዛዝ እጅ መጠምዘዙ ላይ ነው፤ ይህ ይሆን ዘንድም የሚከተሉት ጥያቄዎች ወደ አደባባይ መሰባሰብ የሚያስችሉን የጋራ አጀንዳ (የአብዮቱ ግቦች) ቢሆኑ ለስርዓቱ ‹‹የወንድ በር››፤ ለምንወዳት ሀገራችን ደግሞ የተስፋውን መንገድ ጠራጊ የሚሆኑ ይመስለኛል፡፡

ከፊታችን ያለው የ2007ቱ አምስተኛ ዙር አገር አቀፍ ምርጫ ከመደረጉ በፊት፣ ያን ጊዜ የ97ቱ ቅንጅት ፓርላማ ለመግባት በቅድመ ሁኔታነት አንስቷቸው የነበሩትን ከፊል ጥያቄዎች ጨምሮ ሌሎችም በዚህ ፅሁፍ የተካተቱ ጥያቄዎች ምላሽ ይሰጣቸው ዘንድ ከሥራ ማቆማ አድም አንስቶ ከአገዛዙ ጋር አለመተባበርን የሚያካትትና ለውጡ እስኪመጣ በተከታታይ (በብሔር አግላይ ያልሆነ) መሬት አንቀጥቅጥ የተቃውሞ ሰልፍ መሰል እንቅስቃሴዎችን ለማድረግ ራስን ማዘጋጀት ይጠይቃል፤ ጥያቄዎቹም የሚከተሉት ናቸው፡-

1/ ሁሉንም የፖለቲካና የህሊና እስረኞች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ከእስር መፍታት፤
2/ እስከ ዛሬ ድረስ በሀገር ጥቅም ላይ ለተፈፀመው ጥፋትም ሆነ በሰላማዊ ዜጎች ላይ ለደረሰው ጅምላ ጭፍጨፋ፣ እስር፣ እንግልት፣ አካል መጉደል እና ስደት ኃላፊነት ወስዶ በአደባባይ ይቅርታ መጠየቅ (ካሳ የሚገባቸውን መካስ)፣ ለብሔራዊ ዕርቅ መደላድል መፍጠር፤
3/ አፋኝ የሆኑትን የፀረ-ሽብር፣ የፕሬስ፣ የመያዶች እና የፖለቲካ ማሻሻያ አዋጆችን መሻር፤
4/ ዜጎች በሚያምኑበት የፖለቲካ አስተሳሰብ የመደራጀት መብታቸውን ያለአንዳች ገደብ መልቀቅ፤
5/ ከሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር በእኩል ደረጃ መወያየትና መደራደር፤
6/ የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድን ነፃና ገለልተኛ መሆኑን በሚያረጋግጥ ሁኔታ እንደገና ማቋቋምና የአቅም ብቃቱን መገንባት፤
7/ ፍትሐዊ የመንግስት ሚዲያ አጠቃቀም እንዲኖርና የግል የኤሌክትሮኒክስም ሆነ የህትመት ሚዲያዎች ያለ ከልካይ እንዲኖሩ መፍቀድ፤
8/ የፍ/ቤትን እና የሌሎች የፍትህ አካላትን ነፃነት ማረጋገጥ፤
9/ የፖሊስ፣ የመከላከያና የደህንነት ተቋማት ከፖለቲካ ገለልተኛ እንዲሆኑ ማድረግ፤
10/ ከላይ የተጠቀሱትን ጉዳዮች ተፈፃሚ የሚያደርግ ለየትኛውም የፖለቲካ ድርጅት የማይወግን ነፃ የሆነ አካል ማቋቋም የሚሉት

ጥያቄዎች የመንደርደሪያ ነጥብ መሆን የሚችሉ ይመስለኛል፡፡

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!

ኢትዮሚድያ – Ethiomedia.com
January 5, 2014

Share and Enjoy

  • Facebook
  • Twitter
  • Delicious
  • LinkedIn
  • StumbleUpon
  • Add to favorites
  • Email
  • RSS

ጃዋር መሐመድ በኮካኮላ ላይ ቦይኮት አልጠራንም አለ

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) ትናንት በጋዜጠኛ ክንፉ አሰፋ አማካኝነት ዘ-ሐበሻን ጨምሮ በተለያዩ ድረ ገጾች በተሰራጨው “ኮካኮላ የቴዲ አፍሮ ውል እንዲሰርዝ ዘመቻ ተጀመረ” የሚለውን ዜና ተከትሎ ጃዋር መሐመድ በፌስቡክ ገጹ ባስተላለፈው መግለጫ ይህ መረጃ መሠረተ ቢስ ነው ሲል ገለጸ።

በአሁኑ ወቅት ቦይኮት በደሌ በሚል ተነስተውበት በነበረው እንቅስቃሴ ድል እያጣጣምን ነው ያለው ጃዋር ለቴዲ አፍሮ ያለንን መልዕክት ኮንሰርቱን በማሰረዝ በግልጽ ያሰማን በመሆኑ በኮካኮላ ላይ ይህን ቦይኮት አልጠራንም ብሏል።
teddy afrio
በ2014 ብራዚል ለሚካሄደው የአለም እግር ኳስ ዋንጫ አፍሪካን ወክሎ እንዲገኝ ኮካኮላ ቴዲን የመረጠው መሆኑ የሚታወስ ሲሆን ይህን ተከትሎም ኮካኮላን ቦይኮት ለማድረግ እንቅስቃሴ ተጀምሯል የሚለውን መረጃ ጃዋር መሀመድ “እኛ የጠራነው ቦይኮት የለም” ካለ በኋላ “ቦይኮት ቴዲ የሙዚቃ አልበምና የሙዚቃ ኮንሰርት ግን ይቀጥላል” ብሏል።

ጃዋር በፌስቡክ ገጹ ያሰፈረው የሚከተለው ነው፡-

We are aware of the baseless rumor being circulated about a campaign to Boycott Coca Cola. We would like for you all to know that we have not initiated such campaign and at this time we have no plan to do so. Besides, with our resounding victory with BoycottBedele, our message has been clearly and loudly communicated. Therefore, until further notice, we would like our supporters and the public to know that there is no call for Boycotting Coca Cola. But the campaign to boycott Teddy’s albums and concerts continue.

Thanks,
Jawar teddy afro

Share and Enjoy

  • Facebook
  • Twitter
  • Delicious
  • LinkedIn
  • StumbleUpon
  • Add to favorites
  • Email
  • RSS
Viewing all 8745 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>