Quantcast
Channel: ዘ-ሐበሻ – Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 8745 articles
Browse latest View live

ዛሬም ኢትዮጵያውያን በጅዳ መካ በከፍተኛ ስቃይና እንግልት ላይ ናቸው (በፎቶ የተደገፈ አዲስ መረጃ ከሳዑዲ)

$
0
0

6000bc359d71474716d3500832e9d989

በጅዳ እና አካባቢው የኢትዮጵያውያን ክራሞት

ነብዩ ሲራክ (ከሳዑዲ አረቢያ)

ካሳለፍነው ወር ጀምሮ በመንግስት ጥሪ ወደ ሃገራቸው እንዲገቡ በተደረገው ጥሪ እጃቸውን የሰጡ መኖሪያና የስራ ፈቃድ የነበራቸው ዜጎች ባቀረቡት ቅሬታ ” ወደ ሃገር እንዳንገባ ተደርገን እየተጉላላን ነው! ” ብለውኛል። በቀን በሚሰጠው ደረቅ ብስኩትና ጥራቱ ባልተጠበቀ ሩዝ መጉዳታቸውን የገለጹልኝ ሲሆን መፍትሔ የሚሰጠን የኢትዮጵያ መንግስትም ሆነ የሳውዲ መንግስት ተወካዮች አጥተው ቀን በጸሃይ ፣ ማታ በብርድና በቁር እንግልት እንደደረሰባቸው ተናግረዋል። ወደ ሃገር እንግባ ብለው በተደረገው ጥሪ እጃቸውን የሰጡት መኖሪያና የስራ ፈቃድ የነበራቸው ዜጎች እዚህ በጅዳ ሽሜሲ ብቻ ሳይሆን በሪያድ እስር ቤቶች እንዳሉ እንግልት እየደረሰብን ያሉ ነዋሪዎች ምሬታቸውን ገልጸውልኛል።

ሁከት በጅዳ የንጉስ አብድልአዚአዚዝ አውሮፕላን ማረፊያ-

Screenshot_2014-01-08-01-29-06-1

ከጅዳ መካው የሽሜሲ መጠለያ ተነስተው ወደ ሃገር ለመሳፈር በጅዳ የንጉስ አብድልአዚአዚዝ አየር መንገድ ማረፊያ አውሮፕላን ማረፊያ የደረሱ ቁጥራቸው 1500 በላይ የሆኑ ኢትዮጵያውያን “የያዛችሁት እቃ ከሚፈቀደው ኪሎ በላይ ነው !” በሚል የተፈጠረው አለመግባባት ማክሰኞ ከቀትር በኋላ መጠነኛ ሁከት ተቀስቅሶ እንደነበር እና ከሰአታት በኋላ መረጋጋቱን ተደጋጋሚ መረጃ ደርሶኛል። የማክሰኞው ሁከት መነሻ የተመላሾችን የተከማቸ እቃ ለማየት ወደ ቦታው የደረሱትን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሃላፊ በቦታው መድረሳቸውን ተከትሎ ሲሆን በእንግልቱ የተበሳጩት ዜጎች ሁከት መቀስቀሳቸው ከአይን እማኞች ተደጋጋሚ የስልክ ጥሪ ለመረዳት ችያለሁ። የአይን እማኞች አክለውም ዜጎች ከሃላፊው ጋር ሊጋጩ ሲሉ በጸጥታ አስከባሪዎች ብርታት መትረፋቸውን ከቦታው በሰአቱ የደረሰኝ መረጃ ያስረዳል። ግርግሩ ለሰአት ያህል የቀጠለ ቢሆንም በሰውና በንብረት ላይ ጉዳት አልደረሰም። ሁኔታውን ለማረጋጋት በቦታው የተገኙ ፈጥኖ ደራሽ ፖሊሶች ማረጋጋት ከፈጠሩ እና ሁኔታው ከተረጋጋ በኋላ የአየር መንገዱን ሃላፊ ለጥያቄ ወስደዋቸው እንደነበርና ሃላፊውን ለማስለቀቅ የጅዳ ቆንስል ሃላፊዎች እና ጅዳ የመጡት የሪያዱ አንባሳደር ወደ ቦታው በመንቀሳቀስ ከሰአታት በኋላ ሃላፊውን ይዘው ምሽት ላይ መመለሳቸውን ተጨባጭ መረጃ ደርሶኛል።

የሃላፊውን ለጥያቄ መቅረብ ተከትሎ በጉዳዩ ዙሪያ ያነጋገርኳቸው አንድ ውስጥ አዋቂ ሲናገሩ ” በአውሮፕላን አቅርቦት እጥረት እና እቃችን ሳንይዝ ወይም በአደራ ተቀብሎ ወደ ሃገር የሚያስተላልፍልን እስካላገኘን ወደ ሃገር አንገባም ያሉትን ዜጎች ጉዳይ እንዲመለከቱ በቆንስላው ጥያቄ ወደ አየር ማረፊያው ያቀኑት የአየር መንገዱ ሃላፊ ስለ ዜጎች መጉላላት መረጃ እንዳልነበራቸውና በቦታው ሲደርሱ ከሁከቱ ጋር ተያይዞ ግራ ተጋብተው ታይተዋል።” በማለት ሲያስረዱ በቆንሰሉና በአየር መንገዱ ሃላፊዎች መካከል የመረጃ ክፍተት መኖሩን ገላልጠው አጫውተውኛል።
Screenshot_2014-01-08-01-29-16-1

ይህ በእንዲህ እንዳለ ከዚህ በፊት ከ40 ኪሎ በላይ እቃ መውሰድ አትችሉም የተባሉ ዜጎች እቃ ሃጅ ተርሚናል በሚባለው የአየር መንገዱ ማረፊያ ቦታ በብዛት ተዝረክርኮ እነወደሚገኝና የብዙዎች እቃ አድራሻ እንደሌለው የአይን እማኞች ገልጸውልኛል። “አድራሻ ያለውን እቃም በሚመለከት የጅዳ ቆንስል ሰብስበን እንልከዋለን የሚል ቃል ከመስጠት ባለፈ ምንም አይነት ተጨባጭ እርምጃ እንዳልወሰዱም” በማለት እማኞች ገልጸውልኛል።

ከአስር ቀናት ያላነሰ እንግልታቸውን በማስረዳት የተገፊ ድምጻቸውን እንዳሰማላቸው እንባቸውን እያዘሩና በብስጭት ያስረዱኝ ወገኖች በበኩላቸው ” የአውሮፕላኑን ወጭ የሳውዲ መንግስት ከቻለ የኢትዮጵያ መንግስት እቃችን ይዘን እንድንገባ ለምን አላመቻቸልንም? ሌላው ቢቀር መንግስት በሻንጣው መጫንና ለሳምታት ብስኩት እየተሰጠንና በውሃና ምግብ ግዠ የያዝነውን ገንዘብ ስናጠፋና ስንሰቃይ በዚህ ካልረዳን ወገኖቸ ማለቱ አልገባንም ! ዜጎች አይደልንም? ” ሲሉ በማጠየቅ በተጎዳ ሰሜት ገልጸውልኛል። ከዚህ ጋር በተያያዘ አንድ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ወንድም እንደገለጹልኝ ዜጎችን ማጓጓዙ እንደ በፊቱ በፍጥነት ባይከወንም አልፎ አልፎ መቶና ከመቶ በላይ ዜጎች በተገኘ የበረራ ክፍት ቦታ እየተላኩ መሆኑን በማስረዳት ከቀን ወደ ቀን እየተባባሰ የመጣውን ይህንን ችግር የቆንስሉ ሰራተኞች በተደጋጋሚ ለቆንስል ሃላፊዎች ማሰማታቸውን በመግለጽ መፍትሔ ግን እስካሁን አለመሰጠቱን አክለው ገልጸውልኛል።
Screenshot_2014-01-08-01-29-39-2

የካርጎ መዘጋት መዘዝና የነዋሪዎች ሮሮ-

የአየር መንገድ የካርጎ አገልግሎት ለወራት መሰናከል ተከትሎ በኢትዮጵያ አየር መንገድና በእቃ አቅራቢ የካርጎ ኤጀንቶች በደል ደረሰብን የሚሉ ዜጎች ቅሬታ እያሰሙ ነው ። ይህ ችግርም በነዋሪዎችና በካርጎ ኤጀንሲ ሰራተኞች መካከል ውዝግብ ማስከተሉ አልቀረም። የአየር መንገድ ወደ ኢትዮጵያ የሚደረገው ጉዞ ከስድስት ወራት በላይ ምክንያቱ ግልጽ ባልሆነ ምክንያት ከተዘጋ በኋላ ሰሞኑን ስራ መጀመሩ እየተሰማ ነው ። ያም ሆኖ በጅዳ ዙሪያ ያሉ የካርጎ ኤጀንሲዎች ” ወደ ኢትዮጵያ የካርጎ ግልጋሎት በተለያዩ አቅጣጫዎች እንሰጣለን ! ” በሚል ከፍተኛ ገንዘብ ለእቃው ማስጫኛ እየተቀበሉ እቃውን ቢረከቡም ከስድስት እሰከ አስር ወራት ለሚቆይ ጊዜ እቃውን በመጋዘ ቃላቸውን ጠብቀው እንዳላደረሱላቸው የመጫኛ ማስረጃቸውን እያሳዩ ቅሬታቸውን የገለጹልኝ በርካታ ዎች ናቸው ። የሳውዲ ውጡ ህግ ከተነገረ ጀምሮና ከዚያም ወዲህ በተሰጠው የሰባት ወር የምህረት ጊዜ ጠቃሚ የሚሏቸውን ጥሪት እቃቸውን ለካርጎ ቢያስረክቡም አንድም በካርጎው መዘጋት በተጓዳኝ በካርጎ ኤጀንሲዎች ለአንድ ኪሎ እስከ 10 ሪያል በመክፈል እቃቸውን ቢያስገቡም እቃቸውን ደህንነት በማያውቁበት ደረጃ በንብረታቸው ላይ ብክነት እንዳስከተለባቸው እያዘኑ ሮሯቸውን አጫውረተውኛል።
Screenshot_2014-01-08-01-29-20-1

በጀዛን የዜጎች እንቢታ እና የህግ ታሳሪዎች ሮሮ -

በጀዛን ” ወደ ሃገር እንግባ !” የሚሉ ነዋሪዎችን ጥሪ ተከትሎ የመጓጓዣ ሰነድ ለመስራት የጅዳ ቆንስል መስሪያ ቤት ተወካይ ዲፕሎማት ወደ ቦታው ያቀኑ ቢሆንም “ድረሱልን !” ሲሉ የነበሩ ዜጎች የውሃ ሽታ መሆናቸውን የኮሚቴውን በፊስ ቡክ መኖሩን የሚያሳውቀን የወገን ለወገን የህዝብ ግንኙነት ፊስ ቡክ ጠቁሞናል። በጀዛን የሚገኙ የህግ እስረኞችም በህግ ተይዘው ፍርድ ከተሰጣቸው በኋላ ለአመታት የሚጉላሉ እና በጥርጣሬ ተይዘው ፍርድ ቤት ያልቀረቡ ዜጎች የድረሱልን ጥሪ ዛሬም አላቆመም። “ትኩረቱ ሁሉ ወደ ሃገር ተመላሾች መሆኑ ብቻ ሳይሆን ድሮም ተረስተናል አሁንም ተረስተናል! ” እያሉ ነው! በጀዛን ዙሪያ ባሳለፍነው ሳምንት መረጃ ያቀበለን የወገን ለወገን ደራሽ የህዝብ ግንኙነቱ ገጽ ባስተላለፈው መረጃ ወደ ሃገር ቤት ለመሄድ ሰላላሳዩት ዜጎች ትኩረት በመስጠት የዜጎችን ወደ ሃላፊዎች ለመቅረብ እና ለመሸኘት ፍላጎት አለማሳየታቸውን ሲገልጽም ” እነሆ ግዜው ደረሰና የሁለቱም ሃገር መንግስታት ሁኔታዎችን አስተካክለው በሰማት (አሻራ) የሚሰጡበት ቦታ ተበጅቶላቸው ከቆንስላ ፅ/ቤት ተወካይ በቆንስል አህመድ የሚመራ ቡድን ለዜጎቻችን እዚያው እንዲሰራላቸው በማሰብ ወደ ጂዛን ተጓዙ። አሁንም እዚያው ናቸው። ነገር ግን ነገሮች እንደታሰቡ እየሄዱ አይደለም። ታስቦላቸው የተሄደላቸው ወገኖች እየወጡ አይደለም የሚል አሳሳቢ ዜና ሰማን።አሁን ባለው ሁኔታ ወደ ማቆያ የሚገቡት ሰዎች በቀን መቶም እንደማይደርሱ ተገለፀልን። ከጂዳ ለዚህ ጉዳይ የተንቀሳቀሰው ልኡካን አሁንም ለማገልገል ይጠብቃል፡ ምንም የሚታይ ነገር ግን የለም። በጂዛን አጎራባች ወደ ሆኑ ከተሞችም ከአካባቢው ማህበረሰብ አምስት አምስት ሰዎች ለቅስቀሳ ተልከዋል። ቢሆንም ወገናችን ዜጎቻችን የሚወጡ አይነት አይደለም። በጣም ሚገርም ነው። ” ይላል። የህግ ታሳሪዎች በበኩላቸው የቆንስል ሃላፊዎችን አነጋግረዋቸው “ለእናንተ ጉዳይ አልመጣንም! ” እንዳሏቸው ገልጸውልኛል። የህዝብ ግንኙነቱ ዜጎች ወደ ኋላ ስላፈገፈጉበት ጉዳይም ሆነ በደል ደረሰብን ስለሚሉ ህጋዊ ታራሚዎች የሰጠው መረጃ የለም ። በወገን ለወገን ደራሽ ኮሚቴ ለአንድ ወር በስራ አስፈጻሚነት የሰራሁ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን ለቆንስል ሃላፊዎች ያቀረብኩት የዜጎች አቤቱታ እንዲታረም በተደጋጋሚ አሳስቤ የነዋሪውን አቤቱታ በጀርመን ራዲዮ በማቅረቤ በተወሰደ የ ” በዲሲፕሊን! ” እርምጃ ከኮሚቴው አባልነት በተጽዕኖ መነሳቴ ይታወሳል!

Screenshot_2014-01-08-01-29-51-1

የውጭ ጉዳይ ልዑካን በጅዳ -

በሳውዲ አረቢያ የሪያድ ኢንባሲ አምባሳደርን ጨምሮ ሶስት አባላትን የያዘው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቡድን ከሶስት ቀናት በፊት ጅዳ ገብተዋል። ልዑካኑ በእስካሁኑ ቆይታቸው የኢህአዴግ የድርጅት አባላትንና የጅዳ ቆንስል ሃላፊዎችን በዝግ ያነጋገሩ ሲሆን የውይይታቸው ትኩረት በመጡበት የዜጎችን ወደ ሃገር መግባት ጉዳይ የማፋጠን ስራ ይሁን በሌላ ተዛማጅ ጉዳይ የሚታወቅ ነገር የለም። የልዑካን ቡድኑ አባላት በእስካሁን ቆይታቸው አደጋውን ለመከላከል በጅዳ ቆንስል ሃላፊዎች የተቋቋመውን የወገን ለወገን ደራሽ ጊዜያዊ ኮሚቴ እስካሁን ያላነጋገሩ መሆኑ ታውቋል። የልዑካኑ ቡድንን ኮሚቴውን አለማነጋገሩ ቅያሞት የገባቸው አንዳንድ አባላት በበኩላቸው የዜጎች እንግልት በቅንጅት ጉድለት እየተበራከተ በሄደበት በዚህ አጋጣሚ ኮሚቴው ንቁ ተሳትፎ ማድረግ ላልቻለበት ሁኔታ የቆንስሉ እና የአመራሩ ድክመት እንደሆነ በማስረዳት እያደር ለይስሙላ የተቋቋመ እንጅ ወገንን ለመርዳት ከመካዝን ያለውን ውሃ ለማደል እንኳ አቅም አጥቷል በሚል ከማህበረሰቡ ወቀሳ እየቀረበበት መሆኑን በግልጽ አጫውተውኛል።
a97a08f471f6148ffe0ee14caac97504

በሳውዲ አረቢያ የሪያድ ኢንባሲ አምባሳደርን ጨምሮ ሶስት አባላትን የያዘው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ልዑክ በጅዳ ቆንስል የመንግስታችን ተወካዮች ለተጠቀሱትና በከባቢው ላሉ ችግሮች አፋጣኝ እርምጃ ካልወሰዱ አደጋውን መታደግ ከማንችልበት ደረጃ እንዳይደረስ የብዙ ነዋሪዎች ስጋት ሆኗል። የሳውዲ መንግስትን እና የኢትዮጵያ ኢንባሲና ቆንስል በማስታወቂያ ብቻ የተደገፈ ተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያ ተከትሎ ” ሰነድ የሌላችሁ ዜጎቸወ ከሳውዲ ውጡ !” በሚል ማስተላለፋቸው አይዘነጋም። ያም ሆኖ ነዋሪው በርካታ ያልተሟሉ ቅድመ ሁኔታዎችን በማቅረብ ለመውጣቱ ጥሪ “አሻፈረኝ!” ያሉትን በሽዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች ሮሮ እና ጥያቄ ለመስማትና አፋጣኝ የመፍየትሔ እርምጃ ለመውሰድም የመንግስት ሃላፊዎች ህዝባዊ አስቸኳይ ጥሪ በመጥራት መፍትሔ ያመላክቱ ዘንድ ደግሜ ደጋግሜ እመክራለሁ !
ዛሬም የመረጃ ክፍተቱ ይዘጋ ፣ የምንናገረው ተጨባጭ መረጃ መሆኑን አጣርታችሁ መፍትሔ አፈላልጉ ስል ደጋግሜ” ጀሮ ያለው ይስማ!” እላለሁ !
ቸር ያሰማን !
ነቢዩ ሲራክ

Share and Enjoy

  • Facebook
  • Twitter
  • Delicious
  • LinkedIn
  • StumbleUpon
  • Add to favorites
  • Email
  • RSS

Sport: 3ቱ የቀድሞ ብሔራዊ ቡድናችን በረኞች አሊ ረዲ፣ ደያስ አዱኛና ታድዮስ ጌታቸው የት ይገኛሉ?

$
0
0

ከይርጋ አበበ

በአገራችን እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ በግብ ጠባቂነት ስመ ጥር የሆኑ እንደነ ተካበ ዘውዴ ያሉ በርካታ ስፖርተኞች አሉ። በዘመናቸው ለክለባቸውም ሆነ ለአገራቸው የሚችሉትን አበርክተዋል። ለእዚህ ዝግጅት የኢትዮጵያ ቡና፣ የመብራት ኃይልና ቅዱስ ጊዮርጊስ ክለቦችንና የብሔራዊ ቡድናችንን በር ከጠበቁት ተጫዋቾች መካከል ሦስቱ ያሉበትን ሁኔታ በአጭሩ እነሆ!

ዓሊ ረዲ
ali rade 2

ali rade
ዓሊ ረዲ የኢትዮጵያ ቡና እግር ኳስ ክለብ ደጋፊዎች «ከለላችን» እያሉ የሚጠሩት ቁመተ መሎሎ ግበ ጠባቂ ነው። በአንድ ወቅት በደረሰበት ከባድ ጉዳት ሼህ ሙሐመድ ሁሴን ዓሊ አላ ሙዲ ለህክምና ሙሉ ወጪውን ሸፍነው ካሳከሙት በኋላ የክለቡ ደጋፊዎች «አላሙዲ አላህ ይስጣቸው» ብለው ምስጋናቸውን በአደባባይ ያስነገራቸው የተጫዋቹ ከፍተኛ ባለውለታቸው መሆን ነበር።
ዓሊ ረዲና እግር ኳስ ለመጀመሪያ ጊዜ የተዋወቁት የሀገራችን ስፖርት ባለውለታ በሆነው የኦሜድላ ክለብ ሲሆን፤ ዘመኑም በ1987ዓ.ም ነበር። ኢትዮጵያ ቡና ደግሞ የኦሜድላውን ፍሬ ገና ከእሸትነቱ ጀምሮ እስኪጎመራ ድረስ ተጠቀመበት – ከ1989 እስከ 1995ዓ.ም ድረስ።
ክለቡ ኢትዮጵያ ቡና ጠንካራዎቹን የግብጽ ክለቦች አልሃሊና ዛማሌክ በማሸነፍ የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ክለብ በሆነበት ዘመን የክለቡን በር በንቃትና በታማኝነት ጠብቋል። እንዲሁም የጥሎ ማለፍ ዋንጫዎችን ደጋግሞ ማንሳት የቻለውን ክለብ በር የጠበቀውም ይኼው ቁመተ ሎጋ ግብ ጠባቂ ነበር።
ከተካበ ዘውዴ በኋላ ብሄራዊ ቡድናችንን በር በንቃት የጠበቀ ታታሪ ግብ ጠባቂ ነው እየተባለ የሚጠራው ዓሊ ረዲ ለሀገሩ በተሰለፈባቸው ጨዋታዎችም ቢሆን ሀገራዊ አደራውን ተቀብሎ በኩራት የተወጣ ባለአደራ ተጫዋች ነው።
ዓሊ ረዲ ከኢትዮጵያ ቡና የተለየው ዓሊን ካጋጠመው ከባድ የደም ካንሰር በኋላ ከእግር ኳስ ለረጅም ዓመታት በመገለሉ ሲሆን፣ የቀድሞው ቡናማ በአሁኑ ወቅት የውሃ ሥራዎች እግር ኳስ ክለብ ግብ ጠባቂ ነው።
Deyas adugna
ደያስ አዱኛ
ዲያጎ ጋርዚያቶ በአሰልጣኝነት እየመሩ ወደ አርጄንቲና የተጓዘውን የወጣት ብሔራዊ ቡድናችንን ግብ የጠበቀው ወጣት ተጫዋች ነው። በተለይ ሀገራችን ያደረገቻቸውን ሶስቱንም ጨዋታዎች በቴሌቪዥን ሲያስተላልፉ የነበሩ ጋዜጠኞች የግብ ጠባቂያችን ስም ሲጠሩ «ደያስ አዱግና» እያሉ ሲጠሩት በርካታ ኢትዮጵያውያንን ፈገግ ያሰኙ ነበር።
ደያስ አዱኛ የቅዱስ ጊዮርጊስና መብራት ኃይልን ክለቦች ግብ ጠባቂነት ያገለገለ ታታሪ ግብ ጠባቂ ነበር። ወደ አዲስ አበባ መጥቶ የሁለቱን ክለቦች በር ከመጠበቁ በፊት የሙገር ሲሚንቶ ክለብ ተጫዋች ነበር። በርካታ ታዳጊዎችን ከየመንደሩ እያሰሰ ወደ አደባባይ በማውጣት የሚታወቀው ሙገር ሲሚንቶ ደያስንም ለብሔራዊ ቡድናችንና ለሁለቱ ታላላቅ የአዲስ አበባ ክለቦች ማብቃት ችሏል።
ደያስ አዱኛ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር የነበረውን ቆይታ ካጠናቀቀ በኋላ ኑሮውን ያደረገው አሜሪካ ነው። አሁንም የሚገኘው እዛው አሜሪካ እንደሆነ ለተጫዋቹ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ለዝግጅት ክፍላችን ገልጸውልናል።

ታዲዮስ ጌታቸው
tadios getachew
ታዳጊዎችን በማዕከሉ እያሳደገ ለዋናው ክለብ በማሰለፍ የሚታወቀው ቅዱስ ጊዮርጊስ ይህንን መለሎ ግብ ጠባቂም በአካዳሚው አሳድጎ ለቁም ነገር ማብቃቱ ይነገርለታል። ከ1989ዓ.ም ጀምሮ እስከ 1996ዓ.ም ድረስ የፈረሰኞቹን በር መጠበቅ የቻለው ታዲዮስ ጌታቸው ከክለቡ ጋር የተለያዩ ዋንጫዎችን ማንሳት የቻለ ሲሆን፣ የምስራቅ አፍሪካ ክለቦች ሻምፒዮና ላይም ቢጫና ቀዩን ማሊያ ለብሶ በመጫወት የነሐስ ሜዳሊያ መሸለም የቻለ ግብ ጠባቂ ነበር።
ከፈረሰኞቹ ጋር የነበረውን ቆይታ አጠናቅቆ ወደ ታሪካዊ ተቀናቃኛቸው ኢትዮጵያ ቡና በማምራት የቢጫ ለባሾቹን የግብ ክልል ከዓሊ ረዲ ተረክቦ መጠበቅ ችሏል። ከቡና ጋር የነበረው ቆይታ እንደ አሳዳጊ ክለቡ ያልሰመረለት ታዲዮስ ከክለቡ ጋር ያለውን ውል ሳይጨርስ በ1999ዓ.ም ወደ አገረ አሜሪካ ተጉዟል። ልክ እንደ ደያስ አዱኛ ሁሉ ታዲዮስ ጌታቸውም አሁን በአሜሪካን አገር በሎሳንጀለስ ከተማ ይኖራል።

ለሃገር ውለታ ለዋሉ ክብር እንስጥ!!

የፓርቲያችንን ህጋዊ እንቅስቃሴ ለፖለቲካ ፍጆታ ማዋል የገዥውን ፓርቲ የፕሮፓጋንዳ ውድቀት እና ኢ-ህገመንግሥታዊነት የሚያሳይ ነው!!!

$
0
0

ከአንድነት ለዴሞክራሲ እና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) የተሰጠ መግለጫ!!!

ፓርቲያችን አንድነት የተቋቋመለትን ሕዝባዊ ዓላማ መሰረት በማድረግ በኢትዮጵያ ውስጥ ከ50 ዓመት በላይ ትግል ተደርጎበት እውን መሆን ያልቻለውን ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ሳይሸራረፍ ለማስፈን፤ አምባገነኑን ስርዓት በሰላማዊ ትግል ለመለወጥ እንዲሁም የህግ የበላይነት እንዲረጋገጥ ለማድረግ ህግን መሰረት አድርጎ እየሰራ ይገኛል፡፡ በዚህ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት የማስፈን ትግልም ፓርቲያችን፣ አመራሩና ቁርጠኛ አባላቱ ከፍተኛ መስዋዕትነት ከፍለዋል፤ እየከፈሉም ይገኛሉ፡፡ ዋጋ በከፈሉና ዋጋ እየከፈሉ ባሉ አመራሮቻችንና አባሎቻችን መራራ ትግል ምስጋና ይሁንና በመላ ኢትዮጵያ ሕዝባዊ መሰረት በመጣል ከኢትዮጵያ ህዝብ ጎን መሆናችንንም አረጋግጠናል፡፡ ይህ የፓርቲያችን ጥንካሬ የራስ ምታት የሆነበት ገዥው ፓርቲ ግን ባገኘው አጋጣሚ ሁሉ ህዝባዊ መሰረታችንን ለመናድ በስም ማጥፋት፣ በፍረጃና ባልዋልንበት እንደዋልን የማስመሰል ስራውን አጠናክሮ በመቀጠል በህዝቡ ዘንድ ያለንን መልካም ስማችንን ለማጉደፍ ባገኘው አጋጣሚ ሁሉ እየሰራ ይገኛል፡፡

አንድነትም የገዥውን ፓርቲ ኢ-ህገ መንግስታዊ የሆነ እኩይ ተግባር ተገቢ እንዳልሆነ፣ ለሀገርና ለህዝብ እንደማይጠቅም፣ የህዝብን ጥያቄ በዶክመንተሪ ጋጋታ መመለስ እንደማይቻል፣ ከፍረጃና ከሴራ ተላቅቆ በሰከነ መንገድ ወደ ውይይት እንዲመጣ በተደጋጋሚ መክረናል፤ ሀገራዊ ጥሪም አቅርበናል፡፡ ነገር ግን አምባገነኑ ስርዓት የሚቆጣጠራቸውን የመንግስት ተቋማት በመጠቀም አሁንም በዶክመንተሪ ስም ከማጥፋት፣ ከመፈረጅና ከማስፈራራት መላቀቅ አልቻለም፡፡

ሰሞኑን በተከታታይ 3 ክፍል ተላልፎ ይቀጥላል በተባለውና የፀረ-ሽብር ግብረ ሃይል ከኢቲቪ ጋር በመሆን አዘጋጅቶታል በተባለው ተከታታይ የዶክመንተሪ ፕሮግራም ላይ መሰረት የተደረገው ፓርቲያችን በመላ ኢትዮጵያ ህዝባዊ ንቅናቄ በመፍጠር እንዲሰረዝ እንቅስቃሴ ያደረገበት የፀረ ሽብር ህጉ ላይ ነው፡፡ አንድነት የፀረ-ሽብር ህጉ ይሰረዝ ሲል አሳማኝ መከራከሪያዎችን በማንሳትና በሰላማዊ መንገድ ቢሆንም ገዥው አካል ግን እንደተለመደው ማስተላለፍ ከፈለጉት አላማ ጋር የፓርቲያችንን ስም በማይገባ ቦታ በማንሳትና ለሚመለከተው አካል በህጉ መሰረት አሳውቀን ባካሄድናቸው ሰላማዊ ሰልፎች እና ህዝባዊ ስብሰባዎች ላይ ያስተላለፍናቸውን  አቋሞች  የሃሰት ትርጉም እየሰጠ የተለመደ የዶክመንተሪ ድራማው ማድመቂያ ሲያደርገን ተስተውሏል፡፡  የፓርቲ አመራሮች በህጋዊ ሰላማዊ ሰልፎች ላይ ያደረጉትን ንግግር ቆርጦ በመጠቀም በህዝብ ዘንድ ያለን ተቀባይነት ላይ ተፅዕኖ ለማሳረፍ የታቀደ መሆኑን እንገነዘባለን፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ሁሌም ምርጫ ሲቃረብ እንደሚያደርጉት ሁሉ በ2007 ዓ.ም ለሚካሄደው ሀገራቀፍ ምርጫ የተቃውሞ ጎራውን በፀረ-ሰላምነት ለመፈረጅ እየተደረገ ያለ የኢህአዴግ የምርጫ እንቅስቃሴ ክፍልም ነው፡፡

በዚሁ ዶክመንተሪ ላይ መቀመጫውን በውጭ በማድረግ የተለያዩ ዜናዎችንና ፕሮግራሞችን በማሰራጨት የሚታወቀውን ኢሳት (ESAT) ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ጣቢያ ላይ ፓርቲያችን ለአባላቱ እና ለደጋፊዎቹ መልዕክት ማስተላለፉን እንዲሁም እንደፓርቲ ለማንኛውም ሚዲያ የፓርቲያችንን ሰላማዊ እንቅስቃሴ በተመለከተ ስንጠየቅ የመመለስ መብታችንን በሚጋፋ መልኩ የፓርቲያችንን አቋም አዛብቶ ለማቅረብ ሞክሯል፡፡

ይህም የኢህአዴግን  የፖለቲካ ባህሪ እና አቋም በግልፅ ያሳየ ነው ማለት ይቻላል፡፡ በፓርቲያችን ዕምነት ኢህአዴግ በሚጠላቸው እና በሚያጥላላቸው ሚዲያዎች ሃሳብን መግለፅ በየትኛውም መመዘኛ አሸባሪነት ሊሆን አይችልም፡፡ የኢህአዴግ መንግስት ሲያስነጥሰው ከሚያለቅሱለት የፕሮፓጋንዳው ፍጆታዎች ከሆኑት ሚዲያዎች ውጪ የኔ ያልሆኑ የሌላ ናቸው ብሎ የሚያምን በመሆኑም ፍረጃው ህጋዊ አግባብነትም ሆነ መረጃ የሌለው ባዶ ፍረጃ መሆኑ ከማንም የተሰወረ አይደለም፡፡

ከሁሉም በላይ ህገ መንግስታዊ መሰረት የሌለው ቢሆንም እንኳ ቢያንስ ራሳቸው ላወጡት ህግ  ታምነው ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በማቅረብ ሳያስወስኑ አንድን የሚዲያ ተቋም ያውም ለአንድ አላማ የተቋቋመ የፀረ-ሽብር ግብረሃይል ‹‹የአሸባሪ ድርጅት ልሳን ነው›› ወይም ‹‹አሸባሪ ነው›› በማለት ሲፈርጅ ስናይ አሁንም የሀገራችን ፖለቲካ ፓርቲና መንግስት የተደበላለቁበት፣ አንድ ድርጅት እንደፈለገው የሚፈርጅበት ስርዓት እንዳለ የሚጠቁም ነው፡፡

ፓርቲያችንም ይህንን ህገ ወጥ ፍረጃ በቀላሉ የማይመለከተው መሆኑን እየገለፅን ገዥው ፓርቲ ከድርጊቱ እንዲቆጠብ፤ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንም ለተፈፀመብን የስም ማጥፋት ከተጠያቂነት የማያመልጥ መሆኑን እያሳወቅን አሁንም ህገ-መንግስት የሚጥሰውንና ተቀናቃኝ ሃይሎችን ለማሸማቀቅ እያገለገለ ያለው የፀረ-ሽብር አዋጅ እንዲሰረዝ ሰላማዊ ህዝባዊ ትግላችንን በማጠናከር እንደምንቀጥል እንገልፃለን፡፡ የህዝብ ልዕልና እና የህግ የበላይነት እንዲከበር ትግሉ የሚጠይቀንን መስዋዕትነት እንደምንከፍል ለመላው የኢትዮጵየ ህዝብ በድጋሚ እናረጋግጣለን፡፡

                               አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ

                 ታህሳስ 29 ቀን 2006 .

   አዲስ አባባ

UDJ

                                                               

 

ጠቅላይ ምኒስትራችን ለደቡብ ሱዳን የተመኙትን ለኢትየጵያም ቢያደርጉት

$
0
0

ከታምራት ታረቀኝ

ደቡብ ሱዳን ግጭቱ ተባብሷል፣እልቂቱ ከፍቷል፣የተፈናቃዩ ቁጥር ጨምሯል፣ድርድሩ አልሰምር ብሏል፣ ጠቅላይ ሚኒስትራችንና ውጪ ጉዳይ ምኒስትራቸን ሥራ በዝቶባቸዋል፡፡
የደቡብ ሱዳኑ ፕሬዝዳንት ምክትላቸውን ከሥልጣን ማባረረረራቸውን ተከትሎ የተቀሰቀሰው ግጭት እንበለው ጦርነት አንድም ኢትዮጵያ የወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር በመሆኗ፣ሁለትም ወሰን ተጋሪ ቅርብ ጎረቤት ሀገር በመሆኗ ሶስትም ተመሳሳይ ጎሳዎች እዚህም እዛም ያሉ በመሆኑ አራትም አዲሲቷ በነዳጅ የከበረች ሀገር ለበርካታ ኢትዮጵያውያን የሥራ ቦታ በመሆኗ ወዘተ ምክንያቶች የተቀሰቀሰው ግጭት ኢትዮጵያን በጣሙን ያሳስባታል፡፡ ይህም በመሆኑ ነው ሁለቱ ምኒስትሮች ፋታ ማጣታቸው፡፡
sudan south north sodan
ነገሩ ወደ ጎሳ ግጭት እንዳያመራ ያሰጋል፣

ውጪ ጉዳይ ምኒስትር ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሀኖም 2006 ከጅምሩ ሥራ አብዝቶባቸዋል፡፡ሰውዲ አረቢያ ከሀገሬ ውጡ በማለት ኢ-ሰብአዊ ድርጊት የፈጸመችባቸው ኢትዮጵያዉያንን ጉዳይ ከጅምሩ ተገቢ ትኩረት ባይሰጠውም የዓለም የመገናኛ ብዙኋን በማስተጋባታቸውና ተቀዋሚዎችም በሀገር ወስጥም በተለያዩ ሀገራም ሰላማዊ ሰለፍ በመውታት ጭምር ሰወዲን በኢሰብአዊ ድርጊ ቷ እኛን መነንግስት ደግሞ በቸልተኝነቱ በማውገዛቸው መንገሥት በእቅድ ሳይሆን በግብታዊነት የገባበት ወደ ሀገር የመመለስ ስራ ላይ ዋንኛ ባለድርሻ ሆነው የታዩት ዶ/ር ቴዎድሮስ ናቸው፡፡ስራው ደንገቴ ከመሆኑ በላይ የተመላሾቹ ቁጥር ከተገመተው አይደል ሊታሰብ ከሚችለው በላይ መሆኑ ደግሞ ሌላው ራስ ምታት ነበር፡፡

ይህ ሳይጠናቀቅና መልክ ሳይዝ በጎረቤት ደቡብ ሱዳን የተቀሰቀሰውን ግጭት ተከትሎ የመንግሥት ያለህ፣ከዕልቂት አድኑን፣ከጦርነት እሳት አውጡን የሚል የዜጎች ጩኸት በመሰማቱ በእንቅር ላይ ጆሮ ደግፍ ሆኗል፡፡
በዚህ ውጥረት ወስጥ የሚገኙት ዶ/ር ቴዎድሮስ የደቡብ ሱዳን ግጭት ተባብሶ እልቂት ከመንገሱ በፊት ለግጭቱ ምክንያት የሆኑትን ፕሬዝዳንቱንና ም/ል ፕሬዝዳንቱን ወደ ድርድር ለማምጣት ከአዲስ አበባ ጁባ ተመላልሰዋል፡፡ነገሩ ተባብሶ ወደ ጎሳ ግጭት እንዳያመራ ያላቸውን ስጋትም ገልጸዋል፡፡
በጎሳ ላይ በተመሰረተ የሥልጣን ክፍፍል ከያዙት ሥልጣን አንዱ አባራሪ ሌላው ተባራሪ ሲሆን ጉዳዩ የሁለቱ ሰዎች ብቻ ሆኖ ሊቆም፣ በፖለቲካ መንገድ ብቻ ሊስተናገድ አይቻለውምና ወደ ጎሳ ግጭት ማምራት አይደለም ሲጀመርም በዛው መልክ ነው የሚነሳው፡፡ ሹመታቸው በጎሳቸው እንደመሆኑ ጸባቸውም ጎሳዊ ነው የሚሆነው፡፡ ስለሆነም አስፈሪው የጎሳ ግጭት መቼም የትምና በማንም እንዳይነሳ ዋናው መፍትሄ ከመነሻው ፖለቲካው በጎሰኝነት ዜማ የሚዘፈንበት እንዳይሆን ማድረግና የሥልጣን ክፍፍሉ ጎሳን መሰረት አድርጎ ታማኝ ከሆነ ዘበኛም ቢሆን ምኒስትር አድርገን እንሾማለን እየተባለ የሚፈጸም ሳይሆን በእውቀትና በብቃት ብሎም በሕዝብ መራጭነት ተግባራዊ ማድረግ ነው፡፡

ውጪ ጉዳይ ምኒስትር ዶ/ር ቴዎድሮስ ደቡብ ሱዳን ተገኝተው የተመለከቱት ከአቻዎቻቸው ፖለቲከኞች ጋር ሲነጋገሩ የተገነዘቡት አሳስቧቸው ወደ ጎሳ ግጭት እንዳይሸጋገር መስጋታቸውና ይህንኑ በአደባባይ በይፋ መግለጻቸው ተክክል ቢሆንም እውነቱ የተከሰተላቸው በሰው ቤት ያውም ግጭት ተቀስቅሶ ደም ከፈሰሰ በኋላ መሆኑ ነው አጠያያቂው፡፡

እኛ ቤት፣ ከኢትዮጵያዊነት ጎሰኝነት ቀድሞ መጀመሪያ በየጎሳችሁ ተበታትናችሁ ከዛ በኋላ ኢትዮጵያን በመፈቃቀድ እንመሰርተንለን የሚል ቅዠት ተፈጥሮ፣ እንትንነቴን(ጎሳውን) የማታረጋግት ኢትዮጵያ ትበታትን እየተባለ ተፎክሮ በአንድ ሰሞን የፖለቲካ ስካር ወገን በወገኑ ላይ ጦር እንዲመዝ መደረጉ የሚዘነጋ አይደለም፡፡ ኢትዮጵያዊ አንደ እየምነቱ ለፈጣሪው የሚገዛ ከትውልድ ወደ ትውልድ እየተላለፈ የቀጠለ ጨዋነት የባህሪው መሆኑ እንጂ አንደ ፖለቲከኞቹ ፍላጎት ቢሆን ኢትዮጵያ በዛሬ መልኳ መታየት ባልቻለች ነበር፡፡
ኢትዮጵያዊነትን ማንም በምንም መንገድ ሊያጠፋው አይችልም፡፡ ፕ/ር መስፍን ወ/ማሪያም በ1986 ዓም ኢትዮጵያ ከየት ወዴት በሚል ርእስ በጻፉት መጽሀፍ ገጽ 32 ላይ «የኢትዮጵያ ታሪክ ሊያስተምረን እንደሚችለው ኢትዮጵያዊነት አንደ ላስቲክ ነው ሲስቡት ይሳባል፣ሲለቁት ይሰበሰባል ፣ ማለት ይሳብና ይሳሳል እንጂ አይበጠስም» ይላሉ፡፡ የጎሳ ፖለቲካ አቀንቃኞቹ ካልተሳካው ተግባራቸው ይህን መረዳታቸው ባያጠራጥርም አልሆንልህ አለኝ አጉራህ ጠናኝ ብለው ወደ ትክክለኛው መስመር መመለስን ሽንፈት አልያም ውርድደት ሆኖባቸው እንደ አጀማመራቸው ባይሆንም ዛሬም ጎሰኛነትን ከማቀንቀን አልተመለሱም፡፡

ለሥልጣን መሰረቱ ለሹመት መስፈርቱ የጎሳ ድልድል ሆኖ ማስፈጸሚው ደግሞ በስም ለኢህአዴግ በተግባር ለህውኃት ብሎም ለወሳኞቹ ባለሥልጣኖች ታማኝ ሆኖ መገኘት ሀኖ ያሟላሉ ተብሎ ታምኖባቸው የተሾሙ ወደ ህሊናቸው ሲመለሱ፣ ወይ ታማኝነታቸውን ሲያጓድሉ፣ አልያም እንደታሰቡት ሆነው ሳይገኙ ሲቀሩ በሙስና ወይንም በመተካካት ሰበብ ለእስር ሲዳረጉ ወይንም ሲገለሉ፣አለያም ከሥልጣን ዝቅ ሲደረጉ ድርጅታቸውም ሆነ ጎሳቸው ድምጽ አለማሰማታቸው የእርምጃውን ትክክለኛነት የጎሳ ሥልጣን ክፍፍሉን ጤናማነት የሚያረጋግጥ ተደርጎ ታስቦ ከሆነ ስህተት ነው፡፡
ድርጅቶቹ (ፓርቲዎቹ) ምንም አለማለታቸው አፈጣጠራቸውም ሆነ እድገታቸው ለዚህ የሚያበቃ ነጻነት የሌለቸው በመሆኑ ሲሆን ( የሁሉም ፈጣሪ ህውኃት ስለመሆኑ ፈጣሪውም ተፈጣሪውም በኩራት የሚናገሩት ነው) የጎሳቸው ዝምታ ደግሞ መጀመሪያም ውክልናቸውን አለመቀበሉ ሁለተኛም የሾማቸው አነሳቸው በሚል አይመለከተኝም ስሜት እንደሚሆን ይገመታል፡፡

ፕ/ር መድሀኔ ታደሰ በ1996 ዓም ከአንድ በሀገር ውስጥ ይታተም ከነበረ መጽሄት ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ «ብሔረሰቦች ራሳቸውን በራሳቸው ማስተዳደር አለባቸው ስትል በርግጠኝነት ራሳቸውን በራሳቸው ማስተዳደር አለባቸው፤አሁን በክልል ይሄ ነው ችግሩ፡፡ ከዚህ በላይ ግን ሙሉ በሙሉ ራሳቸውን ማስተዳደር ያልቻሉ ክልሎች ክልላቸውን እንኳን ቢያስተዳድሩ በቂ አይደለም፡በማዕከላዊ መንግሥት ጭምር በውሳኔ ሰጭነት ጭምር መሳተፍ ነበረባቸው፡፡ይህ በሌላበት ሁኔታ የብሔር ጭቆናን መሰረት ያደረገ ሥርዓት መሥርተህ ልትተገብረው ካልቻልክ ጭቆናውን በማባባስ የበለጠ ግጭት እንዲፈጠር ነው የሚያደርገው» በማለት የታሰበው በሚነገርለት ደረጃ እንኳን ተፈጻሚ አለመሆኑን ገልጸዋል፡፡

የአስተዳደር ክልልን በጎሳ የሹመት ድልድልን በጎሳ፣የፖለቲካውን ቅኝት በጎሳ፣ ማህበራዊም ሆነ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴን በጎሳ፣ ወዘተ መቃኘቱ የመጀመሪያው ችግር ሆኖ ይህንኑ በሚነገርለትና በህግ በተጻፈው አግባብ ተግባራዊ አለማድረግ ሁለተኛው ችግር ነው፡፡ በየቦታው በፖለቲካ ፓርቲ መሪነትም ሆነ በክልል አስተዳዳሪነት የሚቀመጡ ሰዎች አመኔታ የሚያጡት ብዙ የሚባልለትን እኩልነት በተጨባጭ ተግባራዊ ለማድረግ በአለመቻላቸውና እንወክለዋለን ከሚሉት ህብረተሰብ ይልቅ ታማኝነታቸውም አገልጋይነታቸውም ላስቀመጣቸው ሀይል መሆኑ ነው፡፡
ነብሳቸውን ይማረውና አቶ መለስ ሳይታሰብ በድንገት በሞት ሲለዩን አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ ወደ ጎን ሊገፉ የማይቻልበት ቦታ ላይ በመገኘታቸው ምክንያት ሙሉው ሥልጣን ባይኖራቸውም የጠቅላይ ሚኒስትርነቱን ቦታ ሲይዙ በህውኃት ሰፈር አሰረክባችሁ መጣችሁ በሚል ጥያቄ መነሳቱን ውስጥ አዋቂዎች በተለያዩ የመረጃ ማስተላለፊያ መንገዶች ገልጸውታል፡፡ በአቶ መለስ የሁለት አሥርት አመታት የሥልጣን ዘመን ያልነበረ የሶስት ምክትል ጠቅላይ ምኒስትሮች ሥልጣን የተፈጠረውም ይህንኑ የህውኃትን ጥያቄ ተከትሎ እንደሆነ ነው የተነገረ የተጻፈው፡፡
ሌሎቹ ድርጅቶች ነጻነታቸውን አረጋገጥው በየራሳቸው እግር መቆም ከቻሉ ተመሳሳይ ጥያቄ ሊያነሱ እንደሚችሉ አያጠያይቅም፡፡ ጥያቄውም ከፖለቲካዊነቱ ጎሰኛነቱ ስለሚያመዝን ለምላሽ ያስቸግራል፣ ውጪ ጉዳይ ምኒስትራችን በደቡብ ሱዳን እንዳይፈጠር ወደ ሰጉት የጎሳ ግጭትም ሊያመራ ይችላል፡፡ ዮሀንስ ገብረማሪያም የተባሉ ጸሀፊ በ1987 ዓም በጦቢያ መጽሔት ጎሰኞችና ጎሰኝነት ያሳፍራሉ ያስፈራሉ በማለት ባሰፈሩት ጽሁፍ «ጎሰኝነት ብዙውን ግዜ ሌሎች ጎሳዎች አደረሱብን የሚሉትን ይም ደርሶብናል ብለው የገመቱትን ጥቃት ለመመከት ወይም ደግሞ ሆን ብሎ ሌሎችን ለማጥቃት የሚውል የፖለቲካ መሳሪያ ሆኖ እያገለገለ ነው፡» ብለዋል፡፡ ጎሰኝነትን በሚያቀነቅኑ ወገኖቸ የሚካሄድ ቅስቀሳን አደገኛነትም ሲገልጹ «ይህ ቅስቀሳ አውቆ አበዶችን ብቻ ሳይሆን መሰሪነቱን ያልተረዱ ብዙ የዋህ ተከታዮችን ሊያስገኝና ሊያሳስትም ይችላል» ይላሉ፡፡
ዛሬ በአብዮታዊ ዴሞክራሲ ገመድ ተሸብበው ፣በማሌ አደረጃጀት ተቆላልፈው፣ በአንድ ለአምስት ተጠርነፈው ህውሀት በቀደደላቸው ቦይ ቢፈሱም አንድ ቀን ግድቡን ጥሶ አልያም መስመሩን ለውጦ ሊፈስ እንደሚችል ያን ግዜ ደግሞ ለቁጥጥርም ለድርድርም እንደሚያዳግትና ከፍተኛ ጥፋት ሊያደርስ እንደሚችል ሌላው ቢቀር በደቡብ ሱዳን ከሚታየው መገንዘብ ይቻላል፡፡ ስለሆነም መሪዎቻችን የደቡብ ሱዳንን ችግር ለመፍታት እየሸመገሉ ከሂደቱ ለራሳቸውም ቢማሩ መልካም ነው፡፡ አስተዋይ ከጎረቤቱ ይማራልና፡፡
የተዳፈነው እሳት ተግለጦ ከተቀጣጠለ፣በድርጅታዊ ቅርጫት ያስገቡት አፈትልኮ ከወጣ ማጣፊያው እንደሚያጥር፣ ነገሩ እንደሚከርና መዘዙ ብዙ ነገር እንደሚመዝ የደቡብ ሱዳኑ ጉዳይ ቅርብና ግልጽ ማሳያ ነውና አንማርበት፡፡
ስለሆነም ዛሬ የጎሳ ፖለቲካ ደቡብ ሱዳን ላይ ስጋት መሆኑ የታያቸው ውጪ ጉዳይ ምኒስትራችን አንድ ቀን እኛም ቤት አደጋ ሊሆን እንደሚችል በማጤን ፖለቲካችንን ከጎሳ ሰገነት ላይ ለማውረድ ቢሰሩ ለርሳቸው ክብር ለሀገርና ለሕዝብም ዘላቂና አስተማማኝ ሰላም ማስገኘት ቻሉ ማለት ነበር፡፡

ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ድርደር፣

ጠቅላይ ምኒስትራችን የወቅቱ የአፍረካ ህብረት ሊቀመንበር፣የቅርብ ጎረቤት ሀገር መሪ ወዘተ አንደመሆናቸው በደቡበ ሱዳን ግጭት አንደተቀሰቀሰ ፈጥነው ወደ ከቦታው በመድረስ ከፕሬዝዳንቱ ጋር በተነጋገሩበት ወቅት መፍትሄው ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ድርድር መጀመር እንደሆነ መናገራቸውን ከዜና ማሰራጫዎች ሰምተናል፡፡ ሀሳቡ የቀረበው ጥይት ከተተኮሰ ደም ከፈሰሰና አቅም ከተፈተሸ በኋላ በመሆኑ ያለቅድመ ሁኔታ የሚለው የተወሰኑ የሀገሪቱን ቦታዎች በመቆጣጠር አቅሙን በፈተሸው አማጺ በኩል ተቀባይነት አላገኘም፡፡ እንደውም ያቀረባቸው ቅድመ ሁኔታዎች በመንግስት በኩል በጎ ምላሽ ሊያገኙ ባለመቻላቸው ከሁለቱም ወገን ተደራዳሪዎችን አዲስ አበባ ማምጣት ቢቻልም ይህ ጥሁፍ ወደ ዝግጅት ክፍሉ እስከተላከበት ቀን ድረስ በግንባር ማገናኘት አልተቻለም፡፡

ጠቅላይ ማኒስትራችን ከዚህ ሂደት ሁለት ነገሮችን ይገነዘባሉ ብለን አንገምት፡፡ አንድ ያለምንም ቅደመ ሁኔታ ድርድር ለደቡብ ሱዳን ብቻ ሳይሆን ለእኛም ሀገር ችግር መፍትሄ መሆኑን ቢያምኑበትና ለተግባራዊነቱ አቅማቸውም ነጻነታቸውም የሚፈቅደውን ቢያደርጉ፡፡ ሁለት በሥልጣን ላይ ያለ ሀይል ከተቀዋሚዎቹ ጋር ለመነጋገርም ሆነ ለመደራደር ሸብረክ የሚለው ብረት አንስተው ዱር ቤቴ ሲሉ ብረት ያነሱትም አቅማቸውን ከፈተሹና ነጻ መሬት መያዝ ከጀመሩ በኃላ መሆን እንደሌለበት አቶ ኃይለማሪያም እየሸመገሉ ቢማሩ በአጭሩ የሥልጣን ዘመናቸው የዘለዓለም ክብር የሚያቀዳጃቸው ተግባር ፈጸሙ ማለት ነበር፡፡
ክቡር አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ ስመ ሥልጣኑን በመሀላ ከተቀበሉ በኋላ ሀላፊነታቸው የቀድሞውን ጠቅላይ ምኒስትር የመለስን ሌጋሲ ማስቀጠል መሆኑን በመግለጻቸው ሰላማዊ ትግል ከመረጡት ጋር ለመነጋገርም ሆነ ኢህአዴግን ማነጋገር በሚገባው ቋንቋ ነው ከሚሉት ጋር ለመደራደር የሚቀርቡ ጥያቄዎችም ሆኑ የተሞከሩ ጅምሮች የማይታለፉ ቅድመ ሁኔታዎች እየቀረቡ ተሰናክለዋል፡፡ ትናንት ዛሬ እንዳልሆነ ሁሉ ነገም ዛሬ አይሆንምና ዛሬ የገፉት የንግግርም ሆነ የድርድር ጥያቄ ነገ ፈልገው ለምነው የማያገኙት ሊሆን ይችላልና ወዳጅ ሳይርቅ ጉልበት ሳይከዳ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ንግግርም ደርድርም መጀመር ለሁሉም ይጠቅማል፡፡

ይህ ጽሁፍ በኢትዮ ምህዳር ጋዜጣ የታህሣሥ 30/2006 ላይ ወጥቷል።

በዓለም አቀፍ ደረጃ ሚሊዮን ለሚቆጠሩ ሴቶች አርዓያ የሆነች ኢትዮጵያዊት ኒይሮ-ሰርጀን –ዶክተር እሙን አብዱ

$
0
0

ከሳዲቅ አህመድ

ወጣቷ ኢትዮጵያዊት ዶክተር ድንቅ የቀዶ-ጥገና ስራዎችን እንደምታከናዉን በአሜሪካ የመገናኛ ብዙሗን ተዘግቧል። እርሷ የሙያ ግዴታዋን ትወጣ እንጂ ያደረገቻቸዉ የቀዶ ጥገናዎች አስደናቂ ናቸዉ ብላ አትገምትም፤ ግን ቤተሰቦቿ እዉነታዉን ያረጋግጣሉ። ኒይሮ-ሰርጀኗ ዶክተር እሙን አብዱ ባለፈዉ አመት መገባደጃ ላይ ያደረገችዉ የቀዶ ጥገና ሁሉንም ያስደነቀ ነበር።

ዶ/ር እሙን አብዱ

ዶ/ር እሙን አብዱ


ነፍሰጡር ባለቤቱ ለወሊድ የተቃረበችዉ ኬኔት ዊሊያም የሐያ አምስት አመት ወጣት ነዉ። የአሪዞና ግዛት ነዋሪ የሆነዉ ኬኔት በገጠመዉ ሐይለኛ የጭንቅላት ህመም ሳቢያ የመዳን ተስፋዉ ሐምሳ በመቶ ነዉ ተብሎ ነበር። የሚወለደዉን ህጻን ድምጽ የመስማትም ህጻኑንን የማየትም እድል እንዳልነበረዉ ተነግሯል። ይህ አሜሪካዊ ወጣት እድሉ ሆኖ የዶክተር እሙን አብዱ ታካሚ ይሆናል፤ እሙንም ቀዶ ጥገናዉን በተገቢዉ መልኩ ታከናዉናለች። ቀዶ ጥገናዉ በፈጣሪ እርዳታ የተሳካ ይሆንና ኬኔት ዊሊያም የሚወለደዉን ልጅ ድምጽ መስማት ብቻ ሳይሆን ለማቀፍም በቅቷል።

ምን ያህል ኢትዮጵያዉያን ኒይሮ-ሰርጀኖች እንዳሉ መረጃዉ ለግዜዉ ባይኖረንም፤ እሙን አብዱ ካሉት ጥቂት ኒይሮ-ሰርጀኖች አንዷ ናት። እሙን ለብዙ ኢትዮጵያዉያን ሴቶች ሁሉንም ማድረግ እንደሚቻል”እሙን” መሆኑንን በተምሳሊትነት የምታሳይ የሰሜን አሜሪካ ኢትዮጵያዉያን-አሜሪካዉያን ማህበረሰብ አባል ናት። ምን አልባትም እናት-አገራችን ዉስጥ በኒይሮ-ሰርጀን የቀዶ ጥገና እጦት አደጋ ላይ ለሚወድቁ ኢትዮጵያዉያን ወገኖቿ ደራሽ ትሆን ይሆናል።

(ሰበር ዜና) እነ ሌንጮ ለታ ኢትዮጵያ ሊገቡ ነው

$
0
0

(በአንድ ወቅት በዘ-ሐበሻ ድረገጽ ወጥቶ የነበረው ሌንጮን እና ፕሮፌስር ይስሃቅን በሚኒያፖሊስ በድርድር ስብሰባ በኋላ የተነሱትን ፎቶ የሚያሳይ ምስል)

(በአንድ ወቅት በዘ-ሐበሻ ድረገጽ ወጥቶ የነበረው ሌንጮን እና ፕሮፌስር ይስሃቅን በሚኒያፖሊስ በድርድር ስብሰባ በኋላ የተነሱትን ፎቶ የሚያሳይ ምስል)


(ዘ-ሐበሻ) “ከእንግዲህ የቀድሞው መንገድ አይሰራም” በሚል የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግንባርን የመሰረቱት የቀድሞ የኦነግ አመራሮች እነኦቦ ሌንጮ ለታ ኢትዮጵያ ሊገቡ መሆኑ ተሰማ፡፡

የዘ-ሐበሻ የሚኒያፖሊስ ምንጮች እንዳስታወቁት ከዚህ ቀደም ኦሮሚያ ክልልን ለማስገንጠል ይንቀሳቀሱ ከነበሩ ሃይሎች ጋር የነበሩት እነ ኦቦ ሌንጮ ለታ የኦሮሞ ዲሞክራሲያዊ ግንባርን በሚኒሶታ ከመሰረቱ በኋላ በሃገር ቤት ገብተው ለመታገል መወሰናቸውን አስታውቀዋል።

ከጥቂት አመታት ወዲህ ፕሮፌሰር ኤፍሬም ኢስሃቅ እነ ሌንጮ ለታን ለማስማማት ወደሚኒያፖሊስ ከ2008 ጀምሮ በተደጋጋሚ ሲመላለሱ እንደነበር የዘ-ሐበሻ ምንጮች በፎቶ ግራፍ ጭምር የተደገፈ መረጃ ያቀረቡ ሲሆን “ከ እንግዲህ የቀድሞው መንገድ አይሰራም” የሚል አቋም የያዘው ይኸው የሌንጮ ለታ ግሩፕ የፕሮፌሰር ኤፍሬም ይስሃቅን ምልጃ ተቀብሎ ወደ ኢትዮጵያ በመግባት በቀጣዩ ምርጫ ለመወዳደር እንደሚዘጋጅ የዘ-ሐበሻ ምንጮች ገልጸዋል።

የሌንጮ ለታ የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግንባር ወደ ኢትዮጵያ በቅርብ ቀን እንደሚገባ ያስታወቁት እነዚሁ ምንጮች፤ በተለይ በአሁኑ ወቅት በርካታ የኦሮሞ ምሁራን፣ የሰብ አዊ መብት ተከራካሪዎች የመብት ጥያቄ አንስተው በአሸባሪነት በታሰሩበት ወቅት በዴሞክራሲያዊ መንገድ ኢሕ አዴግን እንታገላለን ብለው መወሰናቸው በሚኒሶታ የሚገኙ በርካታ ኦሮሞ ኢትዮጵያውያንን እያነጋገረ እንደሚገኝ በተደጋጋሚ መዘገቡ ይታወሳል።

ለትውስታ እነዚህን ታሪካዊ ፎቶዎች እንጋብዝዎ

olf 2

olf 3

olf 4

olf 5

olf 6

Olf

የአዘጋጁ መልዕክት፡ ዘ-ሐበሻን እየተፈታተኑ ያሉ ሁኔታዎች

$
0
0

የተከበራችሁ የዘ-ሐበሻ ድረገጽ ጎብኚዎች!

በቅድሚያ ዘ-ሐበሻን የወቅታዊ መረጃዎች መገኛ አድርጋችሁ በመምረጣችሁና ሁልጊዜም ስለምትጎበኙን ምስጋናችን የላቀ ነው። ዘ-ሐበሻ ከዕለት ወደ ዕለት ተፈላጊነቷ እየጨመረ መሄዱን በየቀኑ ከምናገኘው ትራፊክ ለመረዳት ችለናል። በዚህም ደግሞ እናንተን ዘ-ሐበሻን ታማኝ የዜና ምንጭ አድርጋችሁ በመምረጣችሁ እናመሰግናችኋለን።

የዓለም አቀፍ የድረገጽ ጎብኚዎችን መረጃ ሰጪ ድርጅት (alexa.com) ዘገባ መሠረት ዘ-ሐበሻ በአሁኑ ወቅት በርካታ ጎብኚዎች ካሉት ድረገጽ መካከል አንዱና አንደኛው ነው።

የአሌክሳን የሶስት ወር የትራፊክ ብዛት ካየን በኢትዮጵያ ጉዳይ ነፃ ሆነው ከሚዘግቡ ሚዲያዎች መካከል፦

zehabesha.com ከዓለም 30.459 ደረጃን በመያዝ አንደኛ - በኢትዮዽያ ደግሞ 55 ደረጃ ላይ ትገኛለች
Ethsat.com ከዓለም 35,243 ደረጃን በመያዝ 2ኛ
Ecadforum.com ከዓለም 39,188 ደረጃን በመያዝ 3ኛ
ethiomedia.com ከዓለም 47,852 ደረጃን በመያዝ 4ኛ
Ethiopianreview.com በ54,166 ደረጃን በመያዝ 5ኛ

zehabesha (ይህን ለማረጋገጥ የዌብሳይቶችን ስም በመጻፍ http://www.alexa.com/siteinfo በመግባት ማረጋገጥ ይቻላል)

ዘ-ሐበሻ ቀዳሚውን ሥፍራ የያዘችው በ እናንተ በአንባቢዎቿ ብርቱ ጉብኝት እንደሆነና እኛም 24/7 ድረገጻችንን በወቅታዊ መረጃዎች ማጨቃችን መሆኑ አይተባበልም።

ግን ዘ-ሐበሻ በአሁኑ ወቅት እንደምታቀርበው አገልግሎት ከጎብኚዎቿ የሚገባውን ድጋፍ እያገኘች አይደለችም። ከኢሕአዴግ መንግስት ግን ጡጫዋን እየተቀበለች ቀጥላለች። ባለፉት 24 ሰዓታት ያለን ሰርቨር አንድ ብቻ በመሆኑ ሰርቨራችን መቋቋም ከሚችለው በላይ ጎብኚ ስላለ ድረገጻችን እስከ አገልግሎት አለመስጠት ደርሶ ነበር። በዛ ላይ የወያኔ/ኢህአዴግ መንግስት ከኢትዮቴሎኮም፣ ከጀርመን፣ ከኖርዌይና ከቤልጂየም ተደጋጋሚ ትራፊኮችን በመላክ ድረገጻችን እንዲጨናነቅና ሰዎች እንዳይጎበኙ ለማድረግ የሚያደርገውን የማሰላቸት ተግባር ለመቋቋም ሁለተኛ ሰርቨር እንደሚያስፈልገን ባለፈው ጊዜ ገልጸን ነበር። በሚሊዮን የሚቆጠር የድረገጽ ጎብኚ እያለን ለአንድ ወር የዘ-ሐበሻን የመርጃ ጊዜ ብለን አውጀን ያሰባሰብነው ገቢ $60 ብቻ መሆኑን ስንነግራችሁ እኛም እየተሳቀቅን ነው።

ዘ-ሐበሻን በተለያዩ መንገዶች እየረዱ ያሉ ሰዎች አሉ። እነርሱ እንዴት ዘ-ሐበሻን እየረዱ እንዳሉ ጠይቁ። ሆኖም ግን ከ125 ሺህ በላይ የፌስቡክ ተከታይ ያለው ዘ-ሐበሻ፣ በሚሊኖች የሚቆጠር ጎብኚ ያለው ዘ-ሐበሻ ለውጥ እንዲያመጣ የምትፈልጉ ከሆነ ሁለተኛውን ሰርቨር እንድንገዛና የሳይበር ጦርነት የገጠመውን ወያኔን እንድናሸንፍ ልትተባበሩን ይገባል።

እኛ ያለን አቅም ውስን ነው። አቅማችንን እስኪዳከም ድረስ ነፃ፣ ሚዛናዊና፣ ወቅታዊ መረጃዎችን ለሕዝባችን ማድረሳችን አይቀሬ ነው፤ ሆኖም ግን በርቱ የምትሉን ከሆነ በርቱ የምትሉበትን መንገድ መቀየስ ይኖርባችኋል። ላለፉት 18 ሰዓታት ዘ-ሐበሻ ልትነነበብ ያልቻለችበት ምክንያትም ይኸው ነው።

ዘ-ሐበሻን በገንዘብ ለማገዝ ይኸው ሊንኩ፦




እውነት ያሸንፋል!

የግንቦት 7 ወቅታዊ መልዕክት፡ “ከተገኙት አስከሬኖች ግድያው የቅርብ መሆኑን ማረጋገጥ ይቻላል”

$
0
0

አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ፈረንሳይ ለጋሲዮን በሚገኘው የክብርዘበኛ ጦር ካምፕ ውስጥ ማንነታቸው ያልታወቁ የ6 ዜጎች አስከሬን ለመንገድ ሥራ በተሠማሩ ቆፋሪዎች አማካኝነት መገኘቱ የሰሞኑ አሳዛኝ ዜና ነው።
ginbot 7
አንድ አይነት ቀለም ባላቸው ብርድ ልብሶች ተጠቅልለው ከተገኙ 6 አስከሬኖች የመጀመሪያዎቹ ሁለት ሰለባዎች ታስረውበት የነበረው የእጅ ሰንሰለታቸው እንኳ እንዳልወለቀና ከተቀሩት የአንዱ እጆች ደግሞ የፍጥኝ ወደ ኋላ እንደታሰሩ መገኘታችው ግድያው በቅርብ እንደተፈፀም አንዱ አስረጂ ነው።

በእንዲህ አይነት ጭካኔ የተገደሉ ዜጎች አስከሬን መገኘት በመንግሥት ተብየው አካል ካለመገለጹም በላይ ግቢውን በማስተዳደር ላይ የሚገኘው 3ኛ ክፈለ ጦርም ሆነ በግብር ከፋይ ገንዘብ የሚተዳደሩ መገናኛ ብዙሃን እስከዛሬ አንድም ቃል መተንፈስ አለመፈለጋቸው ጉዳዩን እጅግ የሚያሳዝን ብቻ ሳይሆን የሚያስገርምም አድርጎታል። ይባስ ተብሎም በመንገድ ሥራ ቁፋሮው የበለጠ አስከሬን ሊወጣ ይችላል በሚል ስጋት አካባቢው በፖሊስ እንዲታጠር ከተደረገ በኋላ ሥራውም እንዲቋረጥ ተደርጓል።

በፖለቲካ መስመር ልዩነት ምክንያት ደርግ ያለ ርህራሄ የጨፈጨፋቸውን ከመቃብር እያወጣ ዘመድ አዝማድ በማላቀስ የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ሲዳክር የኖረ አገዛዝ በእንዲህ አይነት አሳዛኝ ሁኔታና አጋጣሚ የተገኘውን የጅምላ አስከሬን አይቶ አንዳላየ ለማለፍ መሞከሩ ለምን ይሆን?

mekabir
አብዛኛው የአዲስ አበባ ነዋሪ እንደሚያስታውሰው የክብር ዘበኛ ጦር ካምፕ በመባል የሚታወቀው የጃን ሜዳ 3ኛ ክፍለ ጦር ግቢ ድህረ ምርጫ 97 ወያኔ ለጅምላ እስር ቤትነት ከተጠቀመባቸው የማጎሪያ ቦታዎች አንዱ ነበር። ከዚያን ጊዜ በፊትና በኋላም ቢሆን ካምፑ በወያኔ ጠላትነት ተፈረጀ በጸጥታ ሠራተኞች ከታገቱ በኋላ አድራሻቸው እስከዛሬ ተሰውሮ ላሉ በርካቶች በምስጢር እስርቤትነት በማገልገል ላይ ከሚገኙ ወታደራዊ ካምፖች አንዱ እንደሆ ይታወቃል።

ዘመድ አዝማዶቻቸው ይመለሳሉ ብለው ሲጠብቋቸው ሳይመለሱ እንደወጡ የሚቀሩ በርካታ ዜጎች አሉ። በእንዲህ ሁኔታ ወጥተው ከቀሩ መካከል ከሰሞኑ የስድስቱ መቃብር በአጋጣሚ ተገኝቷል። የተገነዙበት ብርድ ልብስ ይነትብና ምንም ዓይነት ብልሽት ሳይደርስበት መገኝቱ ግዲያው በህወሃት ዘመነ መንግስት ስለመፈፀሙ ጥሩ ማስረጃ ነው። ለህወሃት ሰው መግደል ሥራ እንጂ ወንጀል አይደለም። በህወሃት ነፍሰ ገዳይ ይሞገሳል ይሾማል እንጂ አይወቀሰም አይጠየቅም። የስድስቱ ስዎች አስከሬን ሲገኝ መንግስትነኝ የሚለው ህወሃት አይቶ እንዳላየ መሆን ብቻ ሳይሆን ሌሎች አካላትም የሥፍራውን ሚስጢር እንዳያዩ ከልክሏል።በቁጥጥሩ ሥር ያሉ መገናኛ ብዙሃንም ዜናውን እንዳይናገሩ ታግደዋል። ህወሃት ከሚሰራቸው አስገራሚ ወንጀሎች መካከል አንዱይሄው ነው። ይሄ ግድያ በሌላ አካል ተፈፅሞ ቢሆን ኑሮ በረከት ስምዖንና እና ሺመልስ ከማል እየተፈራረቁ ያደነቁሩን ነበር።ይሄ የራሳቸው የእጅ ሥራነውና አይነገርም። የሄንንም የሚናገር እንደ ኢሳት ያለ ነፃ ሚዲያ ካለም ይታፈናል። አሸባሪም እየተባለ ይፈረጃል።

ግንቦት ሰባት የፍትህ የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ እነዚህ ዜጎች በህወሃት ተግድለው እንደተጣሉ ያምናል። ውሎ አድሮ እውነቱ እስከሚወጣ ድረስ ግን ዜጎች በሙሉ ይሄን ግድ በተመለከተ መረጃ የመሰብሰብና የማሰረጫት ሥራችውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ እናሳስባለን። ይሄን ወንጀል የፈፀሙ አካላት መጠየቅ አለባቸው። የዜጎች ደም እንዲሁ በከንቱ ፈሶ መቅረት የለበትም።

ለኢትዮጵያ ህዝብ መብትና ጥቅም እንታገላለን የሚሉ የፖለቲካና የስቪክ ድርጅቶች እንዲሁም ለሰው ልጆች የሰብአዊ መብት የሚሟገቱ ሁሉ የተገኘው አስከሬን በአስቸኳይ ተመርምሮ ማንነታቸው ለቤተሰቦቻቸውና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው እንዲገለጽ፤ ተጨማሪ አስከሬን ሊገኝ ይችላል በሚልስጋት የመንገድ ቁፋሮውን ከሰዎች እይታውጪ ለማካሄድ እንዲቋረጥ የተደረገው ሥራ ለህዝብ እይታ ግልጽ በሆነመንገድ በአስቸኳይ እንዲጀመር የመጠየቅ ሃላፊነታቸውን እንዲወጡ ግንቦት 7 ያሳስባል::
mekabir 1
በዚህአጋጣሚ ወያኔ ሥልጣን ከተቆጣጠረበት ጊዜጀምሮ በሱማሌ፣ በጋምቤላ፣ በአዋሳ፣ በጎንደር፣ በአዲስ አበባና ሌሎች የአገራችን ክፍሎች በጠራራ ጸሃይ ካስጨፈጨፋቸው በተጨማሪ በፖለቲካ እምነታቸው ምክንያት ታግተው በየእሥርቤቱ የተወረወሩትንና ከታገቱበት ዕለት ጀምሮ እስከ ዛሬ የደረሱበት ያልታወቁ ወገኖቻችንን ዝርዝር በአስቸኳይ ያሳውቅ ብለን አንመክረውም።እኛ ግን ህወሃት የደበቀውን ወንጀል ሁሉ ህዝብ እንዲያውቀው ለማድረግ ያለምንም ማቅማማት ጠንክረን እየሰራን ነው። መንግስት ነኝ ብሎ በሥልጣን ላይ የሚወጣ ማንኛውም አካል የህዝብ አገልጋይ እንጂ ነፍሰገዳይ እንዳይሆን የጀመርነው ትግል ተጠናክሮ ይቀጥላል።

እንግዲህ ህወሃት በህዝባችንና በአገራችን ላይ የሚፈጽመውን ሰቆቃ ለማስቆም ግንቦት 7 የጀመረውን የነጻነት ትግል አጠናክሮ እንደሚቀጥል እያስታወቅን እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ እንዲህ በየቦታው ተገድሎ ከመጣል ራሱን ለመታደግ ሲል የነፃነቱ ትግል አካል እንዲሆን ጥሪያችንን አሁንም ደግመን እናቀርባለን::

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !!


አዲስ ዓመት ለጋራ ራዕይ –በአበራ ሽፈራው /ጀርመን/

$
0
0

በአበራ ሽፈራው /ጀርመን/

በፈረንጆቹ ወይም እንደ ጎርጎርያን አቆጣጠር 2013 ዓ.ም  በኢትዮጵያና በኢትዮጵያውያን ላይ በአገር ውስጥም ሆነ በውጭው አለም ታላላቅ አሳዛኝና አስቸጋሪ ሁኔታዎች ግጥመውን አልፏል፡: አንዳንዴም ይህ ዓመት ባልነበረ የሚያስብል ነበር :: እንኳን አለፈ ::

ኢትዮጵያውያን በአገር ውስጥ ብዙዎች ለእስር የተዳረጉበት፣ ፍርደገምድል ፍርዶች በፍርድ ቤቶች የታዩበት፣ የፖለቲካ እስረኞች በከፍተኛ ሁኔታ የተበራከቱበት፣ እስር ቤቶች በፖለቲካ አቋማቸውና አስተሳሰባቸው ብቻ በህወሓት ሰዎች አይን ውስጥ በገቡ የተሞሉበት ፣ የነጻው ፕሬስ ከመቼውም ጊዜ በላይ በህወሓቶች ጥቃት የደረሰበት ፣ የአማራ ተወላጆች በዘረኞችና ግልጽ በወጣ የዘር ጥቃት በሚፈጽሙ በህወሃቶች ባለሟሎች እቅድ ማፈናቀል የተደረገበት በዚህም ምክንያት ብዙዎች ለመከራና ለችግር የተዳረጉበት፣ አጥፊው የህወሓት ማኔፌስቶም አሁንም ትግበራውን ይቀጥላል ማኔፌስቶው ሳይሆን ምስጊን የቤንሻንጉልና ጉምዝ ሰዎች በትግበራ ዙሪያ እንደደቡቡ በተጠና መልኩ ማፈናቀሉን ባለማድረጋቸውና ህወሓቶችን በአደባባይ ያጋለጠ ድርጊት በመሆኑ ለቅጣት ተዳረጉ፣ አዛዡ አሳሪ ታዛዡ ታሳሪ ሆነና ድራማው ተጠናቀቀ በዚሁ ክፉ ዓመት : : በተለይም የሙስሊም ወንድሞቻችንና እህቶቻችን የሃይማኖት ነጻነት ትግልን በሃይል ለመጨፍለቅ ታስቦ ብዙዎች በአደባባይ የተገደሉበት፣ የታሰሩበትና እጅግ አስከፊ ግፍ የተፈጸመበት ዓመት ነበር በአገራችን ኢትዮጵያ::

ይኸው 2013 የህወሓት ዘረኛ ቡድን የአገሪቷን ወታደራዊ ኃይል ለመቀራመት በድርጊቱ ጠንሳሽና መሃንዲስ በነበረው መለስ ዜናዊ እቅድና ራዕይ መሰረት ሁሉንም ወታደራዊ ሃይል በህወሓቶች ለማስያዝና የአፈናውን ሥርዓት ለማጠናከር ሲባል በየትኛውም የአገሪቷ ዘመናት ባልታየ መልኩ ከፍተኛ የጀነራልነት ማዕረጎችና ሌሎች ወታደራዊ ሥልጣኖችን 99% በሚባል መልኩ የህወሓትን የበላይነት ለማረጋገጥና ስርዓት የለቀቀውን አገርን የመምራት አቅም ማጣት ለማስጠበቅ ሲባል ምንም ወታደራዊ አቅምና ትምህርት ለሌላቸው ሰዎች ብዛት ያለው የጀነራልነት ማዕረጎችን በመስጠት በአለምና በአገሪቷ  ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ የሹመት ድግስ የተደገሰበት ዓመት በመሆን ተመዝግቧል ::

በዚሁ በ2013 የሰላማዊ ትግል አራማጅ ፓርቲዎች በአገር ውስጥ በተለይም የአንድነት ፓርቲ፣ የሰማያዊ ፓርቲና የመድረክ አመራሮችና አባሎቻቸው ለከፍተኛ ጥቃት የተጋለጡበት፣ በየምክንያቱ አባሎቻቸው ለእስር፣ ለድብደባና ለእስራት የተዳረጉበት ጊዜ በመሆን የሥርዓቱ አስቸጋሪነትን የተመለከትንበት ዓመት በመሆን አልፏል :: የተቃዋሚው ሃይል ከገዢው የማፍያ ቡድንም ጋር  ግልጽ የሆነ ትንቅንቅ ውስጥ የገባበትና የህወሓት ገዢ ቡድንም በከፍተኛ ትዝብት ላይ የወደቀበት ጊዜ በመሆን የተሰናበተን ዓመት ሲሆን በተቃዋሚው ላይ የደረሰው መከራ ግን ከመቼውም ጊዜ በላይ የሆነበት  ዓመት ለመሆን በቅቷል ::

አገራችንና ህዝቦቿ በእነዚህ ሙሰኞችና በዝባዦች እጅ ከወደቀችበት ጊዜ ጀምሮ ፍጹም ባልታየ መልኩ ጥቂቶች እየበሉና እየጠጡ የሚኖሩባት ሌሎች ወይም አብዛኛው ኢትዮጵያዊ ለፍጹም የኑሮ ውድነት የተጋለጠበት ዓመት ከመሆኑም በላይ በኑሮው ውድነት ምክንያትም ህዝቡ ለከፍተኛ የኑሮ ምስቅልቅሎሽ ተዳርጎና ለከፍተኛ ስደትም በመዳረግ በልዩ ልዩ ቦታዎች የሚደርስበት የስደት መከራና ሞት ቀላል አልነበረምና አብዛኛው ህዝቡ ችግሩን ተጋፍጦ መፍትሄ የሚያመጣለት አጥቶ አምላክን በመማጸን ያሳለፈበት አመት በመሆን አልፏል :: ይሁንና ህወሓቶችና ባለሟሎቻቸው ግን በየምክንያቱ ጮማ እየቆረጡና ውስኪ እየተራጩ ዓመቱን ሲያሳልፉ መክረማቸውንና በተለያዩ አገራት ያሸሿቸው የገንዘብም መጠን ቀላል እንዳልሆነና ከሟቹ መሪያቸው ጀምሮ እስከ ትልልቅ ሹማምንቶቻቸው ድረስ የአገሪቷን ገንዘብ ለመበዝበዛቸው የውጭ ሚዲያዎችና እራሱ ኢቲቪ ሳይቀር ተገዶ “ሙሰኞች ነን” ለማለት የሞከሩበት አመት ሆኖ ተመዝግቧል :: ይሁንና ከዚሁ ከሙስና ጋር ተያይዞ ሙሰኛ ጋኖችን ሳይሆን ሙሰኛ ገንቦዎችን በመስበር ሲቀልዱ የታዩበት ዓመት ነበር :: ከዚህም የተረዳነው የጠገቡ ሙሰኞች ያልጠገቡ ሙሰኞችን ሲያጠቁ ተመለከትን ::

በዚሁ ባሳለፍነው የፈረንጆች ዓመት ህወሓት በታሪክ አጋጣሚ ከሱዳን ጋር ባለው የጥፋት ቁርኝት አገርን ለባእዳን አሳልፎ በመስጠት የሚታወቀው ሥርዓት ከኢትዮጵያ ድንበር ሰፊውን ግዛትና ለም የሆነውን የአገሪቷን መሬት ለሱዳን ለመስጠት ውሎችን ለመፈራረምና ለዘመናት ደም እየተከፈለበት የኖረን የአገሪቷን መሬት አሳልፎ ለመስጠት የተዘጋጀበትና ህወሓት ምን አልባትም ኢትዮጵያዊ ነኝ ብሎ የሚያስብ ቡድን እንኳን ሆኖ ቢገኝ በአገሪቷ ታሪክ በክህደት የሚጠየቅበትን ሁኔታ ያስመዘገበበት አመት ሆኖ ከመመዝገቡም በላይ ኢትዮጵያ ከመቼውም ጊዜ በላይ ከአሰብና ከሌሎች በህወሓት ምክንያት ደም ካፋሰሱ የኢትዮጵያ ድንበሮች በተጨማሪ አሁን ደግሞ በዚህ ዘመን ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ አገርን ለመሸጥ ሲደራደሩ የከረሙበት ዓመት በመሆን ተመዝግቧል ::

የብዙዎች የኢትዮጵያ ሱማሌዎችና የአፋር ህዝቦች ደምም በህወሓት ወታደሮች የፈሰሰበትና ህወሓቶች በሌሎች ዓለም ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ግፍ የፈጸሙበትን ማስረጃ የቀረበበት፣ የሰብዓዊ መብት ጥሰት መፈጸማቸውንና ማስፈጸማቸውን የሚያሳዩ ማስረጃዎች የተገኙበትና ያንንም ለማጠናከር ትልቅ ግልጽ ዘመቻ የተከፈተበት ዓመት በመሆን በአውሮፓዊቷ አገር በሲውዲን አገር እንቅስቃሴ የተጀመረበት ዓመት በመሆንና ከዚሁ ጋር ተያያዥ የሆኑ ጉዳዮችን ለማጠናከር እንቅስቃሴ የተጀመረበት ዓመት በመሆንም ይታወሳል 2013 ::

“አልጠግብ ባይ ሲተፋ ያድራል ” እንዲሉ ዘረኛውና አንባገነኑ የህወሓት መሪ ለ21 ዓመታት ለብቻው ይዞት የነበረው የጭቆና ቀንበር ለዘለዓለም ወደዚች ምድር ላይመለስ በሞት በመሰናበቱ ምክንያት አገሪቷን ለከፍተኛ ችግርና አዳጋች ሁኔታ አጋልጧት እንደሄደና ህወሓትንም እርቃኑን አስቀርቶት ባዶ ቡድን መስርቶ የነበረ ለመሆኑ ማስረጃ መሆኑ እስኪታይ ድረስ ተተኪን ለመፍጠር እንኳን እንዳይቻል እያስፈራራ የፈጠረውና የገነባው ሥርዓት ለመሆኑ በግልጽ እስከሚታይ ድረስ በህወሃቶች መካከል ብቻ ሳይሆን በተለጣፊዎቹ የህወሃት ኢህአዴግ ፓርቲዎች ጭምር የዕርስ በርስ ትርምስ የተፈጠረበትና አገሪቷን የሚመሩ ግማሽ ደርዘን ሊጠጋ ትንሽ ቁጥር የቀረው የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሮችን በመያዝ የተመዘገበችም አገር በመሆንና ኢትዮጵያውያንን በማስገረም ያለፈ ዓመት ሆኖ አልፏል ይኸው 2013 ጉደኛ ዓመት ::

ይኸው 2013 በአባይ ግድብ ሰበብ ከመላው ኢትዮጵያና ከመላው ዓለም ከሚገኙ ኢትዮጵያውያን ኪስ የህወሓት ቀማኞች ገንዘብ የሰበሰቡበት፣ በግዳጅ የነጠቁበትና ገንዘባቸውን ለቀማኛ ቡድን ለመስጠት ያልፈለጉ በውጭው አለም የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ደግሞ የአባይን ግድብ እንዲገደብ ቢደግፉም በብዝበዛ፣ በሙስናና በመስረቅና የሃገርን ሃብት በውጭው ዓለም በሚገኙ ባንኮች በማስቀመጥ የሚታወቁትን የህወሓት የማፍያ ቡድንን ከአባይ በፊት ሰብዓዊ መብት እንዲያከብሩ በመጠየቅ፣ መለስና ሌሎች የህወሓት ሰዎች በውጭ ያከማቿቸው ገንዘቦች አንድ አባይን አይደለም ብዙ አባይን ይገነባሉና አውጡና በአገራችሁ አውሉት እያሉና ሌሎች ተመሳሳይነት ያላቸውን ሃሳቦች በማንሳትና በመቃወም በመላው ዓለም ህወሓት የቀለለበት ዓመት ነበር 2013 በእርግጥም ሕወሓት ቀድሞውንም ቢሆን በኢትዮጵያ ህዝብ ፊት የቀለለ ለመሆኑ እራሱ ህወሓትም ያውቀዋል ::

በዚሁ በ2013 በአገራችን በተለይም በጋምቤላ ክልል ሰፊ የመሬት መቀራመት የተፈጸመበትና ከፍተኛ ተቃውሞም በዚሁ ዙሪያ የተደረገበት ዓመት ከመሆኑም በላይ የጋምቤላ ነዋሪ ወገኖቻችንም በተወለዱበት፣ በአደጉበትና ተፈጥሮና ትውልድ ያስረከባቸውን መሬት በህወሓት ቀማኞች በአደባባይ በሃይል የተነጠቁበት ዓመት ነበር :: በሌሎች ክልሎች የገጠር ቦታዎች ብቻ ሳይሆን በከተማ ቦታዎችም ዙሪያ ግልጽ ቅሚያ የተፈጸመበትና ህወሓትን ተው የሚለው ጠፍቶ ያሻውን ያደረገበት ዓመት ነበር ::

የህወሓት አንዱ የመበዝበዣ ተቋም የሆነው የመከላከያ ሚንስቴር መስሪያ ቤትና ተያያዥ መምሪያዎችና የወታደራዊ መዋቅሮች በአገሪቷ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ በአንድ ዘር ስር መውደቁ የታወቀ ቢሆንም የአገሪቷ ሃብት በዚሁ ተቋም በነዚሁ በህወሓት ጀነራሎችና ከፍተኛ መኮንኖች እንደሚበዘበዝ ግልጽ እየሆነ ባለበትና ወቅትና ይህንንም ችግር ለማስቆም የተለያዩ አካላት ጥያቄ ማንሳት በጀመሩበት ወቅት ማንም ምንም አያመጣም ያሉ እስኪመስል ድረስ መከላከያ ኦዲት አይደረግም የሚል ሃሳብ መነሳቱና ጉዳዩ የህግ ከለላ እንዲያገኝ ለማድረግ ጥረት ማድረጋቸው የታየበትና ጉዳዩ በግልጽ እንደሚያሳየው ብዝበዛው በህግ እንዲደገፍ አዋጅ ያስነገሩበት ዓመትም ነበር በእርግጥም አይን ያወጣ ዝርፊያ ለመቀጠል ከፍተኛ መሰረት የተጣለበት ነበር ይህ ክፉ ዓመት:: አይ 2013 ጉደኛ ዓመት ::

የህዝቡን የፍትህና የነጻነትን ጥማት ይልቁንም ለመቀልበስና የህወሓትን ብዝበዛና ጭቆናን ለመቀጠል በታሰበ መልኩ “1 ለ 5″ የሚልን የአፈና መዋቅር ለመተግበር ከፍተኛ ርብርብ የተደረገበትም ዓመትም ነበር::

በሌላ በኩል  በዚሁ አስከፊ ሥርዓት ምክንያት በዓረቡ ዓለም ተበትነው የሚኖሩና በተለይም በሳውዲ አረቢያ በልዩ ልዩ መንገድ ወጥተው ተቀጥረው የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ላይ በደረሰው ችግርና ሰቆቃ ምክንያት ብዙው ኢትዮጵያዊ በዓለም ህዝብ ፊት በዕንባ የተራጨበትና አምላክንም የተማጸነበት ዓመት ሆኖ ነበር :: በዚህ ምክንያት ብዙ ኢትዮጵያውያን ውስጣቸው ያዘነበት ዓመት ነበር::

 

ይህም ሆኖ ግን የኢትዮጵያ ህዝብ ከመቼውም ጊዜ በላይ ህወሓትን ለመጋፈጥና በግልጽ መስዋዕትነት ለመክፈል የቆረጠበት፣ የሠላማዊ ትግል አራማጆችም ትግሉን በተለያዩ አቅጣጫዎች ያደረጉበትና የህወሓትን ማንነት በማሳወቅ ዕርቃኑን እንዲቀር ያደረጉበት ፣ የትጥቅ ትግል አራማጆችም ትግሉን በተለያየ አቅጣጫ በማድረግ ህወሓት ድንጋጤ ውስጥ እንዲገባና የሚይዘውና የሚጨብጠው እንዲያጣ በማድረግ ያደረጉት ትግልም ቀላል አልነበረም:: በዚህ ዙሪያ አርበኞች ግንባር፣ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር፣ የኦጋዴን ነጻነት ግንባርና ሌሎችም ያደረጉት የትጥቅ ትግልና ድል ቀላል አልነበረም:: ከዚህ በተጨማሪ የግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይልም ትግሉን ወደፊት ለመውሰድ የጣለው መሰረት በህወሓት መንደር ትልቅ ድንጋጤን ከመፍጠሩም በላይ በህወሓት ላይ ከፈጠረው ጫና የተነሳ ህወሓት ሳይወድ በግዱ የንደራደር ጥያቄንም እንዲያቀርብ ያስገደደው ሁኔታ ገጥሞታል ::

 

እነዚህ ከላይ ያየናቸው ሁኔታዎችና ሌሎች አሁን ያልጠቀስናቸው ሰፊ የአገራችን ችግሮች በዚሁ በ2013 በመፈጠራቸው ዓመቱ እጅግ አሳዛኝና መራራ አመት ነበር ለማለት ያስችላል :: ለዚህ ሁሉ ችግር ትልቁ ተጠያቂም ህወሓት እራሱ ለመሆኑ ምንም ጥርጥር የለኝም  :: 2014 አዲሱ ዓመት ግን ለዓመታት በኢትዮጵያና በኢትዮጵያዊነት ላይ ከሁሉም በላይ ደግሞ በሰብዓዊ ፍጥረት ላይ ይህ ዘረኛ ቡድን የሚፈጽመውን ግፍ ለማስቆም በጋራ የምንቆምበትና በአገራችን ሁላችንንም በእኩልነት፣ በፍትህ፣ በነጻነት፣ በህግ የበላይነት ሥር ሁላችንም በህግ ፊት እኩል ሆነን የምንኖርባትን አገር ለመመስረትና ለዚህም የህዝብና የአገር ራዕይ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ለራሱ ሲል አቅሙ በቻለ ሁሉ ትግሉን እንዲቀላቀልና ህወሓትን በመደምሰስ በጋራ ሁላችንንም የምትወድ አገር  ልንመሰርትበት የምንችልበትን መሠረት የምንጥልበት ዓመት ሊሆን  ይገባናል  እላለሁ :: ቸር ይግጠመን ::

comment pic

እግዚአብሔር ኢትዮጵያን  ይባርክ !

 

ኬሳ ኬሳ አዱሬን ቢነሳ…(ውስጥ ውስጡን ድመትም ነብር ናት) ክፍል 1( በቶሎሳ በቀለ)

$
0
0

ይድረስ ታሪክ ለመታንሻፈፉ እና በብሄር ለማጋጨረት ለምትጠሩ ሁሉ
Ethiopian Flag

አባቴ አንድ ነገር ሳይጥማቸው ሲቀር ‹‹ኪሳ ኬሳ አዱሬን ቢኒሳ..›› ይላሉ፡፡ ‹‹ውስጥ ውስጡን ድመትም ነብር ናት..›› ማለት ነው፡፡ ይህ የኦሮሞን አባባል የተጠቀምኩት የኦሮሞ ልጆች ላይ ነብር መስለው ድመት የሆኑ የተገላበጠ ገመና ያላቸው እንደ እባብ ቆዳቸውን እየሸለቀቁ ወደ እሳት የሚገፉት ስንኩል ሰዎች ስላሉ ነው፡፡ ለእነዚህ የታሪክ ዝቃጮች ጥያቄ ማቅረብና እና እውነታውን ማሳየት እፈልጋለሁ፡፡ መጀመሪያ ደረጃ ለጁዋር እና ብጤዎቹ መጠየቅ የምፈልገው….የኦሮሞ ህዝብ ከኢትዮጵያ ህዝብ የተለየ ታሪክ አለው ወይ? ኢትዮጵያስ ከኦሮሞ ህዝብ የተነጠለ ታሪክ አላት ወይ? እንደ አለመታደል ሆኖ ጥሩ አስተዳደር ያላገኘው ድፍን የኢትዮጵያ ህዝብ ተረግጦ ተበድሎ እኩል እየተበደለ፣ እየሞተ ነው የኖረው፡፡
አሁን ኦህዲድን ከመሰለ አሸርጋጅና ወገኑን በላ ድርጅት ጀምሮ ለመጣው ሁሉ ሲሰግዱ እጅ መንሻ የሚያቀርቡት የኦሮሞን ልጅ ጭዳ አድርገው ነው፡፡ ይሄ ስልጣን ፈላጊ ኦሮሞ የኦሮሞን ልጅ አሳልፎ መስጠት በፊትም የነበረ ነው፡፡ እውነት እንነጋገር ካልን የአኖሌን ጭፍጨፋ እውን ምኒልክ ነው የፈጸመው? የኦሮሞን ልጅ አጥንት ሲበላው የሚታየው ለገዢው አካል አሸርጋጅ ሆኖ የሚያጎበድድ የኦሮሞ ልጅ ነው፡፡ የኦሮሞን ህዝብ የጨፈጨፈው ጎበና ዳጬ ሆኖ ሳለ አንድም ቀን ስትጠሩት ሰምቼ አላውቅም፡፡ ለምን?…
ስላለፈውና ያልሆነውን ሆነ ብሎ በማውራት ለነገም ስቃይን ማስቀመጥ ምን ይሰራል? እውነት እንነጋገር ከተባለ ማንም ጥሩ ጎን ቢኖረውም መጥፎ ጎን እንዳለውም መዘንጋት የለበትም፡፡ ምኒልክ ሰው ነው ሁሉ ነገሩ ጥሩ ነው ማለት አይቻልም፡፡ እሺ እንዳላችሁት ጎበና ዳጬን በማዘዝ ኦሮሞ ህዝብ ላይ ግፍ ፈጽመዋል ብለን እናስብ፡፡ ግን በስልጣን ዘመናቸው ጥሩም ነገር ማድረጋቸውን አንዘንጋ፡፡
በተጨማሪ የጣሊያንን ወረራ ኃይል ምኒልክ በድል ተወጥተው ባያሸንፉ (የአድዋ ድል..የጥቁር ህዝብ ኩራት) ባይከሰት በጣሊያን ቅኝ ብንገዛ ኖሮ ዛሬ ስምህ ወይም ስማችን ማን ይሆን ነበር? ሮቤርቶ፣ ካርሎስ..ኪኪኪኪ…ይሄ ስምና ማንነት ላይ የሚመጣውን ለውጥ እንተወው፡፡ የኦሮሞ ዋነኛው ስርዓት፣ ባህል፣ እምነት..ዋቄፈታ፣ ዋቄፋና ነው፡፡ ዛሬ የኦሮሞ ማንነት መገለጫ የሆነው ኢሬቻስ ይደረግ ነበር? የገዳ ስርዓትስ ይኖር ነበር? ቅኝ ግዛት ዋነኛ አላማው እንደዚህ አይነት የማንነት መገለጫዎችን ማጥፋት መሆኑን እንዴት ረሳችሁት፡፡ የመዳ ወላቡስ ታሪክ ይቀጥል ነበር ወይ?
ሌላም ነገር ልጠይቅ ወደድኩ፡፡ ዛሬ ምሁር ለመምሰል አነጋገር የምታሳምሩ ታሪክ መስራት ሲያቅታችሁ ከመቶ አመት በፊት የተፈጸመን ነገር እያነሳን እርስ በእርሳችን እንድንናቆር መንገድ ከምትጠርጉ ለኦሮሞ ህዝብ የሚበጀውን ለምን አትጠቀሙም፡፡ አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ ምኒልክ ነው ወይስ ወያኔ ነው የኦሮሞ ህዝብ ራስ ምታት? ዛሬ የኦሮሞን ልጅ እየገደለ፣ እያሰቃየ፣ ለስደት እየዳረገ ያለው ገዢው ወያኔን ለምን ታግላችሁ መጣል አትሞክሩም? ይህን ብታደርጉ ነው ለኦሮሞ ልጅ እውነተኛ ተቆርቋሪ የምትሆኑት፡፡ ያለበለዛ ወዲያልኝ ወዲያ ዋጋም የለሽ ብሬን መልሽ እንደተባለው አይነት ናችሁ፡፡ አሁን እየሞትን ባለፈ ታሪክ ላይ የምታላዝኑ… (ሀሬ ዱቴ ኩር ኢንጀጠኒ..) ይላል አባቴ፡፡ የሞተ አህያ ኩርር…አይባልም እንደማለት ነው፡፡
ከደቡብ አፍሪካ ብሎም ከማንዴላ ምን መማር አለብን? ብሔራዊ እርቅ…ያለፈን ይቅር ብሎ በሰላም መኖር ነው የሚበጀው፡፡ የኦሮሞ ህዝበ እሰከዛሬ ያየው እያየ ያለው ሰቆቃ ይበቃዋል፡፡ አሁንም ቢሆን ኢህአዴግ በስሩ የፈለፈለው ኦህዲድ የሚባል የአሸርጋጆች ቡድን የወገናቸውን ደም መጣጮች ህዝቡን እየሸጡት ነው፡፡ መድረስ ያለብን አሁን በስቃይ ውስጥ ላለው ህዝብ ነው፡፡
በቀጣዩ ክፍል እንገናኝ

እስክንደር ነጋ አሸባሪ ከተባለ ጆን ኬሪና አል ባራዴየም አሸባሪዎች ናቸው ማለት ነው –ግርማ ካሳ

$
0
0

ግርማ ካሳ

Eskinder-Negaኢቲቪ በቅርቡ አንድ በአንድ በኩል አሳዛኝ በሌላ በኩል አስቂኝ ዶኪሚንተሪ ለተመልካቾቹ አቅርቧል። በርካታ ጉዳዮች ተነስተዋል። ለዛሬ፣ የፌዴራል ከፍተኛ አቃቤ ሕግ የሆኑት፣ አቶ ብርሃኑ ወንድማገኝ አንጋፋዉ ጋዜጠኛ እስክንደር ነጋን በተመለለተ፣ በተናገሩት ላይ ጥቂት ሃሳቦችን ለመገልጽ እወዳለሁ። ሰዉዬ ስለ ሕግ፣ ስለ ሕገ መንግስቱ እየደጋገሙ አውርተዋል። ማንም ሕገ መንግስቱን የማክበርና የማስከበር ሃላፊነትና ግዴታ እንዳለበት የገለጹት፣ አቃቤ ሕጉ፣ የአገሪቷ ሕግ ሲናድ ወንጀለኞችን ይዞ ለሕግ ከማቅረብ ወደኋላ እንደማይሉ አሳስበዋል። ማለፊያ ነዉ። ወንጀለኛ መያዝና መቀጣት አለበት። ሕግ መከበር አለበት። ይሄ ብዙ አያከራክረንም።

ነገር ግን «ሕግ፣ ሕግ» እየተባለን፣ ፍጹም ሕገ ወጥ የሆነ ተግባራት፣ ሕግ አስከባሪ ነን በሚሉ እየተፈጸመ መሆኑ ነዉ ብዙ እያከራከረን ያለው። ሕግ ሁላችንንም በእኩልነት የሚዳኝ መሆኑ ቀርቶ፣ ጥቂቶች እንደፈለጉ የሚገለባብጡት፣ የመጨቆኛ መሳሪያን በርት መሆኑ ነዉ እያሳሰብን ያለው። አቶ ብርሃኑ ስለ እስክንደር ነጋ ሲናገሩ የሚከተለዉን አሉ፡

«የእስክንድርንም ኬዝ ቢሆን፣ የ2004 አረብ ስፕሪንግ አይነት፣ ኢትዮያ ዉስጥ የአመጽ ጥሪ በማድረግ ከተንቀሳቀሱ ኃይሎች አንዱ እራሱ ነዉ። እርሱ በተለይም በየተኛዉ እርስ ላይ፣ በመጻፉ ምክንያት፣ አንድም ክስ አልቀረበበትም።የእስክንድር ጉዳይ ከፍሬደም ኦፍ ኤክስፕረሽን፣ ከመናገር ነጻነት ጋር፣ ከመናገር መብት ጋር የተያይዘ በፍጹም አይደለም። ቅድም እንዳልኩት፣ የአመጽ ጥሪ ማስተላለፉ ነዉ። የአምጽ ጥሪው ደግሞ የግንቦት ሰባት ተልእኮን ለማሳካት ነዉ። ከዚህ ጋር እስከ ፌደራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ድረስ በጣም ሰፋ ይሉ ክርክሮችን በተደጋጋሚ አድርገናል።የአገሪቱ የመጨረሻ የሆነው ፌደራል ጠቅላ ፍርድ ቤት ፤ የጠፋተኝነት ዉሳኔ ሰጧል።»

በግብጽ የታየው፣ በኢትዮጵያም እንዲደገም እስክንደር ነጋ የሚፈልግ እንደነበረ ብዙም አያክራክረንም። በአንድነት ፓርቲ ጽ/ቤት በተደረገ ስብሰባ ላይ «እንችላለን! በሌሎች የአፍሪካ ሃገሮች እንደሚቻል አይተናል። ኢትዮጵያ ከእነሱ ቢያንስ ቢያንስ አታንስም። ታሪክ እንስራ!» ያለዉና ኢቲቪ ቀንጥቦ ያወጣዉ አባባል ትክክለኛ አባባል ነው። እስክንደር ነጋ፣ ይሄን አልክዳእም። ሊክድም አይችልም።

«እስክንደር፣ በግብጽ የተከሰተዉ በኢትዮጵያ እንዲከሰት መፈለጉና በዚያ ዙሪያ መንቀሳቀሱ በምን መስፈርትና ሚዛን ነዉ ሽብርተኘንት ተደርጎ ሊወሰድ የሚችለው ? » በሚለው ላይ ነዉ የመጀመሪያ ክርክራችን። በግብጽ የነበረው እንቅስቃሴ ፍጹም ሰላማዊ የነበረ እንቅስቃሴ ነዉ። ከዚህ እንቅስቃሴ መሪዎች መካከል የነበሩ አንዱ ዶክርተር ሞሃመድ አል ባራዴ ይባላሉ። በተባበሩት መንግስታት የአለም አቀፍ ኑክሊያር ኤጀንሲ ሰብሳቢ ሆነው ለበርካታ አመት ያገለገሉ የተከበሩ ሰው ናቸው። እንደ ሳዳም ሁሴን የመሳሰሉ ሽብርተኛ መንግስታት ጅምላ ጨራሽ መሳሪያዎች በማከማቸት ለአለም ስጋት እንዳይፈጥሩ የታገሉ የሰላም ሰዉ ናቸው። እኝህ ሰውና የሚመሪት ድርጅታቸው እንደ ፈረንጆች አቆጣጠር በ2005 የሰላም ኖቤል ተሸላሚ ሆነዋል። ታዲያ ሰላማዊ በሆነ መልኩ፣ አምባገነኑ የሙባረክ መንግስት ለሕዝብ ፍቃድ ተጠያቂ እንዲሆን፣ የስርዓት ለዉጥ እንዲመጣ፣ መታገላቸው እኝህ የሰላም የኖቤል ተሸላምዊ ሽብተኛ ያደርጋቸዋልን ?

ከሰባት ወራት በፊት ጆን ኬሪ፣ ሃርድ ቶክ ቢቢሲ ባዘጋጀው ዝግጅት ላይ፣ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከተማሪዎች ለቀረበላቸው ጥያቄ መልስ ሰጥተው ነበር። የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴሩ ቴዎድሮስ አዳኖም በዚያ ነበሩ። ጆን ኬሪ ንግግራቸውን ሲጀመሩ የተናገሩትን ማንሳት እፈልጋለሁ። በግብጽ ስለነበረው ፣ ሕወሃት/ኢሕአዴግ ሽብርተኘንት ብሎ ስለሚጠራዉ፣ እንቅስቃሴ ሲናገሩ የሚከተለዉን ነበር ያሉት፡

«…the greatest concern has to be the lack of the fulfillment by governments in many countries, of the aspirations of people. Particularly the creation of jobs, and tሀ educational opportunities that are needed, for this modern world….In Egyopt, that was not a revolution that was moved by Islamism, or any ideology ….It was young people.. ..it was you ..people who came to the square , and twitted each other , texted each other , e-mail each other and brought people»

ጆን ኬሪ፣ ሕወሃት/ኢሕአዴግ ንደ ሽብርተኝነት የሚቆጥረዉን በግብጽ የታየውን ሰላማዊ እንቅስቃሴ እንደ ትልቅ ምሳሌ አጉልተው ሲናገሩ፣ እስክንደር ነጋና ሌሎች ከተናገሩት አባባሎች ጋር የሚስማማ ንግግር ሲናገሩ፣ የሕወሃት/ኢሕአዴጉ ዶር ቴዎዶርስ ቁጭ ብለው ያዳምጡ ነበር። ታዲያ ጆን ኬሪ፣ የግብጽን እንቅስቃሰ እበነደገፋቸው፣ ወጣቶች ከግብጽ ወጣቶች እንዲማሩ በማባረታታቸው ችብርተኛ ሆኖን ? ሌላ ሌላም ምሳሌዎች ማቅረብ ይቻላል።

በግብጽ የታየዉ «አምባገነኖች» እምቢ የማለት ሰላማዊ እንቅስቃሴ የአለም አቀፍ ሕግን ያከበረ፣ በሰለጠነው አለም አድናቆትን ያተረፈ፣ የሕዝብ ጉልበት ታፎኖ እንጂ ከተነሳ ተአምር ሊያደርግ እንደሚቻል ያስተማረ ፣ ለአምባገነኖች ፍርሃትን የለቀቀ እንቅስቃሴ ነዉ። ሽብርተኝነት በፍጹም አይደለም።

እንግዲህ ሕወሃት/ኢሕአዴግ እስክንደርን ሽብርተኛ እያለ መጠራቱን ከቀጠለ ጂን ኬሪ፣ የስላም የኖቤል ተሸላሚ የሆኑትን ዶር መሃመድ አልባራዴን የመሳሰሉትን ሽብርተኛ እያለ እንደሆነ መቆጠር ይኖርበታል።

ሌላዉ ማንሳት የምፈልገው አቶ ብርሃኑ ከየት ዘለዉ እስክንደር ነጋን ከግንቦት ስባት ጋር እንዳገናኙት ነዉ። በግብጽ የነበረዉ ሰላማዊ እንቅስቃሴ ነዉ። ግንቦት ሰባት «የሰላም እንቅስቃሴ አይሰራም» ብሎ ነፍጥ ጨብጫለሁ ያለ ደርጅት ነዉ። እንዴት ተደረጎ ነዉ በግብጽ የታየዉን መደገፍ፣ የግንቦት ሰባት አባል የሚያሰኘው ? እዚህ ላይ ሕወሃት/ኢሕአዴጎች እራሳቸው ያስገመቱ ይመስለኛል። ምን አለ ባይቀልዱብን ?

በመጨረሻ በትክክለኛ መንገድ ክርክሮች ተደረገዉ በርካታ መረጃዎች ቀርበው፣ ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ፣ የጥፋተኛ ዉሳኔ እንደሰጠ በመግለጽ አቶ ብርሃኑ፣ የሕግ ስርዓት እንዳለ፣ ለማሳየት ሞክረዋል። እስክንደር ነጋ ቦምብ አላፈነዳም። ቤቱ ተበርብሮ አንድም ጥፋተኝነቱን የሚገልጽ መረጃ አልተገኘም። ወንጀሉ እንደ ጆን ኬሪ፣ ሞሃመድ አልባራዴ የግብጽ ሕዝባዊ እንቅስቃሴን መደገፉ ፣ በሕዝብ ጉልበት ኃይል መተማመኑ ነዉ። ወንጀሉ አገሩን መዉደዱ ነዉ።

«እክንድር ሽብርተኛ መሆኑን የሚያመለከት መረጃ አላየሁምና ልፈታው ነው» ባሉ ጊዜ የጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኛ አቶ አማረ አሞኜ ፣ የሚኒስተሮች ምክር ቤት ተጠርተዉ መመሪያ እንደተሰጣቸው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ አንድ ወቅት ዘግቦልን ነበር። ዳኛ አማረ፣ ፍቃደኛ ባለመሆናቸው፣ ምንም እንኳን ጉዳዩን ሲያዳምጡ የነበሩ እርሳቸው ቢሆንም፣ ጉዳዪን ያላዳመጣ ሌላ ዳኛ (ወይንም ካድሬ) ተመድቦ ነዉ፣ የፖለቲካ ዉሳኔዉን በፍርድ ቤት ያነበበዉ። ሐቁ እንግዲህ ይሄ ነዉ። ኢትዮጵያ ዉስጥ የሕግ ስርዓት የለም። የግብጽ አይነቱን እንቅስቃሴ፣ የሕዝቡ መነሳት ምን ጊዜም አምባገነኖችን የሚያስጨንቅ ስለሆነ፣ ክህደት፣ ሽብር፣ ወዘተረፈ እያሉ ማሰርና መግደል ልማዳቸው ነዉ። ነገር ግን ለጊዜ ያሸነፉ ሊመስላቸው ይችላል እንጂ ወዳቂዎች ናቸው። ይህ በነ እስክንደር ላይ የምናየው ድራማ አገዛዙ በራሱ የማይተማመን፣ የደነበረ መሆኑን ያሳየ ነው፡ በሚቆጣጠሩት ሜዲያ ጠዋትና ማታ መለፈፋቸውም የዉሸታቸውና የግፋቸውን መጠን አይቀንሰውም። ሕዝቡንም ማታለል አይችሉም። ሕዝቡ ያውቃል። ሕዝቡ እስክንደር ነጋ ማን እንደሆነ ያወቃል። እስክንደር ለኢትዮጵያ ሕዝብ ጀግና ነው። እርሱ ቃሊቲ የሚቆዩባቸው ቀናት በጨመሩ ቁጥር፣ እርሱ የበለጠ እየሸነፈ፣ እነርሱ ደግሞ እየመነመኑ ፣ ምናምንቴ እየሆኑ ነዉ። እርሱ በአለም አቀፍ መድረክ እየተከበረ፣ እነርሱ ደግሞ ሃፍረት እየተከናነቡ ነዉ።

‹‹የፍቅር ጉዞ›› ኮንሰርት ቢሰረዝም ሄኒከን ቢራ ለቴዲ አፍሮ 4.5 ሚሊየን ብር ይከፍለዋል

$
0
0

teddy afro
ዛሬ በአዲስ አበባ ታትሞ የወጣው አዲስ አድማስ ጋዜጣ እንደዘገበው ‹‹የፍቅር ጉዞ›› ኮንሰርት ቢሰረዝም ለቴዲ አፍሮ 4.5 ሚሊየን ብር ሄኒከን ቢራ ይከፍላል። የጋዜጣው ዘገባ እንደወረደ ይኸው፦

በደሌ ለኮንሰርቶቹ 25 ሚ.ብር መድቦ ነበር ኮንሰርቶቹ ቢሰረዙም ውዝግቡ አልተቋጨም የቴዲ ደጋፊዎች የአፀፋ ዘመቻ ጀምረዋል

አለማቀፉ የኔዘርላንድ ኩባንያ ሄኒከን ከሚያስተዳድረው በደሌ ቢራ ጋር በመሆን በበርካታ ከተሞች ሊካሄዱ የነበሩ የቴዲ አፍሮ ኮንሰርቶች ቢሰረዙም፣ ቴዲ አፍሮ በውላቸው መሰረት 4.5 ሚ. ብር እንደሚከፈለው ምንጮች ገለፁ፡፡ እስካሁን በአገር ውስጥ ከተካሄዱ ኮንሰርቶች በላቀና ደረጃውን በጠበቀ መንገድ በድሬዳዋ ተጀምሮ በርካታ ከተሞችን እንዲያዳርስ ታስቦ የተፈረመው የቴዲ አፍሮና የበደሌ ቢራ ስምምነት፤ በኢንተርኔት በተካሄደ የተቃውሞ ዘመቻ ታውኮ ነው ሳምንት ሳይሞላው የፈረሰው፡፡ ከ20ሺ በላይ ሰዎች በኢንተርኔት በተሰባሰበ ድምጽ ለተካሄደው የተቃውሞ ዘመቻና ውዝግብ እንደመነሻ ሆኖ የሚጠቀሰው ዐረፍተ ነገር “የአፄ ምኒልክ ጦርነቶች ቅዱስ ናቸው” የሚል አባባል ሲሆን፤ ቴዲ አፍሮ የኔ አባባል አይደለም በማለት ማስተባበሉ ይታወሳል፡፡ በምኒልክ ጦርነት ብዙ ሰው አልቋል በሚል የገፋው ተቃውሞ፤ በደሌ ከቴዲ አፍሮ ኮንሰርት ጋር እንዳይተባበር ለሄኒከን ኩባንያ ጥያቄውን በማቅረብ እንዲሰረዝ አድርጓል፡፡

የቀድሞ የአገሪቱ ነገሥታትን በተመለከተ፣ በተለይም በአፄ ምኒልክ ዙሪያ ከየአቅጣጫው “መልካም ወይም መጥፎ ናቸው” የሚባሉ የንጉሱ ድርጊቶች እየተጠቀሱ በተደጋጋሚ የፖለቲካ ጭቅጭቆች፤ መነሳታቸው አዲስ አይደለም፤ በአንድ በኩል ምኒልክ ለአገሪቱ ነፃነት፣ አንድነትና ሥልጣኔ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክተዋል የሚሉ እንዳሉ ሁሉ፤ ስልጣናቸውን ለማስፋፋት ባካሄዱት ጦርነት ግፍ ተፈጽሟል፤ ብዙ ህዝብ አልቋል ብለው የሚያወግዙም ጥቂት አይደሉም፡፡ በመሃል ደግሞ፣ በታሪክ የተከሰቱ ነገሮችን ወደኋላ ተመልሶ መለወጥ እንደማይቻል የሚገልፁ ወገኖች፤ መጥፎ ነገሮችን እያስተካከልን መልካም ነገሮች ላይ አተኩረን እየወረስን ማሳደግ አለብን በማለት ለማስታረቅ የሚሞክሩ አሉ፡፡ ከተለያዩ አካባቢዎችና ብሔረሰቦች የፈለቁ ጀግኖች ከአፄ ምኒልክ ጋር ለአገራቸው ነፃነትና ስልጣኔ ተጣጥረዋል በማለት ከአስታራቂዎቹ ወገን የተሰለፈው ቴዲ አፍሮ፤ የምኒልክን መቶኛ ሙት ዓመት በማስመልከት ለ“እንቁ” መጽሔት በሰጠው ቃለ ምልልስ፣ ካለፈው ዘመን የሚወረሱ መልካም ታሪኮችን ጠቅሶ፣ የስህተቶችና የጥፋቶች መድሃኒት ፍቅር ነው በማለት የዘረዘራቸው ሃሳቦች ታትመው ወጥተዋል፡፡

“የአፄ ምኒልክ ጦርነቶች ቅዱስ ናቸው” የሚል ሃሳብ ግን እንዳልተናገረና በመጽሔቱ እንዳልታተመ በመጥቀስ ያስተባበለው ቴዲ አፍሮ፤ በኢንተርኔት የተሰራጨው አባባል እኔን አይወክልም ማለቱ ይታወሳል፡፡ የበደሌ ቢራ ባለቤት የሆነው የአለማችን ታዋቂ ቢራ አምራች ኩባንያ ሄኒከን፤ የበደሌ ቢራ ፋብሪካ እና የቴዲ አፍሮ ስምምነት እንዲሰረዝ የወሰነው፤ እንደብዙዎች ኩባንያዎች ሁሉ አደባባይ በወጣ ውስብስብ የፖለቲካ ውዝግብ ውስጥ መዘፈቅ ባለመፈለጉ እንደሆነ ምንጮቹ ተናግረዋል፡፡ እነዚሁ ቅርበት ያላቸው ምንጮች እንደገለፁት፤ በደሌ ቢራ “የፍቅር ጉዞ” በሚል ስያሜ ከዚህ ሳምንት ጀምሮ በበርካታ ከተሞች በተከታታይ ለሚካሄዱ ኮንሰርቶች 25ሚ. ብር ገደማ መድቦ ነበር፡፡ በደሌ 4.5 ሚ. ብር ለቴዲ አፍሮ ለመክፈል ተስማምቶ ውል ሲፈራረም 1.5 ሚ ብር የመጀመሪያ ክፍያ እንደፈፀመ የገለፁት እነዚሁ ምንጮች፤ በተለያዩ ከተሞች የሚቀርቡት ኮንሰርቶች ደረጃቸውን የጠበቁና ድምቀትን የተላበሱ ለማድረግ ከ20 ሚ. ብር በላይ ወጪ ለማድረግ ተዘጋጅቶ ነበር ብለዋል፡፡ በደሌ ቢራ በራሱ መሪነት በሚያዘጋጃቸው ኮንሰርቶች ላይ፣ ከትኬት ሽያጭ የሚሰበሰበውን ገቢ ለበጐ አድራጐት ድርጅቶች ለመለገስ ሃሳብ እንደነበረውም ምንጮቹ ጠቅሰዋል፡፡

በደሌ ከኮንሰርቶቹ ዝግጅት ራሱን ለማግለል ሲወስን፣ ቀደም ሲል የተፈራረመውን ውል በሚመለከት ከቴዲ አፍሮ ጋር ተደራድሮ የውል ማፍረሻ ስምምነት መፈራረሙንም ምንጮቹ ገልፀዋል፡፡ የስምምነት ማፍረሻ ስምምነቱንና የክፍያውን መጠን በተመለከተ በደሌ እና ቴዲ አፍሮ ዝርዝር መግለጫ ካለመስጠታቸውም ባሻገር፣ ከሁሉም ወገኖች መረጃ ለማግኘት የተደረጉ ሙከራዎች አልተሳኩም። በድርድር የተቋጩ ጉዳዮች ላይ ተዋዋይ ወገኖች ጉዳዩን በተናጠል በይፋ ላለመግለጽ መስማማታቸው የተለመደ እንደሆነ ምንጮቹ ጠቅሰው፤ በደሌ የመጀመሪያ ክፍያውን ጨምሮ ለቴዲ አፍሮ 4.5 ሚ. ብር የሚከፍል መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ ብለዋል፡፡ በኢንተርኔት ሲካሄድ የነበረው ዘመቻ፣ የበደሌ እና የቴዲ አፍሮ የስምምነት ውል ከፈረሰ በኋላ ቢረግብም፤ ያንን ተከትለው የመጡ ሌሎች ዘመቻዎች መፈጠራቸው አልቀረም፡፡ የቴዲ አፍሮን ኮንሰርት ለመቃወም የተጀመረው ዘመቻ፣ በተቃራኒ ኮንሰርቱን በመደገፍ ከተፈጠረው ሌላ ዘመቻ ጋር እንካ ሰላንቲያው ቀጥሏል፡፡ በቅርብ ጊዜ የሚካሄድ ኮንሰርት ባለመኖሩ ጭቅጭቁና ዘመቻው ምን ያህል የፌስቡክ ዕድምተኞችን ሳያሰለች ሊቀጥል እንደሚችል ገና አልታወቀም፡፡

ኢትዮጵያዊነት የመንፈስ ንባብ ነው –ለእኔ! ከሥርጉተ ሥላሴ

$
0
0

ከሥርጉተ ሥላሴ 11.01.2014

sreateሰንበትን እንደ መክለፍት በእኛነት ዙሪያ ልል አሰብኩ። …  … አብሶ ሩሄን በትዝታ በሚያባክኑኝ ዬውስጥ – ለውስጥ የመንፈስ ሃዲዶች ዙሪያ ትንሽ ማለት ወደድኩ። የጹሑፉ ጥራት እስተዚህም ነው። ግን የሃሳቤ ፍሰት ማንነቴን ስለሚዳስስልኝ፤ ፍቅሬን – ትዝታዬን ይመግበኛል። ኢትዮጵያዊነት ንባብ ነው። ሲፈቀድልን ብቻ ማንበብ እንቻላለን። ኢትዮጵያዊነት ትርጉም ነው፤ ሲፈቀድልን ብቻ መተርጎም እንቻላለን። ኢትዮጵያዊነት ሚስጢር ነው ሲፈቀድልን ብቻ ነው፤ ቁልፉን መክፈት የሚችለው። ኢትዮጵያዊነት የመኖር ሕይወት ነው ሲፈቅድልን መታደስ ይቻላል፤ ለዛውም አምሮብን። ኢትዮጵያዊነት መንፈስ ነው፤ ሲሰጠን ብቻ ዓይናችን ይከፈታል …. በስተቀር ዲዳ ሃሳብ ማስተናገድ ዕጣችን ይሆናል። ይህ ደግሞ ቅርስ አልባ ባዶነት፤ እርሾ አልባ ዘርየለሽ መሆን ነው። አያድርስ!

 

ኢትዮጵያዊነት ፍጹም ተወዳዳሪነት የማይገኝለት ተናፋቂ ማንነት ነው። ናፍቆቱ ውስጥን እንደ አሻው ገዝቶ አፍርህን በህሊናህ ስትቃኘው ፍውሰትን ያድልኃል፤ው ደግሞ ውበቱ ይቆጣጠርኃል። ስትፈቅድለት ትድናለህ። እሺ ስትለው ትፈወሳለህ፤ በስተቀር ግን ጉጉ ማንጉግ የሆነ አንካሳ መንፈስ ይጨፍርብኃል …፤ እስኪበቃው ያጨቀይኃል። አሸንፈውና ውጣ! … አሸናፊነትን ዋጥ አድርገውና ውስጥህን አሳምርብት …. ጌጥ ይጣላልን?

 

እንጀራን ስትወደው፤ ሽሮ ሰፍ ሲያደርግህ፤ ቁርጡ ሲታይህ፤ ቆሎው ሰፍ ሲያደርግ፤ ምቸት አብሹ ውል ሲልህ፤ ክትፎው ሲመጣብህ ሚጥሚጣዋን ስትዳስሳት፤ ቆጮን ስታላምጠው፤ ጭኮውን ቀረብ አድርገህ ስታሸተው፤ ዳቦው በእንሰት ወይንም በኮባ ተደፍቶ ከነክብሩ በሞገስ  በቁንዶ በርበሪ ለምለም ዝንጣፊ ወይንም ጉዝጓዝ ተሽሞንሙኖ ሲታይህ፤ አንባሻው ሲሸትህ፤ ንፍሮው ሽው ሲልህ፤ ዝግኑ – ጥብሱ – ቅቅሉ – ጎረድ  ጎረዱ፤ ዝልቦው፤ ቦዘናው፤ ገንፎው ቅንጨው፤ ጨጨብሳው፤  ፍርፍሩ ሲያሰኝህ ዕወቀው ይህ ስሜት ውስጥህን ገዝቶ አንተነትህን የሰጠህ ስለመሆኑ። በጣም በእርግጠኝነት  ከዚህ ፈጽሞ አታመልጥምና ውበቱን አጊጥበት! ….

…. አንተን አሳምሮ የሚገልጸህ ተራጓሚህ መሆንህን አትዝለለው፤ እርቀህ የማትርቀው ወስጥህ ነውና – አድምጠው።

ቄጤማው ለሽ ብሎ … ረከቦቱ ተኮፍሶ፤ ጭሱ ትጉልል – ትጉልል እያለ ሀገር ምድሩን ሲያካልለው፤ ማዕዛው የእጣኑ ዝንቅንቁ ጨስጨስ ሲል፤ ፍንጃሉ ወይንም ስኒው ላይ የፈረስ ጭራ መስሎ ቆረር ሲል፤ ጤናዳሙ ጣል ብሎ ወይ በወተት ወይ እንዲሁ፤ ጨው ሆነ ማጣፈጫ ታክሎበት ፉት ፉት – ትኩስ ትኩሱን፤ ዳበስ አድርገው – ሁንለት።  የቡና ቁርሱ በቀለምሽሽ ተሽሞንሙኖ ቀረብ ሲል ቸርፈስ፤  ዘንጣፌ ሚጢሚጣዋ በተን ብላበት፤ ወይ ዳቦዋ … በህብረት  በአብሮነት  ሰምሮ ከልብህ ከት ብለህ ስትስቅ – ስትተራራብ … ያ ነው ፎሎቄው አንተነትህን የሰጠህ ኢትዮጵያዊነት። ይህን ዘለህ ወይንም ጨፍልቀህ ልትሄድ ብትል አይሆንም —  አትችልም በፍጹም፤ እባክህን አትግደርደር። አንተ ማለት የዚህ ውጤት ጭማቂ ነህ።  ማንነትህ የተቀዳው ከዚህ ማርን ከሚያዘንብ ባህል ነው። እዚህ ላይ ያለው ንባብ ልዩ ነው … ይጣፍጣል፤ መንፈስን በሽብሸባ ዘና ያደርጋል፤ በዜማ ይቃኛል። ግን ትጉህ አንባቢ ይሻል – ስትታደል ይገለጽላኃል በስተቀር …. አንተን እራስህን ተላልፈኸዋል …. ተመለስ! የተፈጥሮ መስተውትህን ድጠህ አትስበረው። ይህ ቅልቅል ግን ውህድ ውብ ቅመም ቁንጅናህ እንዲሆን …. አብስለው።

 

ዋው! ስንቱ ይዘርዘር …. የንብ አውራ በመሰለ ሽንጣም ሞሰብ፤ ሌማት፤ ጥራር፤ ሰብሰብ ብለህ ስተታድም፤ ስትጎራራስ፤ በሞቴ አፈር ስሆን፣ ይህችን ይሀችን ብቻ!ች በእኔ ሞት ወይንም በእከሌ ወይንም በእከሊት ሞት እየተባልክ በአፍ በእፍህ ፍቅርን ተጥቅልሎ ስትጎርስ ዬት እንደተቀዳህ ሹክ ይልኃል፤ ጣዕሙን ኑርበት – ለራስህ ብትል። አድምጠው አንተን እራስህን አግኝተህ አንገትህን ቀና አድርገህ እዬው፤ የነፃነት ቅኔ ዘጉባኤ በራስ መተማማን ስሜት እንዲፈነድቅ የረዳህ አንትን በአንተነትህ የፈጠረህ ቅዱስ መንፈስ ነው። የራስህም ጌታ እንድትሆን …. ያደርግኃል። አስተውል እባክህን? … ምንጩ ይህ ነው የማንነትህ ፈርጥ። ስታከበረው ማን እንደ አንተ ጌታ! ውስጥህ የባዕድ ሽፍትንት እንደይጨፍርበት ካልፈቀድክ፤ አንተ ዬዛ የጥቁር አንበሳ ደም ትውፊት ስለመሆንህ አሳምሮ ይነገርኃል – ያስተምርኃል። የዚህ ልዑቅ ንጥር አካል ቤተኛ – ተጋሪ መሆንህ ተሰጥቶኃልና እንኳን ደስ አለህ። …. እንዳይሾልክብህ ግን ጠብቀው!

 

… ያደክበት፣ ያ … ሜዳማ መስክ? ወይንም ያ … ጋራ ሸንተረሩ – ጅረቱ – ፋፏፈቴው የእነ-ባሮ፤ ፤ ዬእነ -አንገረብ የእነ-ጣና የእነ-አባይ፤ የእነ-መረብ፤ የእነ-ቀኃ፤ የቢሸፍቱ ሐይቅ ወዘተ የሌሎችንም ዋናና ገባር ወንዞች፤ ሐይቆች፤ጠረን – ስበት ከልብ ሆነህ መርምረው፤ እዬተራጨህ ትጫወትበት የነበረው ንፁህ አዬር በቅንነት ቅዘፈው፣ ሂድበትበት፤ ዋኝበት፤ ተፈጥሮህ የተቀመረበት የአንት ጸጋ ነው፤ ወስጥህን አሳምርበት፤ የአንተ ልዩ መለያ የተቀረጸበት መንፈስ ነው። በልጅነት ጊዜ ሰኞ ማክሰኞው፤ ቅልሞሹ፤ ገበጣው፤ ድብብቆሹ፤  በማዕድ ጥያቄ ተጠይቆ ላልመለሰ መሸነፉን እድምተኛው ሲወስንበት ፍርዱን ተቀብሎ ተሸናፊው የማይበላውን እንዲባላ በድምጽ ብልጫ ሲወሰንበት፤ ወርርዱ፤ ያ ውድና ደግ የልጅነት ዘመንህ የሰጠህ – የለገሰህ – የሸለመህ ረቂቅ ፍቅርን ካሰብከው በመንፈስህ እንዲሸራሸር ከፈቀድክለት እሱ ነው ተነስቶ የማይጠገብ ኢትዮጵያዊነት ማለት … አትረሳውም አይደል? ወደ ዛ … አዎንታዊ ዕውነት የህሊና ዓይን ላከው … ትበራለህ!

 

የምንጩን ውኃ ገለጥ – ገለጥ አድርገህ ፎልፎል የሚለውን ጎንበስ ብለህ ጠጥተህ ስትራካ እሱ ነው የአንተነትህ ቅኝት – እሺ! ተከታይህም ተራው ሲደርስ ትራፊ ነው ሳይል ተጎንብሶ ጥሙን ሲያረካ አንተ የተቀዳህበት ማንነት እሱ ነው ወርቅ ጸጋ ተመቸው! በቆሬ – በግሬራ – ወተቱ ከዛው ታልቦ ትኩሱን በርከክ ብለህ ስትጎነጭ አቤት ፍሰኃው! ይህ ለውስጥህ በገፍ ማንነትህ ያበቀለ መክሊትህ ነውና አጣጥመው! እርጎውን በፋጋ ጎንበስ ብለህ ውስጥህ ራስ ስታደርግበት፤ እርጎው በጉርና ተገፍቶ ቅቤው ሲወጣ፤ ትኩሷና አናትህን ረጠብ ስታደርግህ ነጮቹ ያልደረሱበት ሳውና ይሉኃል ይህ ነው።

 

ይህ ማንነት ተቀድቶ ያማያልቅ የኤዶም ገንት ነው … ግን ሚስጢር የመተርጎም ብቃቱ ካለህ፤ ከላይ … ከላይ የማታነበንብ ከሆንክ ብቻ …. ይህ መንፈስ ነው ማንነትህ የጸደቀበት – የበቀለበት – ያፈራበት። አትለፈው —-  ነገ ውስጡን አታገኘውማና ጠንቀቅ ነዋ!  አንተ ከሸፍትክበት እሱም ጀርባውን መስጠቱ አይቀሬ ነው – በጊዜ! …. በአንኮላው – በዋንጫው – በብርሌው ጥሩው ገፈታውን እፍ እፍ ብለህ ለቀቅ ስታደርገው፤ በተኃዋን በብርሌ ቆረር እያደረክ ወደ ሰራዊቶችህ ስትልከው፤ ቡቡኙምንም ጥምህን ሲያባርር ረጠብ የሚያደርግህ ያ ውስጥነት ህይውት እስበው፤ ፍቀድና ….  ዘና አድርገህ አጣጥመው … አስላው …. ቁጠረው ….  ሥፍር ቁጥር የሌለው ሐሤት ታገኝበታለህ። ያ ሐሤትህ የተጸነሰበት ጀግናው ማንነትህ፤ የነጠረው የአንተነትህ ጮማ ነው ….

 

ቁምጣዋን፤ ቦላሌዋን፤ ሽርጡን፤ ሳንጃውን – ኮልቱን – አልቢኑን – ግልቢያውን – ዋናውን ጉዞውን – ሁሉንም ከልብህ ሆነህ እሰባቸው፤ በምልሰት ጊዜ ሰጥተህ አጫውታቸው፤ ይሰጥህ የነበረውን ደስታ ምልሰት አድርገልት፤ ያ ነው ውዱ ዕሴትህ፤  ሙሉ ወርዱ፤ ሽብሽብዎ በመቀነት ሸብ ሲል፤ ጃኖው ቀለማሙ ህይወት፤ ጥልፋማ ማንነትህ የተወለደበት ውስጥህ ነው …. ከመንፈሰህ ጋር ስለመሆንህም አረጋግጥ …. ጤናማነትን ይሸልምኃል።

 

እርገት። ኢትዮጵያዊነት ጥሪኝ አለው። ኢትዮጵያዊነት ሥራዓትን ፈጥሮ ጨዋነትን ያበቀለ፤ መቻቻልን ውጦ በውስጡ ያጸደቀ፤ ትእግስትን ተቀበሎ ውስጥን የሚዳኝ የፍቅር ቤት ነው። እያንዳንዱ የአመጋገብ፤ የአኗኗር፤ የዕምነት፤ የወግና የልምድ ሞራሉ ልራቅህ ቢባል የማይቻል፤ መስጥረን፤ ተሸሽገን፤ ተቆራኝተን እዬኖርን ግን ቅብ ሽፍትነት ብታቆለባባስ ትርፉ ትዝብት ብቻ ነው ውጤቱም ባዶነት።

 

ምስጋናዬ ከልብ ነው። ኑሩልኝ የኔዎቼ።

 

ወስጤን ከሽኖ ጌጠኛ ያደረገው፤ የውበቴ ማርዳ፤ የመንፈሴ ዘውድ፤ ኢትዮጵያዊነት ይኑር ለዘለዓለም!

ፈተናን ከመፈጠሩ በፊት አሸንፎ የተፈጠረ ማንነት – ኢትዮጵያዊነት!

 

 

እግዚአብሄር ይስጥልኝ።

የአሰብ ጉዳይ:- “ጦርነት ፈርተን ግን ሀገራችንን አሳልፈን አንሰጥም”–ከአብርሃ ደስታ

$
0
0

 

ገና በጠዋቱ “ዓሰብን ማስመለስ አለብን የምትለው እንዴት ነው? ወደ አላስፈላጊ ጦርነትና ደም ማፋሰስ ልታስገቡን ፈለጋቹ?” የሚል አስተያየት አዘል ጥያቄ አገኘሁ።
asab port
መጀመርያ ወደ ጭንቅላታችን መምጣት ያለበት ጉዳይ ‘የዓሰብ ወደብ የማነው?’ የሚል ነው። ዓሰብ የኢትዮጵያ ልአላዊ ግዛት (ንብረት) ስለመሆኑ ታሪካዊ፣ ፖለቲካዊና ሕጋዊ (በዓለም አቀፍ ሕግ መሰረት) ማረጋገጫዎች አሉን። ዓሰብ የኛ ስለመሆኑ የሚያጠራጥር ምንም ምክንያት የለም። ማስረጃዎቹ (ማረጋገጫዎቹ) እዚሁ ፌስቡክ ላይ ባልፅፋቸውም በወደቡ ባለቤትነታችን ጥርጣሬ አይግባቹ። ስለዚህ ጥያቂያችን ፍትሐብሄር ነው።

ሁለተኛ ጉዳይ ዓሰብ የኛ ቢሆንም አሁን ያለው ግን በኤርትራ ቁጥጥር ስር ነው። ንብረት ሃብታችን ተነጥቀናል ማለት ነው። ጥያቄው መሆን ያለበት ‘ዓሰብ ወደብ ለኢትዮጵያ ያስፈልጋል?’ የሚል ነው። መልሱ: ‘አዎ! ያስፈልጋታል’ ነው። የባህር በሯን የተነጠቀች ብቸኛዋ ትልቅ ሀገር ኢትዮጵያ ናት። በአሁኑ ግዜ የባህር በር የአንድ ሀገር የህልውና በር ነው። የህልውና በሩ መዘጋት የለበትም። ስለዚህ ኢትዮጵያ ንብረቷ (ወደቧ) የማስመለስ መብትም ታሪካዊ ግዴታም አለባት።

 

ሦስተኛ ‘እንዴት ነው ወደቡን ማስመለስ የምንችለው?’ የሚል ጥያቄ ማየት ተገቢ ነው። ምክንያቱም ዓሰብ የኢትዮጵያ ቢሆንም በመሪዎቻችን ሐላፊነት የጎደለው ዉሳኔ ምክንያት ለኤርትራ ተሰጥቶ ይገኛል። ‘ወደባችን አለ አግባብ ለኤርትራ በመሰጠቱ ምክንያት ዓሰብን የማስመለስ ጉዳይ ከባድ ሊያደርገው ይችላል’ የሚል ሐሳብ ቢነሳ አግባብነት አለው። ጦርነትም ሊያስከትል ይችላል የሚል ስጋት ሊቀቅ ይችላል።

ግን ማትኮር ያለብን ስለ ጦርነት አይደለም፤ ስለ ዓሰብ ንብረትነት እንጂ። ዓሰብ የኛ መሆኑ ለዓለም አቀፍ ማህበረሰብ ማረጋገጥ (ማሳመን) ይኖርብናል። በዓሰብ ጉዳይ ፅኑ አቋም ይዘን የኢትዮጵያም የኤርትራም ህዝብ እንዲገነዘበው መጣር አለብን። የዓለም ህዝብ ይሁን መንግስትታት ይደግፉናል። ምክንያቱም የባለቤትነት መከራከርያ ነጥባችን ጠንካራ ነው። የዓለም አቀፍ ሕግም ይደግፈናል። ዓሰብ የኢትዮጵያ ስለ መሆኑ የሚመሰክግሩ የተለያዩ ዓለም አቀፋዊ ስምምነቶችም አሉ።

አራተኛ ዓሰብ የኛ መሆኑ ቢናረጋግጥና ለዓለም መንግስታትና ማህበረሰብ ቢናሳውቅ እንኳ እንዴት ዓሰብን መመለስ እንችላለን? የኤርትራ መንግስትኮ ፍቃደኛ አይሆንም፣ ጦርነት ሊነሳ ይችላል … ወዘተ የሚሉ ጉዳዮች መነሳታቸው አይቀርም። ግን ችግር የለውም። ዓሰብ የኛ መሆኑ ካረጋገጥን ‘ንብረታችን መልስልን’ ብለን የመጠየቅ መብት አለን። የኤርትራ መንግስት ፍቃደኛ ላይሆን ይችላል። ጦርነትም ሊከፍት ይችላል።

እኛ ጦርነት አንፈልግም። ሕጋዊ ንብረታችን (ወደባችን) በሰለማዊ መንገድ እንዲሰጠን ነው የምንጠይቀው። አዎ! ጦርነት አንፈልግም። ጦርነት አንፈልግም ማለት ግን ጦርነት ከፍተን በሃይል የሌላ ሀገርና ህዝብ ንብረት አንወርም ማለት እንጂ ጦርነት ፈርተን ልአላዊ ግዛታችን (ሃብታችን) ለሌሎች ሃይሎች አሳልፈን እንሰጣለን ማለት አይደለም። ጦርነት አንፈልግም ማለት ጦርነት እንፈራለን ማለት አይደለም። አዎ! ጦርነት ስለማንፈልግ ሌሎች ህዝቦችን አንወርም። ጦርነት ፈርተን ግን እናት ሀገራችን አናስደፍርም።

ጦርነት ስለማንፈልግ ዓሰብን በሰለማዊ መንገድ የምንረከብበት መንገድ እናመቻቻለን። የኤርትራ መንግስት ጦርነት ሊከፍትብን ይችላል ብለን ግን ሃብት ንብረታችን ከመጠየቅ ወደኋላ አንልም። ጦርነት ተፈርቶኮ የሀገር ግዛት አሳልፎ አይሰጥም። ጦርነት ተፈርቶኮ ልአላዊ ግዛትን ከማስከበር ወደኋላ አይባልም። በባድመ ጉዳይ ጦርነት ዉስጥ የገባነው ጦርነት ስለምንፈልግ ሳይሆን ልአላዊ ግዛታችን የማስከበር፣ ሀገራችን ከወራሪዎች የመከላከል ሀገራዊ ግዴታ ስላለብን ነው። ጦርነት ፈርተን እጃችንና እግራችን አጣጥፈን የባድመን መሬት ለሻዕቢያ ወራሪዎች አሳልፈን አልሰጠንም።

(በኋላ በፖለቲካዊ ዉሳኔ፣ በመሪዎቻችን ግድየለሽነት ምክንያት ባድመን መስዋእት ከፍለን በደም አስመልሰን ሲናበቃ በእስክርቢቶ ለወራሪዎች ተላልፎ ተሰጠ እንጂ። በጦርነት የተመለሰ ንብረት በድርድር ሲከሽፍ በታሪክ ለመጀመርያ ግዜ ነው። የባድመ ጉዳይ …!)

ምንም እንኳ ጦርነት ባንፈልግም ሃብት ንብረታችን ግን አሳልፈን አንሰጥም። ጦርነት መስዋእት ይጠይቃል። ግን ለሀገራችን መስዋእት ብንከፍል ችግሩ ምንድነው? ለሀገራችንኮ መሞት አለብን። በምንክያት መስዋእት መሆን እንቻላለን። ደግሞኮ ኢህአዴጎች የዓሰብን ጉዳይ ስናነሳባቸው ‘ጦርነት ናፋቂዎች’ ይሉናል። እኔ ግን ለሀገር መስዋእት ብንከፍል ጉዳት የለውም ባይ ነኝ። እንኳንም ለሀገራችን ኢትዮጵያ ለሶማሊያም እየሞትን ነው። ይቅርታ ለሶማሊያም እየሞትን አይደለንም። ምክንያቱ ላልታወቀ ጉዳይ ነው በሶማሊያ እየሞትን ያለነው። ወታደሮቻችን በሀገረ ሶማሊያ እየሞቱ ያሉ ለምን ዓላማ ነው? ዜጎቻችን ዓላማው ለማይታወቅ ጉዳይ በሶማሊያ ከሚሞቱ ለሀገራችን ቢሞቱ አይሻልም ነበር? ኢህአዴጎች ‘ጦርነት ጥሩ አይደለም’ ይሉናል። ጦርነት ጥሩ አለመሆኑ ቢያውቁ ኑሮ ለምን በሶማሊያ ያሉ ወገኖቻችን ወደ ሀገራቸው አያስገቡም?

አዎ! ጦርነት ጥሩ አይደለም። በተቻለ መጠን ጦርነትን ማስወገድ አለብን። ጦርነት ፈርተን ግን ሀገራችንን አሳልፈን አንሰጥም።

አሜን!

የአርቲስት ፈለቀ ጣሴ ሥርዓተ ቀብር በደብረሊባኖስ ገዳም ተፈጸመ

$
0
0

feleke tasse
(ዘ-ሐበሻ) በተለያዩ ትያትሮች እና ፊልሞች ላይ በመተወን የሚታወቀውና ባለፈው ረቡዕ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው አርቲስት ፈለቀ ጣሴ የተወለደው በ1962 ዓ.ም ነበር። ለአጭር ጊዜ ብቻ የታመመው ይኸው ተወዳጅ አርቲስት ሥርዓተ ቀብሩ በደብረሊባኖስ ገዳም ተፈጽሟል።

በአዲስ ከተማ ትምህርት ቤት ትያትር እንደጀመረ የሚነገርለት አርቲስት ፈለቀ በአርቲስት ተስፋዬ አበበ ከሰለጠኑ ተዋንያኖች መካከል አንዱ ለመሆንም በቅቷል። ከዛም በሃገር ፍቅር ትያትር

- የጣር ሳቅ፣
- የቀለጠው መንደር፣
- ጥምዝ፣
- የወፍ ጎጆ፣
- ባልቻ አባነፍሶ፥
በአዲስ አበባ ትያትርና ባህል አዳራሽ፦
- ቀስተ ደመና፣
- የክፉ ቀን ደራሽ፣ የደም ቀለበት፣
- ማዶ ለማዶ፣ ፍለጋ፣
- ጣይቱ፣
- ምርጫው፣
- ሶስና
- የታፈኑ ጩኸቶች በተሰኙና በሌሎችም ትያትሮች ላይ ተውኗል።

ባለፈው ረቡዕ በተወለደ በ44 ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው አርቲስት ፈለቀ ጣሴ፤ከትላንት በስቲያ በደብረሊባኖስ ገዳም፣ ወዳጅ ዘመዶቹ በተገኙበት የቀብር ሥነሥርዓቱ ተፈፅሟል፡፡

ይኸው ተወዳጅ አርቲስት በፊልም ደረጃ “ሰርፕራይዝ” እና “ጥቁር ነጥብ” በተሰኙ ፊልሞችም ላይ መስራቱ ይታወቃል፡፡

ነብስ ይማር።


አቶ ሽፈራው ጃርሶ ባጋጠማቸው የመኪና አደጋ እስካሁን በህክምና ላይ ይገኛሉ ተባለ

$
0
0

 

(ዘ-ሐበሻ) በሚኒስትር ማዕረግ የስኳር ኮርፖሬሽን ዋና ዳይሬክተር አቶ ሽፈራው ጃርሶ ከ2 ሳምንት በፊት ባጋጠማቸው ከባድ የመኪና አደጋ የተነሳ እስካሁን በህክምና ላይ እንደሚገኙ የውስጥ አዋቂ ምንጮች ገለጹ።

shiferaw jarso

ከ2 ሳምንታት በፊት በደቡብ ኦሞ አካባቢ እየተገነባ የሚገኝን የስኳር ፕሮጀክትን ለመጎብኘት ጠ/ሚ/ር ኃይለማርያም ደሳለኝን ጨምሮ በርካታ የመንግስት ባለስልጣናት ወደ ዛው አምርተው እንደነበር የገለጹት ምንጮች በአቶ ሽፈራው ጃርሶ መኪና ላይ በደረሰ አደጋ ባለስልጣኑ ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰባቸው ለማወቅ ተችሏል።

አቶ ሽፈራው ላይ አደጋው የደረሰው በወላይታ አካባቢ እንደሆነ ያስታወቁት ምንጮቹ እንደ አደጋው አሰቃቂነት ሕይወታቸው መትረፉ በራሱ ትልቅ እድል ነው። በአካባቢው ሄሊኮፕተር ተልኮ ወዲያውኑ ወደ ጦር ሃይሎች ሆስፒታል እንደመጡና ህክምናቸውን በዛው እየተከታተሉ እንደሚገኙ ምንጮቹ ጠቅሰው ባለስልጣኑ እስካለፉት 2 ቀናት ድረስ በጦር ኃይሎች ሆስፒታል ህክምና ላይ እንደሚገኙ አስታውቀዋል። ካለፉት 2 ቀናት ወዲህ ያለውን የአቶ ሽፈራው ጃርሶን ሁኔታ ዘ-ሐበሻ ለማጣራት ሞክራ አልተሳካላትም።
ዘ-ሐበሻ ድረገጽ ላይ የሚከተለው ግጥም የዋልድባ የመታረስ ዜና የተዘገበ ሰሞን ወጥቶ ነበር። ግጥሙን ከትውስታ እዚህ አምጥተነዋል።

ስኳር ገዳም ገባ

እያንገራገረ ህዝቡ እያባባ
አበው እያዘኑ ወጣት እያነባ
እየተቃወሙ እየጮሁ እነ አባ
ዜናው በዓለም ዓቀፍ እየተስተጋባ
ድንገት ሳይታሰብ ስኳር ገዳም ገባ
ከፍ ከፍ ብሎ ለዚያውም ዋልድባ
ሲጠፋ ሲሰወር ሲደበቅ ቆይቶ
በአቋሙ ጠንክሮ በአቋሙ ጸንቶ
አመክሮ ሳይዝ ድንገት ገዳም ገብቶ
ጣፋጭ የነበረው ሊመር ነው ከቶ
ለሱ የሚስማማ ስንት ቦታ ሞልቶ
ስኳር እሳት ሆኖ ከገበያ ጠፍቶ
ሊቀመጥ ነው አሉ መቃብር ቤት ገብቶ
ምን ይውጥሽ ይሆን ከእንግዲህ መርካቶ
አባቶ ች ምን አሉ በዋልድባ ያሉ
በአባቶች አጽም ላይ ሸንኮራን ሲተክሉ
ከተቀበረበት እየፈነቀሉ
በደም የበቀለ ሸንኮራ ሊበሉ
በውሳኔ ጸንቶ
ኸረ እግዚኦ በሉ!
ይሄስ ጥሩ አይደለም
ከአቅም በላይ ሆኖ ህዝቡ ቢበደለም
አባቶች ዝም በሉ ይረሱት ግድ የለም
ዋልድባ በጾሙ ምነው ተፈተነ
በገዳሙ ልማድ ትንሽ ከታዘነ
ጸሎቱ እንደወጉ ከተከናወነ
ውሎ አድሮ ይሟሟል ስኳር ስለሆነ
4/3/12 voa radio
ከአዜብ ሮባ

Health: በኢትዮጵያ የዲያሌስስ (የኩላሊት እጥበት) ህክምና ፈተና ገጥሞታል

$
0
0

ከአስመረት ብስራት / በመንግስት ሚዲያዎች የቀረበ ጽሑፍ

በድሬዳዋ በንግድ ስራ ላይ ተሰማርታ ትሰራ የነበረችው ወይዘሪት ሰላማዊት ወንድሙ የኩላሊት ችግር ስለገጠማት ለህክምና ወደ አዲስ አበባ መጥታ በቅዱስ ዻውሎስ ሆስፒታል ክትትል ከጀመረች ወራትን አስቆጥራለች። ከወራት የህክምና ክትትል በኋላ ኩላሊቷ ስራ ማቆሙን የተረዱት ሀኪሞች የዲያሌስስ (የኩላሊት እጥበት) ህክምና እንዲትከታተል ያደርጋሉ። ሆኖም ለዲያሌስስ ህክምናም ሆነ በየእለቱ ለሚታዘዙ ውድ መድሃኒቶች የሚያወጡት ወጪ ከአቅማቸው በላይ ሆኗል።

(ወ/ሮ ሰላማዊት ወንድሙ)

(ወ/ሮ ሰላማዊት ወንድሙ)


ጥሪታቸውን አሟጠው የእህታቸውን ህይወት ለመታደግ የሚጥሩት የሰላም እህትና ወንድሞች የዲያሌስስ ህክምና ለማግኘት ከቀበሌ የሚሰጥ የነፃ ህክምና ወረቀት እንኳን እንደማያገለግል ነው የሚናገሩት። ሌሎች ከፍተኛ ቀዶ ህክምና የሚፈልጉና ውድ የሚባሉት ህክምናዎች የገንዘብ አቅም ለሌላቸው በነጻ የሚሰጥ ቢሆንም ለዲያሌስስ ህክምና ይህ እድል ያለመሰጠቱን ምክንያት አልተረዳነውም ይላሉ። ከዚህም በተጨማሪ ለበሽታው የሚታዘዙ መድሃኒቶች በሀገር ውስጥ አይገኙም። ከተገኙም በኮንትሮባንድና በሌሎች ህገወጥ መንገዶች የገቡ በመሆናቸው ከአንድ እስከ ሁለት ሺ ብር ድረስ ማውጣትን ይጠይቃሉ፡፡ ሁሉም ነገር ተስፋ አስቆራጭና የመኖር ተስፋን የሚያጨልም መሆኑን የምትናገረው ሰላማዊት ቀሪውን ቤተሰብ ችግር ውስጥ ላለመክተት «ምናለ ሞቴን ባፋጠነው» እያለች እንደምትፀልይ ነው የገለፀችው።

ለመዳን ተስፋ አድርጎ ጥሪትን ሟሟጠጥ፤ ከዚያም ተስፋ መቁረጥና ለቋሚው በመጨነቅ እረፍት የሚያሳጣ ችግር ውስጥ መውደቅን የሚያመጣው የኩላሊት ስራ ማቆም ችግር የብዙዎች ፈተና እየሆነ ነው። በህክምናው ውድነት ሳቢያም የበርካቶች ህይወት እያለፈ እንደሆነ በሰፊው ይነገራል።
ሰላማዊትና እሷን መሰሎች ከግሉ የህክምና ተቋም ቢቀንስ ብለው በብቸኝነት የዲያሌስስ ህክምና ወደሚሰጥበት ቅዱስ ዻውሎስ ሆስፒታል መጥተዋል። ቶሎ የመዳን ተስፋ ኖሯቸው ህክምናውን ከጀመሩ በኋላ እጅ ሲያጥር ጭንቅ ሆኗል፡፡

ሌላዋ ከወንጪ አካባቢ የመጣችው ታደሉ ናታ የሀያ አመት ወጣት ናት። ይህች ወጣት ከማህፀን ውጪ ያለ እርግዝና ገጥሟት ወደ ወሊሶ ሆስፒታል ትሄዳለች። እዚያ የቀዶ ህክምና ተደርጎላት ከስቃይዋ ብዙም ሳታገግም ድንገተኛ የኩላሊት ስራ ማቆም ችግር ይገጥማትና በአስቸኳይ የህክምና እርዳታ ካላገኘች ህይወቷ ሊያልፍ እንደሚችል ተነገሯት ወደ ሆስፒታሉ ከመጣች በኋላ ትንፋሽ አግኝታለች።

ይህች ወጣት ከጭንቅ ብትገላገልም በርካታ እሷን መሰል ዜጎች በድንገተኛ የኩላሊት ስራ ማቆም ችግር እየተጠቁ በገንዘብ አቅም ማጣት የተነሳ እርዳታ ሳያገኙ ቤታቸው ሄደው ይሞታሉ፡፡ በግል ሆስፒታሎች በከፍተኛ ገንዘብ የሚታከሙትም ቢሆኑ ቤትና ንብረታቸውን ሸጠው ገንዘቡ ሲያልቅ ህክምናቸውን ያቋርጣሉ ወደማይቀረው ሞትም ይሄዳሉ። ቀሪው ቤተሰብም በድህነት ይማቅቃል።

ለመሆኑ በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል እየተሰጠ የሚገኘው የዲያሊስስ ህክምና ምን ይመስላል? በህክምና ወጪው ላይስ ምን አስተያየት አለ? ስንል በሆስፒታሉ የኩላሊት ህክምናና የዲያሌስስ ክፍል ሃላፊ የውስጥ ደዌና የኩላሊት አስፔሻሊስት ዶክተር ሞሚና መሃመድን አናግረናል፡፡
ዲያሌስስ ማለት በከፊል የኩላሊትን ስራ ተክቶ የሚሰራ ህክምና ነው። በዲያሌስስ የሰውነትን ቆሻሻ የማጣራት፤ በሰውነት ውስጥ ያለን ውሃ የመመጠን፤ የኩላሊትን አቅም ማሳደግና ኤሌክትሮ ላይት የመመጠን ሥራ ይሰራል ይላሉ ዶክተር ሞሚና።

ወጣት ታደሉ ናታ

ወጣት ታደሉ ናታ


ሆስፒታሉ ብቸኛው የመንግስት ተቋም በመሆን ይህንን አገልግሎት መስጠት የጀመረው ከግብፅ መንግስት በተገኘ እርዳታ ከ5 ወራት በፊት ነው። ማሽኖቹም ሆነ አላቂ እቃዎች በእርዳታው የተገኙ ናቸው። በመሆኑም ካለው የአቅም ውስንነት የተነሳ በአሁኑ ወቅት ህክምና የሚሰጠው አጣዳፊ የኩላሊት ችግር ማለትም መዳን የሚችለውን የኩላሊት በሽታ ያጋጠማቸውን ብቻ ነው። ይህም በመሆኑ ሆስፒታሉ የኩላሊት ንቅለ ተከላ የሚያስፈልግ ደረጃ ላይ የደረሱትን ህሙማን ለመርዳት አይችልም።

ዶክተር ሞሚና እንደሚሉት እስካሁን በዚህ አገልግሎት ከስልሳ በላይ ታካሚዎች እፎይታ አግኝተው ወደ ቤታቸው ተመልሰዋል። በብዛት አገልግሎቱን የሚያገኙት ደግሞ ታካሚዎች በእርግዝናና በወሊድ ምክንያት ችግር የገጠማቸው እናቶች ናቸው።
ህክምናውን ካገኙ በኋላ በርካቶች ወደ ቀድሞ ጤናቸው ቢመለሱም አገልግሎት ሳያገኙ ተመልሰው ህይወታቸው ያጡ ሰዎች መኖራቸውንም ይናገራሉ። እናም ሁሉም የኩላሊት ህሙማን እርዳታ የሚያገኙበት መንገድ መመቸቻት እንደሚኖርበት አስምረውበታል —ዶክተሯ፡፡ ህመሙ በየጊዜው እየጨመረ እንደመሄዱ መጠን ህክምናው የጠብታ ያህል ከመሆን ያለፈ ከችግሩ አንፃር ይህ ነው የሚባልና የሚጠቀስ እንዳልሆነም ይናገራሉ።

በአሁኑ ወቅት ለኩላሊት ስራ ማቆም ምክንያት የሆኑት ስኳርና የደም ግፊት ወረርሽኝ በሚመስል መልኩ እየተከሰቱ ከመሆኑ አንፃር ይህ በሽታ በስፋት እየተከሰተ የሚሄድ መሆኑን የሚናገሩት ዶክተር ሞሚና በርካታ ሰዎች የበሽታው ሰለባ ሆነው በሳምንት ሶስቴ ኩላሊታቸው እንዲያጣረ በሚያግዝ መሳሪያ በከፍተኛ ክፍያ እየታከሙ መሆኑን ያብራራሉ፡፡

በሆስፒታሉ የኩላሊት የንቅለ ተከላ ህክምና የሚያስፈልጋቸው ህሙማንን እንደማያስተናግድ ያነሱት ዶክተሯ ይህም በመሆኑ በርካቶች በሆስፒታሉም ሆነ በግል ሲታከሙ ይቆዩና ገንዘባቸው ሲያልቅ ንቅለ ተከላውም ሳይደረግላቸው ህይወታቸው ያልፋል ይላሉ። እሳቸውም በዚህ ሁኔታ በከፍተኛ ሁኔታ ስሜታቸው እንደሚነካ ይናገራሉ «አንዳንዴ…» ይላሉ ዶክተር ሞሚና «አንዳንዴ ይህ ህክምና ባይኖርስ! ብዬ አስባለሁ። ጥሪት ጨርሶ በጭንቀት ከመሞት በሰላም ማሸለብ ይሻላል እላለሁ» ብለዋል።
ይህ ችግር ከመከሰቱ በፊት ህብረተሰቡ በቅድመ መከላከል ስራ ላይ ቢያተኩር የሚሻል መሆኑን የተናገሩት ዶክተር ሞሚና የበሽታው መነሻ ከሆኑት ዋናዎቹ ምክንያቶች የስኳር በሽታ በአለም አቀፍ ደረጃ ግንባር ቀደም ሲሆን ሁለተኛው የደም ግፊት፤ ሶስተኛው ደግሞ ከበድ ባሉ ኢንፈክሽኖች መነሻነት የሚጀምር እንደመሆኑ ህብረተሰቡ እነዚህ ችግሮች እንዳይኖሩ በማድረግ መከላከል ይኖርበታል ሲሉ ይመክራሉ።

ባለሙያዋ እንደሚሉት በሽታው በአብዛኛው ምልክት አያሳይም። ምልክት የሚያሳየው መጨረሻ ላይ ማለትም ኩላሊት ስራውን አቁሞ ከባድ እርዳታ የሚያስፈልግበት ወቅት ላይ ነው። ታዲያ በዚህ ጊዜ ችግሩ ተከስቶ ከማይወጡበት ኢኮኖሚያዊም ሆነ አካላዊ ችግር ከመዳረግ በፊት በአመጋገብ በማስተካከል ራስን ማዳንም ማቆየትም እንደሚቻል ሙያዊ ሃሳባቸውን ያጋራሉ።

ማንኛውም ሰው ጤናማ አኗኗር ሥርዓትን በመከተል ማለትም የአካል ብቃት እንቅስቃሴዎች በማድረግ፣ አትክልት በመመገብ ግፊት ሰኳርና ሌሎች በሽታዎችን በመከላከል በተጓዳኝ ከሚመጡ ችግሮች ራሱን መከላከል ይችላል፡፡
በሆስፒታሉ ሊድን የሚችለውን የኩላሊት በሽታ ህክምና መስጠት መጀመሩ ካልቀረ የተወሰነውን ህብረተሰብ ማገልግል የሚቻልበት አቅም እንዲፈጠር ማድረግ ይገባል የሚል እምነት አላቸው ዶክተር ሞሚና። በተጨማሪም ሆስፒታሉ ባለው አቅም በነፃ ህክምና ለሚገባቸው ሰዎች አገልግሎት ቢሰጥ የተሻለ እንደሚሆንም ይናገራሉ። በሌላ በኩልም ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የበሽታውን አሳሳቢነት በመረዳት ተኩረት ቢሰጥ መልካም ነው የሚል አስተያየትም ሰጥተዋል፡፡

የሆስፒታሉ ፕሮቮስት ዶክተር መሰፍን አርአያ በበኩላቸው በሆስፒታሉ የኩላሊት እጥበት ህክምና ተጀምሮ አገልግሎት መስጠት ከጀመረ ወራትን እንዳስቆጠረና ለአንድ ጊዜ አገልግሎትም አንድ ሺ ብር እንደሚከፈል ተናግረዋል። ይህም በእርዳታ በተገኙትና ለዓመት በሚያገለግሉት ስድስት የማጣሪያ መሳሪያዎችና ሌሎች ግብአቶች እንደተጀመረ ገልጸው እንዴት መጠቀም እንደሚገባ በሆስፒታል ደረጃ ተነጋግረው መወሰናቸውን ያመለክታሉ። በዚህም በርካታ ተከታታይ ህክምና ያላቸው ህሙማን እንዳሉ ቢታወቅም ያለውን ለድንገተኛና ለአጣዳፊ የኩላሊት ስራ ማቆም ችግር ለማዋል ውሳኔ ላይ ተደርሷል።

ለአጣዳፊው ህመም የህወይት አድን አገልግሎት መስጠት የተጀመረ ሲሆን ይህም በግል የህክምና ጣቢያዎች ከሚከፈለው ባነሰ ክፍያ የሚሰራ ነው። ይህም አገልግሎቱ ቀጣይ እንዲሆን ለግብዓት ማሟያ እንዲሆን ታስቦ የተደረገ ነው፡፡ ስራው ከተጀመረ በኋላ አጥጋቢም ባይባል ውጤታማ አገልግሎት መሰጠቱን የተናገሩት ዶክተሩ ችግሩ በነፍሰ ጡር እናቶችና ህፃናት ላይ በሚያጋጥም ወቅት ገንዘብ ኖራቸውም አልኖራቸው አገልግሎቱን እንደሚያገኙ ያብራራሉ። በመሆኑም በተደረገላቸው ህክምና የተነሳ በርካታ ነፍሰጡር እናቶችና ከወሊድ ጋር በተያያዘ ችግር የገጠማቸው ሴቶች ዳግም ኩላሊታቸው አንሰራርቶ እፎይታ አግኝተዋል።

«አቅም የሌላቸውን ሰዎች በምን መልኩ እናስተናገዳቸው? ለሚለው ጥያቄ ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ጋር ተነጋግረን በቀጣይ አገልግሎቱ በጣም በአነስተኛ ክፍያ እንዲሰጥ፤ ያንንም መክፈል ለማይችሉ ደግሞ በነፃ ተሰጥቶ በየጊዜው ሪፖርት እየተደረገ እንደሚወራረድ ቃል ተገብቶ ውሳኔ በመጠባበቅ ላይ ነን» ሲሉ የህክምናው ውድነት የፈጠረውን ችግር ለመፍታት መፍትሄ መቀመጡን ተናግረዋል።

በሌላ በኩል ህክምናው ወድ ከመሆኑ የተነሳ አቅም ያለውም ሆነ የሌለው የነፃ ህክምና ወረቀቱን በተለያየ መልኩ በማውጣት አገልግሎት ለማግኘት እንደሚጥር ተናግረው ይህንን ማጣራት ካልተቻለና ትክክለኛው ችግረኛ ሰው ካልታወቀ ከዚህ በፊት ስራውን ሞከረውት በገንዘብ ማጣት ምክንያት እንደተዘጉት ሆስፒታሎች አይነት እጣ ፋንታ ሊገጥም እንደሚችል ስጋታቸውን አስቀምጠዋል ።

ችግሩ ሰፊና አሳሳቢ እንደመሆኑ ሊያግዙ የሚችሉ ድርጅቶችን (ስፖንሰሮችን) በማፈላለግና አቅሙ ያለው ሰውም ተገቢውን ክፍያ እንዲከፍል በማድረግ የህይወት አድን ስራው እንደሚቀጥል ተናግረው ዲያልስሱ ለእድሜ ልክ የሚያስፈልጋቸው ሰዎችም ተጠቃሚ እንዲሆኑ ይደረጋል ነው ያሉት በረጅም ጊዜ እቅድም የኩላሊት ንቅለ ተከላ ህክምና እንደሚጀመር በመጠቆም።

የሳዑዲ ጉዳይ፡ የአስከሬኑ ሽኝት –ከነብዩ ሲራክ

$
0
0

እጣ ፈንታ …

(ፎቶ ፋይል)

(ፎቶ ፋይል)

ዘመኑ በፈቀደው የአረብ ሃገር ስደትን በኮንትራት ስራ የሳውዲን ምድረ በዳ የባለ ጸጎች ሃገር የረገጠከው ራስክን ደግፈህ ፣ ወላጅ ቤተሰብ፣ ዘመድ አዝማድ ወገኖችህን ለመደገፍ ነበር ። በሳውዲ ቆይታህ በትዕግስት ስታልፍ ያስብከውን ሁሉ ባይሳካም ጋብቻ መስርተህ ሌላዋን የኮንትራት ሰራተኛ ስደተኛ እህትክን ባንድ አቅፈህ ፣ ራስክን በሙያ አንጸህ የተረጋጋ ኑሮን በመኖርህ ላይ እንዳለህ ሳታስበው በውስጠ ደዌ በሽታ ተወጋህ ! ክፉውን ሁሉ የስደት ህይወት በትዕግስት ገፍተህ ደስተኛ ሆነህ ኑሮን ትገፋ እንደነበር አህትህና ባለቤትህ ቅሪት ገላህን ወደ ሃገር ለመሸኘት ለስንብት ስንጓዝ አጫውተውኛል። ፎቶህን አይቸ በህይወት ዘመንህ በአንድ አጋጣሚ አውቅህ እንደነበር ሳውቅ ደነገጥኩ ፣ ድንጋጤየን ዋጥኩት ! ነፍስህን ይማረው ወንደም አለም

ስንብት …
ወደ አልሰሜ እናትና ዘመድ አዝማድ የሚላከውን በድን አካልክን ለመሰናበት በሔድንበት አጋጣሚ በዚያው የሬሳ ማቆያ ጽህፈት ቤት ሃላፊውን ስንት የኢትዮጵያውያን ሬሳ አለ ብየ ጠየቅኩት ። የደስደስ ያለው አረብ ሲመልስ ” አሁን እንኳን ብዙ አይደሉም ፣ ከዚህ በፊት ብዙ ነበር ። እዚህ ማቆያ ውስጥ ፈላጊ ያልመጣላቸው ከአስር የማያንሱ የኢትዮጵያውያን ሬሳ ይገኛል!” ሲል ዘርዘር አድርጎ መለሰልኝ ። ጠያቂ ስለሌላቸው ፣ ስማቸው ስላማይገኝ ሬሳዎች እጣ ፈንታ ብቻ ሳይሆን የሬሳው ማንነት ታውቆ የሚያስቀብር ጠያቂ ከጠፋ በማዘጋጃ ቤትና በፖሊስ እንደሚቀበሩ ያጫወተኝ … ሊሰሙት የሚከብድ እውነት !

ከሬሳው ማስቀመጫ መስሪያ ቤት ሃላፊ ጋር ላፍታ ባደረግነው ቆይታ የሰማሁት አሳዛኝ ነባራዊ ሁኔታ ውስጤን አደማው ። ሬሳውን ወደ ምንቀበልበት የጓዳ በር ለየራሳችን ቆዛዝመን ደረስን: ( ታሞ ፣ እህት ሚስቱ አስታምመውት ፣ ማንነቱ ታውቆ እና ወደ ሃገር መላኪያ ገንዘብ ተገኝቶ ዛሬ ወደ ሃገር ለመሄድ ተዘጋጅቷል ፣ ከምሽቱ 9:45 … የብርቱ ወዳጀ አብሮ አደግ ከፈን ከተቀመጠበት ማቀዝቀዣ ወጣ … በተዘጋጀው የእንጨት ሳጥን ሆኖ ወደ አንቡላንስ ከመሸኘቱ በፊት በስትሬቸር እየተገፋ መጣና ለስንበት ፊቱ በአንድ የፊሊፒን የሬሳው ክፍል ሰራተኛ ተገለጠ … ያ ዘንካታ አይኑን ጨፍኖ ታጋድሟል …አንጀንታቸው የሚላወሰውን እህት ፣ ሚስት፣ ጓደኞች እና ጎረቤቶች ሃዘናቸውን እንደፈለጉ ጮኸው በማይገልጹበት ግቢ የወንድማቸውን በድን ተሰናበቱት … በሬሳው ክፍል ሃላፊ ባጫወተኝ አሳዛኝ ታሪክ ተጽናንቸ የነበርኩት እኔም እህት የወንድሟን ፣ ሚስት የባሏን ግንባር እየሳሙ በታመቀ የሃዘን ስሜት ድምጻቸውን አርቀው እያነቡ ሲሰናበቱት ሳይ ብርክ ያዘኝ !

ሽኝት …

በእርግጥም እኒህኞቹ ወገኖችም ሆኖ ታሞ አስታመውት የሞተው ወንደም እድለኛ ነው! ነገ የሃገሩን አፈር ፣ ታሞ እያለ እናቱን ናፍቆ ሁለቴ ለመሄድ ተነስቶ በተመለሰበት አውሮፕላን ዛሬ በድኑ በውድ ዋጋ ተጭኖ ይደርሳል ! እናት እና ልጅ ተነፋፍቀው አልተገናኙም: ( እናም አልሰሜ እናት አለም ነገ ሬሳ ለመቀበል በጠዋት መርዶ ይጠብቃታል !

ህይወት እንዲህ ነው የሞተውን ነፍስ ይማር ! እናት እና መላ ቤተሰብ ጽናቱን ይስጣችሁ ሌላ ምን ይባል?

ሌላ አሳዛኝ ታሪክ ትረካ በቪድዮ

የሳዑዲ ጉዳይ፡ እድለኛው አስከሬን የሃገሩን አፈር ቀመሰ

$
0
0

ነብዩ ሲራክ (ከሳዑዲ አረቢያ)

ወላጅ እናት ወዳጅ ዘመድ ጓደኞች አስከሬኑን በክብር ተቀብለው ፣ አልቅሰው ተላቅሰው በቀጨኔ መድሐኒአለም ጓሮ የትናንቱን ህያው ካሱ በጋሻው ወንድሜነህ የሃገሩን አፈር ዛሬ አቃመሱት: ( እህትና ሚስት እዚህ ጅዳ በሃዘን ተቆርፍደው ድምጻቸውን ከፍ አድርገው እንዳያለቅሱ እየተሳቀቁ ከእናት ጋር በስልክ ተላቅሰው አይወጣ የለም ፣ እርማቸውን አወጡ::

kassu begashaw አብሮ አደጎቹ እህቱና ውድ ባለቤቱ “ማሙሽ “እያሉ የሚያቀማጥሉት ወንድም ለሃገሩ መሬት በወላጅ ዘመድ አዝማድ ተለቅሶለት በወግ ማዕረግ የሃገሩን አፈር የቀመሰ እድለኛ ነው ። ማንነታቸው ሳይታወቅ ቀባሪ ፈላጊ አጥተው ወይ ሞቱ ተብሎ ወላጅ ዘመድ አዝማድ የሌላቸው አስከሬኖችን እጣ ፈንታ ትናንት የአስከሬኑ ሃላፊ አጫውቶኛልና ወደ ሃገሩ ገብቶ በወግ በማዕረግ ለተቀበረው ማሙሽ ሳይሆን ለራሴ እና ለቀረነው ማዘኑ ይቀለኛል …

ማሙሽ በሽዎች የምንቆጠር ለፍቶ አዳሪ ፣ ሩቅ አሳቢ ቅርብ አዳሪ ዜጎች ሁሉ ምሳሌ ነው ! ማሙሽ ከብዙዎች ጥቂት እድለኞች የሚሆነው ያሰበው ተሳክቶለት ሳይሆን በርሃ ላይ ያለ ቀባሪ አሸዋ በልቶት ባለመቅረቱ ሲሆን ብዙ ሳይታወቁ የጠፉትን እንድናዘክርና የስደትን አስከፊነት የሚያስረዳን ጥሩ ምሳሌ ነው ! ዛሬ ማሙሽ አይሰማም፣ አያይም ፣ አይናገርም … እድለኛው አስከሬን የሃገሩነወ መሬት ቀምሷል … ትዝታው ግን በቤተሰብ በወዳጅ ዘመዶቹ ዘንድ እስከወዲያኛው ይታወሳል!

ከልጅነት እስከ እውቀት አብሮ ያደገው ወዳጀ ፍጹም ከሃዘን ተነስቶ በጻፈው መልዕክቱ “የተሸኘውን አስከሬን ተቀብለን አፈር አለበስነው !” ብሎ የጻፋትን ልብ የምትነካ ማስታወሻ ከዚህች አጭር መግቢያ ጋራ የማሙሽን ፎቶ አጅቤ ላጋራችሁ ግድ አለኝ

” የተሸኘውን አስከሬን ተቀብለን አፈር አለበስነው++++++

•••••••• ሞት ክፉ ነው! በጣም ክፉ! የክፉዎች ሁሉ ክፉ!

•••••••የዛሬን አያድርገውና አብሮ አደግ ጓዴ የራሱንና የእናቱን እንዲሁም የእህቶቹን ህይወት እለውጣለሁ ብሎ ነበር ከሀገሩ የተሰደደው። በልቡም ትልቅ የመሆን ተስፋን ሰንቆ ነገውን በብርሐን ሊሞላ አስቦ ነበር ከቤት አወጣጡ። ግና የሃሳቡን ሳይሞላ፤ የልቡን ሳያደርስ ሞት ቀደመው።
••••••••• አዎ ደግሜ እናገራለሁ ሞት ክፉ አረመኔ ነው!
ሲመጣ ዱካው የማይሰማ፤ ሲሄድ ጥላው ከሰው ልብ አልፎ በሀገር ላይ ሁላ የሚያጠላ የሆነ መዐት ነገር። ሞት የአንድን ሰው ህይወት ነጥቆ ሲሄድ ብዙዎች በህይወት ያሉትን ደግሞ ቅስም የሚሰብር፤ ልብ የሚያደማ እጅግ ከፍተኛ የሆነ የክፋት ሀይልን የተላበሰ ደመኛ ነው።
•••••••••• ዛሬ ይህ ክፉ፥ እጣውን በጓዴ ላይ ጣለና ለፍቶ አዳሪውን፣ እናቱን ወዳጁን የእህቶቹ መከታውን ከቤተሰቡ ነጥሎ ከጓደኞቹ ለይቶ ወሰደው።
•••••••••የወዳጄ ሞት ልቤን ክፉኛ አሳዝኖታል።

ግን•••ግን ሐዘን እኔን ጓደኛውን እንዲህ ያሳመመኝ ያቺ የወለደችው እናቱን እንዴት አርጓት ይሆን?

አብሬው አንድ ሰፈር ስለተወለድኩ የጓዴ ሀዘን እንዲህ አንጀቴን የበላው••• አብረው በአንድ ቤት ተወልደው ያደጉት እህቶቹን የወንድማቸው ሀዘን እንዴት አርጓቸው ይሆን?

•••••አምላክ ሆይ ከሰፊው እጅህ ላይ ብዙ ፀጋዎች እንዳሉ አውቃለሁና እባክህ ለእናቱና ለቤተሰቦቹ ይህንን ከባድ የሀዘን ወቅት ያልፉት ዘንድ ከልባቸው ላይ መፅናናትና መቻልን አኑርልኝ።

++ማሙሽዬ አምላክ ነፍስህን በገነት ያኑራት++

አብሮ አደግህ
ፍጹም አረፋይኔ ” አዎ ሌላ ምን ይባላል ። ሞት ክፉ ነገር ነው!
ለመላ ወዳጅ ዘመድ እግዚአብሔር ጽናቱን ይስጣችሁ!

ነቢዩ ሲራክ

አባጣለው ገብሬና ጓደኞቹ፦(ጌታቸው ከሰሜን አሜሪካ)

$
0
0

(ጌታቸው ከሰሜን አሜሪካ)

ዓመተ ምህረቱንና ወሩን ለጊዜው አላስታውስውም።ድርጊቱ የተፈጸመ ሰሞን ወሬው በየአቅጣጫው በሰፊው ይወራ ነበር።ጉዳዩ ግን የሀገር ድንበር ጉዳይ ነበር።ቦታው ምዕራብ ጎንደር አርማጭሆ ወረዳ ከሱዳን ጋር በሚያዋስነው ሰበካ(አጥቢያ) ወዲ ከውሊ ፈሸካ ከምትባል ቀበሌ የሱዳን ጦር ካምፕ አደረገ የሚል ወሬ የሰሙ ትውልዳቸው እዛው አርማጭሆና ጠገዴ የሆኑ አራት ሰዎች(ገብሬ ተወልደመድህን፤ድረስ ዓይናለም፤አወቀ ዋናሁንና ሌላ አንድ ሰው) መሬቱ የኢትዮጵያ ነው ።የሱዳን ጦር ለምን እዚህ መጥቶ ሠፈር በሚለው ጉዳይ ተቆጥተው ጦሩን መግጠምና ካምፑን ማቃጠል አለብን የሚል አቋም ላይ ደርሰው ተኩስ ከፈቱ።እንዳሉትም የሱዳንን ጦር ሠራዊት ክፉኛ ጎድተው ካምፑን አቃጥለው ክቡር መስዕዋትነት ከፍለው የሀገራቸውን ድንበር አስከብረው አልፈዋል።ሲባል እንደሰማሁት አባጣለው ገብሬ የተመታው ነብሱ ባልወጣች አንድ የሱዳን ቁስለኛ ጦር ሠራዊት እንደሆነና አባጣለውም የታባትክ እንዲህ ነው የምናደርግ እያለ ሲንጎራደድ እንደሆነ ይነገራል።እነዚህ ትልቅ ታሪክ ሰርተው ያለፉ ኢትዮጵያውያንን ታሪክ እንዲዘክራቸው ይደረግ እያልኩ ከዚህ ባሻገር ይህ የሰሜን ምዕራብ ጎንደር ወሰን ለይስሙላ ካልሆነ በስተቀር መንግሥት ድንበር ጠባቂ ጦር ሠራዊት መድቦ የሚያስጠብቀው ሳይሆን በአካባቢው በሚኖሩት ተወላጆች የጎበዝ አለቃ እየተሾመ በሕዝብና በሕዝብ የግል ብረት ተጠብቆና ተከብሮ መኖሩ የትናንት ትዝታችን ሲሆን ያን ዛሬ ላይ ሆነን ስናስበው ነገሮች ተገላብጠው እናገኛቸዋለን።

 

የዛሬዎቹ ገዥዎች በዱር በነበሩበት ወቅት ከሱዳን ለተደረገላቸው ትብብር የኢትዮጵያ ሀብት የሆነውንና ባጥንትና በደም ተከብሮ የኖረውን ለም መሬት ለሱዳን መስጠት ማለት በሕዝብ ላይ ያላቸውን ንቀትና ኢትዮጵያ ጥቂቶች እንዳሻቸው የሚያደርጓት ብቻ መሆኑ ሳይሆን ትናንት ኢትዮጵያ ከመሐዲስቶች (ድርቡሽ) ጋር ስትዋጋ ንጉሧን አጼ ዮሐንስንና ሌሎች ልጆቿን የገበረችበትን መሬት አስልፎ ለጠላት መስጠት ማለት ገዥዎቻችን ምን ያህል ለትውልድ ፤ለሀገርና ለታሪክ የሚያስብ ጭንቅላት ያልፈጠረላቸው እነሱን ብቻ የሚያስቡ አራዊቶች መሆናቸውን እንድንገነዘብ የሚያደርግ ነው።መሬቱ የኢትዮጵያ ሀብት ነው።በመሬቱ ጉዳይ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሳይመክርበት ኢትዮጵያና ሱዳንን የሚያካልለው ድንበር ድንበሩን በሚያውቁ ሰዎችና የታሪክ ተመራማሪ የሆኑ ሰዎች ሳይሳተፉበት ህወሃቶች ደፍርሰው ባደሩ ቁጥር የመሬት ስጦታ ማበርከት ሸክማቸውን የሚያቀልላቸው መስሎ ቢታያቸውም አንዲት ስንዝር መሬትም ብትሆን ለማንም የመስጠት መብቱ በፍጹም የላቸውም።አዎ! ጦሩ ፤ፖሊሱ ፤ ደህንነቱ በእጃቸው እንዳለ እናውቃለን።የአሰብና ከኤርትራ ጋር ደም ያፋሰሰው ጉዳይ እልባት ሳያገኝ ሌላ ጠብ አጫሪ የሆነ መሰሪ ተንኮል መጎንጎን መታጠፊያውን የተበላሸ ያደርገዋል። እንደ ኃይል የሚመኩበትና ደረታቸውን ያሳበጠው መከላከያውም ሆነ ደህንነቱ ነገ ይናዳሉ።ይህ የማይቀር ነገር ነው።ደርግን ይወድቃል ብሎ ያሰበ አልነበረም ነገር ግን በአፍሪቃ ቀንድ ወደር ያልነበረው ግዙፍ ጦር ፈረሰ።ህወሃትንና ደርግን ለንጥጥር አቅርበን ስንመለከትም በገዳይነታቸው አንድ ቢሆኑም በሀገር ጉዳይ ደርግ ዋዛ አልነበረም። በተወሰነ ደረጃም ቢሆን ደርግ በህዝብ ዘንድ ይሁንታ ነበረው።ህወሃት ከሕዝብ ተነጥሎ ቆሞ በየአመቱ የሀገር ጥፋትን ለምን እንደሚያውጅ በውል ሊመረመረ የሚገባው ጉዳይ ነው።

 

ህወሃት ለሱዳን የሚሰጠውን መሬት በትክክል ሱዳን ትጠቀምበታለች ብሎ አስቦ እንዳልሆነና ሱዳኖች ግብር እየከፈሉ ለከብት ግጦሽ ይጥቀሙበት የነበረ የኢትዮጵያ መሬት እንጅ የሱዳን ይዞታ አለመሆኑን ያውቃሉ።የሚያውቀ ከሆነ ለምን መሬታችን አሳልፈው ይሰጣሉ የሚል ጥያቄ ሊነሳ ይችላል። ይህ ግልጽ ነው የህዋሃትን አጀንዳ ምንድን ነው ብሎ ማየት በቂ ነው። ሱዳን ያላትን ኃይል በሙሉ የተሰጣትን መሬት ለሚያለሙ ጥበቃ መመደብ አለባት ወይም ህወሃት የራሱን መከላከያ ኃይል መመደብ አለበት።ይህ ካልሆነ ገና ኢትዮጵያ ይገባኛል የምትለው መሬት ከሱዳን ሳይመለስ ሌላ ወሰን ዘላ እንድትገባ ማድረግ አካባቢውን ሰላም ለማሳጣትና ደም ለማፋሰስ ካልሆነ መሬትህ ይወሰድብሃል የተባለውን የአካባቢ ሕዝብ ከማንም በላይ ህወሃት ጠንቅቆ ስለሚያውቅ በውጤቱ ማንም ትርፍ እንደማያገኝና በህወሃት ላይ የተጀመረውን የተቃዋሚ ኃይሎች ሥርነቀል የሥርዓት ለውጥ ትግልም ሊያዘናጋ እንደማይችል መገንዘብ ይኖርባቸዋል። በርግጥ እንደዚህ ላለው ቀን የሚሆኑትን ውድ የሀገር ልጆች አስቀድመው ገድለዋቸዋል፤ አስድደዋቸዋል ወይም በሌላ ምክንያት በዚህ ክፉ ቀን ለሕዝብ እንዳይደርሱ ተደርጓል። ይሁን እንጅ «እሳት ከነበረበት ረመጥ አይጠፋም ይባላልንና» ጀግናው የሽንፋ ሕዝብ ፤የመተማ የቋራና የአዳኝ አገር የጫቆ ሕዝብ ፤የወልቃይት የጠለምት የጠገዴና የአርማጭሆ ጀግና ሕዝብ ዛሬም እንደትናንቱ አባቶቹ የሚከፈለውን ከፍሎ ድንበሩን እንደሚያስከብር እርግጠኛ ሆኖ መናገር ይቻላል።እንደዚሁም የሌላው አካባቢ ኢትዮጵያዊ የጥቃቱ ዒላማ የሆነው የራሱን የጎበዝ አለቆች እየመረጠ በመተባበር ድንበሩን ማስከበር ይኖርበታል። በተናጠል እየገጠመ የጥቃቱ ሰለባ መሆን አይገባውም የሚገጥመው ከሱዳን ብቻ ሳይሆን ከህወሃትም ጋር ስለሆነ «አንድነቱን አጠንክሮ መዋጋት አለበት በውጭ ያለው ኢትዮጵያዊም አቅሙ በሚፈቅደው መጠን ሕዝቡን ማገዝና ከተቻለም እዛው ተገኝቶ የሕዝቡን ሞት መሞት ክብር ስለሆነ ታሪክ ሊሰራ ይገባዋል እዚህ ሆኖ ማቅራራቱ በቂ አይደለም። ህወሃትን በሚፈልገው ቋንቋ ማናገር ስንችል ነው ሀገርና ሕዝብን የምናድነው;» ከባዶ እየተነሱ ሚንስትር ለመሆን መሮጥና ፈርም ከተባለው ላይ እየፈረሙ ታሪክን ማበላሸት  ሳይሆን ለተተኪ ትውልድ ለሀገር ለሕዝብ ማሰብ ይገባል።ያሁኑ ጠቅላይ ሚንስትር ያለፈውን ጠቅላይ ሚንስትር ውዝፍ ሥራዎች ለመጨረስ ከሆነ ቦታውን ይዞት ያለው ባዶ ቀፎ ከመሆን አይዘልም ። መለስ ሀገርን አጥፍቶ የረጅም ዓመት የቤት ሥራ ጥሎልን ሄዷል።አሁን ያለው ኃይለማሪያም ደሳለኝ ሌላ ሰው ነው ታሪክ መስራት መቻል ያለበት አሁን ነው።ሥልጣኑን መጠቀም ያለበት በል እያሉ ከኋላው ተቀምጠው ለሚጋልቡት ሳይሆን ለራሱ ፤ለቤተሰቦቹ ለሀገር ለህዝብ በተለይም ለተተኪው ትውልድ አስቦ መሥራት ይኖርበታል። በተለይ ጠቅላይ ሚንስትር  ኃይለማሪያም ደሳለኝ  ሥርዓቱን በማራመድ እንደማንኛውም ተጠያቂ ቢሆንም ጎልተው እንደወጡት የህወሃት ነብሰ ገዳዮች የሚታደን አይመስለኝም እነሱ የደረሱበት ልድረስ ብሎ የሚሮጥ ከሆነ ግን ፍርሃትን እንዳዘለ ውለህ ግባ ሳይባል ከጨዋታው ይወጣል። መመርመር ያለበትም ይህ የመሬት ስጦታ ውል የድሮ ህወሃት አጀንዳ  ኢትዮጵያን ለመበታተንና ወደ መጨረሻም «ታላቋን ትግራይ ትግርኝት ሪፐብሊክ » ለመመሥረት በነበረው ወቅት ስለሆነ ወደ ፊት ከእጁ ያለውን ክብር የሚያሰጥና በሕዝብ ዘንድ እምነት እንዲጣልበት የሚያደርግ ተግባር መፈጸም ያለበት ይመስለኛል። ሕዝቡን ለማጭበርበር ጡረታ ወጥተዋል የተባሉት ዛሬም በቁልፍ ጉዳዮች ላይ እጃቸውን እንደሚያስገቡና ውሳኔ እንደሚሰጡ መዘናጋት የለብንም  ለማንኛውም እነሱም ሆኑ አሁን በሥልጣን ላይ ያሉት የህወሃት ገዥዎች በጎ ነገር እንዳይታያቸውና እንዳያስቡ የሚገፋቸው ችግር ብዙ ነው።ለምሳሌ ይህ ዛሬ የተነሳሁበት ሃሳብ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሀብት የሆነውን መሬት ለሱዳን አሳልፎ መስጠት የሀገርን ልዓላዊነት የሚነካና የተዳፈረ ተግባር ነው፤ሁሉንም የሕብረተሰብ ክፍል እርስ በርሱ እንዲጋጭ አድርገዋል፤ገድለዋል ፤አስረዋል፤አስድደዋል፤አፈናቅለዋል፤የኢትዮጵያዊ ዘግነት መብቱን ገፈዋል፤ሀብት ንብረቱን ዘርፈዋል…ወዘተ ይህ ወንጀል ነው።ይህ የሕሊና እርፈት ይነሳቸዋል በውስጣቸው ሰላም እንዲያጡ ያደርጋቸዋል ይታመሳሉ።በሰላም ጊዜ ከሕዝብ ጋር እንዳይኖሩ የሚያደርግ ተግባር ስለፈጸሙ ከሕዝብ መነጠላቸውን ስለሚያውቁ ሕዝብና ሀገርን በማወክ ሥራ ላይ ብቻ የተጠመዱ ናቸው።ስለዚህ አዲሶችና ወጣቶች ወደ ሥልጣን ገበታው ብቅ ያሉትን በህወሃት ስብስብ ውስጥ ለመታቀፍ የሚያስችል ወንጀል እንዲፈጽሙ ያደርጓቸዋል። ልክ አይደለም ይህ መሆን የለበትም የሚሉትን ደግሞ ደብዛቸው እንዲጠፋ ይደረጋሉ። ጠቅለል አድርገን ስንመለከት የህወሃት አመጣጥና ወደፊትም ግዞው ይህ ነው የሚሆነው። የበሉበትን መሶብ የሚደፉ የእናት ጡት ነካሽ ይሏል ይህ ነው።

 

የኢትዮጵያ የቦርደር ኮሚቴ(በውጭ የሚንቀሳቀሰውን የሕዝቡን የኢትዮጵያ የቦርደር ጉዳይ ኮሚቴ ማለቴ ነው) በተደጋጋሚ የሚያወጣቸውን መግለጫዎች ፤በራዲዮ የሚደረጉ ቃለ-ምልልሶች ተከታትያለሁ ለገዥው ቡድን የተላከ እንደሚሆንም አምናለሁ።አንዲት የምትጣል ነገር የላትም የኢትዮጵያና የሱዳኑን ድንበርም ከማንም በተሻለ ስለማውቀው የቦርደር ኮሚቴውን ማመስገንና እንዲበራቱ ማድረግና የምናውቀው ማስረጃ ካለን እንድንሰጣቸውና ከጎናቸው እንደንቆም እየጠየቅሁ ገዥው መደብ አሁንም ባለው አጭር ጊዜ ውስጥ አቋሙን እንዲመረምርና ውሳኔውን እንዲያነሳ ወደ ግጭቱ ሳንገባ መፍትሄ እንዲሰጡበት ማስጠንቀቅ እወዳለሁ።እሳቱ ከተጫረ በኋላ ሰማይ መሬቱን ማየት ፍሬ አይኖረውም። ምናልባት ይህን ስል ይህ ሰው እብድ መሆን አለበት እንደምትሉኝ ይገባኛል። በጣም ጤናማ ሰው ነኝ። ህወሃትና እኔ ስለምንተዋወቅ በገዳዳሙ ምን እያልኳቸው እንደሆነ ግጥም አድርገው ያውቁታል  ለአይን ጤና።

 

በመጨረሻ የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር እንጅነር ይልቃል ጌትነት በዋሽንግተን ዲሲ በጠሩት ስብሰባ የታደሙ ኢትዮጵያዊ ወገኖቼ ስለድርጅቱ ምንነት ሌሎችም ጉዳዮች ካዳመጡ በኋላ አንዳንድ ጥያቄዎች ተነስተው ነበር ሁሉም ጥያቄዎች በተገቢው ተመልሰዋል ብየ አምናለሁ።አንዱና ሁሉም የተቃዋሚ ኃይሎች ሆነ እኛም ልንመልሰው ያልቻልነው ጥያቄ የአንድነት ጥያቄ ነው። ጥያቄው ለእንጅነሩ ቀርቦ ነበር እንጅነሩ ወጣት ነው የሚገርመው ነገር ግን ያለው ፈሪሃ እግዚአብሔርና ትግስቱ ትህትናውና ለወገኖቹ ያለው አክብሮት ምንኛ የላቀ እንደሆነ በአንክሮ ተመልክቸዋለሁ። ስለጥያቄው ሲመልስ እንደ ሰማያዊ ፓርቲ ስለ አንድነት ግንባታ የሄዱበትን ርቀትና ወደፊትም በአንድነት ግንባታ ጉዳይ የድርጅቱን ራእይ በግልጽ አስቀምጦ አንድ ቦንብ የሆነ ጥያቄ ግን ለሁላችንም በተራው ጠይቆናል። ኃይለኛ ጥያቄ ነው። ሰማያዊ ፓርቲ ሆነ ሌሎች የተቃዋሚ ኃይሎች በአፋኙ የህወሃት አምባገነናዊ ሥርዓት እየተዋከቡ ፤እየታሰሩና እየተደበደቡ በዱላ እንደ እባብ ራስ እራሳቸውን እየተቀጠቀጡ አንድነት ለመፍጠር ያንጎላቹ ቢመስሉም አልተኙም እንደማለት ነው።ሁሉም ሥርአቱን እየተጋፈጡ በጋራ ለመስራትና ወደ አንድነት ለመምጣት የሚያደርጉትን ጥረት ገልጾ ነገር ግን እኛ እንዲህ ባለ ሁኔታ ላይ እንገኛለን። በዚህ በውጭው ዓለም ዴሞክራሲ በሰፈነበት አገር በርካታ ኢትዮጵያውያን በሚገኙበት ለምን አንድነት የፈጠረ «የኢትዮጵያ ኮሚዩኒቲ» አልፈጠራችሁም? የሚል ጥያቄ ነበር ለቤቱ የጠየቀው።«የሽ ፍልጥ ማሰሪያው ልጥ» እንደሚባለው እስኪ በራሳችን ላይ እንፍረድና ከጥቂቶችና በጣት ከሚቆጠሩት በስተቀር ሰላም እንዲፈጠር አንድነት እንዲገነባ የሚያደርጉ አጀንዳዎች ዙሪያ ተነጋግረን እናውቃለን? መቼ? በቴሌ ኮንፈረንስና ፓልቶክ እንደምትሉኝ ገባኝ እሱ አይደለም። በጠረጴዛ ዙሪያ ቁጭ ብሎ ሰጥቶ በመቀበል፤ አንተ ትብስ አንቺ በመባባል ኢትዮጵያዊ ባህል በተላበሰ መልኩ ተከባብረን ተመካክረን ሳንፎካከር ትግሬው አማራውን ሳይዘረጥጥ ኦሮሞው ጉራጌውን ሳይነቅፍ ሁሉን አቀፍ መድረክ ፈጥረን ለእኛም ሆነ ለተተኪው ትውልድ ታሪክ ለምን አንሠራም? እንጅነሩ ጥሩ የቤት ሥራ ሰጥቶናል እስቲ ስንቶቻችን እንደጎበዝ ተማሪ የእንጅነሩን ጥያቄ መልሰን እንደምንመጣ እንይ። በተለይ ጋዜጠኞች ፤ኢሳት እንዲሁም ሌሎች የፖለቲካ አክቲቪስቶች በዚህ ዙሪያ ዳሰሳ ብታደርጉ መልካም ነው እላላለሁ።

 

 

ኢትዮጵያ ልዓላዊነቷ ተከብሮ ለዘላዓለም ትኑር!!!

 

ጨርሰን ሳናልቅ ህወሃት የኢትዮጵያን መሬት ለሱዳን አያስረክብም!!

Pen(ጌታቸው ከሰሜን አሜሪካ)

Viewing all 8745 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>