Quantcast
Channel: ዘ-ሐበሻ – Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 8745 articles
Browse latest View live

ቴዲ አፍሮ እና ጥሬ ጨዋዎች

$
0
0

teddy 2
ሁኔ አቢሲኒያዊ - ፒተርቦሮው ዩ.ኬ

ቴዎድሮስ ካሣሁን (ቴዲ አፍሮ) በብዙዎች ሙዚቃ አፍቃሪያን ዘንድ ትልቅ ስፍራየሚሰጠው ወጣት ከያኒ ነው፤ በሙዚቃዎቹ በሚያነሳው ሀገራዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ማኅበራዊ፣ታሪካዊና ወቅታዊ ጉዳዮች የተነሳ የብዙዎችን ቀልብ ለመግዛት የቻለ ይመስለኛል፡፡ የእርሱን ታላቅነት መግለፅ የዚህ ጹሑፍ ዓላማ፣ ጥያቄም፣ የማወቅም ፍላጎት አይደለም፡፡
ይልቁንም ለዚህ አጭር መጣጥፍ መነሻ የሆነኝ ከሰሞኑ በአንዳንድ ጥቃቅን እና አነስተኛ ካድሬዎች እንዲሁም መንግስትን ለምን እንደሚቃወሙ እንኩአን በማያውቁት እንደ እነ ጃዋር መሀመድ የመሳሰሉ ሰሞንኛ ትችታቸውን በመሰንዘራቸውን ምክንያት እኔም የተሰማኝን ልጨምር በሚል ነው፡፡
እንደምናውቀው ቴዎድሮስ ካሣሁን በዚህች የሙዚቃ ህይወቱ ከዛቻ እስከመታሰር ድረስ የደረሰ መሆኑ እሙን ነው ይህም የደረሰበት የተለየ ሰው ስለሆነ ነው
ቴዲ ሺህ ዘመናት ስልጣኔያችንና ታሪካችን፣ ጥበባችን በፍቅር፣ ፍቅራችን በጥበብ የተገመደበት ውሉ ከየት ተጀምሮ የት እንደተቋረጠ ታሪክንእንጠይቅ ዘንድ እንዲህ ሲል በቅኔው ተመራምሮ ያመራምረናል፡-
ብራናው ይነበብ ተዘርግቶ ባትሮኖሱ ላይ፣
የእነ ፋሲለደስ የእነ ተዋናይ፣
የት ጋር እንደሆነ ይታይ የእኛ ጥበብ መሰረቱ…፡፡
እናም እስቲ ታሪክ ይታይ፣ ይመርመር፣ ዘመናትን ያስረጁና የተሻገሩ ብራናዎቻችን ይውጡ፣የሺህ ዘመን የሃይማኖት፣ የጥበብ፣ የታሪክ፣ የሥልጣኔና የፍልስፍና ድርሳኖቻንን ይታዩይመርመሩ… በአክሱም ስልጣኔ፣ በላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ትንግርት፣ በጎንደርበእነ ፋሲለደስ የስልጣኔ አየር ዝናዋ የናኘላት፣ እነዛ ፍቅርን በጥበብ አስውበው በቅኔያቸውናበማኅሌታቸው ሰማይ ሰማያትን ሰንጥቀው በመንፈሳቸው ጸባዖት የደረሱ፣ በፍቅር ጧፍ የነደዱበማሕሌታዩ ያሬድ መንፈስ የተነሱ እንደ ተዋናይ ያሉ የቅኔ የጥበብ ጉልላቶች እንደ አጥቢያኮከብ በደመቁባት ምድር ዛሬን ፍቅር የተራብን፣ ጥበብን የተራቆትን፣ ስለ ፍቅር የደከመንምንድነው ምክንያቱ የሚል ይመስለኛል ቴዲ…፡፡
ቴዲ በሙዚቃው ለታሪክ ያለውን ስሱነትና (sensitivity) እውቀትም (Indigenous Knowledge)አሳይቶናል፡፡ ተዋናይን ስንቶቻችን እናውቀዋለን ተብለን ብንጠየቅ የሚያስተዛዝበን ሳይሆንይቀራል፡፡ በተለይ ደግሞ ለዘመናችን ትውልድ ለአፉም ለልቡም ቅርቦቹ እነ አርሴናል፣ቼልሲ፣ ሜሲ፣ ሮናልዶ፣ እነ ፊፍቲ ሴንት እነ ቢዮንሴ፣ ወዘተ… የባሕር ማዶዎቹ ዝነኞች ናቸውእንጂ እነ ተዋናይን እነ ቅዱስ ያሬድን፣ እነ አጼ ፋሲልን ሊያስባቸው ወኔው ያለውአይመስልም፣ ኅሊናውንም ይደክመዋል እናስ እንዴት፣ ምን ሲደረግስ ሊያስባቸው ይችላል የኔትውልድ፡፡ በቅኔው የተራቀቀና በመንፈሳዊ እውቀቱ አንቱ ስለተባለው ስለ ተዋናይለመስማትም ሆነ ለማወቅ የታሪክ መዛግብትን ማገላበጥ ግድ ይላል፡፡ አሊያም ከቤተክርስቲያን ሊቃውንት አባቶች እግር ስር ቁጭ ማለት ያስፈልግ ይመስለኛል፡፡
ቴዲ በየትኛው መንገድ የሀገሩንና የቤተ ክርስቲያኑን የጥበብ እና የሥልጣኔ ከዋክብቶችንሊያውቅ እንደቻለ ባይነገረንም የትናንትናዎቹን የሀገራችንን ባለውለታዎችና የዘመንፈርጦች ማንነት ለማወቅ እና እንዲሁም ታሪኩን ለመመርመር ግን የተጋና የሰላ አእምሮእንደተቸረው/እንዳለው የግጥሞቹ መልእክቶች ይነግሩናል፡፡ እናም ከታሪካችንናከስልጣኔያችን መሰረት ከአክሱም ተነስቶ በጊዜና በታሪክ ሃዲድ ላይ አሳፍሮን በትላንትታሪካችን ውስጥ ራሳችንን እንድንመረምር፤ ራሳችንን እንድናይ ይወተውተናል፡፡ ለዚህደግሞ ምክንያቱ ይለናል ቴዲ ስለ ፍቅር ዜማው ውብ የግጥሞቹ ስንኞች፡-
. . .የኋለው ከሌለ የለም የፊቱ፣
ሳይራመድ በታሪክ ምንጣፍ፣
ሰው አይደርስም ከዛሬ ደጃፍ፡፡
በማለት ከታሪካችን ጋር እጅ ለእጅ በምናብ ሊያጨባብጠንና ሊያስተያየን ይፈልጋል፤ እናምያለ ትላንት ዛሬ የለም፣ ያለ ዛሬ ደግሞ ነገ አይታሰብም በሚል የመጣንበትና የተጓዝንበትንአኩሪና አሳፋሪ የታሪካችንን ምእራፍ ለማገላበጥ ለደከምን ለእራሱ እና ለእኛ ትልቅ ቁም ነገርያለው ምክር ያስተላልፋል፡፡ ይህ የከያኒው የግጥም ስንኝ የሮማውን ታላቅ የሕግ ሊቅ፣ፈላስፋና አስተማሪ የሆነውን የሲስሮን አባባል አስታወሰኝ፡- ‹‹ከመወለዳችን በፊት ያለውንታሪክ ካላወቅን ዕድሜ ልካችንን ሕጻን ሆነን እንቀራለን፡፡›› ታሪካችንን ለመመርመር እናከታሪካችን ለመማር የደከምን እኛ ዛሬም እንደ አዲስ ሰናፈርስ ስንጀምር ከመጀመር ሀ ሁሳንወጣ እንደ ህጻን ባለህበት እረገጥ የሆንበትና ታሪክን እንድንደግም የተፈረደብን ምስጢሩምን ይሆን በማለት ታሪክ ጠያቂ፣ የታሪክ ወዳጅ፣ ከታሪክ የምንማር እንድንሆን ያተጋናል፡፡
ከምንኮራበት ታሪካችንና ስልጣኔያችን ባልተናነሰ አንገት የሚያስደፋ ስማችንና ማንንታችንበዓለም ፊት በቀየረብን በበርካታ የራብ፣ የእርስ በርስ ጦርነትና መበላላት ታሪክ ዘመናትንውስጥ አልፈናል፡፡ እናም የመጣንበት መንገዱ ረጅም ዘመናቶቻችንም መከራ ሰቆቃና ዋይታ የነገሰባቸው ናቸው ሲል የትናንቱን ታሪክ ለመድገም የተፈረደብን ይመስል ታሪክ ደጋሚዎች እንድንሆን የሆንበትን እውነታ መመርመርና ማየት እንችል ዘንድ ትልቅ ጥያቄያጭርብናል፡፡ ዛሬም እግራችን መሄድ ተስኖት ቆመናል
የእርሱ ደጋፊዎች እንዳሉ ሁሉ የእርሱ ተቃዋሚዎች መኖራቸው ተፈጥሮአዊ ነው ነገር ግን በአሉባልታ የቴዲን ስራዎች ጥላሸት ለመቀባት የሚደረግ ትግል ወይ ቅናት ነው አልያም ለተቀማጭ ሰማይ ቅርቡ ነው እንደሚባለው ይሆናል፡፡
ለእምዬ ምንሊክ ያላቸው ጥላቻ ሰሞኑን ተቀስቅሶባቸው ያዙኝ ልቀቁኝ ሲሉ ከርመዋል አስገራሚው ነገር ምንሊክን ለመሳደብ ቴዲን ሰበብ ማድረጋቸው ነው ሌላው ደግሞ መረጃውን እኔ ለቅቄዋለው ብሎ ማንም ኃለፊነቱን እሰከዚች ሰዐት ድረስ ሳይወስድ እነርሱ ቴዲን እና ምንሊክን መዝለፍ የየእለት ተግባራቸው አድርገውታል፡፡
ምንሊክን ህዝቡ እምዬ ብሎታል ቴዲን ደግሞ የዘመናችን የሙዚቃው ንጉስ ብሎ ሰይሞታል
ደበበ ሰይፉ ጥሬ ጨው በሚለው ግጥሙ እንዲህ ነበር ለነፈዞች የገጠመው

ጥሬ ጨው – ደበበ ሰይፉ
————
መስለውኝ ነበረ ፣
የበቁ የነቁ
ያወቁ የረቀቁ
የሰው ፍጡሮች ፣
ለካ እነሱ ናቸው ፣
ጥሬ ጨው..ጥሬ ጨው
ጥሬ ጨዋዎች ፣
መፈጨት-መሰለቅ-መደለዝ-መወቀጥ-
መታሸት-መቀየጥ
ገና እሚቀራቸው ፣
“እኔ የለሁበትም !”
ዘወትር ቋንቋቸው ።

ለማንኛውም እኔም እንደ ደበበ ሰይፉ ሰሞንኛ የቴዲ ተቺዎችን ጥሬ ጨው ብዬ ሰይሜያቸዋለው፡

 


የዝነኛው አርቲስት ቴዎድሮስ ምትኩ (ቴዲ) የቀብር ሥነ-ስርዓት የፊታችን ቅዳሜ በሜሪላንድ ይፈጸማል

$
0
0

teddy mitiku 2

(ዘ-ሐበሻ) ከቀናት በፊት ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው ታዋቂው የሙዚቃ ሰው ቴዎድሮስ ምትኩ (ቴዲ) የቀብር ስነሥርዓት የፊታችን ቅዳሜ በሜሪላንድ እንደሚፈጸም ቤተስቦቹ ለዘ-ሐበሻ ድረ ገጽ ገለጹ።

ኖቬምበር 11 ቀን 1955 ዓ.ም በአዲስ አበባ የተወለደው ይኸው ታዋቂ የሳክስፎን ሙዚቃ ባለሙያ ህይወቱ ያለፈችው ባለፈው  ቅዳሜ  ዲሴምበር 22 ቀን 2013 በዋሽንግተን ዲሲ መሆኑን ዘ-ሐበሻ ከቀናት በፊት መዘገቧ ይታወሳል።

በሕዝብ ዘንድ እንደተወደደ የኖረው ቴዲ የፊታችን ቅዳሜ  ጸሎተ ፍትሃቱ እና የቀብር ስነ ሥርዓቱ በሜሪላንድ ስለሚፈጸም አድናቂዎቹ በብዛት ወጥተው እንዲሸኙት ቤተሰቦቹ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።

የጸሎትና ፍትሃቱ የሚደረገው ቅዳሜ ከጠዋቱ 9:30 በር ዕሰ አድባራት ደብረሰላም ቅድስት ማርያም ቤ/ክ ሲሆን አድራሻውም የሚከተለው ነው።
Re’ese Adbarat Debre Selam Kidest Mariam
The Ethiopian Orthodox Tewahedo Church
1350 Buchanan St. NW, Washington, DC 20011

ከዚያም የቀብር ስነሥርዓቱ በThe Gate of Heaven Cemetery 13801 Georgia Ave. Silver Spring, MD 20906 ይፈጸማል።

ቴዲን ለመሸኘት የወጣው ፕሮግራም የሚከተለው ነው፦
teddy mitiku
Saturday, December 28, 2013
5:15 AM
Teddy Mitiku’s Hearse Arrives at Re’ese Adbarat Debre Selam Kidest Mariam The Ethiopian Orthodox Tewahedo Church. The church is located on 1350 Buchanan St. NW, Washington, DC 20011.
6:00 AM
The procession of Teddy Mitiku’s casket (carried by six Ethiopian Artists) and family into the church will take place from the entrance on Buchanan Street.
6:00 AM – 9:15 AM
Regular church service will be conducted
9:30 AM – 10:45 AM
Wake ceremony
10:45 AM – 11:15 AM
Memory sharing from family and friends in attendance.
11:15 AM – 11:45 AM
Various Ethiopian artists honor Teddy Mitiku
11:45 AM – 12:00 PM
Preparation to commence procession. Teddy Mitiku’s final resting place will be at The Gate of Heaven Cemetery at 13801 Georgia Ave. Silver Spring, MD 20906
12:05 PM
The Procession will start from the intersection of 16 Street and Buchanan Street, the Procession will turn right onto 16th St
The Procession enters next roundabout and take the 3rd exit onto 16th St/MD-390 N (Crossing into Maryland)
The Procession then turn right onto Georgia Ave and arrives its destination at the Gate of Heaven Cemetery on the right.
Attention: Maryland and the District of Columbia law require that all drivers who participate in a procession must turn both their headlight and hazard lights
1:30 P.M.
Once Teddy Mitiku’s casket arrives at the Gate of Heaven Cemetery, burial ceremony begins.
After we finally lay to rest Teddy Mituku, Funereal Reception takes place at The Blair Apartment -East (next to Giant) 1220 East-west Hwy, Room # 119 (Hospitality Suite), Silver Spring, MD 20910
Place of Mourning until Sunday, December 29, 2013:
The Blair Apartment (East)
1220 East-west Hwy,
Room #119 (hospitality suite)
Silver Spring, MD 20910

አንድነትና የሚሊየንም ድምጽ ለነጻነት ንቅናቄ –አማኑኤል ዘሰላም

$
0
0

amanuelzeselam@gmail.com
ታህሳስ 15 ቀን 2006 ዓ.ም
 

የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር፣ አቶ ይልቃል ጌትነት፣ በዉጭ አገር የሥራ ጉብኘት እያደረጉ እንደሆነ በስፋት እየተዘገበ ነዉ። ታዲያ «ስለ ሰማያዊ ብዙ እየሰማን፣ የአንድነት ፓርቲ ድምጽ ግን ምነዉ ጠፋ። የሚሊየነሞች ድምጽ ለነጻነትስ ወዴት ገባ ?» ብለን የምንጠይቅ ልንኖር እንደምንችል አስባለሁ። በዚህም ረገድ በአንድነት ፓርቲ ዙሪያ አንዳንድ ሃሳቦች ለአንባቢያን ለማካፈል እሞክራለሁ።

በቅድሚያ አንድ መረዳት ያለብን ነገር አለ። የአንድነት ፓርቲና እና ሰማያዊ ፓርቲ፣ ሁለቱም ተመሳሳይ የፖለቲካ ፕሮግራም ቢኖራቸውም ፣ ሁለቱም ሰላማዊ በሆነ መንገድ ለዉጥ ለማምጣት ቢታገሉም፣ የአሰራር ልዩነቶች አሏቸው። የአንድነት ፓርቲ፣ ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግ የትግሉ አካል እንደሆነ ቢያውቅም፣ መሰለፍ ብቻ በራሱ ምንም ሊያደርግ እንደማይችል ጠንቅቆ የተረዳ ደርጅት ነዉ። በዚህም ምክንያት ግብታዊ የሆኑ እንቅስቃሴዎችን ከማድረግ ብዙ ይቆጠባል። ሰልፎችም ሆነ ማናቸዉም አይነት ሰላማዊ እንቅስቅሴዎች ተጠንተዉ፣ በጥንቃቄና ዉጤት በሚያመጣ መልኩ መደረግ አለባቸው ብሎ ያማናል። ካለፈው የቅንጀት ስህተቶች ብዙ የተማረ ነው።

በመሆኑም ሰልፍ አልተደረገም ማለት እንቅስቃሴ የለም ማለት አይደለም። የአንድነት ፓርቲ በአሁኑ ወቅት እያደረጋቸው ያላቸዉን አራት በጣም አስፈላጊና መሰረታዊ ጉዳዮች እንዳካፍል ይፈቀድልኝ፡

1. አንድነት፣ ከሰኔ እስከ መስክረም የተደረገዉን የሚሊየኖችም ድምጽ ለነጻነት እንቅስቃሴዎች፣ እንዲሁም የፓርቲዉ ጠቅላላ ስራዎች፣ ወደ ኋላ ተመልሶ ግምገማ እያደረገ ነዉ። «የቱ መስተካከል አለበት ? የቱ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ? ..»እየተባለ ፣ ጠቃሚ ትምህርቶችን ለማሰባሰብ እየተሞከረ ነዉ። ዝም ብሎ መሮጥ አይደለም። ቆም ብሎም ማሰብና እራስን መመርመር፣ ካለፉትን ተግባራት መማር ያስፈልጋል።

2. ፓርቲው በቅርቡ የአመራር አባላትን ይመርጣል። አብዛኞቹ አገር ዉስጥም ሆነ በዉጭ ያሉ ድርጅቶች አንድ መሪ ነው ለዝንተ አለም የሚመራቸው። የአንድነት ፓርቲን መጀመሪያ ብርቱካን ሚደቅሳ፣ ከዚያም ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራዉ፣ ከዚያም ዶር ነጋሶ ጊዳዳ መርተዋል። አሁን ደግሞ ዶር ነጋሶን ለመተካት ሶስት እጩዎች የምረጡኝ ዘመቻ ላይ ናቸው። እነርሱም የፓርላማ አባል የተከበሩ አቶ ግርማ ሰይፉ፣ ቀድሞ ፓርቲዉን ሲመሩ የነበሩትና በበርካታ አባላት እንደገና እንዲወዳደሩ ግፊት እንደተደረገባቸው የሚነገረዉ፣ አንጋፋው ኢንጂነር ግዛቸው እንዲሁም ኮንሴንሰን ቢልድ በማድረግና በአስተዋይነታቸው የሚታወቁት፣ በአሁኑ ወቅት ፓርቲዉን በፋይናንስ ሃላፊነት የሚመሩት፣ አቶ ተክሌ በቀለ ናቸው።ይህ በአንድነት ዉስጥ እየተደረገ ያለው ፉክክር ፣ በማንም የአገራችን ድርጅቶች ያልታየ ዴሞክራሲያዊ  ፉክክር ነዉ።

3. እርግጥ ነዉ ከአሁን ለአሁን ሕብረት ያስፈልጋል ተብሎ፣ ወደ ኋላ ከሚጎትትና ስራን ከማያሰራ ድርጅት ጋር ሕብረት አይፈጠርም። ሕብረት ሲፈጠር ለዉጤት መሆን አለበት። በዚህም ረገድ አንድነት ከዚህ በፊት አካል ከሆናቸው እንደነ መድረክ ካሉ ስብስቦች ጋር ያለዉን ግንኙነት እየፈተሸ ነዉ። በአንጻሩም ደግሞ ፓርቲውን ሆነ ትግሉ ወደፊት እንዲሄድ ሊረዱ የሚችሉ ፣ ከሌሎች ድርጅቶች ጋር ፣ የላይ ላይ ትብብር ሳይሆን የዉህደት እንቅስቃሴ እያደረገ ነዉ። ከዚህ በፊት እንደ ብርሃን ፓርቲ ያሉ ድርጅቶች ከአንድነት ጋር መዋሃዳቸው ይታወቃል። አሁን ደግሞ አንድነት ፓርቲ ከአንጋፋዉ መኢአድና በአሁኑ ወቅት አስደሳች እንቅስቅሴ በሜዳ ላይ አያደረገ ካለው ከአረና ጋር ለመዋሃድ ትልቅ ሥራ እየሰራ ነዉ።

4. ሰላማዊ ሰልፍ ሆነ ሌላም ሌላም እንቅስቅሴዎች እንዲሁ በግብታዊነት አይሰሩም። ጥናት፣ ጥንቃቄ፣ ዝግጅት ያስፈልጋል። የስሜት ትግል የትም አያደርሰም። ትግሉ የሰከነ፣ የበሰለና ዉጤት የሚያመጣ መሆን አለበት። የአንድነት ፓርቲ የሚሊየነም ድምጽ ለነጻነት በሚል ስም የጀመረው እንቅስቃሴ ክፍል ሁለት፣ ከአመራር አባላት ምርጫ በኋላ፣ ይታወጃል። ይህ እንቅስቃሴ አዲስ አበባ ዉስጥ ብቻ ያተኮረ ሳይሆን፣ በመላ አገሩቷ ያተኮረ፣ ትግሉን አንድ እርምጃ ወደፊት የሚወስድ እንቅስቃሴ ይሆናል። ለዚህም እንዲረዳ አባላት በሰላማዊ ትግል ዙሪያ የተለያዩ ስልጠናዎች እየወሰዱ ናቸው።

እንግዲህ አገር ዉስጥና ከአገር ውጭ ለምትኖሩ ኢትዮጵያዊያን እንዲህ እላለሁ። በአገራችን ሙስና የመስፋፋቱ፣ ዘረኝነት የመብዛቱ፣ የሕግ ስርዓት ያለመኖሩ፣ የኑሮ ዉድነቱ፣ የሰባአዊ መብት ረገጣዉ ፣ ኢትዮጵያ ለብዙሃኑ ሲኦል፣ ከገዢው ፓርቲ ጋር ግንኙነት ስላላቸው ብቻ በአጭር ጊዜ ዉስጥ ሚሊየንር ለሆኑት ለጥቂቶች ገነት ለመሆኗ ምክንያቱ የፖለቲካዉ ችግር ነው። የፖለቲካ ችግርን ለማስተካከል ደግሞ የፖለቲክ ትግል ይጠይቃል። የአንድነት ፓርቲ ይህ ለሰላምና ለፍትህ የሚደረገዉን የፖለቲክ ትግል ለመምራት እየሰራ ነዉ።

የአንድነት ፓርቲ ከሁለት ወራት በፊት ባደረጋቸው አገረ ሰፊ፣ የሚሊየም ድምጽ ለነጻነት እንቅስቃሴዎች፣ በአዲስ አበባ፣ በመቀሌ፣ በጎንደር፣ በባህር ዳር፣ በደሴ፣ በጂንካ፣ በአርባ ምንጭ፣ በወላይታ ሶዳ፣ በባሌ/ሮቢ ፣ በፍቼና በአዳማ ሰላማዊ ሰልፎች አድርጓል። በመቀሌ ሰልፉ ሊደረግ አንድ ቀን ሲቀረዉ የሕወሃት ባለስልጣናት «እንኳን አንድነት፣ ቅንጅትም መቀሌን አልደፈረም»በሚል የቅስቀሳ መኪናዎችን እና ማይክሮፎኖችን በማገታቸውና የአመራር አባላትን በማሰራቸው፣ ከአሥር አምስት ቀናት ቅስቀሳ በኋላ ሰልፉ ሊሰረዝ ችሏል። በባሌ/ሮቢ፣ ኦሕድዶች ሰልፉ ከመደረጉ አንድ ቀን በፊት፣ «ሰልፉን ካደረጋቸው ከፍተኛ ደም መፋሰስ ይሆናል» የሚል ዛቻ በመሰንዘራቸው ፣ ሕዝብን አደጋ ላይ ላለመጣል ሲባል፣ ሰልፉ ሳይደረግ ቀርቷል።

የአንድነት ፓርቲ በአዋሳ፣ በጋምቤላ፣ በወሊሶ፣ በድርደዋና በአሳሳም ሰልፎች ለማድረግ እቅድ ነበረዉ። ነገር ግን በገንዘብ ማነስ ምክንያት እነዚህ ከተሞች ሰልፍ ማድረግ እንዳልተቻለ ነው።

አሁንም ፓርቲዉ የተቻለዉን ለማድረግ የወሰነነ የቆረጠ ቢሆንም፣ ፓርቲዉ የሕዝብ ድጋፍ ከሌለዉ ሊያደርግ የሚችለው የተወሰነ ነዉ። በተለይም የገንዘብ አቅም ላይ ትልቅ ትኩረት መስጠት እፈልጋለሁ። እንዲሁ ለዉጥ ስለተመኘን ለዉጥ አይመጣም። አገር ቤት ያሉ ኢትዮጵያዉያን በጓዳና በሹክሹክታ ብሳታችንን መግለጽ ማቆም ይኖርብናል። ትግሉ የእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊን ተሳትፎ ይጠይቃል። ጠንካራ ፓርቲ ሲመጣ መቀላቀሉ ሳይሆን፣ አሁን ያሉትን፣  እንድ አንድነት ፓርቲ አይነቶችን ጠንካራ እንዲሆኑ ማድረጉ ይበጃል።

ዉጭ አገር ያለነው ፣ ምን እንኳን የመገደል፣ የመታሰር፣ የመዋከብ አደጋ ባያገኝንም፣ ቢያንስ ስራችን እና አፋችን መገናኘት ያለባቸው ይመስለኛል። «አገር ቤት ካሉት ድርጅቶች ለዉጥ ለምን አያመጡም» ብለን መናገርና መጠየቅ ሳይሆን፣ ለዉጥ እንዲያመጡ የነርሱ አካል ሆን ድጋፋችንን መስጠት ይጠበቅበናል። ሕዝቡ ካልተነሳና ካልተነቃነቀ በምን ሁኔታ ለዉጥ ሊመጣ አይችልም። ህዝቡ እንዲነሳ ሕዝቡ መሃከል ሆኖ ትልቅ ድርጅታዊ ሥራ መስራት ያሰልጋል። ይህን አይነት ድርጅታዊ ሥራ ለመስራት፣ ሕይወታቸው ለዚህ ሥራ አላልፈው ከሰጡ አገር ቤት ካሉ ጀግኖች ጎን መቆም ይኖርብናል።

እንግዲህ ለሚሊዮኖች ድምጽ ለነጻነት እንቅስቃሴ ክፍል ሁለት ከወዲሁ ሁላችንም እንዘጋጅ። ፓርቲዉን በገንዘባችን እንደግፍ። በገንዘብ ለመርዳትና ከሚሊዮኖች አንዱ ለመሆን የሚፈልጉ ከሆነ የሚከተለዉን ድህረ ገጽ ይጎብኙ !

http://www.andinet.org/

 

comment pic

 

 

ትንሽ ስለጃዋር መሀመድ _ ከዓለማየሁ መሀመድ

$
0
0

ሁለት ነገሮችን ላንሳ።

1.  የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ትግል መሬት አንቀጥቅጥ ሆኖ ለሁለት ዓመት ገደማ ዘልቋል። በዚህ ትግል ውስጥ በሀገር ቤት ከስርዓቱ ጋር አንገት ለአንገት ተናንቀው ደም ህይወታቸውን ገብረው ትግሉ በማይናወጥ ጽናት ላይ እንዲቆም ያደረጉት ብዙሃኑ ሙስሊሞች ዋጋቸው በክብር መዝገብ ላይ ምንጊዜም ወርቃማ በሆነ ቀለም ተመዝግቦ ይቀመጣል። ከእነሱ ባሻገር በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ትግሉ መሬት ይዞ  በሰከነ መልኩ እንዲጓዝ ያደረጉት አስተዋጽኦም የሚዘነጋ አይደለም። ጃዋር በዚህ ውስጥ ስሙ ሲጠቀስ ነበር። የሙስሊሞች ትግል ላይ ትንሽም ብትሆን አሻራው አርፎበታል። ያኔ ነው። በፊት። አሁንስ?

2.  የኦሮሞ ህዝብ ጭቆና ከሌላው የኢትዮጵያ ህዝብ የተለየ ነው- አይደለም -የሚለው ክርክር ለጊዜው ይቆይና የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ለ40 ዓመታት ሲያቀነቅነው የነበረውና ውጤት ሳይኖረው ዘመናት የቆየው ትግሉ አሁን ‘’የኦሮሞን ህዝብ ትግል በኢትዮጵያ ጥላ ስር’’ የሚለው ሀሳብ አሸንፎ ሲወጣ ጃዋር ብቅ አለ። መጀመሪያ ላይ በሳል በሆኑ፡ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ፡ የሰውን ልጅ በአንድ መነጽር የሚመለከቱ የሚመስሉ ሀሳቦች በጃዋር አፍ ውስጥ ይዋኙ ነበር። ይህም በተቀረው ኢትዮጵያውያን ዘንድም ጃዋር ምናልባት ያረጀውን የኦነግ ጠባብ ብሄርተኝነት ከመቃብር አስቀመጦ የኦሮሞን ህዝብ ከዕውነተኛ ድል የሚያቀርብ አዲስ መንገድ ይጀምራል የሚል ብጣቂ ተስፋ ውስጣቸው የነበሩ ጥቂቶች አልነበሩም። ከመነሻውም የተጠራጠሩት፡ የተደበቀው ማንነቱ አንድ ቀን ይወጣል ብለው በጥርጣሬ ሲመለከተቱት የነበሩት ቁጥራቸው የትየለሌ ነበር። ሆኖም እኔም ሆንክ ጥቂቶች ጃዋርን እንደ አብሪ ኮከብ መመልከታችን አልቀረም። አሁንስ?

ጃዋር አሁን አይሰማም። መስማት የሚፈልገው የፈለገውን ብቻ ነው። በየአዳራሹ የሚሰማው ጭብጨባ ሰርቆታል። ቀልቡ አሁን ከሚኒሶታ እስከ ለንደን በተዘረጋው የ’ኦሮሞ ፈርስት’ ቅልጥ ያለ የወቅቱ ነጠላ ዜማ ላይ ሆኑዋል።

1. የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ትግል በእፎይታ ጊዜ ላይ ቢሆንም የጃዋር ‘ኦሮሞ ፈርስት’ በይፋ ከታወጀችና ‘ሜንጫ’ዋ በሚኒሶታ መድረክ ከተስተጋባች በኋላ የሙስሊሞች ትግል ላይ መጠነኛ ተጽእኖ መፈጠሩ አልቀረም። የሙስሊሙን ትግል የኢትዮጵያ ህዝብ ትግል አድርገው የተሰለፉ ወገኖች በጥቂቱ ማፈግፈጋቸው በመጠኑ ይታያል። ሜንጫ የሚለውን ቃል ጃዋር ሚኒሶታ ላይ ካፈነዳት ወዲህ በሙስሊሙ ማህበረሰብ ዘንድ እንኳን ውዥንብር ተፈጥሯል። እናም የሟችዋ ሚካያ በሃይሉ ዜማን ልዋሰው- “ሸማመተው”::  ህወሀት ሸመተ:: ትግሉ እንዲደበዝዝ ቀን ከሌት ይመኝ የነበረው ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ- ሸማመተው!!

2.  ከምንጊዜውም በላይ የኢትዮጵያ ህዝብ አንድነቱን ለማሳየት፡ በጋራ ወደ ምር ነጻነት ለመምጣት እጅ ለእጅ እየተያያዘ ያለበት ወቅት ላይ እነጃዋር የኦሮሞ ብሄርተኝነትን ወደ ጠባቡ ጽንፍ ወስደውት ዘራፍ ማለት መጀመራቸው በተወሰነ ደረጃ ለህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ ከሰማይ የወረደ አዱኛ ሆነለት:: አሁንም ሚካያ ትላለች -“ሸማመተው” – ህወሀት ሸመተ::

እነ ጃዋር እየተናገሩ ነው:: ‘ኦሮሞ  ፈርስት’-‘ ማይ ካንትሪ ኢዝ ኦሮሚያ’ ::  የህወሀት የፌስቡክና ትዊተር ሰራዊቶች ስማቸውን በኦሮምኛ ለማድረግ ከብርሃን ነበር የፈጠኑት:: እናም ‘ኦሮሞ  ፈርስት’  መፈክራቸው ሆኖ አጼ ሚኒሊክ ላይ እርግማናቸውን ውእግዝ ከማርዮሱን እያዘነቡት ነው።

ጭብጨባው ቀልጧል። ነጠላ ዜማው ሰማይ ምድሩን አድምቆታል፡፡ እነጃዋር በህወሀት ነጠላ ዜማ ዳንሱን እያቀለጡት ነው። የሚሰማ ጆሮ የላቸውም። ልባቸው ሸፍቷል። አውቀው ይሁን ሳያውቁት ከህወሀት መንደር ዘልቀው የልፊያ ፖለቲካውን ተያይዘውታል። ጭብጨባ ክፉ ነው። ላላወቀበት ስካር ነው።

ሰሞኑን ከጨፌ ኦሮሚያ አንድ መረጃ ደርሶኛል። ሳይላመጥ አይቀርብም በሚል ለጊዜው ይዤዋለሁ። እነጃዋርን የተመለከተ ነው። ምናልባት መረጃውን በማስረጃ ማስደገፍ ከቻልኩኝ በድብቅ የተፈጸመውን የእነጃዋርንና ህወሀትን ጋብቻ ይፋ አደርጋለሁ።

እስከዚያው ጩኧቱን እየሰማን እንቆይ። መልካም ጋብቻ የምንልበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም።

comment pic

ሰላማዊ ትግል እና ባህሪያቱ: ስልጠና ክፍል አምስት፥ ከ1924 – 2002 በኢትዮጵያ የተደረጉ ምርጫዎች ግምገማ –በግርማ ሞገስ

$
0
0

በግርማ ሞገስ
ቅዳሜ ታህሳስ 12 ቀን 2006 ዓ.ም.

Girma Moges

ግርማ ሞገስ

የስልጠና ክፍል አምስት ግብ በዐፄ ኃይለስላሴ ዘመነ መንግስት (1924-1967)፣ በደርግ ዘመነ መንግስት (ከ1967 – 1983)፣  (3ኛ) በህውሃት/ኢህአዴግ ዘመነ መንግስት (1983 – 2002) የተደረጉትን ምርጫዎች በአጭር በአጭሩ መጎብኘት እና  መገምገም ነው። ምርጫ 97 ግን በርከት ያሉ ትምህርቶች በመለገሱ ሰፋ አድርገን እንጎበኘዋለን።
ምስጋና፥ ይኽን ግምገማ ሳዘጋጅ ከሌሎች መረጃ ምንጮች በተጨማሪ “ግንቦት 7” በሚል ርዕስ ክፍሉ ታደሰ ስለ ምርጫ 97  ዝግጅት፣ ሂደት እና አፈጻጸም የጻፈውን መጽሐፍ አና “ነፃነት እና ዳኝነት” በሚል ርዕስ ስየ አብርሃ ከጻፈው መጽሐፍ ውስጥ  ስለምርጫ 97 አንስቶ ምክሮች የሚለግስበትን ጠቃሚ ምዕራፍ ተጠቅሜያለሁ። እንዲሁም የታሪክ ባለሙያዎቹን የባህሩ  ዘውዴን እና የተክለ ፃድቅ መኩሪያን መጽሐፍቶች ተጠቅሜያለሁ። ለሁሉም ምስጋናዬ ገደብ የለውም።   – ቀጣዩን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ–

የሳዑዲ ጉዳይ፡ “31.700 በላይ ኢትዮጵያውያን የቤት ሰራተኞች ከአሰሪዎቻቸው ጠፍተዋል! “

$
0
0

ነብዩ ሲራክ ከሳዑዲ አረቢያ

(ፎቶ ፋይል)

(ፎቶ ፋይል)

የማለዳ ወግ … የተረሱት ኢትዮጵያውያን የኮንትራት ሰራተኞች በጭንቁ ቀን! 

“31.700 በላይ ኢትዮጵያውያን የቤት ሰራተኞች ከአሰሪዎቻቸው ጠፍተዋል! ”
እለተ ሃሙስ ታህሳስ 17 2006 የወጣው አረብ ኒውስ ” Over 31,000 Ethiopian maids ran away “ሳለፍናቸው አመታት ወደ ሳውዲ መጠው ከነበሩት ኢትዮጵያን መካከል ከ 31 ሽህ በላይ የቤት ሰራተኞች ከአሰሪዎቻቸው ጠፉ !” የሚለውን ዜና የሳውዲ መንግስት ስታስቲክ መረጃ ጠቅሶ አስነበበን ። አረብ ኒውስ ያስተላለፈውን መረጃ ካነብኩ ትዝ ያለኝ በተለያዩ የሳውዲ ከተሞች እንደ ጨው የተበተኑት በኮንትራት ስራ የመጡ የተረሱት በኮንትራት ሰራተኝነት ከቤተሰብ ጀምሮ በደላላ ፣ በመንግስት ሃላፊዎች ብልሹ አሰራር እዚህ በሰው ሃገር ለከፋ አደጋ የተዳረጉት የኮንትራት ሰራተኞ እህቶች ጉዳይ ነው ። አዎ የእኒህ እህቶች መዳረሻ ባለመታወቁ አበሳቸው ዘልቆ ቢያሳስበኝ የማለዳ ወጌ ቅኝት ለማድረግና የማውቀውን መረጃ ለማስጨበጥ ብዕሬን ለማንሳት ተገደድኩ …

“ከጨለማው ህዳር” እስከ ታህሳስ አጋማሽ …

በህዳር መባቻ ግፍ ተጭኖናል የዘንድሮን ህዳር ጨለማ ማለታችን ቢያንስ እንጅ አይበዛበትም። በጨላማው ህዳር ድህነትና የኑሮ ውድነት በለምለም ሃገራችን ተደላድለን እንዳንቀመጥ ያደረገን ስደት ዛሬ የከፋ ሆኗል። እንዲከፋ ምክንያቶቹ ብዙ ቢሆንም በአቋራጭ ኑሯቸውን ለመቀየር የቋመጡት ህገ ወጥ አንዱ መሆኑና ይህም የጥቂቶች ባላስፈላጊ ስራ መሰማራት ስማችን አክፍቶት ለሃጣን የመጣው ለጻድቃን እንዲሉ በላባቸው ለሚያድሩት መፈናቀል ምክንያት መሆኑን ሳልጠቅሰው ማለፍ አልወድም ። እናም ዛሬ የመቶ ሽወች ኑሮ ተናግቷል! በጨለማው ህዳር!

በጨለማው ህዳር በዋና ከተማዋ በሪያድ የመንፉሃን ግርግር ተከተለ። የታየው ሁከት የብዙዎቻችን ትኩረት ሳበው! ትኩረቱ ያተኮረውህጋዊ ሰነድ የሌላቸው በተለይም የመንን ድንበር ተሻግረው ፡ ሃጅና ኦምራን ታከው የመጡት ዜጎች ጉዳይ ሆነ ! በግርግሩ የታየውን ጭካኔ በመፍራት የመንፉሃ ነዋሪ ያገሬ ሰው ጎጆውን እያፈራረሰ ሃገሩን ጥሎ ወጣ … ተሸኘ ! የሳውዲ መንግስትን ጨምሮ የኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ ባልጠበቁት ሁኔታ እዚህ ባደረሰን ሁለት ወር በተጣጋው ጊዜ ወደ 160 ሽህ የሚገመት ወገን ወደ ሃገሩ መግባት ከአስገራሚም አስገራሚ ነው ተባለ ። ከሪያድና ከምዕራቡ የሳውዲ ክፍል አንዳንድ ከተሞች የወጣውን ነዋሪ ብዛት የተመለከተ ባይተዋር ቁጥሩን በአግርሞት ቢመለከተው አያስገርምም ። እኛ በሳውዲ ውስጥ የባጀን የከረምን ግን “ጅዳ መች ተነካና ትገረማላችሁ ፣ ጀዛን ፣ አብሃ ፣ ከሚስ ምሸት ፣ ጣይፍና እና በሌላ ሌላው የከተመው ኢትዮጵያዊ መች ተነካና ትገረማላችሁ ? ” ማለት ያዝን … በቀቢጸ ተስፋ ወደ ሃገር መግባቱን አሻፈረኝ ያለው አድፋጩን ሰነድ የሌለውን የተጨነቀ ወገን ” ከሳውዲ ውጡ ” ከሚለው ጋር ሌላ ተደጋግሞ የተነገረ ግን ስላልተቀበልነው ልብ ያላልነውን መረጃ ቆንስልና ኢንባሲዎች ይዘውት ብቅ አሉ ። በቀጣዩ መጠነ ሰፊ የማጣራት ዘመቻም ከአሰሪው (ከከፊሉ) ጋር የማይሰራ እንደ ህጋዊ ስለማይቆጠር የሳውዲ መንግስት በፈቃደኝነት እጃቸሁን ሰጥታችሁ ወደ ሃገር ግቡ ሲል ደጋግሞ አስታወቀ ። ወደ ሃገር መስደድ እንደተጠናቀቀ አንወጣም ባሉት ላይ ፍተሻ በማድረግ በእስራትና በገንዘብ እንደሚቀጣ ኢንባሲና ቆንስል መስሪያ ቤቶች ሲያስታውቁ ወሽመጡ ያልተቆረጠ አለ ለማለት እቸገራለሁ ። እንዲህ እያልን የቆጥ የባጡን እያነሳን እየጣልን “ወደ ሃገሩ መግባት ሲገባው ሳይገባ የቀረው ቁጥር 80 ሽህ ፣100 ሽህ ፣150 ሽህ ይደርሳል !” ያለን ስነዘባራ መንፉሃ ዳግም በፍተሻ ትናጥ ያዘች! ረቡዕ ታህሳስ 16 2006 …

ለአንድ ማለዳ ወግ ቅኝቴ ይሆን ዘንድ ነፍሴ ፈቅዳለችና እናወጋዋለን!

ከጅዳ የሽሜሲ ጊዜያዊ ማቆያ የሚደርሰኝ ሮሮ !

“የሳውዲ መንግስት ህጋዊ ሰነድ የሌላቸው ሳውዲን ለቀው አንዲዎጡ ያስተላለፈውን እና የኢትዮጵያ ኢንባሲና ቆንስለወ መስሪያ ቤቶች ዜጎች ሀጉን አክብረው ወደ ሃገራቸው እንዲወጡ
ያስተላለፉትን ተደጋጋሚ ማሳሰቢያዎች በመረዳት ወደ ሃገር ለመግባት ወደ ሽሜሲ መጠለያ በመሄድ እጃችን የሰጠን ዜጎች እየተንገላታን ነው! ” በማለት ሮሮና ቅሬታቸውን ያቀረቡ ወገኖች መጠለያ እንደገቡ በኢትዮጵያ መንግስት የመጓጓዣ ሰነድ የተሰጣቸው ቢሆንም የሳውዲ ፖስፖር ሃላፊዎች የቀረበላቸውን ሰነድ በማጣራት የመውጫ ሰነድ ለመስጠት አንግልት አያደረሱባቸው መሆኑን ገልጸውልኛል። ጉዳያቸውን ለማስፈጸም በአውቶቡስ ላይ እና በመጠለያው ግቢ ውስጥ ተበትነው በመጠባበቅ ላይ እንደሆኑ የገለጹልኝ እኒህ ወገኖች የአቅመ ደላማ ሴቶችና ህጻናትን እንግልት ከግምት ውስጥ በማስገባት የጅዳ ቆንስል ሃላፊዎች ከሚመለከታቸው የሳውዲ መንግስት ሃላፊዎች ጋር በመነጋገር አስፈላጊውን ትብብር ያደርጉላቸው ዘንድ ጠይቀዋል።

እኒሁ ሮሯችን ለሚመለከታቸው እንዳሰማ የተማጸኑኝ ወገኖች ወደ ጅዳ ቆንሰል ሃላፊዎች ስልክ ደውለው ስልክ ስለማያነሱ ወደ እኔ መደወላቸውን የገለጹልኝ ሲሆን ወደ ሃገር ግቡ ተብለን ወደ ሃገር እንግባ ባልን እንግልት ሊደርስብን አይገባም ሲሉ ” አሁን በደል እያደረሰብን ያለው ሳውዲ ኢሚግሬሽን መፍትሄ እንዲሰጠን ዲፕሎማቶች የተቻላቸውን ያድርጉልን! ” ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል ። በሌላ በኩል ወደ መጠለያው ገብተው አስፈላጊውን ሰነድ ያሟሉ አንዳንድ ነዋሪዎች መካከል ሻንጣችን ጠፋብን የሚሉና ከአንድ ሻንጣ በላይ እንዳይዙ የተከለከሉ ነዋሪዎችም ተመሳሳይ ቅሬታቸውን ገልጸዋል።

ጉዳዪን ለማሳወቅና ዝርዝር ማብራሪያ ለማግኘት ወደ ጅዳ ቆንስል ሃላፊ ወደ አቶ ዘነበ ከበደ እና ወደ ምክትላቸው አቶ ሸሪፍ ስልክ በመደወል ያደረግኩት ሙከራ ዛሬም አልተሳካም!

ሰላም ለሁላችሁ ይሁን!

ነቢዩ ሲራክ

በሚኒሶታ የደብረሰላም መድሃኔዓለም ቤ/ክ ምእመናን “የሕዝብ ድምጽ ይከበር”ሲሉ መግለጫ አወጡ

$
0
0

የሚኒሶታው ደብረሰላም መድሃኔዓለም ቤ/ክ በገለልተኝነት እንዲቆይ በሕዝብ ድምጽ ብልጫ መወሰኑ ይታወሳል። ሆኖም ግን ይህን ውሳኔ የቤ/ክርስቲያኑ ካህናት ለመቀልበስ ጥረት በማድረግ ላይ መሆናቸውን በመግለጽ ለሰላም እና ለአንድነት የቆሙት ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ምእመናን የሚከተለውን መግለጫ አውጥተው በትነዋል።

12/26/2013

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ ፤አሜን!

ለሚኒሶታ ደብረሰላም መድኃኔዓለም የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ምዕመናን

የሕዝብ ድምጽ ይከበር!!! የምንኖርበትን አገር ሕግና ሥርዓትም እናክብር!!!

deb

ባለፈው ዲሴምበር 15/2013 ዓ.ም የቤተክርስቲያናችን ጠቅላላ የአባላት ጉባኤ የደብረሰላም መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን የአስተዳደር ገለልተኝነት አስመልክቶ ባለበት እንዲቀጥል በከፍተኛ የአብላጫ ድምጽ መወሰኑ ይታወቃል። ይህም ታሪካዊና አርአያ የሆነ፤ ዲሞክራሲያዊ አሰራር የሰፈነበት ስብሰባ ይበል የሚያሰኝ ነው።

የሕዝብ ውሳኔም ከማንምና ከሁሉም በላይ ስለሆነ ማክበርና ማስከበር ደግሞ የሁላችንም ኃላፊነት ነው። ይሁን እንጂ አንዳንድ የአስተዳደር ቦርድ አባላት ድርሻና ኃላፊነታቸውን በቅጡ ያልተረዱ ካሕናት ይህንን የሕዝብ ውሳኔ በተዛባ መልክ በመተርጎም የተላለፈውን ውሳኔና ወደፊት ቢደረጉ ይጠቅማሉ ተብለው በሀሳብ ደረጃ የቀረቡትን በመደባለቅ ሰላምና አንድነትን ለማወክ የሚደረገው አካሔድ እጀግ አሳዝኖናል አስቆጥቶናል።

በተለይም የቤተክርስቲያኑ ተቀዳሚ ካህን/ መንፈሳዊ አባት ከኃላፊነታቸው ውጪ የጠቅላላው ስብሰባ ውጤትን ካሕናቱ ባቀረብነው ሃሳብ መሰርት ነው የተወሰነው በማለት ሕዝቡ ከወሰነው ውሳኔ በተዛባ መልኩ መናገራቸው የሕዝብን ድምጽ እንደመናቅ ሆኖ አግኝተነዋል። ሕዝቡ በምን ላይ ድምጹን እንደሰጠ ጠንቅቆ ያውቀዋል። የስብሰባውንም ውጤት ለሕዝብ የመግለጽ ሥልጣንና መብት ያለው የቦርዱ ሊቀመንበር ብቻ ናቸው።

በቤተክርስቲያናችን የመተዳደሪያ ደንብ አንቀጽ 6 ክፍል 3 ፊደል ’ሀ’ ተ.ቁ. 6 ላይ የቤተክርስቲያኑ ይፋዊ/ኦፊሴሊያዊ/ ቃል አቀባይ የቦርዱ ሊቀመንበር መሆኑን በግልጽ ይደነግጋል። በመተዳደሪያ ደንቡ አንቀጽ 7 በፊደል ‘ሠ’ ላይም የቤተክርስቲያኑ ተቀዳሚ ካህን እንደማንኛውም የባላአደራዎች ቦርድ አባልነታቸው ለቤተክርስቲያኑ መተዳደሪያ ደንብ ድንጋጌዎች ሁሉ ተገዢ ናቸው ይላል። ስለዚህ ይህ አካሔድ በአስቸኳይ ሊታረም ይገባዋል እንላለን።

ከዚህም በተጨማሪም በሥርዓተ ቅዳሴ ም.2 ቁ 43 ላይ ማንም ቅዳሴውን ማወክ እንደማይገባው እንዲህ በማለት ይገልጻል። ‘ ክቡር ሚስጢርን ለመቀበል የተሰበሰቡ ምእመናን ሁሉ የእግዚአብሔርን ነገር ለመስማት ከቤተክርስቲያን ውስጥ በጸጥታ ይቁሙ። የሚናገርም የሚስቅም አይኑር፤ቤተክርስቲያን የነገር ቦታ አይደልችምና የጸሎት ቦታ ናት እንጂ። ’ ይህንን የሚያውቁ ካህናት ግን የቤተክርስቲያናችንን ሰላምና አንድነት ለማናጋት የሕዝቡን ውሳኔ ላለመቀበል ከሚያንገራግሩ ሰዎች ጋር ወንጌል እየተሰበክ በመቅደስ ውስጥና ከመቅደስም በመውጣት ስብሰባ በማድረግ ቆመንለታል የሚሉትን ሥረዓተ ቅዳሴ ራሳቸው ሲጥሱት ተስተውለዋል። ይህም ድርጊት ፈጽሞ መደገም የማይገባው ነው በማለት እንመክራለን።

የምንኖርበትን አገር ሕግና ሥርዓት ተከትሎ በሰላም እያመለከ ያለን ግለሰብም ሆነ ስብስብ በማንኛውም መንገድ መረበሽና ሰላምን ማደፍረስ፣ ረብሻን ማነሳሳትና ከሥረዓት የወጣ ድምጽ ማሰማትም ሆነ ተቃውሞ ማድረግ በአሜሪካ የወንጀለኛ መቅጫ ሕግ 9/42 መሰረት የሚያሰቀጣ ነው።

ምንም እንኳን ክርስትና ወንድምን/እህትን በአለማዊ ፍርድ ቤት ከሶ ማስቀጣትን ባይደግፍም ለቤተክርስቲያናችን ሰላምና ሥርዓት መከበር ስንል ከሥርዓት በመውጣት ሰላማችንን ለማደፍረስ

የሚሞክሩትን ሁሉ ለሕግ አካላት የምንከስ መሆኑን አበክረን እናስገነዝባለን። ሕግን አለማወቅ ከቅጣት አያድንም እና!

በሕዝብ በተላለፈው ውሳኔም ሆነ በቤተክርስቲያኑ አስተዳደር አቋም ላይ ቅሬታ አለኝ የሚል ሁሉ ይግባኙን አግባብንት ላለው አካል በሕጋዊ መንገድና ሥርዓትን በተከተለ መልኩ ብቻ ማቅረብ ይኖርበታል። ካሕናቱም ቢሆኑ በዚህ አገር የቤተክርስቲያናት ማቋቋሚያ ሕግጋት የሚመሩና የሚተዳደሩ እንጂ አሜሪካን አገር ላይ በሥራ ሊውል በማይችል የኢትዮጵያ የቤተክርስቲያን ማስተዳደሪያ ደንብ መሰረት የሚተዳደሩ እንዳልሆኑ ሊያውቁ ይገባል።

ስለሆነም የክርስትና ሕይወታቸው ብቻ ሳይሆን ሥጋዊ ሪከርዳቸውና ሕይወታቸውም ቢሆን ችግር እንዳይገጥመው ሊያስቡበት ይገባል እንላልን። ሕግን ባለማወቅ ወይንም ባለመረዳት በሌሎች አካባቢዎች ሁከት በመፍጠር በቤተ ክርስቲያን ላይ የደረሰው ሥርዓት አልበኝነት በሚኒሶታ ደብረሰላም መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ላይ ፈጽሞ እንዲከሰት አንፈቅድም።

ለሰላምና ለአንድነት የቆሙ ምእመናን

እኛና እነሱ/ ዝቅ እንበል/ በጌዲዮን ከኖርዎይ

$
0
0

እኛና እነሱ/ ዝቅ እንበል/

ጌዲዮን ከኖርዎይ

Norway

በአለም ላይ ካሉ ሃገሮች ውስጥ ስልጣን የሌለበት ሃገር ቢኖር ወይም ባለስልጣኑ ህዝብ የሆነበት ሃገር ቢኖር ሳላጋንን ኖርዎይ የምትባለው ሃገር ናት ማለት እችላለሁ፥፥ በግልፅ ህዝቡ የሚፈልገውን፥ ያስተዳድረኝ እገዛለታለሁ ብሎ አምኖ ድምፁን የሚሰጥለት መሪ፥፥ መሪውም ከልቡ እራሱን ዝቅ አርጎ ለሃገሩ፥ ለወገኑ የሚሰራበት ሃገር፥፣ ህገመንግስቱ ወይም በኖርዌጅያኑ አጠራር /GrunnLov/ ለሁሉም እኩል የሚሰራና ተፈፃሚ የሚሆን፥፥

በቃ ዋናው ነገር ህገመንግስቱን አትንካ ነው፥፥
አስታውሳለሁ በአንድ ወቅት የአለም መንግስታት ተባብረው ቢንላዲንን ለመደብደብ ብለው አፍጋኒስታንን በሚደበድቡበት ወቅት የኖርዎይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለተለያየ የስራ ጉዳይ በሚል በብዛት ወደ አፍጋኒስታን ይመላለሱ ነበርና እዛም ሲመላለሱ በአፍጋኒስታኖቹ ባህል ስጦታ የተለመሰ ነገር በመሆኑ ለካ አቶ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርዬ አንድ ምንጣፍ በስጦታ አጊንተው ሲመለሱ ስጦታው ወደድ ያለ ሆኖ እያለ ለኖርዌጂያን ግብር ስብሳቢ ቢሮ ወይንም /tax Administration/ ማስመዝገብ ሲገባቸው ዘንግተውት በኖርዎይ ትልቅ መነጋገሪያ ርእስ ሆኖ ሚዲያዎች ቁም ስቅላቸውን ሲያበሉአቸው ነበር፥ እንዲሁም ባንድ ወቅት የትራንስፖርት ሚኒስትርዋ በአንድ ወቅት አነስተኛ መርከብ ለመመረቅ ተጋብዘው በሄዱበት ወቅት ከአንድ ባለሃብት የእጅ ሰንሰለት የወርቅ በስጦታ አጊንተው እሳቸውም ዋጋው ውድ መሆኑን በለመረዳት ይመስላል ሳያስመዘግቡ በመቅረታቸው ሚዲያዎች ነገሩን ይደርሱበትና ካራገቡት በኋላ ታክስ አስቆርጠውባቸዋል ሚኒስቴርዋም ስጦታውን በመቀበላቸው እንደተፀፀቱ ለህዝባቸው ተናግረዋል፥፥
አሁን ግን ይህችን አጭር ፅሁፍ ለመፃፍ ያነሳሳኝ ከዚሁ ከኖርዎይ ሳልወጣ በዚህ በፈረንጆች ገና ዋዜማ በኖርዎይ ውስጥ ተሆነውን በሃገራችን ህልም ሳይሆን ቅዠት ወደሆነብኝ ነገር ልውሰዳችሁ፥፥
ከሶስት ወር በፊት በሴፕቴምበር 2013 በኖርዎይ በተደረገው የጠቅላይ ሚኒስቴር ምርጫ ተሸንፈው ስለጣናቸውን ያስረከቡት በኖርዎይ ምናልባትም ቁጥር አንድ ተወዳጅ ናቸው የሚባልላቸው የንስ ስቶልተንበርግ እንደውም ለምርጫው ጊዜ ታክሲ ሾፌር ሆነው ቅስቀሳ ሲያረጉ በነበረበት ጊዜ በኢሳት፥ በቢቢሲ የተዘገበላቸውhttp://ethsat.com/video/esat-kignet-taxi-shofieru-prime-minister/ የነበሩት ጠቅላይ ሚኒስቴር ለአሁኑ ገና በአል ዋዜማ ስራ ከለቀቁ በኋላ የመጀመርያ ስራቸው ያረጉት የገና ዛፍ መሸጥ ነበር፥፥
ዜናውን ሳየው ብዙም አልደነገጥኩም፥ ግን ቅናት አደረብኝ እንደውም ተስፋ ነው የቆረጥኩት፥፥
ሰውዬው እንዳልኩት በአንድ ወቅት በተለይ ኢኮኖሚ ክራይስስ ተብሎ አውሮፓውያኑ እየተጨናነቁ በነበረበት ወቅት ሃገራቸውን በብቃት ችግሩ ባጠገቧም ሳይደርስ ስላሳለፉት የሃገሪቷ ቁጥር አንድ ተወዳጅ ሰው ከንጉሱም በላይ ተብሎ ሚዲያ ላይ ወቶ እንደነበር አስታውሳለሁ፥ ሃብታም ናቸው፥ እውቀት አላቸው በነገራችን ላይ አባታቸውም የኖርዎይ ጠቅላይሚኒስቴር ሆነው አገልግለዋል፥፥ ብቻ ለማጠቃለል ያህል ሰዎቹ ከራሳቸው በላይ የሚያስቀድሙት ብዙ ነገር ዓላቸው፥ ህዝባቸው፥ ሃገራቸው፥ አላማቸው፥ ግባቸው፥ ሌላም ሌላም
እንግዲህ እስካሁን ስለ እነሱ ነው ያወራሁት ግን እኛስ?

እኛ ማን ነን?
ለምንድነው የምንታገለው?
ለማን ነው የምንታገለው?
ምንድነው አላማችንና ግባችን?
ወደኛ ሲመጣ ይህ ጥያቄ ለሁላችን በግለሰብ ደረጃ መልስ ሊያገኝ የሚገባው ጥያቄ ይመስለኛል፥፥
ዝቅ እንበል!
እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ!


የዘፋኞቻችን ሞራልና ስብእና

$
0
0

ከጥበቡ ተቀኘ

የሃገራችንን የሙዚቃ ስራ ድሮ በሽክላ ኋላ ላይ በካሴት አሁን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ በሲዲ ታትሞ ገበያ ላይ ሲቀርብ እንገዛና ከማዳመጥና ከማጣጣም አልፈን እንደ ቅርስ በየቤታችን የምንወዳቸውን ዘፋኞች ስራ እናስቀምጥ ነበር:: ከዚሁ ጉዳይ ጋር ተያይዞ የለመድናቸው የሙዚቃ ቤት ስሞችም ነበሩን ታንጎ ፣ አምባሰል ፣ ሶልኩኩ ፣ ኤሌክትራ ፣ ዜድ… አድራሻችን ከመርካቶ ዝቅ ብሎ፣  ከአውቶቡስ ተራ አጠገብ ፣ አንዋር መስጊድ ፊት ለፊት… ግጥም ይልማ ገብረአብ ፣ ዜማ አበበ መለሰ ፣ ከመድረክ የቀረጸው ከድር ጭቅሳ… የሚሉ ጽሁፎች በየካሴትና ሲዲው ላይ ይታይ እንደነበር ካስታወስኩኝ በኋላ ወደ ዛሬ ዋናው ጉዳዬ እገባለሁ::

radar_teddy_afro_back_smiling

ኣሁን በተለይ ያለፉትን ሶስትና አራት አመታት ትላልቅ የማስታወቅያ ባነሮች ላይ የዘፋኙ ፎቶ አጠገብ በጣም በትልቁ ሜታ ቢራ፣  ቅዱስ ጊዮርጊስ ቢራ፣  በደሌ ቢራ፣  ባቲ ቢራ፣ ሐረር ቢራ… የሚል ማስታወቅያ ማየት የተለመደ ነገር ሆኗል::በጣም የሚገርመው ደግሞ ዘፈኖቹን ልንሰማ ሲዲውን ስንገዛው ከሲዲው ጀርባ ይሄንኑ የቢራ ማስታወቅያ ቤታችን ይዘነው እንመጣለን:: እኔ ይሄንን ካየሁ በኋላ ለልጆቼማ ኑ በቢራ ተደሰቱ የሚል ማስታወቅያ ያለበት ሲዲ ይዤ ላለመግባት ወስኜ መግዛቱንም ትቼዋለሁ:: ሙዚቃው በሙዚቃ ቤት ብቻ ሳይሆን በቢራ ፋብሪካዎች ስፖንሰርነት እየወጣ እንደሆነም በሰፊው ማየት ይቻላል:: ለመሆኑ ሙዚቃው ካለ ቢራ ማስታወቅያ መሰራት አይችልም? ዘፋኞቹስ ለልጆች እና ለሚያድጉ ወጣት ጎረምሶች የወደፊት እጣ እንዳይናጋ ወይ እንዳይበላሽ በመቆርቆር ይሄ የሚያስነውር አካሄድ አይሆነንም ፣ አይበጀንም አይሉም እንዴ? ነፍሱን ይማርና ተፈራ ካሳ ለህዝብ ትምህርቱን በዘፈን እንዲ ነግሮን አልፏል:
ShewandagnHailuAddisAlbum
በመጠጥ ደስታ ይገኛል ብላችሁ

መጠን አትለፉ ትቃጠላላችሁ

ለነገሩ ቴዲ አፍሮ ወዶ ከፈረመና ከሰራ በኋላ እኔ አልፈልግም ፣ ይሄንን ጉዳይ እቃወማለሁ ፣ እንደውም እከሳለሁ ብሎ ቡራ ከረዩ አብዝቶ እንደነበር ይታወቃል ግን የፈጠረው ምንም ነገር እንደሌለ መገንዘብ ችያለሁ:: ይልቁንስ አሁን ከቅርብ ቀን በፊት ልጆች የኔን ፎቶ ከቢራ ጋር እንዲያዩት አልፈልግም ፣ ለወጣቶች ጥሩ አርአያ መሆን እፈልጋለሁ ሲል የነበረው እራሱ ቴዲ ለቢራ ፋብሪካ ፈረመ የሚል ዜና አንብቤ ወይ ስብ እና እያልኩ ነበር:: ዘሪቱ ከበደ በዚህ ከቢራ ፋብሪካ ስፖንሰርነት ጋር በተያያዘ ጉዳይ በጣም ጠንካራና የምትመሰገን ሴት ዘፋኝ እንደሆነች አስመስክራለች::

ግን ይሄ ሁሉ የሞራል ድቀትና አደገኛ ግድየሌሽነት በሃገራችን የሙዚቃ ኢንዱስትሪ ውስጥ በተለይ በዘፋኞቻችን ላይ እንዴት ሊመጣ ቻለ? ኪነጥበባውያንስ ነፍሳቸው ምን ያህል ብትደነድን ነው ይሄንን ኑ  በቢራ ተደሰቱ  የሚል መአት ሲዲያቸው ላይ ለጥፈው ግዙን የሚሉት? መጠጥን ማስተዋወቅ ከስነ ጥበብና ትውልድን ከማስተማር ጋር ምን አያያዘው? ከሰፊው ህዝብ በፊት እንዲህ አይነት አካሄድ ለአገር ጥሩ እንዳልሆነ የሙዚቃ ሰዎቻችን እንዴት ማወቅ ተሳናቸው?

አቤት ጥያቄዎቼ ብዛታቸው በዚህ ጉዳይ ላይ ትንሽ ነገር መጻፍ አስቤያለሁ ያልኩት ወዳጄ ‘አንተ እኮ በጣም የምትገርም እውነቱን አልቀበልም ብለህ ዝም ብለህ የምትንገላወድ ምስኪን ፍጡር ነህ:: እዚ አገር ዘፋኙ እንዴት ሞራሉና ስብእናው ወርደ ትለኛለህ? የዚ አገር ዘፋኝ አይደለም እንዴ እየዘመረ አምባገነኑን መለስ ዜናዊን ነቢይ ነው ሲለን የነበረው? የዚ አገር ዘፋኝ አይደል እንዴ የማያቀውን ታሪክ አዋቂ ነኝ እያለ የሚዘላብደው? የዚ አገር ዘፋኝ አይደል እንዴ በመሃይምነቱ ዘሎ ፓርቲዎች አስታርቃለሁ የሚለን? የዚ አገር ዘፋኝ ሲጀመር ምን አይነት ሞራል እና ስብእና አለው እና ነው አሁን ሞራሉ ወደቀ ምናምን እያልክ የምትቀባጥረው? የበውቀቱ ስዩም እና የሌሎች ታላላቅ ደራስያን መጽሃፍ ምረቃ ላይ የማይገኙ ዘፋኞችና የኪነጥበብ ሰዎች አይደሉም እንዴ በሚኒስትሩ በረከት ስምኦን መጽሃፍ ምረቃ ምሽት እንግዳ ከበር ከመቀበል አንስቶ እስከ ዝግጅቱን መምራትና ማድመቅ ሲያሽቃብጡ የነበሩት? የዚ አገር ዘፋኝ እና የኪነጥበብ ሰዎች ያለ ምንም እውቀት የሚሰብኩን ሁሉ ስለ አባይ፣ ስለ ህዳሴ፣ ስለ ትራንስፎርሜሽን እና ስላለው የሃገሪቷ እድገት አይደለም እንዴ? የህዝብ መበደል፣ የኑሮ መወደድ፣ የህዝብ በህግ ጉዳይ ያላግባብ መንገላታት መቼ ተሰምቷቸው ያቃል እና ነው ዛሬ ሞራላቸው ወደቀ የምትለኝ? ‘ ብሎ በቁታ እየገነፈለ ተወኝ አለኝ:: ወድያው ደግሞ “ግን ደሞ” ብሎ ጀመረ “ግን ደሞ አንዳንድ በጣት የሚቆጠሩ ነፍሳቸውን ጊዜያቸውንና ሁለመናቸውን ለኪነ ጥበብ የሰዉ እንዳሉም የማላቅ አልምሰልህ እኔ እነዛን ጥቂቶችን እጅግ በጣም አከብራቸዋለሁ” ብሎኝ ሌላ ጨዋታ አውግተን ተለያየን:: እኔም ብዙ ማሰብ ጀምሬ አውጥቼና አውርጄ…..
Michael Belayeneh kuku
እውነትም ከዘፋኞች ሞራል ዝቅጠት ጀርባ የሚታይ ወይ አላዋቂነት ፣ ወይ ጥቅም እስካገኘሁ ምናገባኝ ማለት ፣  ወይ ደግሞ ትልቅ ድንቁርና አለ በሚለው ተስማማሁ:: እንደዚህ ያልኩበት ምክንያት ምንድነው? ነጥቦቼንም በዚህ መልኩ አስቀመጥኩ

  • ኮፒ ራይቱ አላሰራ አለን፣ ተቸግረናል፣ በጣም ተቸገርን፣  እየተዘረፍን ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ መፍትሄ ይፈልግልን በማለት ከቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስቴር ጋር ስብሰባ ሲያደርጉ አምሽተው ተቸግረናል እየተዘረፍን ነው ባሉበት አፋቸው ዝግጅቱ ላይ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ በስጦታ መልክ የወርቅ ብእር እንደሰጡዋቸው ሳስታውስ፣
  • ባደባባይ ሰው እንዲገደል ያደረገ መሪ ሲሞት ከተከበረው ብሄራዊ ቲያትር እስከ ቤተመንግስት ምነው ተለየኸን መስከረም ሳይጠባ የሚለውን ዘፈን እየዘፈኑ ነጠላ አደግድገው (ለቅርብ ዘመዶቻቸው የማያደርጉትን) እያለቀሱ መሄዳቸውን ሳስብ፣
  • ከእንግዲህ ሻማ ለልደት ነው እያሉ የማያቁትን የኢንጅነሪንግ ሙያ እየተጨማለቁበት ሳይ ከአንድ ግድብ ምረቃ በኋላ ኢትዮጵያ ውስጥ የኤሌክትሪክ ችግር እንደማይኖር ማብራሪያና ዲስኩር የሰጡትን ሳስበው፣
  • ታላቅ የኦርቶዶክስ አማኝ ነኝ በማለት የማያቁትን የቤተ ክርስቲያንን ህግና ቀኖና ባልተከተለ መልኩ በድፍረት መዝሙር ዘምረው ማሪያም ማርያም የሚል ነጠላ ዜማ በለቀቁ ማግስት ዳንኪራና አስረሽ ምቺው ማድረጋቸውን ሳስበው፣
  • እንኳን ሌላ ሰው ያላግባብ ታሰረ ሊሉ እራሳቸው ያላግባብ ታስረው ያለ ወንጀሌ ነው የታሰርኩት በጣም ተበድያለሁ ለማለት ድፍረትና ብቃት የሌላቸው እንደሆኑ ሳስበው፣
  • ዘፈን እምቢ ሲላቸውና ከገበያ ሲወጡ በመሃይምነት እንዲሁም በከባድ ድፍረት ጌታ ጠርቶኝ ነው ብለው ለሃይማኖትም ለህዝብም ክብር ሳይሰጡ የስብከትንና የዝማሬን ተአምራዊ ጥበብ ምንም ሳይማሩ የፕሮተስታንት ዘማሪ ሲሆኑ ሳይ፣
  • እከሌ ሮጦ ሲያሸንፍ ሲዘፍኑ ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ሲዘፍኑ ለአባይ ግድብ ሲዘፍኑ ሳውዲ ለሞቱት ሲዘፍኑ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሲሞቱ ሲዘፍኑ ጥበብን ከውስጣዊ ስሜታቸው ሳይሆን ከጊዜውና ከሰሞኑ ወሬ ጋር ሊወስዷት ሲፈልጉ ዜና የሚመስል ዘፈን አቅርበው ስሰማ፣
  • በመሃይምነትና በድንቁርና ታውረው ያልሰሩበትንና ያልለፉበትን የሌላ ሰው ዘፈንና ዜማ ከአገር ውስጥም ከውጭም ወስደው በማስረጃ ሲቀርብባቸው ይቅርታ በስህተት ባለማወቅ ነው እንደማለት ይህንን ፕሮግራም ይሰራ የነበረውን ለምን ይዋሻል ራዲዮ እስከማዘጋት መድረሳቸውን ስሰማና ሳይ፣

እነዚህንና ሌሎች ብዙ ያልዘረዘርኳቸውን ነጥቦች ካየን የኢትዮጵያ ኪነጥበብ በተለይ ሙዚቃ ከባለሙያ የእውቀት ማነስ ችግር የተነሳ ወርዶ በዚህ ባለንበት ዘመን እንኳን ራሱን መደገፍ እንዳቃተው ግልጽ ይሆንልናል:: ግን ዘፋኞቻችንና የኪነጥበብ ሰዎች ይህንን ችግር በጣም በሰለጠነ መንገድ ከመፍታት ይልቅ እራሳቸውን አዋርደው ያለቢራ ፋብሪካዎች ማስታወቅያ ካሴታቸውን ማሳተም ከማይችሉበት ደረጃ መድረሳቸውን በግልጽ የተናገሩ አይመስለኝም:: እንደውም ጥሩ ነገር በመስራት ያለብን ችግር ሊቀረፍ ይችላል ብለው ከማሰብ ከባለስልጣን ጋር፣ ከካድሬ ጋር፣ ከባለሃብት ጋር በመሞዳሞድ ሊያልፉ ያሰቡ ይመስለኛል:: ይህ ደግሞ በጣም አስነዋሪና ከኪነጥበብ ሰው ሳይሆን ከአየር በአየር ነጋዴ የሚመነጭ ተራ ውርደትና ስግብግብነት ነው::
Nesanet-Melese
ጊዜውን በውል ባላስታውሰውም በዚህ ሶስት አራት አመት ውስጥ የኢህአዴግ ባለስልጣኖች ያሳተሙትን የህዳሴ ዋዜማ የተሰኝውን DVD አባዝቶ በህገ ወጥ መንገድ ሲሽጥ የተያዘ ሰው 15 አመት እንደተፈረደበት ሰምተን ማንም እየተነሳ የድምጻዊያኖቻችንን ካሴት እና ሲዲ ለዘመናት በህገ ወጥ መንገድ ሲሸጥ ምንም አለመደረጉ ከዘፋኞቻችን በላይ እኔን ለምን እንዳስቆጨኝ አላውቅም::

የራሳቸውን መብት ሳያስጠብቁና ኮፒ ራይታቸውን ታግለው ሳያስከብሩ ዘፋኞቻችን ለኛና ለመጪው ትውልድ ያስባሉ ማለት ዘበት ነው ግን ቢሆንም ካለባቸው ችግር ለመውጣት የጀመሩት መንገድ ትክክል እንዳልሆነና ነገ ሁላችንም በልጆቻችን ፊት ሊያሳቅቀን የሚችል የሞራል ዝቅጠት መሆኑን ሳልጠቁም አላልፍም:: አርአያ የሚለው ቃል ለነገ ከማሰብና ለመጪው ትውልድ ከመጠንቀቅ ጋር አብሮ የሚሄድ ትርጉም ያለው ትልቅ ቃል ነው:: ይሄ ቃል ተረስቶ ወይ ደግሞ የሰው ስም ብቻ ሆኖ እንዳይቀር ካለኝ ስጋት ይቺን ጽፌያለሁ ደህና ሁኑ::

በጎንደር ዳባት ሕጻን ሰለሞን ላይ ማን የጥይት እሩምታ አወረደበት?

$
0
0

Gonder
ከዳዊት ሰለሞን

ሰሜን ጎንደር ዳባት ወረዳ ነዋሪ የነበሩት የ55 ዓመቱ አቶ ማስረሻ ጥላሁን የተመሰከረላቸው አርሶ አደር ገበሬ በመሆናቸው የክልሉ ግብርና ጽ/ቤት ሞዴል አርሶ አደር በማለት ሸልሟቸዋል፡፡የሁለት ወንድና የአምስት ሴት ልጆች አባት የሆኑት አቶ ማስረሻ ወሰኔን ገፍተሃል የሚል ክስ ቀርቦባቸው በዳባት ፍርድ ቤት 300 ብር መቀጮ ተጥሎባቸው በመክፈል ወደ እርሻቸው ቢመለሱም የገበሬ ቀበሌ ማህበሩ ሊያስቀምጣቸው አልቻለም፡፡

ጥቅምት 15/2006ዓ.ም ከሁለተኛ ልጃቸው ሰለሞን ማስረሻ ጋር አትክልት ተክለው አመሻሹ ለይ ተዳክመው መኖሪያ ቤታቸው ገብተዋል፡፡ማለዳ 12፡00 ከመኝታው ባላቋረጠው የውሾች ጩህት ከእንቅልፉ ተነሳው ሰለሞን በሩን ከፍቶ ሲወጣ የጥይት እሩምታ ይወርድበታል፡፡አባት ልጄን ብለው የሌሊት ልብሳቸውን እንደለበሱ ወደ ውጪ ሲወጡ የጥይቶቹ አቅጣጫ ወደ እርሳቸው በመዞሩ ማን እንደተኮሰባቸውና ማን እንደመታቸው ለማየት እንኳን ሳይታደሉ ይህችን ጨካኝ አለም ተሰናበቱ፡፡

መኖሪያ ቤቱ ላይ በሚወርደው የጥይት እሩምታ የተነሳ ሁለት ላሞችና አንዲት ጊደር ተገደሉ፡፡የስምንት አመቷ ስለእናት ማስረሻ ቀኝ እጇ ላይ በጥይት ተመታች፡፡ባለቤታቸውን በሞት የተነጠቁትና ምንም የማታውቀውን ህጻን ልጃቸውን አካለ ጎደሎ ያደረገባቸውን ጥይት ማን እንደተኮሰው ለማወቅ ለዳባት ወረዳ ፖሊስ ጣቢያ አቤት ሲሉ ‹‹ባለቤትዎ ሽፍታ መረጃ ስለደረሰን ግድያውን የፈጸመው የጸረ ሽብር ግብር ሃይል ነው››ተብለዋል፡፡‹‹ሽፍታ እንዴት ባለ80 ቆርቆሮ ቤት ይሰራል?ልጆቹን ያስተምራል?ሞዴል አርሶ አደር ተብሎ ይሸለለማል?በየት አገር በብአዴን ስብሰባ ላይ እንድትገኝ ተብሎ በደብዳቤ ይጠራል?እንዴት ሽፍታ የመለስ ዜናዊን አደራ ለመወጣት በምንችልበት ሁኔታ ለመወያያት እንድንነጋገር ይባላል? ›› ጥያቄዎቹን ፖሊሶቹ ሊመልሱላቸው ባለመቻላቸው ወደ ክልሉ አስተዳደር አምርተዋል፡፡ክልሉ ለዞኑ ዞኑ ለወረዳው ደብዳቤ እየጻፈ እስካሁን ድረስ የአቶ ማስረሻ እውነተኛ የግድያ መንስኤ መታወቅ አልቻለም፡፡
999933_654015557990530_568853481_n
zemecha meles

Health: “ባለቤቴ እንደምትወደኝ አውቃለሁ፤ የወሲብ ፍላጎት ግን የላትም፤ በዚህ የተነሳ ትዳሬ አደጋ ላይ ነው”

$
0
0

በዘ-ሐበሻ ጋዜጣ ቁጥር 58 ላይ ታትሞ የወጣ

ባለትዳር ነኝ፡፡ ከባለቤቴ ጋር ትዳር የመሰረትነው ከዩኒቨርሲቲ ተመርቀን ስራ እንደጀመርን ነበር፡፡ ባለቤቴ እጅግ ሲበዛ ዝምተኛ፤ እና አይን አፋር ነች፡፡ በታማኝት እና በፍቅር በቆየንባቸው ዓመታት ‹‹ከጋብቻ በፊት ወሲብ መፈፀም የለብንም›› የሚል አቋም ስለነበራት እስከምንጋባ ድረስ ቃሏን ጠብቄ ቆይቻለሁ፡፡ ወደ ትዳር ከገባን በኋላ ግን ባለቤቴ ወሲብ ለመፈፀም ያላት ፍላጎት እጅግ አነስተኛ ነው፡፡ ወሲብ ከመፈፀም በኋላ የደስታን ስሜት ሳይሆን የመከፋት መንፈስ ነው የሚታይባት፡፡ ወደ ትዳር እንደገባን ባሉት አንድ እና ሁለት ዓመታት ጥሩ የሚባል የትዳር እና ፍቅር ጊዜ የነበረን ቢሆንም ወሲባዊ ህይወትን ግን ከጀመርን በኋላ አስደሳች እና ጣፋጭ ባለመሆኑ የተነሳ ሁልጊዜ አዝን ነበረ፡፡ ከዚያ በኋላ ባሉት ዓመታትም ከቀን ወደ ቀን የባለቤቴ የወሲብ ፍላጎት መቀነስ እና ደስተኛ አለመሆን እያሳሰበኝ መጥቷል፡፡ በትዳራችንም ላይ የመቀዛቀዝ ስሜትን ፈጥሯል፡፡ አንድ ነገር በእርግጠኝነት መናገር እችላለሁ፤ እኔ እንደምወዳት ሁሉ እሷም ትወደኛለች፡፡ የተፈጠረባት የወሲብ ፍላጎት መቀነስ ችግርን በተመለከተ በግልፅ ለማውራት ፍቃደኝነት ብዙም አይታይባትም፡፡ የወሲብ ጥያቄ ገና በማነሳባት ወቅት የመረበሽ፣ የመደንገጥ እና የመፍራት ስሜትን ስለምታንፀባርቅ እኔም እረበሻለሁ፡፡ በአንድ ጊዜም ፍላጎቱን አጣዋለሁ፡፡ የነገሩ መደራረብ እና መደጋገም እኔን ከትዳሬ ውጪ እንድመለከት እያደረገኝ ሲሆን የወሲብ ፍላጎት ከእኔ እንጂ ከእሷ መጥቶ አያውቅም፤ በእኔው ግፊት በወር አንዴ ወይንም ሁለቴ ግንኙነት ብንፈጽም ነው፡፡ በግልጽም ምንም አይነት ፍላጎት እንደሌላት ነግራኛለች፤ የሚገርመው ነገር እናቷም የተመሳሳይ ችግር ተጠቂ ነበሩ፡፡ ሁኔታው እጅግ እያስፈራኝ ስለሆነ እና ለትዳራችንም አደጋ ስለሆነ መፍትሄ ነው የምትሉትን ነገር ጠቁሙኝ፤ እኔም ምን ማድረግ እንዳለብኝ ምከሩኝ፡፡ ፋንታሁን ነኝ

ask your doctor የዶ/ር ዓብይ ዓይናለም ምላሽ፦ ውድ ጠያቂያችን ፋንታሁን በቅድሚያ ችግርህን ገልፀህ ከዘ-ሃበሻ ጋር ለመመካከር ስለወሰንክ እናመሰግናለን፡፡ በመቀጠል ወደ ጉዳይህ ስንገባ በትዳር አጋርህ ላይ የተፈጠረው የወሲብ ፍላጎት መቀነስ ብሎም መጥፋት እንዳስጨነቀህ እና እንዳሳሰበህ ምንም እንኳን እናንተ ብትዋደዱም በመሀከላችሁ የተፈጠረው ችግር ሊለያያችሁ እንደሚችል ያለህን ስጋትህን ገልፀሀል፡፡ ውድ ጠያቂያችን ፋንታሁን በቅድሚያ አንድ ነገር ተገንዘብ፡፡ ይህ አይነቱ ችግር የአንተ እና የባለቤትህ ችግር ብቻ ሳይሆን የበርካታ ባለትዳሮች ችግር መሆኑን፡፡ ሌላው በቅርቡ በእስራኤል ሀገር በኢየሩሳሌም ዩኒቨርሲቲ በተደረገ አንድ ጥናት ወሲብ የመፈፀም ፍላጎት ከሰው ወደ ሰው የተለያየ መሆኑን እና በተፈጥሮ አንዳንድ ሰዎች ከፍ ያለ ወሲባዊ ፍላጎት ሲኖራቸው ሌሎች ደግሞ አነስተኛ የሆነ ወሲባዊ ፍላጎትን ይዘው ይወለዳሉ፡፡ በዚሁ ጥናት ላይ በተደረገ ፆታዊ ንጽጽሮሽም ሴቶች ከወንዶች ያነሰ ወሲባዊ ፍላጎት እንዳላቸው ተደርሶበታል፡፡ ይሁን እንጂ የአንተ ባለቤት ላይ እንደሚታየው አይነት ዝቅተኛ የሆነ ወሲባዊ ፍላጎት (ሴክሽዋል ዲዛየር) በእንግሊዝኛ ሀይፓ አክቲቭ ሴክሽዋል ዲዛየር ዲስኦርደር በመባል የሚታወቅ ሲሆን ዋነኛ መገለጫውም ምንም አይነት አካላዊም ሆነ አዕምሮአዊ ችግር ሳይኖር ወሲባዊ ፍላጎትን ማጣት እና በወሲባዊ እንቅስቃሴ ምንም አይነት የደስታ ስሜት ያለመስማት ይልቁኑ፣ በተግባሩ የመረበሽ ስሜትን ማስተናገድ ነወ፡፡ ይህንን መሰል ስሜት በርካታ ሴቶች በተለያየ ምክንያት ለተወሰነ ጊዜ የሚያስተናግዱት ሲሆን በአንዳንድ ሴቶች ላይ መጠኑም ሆነ የጊዜ ርዝማኔውም ከፍ ያለ ነው፡፡ ቀደም ባለው ጊዜ ይህ አይነቱ የወሲብ ፍላጎት መጥፋት እንደ ችግር አይቆጠርም ነበር፡፡ በጉዳዩ ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ የስነ ወሲብ ባለሞያዎቹ ዊልያም ማስተር እና ቨርጂኒያ ጆንሰን ጥናት እና ምርምር ካካሄዱ በኋላ ግን እንደ ችግር ትኩረት እያገኘ የመጣ፡፡ በተመሳሳይ ሄለን ሲንገር ካፕላን በተባለች የስነ ወሲብ ባለሞያ አማካኝነት በተደረገ ጥናት ወሲባዊ ፍላጎት (ሴክሽዋል ዲዛየር) በወሲብ ዑደት ውስጥ ወሲባዊ ፍላጎት (ሴክሽዋል ዲዛየር) በወሲብ ዑደት ውስጥ ከመነቃቃት፣ ከእርካታ እና ወደነበርንበት ቦታ ከመመለስ (Arousal, orgasm and resolution) በፊት የሚከሰት የዑደቱ የመጀመሪያው ክፍል መሆኑን ጠቅሳለች፡፡ ስለዚህ በውስጣችን የወሲባዊ ፍላጎት መፈጠር በወሲባዊ እንቅስቃሴ ዑደት ውስጥ የመጀመሪያው እና ወሳኙ ነገር ነው፡፡ ይሁን እንጂ እንደ አንተ ባለቤት ወሲባዊ ፍላጎት ከነጭራሹ ማጣት በእንግሊዝኛ ሀይፓ አክቲቭ ሴክሽዋል ዲዛየር ዲስኦርደር የሚባል ሲሆን፣ ዋና መገለጫውም ምንም አይነት አካላዊም ሆነ አዕምሮአዊ ችግር ሳይኖር ወሲባዊ ፍላጎት መቀነስ ወይንም መጥፋት ሲሆን፣ ይህን አይነት ስሜት የሚያስተናግዱ ሴቶች ወሲብ መፈፀምን ሲያስቡ እሱን ተከትሎ የሚመጣው ደስታ ሳይሆን የሚያስቡት የሚሰማቸውን ህመም እና የሚመጣባቸውን ጥሩ ያልሆነ ትውስታ ነው፡፡ በዚህም የተነሳ ሁልጊዜ የወሲብ ጥያቄ ሲቀርብላቸው የመከፋት፣ የመደበር እና የመነጫነጭ ስሜትን ያንፀባርቃሉ፡፡ በዊልያም ማስተር እና በቨርጂኒያ ጆንሰን አማካይነት የተደረገው ጥናት እንደሚጠቁመው የወሲባዊ ፍላጎት መቀነስ ችግር ሶስት አይነቶች አለው፤ እነሱም፡-
- በህይወት ዘመን ውስጥ ዘላቂ እና አጠቃላይ የሆነ ወሲባዊ ፍላጎት ማጣት
ይህ አይነት ችግር ያለባት ሴት ዝቅተኛ ወይንም ምንም አይነት ወሲባዊ ፍላጎት የላትም ኖሯትም ላያውቅ ይችላል፡፡
- ከጊዜ በኋላ የተፈጠረ እና ቦታ ለይቶ የሚጠፋ ወሲባዊ ፍላጎት፣
ይህ አይነቱ የወሲባዊ ፍላጎት መቀነስ ጤናማ የሚባል ወሲባዊ ባህሪ የነበራት ሴት ከጊዜ በኋላ ከትዳር አጋሯ ጋር ወሲብ የመፈፀም ፍላጎትን ታጣዋለች፡፡ ከሌላ ሰው ጋር ግን የመፈፀም ፍላጎት ሊኖራት ይችላል፡፡
- ከጊዜ በኋላ የተፈጠረ እና አጠቃላይ የሆነ ወሲባዊ ፍላጎት ማጣት፣
ይህ አይነቱ ወሲባዊ ፍላጎት የማጣት ችግር ከጊዜ ወደ ጊዜ የሚፈጠር እና ቦታ እና ጊዜን ሳይለይ ሙሉ ለሙሉ ፍላጎት ማጣት ነው፡፡
ውድ ጠያቂያችን ፋንታሁን ከላይ ከተዘረዘሩት የወሲብ ፍላጎት መቀነስ አይነቶች በመነሳት ባለቤትህ በየትኛው ምድብ ውስጥ እንዳለች እወቅ፡፡ ሌላው ስለ ሴቶች ወሲባዊ ባህሪ ማወቅ ካለብን በርካታ ነገሮችን መካከል አንዱ እና ዋነኛው ነገር ሴቶች እንደ ወንዶች በፍጥነት ወሲባዊ ፍላጎታቸው አይነሳሳም፣ ሌላው ሴቶች ወሲባዊ እርካታን ማስተናገድ የሚጀምሩት በስጋዊ ግንኙነት ብቻ ሳይሆን ከዚያ በፊት በሚደረጉት ጨዋታዎች እና አካላዊ መቀራረቦች ጭምር ነው፡፡ ውድ ጠያቂያችን ፋንታሁን በቀጥታ ወደ አንተ ባለቤት ጉዳይ ስንመጣ በባለቤትህ ላይ የሚታየው የወሲባዊ ፍላጎት መቀነስ በተለያዩ ምክንያቶች ሊከሰት ይችላል፡፡ እነዚህን ምክንያቶች በአራት ዋና ዋና ክፍል ማስቀመጥ እንችላለን፡፡
- ግለሰባዊ ችግር
- የመጣንበት ቤተሰብ ሁኔታ
- በጥንዶች መካከል ያለው የመቀራረብ ደረጃ
- የሌላ ጤና ችግር ተጽዕኖ
እነዚህን ዋና ዋና ምክንያቶች ሰፋ አድርጎ ለመመልከት ያህል፣ ግለሰባዊ ችግር በምንልበት ወቅት ከዚህ በፊት በነበረን ህይወት ከወሲብ መፈፀም ጋር በተገናኘ የሚፈጠር የፍርሃት ስሜት፣ በተለያየ ምክንያት የሚከሰት የድብት ስሜትት የትዳር ወይንም ወሲብን አስመልክቶ የሚኖር የተሳሳተ እምነት፣ በራስ ያለመተማመን እና ለራስ ዝቅተኛ የሆነ ግምት መስጠት፣ የስራ ጫና እና የሀሳብ ብዛት በራሱ ወሲባዊ ፍላጎት መቀነስን ሊያስከትል ይችላል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ኃይል በተቀላቀለበት መንገድ የሚፈጠር ወሲባዊ ጥቃት እና ጥቃቱን ተከትሎ የሚፈጠር የስሜት ስብራትም ወሲብን ከዚያ መጥፎ አጋጣሚ ጋር በማስተሳሰር ስለወሲብ ጥሩ ያልሆነ ስሜትን ማዳበር ነው፡፡ ይህ ስሜት ደግሞ የወሲብ ፍላጎት መጥፋትን ሊያስከትል ይችላል፡፡
በተመሳሳይ የመጣንበት የቤተሰብ ይንም ያደግንበት ሁኔታም መሰል ችግርን ሊያስከትል ይችላል፡፡ በተለይ ያደግንበት ቤተሰብ ጥብቅ እና ሃይማኖታዊ ከነበረ እና ወሲብን እንደ ሐጢያት፣ እንደ እርከሰት እና አሳፋሪ እንደሆነ ነገር እንድንመለከት አድርገው ካሳደጉን ወሲብን የመጥላት እና ፍላጎት የማጣት ስሜት እንዲፈጠር ሊያደርገን ይችላል፡፡
በሌላ በኩል በጥንዶች መካከል ያለው የመቀራረብ ሁኔታም ወሲባዊ ፍላጎት መቀነስን ሊያስከትል ይችላል፡፡ በጥንዶች መካከል ያለው መተሳሰብ፣ መከባበር እና መቀራረብ ከወሲብ የሚገኘውን የእርካታ ደረጃ ይወስነዋል፡፡ ለምሳሌ በጥንዶች መካከል ያለመከባበር እና የመናናቅ ስሜት ካለ፣ መተቻቸት እንዲሁም መከራከር እና እኔ እበልጥ እኔ እበልጥ እና መሰል ጤናማ ያለሆኑ ግንኙነቶች ካሉ ፍቅርን የማሻከር ብሎም ወሲባዊ ፍላጎት መቀነስን ከፍ ሲልም የማጥፋት አቅም አላቸው፡፡
ከላይ ከተጠቀሱት ምክንያቶች በተጨማሪ በውስጣችን ወሲባዊ መነቃቃት እንዲፈጠር ምክንያት የሚሆኑት ሆርሞኖች በተለያዩ የጤና ችግሮች የተነሳ ምርታቸው መቀነስ እንዲሁም ለተለያዩ ህመሞች ተብለው የሚወሰዱ መድሃኒቶች የጎንዮሽ ጉዳትም የወሲብ ፍላጎት የመቀነስ ችግርን ሊከስት ይችላል፡፡
ውድ ጠያቂያችን፡- ፋንታሁን የወሲብ ፍላጎት መቀነስ በሴቶች ላይ ብቻ ሳይሆን በወንዶችም ላይ አነስተኛ ይሁን እንጂ ይከሰታል፡፡ ከላይ የጠቀስናቸው አራት ዋና ዋና ምክንያቶች በተለይ በሴቶች ላይ የወሲባዊ ፍላጎት መቀነስን ሊያስከትሉ የሚችሉ ሲሆን፣ የፍላጎት መቀነሱ ወይንም መጥፋቱ ጊዜው አሊያ ዘላቂ ሊሆን የሚችል ሲሆን አንዲት ሴት ግን የዚህ ችግር ተጠቂ ነች ብሎ ለመደምደም የሚከተሉት ባህሪያት መስተዋል አለባቸው፡፡ የመጀመሪያው የወሲብ ፍላጎት መጥፋቱ ጊዜን እና ቦታን ሳይለይ ሁልጊዜ የሚከሰት ከሆነ፣ ሌላው ወሲብ ለመፈፀም ውስጣዊ የሆነ ፍላጎት ቢኖርም እንኳን ሰውነት እና ወሲባዊ አካላት ለግንኙነት ዝግጁ ያለመሆኑ ዋና መገለጫዎች ናቸው፡፡ እነዚህ ምልክቶች በስፋት ከታዩ ያቺሴት የዚህ ችግር ተጠቂ ነች ማለት እንችላለን፡፡
ወደ መፍትሄው ስንመጣ ከላይ ለመጠቆም እንደተሞከረው ወሲባዊ ፍላጎት መቀነስ ወይንም መጥፋት በተለያዩ በርካታ ምክንያቶች የሚከሰት በመሆኑ የተነሳ እንደ መንስኤው ሁሉ መፍትሄውም የተለያየ ነው፡፡ ምን አልባትም መፍትሄው የህክምና እና የስነ ልቦና ድጋፍን ያጣመረ ስለሚሆን የችግሩ ባለቤትም ሆነ የትዳር አጋሯ ጥንካሬን እና ከችግሯ ለመውጣት ያላትን ቁርጠኝነት ይጠይቃል፡፡ ህክምናን መሰረት ያደረገው መፍትሄ ስንመጣ ለድብርት ማስለቀቂያ ተብለው የሚሰጡ አነቃቂ እንክብሎች አዕምሮንም ሆነ አካልን የማነቃቃት እና ዘና የማድረግ ባህሪ ስላላቸው ወሲባዊ ፍላጎትን ከፍ የማድረግ አቅምም አላቸው፡፡ ስለዚህ እነዚህን መሰል መድሃኒቶች የወሲብ ፍላጎት መቀነስ ችግር ሲከሰት የሚሰጡም ናቸው፡፡ እነዚህ መድሃኒቶች የጎንዮሽ ችግር ሊያስከትሉ ስለሚችሉ ባለሞያዎችን ቀርቦ ማነጋገር የግድ ነው፡፡
ከዚህ ሌላ ወሲባዊ ፍላጎት መቀነስ ወይንም መጥፋት በስነ ልቦና ባለሞያ አማካኝነትም ሊደገፍ ይችላል፡፡ ምክንያቱም ወሲባዊ ፍላጎት መቀነስ አልፈለግም ከሚል እና ከመሰል ለራስ አነስተኛ ግምት ከመስጠት ጋር የሚገናኝ ችግርም ስለሆነ ለራስ የምንሰጠው ግምት እና ክብር ከፍ ባለ ቁጥር እየተስተካከለ ሊሄድ ይችላል፡፡ ስለዚህ የስነ ልቦና ባለሞያው ይህንን ሂደት ሊደግፍ ይችላል፡፡ ውድ ጠያቂያችን በጥንዶች መካከል ጤናማ ያልሆነ ግንኙነት ካለ ማለትም ያልተፈታ ቅራኔ፣ ግጭት ወይንም አለመግባባት ካለ በዚያ ባልተረጋጋ መንፈስ ውስጥ ሆነው ለግንኙነት መነሳሳት አስቸጋሪ ስለሚሆን የወሲባዊ ፍላጎ መጥፋት ይከሰታል፡፡ ስለዚህ በጥንዶች መካከል የተፈጠረን ቅራኔ ወይንም ግጭት ካለ በቶሎ መፍታት ይህንን ችግር ለመቅረፍ ወሳኝ ነው፡፡ በሌላ በኩል ከላይ ወሲባዊ ፍላጎ መቀነስን ሊያስከትሉ የሚችሉ ነገሮችን ስንዘረዝር ቀደም ባለው ህይወታችን ላይ የተፈጠረ እና ከወሲብ ጋር የተከሰተ መጥፎ አጋጣሚም የወሲብ ፍላጎት መቀነስን ስለሚያስከትል ስለአጋጣሚው በግልጽ በማውራት በዚያ አጋጣሚ የተፈጠረውን ፍርሃት እና የተሳሳተ እምነት ከውስጣችን እንዲወጣ ማድረግ አለብን፡፡ በግልፅ መነጋገር ሲባል ደግሞ በመወነጃጀል እና በጭቅጭቅ መንፈስ ሳይሆን በመረዳዳት እና ችግሩን ለመፍታት ቁርጠኝነት በማሳየት መሆን ይኖርበታል፡፡

ልጓሙን የበጠሰው የፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም የስድብ ፈረስ ዳኛቸው ቢያድግልኝ

$
0
0

በ ዳኛቸው ቢያድግልኝ

ፕሮፌሰሩ በጽሁፎቻቸው እንዲህ ብለውናል

“…በዓለም ሕዝቦች መሀከል ውድድር ቢደረግ ያለጥርጥር አበሻ አንደኛ ከሚወጣባቸው ነገሮች አንዱ ልመና ሳይሆን አይቀርም፤ ለአበሻ፣ ልመና የኑሮ ዘዴ ነው……” http://www.goolgule.com/abesha-and-begging-1/

“…አዳም አበሻ ሳይሆን አይቀርም፤ ሁሉንም ነገር ብላ ከተከለከለው በቀር ብሎ ያስቀመጠው ይመስላል፤ በላባችሁ ወዝ ብሉ ተብለው አዳምና ሔዋን መረገማቸውን አበሻ ገና አልሰማም፤ አበሻ የተፈጠረው ገነት ውስጥ ቁጭ ብለህ ያለውን ሁሉ ብላ በተባለበት ጊዜ ነው፤ እግዚአብሄር አበሻን ሁሉንም ብላ ሲለው ምናልባትም በጆሮው ጭራሽ አታስብ ብሎት ይሆናል …….” (ሰረዝ የተጨመረ)

እስከናካቴው “ሆድ” የሚባል ቃል ከአበሻ ቋንቋ ፈጽሞ ቢሰረዝ ቋንቋው ብቻ ሳይሆን አበሻም ጉድ ይፈላበታል። አዕምሮ ፣ ሕሊና የሚባሉትን ቃላት አበሻ አያውቃቸውም፤ ተግባራቸውንም ሁሉ ለሆድ ሰጥቶታል። (ሰረዝ የተጨመረ) http://www.zehabesha.com/amharic/archives/9015

 

ልጻፍ ልተው… ምናልባት… እንዲያው ምናልባት በዚሁ የሚያበቁ ከሆኑ አይቶ እንዳላየ ማለፍ ይሻል ይሆናል ስል ልጓሙን የበጠሰው የስድብ ፈረሳቸው በማንአለብኝነት ጋለበብን። ባእዳን አበሽ እያሉና እየሰደቡ ይገድሉናል። የራሳቸው ታሪክ በረሀብ ቸነፈርና ስደት የተሞላ እንዳልሆነ ሁሉ በመዝገበቃላታቸው ውስጥ ኢትዮጵያን የረሀብ ምልክት አድረገው የሚያዋርዱን በርካታዎች ናቸው። ፕሮፌሰሩ በአንድ ወቅት ሲሉ እንደሰማሁዋቸው ወያኔዎች ከዱር ወደከተማ ሲገቡ ህዝቡን ፈሪ ለማድረግና የሚያከብረው ምልክት ለማሳጣት በየቀዬው በህብረተሰቡ ዘንድ የሚከበሩትን እያፈላለጉ በአደባባይ ፂማቸውን ይዘው በመጎተት ያዋርዱዋቸው ነበር። ይህን መሰሉ የወያኔዎች ተግባር በሚያሳዝን ሁኔታ በፕሮፌሰሩም ላይ በተደጋጋሚ ደርሶባቸዋል። የወያኔዎች ኢትዮጵያዊነትንና ኢትዮጵያን የማዋረድ ዘመቻ ዛሬም እንደቀጠለ ነው። ታዲያ ይህ ባለበት ሁኔታ የእውቀት ጣርያ ላይ ደርሰዋል የሚባሉት አዛውንቱ ፕሮፌሰር መስፍንም በአሮጌና ያለአግባብ በተደረደረ ምሳሌ ይህን መከራ የበዛበትን ህዝባችንን በሚሸነቁጥ የጅምላ ስድብ መቀጥቀጣቸው ግር የሚያሰኝ ሆነብኝ። ይህ ወቅትና ሁኔታን ያላገናዘበ መፍትሄ የመጠቆም፣ የማስተማር አቅምም የሌለው ኢትዮጵያዊነትን የሚያዋርድ ጅምላ ስድብና ሽሙጥ በተከታታይ ሲወርድብን አይቶ እንዳላየ ማለፉ ክብራችንን ለማጉደፍና ለማዋረድ ኢትዮጵያችንን ለማንቋሸሽ ለሚተጉት ዱላ ማቀበል ይሆናል። እናም ይህ ጥያቄ ይከነክነኝ ገባ። እውን አበሻ ሥራ ጠል፣ ለማኝና ሆዳም ነውን? በምን ጥናት በማንስ ትንታኔ?

 
እድሜአቸውን ሙሉ ሀገራችንን አገልግለዋል ሲባል መስማቴ ብቻ ሳይሆን በባህላችን አዛውንት ይከበራልና ክብራቸውን የሚያጎድፍ ትችት ማቅረብ አልፈልግም። ቢሆንም ታድያ የሰሞኑ ማቆሚያ ያጣው የስድብ ጅራፍ ዘላቂ ጉዳቱ ከፍተኛ ነውና አክብሮቴን ሳላጎድል እባክዎን የስድብ ፈረስዎን ልጓም ያዝ አድርጉልን እላለሁ።
በሀገራችን አዋቂ ነን የሚሉ ሰዎች ከነሱ የተለየ ሃሳብ ይዞ የሚመጣን ተወያይቶ የተሻለውን ሃሳብ ከመደገፍ ይልቅ ለየት ያለ ሃሳብ ያቀረበውን አንገት የሚያስደፋ የስድብ ናዳ ማውረድ ይቀላቸዋል። ይህንን በመፍራት አዋቂዎቹ ግዙፍ ስህተት ሲፈጽሙ በዝምታ ማለፍ ለሌላ ስህተት በር መክፈት ይሆናል። አንዳንድ ሰዎች ደግሞ ጽሁፍን በይዞታው ሳይሆን በጸሃፊው ማንነት እየመዘኑ ጸሀፊው በግልጽ ያስቀመጠውን ሃሳብ ወደጎን ትተው ያልተባለውን መልካም ሃሳብ ፍለጋ እየማሰኑ የራሳቸውን ትርጓሜ ይሰጣሉ። ሰአሊ በስህተት የረጨውን ቀለም “አብስትራክት” ነው ብለው በምናባቸው ውብ ስዕል እንደሚሰሩት አይነት ከስድብ ጀርባ ሙገሳ መፈለጉ ከንቱ ነው።

 
የፕሮፌሰር ተከታታይ ጽሁፎች የተጻፉት ኢትዮጵያን በስፋት በማያውቅ ሰው፣ ሀሳብን ለህዝብ ለማቅረብ ምን አይነት ጥንቃቄ የተመላበት የምርምር ጥበብ አስፈላጊ እንደሆነ በማያውቅ ሰው ቢሆን፣ ሀሳብን የማስፈር ዓላማና ግብን መረዳት በማይችል የእውቀት አድማሱ ያልሰፋ፣ በሌሎች ሀገራት የሚኖሩ ሰዎችን አኗኗር በተመለከተ ምንም ግንዛቤ በሌለው ሰው ወይም እንዲያው ለፌዘኛ የመሸታ ቤት ቀልድ ሲባል ለተወሰኑ ታዳሚዎች የቀረበ ቢሆን ምንም ትኩረት መስጠት ባላስፈለገ ነበር። ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም ግን አለምን ተዘዋውረው የጎበኙና ያልኖሩበትን ዘመንና ያልጎበኙትን አገር ህዝብ አኗኗር በምርምርና በንባብ ጠንቅቀው የተረዱ እድሜ የጠገቡ ምሁር ናቸውና በምንም ጥናታዊ መረጃ ባልተደገፈ መንገድ የአንድን ጥንታዊና ታሪካዊ ሀገር ሕዝብ በዚህ መልኩ ማሳነስና ከሌላ ፕላኔት የመጣ ሰንካላ ፍጡር ማስመሰል እድሜያቸውንና እውቀታቸውን አይመጥነውም። የአንድ ሀገር 90 ሚሊየን ሕዝብ በአንድ ቅንፍ ውስጥ “አበሻ” ብለው ከተው እንኳን የሰው ልጅ ቀርቶ ማንኛውም ማህበራዊ እንስሳ የሚያደርገውን ተሳስቦ፣ ተዛዝኖ፣ ተካፍሎ መኖርን በዚህ መልክ አሳንሶ ኢትዮጵያዊነትን ማዋረድ ታላቅ ስህተት ነው።

 

ኢትዮጵያዊነትን እያዋረዱ አገር አልባ ሊያደርጉን አዲስ ታሪክ ሊጽፉልን ያሰፈሰፉ ጠላቶች አራት ኪሎ በተቀመጡበት ሰዓት፤ ከልመና ግርድና ይሻላል ብለው የፕሮፌሰሩ የልጅ ልጆች በመላው አለም ተበትነው ለራሳቸውና ለቤተሰባቸው ቢያልፍልን ብለው በሰው ሀገር እየተደፈሩ፣ እየተዋረዱ በሚዳክሩበት በዚህ ዘመን፣ በርካታ እናቶች አራስ ልጆቻቸውን ታቅፈው ትንሽ ሳንቲም ለማግኘት በየመንገዱ ዳር ጥቂት የተቀቀለ ድንችና ንፍሮ ለመሸጥ ጸሀይና ብርድ ሲፈራረቅባቸው ውሎ በሚመሽበት ዘመን፣ ደካማ እናቶች ወገባቸው እስኪጎብጥ ቅጠልና ጭራጭሮ ተሸክመው የእለት ጉርሳቸውን በሚያገኙበት ሀገር፣ ተራራ የሚያክል ሸቀጥ በጭንቅላታቸው ተሸክመው የሚሮጡ ወገኖች በሚርመሰመሱበት ሀገር፣ ህጻን አዛውንቱ ትንሽ ባገኝ ብሎ ሊስትሮና ማስቲካ ነጋዴ በሆነበት ሀገር ፕሮፌሰሩ ኢትዮጵያውያን ሥራ-ጠል ሆዳምና ለማኝ መሆናችንን አስረግጠው ሲነግሩን መስማት እጅጉን ያማል።
 

ሀገር በሞታቸው ያቆዩልን ተዋርደው አጽማቸው ከመቃብር ሀውልታቸው ከቆመበት እየፈረሰ ባለበት፣ የኢትዮጵያን ገጽታ ማቆሸሽ የመንግስት ፖሊሲ በሆነበትና ግፈኞችና ጎጠኞች ሰው በሀገሩ ሰርቶ ሰው መሆን እንዳይችል በየማዕዘናቱ እየበተኑት ባሉበት የመከራ ጊዜ የኛው የተማሩ አዛውንት ዋናው ተሳዳቢ መሆናቸው ያሳዝናል። አብረን ስለበላን ሆዳም፣ ተቸግሬአለሁ ብሎ ድጋፍ ለጠየቀ ወገን ስለለገስን ኅሊና ቢሶች አሉን። ሰውን ከመዝረፍ መለመንን ስለመረጠ ፈሪና ጅል፣ ስላመነ ሞኝና ተላላ አድርጎ መመልከት ነውር ነው። ይህ መተዛዘንና ተካፍሎ መብላት ቀለም ያልቆጠረው ኢትዮጵያዊ ያቆመውን መሰረትና ያቆየውን ባህላዊ እሴት ልናከብረውና ልንከባከበው ይገባል። በተከታታይ በፕሮፌሰሩ የተጻፉት ጽሁፎች የሚደመድሙት አበሻ ስራ ጠል መሆኑን፣ ሆዳምነቱንና፣ ለማኝነቱን ነው። በሚቀጥለው ጽሁፋቸው ደግሞ ሌላም ሊያስከብሩን የሚገባቸውን ባህሪያችንን ልናፍርባቸው የሚገቡ አጉል ገጽታዎች አድርገው ይጽፉልን ይሆናል። ይህ ወይ እራስን ከፍ ከፍ ለማድረግ ሌላውን ዝቅ ዝቅ ማድረግ በመፈለግ አለዚያም ተስፋ የቆረጠ ሰው አገርን በጅምላው ሊያስነውር የሚያደርገው ድርጊት ይመስላል።
 

ለመሆኑ ፕሮፌሰሩ ሆድ መውደድን እንዴት ይገልጹታል? ምግብ መውደድ፣ መውደድ ብቻ አይደለም አጣፍጦና አስውቦ መብላት አንደምንስ ያስወቅሳል? በውጪው አለም የምግብ ስራ ጥበብ ምንኛ የተከበረ ሙያ መሆኑን፣ ቴሌቪዥኑ በሙሉ በምግብ ስራ ፕሮግራም መጨናነቁንና የምግብ ስራ ጥበብ መጻህፍት ጸሀፊዎች ምንኛ የተከበሩ መሆናቸውን እንዴት ዘነጉት? ምግብ እኮ የህልውና መሰረት ነው በአካል ለመዳበር፣ አእምሮን ለማጎልበት፣ የማስታወስና የማሰብ አቅምን ከፍ ለማድረግ የታመቀውን የተፈጥሮ አቅም ለማውጣት የሚያግዝ ነው። በጣም የሚገርመው ደግሞ ቢወደውም ጥቅሙን ቢረዳውም እንኳ አልሚ ምግብ አግኝቶ ሳይሆን በተገኘው ምግብ ሆዱን ሞልቶ የሚያድር እንኳን በሌለበት ሀገር ውስጥ ለሚገኝ ሕዝብ በረሀቡ ላይ ሆዳም የሚል የስድብ ምርቃት ማከሉ አሳዛኝ ነገር ነው። ምክርም ይሁን ግልጽ ዓላማ የሌላቸው ጽሁፎች መጻፉ ግቡ ኢትዮጵያን ለሚያዋርዱት ‘ምሁራዊ’ ድጋፍ መስጠት ብቻ ይመስለኛል።

 
በምግብ አብዝቶ መብላትና ሲያመነዥጉ በመዋል የሚታወቁት የሌሎች አገሮች ዜጎች ናቸው። ይህንን የማያውቅ ከመንደሩ አለፍ ብሎ የማየት እድል ያልገጠመው ሰው እንጂ እንደ ፕሮፌሰር አውሮፓ ኤዥያና ሰሜን አሜሪካን ያሰሰ ሊሆን አይችልም። ለዚያውም ባንድ ወገን ሆዳምና አይነቱና ብዛቱ ወደር የማይገኝለት ምግብ ስለመብላቱ የሚነገርለት ሕዝብ በሌላው የፕሮፌሰሩ ፅሁፍ ለማኝነቱንና አምላክ ደድብ ያለው ሥራ-ጠልነቱ ይበሰርለታል። አንዱን ፅሁፋቸውን ከሌላኛው ማገናኛ ድልድዩ ምን ይሆን ያሰኛል። ለማኝ እኮ አጣጥሞና አማርጦ ለመብላት ያልታደለ ምርጫ አጥ ነው። ሥራ ጠልቶና ለምኖ አማርጦ መብላት ከተቻለማ ኢትዮጵያችን መና ከሰማይ የሚዘንብባት ሁናለች ማለት ነው።

 
ኢትዮጵያዊም ሆነ ሌላው በገበታ ዙሪያ የሚሰባሰበው ለመብላት ምክንያት በመፈለግ አይደለም፤ ምግቡ የመገናኛው ማጣፈጫ እንጂ። ሰርግም ሆነ መልስ፣ ልደትም ሆነ ተዝካር፣ ፋሲካም ሆነ እንቁጣጣሽ በጋራ ገበታ መቀመጥ መሰረታዊ ምክንያቶቹ ማህበራዊ ግንኙነቶች ናቸው። የሰው ልጅ ማህበራዊ እንስሳ ነው። አብሮነቱን ካላዳበረ ተነጣጥሎ ይሞታልና የትኛውም ማህበረሰብ በየትኛውም የዓለም ጫፍ ቢኖር በራሱ መንገድ ይሰባሰባል። አብሮ ያድናል፣ ተጋግዞ ያርሳል፣ ፈረቃ ገብቶ ያመርታል። ያንን ውበት ለመስጠትና አብሮነቱን ለማሳመር ደግሞ በጋራ ገበታ ይቁዋደሳል። ታዲያ ለምንድን ነው ኢትዮጵያውያን አብረው መብላታቸው ልዩ እንከን ተደርጎ የሚቀርበው? እንዲያውም ኢትዮጵያውያንን ሰብስቦ የያዘው ጠንካራ ድር ቢኖር እንዲህ ያለው በደስታና በሀዘን አብሮ መሆኑ ነው። አብሮ ያቆመን ሲወርድ ሲዋረድ የመጣው ባህላዊ እሴት እንደ ሁዋላ ቀርነትና ሆዳምነት ሲቆጠር ስቆ ማለፉ የሚያስከትለውን እራስን የማዋረድን ጣጣ ልብ ያለማለት ነው። ኢትዮጵያውያን ለዘመናት የቆዩ በአብዛኛው ከሀይማኖት ጋር የተገናኙ አሰባሳቢና አገናኝ በዐላት አሏቸው። በለጸጉ የሚባሉት አገሮች ደግሞ ከሀይማኖታዊ በአላት በተጨማሪ ለንግድ የሚመቹ አዳዲስ በዐላት እየፈጠሩ አብሮነታቸውን የሚያጠናክሩበትን መንገድ ፈጥረዋል። የእናት ቀን፣ የአባት ቀን፣ የፍቅር ቀን፣ የምስጋና ቀን እያሉ አብረው ይበላሉ ይጠጣሉ። ስለዚህም ኢትዮጵያውያንን አብረው በመብላታቸው ሆዳም የሚላቸው በርዕሰ ጉዳዩ ላይ ትንሽም ቢሆን ጥናት ያላደረገ ብቻ ነው።

 

ከዚህ ቀደም እንደ ጻፍኩት ኢትዮጵያውያንን ‘አበሻ’ ባልል እመርጣለሁ ምክንያቱም ኢትዮጵያ የሚለውን ስም ለማሳነስ በርካቶች አበሻ የሚል ስያሜ ላይ በመንጠልጠል መጥፎና ደካማ የሆነውን ነገር ሲያጎሉ ማየት እየበዛ ነው። ‘አበሽ’ የሚለውን የንቀት መሰል አጠራር የሚጠቀሙትም እነማን እንደሆኑ እናውቃለንና ኢትዮጵያ እያልኩ እቀጥላለሁ። እናም ክቡር ፕሮፌሰር የአለም ሕዝብ ከእንቅልፉ ተነስቶ ማዛጋት ሲጀምር ነቃ የሚያደርገውን ቡና…. ፓስታና ማኮሮኒ እያማረጠ የሚበላበትን ስንዴ…. ‘ግሉቲን’ ሆዱን እየነፋው ፊቱን እያዠጎረጎረ የሚያስቸግረውን ሕዝብ ጤናማ የሆነ እሹኝ ፈትጉኝ የማይለውን ጤፍ ጠገብ ሲል ደግሞ የበላውን የሚያወራርድበትን ጥሙን የሚያስታግስበትን ገብስ ለአለም ያበረከተው “ሰነፍ፣ ሆዳምና ለማኝ” እየተባለ የሚዘለፈው የኢትዮጵያ ገበሬ ነው። የሀገሬ ገበሬ ጀምበር ወጥታ እስክትጠልቅ ድረስ የሚተጋ ጠዋት ያሟሸውን አፉን ማታ ባገኛት እፍኝ እህል እየዘጋ የሚኖር ነው። ይህ ደግሞ ከሰማንያ በመቶ በላይ ኢትዮጵያውያንን ይወክላል። ይህ ወገንዎ ክብር እንጂ ስድብ፣ ሙገሳ እንጂ ውርደት አይገባውም። በምንም መልኩ ኢትዮጵያውያንን እርሶንም ጨምሮ እግዜር በጆሮአችንን አታስቡ ብሎ መርጦ አላደደበንም። ያንን ስድብ ተቀብለው የሚኖሩ ደደቦች ካሉ ምህረቱን ያውርድላቸው። ሀገራችንን ለማጥፋት የሚያዋርዱን በቂ ጠላቶች አሉንና እራሳችንን በማዋረድ ለጠላት ስራውን አናቅልለት።

 
ኢትዮጵያውያንን ከሀገራቸው ውጪ የሚያሳዩትን የስራ ፍላጎትና መነሳሳት ለመመልከት እድል ላገኙ ሁሉ ኢትዮጵያውያን ሀገሬውንም ሆነ ሌሎቹን መጤዎች በልጠው ሲተጉና ውጤትም ሲያመጡ እንጂ ሰነፍ በመሆን ከሌላው አንሰው አያዩም። ስለዚህ በጅምላ ኢትዮጵያውያንን ስራጠል ሰነፍ አድርጎ መኮነኑ ውሃ አያነሳም። ኢትዮጵያውያን ስራጠል ከሆኑ በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ወጣቶች ስለምን ወደ አረብ አገር ሊሄዱ ቻሉ? ለልመና ነበር? ለመሆኑ ኢትዮጵያውያን በተሰደዱባቸው ሀገራት በአውሮፓና አሜሪካ በአፍሪካ ሀገራትም እንኳን የሚታወቁት በስራ አይደለምን? ባዶ እጃቸውን ከሀገር ወጥተው አዲስ ሀገር ውስጥ ኑሮ መስርተው ከብረው ለመኖር የቻሉት በአስማት ነውን? ስለዚህ ፕሮፌሰሩ እነዚህ በአንዲት ጀንበር ዘርፈው የከበሩ ነጣቂዎችን መንግስት ብለው መንግስት አንደተቀበለው ቻይና እንዳረጋገጠው ብለው ስንፍናችንን ሲደመድሙ የፌዘኛ እንጂ ምሁራዊ ትችት አይመስልም። አንድን በይሉኝታና በፈሪሃ እግዚአብሄር (አምላክ) የሚኖርን ሕዝብ አዕምሮና ሕሊና ቢስ የሚል ሰው እውን ሕሊናና አእምሮ አለው ብሎ መገመትስ ይቻላልን?
ኢትዮጵያውያንስ እንዴት ሁኖ ነው በሆዳቸው ነው የሚታወቁት የተባለው? ኢትዮጵያውያን ተጋብዘው ድግስ እንኳን ሲሄዱ “ቤታቸው ምግብ የለም እንዴ” ላለመባል እቤታቸው በልተው የሚሄዱ ናቸው። ነፃ ምግብ አለ ሲባሉ ለሳምንት የሚበቃ ቀለብ በሆዳቸው ለመጫን የሚዳዳቸው ሌሎች አንጂ ኢትዮጵያውያን አይደሉም። ኢትዮጵያዊውማ ከሆዴ ይልቅ ክብሬ በማለት እርቦትም አሁን በላሁ ነው የሚለው።

 
ሰዎች ይህንን ስራ ከምሰራ ለምኜ እበላለሁ የሚሉበት ዘመንም ከነበረ በትንሹ ግማሽ ምዕተ አመትን አሳልፏል። ይህም ክስ እውነት እንኩዋን ቢሆን ኢትዮጵያውያንን ለይቶ ከንቱና ርካሽ የሚያደርግበት ምንም ሚዛን የለም። በየትኛውም የአለም ክፍል ቢሆን በአንድ ወቅት የተናቀ ስራ ነበር። ዛሬም ቢሆን ይህን ከምሰራ ዌልፌር ምን አለኝ ብሎ እጁን አጣጥፎ የሚቀመጥ ስንት ፈረንጅ በየሀገሩ አለ። ሌላም አንድ እውነት አለ፣ ሰዎች ከልምዳቸው ውጪ የሚመጣን ነገር የመቀበል ፍላጎታቸው ውሱን ነው። ለምሳሌ ከብት አርቢዎች እርሻን በንቀት ይመለከታሉ። አንዳንድ ከብት አርቢዎች ለምን እነደዚህ ያለ ስራ አትሰሩም የሚባል ከአካባቢው ሁኔታ ጋር የተያያዘ ጥያቄ ሲቀርብላቸው የኛ ዘሮች ይህንን አይሰሩም ይህን የሚሰሩት ሌሎች ናቸው ይላሉ። አንጥረኞች፣ አዝማሪዎች፣ ነጋዴዎች ሁሉም የለመደውን ስራ አጥብቆ መያዝ የኢትዮጵያውያን ብቻ ባህሪይ አይደለም። እንዲያም ሆኖ ኢንጅነሮች፣ የሙዚቃ ጠበብቶች፣ ዶክተሮች የመንግስት ተጡዋሪ ላለመሆንና ለቤተሰባቸው የተሻለ ህይወት ለመስጠት ስራ ሳይንቁ ከጠዋት እስከማታ መኪና በመጠበቅ፣ ታክሲ በመንዳት፣ ዘበኛ በመሆን፣ ጽዳት ሰራተኛ በመሆን ይዳክራሉ። እንዴት ነው ይህን ህዝብ ስራጠል አድርጎ መኮነን የተቻለው?

 
በሀገራችን ያለጥናትና በቂ መረጃ በምሁሩ ምክር የሰው ንብረት መውረስና ማህበራዊም ሆነ ኢኮኖሚያዊ ጥፋት በስመ ሶሻሊዝም በተፈጸመበት ጊዜ የተመለከትነው አንድ እውነት አለ። ሁለት ስራ መስራት አድሃሪነት ነበር ገንዘብ መያዝና ፈጠራ ወንጀል ነበር። ሶሻሊዝምን ያመጣውና መስራትንና መክበርን ወንጀል ያደረገው ተማርኩ ያለው ወገን የመረጠው የሶሻሊዝም መንገድ ነበር። እንዲያም ሆኖ በአዋጅ ሰዎች ድህነትን እንዲቀበሉ በተደረገበት ጊዜ እንደ አቅምቲ ከበርቴ ተብለው ሀብት ንብረታቸው እየተዘረፈ ሰዎች ወደ እስርቤት በተጋዙበት ጊዜ አዲስ አበባ የተከፈቱ ምግብ ቤቶች (ኢድዩ ቤቶች)፣ ባልትና ቤቶች ሁሉ ሕዝባችን ችግሩን ለማሸነፍ ምን ያህል የሚፍጨረጨር እንደነበረ የሚያስመሰክር ታሪካዊ ወቅት ነበር። እነዚያ “እመቤቶችና ወይዛዝርቶች” ሆቴል ቤት ከፍቼ ለማንም ከማስተናግድ ልመና እመርጣለሁ አላሉም።

 
ኢትዮጵያውያኖች ለማኞች መሆናችንን ፕሮፌሰር በተለያየ ምሳሌም አስቀምጠዋል። መንግስትን መጠየቅን፣ ሰውን መማለድን (ድርድርን)፣ ትህትናንና ሰላማዊነትን ፕሮፌሰር በልመናነት መድበውታል። እውነታው ግን እነኚህ ባህሪያት አስተዋይነትንና ህግ አክባሪነትን ነው የሚያመለክቱት። ሁሉንም በጉልበት የሚያስፈጽም ማህበረሰብ በሰላም መኖርም አይችልም። በርካታ ታጋዮች የኔ መንገድ ብቻ ነው ትክክል በማለት የተለየ አመለካከት ባሳየው ላይ ተከታታይ በደልን በመፈጸማቸው ሰዉ ክፉኛ እንዲሸማቀቅ ተደርጎአል። ነገርግን ሕዝቡ የለማኝ ባህሪ ተጠናውቶታል ብሎ መደምደም ከባድ ስህተት ነው። ፕሮፌሰር ደግሞ ሰላማዊ ትግል ብቻ የሚሉ እንደመሆናቸው መጠን ዘራፍ ብሎ ለዱላ ከመጋበዝ ይልቅ መንግስትን በጥሞና መማለድን የሚደግፉ ኢንጂ እንዴት የሚኮንኑ ሊሆኑ ይቻላቸዋል?

 

የመጽዋችና የተመጽዋች ግንኙነት ያለው ደግሞ በኢትዮጵያ ብቻ አይደለም። ምክንያቱም ያለውና የሌለው በየሀገሩ ነው ያለው። ያለው ደግሞ ለተቸገረው መቸርን የማያውቅ ከሆነ በሰላም ወጥቶ መግባትም አይቻልም። ከመለመን ይልቅ በጉልበት ቀምተው የሚወስዱ ነጣቂዎች የበረከቱበት ሀገር ይሻላል የምንል ካለን የማሰብ አቅማችን ተናግቶአል ማለት ነው። ኢትዮጵያውያን ካላቸው ላይ ቀንሰው ለሌላው መስጠታቸው የስነምግባርና የሞራል ባለጸጋ መሆናቸውን ያመለክታል እንጂ ልመናን የሚያበረታቱ ሰነፍ ማምረቻዎች አያሰኛቸውም። ጧሪ ያጡ አዛውንቶች፣ የአካል ጉዳተኞችና ህመምተኞች በመሆናቸው ስራ ማግኘት የማይችሉና ጤነኛም ሆነው ስራ ማግኘት ያልቻሉ መለመን ሊገደዱ ይችላሉ። ይህ ሰነፍ አያስብላቸውም። ባደጉት ሀገራትም የ ‘ዌልፌር/ድጎማ’ አሰራር አላቸውና ድጋፍ ለሚሹ ወገኖች የተለያዩ እርዳታዎችን ይለግሳሉ። ይህ መንግስታዊ ድጋፍ በሌለባት ኢትዮጵያ ወገን ወገኑን መርዳቱ አስፈላጊና የሚደነቅ እንጂ የሚያስወቅስ አይደለም። ኢትዮጵያውያን ይህንን የመረዳዳት ባህል ባያሳድጉ ኖሮ የኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት በተበተነ ጊዜ መሳርያውን ተሸክሞ ሰለ እግዚአብሄር ውሀ ስጡኝ ብሎ ባልጠየቀ ነበር። ተደራጅቶ መዝረፍ ሲችል ወርቅ ቤት ተደግፎ የሚለምን በዲሲፕሊን የታነጸ ጦር ኢትዮጵያ ብቻ በመኖሩ ጨዋና ህግ አክባሪ ያደረገንን ባህል ልናመሰግን ይገባል። ከዚህም ባሻገር ‘ልመና’ የሌለበት አገር የለም። አሜሪካም ሆነ አውሮፓ ወይም ኤዥያ በውበቱ ከሚያፈዝ ህንጻ ስር ቆቡን ዘርግቶም የሚለምን ሆነ ፕሮፌሰር እንደጠቅሱት የድሬዳዋ ለማኝ ብር ስጠኝ እያለ እንደማዘዝ የሚያደርገው ለማኝ ሞልቶዋል።

 
ልመናና ጸሎት ተመሳሳይ ትርጉም ከተሰጣቸው ደግሞ ሁሉም አገሮች ውስጥ ጸሎት አለና ልመናው አለምን አስጨንቆአል ማለት ነው። ድርድርም ልመና ከተባለ በትህትና የቀረቡ ጥያቄዎች ሁሉ ልመና ይደረጋሉና ጨዋነት እንደክፉ ባህሪ ሊታይ ነው ማለት ነው። ላሊበላነትም የልመና መስክ ሆኖ ተተችቷል። ነገር ግን ዘፋኝ ሲዲ አሳትሞ ለገበያ ሲያቀርብ ለማኝ አንለውም። አዝማሪዎችና ላሊበላዎች ደግሞ ዛሬ ላለው ኪነታዊ ጥበብ መሰረቶች ናቸው። ስለምን የቀድሞውን ነገር ሁዋላ ቀርና እርባና ቢስ እንደምናደርግ አይገባኝም።
የቆሎ ተማሪ በልመና ስለተለከፈ አይደለም የሚቀፍፈው። የሀገሬ ባላገርም የትምህርትን አስፈላገነት ስለተረዳ ካለችው ቆንጥሮ ያካፍላቸዋል። ፕሮፌሰርም ሲማሩ የተሰጣቸው መማርያ፣ የጠጡት ወተትና ልብሳቸውን ያጠቡበት ሳሙና እንደ ቆሎ ተማሪዎች ሰለ ማርያም ብለው ቆዳ ለብሰው ቀፈፋ ባይዞሩም ያው ከንጉሱና ከህዝቡ ቀፈፋ ነበር። እኛ ካልቻልንበት ያልቻልነውን በመጠቆም ማሻሻል እንጂ ያለፈው ትውልድ በቻለውና ባወቀበት መንገድ ሰርቶ ያቆመልንን አገር ማዋረድ ወንጀል ነው።

 
ኢትዮጵያ እንደ ሀገር የቆመችው ባሉን ማህበራዊና ባህላዊ እሴቶቻችን ነው። የድሮውን አሳድጎ ዘመናዊ ማድረግ ወይም የተኮረጀውን ከሀገር አስማምቶ ጥቅም ላይ ማዋል ስላቃተን የነበረውን ስንወነጅል ልንኖር አይገባም። አገርን በጅምላ ስንወነጅል ራሳችን የምናበረክተውን እንገምግም። ራስን እያዋረዱ ክብር መሻት ሞኝነት ነው። ከልመና ለመውጣትና ገበና ለመሸፈን አስፈላጊ የሆኑ ተቋማት እንዲፈጠሩ ማበረታት ያሉትንም ማጠናከር እንጂ ወገን በሀዘኔታ ካለችው ላይ ስለሰጠ የተቸገረም ስለለመነ ማውገዙና በሽሙጥ መውገር ምን ይረባናል? ማንም በእርግጠኛነት ሊናገር የሚችለው ኢትዮጵያውያን ለማኝ፣ ሆዳምና ሥራ-ጠል ሳይሆኑ ዘመናትን የሚሻገር ባህልን ያሳደጉ ሲቸገሩ ተረዳድተው ሲመቻቸው አብረው ተደስተው የሚያኖራቸውን ባህል ያቆዩ ታታሪ ሰራተኞችና የሚረዳዱ መሆናቸውን ነው። የእውቀት መነጽራችን ይህንን ላላስመለከተን መቃወምና መንቀፍ ብቻ የእውቀት ምልክት የሚመስለን ህዝብን ከመስደቡ ብንታቀብና የማስተዋል አቅማችንን ብናዳብረው ይበጃል።

 
ሀገር አዋራጅ መሰረተቢስና ውልየለሽ ጅምላ ስድብን እውነት ነው ብሎ መቀበል ተቀብሎም ስድቡ ይገባናል በማለት እየተቀባበሉ መሰዳደብ ትክክል አይደለም። ስለዚህም በተከበሩ ፕሮፌሰር ስለተጻፈ ብቻ እንደታላቅ ግኝት በየሚዲያው ማሰራጨቱም “ሞኝን አንዴ ስደበው እራሱን ሲሰድብ ይኖራል” የሚለውን ብሂል በተግባር ማዋል ይሆናል። ኢትዮጵያንና በልጆቿ እየተሸረሸረ ያለውን ኢትዮጵያዊነትን እናድን ዘንድ እንትጋ።

 
comment_stage_5biyadegelgne@hotmail.com

 

 

እኔ ጃዋርን ብሆን ኖሮ ከዓለማየሁ መሀመድ(2)

$
0
0

ከዓለማየሁ መሀመድ(2)

በትላንቱ ጽሁፌ ጃዋርና ህወሀት የፈጸሙትን ለጊዜው መረጃው ብቻ ስላለኝ ያጋብቻ ጉዳይ አንስቼ በቀጠሮ ነበር የተለያየነው። ማስረጃው በቅርቡ እጄ እንደገባ ሰማንያ ተፈራርመው የሰሞኑን የፌስቡክ ግርግር እንዴት እንደገቡ ይፋ አደርጋለሁ። እስከዚያው ታገሰኙ።

ለአሁን ጃዋርን ብሆን አማረኝ

አዎ! ጃዋርን ብሆን ይሄን ጊዜ እነዚህን ነገሮች አደርጋለሁ

1. የኬንያና የህወሀት መንግስታት ተስማምተው የኦሮሞ ልጆችን እያደኑ ነው። ሰሞኑን ከወደ ኬኒያ እንደሚሰማው ከ 500 በላይ የወያኔን መንግስት ሸሽተው ኬኒያ የተጠለሉ ኦሮሞዎችን ኬኒያ አሳልፋ እየሰጠች ነው። በኦሮሞ ነጻነት ግንባር ኦነግ ስም ኦሮሞች ተለቅመው ለወያኔ መንግስት እየተሰጡ ነው። ይህ ዘመቻ አሁንም ቀጥሏል። እናም እኔ ጃዋርን ብሆን ኬኒያ እያደረገች ያለችው ድርጊት ዓለም ዓቀፉን የስደተኞች መርህ የሚጣረስ በመሆኑ ለመንግስታቱ ድርጅት፡ ለዓለም ዓቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ተቋማት፡ ለኬኒያ ፓርላማ እና ለሌሎች ድርጅቶችና መንግስታት አቤቱታ እንዲቀርብ አስተባብራለሁ። ጊዜ የሚሰጠው ጉዳይ ባለመሆኑ ያለኝን ማህበራዊ ቦታና ተቀባይነት ተጠቅሜ፡ ሰፊ የቅስቀሳ ስራ በማከናወን ኬኒያ ላይ ጫና እንዲፈጠር አደርጋለሁ።

2. በምስራቅ ሀረርጌ ከሶማሌ ክልል ድንበርተኛ በሆኑ ወረዳዎች ላለፉት ሶስት ዓመታት በልዩ የሶማሌ ክልል ታጣቂዎች እየተፈጸመ ያለው መጠነ ሰፊ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ሰሞኑን ተባብሶ መቀጠሉ እየተነገረ ነው። የሶማሌ ልዩ ሃይሎች የኦሮሞ ሴቶች እየደፈሩ፡ናቸው። ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው በተለያዩ አጎራባች አከባቢዎች የተሰደዱት ወገኖች ቁጥር ከፍተኛ ነው። የሚበሉት ያጡ ህጻናት እየረገፉ ናቸው። እናም እኔ ጃዋርን ብሆን ተመሳሳይ የቅስቀሳ ዘመቻ በመክፈት ጉዳዩ በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ሰሚ እንዲያገኝና ወገኖቼ ከስቃይ እንዲድኑ የሚቻለኝን አደርጋለሁ። የገቢ ማሰባሰቢያ መድረኮች እንዲዘጋጅ እየቀሰቀስኩ ገንዘብ አሰባስቤ ለእነዚያ እየረገፉ ላሉት ህጻናት፡ መሄጃ መድረሻ ላጡት ወገኖቼ እደርስላቸው ነበር።

3. የወያኔ እስር ቤቶች በኦሮሞዎች ተጥለቅልቋል። በቅርቡ ኢንጅነር ተስፋሁንን ጨምሮ በርካታ ኦሮሞዎች በወያኔ የጭካኔ ተግባር በእስር ቤት እያሉ ህይወታቸውን አጥተዋል። ከሰሞኑ ሁለቱ የኦሮሞ መብት ታጋዮች አቶ በቀለ ገርባና አቶ ኦልባና ሌሊሳ በአንድ ዓይነት ህመም እየተሰቃዩ ነው። ህክምና ተነፍገው በከፍተኛ ስቃይ ላይ እንዳሉ ተሰምቷል። እናም እኔ ጃዋርን ብሆን ለእነ አምንስቲ ኢንተርናሽናል፡ ሂውማን ራይትስ ዎች እና ተጽእኖ ለሚፈጥሩ አካላት ጉዳዩን በማሳወቅ እስረኞቹን ከሞት እታደጋለሁ። ገንዘብ እንዲሰባሰብ በማድረግ ለእስረኞቹ ቤተሰቦች እርዳታ እንዲደረግ እቀሰቅሳለሁ።

ሌላም…. ሌላም…..

ግን ጃዋርን አይደለሁም። ባለኝ አቅም ጥረት እያደረኩ መሆኔን ግን መግለጽ እፈልጋለሁ። ጃዋር ካለው ማህበረሰባዊ ተቀባይነት አንጻር ከእኔ የተሻለ ውጤት ሊያስመዘግብ ይችላል ከሚል መነሻነት ነው ጃዋርን መሆን ያማረኝ።

ጃዋር ጆሮው ላይ የሚያቃጭለው የሙታን ድምጽ ነው። በዓይነ ህሊናው የሚሽከረከረው የሙት መንፈስ ነው። እየተላፋ ያለው ከማይጨበጥ ከማይዳሰሰው ጋር ነው። በህይወት ስላሉት ከንፈር እንኳን መምጠጪያ ጊዜ አላገኘም። ጠዋት ተነስቶ እስኪመሽ በኮምፒውተሩ ቂጥ ስር ተወሽቆ ኦሮሞ ፈርስት እያለ ማላዘኑ ተመችቶታል። የኬኒያዎቹ ኦሮሞዎችን ስቃይ የሚሰማበት ጆሮ የለውም። ለምስራቅ ሀረርጌዎቹ ህጻናት ሲቃ ጊዜም ሊሰጥ አልፈቀደም። በየእስር ቤቱ ለሚሰቃዩ የኦሮሞ ልጆች የሚያዝን ልቦና አልሰጠውም። ጸሀይ ወጥታ እስክትጠልቅ ከታሪክ ተራራ ጋር ይላፋል። ይቸከችካል። መሰሎቹ ጃስ ሲሉት ደስ ይለውና አሁንም ይቸከችካል። ሙቀቱ ተመችቶታል። ጭብጨባው ልቡን ላይ የትዕቢት ተራራ ቆልሎለታል። ድሮውንስ የኦሮሞ ህዝብ ስቃይ ለሱ የግል ዝና መሸመቺያ እንጂ መቼ መቆርቆር ከአጠገቡ ደርሳ?

ለማንኛውም በቅርቡ የጃዋርንና የህወሃትን ጋብቻ የተመለከተውን ማስረጃ ይዤ እመለሳለሁ። ለዘነጋችሁ; ጃዋር የወያኔ አሻንጉሊት የሆነው ኦህዴድ ልጅ ነው። ውለታ አለበት። ለአቅመ ፖለቲካ እንዲደርስ ያበቃውን ኦህዴድን(ህወሀትን) ቢረሳ አምላክም ደስ አይለውም። ወደፊት የማካፍላችሁ ዕውነትም ከዚሁ ጋር የተያያዘ ነው።

በመጨረሻም ለፈርስቶች መልካም የጩኧት ጊዜ። ሙቀቱ ሲለቃችሁ እንገናኝ።

comment pic

የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ጠቅላላ ጉባኤ ተከፈተ::

$
0
0
Andinet Party

ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳ ‹‹የአባይ ግድብ በየትኛውም መመዘኛ የአንድ ግለሰብና ፓርቲ ራዕይ መሆን አይችልም፡፡ኢህአዴግ ራሱን የግድቡ ባለቤት በማድረግ ተቃዋሚዎችን በተለይም አንድነትን የግብጽ መንግስት ተላላኪ አድርጎ መሳሉ ነውረኝነት ነው፡፡አንድነት አሁንም ኢትዮጵያ አባይን የመጠቀም ህጋዊና ታሪካዊ መብት ያላት መሆኑን አንድነት ያምናል፡፡አንድነት የትም ፍጪው ዱቄቱን አምጪው የሚል አስተሳሰብ እንደሌለው በድጋሚ ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡

‹‹2007ን ለዲሞክራሲያዊ ለውጥ ›› በሚል መሪ ቃል ከመላ ሃገሪቱ ተወክለው የመጡ ከ450 በላይ የአንድነት አመራሮች/አባሎች በተገኙበት በዛሬው ቅዳሜ እለት ጠቅላላ ጉባዬውን ፓርቲው በደመቀ ሁኔታ እያካሄደ መሆኑን ከአዲስ አበባ ምንጮች ገልጸዋል:

የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ በቀጣዮ የ2007 አገር አቀፍ ምርጫ መሳተፍ የምርጫውን ሜዳ መስፋትና መጥበብ ተከትሎ የሚወሰን መሆኑን አቶ ዘካሪያስ የማነብርሃን ገልጸዋል፡፡

የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ በቀጣዮ የ2007 አገር አቀፍ ምርጫ መሳተፍ የምርጫውን ሜዳ መስፋትና መጥበብ ተከትሎ የሚወሰን መሆኑን አቶ ዘካሪያስ የማነብርሃን ገልጸዋል፡፡

ይህ በዛሬው እለት የተከፈተው የጠቅላላ ጉባዬ ስብሰባ ነገም የሚቀጥል ሲሆን እንዲሁም በተጨማሪ ዛሬ ቅዳሜ ለሊቱን የፐርቲው ስራ አስፈጻሚ ስለወደፊቱ የፓርቲው የትግል ስልትና ብቃት ያላቸው አባላትን በመመልመል የፓርቲውን አደረጃጀት አሁን ካለው በእጥፍ በማሳደግ በ2007ዓ.ም በሚደረገው ሀገር አቀፍ ምርጫ ህዝብን አስተባብሮ በአሸናፊ ለመውጣት በሚቻልባቸው ስልቶች ዙሪያ የጠለቀ ውይይት ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል::

Andinet Party 4አንድነት ለጠቅላላ ጉባዬው የሚሆን አደራሽ ለማግኘት በየሆቴሉ እና አደራሽ አከራዮች ቢፈልግም ከገዢው ፓርቲ በተደረገ ማስፈራሪያና ተጽእኖ ማንም ሊያከራየው ፈቃደኛ ካለመሆኑም በላይ የህዝብ ንብረት የሆነውም የምርጫ ቦርድ አደራሹን ሰበብ በመፍጠር ከልክሎታል::

ከአፋር ክልል ተወክለው የመጡት የአንድነት አባል ሚከተለውን ብለዋል “ኢህአዴግ ወድቋል እሱን ለማስወገድ ያቃተን በኛ ችግር ነው፤ ኢትዮጵያ የባህር በር ያስፈልጋታል አንድነት ለአፋር ክልል የበለጠ ትኩረት ይስጥ” ብለዋል፡፡ ከኦሮሚያ ቦረና ዞን የተወክለው የመጡት አባል በበኩላቸው ኢህአዴግን ለመጣል እታች ድረስ የተዘረጋው መዋቅር መጠናከር እንዳለበት ተናግረዋል፡፡ ከቤንሻንጉል ክልል ተወክለው የመጡት አባል በ2005ዓ.ም ይደረጋል ተብሎ የነበረው ሰላማዊ ሰልፍ በመቅረቱ ህብረተሰቡ ቅሬታ ማቅረቡን ተናግሯል፡፡

 

 

 

 

 

 

 

አንድነት ፓርቲና ዴሞክራሲያዊ ባህሉ
————————————
በነብዩ ኃይሉ
—————–
መጪዎቹ ሁለት የእረፍት ቀናት ለአንድነት ፓርቲ አባላት በናፍቆት የሚጠበቁ ሆነዋል ፤ ምክንያቱ ደግሞ ለወራት ዝግጅት ሲደረግበት የቆየው የፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤ ቅዳሜና እሁድ (ታህሳስ 19 እና 20) የሚካሄድ መሆኑ ነው፡፡ የአንድነት ፓርቲ የቀደመ ተሞክሮ እንደሚያስረዳው ከፍተኛ የስልጣን አካል የሆነው ጠቅላላ ጉባኤ እንዲያው ለወጉ የሚሰበሰብ አይደለም፡፡ ይልቁኑም በግልፅ የሚታይ የአመራር ለውጥ የሚደረግበትና ወሳኝ ፖለቲካዊ ውሳኔዎችም የሚስተናገዱበት ነው፡፡

አንድነት በ2001 እና በ2004 ባደረጋቸው ጠቅላላ ጉባኤዎች በግልፅ የሚታይ የአመራር ለውጥ ማድረጉ ይታወሳል፡፡ ይህ የፓርቲው አካሄድ በሀገር ደረጃም ቢደረግ የሚያስብሉ ዴሞክራሲያዊ ክዋኔዎችንም ያካተተነው፡፡ በሌሎች ፓርቲዎች ሲደረግ የማይስተዋል ቢሆንም አንድነት በሁለቱም ጉባኤዎች ሊቀመናብርቱን የመረጠው ጠንካራ ፉክክር ካደረጉ በኋላ ነው፡፡

በ2001ዓ.ም በተደረገው የፓርቲው የመጀመሪያ ጠቅላላ ጉባኤ ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ፣ ኢ/ር ግዛቸው ሽፈራው እና አቶ ተመስገን ዘውዴ ጠንካራ ፉክክር ካደረጉ በኋላ ጉባኤው ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳን በሊቀመንበርነት መርጧል፡፡

በ2004ዓ.ም በተደረገው የፓርቲው ሁለተኛ ጠቅላላ ጉባኤም ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ፣ ዶ/ር ንጋት አስፋው እና ኢ/ር ዘለቀ ረዲ ጠንካራ ፉክክር ካደረጉ በኋላ ጉባኤው የቀድሞውን የሀገሪቱን ፕሬዘዳንት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳን የአንድነት ሊቀመንበር እንዲሆኑ መርጧል፡፡

አንድነት በመጪው ቅዳሜና እሁድ (ታህሳስ 19 እና 20) በሚያደርገው ልዩ ጠቅላላ ጉባኤም በግልፅ የሚታይ የአመራር ለውጥ ለማደረግ ተዘጋጅቷል፡፡ ኢ/ር ግዛቸው ሽፈራው፣ አቶ ተክሌ በቀለ እና አቶ ግርማ ሰይፉ የምረጡኝ ቅስቀሳቸውን ተያይዘውታል፤ አንድነትም ይህን ዴሞክራሲያዊ ባህሉ አንግቦ የኢትዮጵያን ህዝብ የስልጣኑ ባለቤት ለማድረግ የጀመረውን ጉዞ ይቀጥላል፡፡

እኔ ኣላውቅም ፈራሁ ጁሃር (ሄኖክ የሺጥላ)

$
0
0

የበደሌ ቢራ ፋብሪካ ከአዲስ አበባ 483 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ኢሉ-ኣባ-ቦራ ( Eloo The father of Holstein Friesian) ኢልባቡር ከተማ በሁለት መቶ ሃምሳ ሺ ስኩውር ሜትር ይዞታ ላይ ስራውን እንደ ኣውሮጳውያን ኣቆጣጠር በ 1993 ማከናወን የጀመረ ትልቅ የቢራ ማምረቻ ድርጅት ነው።

ኢሊባቡር መልካም ምድራዊ ኣቀማመጡም ሆነ ምድራዊ ልምላሜው፥ እንደ በቆሎ ፤ ገብስ፤ ጤፍ፤ የቅባት እሎች፤ ማር፤ ከነ ቦራ ደሞ ወተት፤ ቅቤ እና ወዘተ የሚዘራባት፤ የሚታጨድባት፤ የሚቆረጥባት፤ የሚታለብባት ሃገር እንድትሆን ኣድርጉዋታል።

Henok-Yeshitela-150x150

Poet Henok-Yeshitela

ኢሊባቡርን የጽሁፌ መንደርደሪያ አደረኩ እንጂ ዋናው ነጥቤ እሱ አይደለም። ዛሬ መናገር ወይም መጻፍ የፈለኩት ቴዲ አፍሮ በቅርቡ በመላው ኢትዮጵያ የሙዚቃ ዝግጅቱን እንዲያሳይ ወኪል የሆነውን የበደሌ ቢራን ያለመጠጣት አድማ ( boycotting) በመላው ኢትዮጵያ ይደረግ ዘንድ አንዳንድ ግለሰቦች የጀመሩትን ነገር ሰምቼ፤ ለምን በደሌን፤ ለምን ቴድን የሚል ጥያቄ ለሚጠይቁ፤ መልስ የሚመስለኝን ለመተየብ፤ ከተቻለም ለማሳየት መመኮር በመሻቴ ነው ።

ቴዲ አፍሮ በቅርቡ በ ጋዜጣ ላይ ስለ አድዋ ድል በሰጠው አስተያየት የተቆጡ፤ የተቀየሙ ግለሰቦች፤ ቴዲ አፍሮ ጥቁር ሰው ብሎ ንጉስ ሚኒሊክን፤ ከዛም በላይ አድዋ ድልን በመዘከሩ የተበሳጩ የህብረተሰብ አካሎች፤ ቴዲ አፍሮ ከዚህ ቀደም ጃ ያስተሰርያል ብሎ በመዝፈኑ ቂም የቁዋጠሩ ሰዎች፤ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በሊግ ኦፍ ኔሽን በ 1936 የኢጣልያንን የተለከለ የኬሚካል መሳሪያ መጠቀምን በመቃወማቸው፤ ኢትዮጵያን የ ዩናትድ ኔሽን ኣባል በማድረጋቸው፤ ቅራኔዎችን አብርደው ያፍሪካን ህብረት በመመስረታቸው፤ ለነዚህ ጉልህ አስተዋጾዎቻቸው በመዝፈኑ፤ ለነዚህ ለተጠቀሱት መልካም ስራቸው መታሰቢያ የጭንቅላቱ ውጤት የሆነውን ሙዚቃ በማበርከቱ፤ ቴዲ አፍሮ ፤ አቀንቃኝ ና አዝማሪ ፤ ገጣሚና ስዓሊ፤ ሃያሲና ደራሲ፤ ጸሃፊ ተውኔቱና ብላታው፤ አፉን በለጎመበት ዘመን፤ በብእሩ የታሪክ ጋሻ፤ በግጥሙ ለቆሰለ ታሪክ ማገገሚያ፤ በዘፈኖቹ ( ከ ማሊ ሱፊዎች ባልተናነሰ መልኩ) የነብስን ክር እየተጫነ ያላስለቀሰው፤ ያላስተከዘው፤ ሰው እንደሌለ የገባቸው ሰዎች፤ በይበልጥም የአድዋ ድል፤ የጥቁር አንበሳዎች ድል መሆኑን ያሳየበት በመሆኑ እና ይህም የሚያማቸው ሰዎች፤ ዛሬ በደሌ ቢራ ቴዲ አፍሮን ስፖንሰር ስላደረገ፤ በደሌ ቢራን ያለመጠጣት አድማ ጠርተዋል። አሁን ቴዲ አፍሮን አብዶ በረንዳ ( የጫት ማከፋፈያ በረንዳ ነው) ቢሆን ስፖንሰር ያረገው ምን ሊሉ ነበር።። ባረገው እና የተከታዮቻቸውን መልስ ባየን። አንድ ጊዜ ቆይ ጠብቁኝ ሳቄ መጣብኝ ያለው ተናጋሪ ማን ነበር።

አዲሱ የቴዲ አፍሮ አልበም ( ጥቁር ሰው) የብዙዎቹን ኢትዮጵያዊያኖች ድምጽ ያስገኘለትን ያህል፤ ንጉስ ሚኒሊክ በድሎናል፤ ጡታችንን ቆርጦዋል፤ ወዘተ ወዘተርፈ ለሚሉት ደሞ፤ ከሚኒሊክ መፈጠር፤ ከታሪክ አንቅጽነቱና አኩሪ ገድሉ ጋር የጀመሩትን እጹብ ጸብ ውሃ የሚደፋበት በመሆኑ፤ ጠላት ሊያፈራበት እንደሚችል መገመት ብዙም አይዳግትም። እናም እነዚህ ሰዎች ቀደም ብዬ እንደ ጠቀስኩት፤ በደሌ ቢራን ያለመጠጣት አድማ እናድርግ እያሉ ነው። ልክ ናቸው፤ ህዝብ በጥላቻም በቢራም ሰክሮ እንዴት ይሆናል፤ ባንዱ ብቻ ይበቃልና።

በነገራችን ላይ ይህንን አድማ ለማስመታት ከሚራወጡት እና ከሚሯሯጡት ሰዎች መሃከል አንዱ ጁሃር መሀመድ መሆኑን ሰምቼ አፍሬ ጥፍሬ ውስጥ ልገባ ነበር። ባንድ ወቅት ይሄ ወጣት ፖለቲከኛ ስለ ራሱ ሲናገር “እኔ እናቴ መንዜና የኦርቶዶክስ ክርስቲያን ነች አባቴ ደሞ ኦሮሞና ሙስሊም ነው ፤ ታዲያ ከኔ በላይ ኢትፖጵያዊነትን የሚወክል ምንነት ኣለ ወይ” ብሎ ነበር። መልሱ ሊሆን ይሚችለው ጁሃርዬ በውነትም የለም፤ እንዳንተው አቶ መለስም እኮ የተላቀቀ ነገርን ማጣበቅ የሚችል (ኡሁ የሆነ) (UHU…glue) ደም ነበራቸው፤ ግን ደሙ ሳይሆን የደሙ ባህሪ ነው ወሳኙ ነገር። የተሸከምነው ደም ሳይሆን በውስጣችን ያፋፋነው ስብዕና ነው ማንነት ፤ ማንነት ስራ ነው እንጂ አንተ እንዳልከው የ-ኢ-ተጎራባች ዘር ደም ውህደት (ኬሚስትሪ ውጤት አይደለም)፤ ክርስቶስ ( ኤሳው… ኣለይሁ ሰላም) በ-በረት ተወለደ ብለን እናምናለን፤ ግን እንደ ሰብኣዊ ፍጡር በ-በረት መወለዱ ሳይሆን ሰው ሆኖ ሲኖር ያደረገውን ነገር ነው የምናስበው፤ ስለ ነብዩ ሙሃመድ (ሰ.አ.ወ) ኣንድ ሙስሊም ሲያስብ ስለ ዘራቸው ሳይሆን ስለ ስራቸው ነው የሚያስበው ብዬ አስባለሁ ።

ባንድ ወቅት ይሄው ሰው፤ ፹ ከ ፻ የሚሆነው የሃገሬ እስላም ኦሮሞ ነው፤ እናም የኦሮሞ ህዝብን ኢምፓወር ማድረግ፤ እስልምናን ኢምፓወር እንደማረግ ነው አለን፤ ለመስማት አይደል የተፈጠርነው እናም ሰማነው፤ ባሜጃ አለን ዝም ብለን ሰማነው፤ ቀጥሎም ኢትዮጵያ አውቶ ኦፍ ኦሮሚያ አለን እሱንም ሰማነው። በነገራችን ላይ ኢትዮጵያ ኣውት ኣፍ ኦሮሚያን ወደ ፈርንጅኛ ስቀዳው ( the child give birth of her mother) ኣይመስላችሁም ? ለመተርጎም የተገደድኩት የመጀመሪያው ራሱ እንግሊዘኛ መሆኑን ስለተጠራጠርኩ ነው። ለነገሩ ስታንፈርድና ኮሎምቢያ ዩንቨርስቲ እኮ መፈክር አያስተምሩም።

እና ዛሬ በደሌ መጣ እና ወንድሜ ጁሃር ሰማኒያ ከመቶ ካለው ሃሳብ ጋ ግንባር ለግንባር ተጋጨ ( head on collusion) እናም ሁለት የሚጋጩ ነገሮችን እንግዲህ እናስተውላልን።

፩) መቼም ፹ ከመቶው እስላም ኦሮሞ ነው ብለኽን፤ አንተም በዘር ብቻ ሳይሆን በእምነትም ጭምር ጠበኽ፤ ኣልገባኝም ታዲያ እንዴት ነው፤ እነማን ቦይ ኮት እንዲያረጉልኽ ነው ጥሪውን ያቀረብከው፤ ፳ ፐርሰንቱ እስላም ያልሆነው ኦሮሞ ? ደሞ ከ ፹ ከመቶ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ውስጥም ቢሆን አዲስ የበደሌ አድመኛ ማግኘት ይቸግራል ብዬ አስባለሁ፤ ምክኒያቱም እነሱ ላንተ ሲሉ ሳይሆኑ ለዲናቸው ሲሉ ድሮም እንዲህ አይነቱን ነገር ይነኩት ነበር ብዬ አላስብም፤ በፍጽም አያደርጉትም፤ ታዲያ የማይጠጡ ሰዎችን ነው አድማ የጠራነው፤ ወይስ ሙሉ የኢትዮጵያዊነት ማሳያ ምሳሌ እንድትሆን ያደረገችህ የመንዜዋ እናትህን ዘመዶች፤ እኔ ኣላውቅም ፈራሁ ሄኖክ ነው ያለኝ የልጅነት ጉዋደኛዬ፤ ባንድ ትልቅ የውሃ ጉድጉዋድ ውስጥ እንሹለክ ስለው። እኔ አላውቅም ፈራሁ ጁሃር።

ዛሬ ጀርመን ያላትን ቅርጽ እንድትጠብቅ ወይም እንዲኖራት ያደረገው ኦቶ ቮን ቢስ ማርክ፤ የደም ትግል ውጤት ነው። ታዲያ ጀርመኖች በ ቢስ ማርክ ተናደው ፒሊሲነርን ( የጀርመን ታዋቂ ቢራ ነው) ቦይ ኮት እናርግ አላሉሉም። በፈረንሳይ እንዲህ የሚባል ታሪክ አለ፤ በአሜሪካም፤ ኣረ ሆመር በጥንታዊያኖቹ የግሪክ ዘመን ስለነበረው ጦርነትም ጽፎዋል፤ ስለ ስርኣቱ፤ ስለ አገማምኖን እና የወንድሙ መንግስት፤ ስለ ሄለናዊው ስርዓት፤ ከዚያም በሁዋላ እነ ዳንቴ ስለ ጻፉት ስለ ዲቫይን ኮሜዲ፤ ፍሬድሪክ ዊልሃልም ኒቺ ስለተራቀቀበት የማህበረሰብ ስነ ልቦና፤ እነ አልበርት ካሙ ስለጻፉለት የፈረንሳይ ማህበረስብ እና በየስራቶቹ ውስጥ ስለ ነበርው ፍዳ፤ እነ ልዮ ቶሎስቶይ በሰላ ብእራቸው ስለዘገቡት የሩሲያ የጭቆና ቦለቲካ፤ እነ ፓብሎ ፒካሶ ጉሬንሽያ ብለው ስለገለጹት የስፔን ከተማ ስለ ስንቱ ለዚህ ለወጣቱ ፖለቲከኛ እንንገረው እስኪ ባክህ ጁሃርዬ ገረፍ ገረፍ አርጋቸው (በቃ እንደውም ለዚህ ክረምት ለፐርሰናል ዲቨሎፕመንት…ትመለከታቸው ዘንድ እጠይቅሃለሁ (ማሳሰቢያ በኣብዛኛው በአማራ ጻሀፊ አይደልም የተጻፉት ቢሆኑም ደሞ ኣነተ ሃምሳ ፐርሰንት አማራ አይደለህ እንዴ፤ የምሬን እኮ ነው)

በታሪክ ላይ ጥላሸት መቀባት በፍጹም ለማንም አይሳካም፤ ወደድንም ጠላንም፤ ጠቅልለን የምንጎርሰውን እንጀራ የፈጠሩት አባቶቻችን ናቸው፤ ለሆዳችን ያለን ቅርበት ለታሪካችንም ይኑረን። ቴዲ እንዳለው ክፉውን በክፉ ለመመለስ ማሰብ ሌላ ክፉነት ነው። ሁለቱ ደሞች እንደ ደም ይሰሩ፤ ያስቡ ዘንድ ሰው እንሁን።

ሄኖክ የሺጥላ

 

 


ፍትህ የተጠማች ነብስ (Video)

ሆቴል ውስጥ የተደባደቡት የብሔራዊ ቡድናችን ተጫዋቾች ሲሳይ ባንጫንና አበባው ቡታቆ ተቀጡ

$
0
0

Abebaw-Butakoየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዲሲፕሊን ጥፋት ፈፅመዋል ባላቸው ተጫዋቾች ሲሳይ ባንጫ እና አበባው ቡታቆ ላይ የገንዘብ ቅጣት መንግስታዊው ሚዲያ ራድዮ ፋና ዘገበ። ሲሳይ ባንጫ የአስር ሺህ አበባው ቡታቆ ደግሞ የአምስት ሺህ ብር ቅጣት ነው በፌዴሬሽኑ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ የተወሰነባቸው።
እንደ ፋና ዘገባ ተጫዋቾቹ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ካላባር ላይ ከናይጄሪያ አቻው ጋር ከተጫወተ በኋላ ቡድኑ ባረፈበት ሆቴል ውስጥ በመጣላታቸው ነው ቅጣቱ የተወሰነባቸው። ፌዴሬሽኑ ዛሬ ባወጣው መግለጫ እንዳመለከተው ግብ ጠባቂ ሲሳይ ባንጫ ከቡድን አጋሩ ጋር መጣላቱን በማመን ይቅርታ ጠይቋል።
ራድዮው ጨምሮም በተመሳሳይም ተከላካዩ አበባው ቡታቆ የፀቡ መነሻ እንዳልሆነ በመግለፅ ነገር ግን ከቡድን አጋሩ ጋር መጣላቱ ስህተት መሆኑን አምኖ ይቅርታ ጠይቋል።
የፌዴሬሽኑ አመራሮችም በወቅቱ በተጨዋቾቹ የተፈፀመውን የስነ ምግባር ግድፈት በተመለከተ የምስክርነት ቃላቸውን መስጠታቸውንም ነው መግለጫው ያመለከተው። ከዚህም በመነሳት በፌዴሬሽኑ መተዳደሪያ ደንብ መሰረት የገንዘብ ቅጣቱ የተወሰነባቸው ሲሆን ወደፊትም እንዲህ ዓይነት
ከባድ ጥፋት እንዳይፈፅሙ ከባድ ማስጠንቀቂያም እንዲደርሳቸው መወሰኑን ነው ፌዴሬሽኑ መግለጹን ራድዮው ዘግቧል።

አዲስ አበባ በቤት ኪራይ ንረት እየተናጠች ነው

$
0
0

ዜና ትንታኔ ከብርሃኑ ፈቃደ
(ለሪፖርተር ጋዜጣ እንደጻፈው)

የመኪና ራዲያተር ጥገና ባለሙያ ነው፡፡ በኪራይ ምክንያት በሚሠራበት ሰባተኛ አካባቢ የተደረገበት ጭማሪ አስደንጋጭ ሆኖበት ሲበሳጭ ከርሟል፡፡ አንድ ሺሕ ብር ይከፍልበት የነበረው ቤት፣ ‹‹ብዙ ግብር መጥቶብኛል፤ ስለዚህ ሁለት ሺሕ ብር ተጨማሪ ክፍያ መደረጉንና የኪራዩ ዋጋ ሦስት ሺሕ ብር መሆኑን እንድታውቀው፤›› የሚል ቀጭን መልዕክት ደርሶት ከአከራዩ ጋር ተጨቃጭቆ መክረሙን የሚናገረው ወጣቱ ሰው፣ አልታይ ዘለቀ (ስሙ ተቀይሯል) ነው፡፡

ለጭማሪው በአከራዩ የቀረበውን ምክንያት የማይቀበለው አልታይ፣ ‹‹እንዴትም ተብሎ ግብር ቢጨምር፣ ከመንገድ ዳር ርቆ የትኛውም ደንበኛ ቤቱን አይቶ ለመምጣት በማያስችለው አካበቢ ላይ ለሚገኝ ቤት፣ ሥራው በተባራሪ እየተሠራ፣ ሥራውን ለሚያመጡ ደላሎች ኮሚሽን እየከፈልኩ ለምሠራው ሥራ በአንድ ጊዜ ይሄን ያህል ጭማሪ ማድረግ ወዴት እየወሰደን እንደሆነ ግራ ገብቶኛል፤›› ሲል ይኮንናል፡፡ የአንድ ልጅ አባት የሆነው አልታይ፣ የራሱንና የባለቤቱን ቤተሰቦች ጨምሮ ሦስት ቤተሰብ የሚያስተዳድርበት ይህ ሙያው ከዚህ ሁሉ ቤተሰብ ቀለብና ወጪ ተርፎ በአንድ ጊዜ ጭማሪ በተደረገበት ልክ የሚበቃ ገቢ ካላገኘበት፣ ወደ ክፍለ አገር አለያም ወደ ዓረብ አገር ለመሰደድ ማሰቡን ተናግሯል፡፡
appartment in addis
የአልታይ ጓደኛ የሆነው ሌላው አስተያየት ሰጪ ከጓደኞቹ ጋር በመሆን ትምህርት ቤት ከፍቶ መሥራት ከጀመረ ሦስት ዓመታት መቆጠራቸውን ይገልጻል፡፡ ያለቻቸውን ገንዘብ አሟጥጠው፣ ከጥቃቅንና አነስተኛ ገንዘብ ተቋማት ተበድረው የሚያንቀሳቅሱትን ትምህርት ቤት የከፈቱት ሕንፃ ከግለሰብ ተከራይተው ነው፡፡ ለኪራይ በዓመት ከአምስት መቶ ሺሕ ብር በላይ ይከፍላሉ፡፡ ማስፋፊያ ለማድረግ ሌላ ተጨማሪ የግለሰብ ሕንፃ መከራየት ግድ ሆኖባቸው መገኘቱን ተናግረዋል፡፡ ከአንደኛ ክፍል እስከ 12ኛ ለማስተማር የሚያስችሉ ክፍሎችን ለማሟላት የግለሰብ ሕንፃ በውድ ዋጋ መከራየትና መሥራት አማራጭ የለውም ይላሉ፡፡ ሥራው እንዲህ ያለው አላስፈላጊ ጫና ባይኖርበት ኖሮ የበለጠ ጥሩ ሥራ ለመሥራት ያመቻቸው እንደነበርና ይበልጥ የሰው ኃይል ቀጥረው፣ በርካታ ተማሪዎችን ማፍራት የሚያስችላቸውን መንገድ የቤት ኪራይ ዋጋ እንዳራቀባቸው ተናግረዋል፡፡

መንግሥት ለትምህርት ዘርፍ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጥ ቢያስታውቅም፣ በደህናው ጊዜ ቦታ በርካሽ አግኝተው ሕንፃ የሠሩ ሰዎች በኪራይ ከሚያግበሰብሱት ገቢ የማያገኘውን ታክስ፣ እኒህ ተከራዮች ከሚሰጡት የትምህርት አገልግሎት ከፍተኛ ታክስ ይሰበስባል፡፡ ሆኖም ትህምርት ቤት መሥሪያ ቦታ ማግኘት የማይታሰብ እንደሆነባቸው የሚገልጹት አስተያየት ሰጪ፣ የሊዝ ግዥ ለማድረግ የሚቀርበው መነሻ ዋጋ በአስገራሚ ሁኔታ በካሬ ሜትር እስከ አሥር ሺሕና በዚያም በላይ በመድረሱ መቸገራቸውን ይገልጻሉ፡፡ መንግሥት ለትምህርት ዘርፉ እንደቆዳና ሌሎች ፋብሪካዎች የሰጠውን ማበረታቻ ሲሰጥ ማየትም አልቻንም ይላሉ፡፡ በሊዝ ጨረታ መነሻ ዋጋ መሬት እንደልብ ከተማው ላይ ለእነዚህ ዘርፎች ሲሰጥ ይታያል፡፡

ከቻይናና ከሌላውም አገር ለመጡ ‹‹የውጭ ባለሀብቶች›› የሚሰጠው ድጋፍ በትምህርቱ ዘርፍ አገልግሎት ሰጥተው፣ ብዙ ሠራተኛ ቀጥረው ለሚያሠሩትና ከፍተኛ ግብር በመክፈል አስተዋጽኦ ለሚያበረክቱት ሰዎች ምንም ዓይነት ድጋፍ ከመንግሥት እያገኙ እንዳልሆነ በመግለጽ መቸገራቸውን አስታውቀዋል፡፡ ሕንፃ አከራይ እንዲያገኝ የተመቻቸለትን ጥቅም፣ ለብዙ ሰው የሥራ ዕድል አስገኝተውና አገልግሎት ለሕዝቡ ሰጥተው የሚሠሩ ሰዎች እንደአስቷጽኦዋቸው የሚጠቀሙበትን ዕድል አለማግኘታቸውን ይገልጻሉ፡፡ መንግሥት ለአከራይ እንጂ ለሠርቶ አሠሪና በኢኮኖሚው ውስጥ እሴት ጨማሪ ለሆኑ አካላት በመሬት አቅርቦት የሚያድርገው ድጋፍ ከወለል በታች መሆኑን በመግለጽ ይተቻሉ፡፡

‹‹የመንግሥት የመደብ ጨቋኝነት ሚና››

በአዲስ አበባ ሕንፃ የገነቡ አብዛኞቹ ከመንግሥት የ70 ከመቶ ብድር አግኝተው፣ መሬት ተመርተው ወይም በርካሽ ተጫርተው በሊዝም ሆነ በይዞታ ከገዙ በኋላ ያለምንም ድካምና ውጣውረድ በመንግሥት ገንዘብ በገነቡት ሕንፃ ያለሐሳብ ሀብታሞች እንዲሆኑ በመንግሥት ዕድሉ የተሰጣቸው ናቸው፡፡ መኪና ገጣጥመው፣ ትምህርት ቤት መሥርተው፣ በፋብሪካ አምርተው ለመሥራት የሚጣጣሩ ሰዎች የማያገኙትን የገቢ ዝቆሽ፣ ሕንፃ አከራዮች በመንግሥት ተባባሪነት የሚያገኙትን ጥቅምና የዳጎሰ ገቢ በመመልከት፣ አንድ ሕንፃ በባንክ ብድር በመሥራትና ሕንፃውን ለብድር ማስያዣነት በመዋል ገርበብ ባለው የብልጽግና በር በኩል ሾልከው የተመነደጉ ጥቂት አይደሉም፡፡

በአገሪቱም ሆነ በአዲስ አበባ መዲናም መንግሥት የሚፈልገውን ያህል የማኑፋክቸሪንግ ወይም የኢንዱስትሪ መስኮች አለመስፋፋት ችግሮች መንስዔ ከሆኑ ምክንያቶች መካከል እነዚህ አቋራጭና በቀላሉ የዕድሜ ልክ ባለሀብት መሆን የሚቻልባቸው መንገዶች ተጠቃሾች ናቸው፡፡ አንድ ባለፋብሪካ ወይም ባለትምህርት ቤቱ ባለጉዳይ እንደሚጠቅሱት ሥራቸው በበርካታ ሰዎች ትከሻ ላይ የወደቀ ነው፡፡ ብዙ ሠራተኛ ተቀጥሮና እሴት ተጨምሮ የሚሠራው ሥራ ትርፍ ማስገኘት የሚጀምረው ከፕሮጀክቱ ትግበራ አራት ወይም አምስት ዓመታት በኋላ ሊሆን ይችላል፡፡ በአንፃሩ ሕንፃ ሠርተውና ሸንሽነው የሚያከራዩ ግን ቦታ አጥቶ የተቸገረ ነጋዴ ወይም ሌላው አካል በካሬ ከ500 እስከ 5,000 ብርና ከዚያም በላይ እየከፈለ ለመሥራት የሚገደድ ጭሰኛ ሆኗል ይላሉ፡፡ አከራዮች ከኪራይ በሚሰበስቡት ገንዘብ የባንክ ዕዳ ከፍለው ሀብታቸው የማይነጥፍ ቱባ ሀብታሞች ይሆናሉ፡፡

ስለዚህ ፋብሪካ ከመገንባትና ለኢኮኖሚው እሴት የሚጨምሩ ዘርፎች ላይ ከመሠማራት ይልቅ በአቋራጭና በአጭር መንገድ ሀብታም የሚያደርጉ አማራጮች በመንግሥት በኩል ስለተመቻቹ፣ ለምን ብለው ይደክማሉ፤ ለነገሩ የደከሙትስ ምን አተረፉና የሚል መከራከሪያ በከተማው በሰፊው የሚደመጥ ሙግት ሆኗል፡፡

መምህር በቀለ የተባሉ በጡረታ ላይ የሚገኙ መምህር በአንድ ወቅት በኅብረተሰብ ሳይንስ ትምህርት ወቅት ስለመንግሥት ሥርዓትና አወቃቀር ሲያስትምሩ ‹‹መንግሥት የመደብ መጨቆኛ መሳሪያ ነው፤›› በማለት ይገልጹ ነበር፡፡ ይህም ሲባል የበላይ መደብ ያላቸው፣ በካፒታልና በገንዘብ አቅማቸው የተነሳ የመንግሥትን አገልግሎት በቀላሉ ለማግኘት የሚቻላቸው መሆናቸውን ለማመልከት የሚጠቀሙበት አገላለጽም ነው፡፡

ቤት መግዛት ባትችል ትከራያለህ፣ መከራየት ባትችል ግን?

በአሜሪካ የኪራይ ቤቶችን በማስመልከት ከጥቂት ሳምንታት በፊት አንድ ጥናት ይፋ ተደርጎ ነበር፡፡ በኪራይ ቤቶች ዙሪያ በሀርቫርድ ዩኒቨርሲቲና በአጋሮቹ የተደረገው የጋራ ጥናት እንደሚያመለክተው፣ የቤት ኪራይ ዋጋ እ.ኤ.አ. ከ1980ዎቹ ጀምሮ እየጨመረ ይገኛል፡፡ በአንፃሩ የዜጎች ገቢ በየጊዜው እየቀነሰና እያነሰ መምጣቱን ተመልክቷል፡፡ የሀርቫርድ የኪራይ ቤቶች ጥናት እንደሚያረጋግጠው፣ ከሆነ ከ11.3 ሚሊዮን ያላነሱ አሜሪካውያን የራሳቸው ቤት ሊኖራቸው የሚችልበት አቅም የላቸውም፡፡ የኪራይ ቤት ጥገኛ ናቸው፡፡ በዚህ ሳቢያ ከግማሽ በላይ ገቢያቸውን ለኪራይ በመክፈል ለአስከፊ ወጪ የተዳረጉና ልፋታቸውን ለኪራይ የሚገብሩ መሆናቸውን ጥናቱ አረጋግጧል፡፡ ከእነዚህ ትንሽ ዝቅ ያለ ገቢ ያላቸው ግለሰቦች ዝቅተኛ የሚባለው የኪራይ ወጪያቸው፣ የገቢያቸውን 30 ከመቶ ለኪራይ የሚከፍሉ ናቸው፡፡

ከሁለት አሜሪካውያን አንዱ በቤት ኪራይ ወጪ ናላው የሚናውዝ መሆኑን የሚጠቁመው ጥናት፣ በአሁኑ ወቅት ለከፍተኛ የኪራይ ጫና ከተዳረጉት 12 ሚሊዮን አሜሪካውያን ባሻገር 21.1 ሚሊዮን አሜሪካውያን ለቤት ኪራይ ወጪ መሸፈኛነት ገቢያቸውን በማሟጠጥ ላይ የሚገኙ ናቸው፡፡

ጥናቱ ሰፊና አስገራሚ ዕውነታዎችን ማስነበቡን ይቀጥላል፡፡ አሜሪካውያን በፌደራል መንግሥታቸው ደረጃ በሰዓት በአማካይ የሚያገኙት ገቢ 7.5 ዶላር (በወቅቱ ምንዛሪ ቢመታ 150 ብር መሆኑ) ነው፡፡ ሆኖም ባለሁለት መኝታ ክፍል ደህና መኖሪያ ቤት መከራየት የሚፈልግ አሜሪካዊ፣ በየትኛውም የአሜሪካ ግዛቶች ይህን መሰል ቤት መከራየት የሚችለው በሰዓት ቢያንስ 20 ዶላር (በሰዓት 400 ብር ያህል) ገቢ ማግኘት የቻለ እንደሆነ ነው ሲል ጥናቱ ማረጋገጫውን አስፍሯል፡፡ ከሁለት መኝታ ቤት ያነሰ ግን ደግሞ ደህና ሊባል የሚችል ቤት መከራየት የሚፈልግ ሰው የሰዓት ገቢው 12 ዶላር መሆን ይጠበቅበታል፡፡ ስለዚህ በየትኛውም የአሜሪካ ግዛት በሰዓት 7.5 ዶላር ዝቅተኛውን ገቢ የሚያገኝ አንድ ዜጋ ደህና የሚባለውን ቤት ተከራይቶ መኖር አይችልም፡፡

ኪራይ የሚያንረው ባለንብረቱ ነው

የኢትዮጵያ በተለይ የአዲስ አበባ ሁኔታ ይህንን ይመስላል፡፡ ኮንዶሚኒየም ተከራይቶ ለመኖር የሚችለው ሰው ወርኃዊ ገቢው ቢያንስ ከአምስት ሺሕ ብርና ከዚያም በላይ መሆን እንዳለበት ጥናት ማድረግ ሳያስፈልገው የሚታወቅ ነው፡፡ በከተማው ትልቁን የገቢ ምንጭ የሚበዘብዘው የኪራይ ዋጋ እንደሆነ ተራ አባወራ ብቻም ሳይሆን ሕንፃ ተከራይተው ቅርንጫፎቻቸውን የሚስፋፉ ባንኮች ሳይቀር የሚገነዘቡት ነው፡፡ የባንክ አገልግሎት እምብዛም በማይፈለግባቸው የአዲስ አበባ ጠረፍ አካካቢ የተከፈቱ የባንክ ቅርንጫፎች ሲናገሩት የሚደመጥ ነው፡፡

በአንፃሩ በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ቢሮ ለመከራየት ሁለት ጉዳዮች ቦታ እንዳላቸው የሚገልጹት የኢኮኖሚ ባለሙያው ዶክተር ደምስ ጫንያለው ናቸው፡፡ አንደኛው ቤቱ የሚገኝበት ቦታ ለኪራይ ዋጋው ከፍተኛ መሆን አስተዋጽኦ ያደርጋል፡፡ ‹‹ዓይን ቦታ›› ተብሎ በልማድ የሚጠቀሰው አገላለጽ በተለይ በንግድ ሥራ ለተሰማሩ ሰዎች የተለመደ ሲሆን፣ ገበያ እስካለውና ወጪያቸውን ሸፍኖ ትርፍ እስካስገኘ ድረስ፣ ለትራንስፖርትና ለመሳሰሉት አገልግሎቶች ያለው ምቹነት እየታየ ዋጋው እንደሚለያይ ከምሁሩ ገለጻ ለመረዳት ተችሏል፡፡

ሌላኛው ዋጋውን ውድና ተገቢ ሊያደርገው የሚችለው ምክንያት የቤቱ ወይም የንብረቱ ባለቤትነት ነው፡፡ በግለሰቦች ይዞታና በተቋማት መካከል ባለው ልዩነት መካከል የዋጋው ከፍተኛነትና ዝቅተኛነት ሊንፀባረቅ እንደሚችልም ዶክተር ደምስ ይገልጻሉ፡፡

በኢኮኖሚ ሙያቸው የማማከርና የጥናት ሥራዎችን የሚያካሂዱት ዶክተር ደምስ፣ የኪራይ ዋጋ ከውል ውጭ ያለአግባብ ተጨምሮባቸው የተከራዩትን የግለሰብ ቤት ለመልቀቅ መገደዳቸውን ገልጸዋል፡፡ ‹‹ከግለሰብ ተከራይተን ነበር የምንሠራው፡፡ ስድስት ወር እንኳ ሳንቆይ በአንድ ጊዜ 35 ከመቶ ያህል ጨምረውብናል፤›› ያሉት ዶክተር ደምስ፣ አብዛኞቹ ግለሰቦች ሀብቱ ስላላቸው ዋጋ እንዳሻቸው ይጨምራሉ እንጂ ገበያው ላይ ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ አይተውና ጥናት አድረገው የሚጨምሩ እንዳይማስላቸውም ገልጸዋል፡፡ በመሆኑም ለአንድ ዓመት በውል ተዋውለውና ቅድሚያ መክፈል የሚጠበቅባቸውን ከፍለው ሥራ ቢጀምሩም፣ ከውል ውጭ በተደረገው ጭማሪ ቅር ተሰኝተው ሌላ አካባቢ ፈልገው ለመግባት ተገድደዋል፡፡

የአዲስ አበባ የቤት ኪራይ ለአብዛኛው ሰው የሚቀመስ አለመሆኑን ምሁሩ ብቻም ሳይሆን ነዋሪዎችና ነጋዴዎች የሚስማሙበት ሀቅ ነው፡፡ ለዚህም ይመስላል አንዳንድ ሰዎች ‹‹ከፒያሳና ከቦሌ ዕቃ መግዛት ለነጋዴው የቤት ኪራይ እንደመክፈል ይቆጠራል፤›› ሲሉ የሚደመጡት፡፡ በእነዚህ አካባቢዎች የሚሸጡት ዕቃዎች መርካቶና ሌላው አካባቢ ከሚሸጡት የተለዩ ሆነው ሳይሆን በዋጋቸው የማይቀመሱ ሆነው ስለሚገኙ የሚነገር አገላለጽ ነው፡፡ በከተማው ለሱቅ ኪራይ በካሬ የሚከፈለው ክፍያ በአስገራሚ ፍጥነት እየጨመረ መጥቷል፡፡ በቦሌ አካባቢ ከሚገኙ ሕንፃዎች መከራየት የሚፈልግ ነጋዴ፣ በአማካይ በካሬ ከሁለት ሺሕ እስከ ሦስት ሺሕ ብር ይጠየቃል፡፡ አምስት መቶ ብርና ከዚያ ያነሰ ዋጋ በካሬ የሚከፈልባቸው ሕንፃዎች ቢኖሩም፣ አዳዲስ የተሠሩት ግን በዚህ ዋጋ የሚደፈሩ አይደሉም፡፡ አካባቢ የቤት ኪራይ ዋጋን በዚህ መልኩ ሊወስን ቢችልም፣ የግል አከራዮች የሚያደርጉት ጭማሪ ባለንብረትነታቸው ላይ ያጋድላል፡፡

በአንፃሩ አከራዮች የየራሳቸውን አካሄድ እንደሚከተሉና በርካታ ወጪዎችን በማውጣት፣ ጥሪታቸውን አሟጠው ለገነቡት ሕንፃ ተመጣጣኝና ተከራዮችንም የማይጎዳ የኪራይ ዋጋ እንደሚጠይቁ ይሟገታሉ፡፡ በተለይ ከመገናኛ እስከ ሃያ ሁለት ባለው መስመር ሕንፃዎቻቸውን የሚያከራዩ ባለንብረቶች፣ በመንገድና በባቡር መስመር ግንባታ ምክንያት ሥራ በመጥፋቱ ምክንያት ኪራይ በግማሽ የቀነሱ መሆናቸውን ይገልጻሉ፡፡ የገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣንም በመንገድ ሥራው ምክንያት ሥራ ቀንሶባቸዋል ባላቸው ድርጅቶችና አነስተኛ ነጋዴዎች ላይ የሚጥለው ታክስ ላይ አስተያየት ሲያደርግ ተስተውሏል፡፡

በአዲስ አበባ ኬሻ በጠረባ ከሚተኛባቸው የጎጃም በረንዳ፣ የአሜሪካ ግቢ፣ የሰባተኛ ሰፈሮች አንስቶ እስከ ቦሌ፣ ገርጂ፣ ቤቴል የመሳሰሉት አካባቢዎች ቤት የሚከራይባቸው ናቸው፡፡ ኬሻ በጠረባዎቹ ቤት ለአዳር ያከራያሉ፡፡ ኬሻ በጠረባ እየተባሉ የሚታወቁት ቤቶች፣ ድሮ ድሮ ኬሻ፣ አሁን አሁን ካርቶን ተነጥፎ ለአንድ አዳር ሰው እንደጣውላ ተደርድሮ የሚታደርባቸው ቤቶች ናቸው፡፡ እነዚህ ቤቶች ድሮ ከነበራቸው ማደሪያ የለሽ ደንበኛ ባሻገር፣ ከየክፍለ አገሩ ይጎርፉ የነበሩ የዓረብ አገር መንገደኞች የሚያገኙት ገቢ አስተማማኝ ሆኖላቸው ቆይቷል፡፡ ዓረብ አገር የሚሄዱ ሴቶች እንደከተማው ማደሪያ ቢስ ሰካራም ሳይሆን እጥፍ ከፍለው ያድሩ እንደነበር ሪፖርተር ያነጋገራት የጎጃም በረንዳ ኬሻ በጠረባ አከራይ ሺመታ አሕመድ ታስታውሳለች፡፡ አሁን ግን በጎጃም በረንዳ ኬሻ በጠረባ እያበቃለት መምጣቱን የሚጠቁም አካሄድ በባቡሩ መስመር ግንባታ እየታየ ነው ትላለች፡፡ ከፊት ለፊት የነበሩት ሱቆች አብዛኞቹ በመፍረሳቸው፣ አልጋ ያከራዩ ከነበሩት ቤቶች አንዳንዶቹ ለሱቆች ዕቃ ማከማቻነት እየዋሉ መምጣታቸውን ትገልጻለች፡፡ አብዛኞቹ ግን ለአዳር ከሚያከራዩዋቸው ቤቶች ውስጥ አብረው የሚኖሩ በመሆናቸው፣ ቤቶቹ ሲፈርሱባቸው ዕድል ከቀናቸው ኮንዶሚኒየም ቤት የሚቀየርላቸው በመሆኑ የገቢ ምንጫቸው ላይ አደጋ እንደተጋረጠበት ሥጋት የገባቸው ናቸው፡፡

ከእነዚህ ባሻገር ያሉት የገርጂና የቦሌ ቤቶች ቅንጡ ናቸው፡፡ የሚከራዩት በድረ ገጽ በሚለቀቁ ማስታወቂያዎች ሲሆን፣ ከ800 (16,000 ብር) እስከ 4,000 ዶላር (80,000 ብር) ድረስ የኪራይ ዋጋ የሚጠየቅባቸው ቤቶችም በአዲስ አበባ ጥቂት አይደሉም፡፡ አብዛኞቹ ቦሌ፣ ኦሎምፒያ፣ ገርጂ (በይበልጥ ሰንሻይን አፓርታማዎች)፣ ካዛንቺስ አካባቢ የሚገኙ ቤቶች ባለአንድ፣ ባለሁለትና ባለሦስት መኝታ መሆናቸው እየተገለጸና ዘመናዊ የቤት ውስጥ ቁሳቁስ እንደተሟላላቸው የሚገልጹ ማስታወቂዎች የሚያጅቧቸው ናቸው፡፡

ኪራይ የሚቆልሉት ደላሎች ናቸው

ከፍና ዝቅ ያለውን የአዲስ አበባ የኑሮ ቅኝት እንዲህ የሚመሰክሩት የአዲስ አበባ የኪራይ ቤቶች፣ በመካከሉ ላለው ነዋሪ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ጫና የሚፈጥሩ ሆነው ይገኛሉ፡፡ በአዲስ አበባ ሌላው ጥልቅ ችግር ለመሆኑ በመንግሥትም በሕዝቡም ስምምነት የሚደረግበት ትልቅ ችግር የደላሎች ሚና ነው፡፡ የአዲስ አበባ አስተዳደር በተለያዩ አጋጣሚዎች የደላሎችን ተግባር በማስመልከት ከፍተኛ ቅሬታ ሲያሰማ ማድመጥ የተለመደ ነው፡፡ ከጥቂት ወራት በፊት ስለብርቱካን ዋጋ መወደድ ለማሳሰብ በተጠራው የንግድ ሚኒስቴር ስብሰባ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ ንግድ ቢሮ ደላሎች ከሚችለው በላይ ሆነውበት መቸገሩን አስታውቋል፡፡

ጥቂት ቢቆይም የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን፣ ‹‹ጉዳይ እናስፈጽማለን›› በሚሉ ደላሎች መቸገሩን አስታውቆ ነበር፡፡ ዋናው መሥሪያ ቤት ድረስ ሰተት ብሎ የረዘመው የደላሎች እጅ፣ በተለይ ከሦስት ዓመት በፊት ጡዘት ላይ ደርሶ የነበረውን የአነስተኛ ግብር ከፋዮች ጉዳይ መነሻ በማድረግ በባለሥልጣኑ ጉዳያቸውን ሊያይ የሚችል አካል እንደሚያውቁና እንደሚያስጨርሱላቸውና ውክልና ሳይቀር እንዳላቸው በመግለጽ የመንግሥት ባለሥልጣናትን ሳይቀር ማስቸገራቸው ሲነገር ቆይቷል፡፡

ይህ መሆኑ ደግሞ በየትኛውም የአዲስ አበባ ከተማ ጉዳይ ላይ ደላሎች አይነኬና የማይፈነቀል ሚና ይዘው ለመቆየታቸው ምክንያት ሆኗል፡፡ ከቤት ሠራተኛ ቅጥር ጀምሮ በቤት ሽያጭና ግዥ፣ አሁን በግልጽ አይሁን እንጂ በድብቅ የመሬት ሽያጭና ግዥ በማካሄድ፣ ከውጭ ዕቃ በማስመጣትና ደንበኛ በማፈላለግ ላይና በየትኛውም የኢኮኖሚ አውታር ላይ የደላሎች ሚና ከደም ሥር በላይ ሆኖ ይታያል፡፡

በቤት ኪራይ ላይ የሚታየው የደላሎች ጣልቃ ገብነት ደግሞ አብዛኛውን የከተማ ነዋሪ ከማንገሽገሽ አልፎ አንዳንዶችን ለጠብ ሲጋብዝ ማየት እየተለመደ ነው፡፡ በኮንዶሚኒየም ቤቶች ለሚከናወኑ የኪራይ ድርድሮች ደላሎች ማዕከላዊውን ቦታ ይይዛሉ፡፡ ያለደላሎች ጣልቃ ገብነት የትኛውም ቤት አይከራይም፣ አይሸጥም ሲባል መስማት የተለመደ ነው፡፡ በመካኒሳ ባቱ አራት ባለሁለት መኝታ ቤት ለመከራየት ፈልጋ ዘበኞችን የጠየቀችው እመቤት ጌታቸው የተባለች ወጣት፣ አከራዩን በስልክም በአካልም ማግኘት እንደማትችል ይልቁንም የቤቱን ቁልፍ ከያዘው ደላላ ጋር ተነጋግራ ከተስማማች መከራየት እንደምትችል እንደተነገራት ለሪፖርተር ገልጻለች፡፡

በገዥና ሻጭ መካከል በቀጥታ የሚደረጉ ስምምነቶችን በዚህ ምክንያት ማድረግ አደጋች ሆኖ ይታያል፡፡ አንዳንድ የኮንዶሚኒየም ኮሚቴዎች ግን ይህንን አጥር በመስበር፣ በአከራይና ተከራይ መካከል ቀጥተኛ ግንኙነት እንዲኖር ለማድረግ ሲጣጣሩ ይታያሉ፡፡ ደላሎች ለአከራዩ የቅድሚያ ክፍያ ለአንድ ዓመት፣ ለስድስት ወር አለያም ለሦስት ወር የሚደረጉ የኪራይ ክፍያዎች ላይ ከሦስት እስከ አምስት በመቶ የአገልግሎት በማስከፈል እንደሚያከራዩ ሲገለጽ፣ ደላሎች በባለቤት ስም ሆነው ለሚያከራዩት ቤት እስከ አሥር በመቶ እንደሚያስከፍሉም ይታወቃል፡፡

የቤት ኪራይ ዋጋን በሚመለከት በአሜሪካ እንደሚሠራው ዓይነት ጥናት በኢትዮጵያ ይፋ ሲደረጉ ባይታም፣ ለአገሪቱ የዋጋ ንረትና ግሽበት አስተዋጽኦ እንዳለው የማዕከላዊ ስታቲስቲክስ በየወሩ ይፋ የሚያደርገው የሸማቾች ዋጋ መመዘኛ አሃዝ ያመለክታል፡፡ የስታቲስቲክስ ኤጀንሲ የሸማቾች ዋጋ መመዘኛ ኢንዴክስ (ሸማቾች ለተወሰኑ ዕቃዎችና አገልግሎቶች የከፈሉትን አማካይ የዋጋ ለውጥ ለመለካት የሚያገልገግል ጠቋሚ አሃዝ ነው ሲል ኤጀንሲው ይገልጸዋል) ሲተነትን፣ ምግብ ነክ የሆኑና ምግብ ነክ ያልሆኑ የሸማቾች ዋጋ መመዘኛ ኢንዴክስ ብሎ ባስቀመጣቸው መለኪያዎች መሠረት፣ ምግብ ነክ ካልሆኑት መመዘኛ አሃዞች መካከል፣ የሸማቾች የችርቻሮ መመዘኛ ዋጋን በዘንድሮውና በዓምናው መካከል ያለውን ልዩነት በማነፃፀር ያቀርባል፡፡ በዚህ መሠረት ከቤት መሥሪያ ዕቃዎች፣ ከውኃና ኢነርጂ ወጪዎች ጋር የተደለደለው የቤት ኪራይ አንድ ላይ 7.8 ከመቶ ጭማሪ በማሳየት፣ ባለፈው ዓመት ኅዳር ወር ላይ ከነበረው አገር አቀፍ ጠቅላላ የችርቻሮ ኢንዴክስ ጋር ሲነፃፀር የ7.9 ከመቶ ጭምሪ እንዲሳይ ምክንያት ለመሆን መቻሉን የስታቲስቲክስ ኤጀንሲ ይፋ አድርጓል፡፡ እስካሁን ባለው አካሄድም የቤት ኪራይ ወጪ ሲጨምር እንጂ ሲቀንስ አልታየም፡፡ ሆኖም ይህ ጠቋሚ አሃዝ የቤት ኪራይ ዋጋን በተናጠል ካለማመልከቱም በላይ፣ ምን ያህል የቤት ተከራዮች እንዳሉ (የመኖሪያና የሥራ ቦታ) አያሳይም፡፡ ምን ያህል ተጨማሪ ተከራይ ሊኖር እንደሚችል፣ የኪራይ ዋጋ በቀጣዩ ወር ወይም ዓመት ምን ያህል ሊሆን እንደሚችል ወዘተ. ያለውን ትንታኔም የሸማቾች ዋጋ መመዘኛው አይጠቁምም፡፡

Sport: “ኢትዮጵያን አሸንፈን ለዓለም ዋንጫ በማለፋችን የቼልሲ ተጨዋቾች ደስታቸውን ገልፀውልኛል›› –ኬኔት ኦሜሮ (Kenneth Omeruo)

$
0
0

ናይጄሪያ የዓለም ዋንጫ ህልሟን እውን ለማድረግ ኢትዮጵያን ማሸነፍ ነበረባት፡፡ አዲስ አበባ ላይ 2-1 ድል ካደረገች በኋላ በካላባር ከተማም በሌላ ድል ቲኬቷን ቆረጠች፡፡ ኬኔት ኦሜሮ ከፈንጠዚያው በኋላ ወደ ቼልሲ ሲመለስ ዴቪድ ሉዊዝ ጨብጦት ‹‹ወደ ብራዚል እንኳን ደህና መጣችሁ›› ብሎታል፡፡ ሉዊስ በሀገሩ የሚስተናገደውን ውድድር አስመልክቶ ያበረታታው ወጣት በቼልሲ ተሰላፊነትን አያግኝ እንጂ የስታምፎርድ ብሪጁ ክለብ ንብረት ነው፡፡ በሰማያዊዎቹ ክለብ ውስጥ የሚገኙት የሉዊዝ ሀገር ልጆች ኦስካር፣ ራሚሬዝና ዊልያንም የ20 ዓመቱን የመሀል ተከላካይ ‹‹እንኳን ደስ ያለህ›› ብለውታል፡፡ ከዚያም ሌሎቹም ተጨዋቾች እየተፈራረቁ ቀጥለዋል፡፡

omerou2

ኦሜሮ በቼልሲ ገና የመጀመሪያ ጨዋታውን እንኳን አላደረገም፡፡ ሆኖም በተጨዋቾች ዘንድ ይወደዳል፡፡ 59 ቁጥር ማሊያ ያደርጋል፡፡ በጆዜ ሞውሪንሆም የዋናውን ቡድን ማሊያ እንዲሰጠው ተደርጓል፡፡ ተስፋም ጥለውበታል፡፡ ስለዚህ ከሙሉ ቡድኑ ጋር አብሮ ልምምድ ይሰራል፡፡
በ2014ቱ የዓለም ዋንጫ ላይ ከወጣት ከዋክብት መካከል ኦሜሮ እንደሚካተትበት ከወዲሁ ግምት ተሰጥቶታል፡፡ ይህ ዓመትም በጥሩ ሁኔታ አልፎለታል፡፡ ናይጄሪያ ከኬፕቬርዴ ጋር ባደረገችው ጨዋታ ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ለሀገሩ ብሔራዊ ቡድን ተሰልፏል፡፡ በብራዚል የኮንፌዴረሽን ዋንጫ ላይ ተሳትፏል፡፡ ለ15ኛ ጊዜ ለንስሮቹ ባደረገው የካላባር ጨዋታም ሃገሩን ለዓለም ዋንጫ ለማሳለፍ በቅቷል፡፡
‹‹በዓለም ዋንጫ ላይ ለመጫወት ስመኝ ኖሬያለሁ›› ኦሜሮ ይናገራል፡፡ ‹‹በኮንፌዴሬሽንስ ካፕ ላይ መሳተፋችን ዓለም ዋንጫ ላይ የመቅረብ ፍላጎታችንን ጨምሮልናል፡፡ አሁንም የምድብ ድልድሉን በጉጉት እጠባበቃለሁ፡፡
‹‹በቼልሲ ብቻ ትኩረታችንን በክለባችን ላይ አድርገን እንሰራለን፡፡ አንዳንድ ጊዜ ጆዜ ያስቀናል፡፡ ባለፈው ሳምንት አንድ የልምምድ ፕሮራም ላይ አንድ ኳስ ላቀብል ብዬ ተበላሸብኝ፡፡ ጆዜም እንዲህ አለኝ፡፡ ‹‹በዓለም ዋንጫ ላይ እንዲህ ካደረግክ ናይጄሪያ ከውድድሩ ትወጣለች›› ሁላችንም ሳቅን፡፡ አሁን ስለ ዓለም ዋንጫ በተጨዋቾች መካከል ምንም ነገር የለም፡፡ ያለው ዝምታ ብቻ ነው፡፡ ከዕጣው ድልድል በኋላ ግን ጫጫታ ይኖራል፡፡
‹‹ስለዓለም ዋንጫው ከሉዊዝ ጋር አውርተናል፡፡ ጥሩ እንግሊዝኛ ያወራል፡፡ በእውነቱ መልካም ሰው ነው፡፡ ከኢትዮጵያ ጋር ልንጫወት ስንሄድ ሉዊዝ ‹‹እውን አሁን ለዓም ዋንጫ ልታልፉ ነው›› እያለ ሲያሾፍብን ነበር፡፡ አሸንፈን ስንመለስ ግን ሁሉ ደስታቸውን ገልፀውልናል፡፡ ሉዊዝም ‹‹ጥሩ ሰርታችኋል፣ እንኳን ወደ ብራዚል ደህና መጣችሁ›› ብሎ ተቀብሎናል፡፡
‹‹ለዓለም ዋንጫ ማለፍ ትልቅ ነገር ነው፡፡ ሁሉም በጣም ደስተኛ ሆኗል፡፡ ልክ የአፍሪካ ዋንጫን እንዳነሳንበት ጊዜ አይነት ነው፡፡ ህዝብ ወደ ጎዳናዎች ወጥቷል፡፡ ደጋፊዎቻችንን ቅር አላሰኘንም፡፡ ለእነርሱ ሲባል ማለፍ ነበረብን፡፡ (በኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ላይ ከስፔን ጋር ስንጫወት የትከሻ) ጉዳት በደረሰብኝ ጊዜ ከደጋፊዎች መልዕክቶችና ትዊቶች ይደርሱኝ ነበረ፡፡ እኔን ለማየት ምን ያህል እንደናፈቁ ይገልፁልኛል፡፡ አሰልጣኝ ስቴፋን ኬሺም በምን አይነት ጤንነት ላይ እንዳለሁ እየደወለ ይጠይቀኝ ነበር፡፡ አሁንም የቡድኑ አባል መሆኔን ይነግረኛል፡፡ ስለዚህ በድጋሚ ለመጫወት ጓጉቼ ነበር››
ለንስሮቹ የዘንድሮ አምስተኛው የዓለም ዋንጫ ነው፡፡ 160 ሚሊዮን ህዝብ ያላት ሀገር ቡድኗን በታላቅ ስሜት ትደግፋለች፡፡ ‹‹ልጅ ሳለሁ ናይጄሪያ ስታሸንፍ ባደግኩባት ዋና ከተማ አቡጃ ህዝቡ አደባባይ ወጥቶ ደስታውን ሲገልፅ እኔም ተቀላቅያቸው ነበር፡፡ አባቴ የቧንቧ ሰራተኛ ነው፡፡ እናቴ ደግሞ ትንሽ ሬስቶራንት አላት፡፡ የናይጄሪያ ጨዋታዎች ሁልጊዜ እንከታተል ነበር፡፡
‹‹ገና ልጅ ሳለሁ አንድ ቀን የናይጄሪያን ብሔራዊ ቡድን ማሊያ መልበሴ እንደማይቀር እናቴ ትነግረኝ ነበር፡፡ እንዳለችውም ሆነ፡፡ በ2009 የዓለም ከ17 ዓመት በታች የዓለም ዋንጫ በአቡጃ ተዘጋጅቶ ነበረ፡፡ ያም እናቴን በጣም አስደስቷታል፡፡ ምንም ያመለጣት ነገር የለም፡፡ ሬስቶራንቷን ሳይቀር ዘግታ ወደ ስታዲየም መጥታለች፡፡ ሁልጊዜም መልካም ዕድል እንዲገጥመኝ ትመኛለች››
በ1994 ናይጄሪያ በዓለም ዋንጫ የመጨረሻ 16 ቡድኖች አንዷ ስትሆንና በፈረንሳይ የዓለም ዋንጫ (ኢትዮጵያን… ወደ ገጽ 23 የዞረ)

 

ስትሳተፍ ኦማር ጨቅላ ህፃን ስለነበር አያስታውስም፡፡ ‹‹ሰዎች ሁልጊዜ ስለ 1994ቱ ቡድን ያወራሉ፡፡ ማይክል አሜናሎ (የአሁኑ የቼልሲ የቴክኒክ ዳይሬክተር) የቡድኑ አባል ነበር፡፡ የአሁኑ የንስሮቹ አሰልጣኝ ኬሺ ደግሞ የቡድኑ አምበል ነበር፡፡ ‹‹ሲመክረን በአሁኑ ቡድን ውስጥ ከ1994ቱ ቡድኑ ጋር የሚመሳሰል መንፈስ እንደሚመለከት ይነግረናል፡፡ ይህ ደግሞ ለእኛ ብዙ ትርጉም አለው›› አሚሮ ለ1994ቱ የአፍሪካ ሻምፒዮን ያለውን ክብር ይገልፃል፡፡
‹‹በብሔራዊ ቡድኑ ውስጥ አንድነት የሌለባቸው ጊዜያት ነበሩ፡፡ በ2010 በውጤቱ ሃገሪቷ አዝና ነበር፡፡ ፕሬዝዳንቱ ጉድላክ ጆናታን ቡድኑ በደቡብ አፍሪካ ባሳየው ብቃት በጣም ከመቆጣታቸው የተነሳ ለተወሰነ ጊዜ አግደውት ነበር፡፡ አሁን ግን በቡድኑ ዙሪያ ያለው ነገር ሁሉ በጣም ጥሩ ነው፡፡ በህብረት እንሰራለን፡፡ ብትመለከተን ሁሉም እርስ በርሱ ቀልድ ሲለዋወጥ ታያለህ፡፡ በቡድናችን ውስጥ አዙቢኬ ኤግዌክዌ የተባለ ቀልድ ወዳጅ ተጨዋች አለ፡፡ በናይጄሪያ ለዋሪ ዋልቭስ ክለብ የሚጫወተው የመሀል ተከላካይ ነው፡፡ ካልጮኸ አያወራም፣ በጣም ቀልደኛ ነው፡፡ አሰልጣኛችንን እንኳን ሳይቀር ያስቃቸዋል፡፡ የአፍሪካ ዋንጫን አሸንፈናል፡፡ በኖቬምበር የዓለም ከ17 ዓመት በታች ዋንቻ አንስተናል፡፡ እንደገናም ለብራዚሉ የዓለም ዋንጫ አልፈናል፡፡ በዓለም ዋንጫ ላይ ደግሞ ተደናቂ ነገር ማሳየት አለብን›› ይላል፡፡
ኦሜሮ እዚህ ደረጃ ላይ የደረሰው በቀላሉ አይደለም፡፡ ከአቡጃ ጎዳናዎች ተነስቶ ብዙ ለፍቷል፡፡ ‹‹የአቡጃ ልጅ ነኝ፡፡ ያደግኩት እግርኳስን በሚያፈቅር ቤተሰብ ውስጥ ነው፡፡ አባቴ ግብ ጠባቂ ነበር፡፡ በከፍተኛ ደረጃ አልተጫወተም እንጂ ታላቅ ወንድሜም እንዲሁ ይጫወታል፡፡ ታናሼ ለሙከራ ስታንዳርድ ሉዬዥ ይሄዳል፡፡ የአንድ ክለብ አሰልጣኝ ወደ ቤታችን መጥቶ ከወላጆቼ ጋር ተነጋገረ፡፡ ልጃችሁ ከእኔ ጋር ይጫወታል አላቸው፡፡ ዕድሜዬ 10 ዓመት እስኪሞላኝ ድረስ በባዶ እግሬ ተጫውቻለሁ፡፡ በ2009 ለሁለት ወራት ሙከራ ወደ አንደርሌክት ሄጄ ተመለስኩ፡፡ ከዚያም ስታንዳርድ ሊዬዥ ላከልኝ፡፡ ለሊዬዥ ተጠባባቂ ቡድን ውስጥ መጫወት ጀመርኩ፡፡ ከዚያም ከ20 ዓመት በታች የዓለም ዋንጫ ላይ ቀረብኩ፡፡ ቼልሲም ሊያስፈርመኝ ፍላጎት አሳየኝ፡፡ የጠራኝ ኤሚላኖ ነበር፡፡ ላምን አልቻልኩም፡፡ ያደግኩት ቼልሲን እያየሁ ነው፡፡ ሚኬልን እወደዋለሁ፡፡ ስለሴሌስቲን ባባደሮም እሰማ ነበር፡፡ ቼልሲ ሲያሸንፍ በናይጄሪያ ልክ የሀገራቸው ቡድን ያሸነፈ ያህል ይጨፍራሉ፡፡ በናይጄሪያ ከማንቸስተር ዩናይትድ የበለጠ ቼልሲ ብዙ ደጋፊ አለው፡፡ ዩናይትድ በሁለተኛ ደረጃ ይጠቀሳል፡፡
‹‹ቼልሲን ማንቸስተር ዩናይትድ ሲጫወቱ በአንዳንድ ቦታዎች ሁከትና ጥል ይነሳል፡፡ በከተማ ውስጥ ወዲያ ወዲህ የሚሉ ብስክሌተኞች የቼልሲን ወይም የማንቸስተር ዩናይትድን አርማ የውለበልባሉ፡፡ በናይጄሪያ እግርኳስ ይህን ያህል ይወደዳል፡፡
‹‹ቼልሲ እንዳስፈረመኝ ሳይውል ሳያድር ለዴን ሃግ ክለብ በውሰት ሰጠኝ፡፡ ብቃቴን እንዳሻሽል ተብሎ ነው፡፡ ደጋፊዎቻቸው በጣም ስሜታዊ ናቸው፡፡ ለእያንዳንዱ ተጨዋች ብቃቱን እንዲያሳድግ በደጋፊዎች በግል መዝሙር ይወጣለታል፡፡ የዴንሃግ ክለብ ደጋፊዎች ስሜት እየጠሩ ዘምረዋል፡፡
‹‹እዚህ ነው፣ እዚያ ነው፡፡ ሁሉ ቦታ ነው እያ ይዘምሩልኝ ነበር››
አሜሮ የተጎዱ ተጨዋቾችን ለመተካት ሲባል በቀኝ መስመር ተከላካይነት ተጫውቷል፡፡ ሆኖም ‹‹ምርጡ ቦታዬ የመሀል ተከላካይ ቦታ ነው›› ይላል፡፡ አሰልጣኝ ሞውሪንሆም በትክክል መዝነውታል፡፡ ‹‹(ሞውሪንሆን) ጓደኛዬ ኬኔት›› እያለ ይጠራኛል፡፡ ስለ እኔ የሚያወራበት መንገድ ሁሉ ደስ ይላል፡፡ ከአፍሪካ ዋንጫ በኋላ እንደፈለገኝ ሚኬል ነግሮኛል፡፡ ስላወቀኝ በጣም ተደሰትኩኝ፡፡
‹‹በናይጄሪያ ሁሉም ሰው ልጅ ሰው ይለዋል፡፡ ስትቀርበው ደግሞ ልዩ ሰው መሆኑን ትረዳለህ፡፡ ተጫዋቾች ያከብሩታል፡፡ ተጨዋቾችን እንዴት መያዝ እንዳለበት ያውቅበታል፡፡ ከእኛ ጋር እንዴት መነጋገር እንደሚገባውም ይረዳል፡፡ ልምምዱ ምርጥ ነው፡፡ በመጀመሪያ ለመልመድ ተቸግሬ ነበር፡፡ ከዌስትሃም ጨዋታ በፊት ተጋጣሚያችን በምን አይነት ዘዴ እንደሚጫወት ያውቃል፡፡ ጆዜ በልምምድ ሜዳ ላይ የሚናገረው ሁሉ በጨዋታ ላይ ሲሆን ታየዋለህ፡፡ በዚህ ምክንያት የበለጠ አክብሬዋለሁ፡፡
‹‹ተጨዋቾች ጥሩ ሰዎች ናቸው፡፡ ማይክል ኤሲዬን ለእኔ መልካም ነው፡፡ አሽሊኮል ሁልጊዜም ያበረታታኛል፡፡ ትክክለኛ ሸርተቴ በወረድኩ ቁጥር የእርሱን የማበረታቻ ድምፅ ትሰማለህ፡፡ አይዞህ ኬኔት ይለኛል፡፡ ጊዜህ ይመጣል፡፡ ሩቅ አይደለም፡፡ ዕድል ስታገኝ ተጠቀምበት እያለ ይመክረኛል፡፡ ጆን ቴሪም እንዲሁ ጥሩ ሰው ነው፡፡ ያወያየናል፡፡ ግዙፍና ጠንካራ ነው፡፡ እንደ ወጣት ተጨዋችነቴ አንጋፎቹ በልምምድ ላይ ብዙ ሲሰሩ ስመለከት ለራሴ ብዙ መስራት እንዳለብኝ እነግረዋለሁ፡፡
‹‹በልምምድ ላይ በትኩረት ተግቼ መስራት አለብኝ፡፡ እያንዳንዱ አጥቂ የየራሱ ተሰጥኦ አለው፡፡ ለአምስት ደቂቃዎች ጎል ካልተቆጠረብህ በየትም ቦታ ብጫወት እችላለሁ ብለህ ታምናለህ፡፡ ከፈርናንዶ ቶሬዝ ጋር በተቃራኒ ሆነህ መጫወት ይከብዳል፡፡ ጠንካራ መሆን አለብህም፡፡ እንዳያልፍህ መጠንቀቅ ይገባሃል፡፡ እነዚህ በቤልጂየም ሳለሁ ስከታተላቸው የነበሩ ታላቅ ተጨዋቾች ናቸው፡፡ ከእነርሱ ጋር መጫወት ያስደስታል፡፡ ሳሙኤል ኤቶ በአፍሪካ ትልቅ ተጨዋቾች ነው፡፡ ኤቶንና ኤሲዬንን ማግኘት በመቻሌ በጣም ደስተኛ ሆኛለሁ›› እያለ ኦሜሮ በቼልሲ ህልሙን እየኖረ መሆኑን ያስረዳል፡፡ ህልሙ ግን በዚህ አያበቃም፡፡ ከፕሪሚየር ሊጉ ታላላቅ ክለቦች በአንዱ ውስጥ በቋሚነት መጫወት ደግሞ ቀጣይ ምኞቱ እንደሚሆን ጥርጥር አይኖርም፡፡

 

Health: 9ኙ ቦርጭን ማጥፊያ የምግብ ዓይነቶች

$
0
0

(ይህ ጽሁፍ በዘ-ሐበሻ ጋዜጣ ቁጥር 58 የታተመ ነው።)
ሆድ አካባቢ የሚገኝን የስብ መጠን(ቦርጭን) ለመቀነስ ሙከራ ሲያደርጉ የፕሮቲን ይዘታቸው ከፍ ያለ፣ ሰውነት ውስጥ ተቋጥሮ የሚገኝን አላስፈላጊ ውሃ ማስወገድ የሚችሉ እና የምግብ መፈጨት ሂደትን የሚያቀላጥፉ ምግቦችን መርጦ አዘውትሮ መመገብ ይመከራል፡፡ እነዚህ ምግቦች የምግብ መፈጨት ሂደትን ቀልጣፋ ከማድረግ ባሻገር ሆድ አካባቢ የሚገኝን አይነተኛ ሚና ይጫወታሉ፡፡
ቦርጭን (ሆድ አካባቢ የሚገኝን የስብ መጠን) ሊቀንሱ የሚችሉ የምግብ አይነቶች የሚከተሉት ናቸው፡፡
color-133-Tomato-2
ቲማቲም

ቲማቲም ስብን ለማቃጠል ከሚረዱ ምግቦች ውስጥ አንዱና ዋነኛው ነው፡፡ ቲማቲም የማይነጥፍ ‹‹Anti oxidants›› በአጭሩ ኦክሲጅን ከሌሎች ‹ፍሪ ራዲካልስ› ከሚባሉ ንጥረ ነገሮች ጋር ውህደት በመፈፀም ሰውነት ላይ ሊያስከትል የሚችለውን ጉዳይ ይከላከላል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ቲማቲም ‹ሌፕቲን› የተሰኘ ፕሮቲን ሰውነታችን ውስጥ በብዛት እንዲመረት ስለሚያግዝ የምግብ ፍላጎትን ይጨምራል፡፡ እንዲሁም የምግብ መፈጨት ሂደትን ቀልጣፋ ያደርጋል፡፡
ሀባብ

ሀባብ የውሃ ሀብታም ነው፡፡ 94% የሚደርሰው ይዘቱ ውሃ ነው፡፡ በዚህ ምክንያት ተመራጭ አነስተኛ ካሎሪ ያለው ፍራፍሬ ነው፡፡ ሆድ አካባቢ የሚገኝን አላስፈላጊ ፈሳሽ በማስወገድ የሆድ መጠን እንዲስተካከል ያደርጋል፡፡ ሆድ አካባቢብቻ ሳይሆን ሌሎች የሰውነት ክፍሎ ውስጥ ውሃ አለአግባብ እንዳይጠራቀም ያደርጋል፡፡
እንጉዳይ

እንጉዳይ የ‹ፋይበር› ይዘቱ ከፍተኛ ስለሆነ ረዘም ላለ ጊዜ ጥጋብ እንዲሰማችሁ በማድረግ የምግብ ፍላጎታችሁን እና አወሳሰዳችሁን ይቀንሳል፡፡ የምግብ መንሸራሸር ሂደትንም ያቀላጥፋል፡፡
papaya
ፓፓያ
ፓፓያ ሆድ አካባቢ የሚገኝን ስብ ለማቃጠል በእጅጉ ይረዳል፡፡ ‹ፓፔይን› የሚባል ኢንዛይም ውስጡ ስለሚይዝ ይህ ኢንዛይም ደግሞ ምግብ በፍጥነት እንዲሰባበር እና ሆድ ልሙጥ እንዲሆን ያግዛል፡፡ ይህ ብቻ ሳይሆን ፓፓያ አላስፈላጊ እብጠት እና መነፋትን ያስተካክላል፤ የምግብ መፈጨት ሂደትንም ቀልጣፋ ያደርጋል፡፡
ኦሊቭ ኦይል
ብዙዎቻችን ክብደት ለመቀነስ ሙከራ ስናደርግ ከስብ ነክ ነገሮች እንድንርቅ ተመክረናል፡፡ ነገር ግን ኦሊቭ ኦይል ውስጥ የሚገኘው ኦሌይክ አሲድ ደማችን ውስጥ የሚገኝን የስኳር መጠን በመቆጣጠር ለክብደት መቀነስ ቀላል የማይባል አስተዋፅኦ ያበረክታል፡፡
አልሞንድስ
አልሞንድስ የካሎሪ ይዘታቸው ከፍተኛ ቢሆንም ሆድ አካባቢ ውፍረት በመፍጠር ግን አይታሙም፡፡ ይልቁንም ለቆዳ ጤንነት መጠበቅ እገዛ ሊያደርግ የሚችል ቫይታሚን ሲ ውስጣቸው ይገኛል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የፋይበር ይዘታቸው ከፍተኛ በመሆኑ የምግብ ፍላጎትን ያስተካክላሉ፤ የምግብ መፈጨት ሂደትን ያፋጥናሉ፡፡ ይህ በበኩሉ ሰውነታችን ውስጥ የሚገኝን አላስፈላጊ ስብ በማቃጠልና በማቅለጥ ክብደት እንድንቀንስ ያግዛል፡፡
banana
ሙዝ
ክብደት ለመቀነስ ሙከራ ስናደርግ ብዙዎቻችን ሙዝ መመገብ እናቆማለን፡፡ ይሁን እንጂ ሙዝ የፖታሺየም ይዘቱ ጥሩ በመሆኑ ሰውነት ያለአግባብ የሚቋጥረውን የውሃ መጠን ይቀንሳል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ሙዝ በፋይበር የበለፀገ ስለሆነ የምግብ ፍላጎታችሁ ያለአግባብ ሳይጨምር ጤናማ ሆኖ እንዲቆይ እገዛ ያደርጋል፡፡
አፕል
አፕል መርዛማ ነገሮችን የማስወገድ ባህሪ አለው፡፡ በዚህ ምክንያት የምግብ መፈጨት ሂደትን ቀልጣፋ ያደርጋል፤ ሰውነታችን ውስጥ የሚገኝ አላስፈላጊ ውሃም እንዲወገድ ያደርጋል፡፡
ኦትስ
ኦት የካሎሪ ይዘቱ አነስተኛ ቢሆንም ለሰውነት የሚሰጠው ኃይል ግን ከፍተኛ ነው፡፡ ክብደት መቀነስ ስትፈልጉ ታዲያ ጠዋት ከቤታችሁ ኦትስ ቀማምሳችሁ ብትወጡ በቂ ኃይል ስለሚሰጣችሁ የምግብ ፍላጎታችሁን ጋብ አድርጎ በማዋል ክብደት እንድትቀንሱ ያደርጋል፡፡

Viewing all 8745 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>