Quantcast
Channel: ዘ-ሐበሻ – Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 8745 articles
Browse latest View live

የኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን በዣንጥላና በምንጣፍ መለመንን ከልክላ በካሽ ርጅስተር ተጠቃሚ ልትሆን ነው

$
0
0

ቅዳሜ ዕለት የወጣው አዲስ አድማስ ጋዜጣ እንዘገበው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክ በዣንጥላና በምንጣፍ መለመንን ከልክላ በካሽ ርጅስተር ልትጠቀም መሆኑን ዘግቧል። ጋዜጣው ጨምሮም ምእመናን ለቤ.ክ ሲሰጡ ደረሰኝ የሚጠይቁበት አሰራር ይኖራል ብሏል።

የአዲስ አድማስ ሙሉ ዘገባ እንደሚከተለው ነው።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ገዳማት፣ አድባራትና አብያተ ክርስቲያናት የካሽ ሬጅስተር ማሽንን ለገቢ መሰብሰቢያነት ለመጠቀም የሚያስችላቸው ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ መኾኑ ተገለጸ፡፡

ዘመኑን ያልዋጀውንና ጥራት የጎደለውን፣ ለሙስናና ብክነት የተጋለጠውን የቤተ ክርስቲያኒቱን የፋይናንስ አሠራርና ቁጥጥር ችግር ግልጽነት፣ ወጥነት፣ ተቀባይነትና ተጠያቂነት ባለው የፋይናንስ አያያዝ ሥርዐት ለመቅረፍና ለማድረቅ ያስችላል፤ በሚል በቀረበው የሀገረ ስብከቱ የሒሳብ አያያዝ ፖሊሲና ዝርዝር የአፈጻጸም መመሪያ ረቂቅ ላይ እንደተጠቀሰው÷ በማንኛውም መንገድ የተሰበሰበ ገቢ ገንዘብ ሕጋዊ የገቢ መሰብሰቢያ ደረሰኝ ወዲያውኑ ሊቆረጥለት የሚገባ ሲኾን ይህም በዋናነት በካሽ ሬጅስትር ማሽን እንደሚከናወን ተመልክቷል፡፡
bole_church_ethiopia-300x225 (1)
የሀ/ስብከቱ አብያተ ክርስቲያናት የካሽ ሬጅስተር ማሽን ተጠቃሚ መኾናቸው በገቢ ሒሳብ አሠራርና ቁጥጥር እያጋጠሙ ያሉ ችግሮችን ለመከላከል ያስችላል፡፡ በጥናቱ ላይ በመነሻነት ከተዘረዘሩት ችግሮች ለመረዳት እንደሚቻለው በዕለት ገቢዎችና ደረሰኝ አጠቃቀም ረገድ፡- የቤተ ክርስቲያኒቱን የገንዘብ ገቢ ሰነዶች በሕገ ወጥ መንገድ አሳትሞ በቤተ ክርስቲያኒቱ ስም ለግል ገንዘብ ይሰበሰባል፤ በጠቅላይ ቤተ ክህነቱ የተከለከለ ደረሰኝ ጥቅም ላይ የሚውልበት አጋጣሚ ታይቷል፤ ከደረሰኙ በበራሪው/ለከፋዩ ከሚሰጠው/ የተለየ መጠን በቀሪው ላይ መጻፍና የግል ጥቅምን ማካበት ይዘወተራል፤ በዘወትርና በክብረ በዓላት በርካታ ገንዘብ ገቢ ቢኾንም በዕለቱ ወደ ባንክ ያለማስገባት ኹኔታ አለ፤ ምእመናን ለሚከፍሉትና ለሚሰጡት ገንዘብ ከመተማመን አንጻር ደረሰኝ የመቀበል ልማድ የለሌላቸው መኾኑን እንደክፍተት በመጠቀም ለቤተ ክርስቲያን የመጣው ገንዘብ ‹‹በየመንገዱ እየተንጠባጠበ ወፎች የሚለቃቅሙት ይበዛል፤›› በሥራ ላይ ያልዋሉ የገንዘብ ገቢና ወጪ ሰነዶች (ሞዴላሞዴሎች ሴሪ ንምራ ቁጥር) መሠረታዊ ችግር ተጠንቶ መፍትሔ አልተሰጠም፡፡

በንግሥ፣ በወርኃዊ በዓላትና በዕለተ ሰንበት በሙዳየ ምጽዋት ሳይኾን በተዘረጋ ጨርቅ ላይ የሚሰበሰብ ገንዘብ መኖሩን የሚጠቅሰው ጥናቱ÷ በዚህ መልክ የተሰበሰበው ገንዘብ ሀ/ስብከቱ በታኅሣሥ፣ 2003 ዓ.ም. ባስተላለፈው የገንዘብ ቆጠራ፣ የንብረት አመዘጋገብና አጠባበቅ የሥራ መመሪያ መሠረት የምእመናንና ካህናት ሰበካ ጉባኤ ተወካዮች በሙሉ በተገኙበት ቆጠራ የማይካሄድበትና በተወሰነ መልኩም ሙሉ ገንዘቡ ገቢ የማይደረግበት ኹኔታ በመኖሩ አሠራሩ ለብኩንነት፣ ሐሜትና አሉባልታ መጋለጡን ገልጧል፡፡ በንግሥ በዓላት ወቅት ጥላ ዘቅዝቀው የሚለምኑ ሰዎች ኹሉም ስለማይታወቁ የተኣማኒነት ችግር አለ፡፡ በስእለትና በሙዳየ ምጽዋት በውጭ ምንዛሬ የሚገቡ የውጭ ሀገር ገንዘቦች በመመሪያው መሠረት በዕለቱ የባንክ ምንዛሬ ወደ ብር እየተቀየሩ በተገቢው መንገድ ገቢ አለመኾናቸው፣ በምትኩ ቅያሬው ወጥነት ያለውና ለብኩንነት የተጋለጠ እንደኾነም ተዘግቧል፡፡

በቃለ ዐዋዲ ድንጋጌው የተመለከተውንና በዝርዝር የሥራ መመሪያ የተላለፈውን የገቢ አሰባሰብ በተሻለ አሠራር ያጠናክራል የተባለው በፖሊሲና መመሪያ ረቂቁ የሒሳብ ሰነዶች አያያዝ፣ ምዝገባና አወጋገድ መሠረት÷ ለሒሳብ ሥራ የሚያገለግሉ ደረሰኞችና ቫውቸሮች የዋና ተጠቃሚውን ተቋም ስም ይዘው በሀገረ ስብከቱ ምስጢራዊ ኮድ ይዘው ይታተማሉ፤ የማሳተም ሓላፊነቱም የሀገረ ስብከቱ የፋይናንስና በጀት ዋና ክፍል ሲኾን ይህም በዋና ሥራ አስኪያጁ ፈቃጅነት የሚከናወን ይኾናል፡፡Cash register machine

በማንኛውም መንገድ የተሰበሰበ ገቢ ሕጋዊ የገንዘብ መሰብሰቢያ ደረሰኝ ወዲያውኑ ሊቆረጥለት ይገባል፤ ይህም በዋናነት በካሽ ሬጅስተር ማሽን ተፈጻሚ ይኾናል፤ የገንዘብ መሰብሰቢያ ደረሰኝ ከገንዘብ ሰብሳቢ ውጭ መያዝና መጠቀም አይቻልም፡፡ ማንኛውም የገንዘብ ስጦታ በገንዘብ ያዡ በኩል መሰጠት ይኖርበታል፤ ስጦታው እንደተበረከተም ወዲያውኑ የገንዘብ መቀበያ ደረሰኝ ሊቆረጥለት ይገባል፡፡ በዐይነት የሚሰጥ ስጦታ በግዥ፣ ሽያጭና ንብረት አስተዳደር ፖሊሲና ዝርዝር የአፈጻጸም መመሪያ መሠረት በተተመነለት ዋጋ ይመዘገባል፡፡
cash rigestor
ከአጥቢያ አብያተ ክርስቲያን ውጭ በሙዳየ ምጽዋት ሣጥን ገንዘብ መሰብሰብ አይቻልም፤ ቋሚ ሙዳየ ምጽዋት በቅጽረ ቤተ ክርስቲያን የሚቀመጥበት ቦታ ተጠንቶ በሰበካ ጉባኤው መጽድቅ አለበት፤ ለቆጠራ ካልኾነ በቀር ከተቀመጠበት ማንቀሳቀስ አይቻልም፤ በትከሻና ተይዘው የሚዞሩ ሙዳየ ምጽዋት ሣጥኖች ሙሉ መረጃ ተመዝግቦ ይያዛል፡፡ የሙዳየ ምጽዋት ቆጠራ በሚካሄድበት ወቅት ሣጥኖቹ ከመከፈታቸው በፊት ሁሉም ቆጣሪዎች የቁልፍ ካዝናውና የቁልፍ ሣጥኖች፣ የሣጥኖቹን ብዛትና እሽጋቸው አለመከፈቱን ማረጋገጥ ይኖርባቸዋል፤ የተቆጠረ ገንዘብ ሙሉ በሙሉ ወዲያውኑ ካልተቻለ ከሌላ ገንዘብ ጋራ ሳይቀላቀል በበነጋው ወደ ባንክ አካውንት መግባት አለበት፤ ዣንጥላን፣ ምንጣፍንና የመሳሰሉትን በመጠቀም ገንዘብ መሰብሰብ ፈጽሞ የተከለከለ ይኾናል፡፡

[የሀገረ ስብከቱ የመዋቅርና አደረጃጀት ሰነድ አካል የኾነው የሒሳብ አያያዝ ፖሊሲና ዝርዝር የአፈጻጸም መመሪያ ጥናት ረቂቅ እንደሚያትተው÷ የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት፣ የክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ጽ/ቤቶች፣ የልማትና በጎ አድራጎት ተቋማት፣ ደረጃ አንድ እና ሁለት የኾኑ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት በኮምፒዩተር የታገዘ የሒሳብ አያያዝ ዘዴን/ሥርዐት እንዲከተሉ ይደረጋል፡፡ የሒሳብ አያያዝ ዘዴውም የሁለትዮሽ የሒሳብ አያያዝ ዘዴ(Double entry system) ሲኾን በአክሩዋል ቤዝስ ከሚጠቀሙት ከልማት ተቋማት በስተቀር የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከትና በሥሩ ያሉ ሌሎች ተቋማት በጥሬ ገንዘብ ላይ የተመሠረተ፣ ገቢንና ተከፋይን በታሳቢነት በሚያስላው የሒሳብ አያያዝ ዘዴ(Modified cash bases) እንዲከተሉ ለማድረግ መታቀዱ ተገልጦአል፡፡ በኮምፒዩተር የሚታገዘው የሒሳብ አያያዝ ሶፍትዌርም በሀገረ ስብከቱ ተመርጦ የተዘጋጀው እንደሚኾን ታውቋል፡፡

የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ዕውቀትና ዘመናዊው የፋይናንስ ሞያ በጥምረት ሥራ ላይ ለሚውልበት ለዚህ አሠራር ተፈጻሚነት÷ ከሀገረ ስብከቱ፣ ከክፍለ ከተማ ጽ/ቤቶችና አጥቢያ አብያተ ክርስቲያን ተመርጠው ለተውጣጡና ለሚመለከታቸው የሒሳብና የቁጥጥር ሓላፊዎችና ሠራተኞች ሥልጠና እንደሚሰጥ የተጠቆመ ሲኾን የሀገረ ስብከቱ ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂና ዶኩመንቴሽን ዋና ክፍል በማእከል ሙሉ በሙሉ የሚቆጣጠረው የመሠረተ - ቴክኖሎጂው ዝርጋታ በሚተገበርባቸው ተቋማትና አብያተ ክርስቲያናትም በግልጽ የፕሮጀክት አሠራር እንደሚፈጸም ተገልጧል፡፡]
ዘመናዊው የፋይናንስ አሠራር በሀገረ ስብከቱ ተቋማትና አብያተ ክርስቲያናት ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ሲኾንም በተጭበረበሩ ደረሰኞችና በማይታወቁ የገንዘብ አሰባሰቦች የግል ጥቅምን ማካበት በመከላከል ለክትትልና ቁጥጥር አመች ለማድረግ እንደሚያበቃ ተመልክቷል፡፡ በሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት፣ በልማትና በጎ አድራጎት ተቋማቱ እንዲሁም በአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናቱ የሚዘጋጁ የፋይናንስ ሪፖርቶች ግልጽነት፣ ወቅታዊነትና ተኣማኒነት/ተቀባይነት እንዲኖራቸው ለማድረግ፣ ሀገረ ስብከቱ በሚሰበሰበው የኻያ በመቶ ፈሰስና ከአብያተ ክርስቲያናቱ በቅጽ ተሞልቶ በሚላከው ሒሳብ መካከል በየዓመቱ የሚያጋጥመውን ልዩነት ለማስወገድ እንደሚያስችል ተገልጧል፡፡

ይህም በሒደት ከፍተኛ የሀብት ክምችት የሚገኝበት የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በፋይናንስ አሠራሩና መልካም አስተዳደሩ የሁሉም አህጉረ ስብከት ሞዴል በመኾን ቤተ ክርስቲያኒቱ በመንበረ ፓትርያርክ ደረጃ ማእከላዊ የፋይናንስና በጀት አስተዳደር ይኖራት ዘንድ መሠረት ለመጣል፣ የካህናቷን ኑሮ በማሳደግና በማሻሻል ሐዋርያ ተልእኮዋን ለማጠናከር ከፍተኛ አቅም የምትፈጥርበት መሠረት ለመጣል እንደሚያስችላት ታምኖበታል፡፡


በሳዑዲ አረቢያ ዛሬ የተነሳው የሸሜሲ መጠለያ ሁከት እልባት ሳያገኝ ቀረ

$
0
0

በሳዑዲ አረቢያ የሚገኘው ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ በፌስቡክ ገጹ እንደዘገበው፦
የዛሬው የሽሜሲ መጠለያ ሁከት …

የጅዳ ቆንስል መስሪያ ቤት ” ህጋዊ ሰነድ የማታሟሉ ወደ ሃገር ቤት ግቡ! ” ያወጣውን ተደጋጋሚ መረጃ ተከትሎ ከአምስት ቀናት ጅምሮ ወደ ሽሜሲ መጠለያ በአስር አውቶቡስ በላይ ሆነው የገቡ ኢትዮጵያውያን ሜዳ ላይ ተጥለው ለከፋ መጉላላት መዳረጋቸው ገልጸዋል። አኒሁ ቅሬታ አቅራቢ ዜጎች በማከልም የጅዳ ቆንስል ሃላፊዎች ዛሬ ጠዋት ሊያነጋግሯቸው የመጡ ቢሆንም ” ተረጋጉ እንመለሳለን !” ብልዋቸው መፍትሄ ሳይሰጧቸው እንደሄዱ ገልጸውልኛል። የሃላፊዎች ሙሉ ቀን መጥፋት ያበሳጫቸው ነዋሪዎች ዛሬ ከቀትር በኋላ በነፍሰ ጡር ፣ በህጻናት ላይ እያደረሰ ያለውን መንገላታት እየጎዳቸው መሆኑን በመግለጽ ለሳውዲ ሃላፊዎችን መፍትሔ ቢጠይቁም ” መፍትሄው በእናንተ ሃላፊዎች እጅ እንጅ ፣ በእኛ እጅ አይደለም! ” በማለት እንደመለሱልቸው እና ነዋሪው በብስጭት አስወጡን በሚል ወደ በሮች ቢጠጋም በወታደሮች መከልከላቸው በምሬት ገልጸውልኛል። ለሶስት ሰአታት በመጠለያው ውስጥ በተከሰተው ተቃውሞ የጅዳ ቆንስል ሃላፊዎች ጉዳዩን አሳሳቢነት በመረዳት ወደ ቦታው በመሄድ ነዋሪውን አለማረጋጋታቸውን ብዙዎችን አሳዝኗል ።

(ፎቶ ፋይል)

(ፎቶ ፋይል)


ዛሬ በሽሜሲ መጠለያ የተነሳው ግርግር መንስኤነት በጅዳ ቆንስል ሃላፊዎች እና በሳውዲ የመጠለያው ከፍተኛ ሃላፊዎች ጋር በተከሰተ አለመግባባት እንደሆነ ጉዳዩን ለማጣራት ባደረጉት ሙከራ ለመረዳት ችያለሁ! የአለመግባባቱ ምንጭም መኖሪያ ፍቃዳቸውን ጥለው ወደ ሃገር የሚገቡ ዜጎችን ሰነድ ማጓተት ተከትሎ የቆንስል ሃላፊዎች ” ወደ ሃገር መግባት የሚፈልጉ ዜጎቻችን የመውጫ ሰነድ እስካልተሰጠ ድረስ ሰነድ አንሰራም!” አስገዳጅና ጠቃሚ መከራከሪያ በማቅረባቸው እንደሆነ ያሰባሰብኳቸው መረጃዎች ይጠቁማሉ! ጉዳዩን ለማጣራት ወደ ጅዳ ቆንስል ሃላፊዎች ስልክ በመደወል ያደረግኩት ሙከራ አልተሳካም ።

የሽሜሲ ተቃውሞ እልባት ሳያገኝ በዚህ መልኩ ከቀጠለ እና ነዋሪዎች በሁኔታው ተማረው በሚወስዱት ተቃውሞ ለረብሻና ሁከት ሰበብ እንዳይሆን ሊታሰብበት የሚገባ ሲሆን ነዋሪውም ምግብና ውሃ በአግባቡ እስከ ቀረበ ድረስ ጉዳዩን በትዕግስት ሊጠባበቁ እንደሚገባ ይመከራል! በተመሳሳይ ሁኔታ ወደ ሃገር እንግባ በሚል በግላቸው ወደ ሽሜሲ መጠለያ የሄዱት በመቶዎች የሚቆጠሩ ዜጎችም በመጠለያው በት በመጉላላት ላይ መሆናቸውን ገልጸውልኛል። አቤቱታቸውን በተደጋጋሚ ያቀረቡልኝ ነዋሪዎች እኔን ሳይቀር “ድምጻችን አታፍንብን ፣ ለአለም አሰማልን! “ሲሉ ሃይለ ቃልን ጨምረው ወቅሰውኛል !

ቸር ያሰማን

የኢትዮጵያ አየር ኃይል ለዳግመኛ ክህደት እንዳይደረግ ሲሉ የቀድሞ አየር ኃይል አባላት ወቅታዊ ጽሁፍ በተኑ

$
0
0

የቀድሞው የኢትዮጵያ አየር ኃይል አባላት በወቅታዊ ሁኔታዎች ላይ በመመርኮስ “በደም የተገነባ ተቋም” በሚል በበተኑት ጽሁፍ የአየር ኃይል ለዳግመኛ ክህደት እንዳይበተን ሲሉ አሳስበዋል። ለዘ-ሐበሻ የደረሰው የቀድሞው አየር ኃይል አባላት ጽሁፍ እንደሚከተለው ተስተናግዷል።
ethiopian airforce
በደም የተገነባ ተቋም
የኢትዮጵያ አየር ኃይል
(ለዳግመኛ ክህደት እንዳይዳረግ)

ግንቦት 83/91 ላይ የኢትዮጵያ ሰማይ ክፉኛ በሃዘን ሲመታ ፣ ደመናው ሲጠለሽ ፤ ወንዞች መደፈራረስ ሲጀምሩ፤ የሰውን ልብ ባር ባር ሲለው …….. የክፉው ቀን ጅማሮ ፣ የውርደት ሃሌታ ፣ የሃገር አልባነት ስሜትና የዜግነት ውርደት ደጃፍ ላይ መውደቃችን እውነት ነበር ።
ውርስ ከአባት ወደ ልጅ ሊተላለፍ ካልቻለ ፤ አባት የጀመረውን ልጅ ካልቋጨው ፤ አዲስ መንግስት ሲቀየር የድሮውን በጐ ነገር ሁሉ ብትንትኑን አውጥቶ ካጠፋ ፤ የትውልድ ቅብብሎሽ ገደል ገባ ማለት አይደል ? እናም በአገሬ ምድር ላይ የእርግማን ዘመን ያኔ “ በ1991 “ “ ሀ “ ብሎ ጀመረ ።
ሌባው ከሳሽ … ቀማኛው ፈራጅ የሆነበት ፤ አባት ተቀምጦ ልጅ የሁሉ ነገር አዛዥ ሲሆን ፤ አህያ ወደ ሊጥ … ውሻም ወደ ግጦሽ ከተሰማራ …. እነሆ ዘመነ ብልሹ ላይ መድረሱን ያልተረዳ ካለ … እሱ ባይፈጠር …. እናቱ ሆድ ውስጥ ውሃ ሆኖ ቢቀር ይሻለው ነበር ።

ሙሉውን ዘገባ በPDF ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

ዝነኛው አርቲስት ቴዎድሮስ ምትኩ አረፈ

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) አርብ ሴፕቴምበር 7 ቀን 2013 ታዋቂው የሙዚቃ ሰው ቴዲ (ቴዎድሮስ) ምትኩ በሜሪላንድ ግዛት ሆስፒታል መግባቱ ተገለጸ በሚል ዘ-ሐበሻ ዘግባ ነበር። ይህ ዜና እንደተሰማም በርካታ የኢትዮጵያ ሙዚቃ አፍቃሪያን ይህን ዝነኛ አርቲስት ፈጣሪ ምህረቱን እንዲሰጠው ሲጸልዩ ቆይተው ድምጻዊው ከሆስፒታል ተሽሎት ወጣ።

ሆኖም ግን ዛሬ ጠዋት ዲሴምበር 22 ቀን 2013 ዓ.ም 4፡06 ላይ ኢትዮጵያውያንን ከ1960ዎቹ ጀምሮ ሲያዝናና የነበረው ቴዎድሮስ ምትኩ ማረፉ ተሰምቷል። የድምጻዊው የቀብር ቦታ እና የፍትሃት ሁኔታው ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ባይሰማም፤ የፊታችን ማክሰኞ ሊሆን ይችላል የሚል መረጃ ግን ለዘ-ሐበሻ ደርሷል። ሁኔታውን ተከታትለን እንዘግባለን።

ዝነኛው ቴዎድሮስ ምትኩ የጥላሁን ገሰሰ ባለቤት እህት ከሆነችው ወ/ሮ መአዛ በዙ ጋር ላለፉት 22 ዓመታት በትዳር ዓለም ቆይቷል።

ዘ-ሐበሻ በዚህ ታዋቂ የሳክስፎን ባለሙያ የተሰማትን ሃዘን እየገለጸች ታዋቂው ጸሐፊ ዳግላስ ጴጥሮስ እንደ አርቲስት ቴዎድሮስ ምትኩ ያሉ ዝነኞችን ለማስታወስ የጻፈውን ለግንዛቤ አስተናግዳለች።
ከዳግላስ ጴጥሮስ
የአንድ ጐልማሳ ዕድሜን ያህል ወደ ኋላ ዞር እንድንል የዛሬው ርዕሰ ጉዳዬ ትዝታ ይቀሰቅሳል – ከ1960ዎቹ ዓመታት በፊት፡፡ በእነዚያ ዓመታት ውስጥ በትምህርት ቤቶቻችን ውስጥ በድንቅ ባህልነቱ የሚጠቀስ አንድ ጥበብ በተለየ ሁኔታ አብቦ ነበር፡፡ ያውም የሙዚቃ ጥበብ፡፡
ይሁን እንጂ ይህን መሰሉ ባህል ከዘመን ዘመን የሚሸጋገር ፍሬ እንዳያፈራ «የሥርዓቶች ዋግ መትቶት» በአበባ ብቻ ሊቀር ግድ ሆኗል፡፡ በጭንገፋ ተመትቶ «ግባ መሬቱ» የተፈፀመው ይህ የጥበብ ቡቃያ ፍሬው ከትውልድ ትውልድ እንዳይተላለፍ በእሸትነቱ ስለ ተቀጨ እነሆ የዛሬው ጥበብ ነክ ችግራችን ገዝፎና ሥር ሰዶ «ለወይነዶ!» ቁጭት ዳርጎናል፡፡
ዝነኛው አርቲስት ቴዎድሮስ ምትኩ አረፈ
«ዛሬ» የሚለው ቃል በጽሑፌ ውስጥ መደጋገሙ አለብልሃት አይደለምና አንባብያን እንድትታገሱኝ በመቅድም አቤቱታ እማፀናለሁ፡፡
እናም የዛሬን አያድርገውና ለልዩ ልዩ ሕዝባዊ ክብረ በዓላት በመዲናችን አዲስ አበባና በዋና ዋና የሀገራችን ከተሞች በዓላቱን የሚያደምቁት የማርች ባንድ (በተለምዶ ማርሽ ባንድ የሚባለው) ሙዚቀኞች ከወታደራዊ ክፍሎች የተገኙት ብቻ አልነበሩም፡፡ ከእነርሱ ባልተናነሰ ደረጃ ያውም በተሟላ ዘመናዊ የሙዚቃ መሣሪያዎች ተደራጅተውና ማራኪ የደንብ ልብስ ለብሰው ጥዑም ዜማቸውን ለሕዝብ የሚያቀርቡ የትምህርት ቤት የሙዚቃ ባንዶች ያበቡበት ወቅት ነበር፡፡ ወጣትነት በለገሳቸው መለሎ ቁመት እየተውረገረጉ የተመልካችን ቀልብ ይስቡ የነበሩት እኒያ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ታዳጊ የሙዚቃ ጠበብት ዘግይቶ በተፈጠረው ትውልድ ይዘነጉ ካልሆነ በስተቀር በታሪክ መዝገብ ውስጥ ግን ህያው እንደሆኑ መቆየታቸውን የሚደልዝ የተሟጋች ብዕር አይኖርም፡፡
ዳግማዊ ምኒልክን፣ ኰከበ ጽባሕን፣ የደሴው ወ/ሮ ስሂንና የናዝሬቱን አፄ ገላውዲዎስ ትምህርት ቤቶች ብቻ ለጊዜው በክብር ልዘክር፡፡ እነዚያ ትምህርት ቤቶች የነበራቸው የሙዚቃ ባንዶች (ኦርኬስትራና ማርቺንግ ባንድ) በወቅቱ ለተደረሰበት የሙዚቃ ዕድገት ከፍታ ብቻ ሳይሆን በእነዚያ የሙዚቃ ባንዶች ውስጥ ተፈጥረው፣ አድገውና በጥበቡ ተራቅቀው ከሙዚቃ ጋር ነፍስና ሥጋቸው እንደተቆራኘ የሚገኙ ባለሙያዎች ቁጥር ቀላል የሚሰኝ አይደለም፡፡ ሌሎቹን ጥበባት ወቅትና ጊዜ ሲፈቅድ አስታውሳቸዋለሁ፡፡
«ክርስቶስ ለሥጋው አደላ” እንዲሉ የዚህ ጽሑፍ አቅራቢ ዕውቀት የተጐነጨበትን የዳግማዊ ምኒልክ ትምህርት ቤት የሙዚቃ ባንድ የሚያስታውሰው በትልቅ አክብሮት ነው፡፡ ልዩ ልዩ ክበረ በዓላት ሲመጡ አዲስ የሙዚቃ ቅንብር ለመፍጠር ቀን ከሌት ይደረግ የነበረው ኃላፊነት የተሞላበት የተማሪ ጓደኞቹ የሸብ ረብ ዝግጅት አስደናቂ የሚሰኝ ብቻ ሳይሆን ከግምት በላይ ሊነገርለት የሚገባ ነው፡፡ በወርቃማ ጐፈርና በቀይና ቢጫ ቀለማት የተዋበው የተማሪዎቹ የሙዚቃ ባንድ ገና የትምህርት ቤቱን በር አልፎ ወደ ዋናው የአራት ኪሎ አውራ ጐዳና ሲገባ በዕልልታ ይቀርብለት የነበረው የሕዝብ አቀባበል ወደር አልነበረውም፡፡ በዚህ ትምህርት ቤት የሙዚቃ ባንዶች ውስጥ ያገለግሉ የነበሩት የያን ጊዜዎቹ ተማሪዎች በኋለኞቹ የጉልምስና ዕድሜያቸው ለኢትዮጵያ ሙዚቃ ዕድገት የተጫወቱት ሚና እንዲህ በዋዛ በቀላል የሃሳብ ጥቅሻ የሚታለፍ ስላይደለ ጥቂቶቹን ብቻ ለአብነት በመጥቀስ ዝርዝሩን በይደር ማስተላለፉ ይበጃል፡፡

ወደ ኰከበ ጽባሕ ትምህርት ቤት እስኪዛወር ድረስ የዳግማዊ ምኒልክ ትምህርት ቤት ማርቺንግ ባንድ ታንቡር መች የነበረው የሙዚቃው ሊቅ ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደና በያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቤት ውስጥ ከከፍተኛ የሥራ መሪነት እስከ መምህርነት እያገለገለ የሚገኘው አቶ ሰሎሞን ሉሉን ብቻ ለአብነት አስታውሼ ልልፍ፡፡ አቶ ሰሎሞን ሉሉ አሁን በሥራ ላይ ያለው የኢትዮጵያ ሕዝብ ብሔራዊ መዝሙር የዜማ ደራሲ እንደሆነም ማስታወሱ አስፈላጊ ነው፡፡
እኒህን መሰል ጐምቱ የሙዚቃ ጠበብት ተኰትኩተው ያደጉት በአንጋፋው የዳግማዊ ምኒልክ ትምህርት ቤት የሙዚቃ ባንድ ውስጥ ነው፡፡ እኒህንና ሌሎች በርካታ ወጣቶችን ሲያሰለጥኑ የነበሩት አቶ ዘውዱና አቶ መብራቱም የማይዘነጉ የጥበቡ ፊታውራሪዎች ነበሩ፡፡
የኰከበ ጽባሕ ትምህርት ቤት የሙዚቃ ባንድም ልክ እንደ ትምህርት ቤቱ ስም ሁሉ በወቅቱ የፈካ አጥቢያ ኰከብ ነበር፡፡ በዚያ የሙዚቃ ባንድ ውስጥ አድገው የወጡት ወጣቶችም በሀገራችን የሙዚቃና የቴአትር ጥበብ ላይ ያሳረፉት በጐ አሻራ ሊዘነጋ ከቶውንም አይችልም፡፡ ጥቂቱቹን ልዘክር፡፡ የትምህርት ቤቱ ዘንግ ወርዋሪ፣ ትራንፔት ተጫዋችና ድምፃዊ የነበረው ዓለሙ ገብረአብ እንዴት ይረሳል፡፡ ዓለሙ ገብረአብ ሕይወቱ እስካለፈ ጊዜ ድረስ የብሔራዊ ቴአትር ቤት ፈርጥ ተዋናይ ነበር፡፡
ዛሬ በውጭ ሀገራት ኑሮአቸውን የመሠረቱት ዝነኞቹ የሙዚቃ ባለሙያ ወንድማማቾቹ ተሾመ ምትኩና ቴዎድሮስ ምትኩ የኰከበ ጽባሕ ትምህርት ቤት የሙዚቃ ባንድ አባላት ነበሩ፡፡ በያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቤት ከዲሬክተርነት እስከ መምህርነት የዘለቀው አቶ ተክለ ዮሐንስ ዝቄ የዚሁ ትምህርት ቤት ፍሬ ነው፡፡ ታምራት ፈረንጅ፣ ተስፋዬ መኰንን፣ ታምራት ሎቴ፣ ሞገስ ሀብቴ ብዙዎቹ በሕይወት ባይኖሩም በተነደፉበት የሙዚቃ ፍቅር እስከ መጨረሻ የዘለቁት የኰከበ ጽባሕ ትምህርት ቤት ባንድ ከጥበቡ ፍቅር ጋር ስላቆራኛቸው ነበር፡፡ የእነዚህ ወጣቶች አሠልጣኝ የነበሩት አቶ ማሞ ደምሴና አቶ ጌታነህ ታደሰም አይዘነጉም፡፡ በምሥረታውና በማጠናከሩ ሂደት ላይ የጐላ ድርሻ የነበራቸው ዳኒሻዊውን ፓል ባንክ ሃንሰንን የመሳሰሉ የውጭ ሀገር መምህራንን ለጊዜው በማስታወስ ብቻ እናልፋቸዋለን፡፡
የዝነኛው የደሴው ወ/ሮ ስሂን ትምህርት ቤት የወጣቶች ፖለቲካዊና ሁለገብ ገናና ተሳትፎ በታሪክ የከበረ ቦታ እንዳለው አይደለም የሰው ምስክርነት ሣር ቅጠሉም ቢሆን እኔ ልናገር ብሎ ለዋቢነት መሽቀዳደሙ አይቀርም፡፡ በተለይ ግን የወ/ሮ ስሂን ትምህርት ቤት የሙዚቃ ባንድ በወቅቱ የነበሩትን ወታደራዊ የሙዚቃ ባንዶችን ብቃት በከፍተኛ ሁኔታ ይፈታተን እንደነበር ዕድሜውን የታደሉት ሁሉ የሚያስታውሱት ነው፡፡
የናዝሬቱ ዓፄ ገላውዲዎስ፣ የሐረሮቹ መድኃኒዓለም ትምህርት ቤት እና የመምህራን ማሠልጠኛ ተቋም የሙዚቃ ባንዶችም የነበራቸው ዝና እንዲሁ በጥቂት ቃላት እየታወሰ የሚታለፍ ባይሆንም ዝርዝሩን ለታሪክ ጸሐፍት በመተው ለዝክር ያህል ስማቸውን አስታውሰን እናልፋለን፡፡ የአዲስ አበባዎቹን መድኃኒዓለም ትምህርት ቤትና ተፈሪ መኰንን ትምህርት ቤትን በተመለከተ ግን ንባቤና መረጃዬ ስላልዳበረ እንዲህ ነበሩ ለማለት ድፍረት አጥቻለሁ፡፡ እነዚህን ሁለት ትምህርት ቤቶች በተመለከተ አዋቂዎች ቢያስተምሩን ነበርኩበት ባዮች ቢያሳውቁን ለዕውቀታችን በእጅጉ ይጠቅመናል፤ ከስህተትም ይታደገናል፡፡ መድኃኒዓለም ትምህርት ቤትን ካነሳሁ አይቀር ብዕረ መንገዴን በትምህርት ቤቱ ዋና መግቢያ ላይ ይነበብ የነበረውንና በፍፁም ከህሊናዬ ሊወጣ የማይችለውን ጥቅስ አስታውሼ ልለፍ፤ «ከዚህ ከማይሞተው የሰው ልጅ ማደጊያ ሥፍራ ግቡ» የሚለውን፡፡ ዛሬስ ያ ጥቅስ በቦታው ይገኝ ይሆን?
በውስን የጋዜጣ ገጽ ግዙፍ ሃሳቦችን ማስተናገድ ፈተናው የትዬለሌ መሆኑን አንባቢያን እንደሚረዱት ተስፋ በማድረግ ወደ ማጠቃለያው ሃሳብ ብዕሬን በፍጥነት ማንደርደሩን መርጫለሁ፡፡
ዛሬን ከቀዳሚ ዘመናት ጋር እያስተያዩ ይህ ጐደለ ይህ ሞላ ማለቱ አግባብ ባይሆንም ትናንትን ከዛሬ ጋር እያነፃፀሩ መልካሙን ማስታወሱ ግን ተገቢነት ይኖረዋል፡፡ ለምን ቢሉ፤ «ብልህ ከትናንት ይማራል፣ ሞኝ ግን ዕለት በዕለት ይሳሳታል» እንዲሉ መሆኑ ነው፡፡
ከላይ በተዘረዘሩት ትምህርት ቤቶች የሙዚቃ ባንድ ውስጥ አባላት የነበሩት ወጣት ተማሪዎች ትምህርት ቤታቸውን ከተሰናበቱ በኋላ ምን ሠሩ? ምን ፈፀሙ? ዛሬስ የት ናቸው? ተገቢ ጥያቄዎች ናቸው፡፡
በታዳጊነት ዕድሜ ከመደበኛው ትምህርታቸው ጐን ለጐን በሙዚቃ ፍቅር የወደቁት እኒያ ወጣቶች የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በአሸናፊነት ተወጥተው በልዩ ልዩ ሙያቸው ለሀገራቸው ኩራት እንደነበሩና እንደሆኑ ሥራቸውና ስማቸው ምስክር ነው፡፡
ለአብነት ያህልም በዘመኑ ዝነኛ ባንድ የነበረውን «ሶል ኤኰስ» በመባል ይታወቅ የነበረውን ባንድ የመሠረቱት በኰከበ ጽባሕ የሙዚቃ ባንድ ውስጥ የነበሩት ተስፋዬ (ሆዶ) መኰንን (ከበሮ መቺ)፣ ታምራት ፈረንጅ (ትራምፔት ተጫዋችና ድምፃዊ)፣ ተክለ ዮሐንስ ዝቄ (ትራምፔት)፣ ተሾመ ምትኩ (ጋራ ሥር ነው ቤትሽ፣ ሞት አደላድሎን፣ ሃሳቤን የመሳሰሉት ዝነኛ ዜማዎቹ ይጠቀሳሉ) እና ቴዎድሮስ ምትኩ (ሳክሲፎኒስት) የመሳሰሉት ናቸው፡፡ እነዚህ የኰከበ ጽባሕ ፍሬዎች ከሶል ኤኰስ በፊትም ዙላ ባንድን መሥርተው ነበር፡፡ «ሶል ኤኰስ» ባንድን ወደ «አይቤክስ ባንድ» ከዚያም «ሮሃ ባንድ» ወዘተ. እየተባለ የስም ሽግግር በሚደረግበት ጊዜ ሁሉ እነዚያ ወጣቶች በንቃት ተሳታፊ ነበሩ፡፡
በዚያ ዘመን የነበሩት ብዙዎቹ የትምህርት ቤቶቹ የሙዚቃ ባንድ አባላት በሀገራችን የሙዚቃ ጥበብ ውስጥ ያበረከቱት አስተዋፅኦ ዛሬም ድረስ የደበዘዘ አይደለም፡፡ እንዲያውም ብዙ ታላላቅ የጥበቡ ሰዎችን አሁን ድረስ ለደረሱበት ደረጃ መሠረት የሆናቸውን መደላድል ጥቀሱ ቢባሉ ያለጥርጥር ምሥጋና የሚያቀርቡት ላሳደጋቸው የየትምህርት ቤቱ የሙዚቃ ባንድ እንደሆነ መገመት አይገድም፡፡
ይህ ታላቅ የጥበብ መክሊት በዛሬዎቹ ትምህርት ቤቶቻችን ውስጥ አለወይ? ርግጥ የዕውቀትና የጥበብ ሁሉ መፍለቂያው ትምህርት ቤት መሆኑ መስካሪ አያሻውም፡፡ ግን ግን በየትምህርት ቤቱ ለዛሬውም ሆነ ለነገው ሙዚቃችን መሠረት ሊሆን የሚችል ሥራ እየተሠራ ነው? ከመደበኛው ሥርዓተ ትምህርት ጐን ለጎን ለሙዚቃ ጥበብ እየተሠጠ ያለው ትኩረት ምን ያህል ነው? የትምህርት ሚኒስቴር መሥሪያ ቤታችን «የተቀበረውን ውጤታማ መክሊት» ቆፍሮ ለማውጣት ምን እየሠራ ይሆን? ዳግማዊ ምኒልክ፣ ኰከበ ጽባሕ፣ ወ/ሮ ስሂን … ትምህርት ቤቶችስ «ነበር» ታሪካቸውን ማደስ አይገባቸውምን? የኢትዮጵያ ሙዚቃ ወድቋል ወይም ተነስቷል እያልን መከራከራችን ብቻ በራሱ በቂ ይሆናልን? ምን ያህሉን መክሊቶቻችንስ አርቀን በመቆፈር ያለማስተዋል ቋጥኝ ጭነንባቸው ቀበርናቸው ይሆን? እንወያይበት፣ እንምከርበት፡፡ ከንባቤ ጎን ለጎን ለዚህ ጽሑፍ በቂ ግብዓት በመስጠት የተባበሩኝን አርቲስት እሸቱ ጥሩነህ፣ ደራሲና ሃያሲ አስፋው ዳምጤና አቶ ተክለዮሐንስ ዝቄን ክብረት ይስጥልኝ በማለት በአንባቢያን ስም የማመሰግነው በታላቅ አክብሮት ነው፡፡ ሰላም፡፡

የአማራ ዴ/ኃ/ን ለሱዳን ተላልፎ በተሰጠው መሬት ዙሪያ “ዳሩ ካልተጠበቀ መሃሉ ዳር ይሆናል” የሚል መግለጫ አወጣ

$
0
0

Amara Democratic Force
ጋዜጣዊ መግለጫ 

“ዳሩ ካልተጠበቀ መሃሉ ዳር ይሆናል”!!

ከአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ (አዴኃን) የተሰጠ መግለጫ

ታህሣሥ 10 ቀን 2006 ዓ.ም.

በዓለም ላይ እስከአሁን የተከሰቱ መንግሥታት (ቅኝ ገዥዎችን ጨምሮ) ጨቋኝ (አምባገነን)፣ በዝበዥ፣ ዘራፊ (በሙስና የተዘፈቀ) … ወዘተ ሊሆኑ ይችላሉ። አሁን ኢትዮጵያን በመግዛት ላይ እንዳለው የትግሬ ዘረኛ ቡድን የሚገዛትን ሀገርና ሕዝብ የሚጠላና ሀገሩንም ለማጥፋት 24 ሰዓት የሚሠራ መንግሥት ግን እስከ አሁን በታሪክ አልታየም። ወደፊትም ከወያኔ በስተቀር የሚገዛትን ሀገር፣ ታሪኳንና ሕዝቧን የሚጠላና ሆን ብሎ ለማጥፋትም ቀን – ተሌት የሚጥር መንግሥት በምድር ላይ ይከሰታል ብለን አናምንም። ይህ የትግሬ ዘረኛ ቡድን ኢትዮጵያንና ሕዝቧን መጥላቱን የሚያሳይ የድርጊቱን ሥንክሣር መዘርዘር ቢቻልም፣ በአሁኑ ሰዓት የተከሰቱ ሁለት ታላላቅ ብሔራዊ ጉዳዮችን ብቻ እንኳ ብናይ ዘረኛው ቡድን ምን ያህል የሚገዛትን ሀገርና ሕዝቧን አምርሮ እንደሚጠላ ፍንትው አድርገው ያሳያሉ፦

  1. በሣዑዲ አረቢያ የወገኖቻችን ደም  በግፍ ሲፈስስ፣ እህቶቻችን ያለርህራሄ በቡድን ሲደፈሩ፣ በ21ኛው ክ/ዘመን በሰው ልጅ ላይ የፈፀማል ተብሎ የማይታሰብ ኢሰብአዊ ግፍ ሲፈፀምባቸውና በአጠቃላይ በሀገሪቱ ላይ ብሔራዊ ውርደት ሲደርስ የትግሬው ዘረኛ ቡድን “የሣዑዲ አረቢያ መንግሥት በሀገሩ ላይ ይህንን ማድረግ መብቱ ነው” ነበር ያለው።
  2. በዚህ ሰቅጣጭ ሐዘን ውስጥ ተውጠንና በስቃይ ላይ ያሉ ወገኖቻችንን ለመርዳት ላይ ታች በምንልበት ጊዜ ኢትዮጵያን ለማጥፋት ታጥቆ የተነሳው የትግሬው ዘረኛ ቡድን አባቶቻችን ደማቸውን በማፍሰስና አጥንታቸውን በመከስከስ ጠብቀው ያቆዩትን 1600 ኪ/ሜ ርዝመትና ከ20-60 ኪ/ሜ ወደ ኢትዮጵያ ጥልቆ የሚገባውን ከሱዳን የሚያዋስነውን ድንበራችንን በሕገወጥነት ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጀርባ ፈርሞ ለሱዳን አስረከበ። ምንም እንኳን በሚስጥር ሊይዘው ቢሞክርም የድንምበር ማካለሉ ከጥር ወር 2006 እስከ መስከረም 2007 ችካል በመቸከል እንደሚጠናቀቅ ታውቋል።

የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ (አዴኃን) ይህንን ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጀርባ የሚደረግ ሕገወጥ የድንበር ክለላ አጥብቆ መቃወምና ማውገዝ ብቻ ሳይሆን እንዳባቶቹ ደሙን አፍስሶና አጥንቱን ከስክሶ ታሪካዊ ድንበሩን ለማስከበር ቆርጦ ተነስቷል። ባንዳ የባንዳ ልጆች ከአባቶቻቸው የወረሱትን ሀገር የማጥፋትና የመሸጥ ውርስ ተግባራዊ ሲያደርጉ እኛ የአርበኛ ልጆች ነን የመንል ይህንን ደባ ዝም ብለን ብንመለከት ድንበር ላይ የተከሰከሰው የአባቶቻችን አጥንት እሾህ ሆኖ ይዎጋናል። በመሆኑም በአካባቢው ያላችሁ ታጋይ ኃይሎችና የገፈቱ ቀማሽ የሆንከው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ በርስቱና በሚስቱ ያልሞተ ወንድ ልጅ ወንድ አይደለምና ወንድ ልጅ ነኝ ያልክ ሁሉ ተባበረን፣ ከዚህ በላይ የሞት ሞት የለምና።

አዴኃን ይህንን ድርጊት አምርሮ የሚቃወመው እንዲያው በጭፍኑ ኢትዮጵያ ከሱዳን ጋር ሕጋዊ የሆነ ድንበር አይኑራት ብሎ አይደለም። የድንበር ስምምነቱ ኢትዮጵያን ጎድቶ ሱዳንን የሚጠቅም፣ ከ110 ዓመታት በፊት የፈረሰና ሕጋዊ ያልሆነ ውልን መሠረት ያደረገ፣ በጉዳዩ ላይ ጥልቅ ጥናት ያደረጉ ኢትዮጵያውያንን ጥናትና ውትወታ ግንዛቤ ውስጥ ያላስገባና በአጠቃላይ ከኢትዮጵያ  ሕዝብ ጀርባ በደባና በሕገወጥነት የተፈረመ ውል በመሆኑ እንጅ።

በጉዳዩ ላይ ጥልቅ ጥናት ያደረገው የኢትዮጵያ የድንበር ኮሚቴና ከዚያ በፊትም ጥናት ያደረጉ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ምሑራን እንደሚሉን ከሆነ ይህ ዛሬ የትግሬው ዘረኛ ቡድን ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጀርባ ለተፈራረመው ውል ዋቢ የሚያደርገው ውል በዳግማዊ አፄ ምኒልክና በጊዜው የሱዳን ቅኝ ገዥ በነበረችው እንግሊዝ መካከል የተፈረመው እ.አ.አ 1902 ነበር። አፄ ምኒልክ ይህንን ውል የፈረሙት በኃይል ተገድደውና በይዞታቸው ሥር የነበሩ ብዙ መሬቶችን ለቀው ነበር። በዓመቱ በ1903 የእንግሊዙ የጦር መኮንን ሻለቃ ጉዊን ድንበሩን ከስምምነቱ ውጭ ብቻውን ሄዶ ከመከለሉም በላይ አፄ ምኒልክ ተገድደውም ቢሆን የፈረሙትን ካርታ አዛብቶ ኢትዮጵያን እየጎዳ ችካል ቸከለ። ይህንንም ሻለቃ ጉዊን ከተሰጠው ሥልጣን በላይ ሄዶ መሥመሩን በማዛባት ከኢትዮጵያ መሬት እንደወሰደ በራሱ ሪፖረት ላይ በግልፅ ሳይደብቅ ጽፏል። እንግሊዞችም በ1902 የተፈረመበትን ካርታ ጥለው በችካሉ መሠረት በ1903 አዲስ ካርታ በመሥራት እነርሱ ከፈረሙበት በኋላ አፄ ምኒልክን ለማስፈረም ቢሞክሩም ከስምምነት ውጭ ለተቸከለው የጉዊን ክለላ ዕውቅና በመንፈግ ሳይፈርሙበት ቀርተዋል። የትግሬው ዘረኛ ቡድን አፄ ምኒልክ፣ አፄ ኃይለሥላሴና ደርግ የጉዊንን መሥመር ተቀብለዋል እያለ የሚያላዝነው ይህንን የመሰለውን ሐቅ በመካድ ነው። ይህንንም ዓይን ያወጣ የወያኔን ቅጥፈት አዴኃን ብቻ ሳይሆን ሰኞ 19 ኖቬምበር 2007 (እ.አ.አ.) ሱዳን ትሪቢዩን የተባለ ጋዜጣም “ድንበሩን አስመልክቶ የሱዳን መንግሥት ከቀደምት የኢትዮጵያ መንግሥታት ጋር የነበረው ግንኙነት ቀና አልነበረም። በድንበሩ ጉዳይ ላይ ለመነጋገር የመጀመሪያው ፈቃደኛ መንግሥት ገዥው የኢሕአዴግ መንግሥት ብቻ ነው” በማለት መሥክሮበታል።

ጥሪ፦     

ውድ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ! የፖለቲካ ድርጅቶችና የሲቪክ ማህበራትም ጭምር፣ ይህ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጀርባ በሀገር ከሃዲው የትግሬ ዘረኛ ቡድ ከጎንደር፣ ከጎጃም፣ ከወለጋና ከኢሊባቡር ክፍለ ሀገሮች ተቆርሶ ለሱዳን የሚሰጠው ለም መሬት የክፍለ ሀገራት ተወላጆቹ መሬት ብቻ አይደለም፤ የአንተም የኢትዮጵያዊው መሬት እንጅ። በመሆኑም አዴኃን ይህንን በባንዳ ልጆች የተጋረጥብንን ኢትዮጵያን የማጥፋት ታላቅ አደጋ ለመቀልበስ ስንል ያሉንን ጥቃቅን ልዩነቶች ወደጎን በመተው፣ ከምንጊዜውም በላይ እጅ ለእጅ ተያይዘንና ያለንን አቅም ሁሉ አስተባብረን በመነሳት የዜግነት ግዴታችን እንድንወጣ አስቸኳይ ጥሪውን ያስተላልፋል። “ዳሩ ክልተጠበቀ፣ መሀሉ ዳር ይሆናል” እንደሚባለው የትግሬውን ዘረኛ ቡድን በተባበረ ክንድ ዛሬውኑ ካላስወገድነው በስተቀር እናት ሀገራችን ኢትዮጵያን የማፈራረስ ዕኩይ ተልዕኮው የድንበር መሬቶችን እየቆረሰ ለጎረቤት ሀገራት በመስጠት ብቻ ያቆማል ብሎ ማሰብ ፍፁም የዋህነት ነው።

ለመከላከያ ሠራዊት፣ የፖሊስ ኃይልና የኢሕአዴግ ደጋፊዎች፣ እናንተ የምትደግፉት ሀገር አጥፊው የትግሬ ዘረኛ ቡድን አባቶቻችን ደረታቸውን ለጦር፣ እግራቸውን ለጠጠር ሰጥተው በደማቸው ያቆዩአትን ይህችን ጥንታዊትና ታሪካዊት ሀገራችንን እያጠፋት እንደሆነ ለእናነተ የተሠወረ አይደለም። ይህንን ሀገር የማጥፋት ወንጀል የሚፈፅመው ደግሞ እናንተን በመሣሪያነት በመጠቀም ስለሆነ ይህንን ተገንዝባችሁ አሁኑኑ ከሕዝባችንና አደጋውን ለመቀልበስ ከሚታገሉ ኃይሎች ጎን በመቆም ሀገራችሁን እንድትታደጉ ስናሳስብ፣ ጥሪያችን ችላ በማለት ለሀገር አጥፊው ቡድን ተባባሪነታችሁን ከቀጠላችሁበት ግን ታሪክና ሕዝብ ይቅር እንደማይላችሁ በጥብቅ ልናስጠነቅቃችሁ እንወዳለን።

ለብአዴን አባላት፦ “እሣት አመድ ይወልዳል” እንደተባለው ካልሆነ በስተቀር፣ አባቶቻችሁ ኢትዮጵያን ከሚያጠፋ ጠላት ጋር ተባብረው እናት ሀገራቸውን አላጠፉም፤ ይልቁንም ደማቸውን አፍስሰውና አጥንታቸውን ከስክሰው የታፈረችና አንድነቷ የተጠበቀ ኢትዮጵያን ለእናንተ አስረከቧችሁ እንጅ። እናንተ ግን የጀግኖች አባቶቻችሁ የባሕሪ ልጆች መሆን አቅቷችሁና አደራቸውን በልታችሁ ኢትዮጵያን ለማፈራረስና አማራን ለማጥፋት ቆርጦ ለተነሳው የትግሬ ዘረኛ ቡድን አሽከር ሆናችሁ እናት ሀገራችሁንና ወገናችሁን እያጠፋችሁ ነው። “ለእንጀራየ፣ ለልጆቼና ለቤተሰቦቼ ስል ወይም ተገድጀ ነው ይህንን የማደርገው” የሚለው ውሃ የማይቋጥር ምክንያት እንደማያዋጣችሁ አውቃችሁ የጋራ ሀገራችንንና ወገናችንን ለመታደግ አብራችሁት እንደትቆሙ አዴኃን ከልብ የመነጨ የሀገር አድን ጥሪ ያቀርብላችኋል።

ወንድም ለሆነው የሱዳን ሕዝብ፦ የኢትዮጵያና የሱዳን ሕዝብ ለብዙ ሺህ ዘመናት ከአንድ ወንዝ ከተቀዳ ውሃ እየጠጣ፣ በመከባበር ላይ በተመሠረተና በመልካም ጉርብትና አንዱ ለሌላው የችግር ጊዜ ደራሽ ሆኖ የኖረ ወንድማማች ሕዝብ ነው። ነገር ግን ዛሬ የትግሬው ዘረኛ ቡድን በሀገር ውስጥ የሚገኙ ነገዶችን እርስ በእርሳቸው ከማናከስ አልፎ የኢትዮጵያን ሕዝብ በተለይም የአማራውን ነገድ ወንድም ከሆነው የሱዳን ሕዝብም ለማናከስ ቆርጦ የተነሳ በመሆኑ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ዕውቅና ውጭ የተፈረመን የድንበር ስምምነት እንዳይቀበል በጥብቅ እናሳስባለን።

በመጨረሻም የዓለም ምንግሥታትና ዓለም – አቀፍ ሠላም ወዳድ ሕብረተሰብም የወያኔ ዘረኛ ቡድን ኢትዮጵያንና የኢትዮጵያን ሕዝብ ፈፅሞ እንደማይወክልና አሁን ከሱዳን መንግሥት ጋር በድብቅ የተፈራረመውንም የድንበር ስምምነት ንቅናቄያችን አዴኃን እና የኢትዮጵያ ሕዝብ እንደማያውቁት ተገንዝበው ስምምነቱ አሁንም ይሁን ወደፊት በሁለቱ ሀገራት ሕዝብ መካከል የሚፈጠረውን ቀውስ ከግምት ውስጥ በማስገባት ለስምምነቱ ዕውቅና እንዳይሰጡና በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ የሚፈፀመውን ይህንን ሤራ እንዲቃወሙ አዴኃን ጥሪውን ያስተላልፋል።

በደም የተረከብናትን ሀገር በደም እንጠብቃታለን!!

 

የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ

የኢህአዴግ አዲሱ አሰላለፍ ፪ –ከተመስገን ደሳለኝ (ጋዜጠኛ)

$
0
0

samora and azeb

በድህረ-መለስ ኢትዮጵያ የፖለቲካው ሥልጣን በስርዓቱ ልሂቃን መካከል ከሚደረገው የኃይል መተናነቅ አንጻር፣ ዛሬም ከመፈራረቅ ጣጣው የተላቀቀ የማይመስልባቸው ምልክቶች መታየታቸው እንደቀጠለ ነው፡፡ ከአራት ወር በፊት በዚህ መፅሄት ላይ ‹‹አዲሱ የኢህአዴግ አሰላለፍ›› በሚል ባቀረብኩት ፅሁፍ በገዥው ፓርቲ ውስጥ ተፈጥሮ ከነበረው ክፍፍል የትኛው ቡድን የበለጠ ጉልበት አግኝቶ በአሸናፊነት መውጣት እንደቻለ ከገለፅኩ በኋላ ፅሁፉን የቋጨሁት እንዲህ በማለት ነበር፡- ‹‹የፓርቲው የታሪክ ድርሳን እንደሚነግረን ‹ይሆናሉ› የተባሉት ተቀልብሰው፣ ባልተጠበቁ ሁነቶች (የኃይል መገለባበጥ ተከስቶ) ፖለቲካው የሚመራበት አጋጣሚ ሊፈጠር የሚችልበት ዕድል ሊኖር እንደሚችልም መዘንጋት አያስፈልግም፡፡››

እነሆ በዚህ ፅሁፍ ደግሞ በቅርቡ በተጨባጭ የታዩትን አዳዲስ ኩነቶች እና ይህንኑ ተከትለው ሊመጡ ይችላሉ ብዬ የምገምታቸውን ‹የቢሆን ዕድሎች› (Scenarios) ለማየት እሞክራለሁ፡፡
ሰላም የራቀው-ኢህአዴግ
በግንባሩ አባል ድርጅቶች መካከል ዛሬም ድረስ ሙሉ በሙሉ የተረጋጋ ፖለቲካ አልሰፈነም፤ የዚህ ዋነኛ ምክንያቱ ደግሞ፣ ቁልፍ የሥልጣን ቦታዎችን ጠቅልሎ ይዞ በነበረው በቀድሞ ሊቀ-መንበሩ ህልፈት ሳቢያ የተፈጠረው የአመራር ክፍተት እና እርሱን ሊተካ የሚችል መሪ ማግኘት ባለመቻሉ ይመስለኛል፡፡ እንዲህ አይነት አጋጣሚዎችም በተለይ እንደ ኢትዮጵያ ባለ ከሕግ ይልቅ የጠመንጃ ኃይልና የግለሰብ አምባገነናዊነት በገነነበት ሀገር ‹የማይገመቱ ክስተቶች› (Unpredictable Event) ማምጣታቸው የሚጠበቅ ነው፡፡

የሆነው ሆኖ በዚህ አጀንዳ ለመመልከት የምሞክረው ጉዳይ፣ በአሁኑ ጊዜ ሀገር እየመራ ያለው ኃይል ለሁለት የተከፈለ ቢሆንም፣ በአንፃራዊነት በጥምር የሚሰራ መሆኑን በማስረገጥ ነው፡፡ የእነዚህ ሁለት ቡድኖች የጉልበት ምንጭም የታጠቀውን ኃይል በመቆጣጠር እና የፖለቲካውን ሥልጣን በመያዝ ላይ የተመሰረተ ነው፤ ይኸውም ሠራዊቱ እና የደህንነት መስሪያ ቤቱ ሙሉ በሙሉ በህወሓት ሰዎች ሲንቀሳቀሱ፣ ፖለቲካውን ደግሞ የብአዴን መሪዎች፣ ከተወሰኑ የኦህዴድና ደህአዴን የአመራር አባላት ጋር ተባብረው መያዛቸውን የሚያሳዩ ምልክቶች መኖራቸው ነው፡፡

የህወሓት ኃይል

ህወሓት የቀድሞው ፍፁማዊ የበላይነቱን ለመመለስ ዋና ችግር የሆነበት በውስጡ ለተፈጠረው መከፋፈል እስካሁን መፍትሄው ተለይቶ አለመታወቁ ነው፤ ከዚህ ቀደም በዚሁ መፅሄት፣ አንዱ ኃይል የተሻለ ጉልበት በማግኘቱ ሌላኛውን (እነአዜብ መስፍንን ጨምሮ አባይ ወልዱና ቴዎድሮስ ሀጎስን የመሳሰሉ ከፍተኛ ካድሬዎች የተሰባሰቡበትን) በመብለጥ በተወሰነ ደረጃም ቢሆን እንቅስቃሴያቸውን መገደቡ ተሳክቶለት እንደነበረ ማስነበቤ ይታወሳል፡፡ ይህ ክፍፍል ምንም እንኳ እንደ 1993ቱ ከፓርቲ እስከ ማስወጣት የሚደርስ አለመሆኑ ቢታወቅም፣ ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል እና ጌታቸው አሰፋ የተሰለፉበት ቡድን ተፅእኖ ፈጣሪ ሆኖ መውጣት ችሏል፤ ይህም ሆኖ ውስጥ ውስጡን የሚገመደው ተንኮልም ሆነ ሽኩቻ ገና መቋጫ አለማግኘቱ ግልፅ ነው፡፡
በዚህ ፅሁፍ ጠመንጃ የታጠቀውን ክፍል ‹የህወሓት ኃይል› እያልኩ የምገልፀበት ዓብይ ምክንያት፣ በጄነራል ሳሞራ የኑስ ኤታ ማዦር ሹምነት የሚመራው የመከላከያ ሠራዊት እና በማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ጌታቸው አሰፋ ስር ያለው የደህንነት ኃይል ለሚደግፉት ቡድን መጠናከር እያበረከቱት ያለውን አስተዋፅኦ ከግምት በመክተት ነው፡፡ ሁለቱም ሰዎች ለመለስ ፍፁም ታማኝ የነበሩ ቢሆንም፣ ከህልፈቱ በኋላ እንደእርሱ ተጭኖ ሊቆጣጠራቸው የሚችል ጉልበታም ህወሓትን ጨምሮ በሁሉም የግንባሩ አባል ፓርቲ ውስጥ አለመኖሩ፣ በፖለቲካው ‹ቼዝ› የ‹ዘመነ መሳፍንቱ›ን ሚካኤል ስሁል አይነት ሚና እንዲጫወቱ አስችሏቸዋል፤ ሁለቱም ከስራቸው የነበሩትንና ‹ስልጣን ሊጋፉ ይችላሉ› ብለው የጠረጠሯቸውን ባልደረቦቻቸውን አስቀድሞ ገለል ማድረጉ ከሞላ ጎደል የተሳካላቸው ይመስለኛል፡፡
በተለይም ጌታቸው አሰፋ ከራሱ ወንበር አልፎ ከእነአዜብ መስፍንና አባይ ወልዱ ጋር በመተባበር አንድ ቀን በጠቅላላው የመንግስት የሥልጣን እርከን ላይ ‹ናቡቴ ሊሆን ይችላል› የሚል ስጋት ያሳደረበትን እና ‹መለስ ዜናዊ ሞት ባይቀድመው በእርሱ ቦታ ሊተካው ነበር› እየተባለ የሚነገርለትን የመረጃ ኃላፊ ወልደስላሴ ወልደሚካኤል በሙስና የሚወነጀልበትን መንገድ አመቻችቶ ለእስር ባይዳርገው ኖሮ ‹‹ለቁርስ ያሰቡንን…›› አይነት ታሪክ ራሱን መድገሙ አይቀሬ ነበር ብዬ አስባለሁ፡፡
ጄነራል ሳሞራ የኑስ በበኩሉ ተቀናቃኙ አድርጎ ይመለከታቸው የነበረው ሶስቱ ከፍተኛ መኮንኖች እንደ ወልደስላሴ ‹ፍንቀላ መሳይ ነገር ሊሞክሩ ይችላሉ› ተብለው አይደለም፡፡ የእነርሱ የመጀመሪያው ችግር ከወታደራዊ ዲሲፕሊን በማፈንገጥ አለቃቸውን አለማክበራቸው ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ ሳሞራ ‹በየትኛውም ምክንያት ከኃላፊነቴ ብነሳ የቆየ ፋይል አገላብጠው አደጋ ላይ ሊጥሉኝ ይችላሉ› በሚል ስለሚጠረጥራቸው ነው፡፡ እነዚህ መኮንኖች የሰሜን ዕዝ አዛዥ ሌፍተናንት ጄነራል ሰዓረ መኮንን፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ መልካም ግንኙነታቸው እንደቀድሞው እንዳልሆነ የሚነገረው የሰሜን ምዕራብ ዕዝ አዛዥ ሌፍተናንት ጄነራል አበባው ታደሰ እና የአየር ኃይሉ አዛዥ ሜጀር ጄነራል ሞላ ኃይለማርያም ናቸው፡፡ እናም ሰዓረ እና አበባው በቀጥታ ሠራዊት ከሚያዙበት ቦታ ተነስተው በመከላከያ ሚኒስትር ውስጥ በቢሮ ስራ ላይ ሲመደቡ፣ ሞላም ከነበረበት ኃላፊነት አኳያ ብዙም ይመጥነዋል የማይባል የቢሮ ስራ ተሰጥቶታል፤ በእርሱም ቦታ ሜጀር ጄነራል አደም መሀመድ ተተክቷል፡፡ የሳሞራ እና የሞላ ልዩነት በመለስ ዘመንም በአደባባይ የሚታወቅ እንደነበረ ሰምቻለሁ፡፡
Samora (2)
ለጉዳዩ ቅርብ ከሆነ የመረጃ ምንጬ እንዳረጋገጥኩት የአስተዳደር ዘይቤውን በማኪያቬሊያዊ አስተሳሰብ (ከፋፍለህ ግዛ) የሚያሳልጠው የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ፣ ለሞላ ትዕዛዝ የሚሰጠውም ሆነ ማንኛውንም ጉዳይ በተመለከተ የሚያነጋግረው የዕዝ ተዋረዱን ጠብቆ በኤታ ማዦሩ በኩል ሳይሆን፣ በቀጥታ በመገናኘት መሆኑ፣ አየር ኃይሉን ከመከላከያ ሚኒስቴር የተገነጠለ አስመስሎት ነበር፤ ይህ ሁኔታም በሁለቱ መኮንኖች መካከል ያለው ግንኙነት የሥልጣን ተዋረድን የጠበቀ እንዳይሆን በማሰናከሉ በጄነራሉ ላይ ደፍሮ የማይናገረው ቅሬታ ሊያሳድርበት ችሏል፤ ከመለስ ህልፈት በኋላም ሳሞራ ሂደቱን ለማስተካከል መሞከሩ፣ በየግምገማው ላይ እስከ መዘላለፍ አድርሷቸው ነበር (በነገራችን ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ወደ ሥልጣን ከመጣ በኋላ እንደ ጦር ኃይሎች አዛዥነቱ፣ ከጄነራሎቹ ጋር መደበኛ /Official/ በሆነ መንገድ ትውውቅ አላደረገም፤ እነዚህ ሶስት ጄነራሎችም ለዚህ አይነቱ የአሰራር መፋለስ ጥፋተኛ የሚያደርጉት አለቃቸውን ሳሞራ የኑስን ነው፤ ከምንጮቼ እንደሰማሁት ከሆነም ከወራት በፊት ኃይለማርያም ደሳለኝ በተገኘበት ‹ጎልፍ ክለብ› በሚባለው የጄነራሎቹ መዝናኛ በተዘጋጀ ፕሮግራም ማጠናቀቂያ ላይ ሳሞራ አንድ ጠረጴዛ ከበው ወደ
ተቀመጡት እነዚህ ጄነራሎች ጋ ሄዶ ‹ኑ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ላስተዋውቃችሁ› ማለቱን እና እነርሱም በጥያቄው ተበሳጭተው ቢሮ ያላቸው መሆኑን እና ክብራቸውን በሚመጥን መልኩ መተዋወቅ እንደነበረባቸው በኃይለ ቃል መመለሳቸውን ነው)

የሳሞራ የኑስ እና ሰዓረ መኮንን መነቋቆር ከትግሉ ዘመን ጀምሮ የመጣ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ሆኖም ሳሞራ ከማንም በላይ የሚፎካከረውም ሆነ መበለጥ የማይፈልገው በሟቹ ጄነራል ኃየሎም አርአያ እንደ ነበር የቀድሞ ጓዶቻቸው ያስታውሳሉ፤ ይህ ሁኔታ ዛሬም ድረስ በስራ ላይ ያሉ መኮንኖችን ‹የሳሞራ› ወይም ‹የኃየሎም ተከታይ› በማለት መከፋፈሉ በጓዶቻቸው እና በፓርቲው መሪዎች አካባቢ የሚታወቅ ነው፡፡ ሌላው ቀርቶ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ለማዕረግ እድገት የተለየ የድጋፍ አስተያየት የሚያገኙት በዛን ዘመን ‹የሳሞራ ተከታይ› የሚባሉት እየተመረጡ እንደነበረ በወሬ ደረጃ ይናፈሳል (በነገራችን ላይ ጄነራል ሳሞራ ከጤንነት ጋር በተያያዘ በአጭር ጊዜ ውስጥ በጡረታ ይሰናበታል በተባለበት ጉዳይ ላይ እያንገራገረ እንደሆነ ከመከላከያ አካባቢ የሚወጡ መረጃዎች ያመላክታሉ፤ እንደ ምክንያት የሚጠቀሰው ደግሞ ‹ለእኔ በጎ አመለካከት የላቸውም› በሚል የሚጠራጠራቸው ጄነራሎች በሥራ ላይ እያሉ የእሱ ጡረታ መውጣት ከመስሪያ ቤቱ ጋር ተያይዘው የሚነሱ ያደሩ የሙስና ካርዶች የሚመዘዙበትን ዕድል ያሰፋዋል የሚል ነው፤ በተለይም በግዙፍ የቢዝነስ ሥራዎች ላይ በታላቅ ተፎካካሪነት እየተሳተፈ የሚገኘው ‹መቴክ› ምንም እንኳ ማረጋገጫዎች ባይቀርቡበትም በመከላከያ ሥር ከነበረበት ዘመን እስከ 2002 ዓ.ም መጨረሻ ድረስ ከግዥዎች ጋር ተያይዘው የሚነሱ በርካታ የሙስና ሁኔታዎች በመኖራቸው ነው፡፡
መቴክ ካለፉት አራት ዓመታት ጀምሮ በአዋጅ የልማት ድርጅት እንዲሆን ቢደረግም፣ ዛሬም ዳይሬክተሩ የሠራዊቱ አባል ብርጋዴር ጄነራል ክንፈ ሲሆን፣ መከላከያ ደሞዝ የሚከፍላቸው ጥቂት የማይባሉ ሠራተኞችንም እንዳቀፈ ይታወቃል፡፡ እናም ሳሞራ ሃሳቡ ከተሳካለት ለጥቂት ተጨማሪ ዓመታት በሥልጣኑ ላይ ሲቀጥል፣ አሊያም ‹የወንድ በር› ለማግኘት በትግሉ ዘመን የእርሱ ሰልጣኝ እንደነበረ የሚነገርለትን እና በቅርቡ ብቸኛው ከሜጀር ወደ ሌፍተናት ጄነራል ማዕረግ ያደገው ዮሀንስ ገ/መስቀል እንዲተካው መንገድ ጠረጋውን ማመቻቸቱ ትኩረት ሰጥቶ የሚሰራበት ጉዳይ ይመስለኛል)
samora
ይህም ሆኖ የተኮረኮርን ያህል የምንስቀው ጄነራል ሳሞራ የኑስ በቅርቡ ለታተመው ‹‹ህብረ ብሔር›› መፅሄት ሙስና ለሠራዊቱ አደገኛ መሆኑን እንዲህ በማለት መግለፁን ስናነብ ነው፡-
‹‹ሙስና ሠራዊቱን ሊያበላሸው ይችላል፡፡ ሙስና ፀረ-ልማት ነው፤ ሠራዊቱን ሊበትነው እና ሕዝባዊ ባህሪውን እንዲያጠፋ ሊያደርገው ይችላል፤ አንድ ሠራዊት ሠራዊት ነው የሚባለው እንደ ወታደር እንደ አንድ አካል ሲያስብ እንጂ ለግሉ ሲያስብ አይደለም፡፡ …በአጠቃላይ (ሠራዊቱ) በዚህ ነው የሚፈርሰው፡፡››
መቼም ጄነራሉ ይህንን የተናገረው እራሱን ጨምሮ በርካታ ከፍተኛ መኮንኖች እንደ እንግሊዝ ንጉሳውያን ቤተሰቦች በተንጣለለ ቪላ ቤት ውስጥ፣ የተቀማጠለ ኑሮ መኖራቸውን ረስቶት አይመስለኝም፤ ‹ይህ የተንዛዛ ወጪያቸውም የሚሸፈነው ከደሞዛቸው በሚያገኙት ገቢ ነው› ብሎ ቧልት መሳይ ክርክር ሊያመጣ አይችልም፡፡ ይሁንና እታች ያለው ጭቁን የኢትዮጵያ ሠራዊት ምንም እንኳ በአለቆቹ ‹ቴክሳስ›ነት ላይ ለመቆጣት ባይደፍርም፣ እንደማንኛውም ዜጋ ለኑሮ ውድነትና አስከፊ ድህነት የተጋለጠ መሆኑን መካድ አይቻልም፡፡
የሆነው ሆኖ ተሰሚነታቸው እየተቀዛቀዘ የመጣው አቦይ ስብሃት ነጋ ከወራት በፊት ለ‹‹ውራይና›› መፅሔት ‹‹ህወሓት ትንሳኤ ያስፈልገዋል›› በማለት የሰጡትን ምክር ተከትሎ፣ ጄነራል ሳሞራ እና አቶ ጌታቸው አሰፋ፣ ከድርጅቱ ምክትል ሊቀ-መንበር ዶ/ር ደብረፅዮን ጋር በመተባበር ህወሓትን ለማጠናከር እና በፖለቲካ ውስጥ የነበረውን የአንበሳውን ድርሻ ለማስከበር (ጉዳዩን ከለጠጥነው ደግሞ ‹ለማስመለስ›) እየሰሩ እንደሆነ ይነገራል (በነገራችን ላይ የሳሞራና ጌታቸው ተፅእኖ መጨመሩን ለመረዳት፣ መከላከያ ‹አገራዊ ጥቅምንና ደህንነትን ለመከላከል› በሚል ‹እጅግ ጥብቅ ሚስጢር ብሎ የሰየማቸውን የሰው ኃይል ፕሮፋይል፣ የሒሳብ መዝገቦችና ሰነዶች እና የክፍያ ማስረጃዎች ለማንም አካል እንዳይገለፅ› የሚያስችለውን ስልጣን፣ ደህንነቱ ደግሞ በስራ ላይ የሚፈፅማቸው ማንኛውም ጉዳዮች ወደፊት በህግ እንዳይጠይቅ እስከ መከላከል የሚደርሰውን አዲስ የተዘጋጁትን አዋጆች ማንበቡ በቂ ነው፡፡ በርግጥ እነዚህ ባለሥልጣናት እንዲህ ባለ ተመሳሳይ መንገድ እንዲጓዙ ያስተሳሰራቸው አንዱ ጉዳይ ‹ህወሓት ተዳከመ፣ ተሸነፈ፣ አበቃለት…› የሚለው የካድሬውና ደጋፊው ቁጭት እንጂ ወትሮም መልካም ግንኙነት ኖሯቸው አይመስለኝም)

ለማንኛውም በጥቅሉ ሲታይ የህወሓት ትልቁ ችግር ተብሎ በአመራር አባላቱ የሚጠቀሰው ‹በዚህ ወቅት ወደፊት መምጣት የሚችሉ ጠንካራ ቴክኖክራቶችን አለማፍራቱ፣ ሁለንተናዊ ድጋፍ የሚያደርግለትን የታጠቀውን ኃይል ተጠቅሞ የፖለቲካ ልዩነቱን ጨፍልቆ በአሸናፊነት ይዞት መውጣት የሚችል መሪ እንዳይኖረው አደረገ› የሚል ነው፡፡ በርካታ የላይኛ እና የታችኛው ካድሬዎችም ‹ለእንዲህ አይነቱ ክፉ ጊዜ ድርጅቱ የሚያስፈልገው፣ በትግሉ ዘመን ልምድ ያካበተ ታጋይ ብቻ ነው› የሚል አቋም እንዳላቸው ይነገራል፡፡ ስርዓቱ ከሚያራምደው ርዕዮተ-ዓለም ጋር ጠንካራ ትውውቅ ያሌለውን እና የትግሉን ዘመን በአሜሪካን ሀገር በማሳለፉ ‹የምዕራባውያን ድጋፍ አለው› ለሚባለው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም የሚሰጡት ዝቅተኛ አመለካከት መግፍኤም ይኸው ይመስለኛል፡፡
ለነገሩ እርሱም ቢሆን በጠንካራ ድርጅታዊ ዲሲፕሊን ካለመታነፁ እና መሰል ጉዳዮች ጋር በሚያያዙ ምክንያቶች ለትንፋሽ ጊዜ የማይሰጠውን የድርጅት ሊቀ-መንበርነትንም ሆነ የጠቅላይ ሚኒስትርነት ቦታ የሚወራውን ያህል ይፈልገዋል ብሎ መደምደሙ አስቸጋሪ ነው ብዬ አስባለሁ፤ ከዚህ ይልቅ በተፈጥሮ ከታደለው የተግባቢነት ባህሪው አኳያ እንደ ሕዝብ ግንኙነት የመሳሰለ ብዙም የማያጨናንቅ ሥራን ይመርጣል፡፡ ለዚህም ይመስለኛል ከሰለጠነበት ሙያ ጋር የቀጥታ ተያያዥነት ያለውን የጤና ጥበቃ ሚኒስትር በሚመራበት ዘመን፣ ከውጭ ሀገር በርካታ የተቋረጡ ፈንዶችን እንደገና ለማስለቀቅ መቻሉ እንደ ታላቅ ስኬት የሚወራለት፤ አልፎ ተርፎም ‹ወባን ከኢትዮጵያ ምድር ለማጥፋት ብርቱ ትግል አደረገ› ተብሎ በዓለም አቀፍ ደረጃ ሳይቀር እስከ መሸለም የደረሰው እዚህ መስሪያ ቤት እያለ እንደሆነም ይታወቃል፡፡

ትንቅንቅ

ትንቅንቅ


በሌላ በኩል ደግሞ በፓርቲውም ሆነ በመንግስት አስተዳደር ከህወሓት ሰዎች ትልቁን ስልጣን የያዘው ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ከምዕራባውያን ጋር የቆየ ቀረቤታ እንዳለው ሰምቻለሁ፤ እንደሚታወሰው ደብረፅዮን ከክፍፍሉ በፊት (የደህንነት መስሪያ ቤቱ እንዲህ እንደ ዛሬው እጅግ ዘመናዊ በሆነው የቻይና ቴክኖሎጂ ሳይጥለቀለቅ) ከነበረው ከፍተኛ የሥልጣን ቦታ ላይ ተነስቶ፣ ቁልቁል ወርዶ በሁመራ በአንድ ዞን እንዲሰራ የተመደበው (ሁላችንም ስንገምት እንደነበረው) የአንጃው አባል ወይም ደጋፊ ሆኖ አይደለም፤ ይልቁንም የእነስዬ-ተወልደ ቡድን በመባል የሚታወቀው (‹አፈንጋጩ› ኃይል) ደብረፅዮንን በሲ.አይ.ኤ እና ሞሳድ ወኪልነት የመክሰሱ ጉዳይ የድርጅቱን በርካታ አባላት ቀልብ በመሳቡ፣ መለስ ይህንን ተከትሎ ከሚመጣበት አደጋ ራሱን ለመከላከል የወሰደው እርምጃ በመሆኑ ነው፡፡ በዚህም ምክንያት እስከ 1998 ዓ.ም መጨረሻ ድረስ በሁመራና ራያ አካባቢዎች በዞን ደረጃ ለማገልገል ተገዷል፡፡ እናም እርሱን የምዕራቡ ዓለም ፊት-አውራሪ አሜሪካና ሸሪኮቿ ወዳጅ ነው የሚያስብለው በቀድሞ መስሪያ ቤቱ በኩል በነበረው ግንኙነት ይመስለኛል።

የፖለቲካውን መዘውር የጨበጠው ኃይል

የዚህ ቡድን አምበል እንደ ድርጅት ብአዴን ቢሆንም፣ በቋሚ ተሰላፊነት ኃይለማርያም ደሳለኝ፣ አባዱላ ገመዳ፣ ሙክታር ከድር እና ሬድዋን ሁሴን እንደሚገኙበት ይነገራል፤ ለብአዴን ‹በተሻለ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ላይ ለመገኘቱ መደላድል ፈጥሮለታል› የሚለውን ሙግት ምክንያታዊ የሚያደርገው ደግሞ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የፖሊሲና ጥናት ምርምር አማካሪ በረከት ስምዖን፣ የኢህአዴግን የካድሬ ማሰልጠኛ ማዕከል በዳይሬክተርነት የሚመራው አዲሱ ለገሰ፣ ደርቦ ይዞት የነበረውን የትምህርት ሚኒስትርነት ለሽፈራው ደሳለኝ በመልቀቅ፣ በአሁኑ ወቅት ሙሉ የስራ ጊዜውን በግንባሩ ፅ/ቤት የሚያውለው ም/ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን እና የፌዴሬሽን ም/ቤት አፈ-ጉባኤው ካሳ ተክለብርሃን የያዙት ሥልጣን ያለውን የፖለቲካ አቅም መመዘኑ ይመስለኛል፡፡ በመከላከያ ሠራዊቱ ውስጥም ከሳሞራ አንድ እርከን ዝቅ ባለ ሥልጣን ከሌሎች ሁለት ጄነራሎች ጋር የሚገኘው አበባው ታደሰ እንደ ቀድሞው በዕዝ አዛዥነቱ (በቀጥታ በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ወታደሮችን ማንቀሳቀስ የሚችልበት) ላይ ቢሆን ኖሮ ጥንካሬውን የተሟላ ማድረጉ አይቀሬ እንደነበረ መገመት ይቻላል፡፡

ከዚህ ሌላ ለእነበረከት ቡድን ተጨማሪ የፖለቲካ ጉልበት እየሆናቸው ያለው የኃይለማርያም ደሳለኝ ቢሮ እና በአባዱላ ገመዳ አፈ-ጉባኤነት የሚመራው የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ነው፡፡ አባዱላ፣ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ሪፖርት ለማቅረብም ሆነ ለመታዘዝ ፍቃደኛ ያልሆኑ አንዳንድ ባለስልጣናት፣ በውስጥ መስመር በሚተላለፍለት ‹ጥቅሻ› በምክር ቤቱ በኩል የሚመለከተው የቋሚ ኮሚቴ አባላት አስጠርቶ የተሰጠውን ኃላፊነት የሚገመግምበት ስልት እየተገበረ ነው፡፡ በአናቱም ምን ጊዜም የሳምንቱን የሥራ መጨረሻ ቀን አርብን ጠብቆ የሚሰበሰበው የሚኒስትሮች ም/ቤትን ከሞላ ጎደል ይህ ቡድን እየጠቀመበት ይመስለኛል፡፡ በርግጥ ሚኒስትሮቹ በሚገናኙበት አብዛኛውን ሰዓት ሳይግባቡ (በጭቅጭቅ) ማሳለፋቸው ይነገራል፤ የዚህ ምክንያቱ ደግሞ በአቶ መለስ ዘመን ም/ቤቱ የሚሰበሰበው የተለያዩ አጀንዳዎችን ለማቅረብ እና በቀረበው አጀንዳ ላይ ለመከራከር (ለመመካከር) ሳይሆን፣ መለስ ወስኖ የመጣበትን የሥራ ድርሻ ተቀብሎ ለመበተንና ሪፖርት ለመስማት የነበረው አሰራር፣ ዛሬ ተቀይሮ በርካታ የተነቃቁ ሚኒስትሮች የየራሳቸው ሃሳብ ተቀባይነት እንዲያገኝ (ለማንፀባረቅ) የሚታገሉበት መድረክ ወደ መሆን በመሸጋገሩ ነው፡፡ ይህም ሁናቴ ዋናውን የመንግስት ሥራ የመገምገም እና የማስፈፀም አቅምን ሳይቀር ከሚኒስትሮች ም/ቤት ወደ ኢህአዴግ ሥራ አስፈፃሚ አሻግሮታል የሚያስብሉ ማሳያዎች አሉ፡፡ ይሁንና በዚህስብሰባ ላይም ቢሆን ደፈር ብሎ ከበረከት ስምዖን እና አባይ ፀሀዬ የተሻለ አዳዲስ ሃሳብ የሚያቀርብ ባለሥልጣን እንደሌለ ሰምቻለሁ (በነገራችን ላይ ምክንያቱን ባላውቅም የጠቅላይ ሚኒስትሩ ‹የፖሊሲና ጥናት ምርምር አማካሪ› ተደርገው የተሾሙት በረከት ስምዖን፣ አባይ ፀሀዬ፣ ኩማ ደመቅሳ እና ዶ/ር ካሱ ኢላላ የሥራ ቦታቸው በጠቅላይ ሚኒስትሩ ፅ/ቤት ሳይሆን መገናኛ አካባቢ በሚገኝ አንድ ህንፃ ላይ ነው፡፡ የተሰጣቸው ኃላፊነት ኃይለማርያምን በቅርብ እንዲያገኙ ከማስገደዱ እና በግልፅ ከሚታወቀው የአማካሪ አስፈላጊነት አኳያ ካየነው ግን ግራ የሚያጋባ ይመስለኛል)

አቶ አባይ ጸሐዬ

አቶ አባይ ጸሐዬ

ጠቅላይ ሚኒስትሩ…

ኃይለማርያም ደሳለኝ ይህንን ቦታ ከያዘ በኋላ፣ ብዙዎች በስልጣኑ የማዘዝ አቅሙ ላይ አመኔታ እንደሌላቸው (አንጋፋ ታጋዮች እንደ ‹አሻንጉሊት› ሊጠቀሙበት እንደሚችሉ) ደጋግመው መግለፃቸው ይታወሳል፡፡ በግልባጩ ‹አፈንግጦ ለመውጣት መሞከሩ አይቀሬ ነው› የሚሉ ግምቶች ነበሩ፡፡ በርግጥ እነዚህ መላ-ምቶች ዛሬም ድረስ እልባት ባያገኙም፣ እዚህ ጋ ያልጠቀስኳቸው አንዳንድ ጉዳዮች ላይ ያሳያቸው ወጣ ያሉ አቋሞቹን ሳስተውል ግን፣ አሁን ያለው አሰላለፍ (የአነበረከት እና አባዱላ ፖለቲካዊ መጠናከር) ለእርሱም የተረፈው ይመስለኛል፡፡ እንዲሁም ከቤንች ማጂ የተባረሩ አማርኛ ተናጋሪዎችን አስመልክቶ በድርጅቱ ውስጥ ባልተለመደ መልኩ ‹አጥፊዎቹ ላይ እርምጃ እወስዳለሁ› ከማለት አንስቶ (በነገራችን ላይ በአማካሪ ብዛት እንዲከበብ ካደረገው ምክንያት አንዱ ጓዶቹ በዚህ ንግግሩ መበሳጨታቸው ነው) በቅርቡ ህወሓትን ለመሸምገል በተዘጋጀ መድረክ ላይ ‹ሁኔታዎች እንዲህ እየተካረሩ ከሄዱ ወደ ማሰሩ መግባታችን አይቀርም› በማለት ማስፈራራቱ እና በቴዎድሮስ አድህኖም የሶሻል ሚዲያ አጠቃቀም ላይ የመቆጣቱ ጉዳይ ድረስ የሚካተቱ እውነታዎች ሰውየው የራሱን መንገድ ለመከተል እየሞከረ መሆኑን ያሳያሉ ብዬ አስባለሁ፡፡

የሆነው ሆኖ እነዚህ ሁናቴዎች የፖለቲካውን ጉልበት ሙሉ በሙሉ በብአዴንና በተባባሪነት በጠቀስኳቸው የኦህዴድና ደህአዴን የአመራር አባላት አካባቢ ቢያከማቻቸውም፣ በማንኛውም ሰዓት ያሻውን ማድረግ የሚችለው የታጠቀው ኃይል ደግሞ ከህወሓት ጎን እንደተሰለፈ ይገኛል፡፡ መጪውን ጊዜም አዲስ ክስተት እንድንጠብቅ ገፊ ምክንያት ይህ አይነቱ የኃይል አሰላለፍ ይመስለኛል፡፡

ምን እንጠብቅ?

ከረጅሙ የፓርቲ ፖለቲካና መንግስታዊ መንገራገጮች በኋላ፣ የሁለቱንም የኃይል መሰረቶች ጠቅልሎ በመዳፉ ሥር የከተተው መለስ ዜናዊ በሞተ ማግስት ‹የኃይል መገዳደሮች ሊከሰቱ ይችላሉ› የሚለው የብዙዎቹ ግምት ነበር፤ ከወራት በፊት አስነብቤ በነበረው ከላይ በተጠቀሰው ፅሁፍም ግምቶቹ እውን መሆን እንደ ጀመሩ ማሳያዎች ማቅረቤ ይታወሳል፡፡ ኢህአዴግ ውስጥ ራሳቸውን ያቧደኑት ኃይሎች ዋነኛ ግብ ከሥልጣን የሚነሱ ጥቅሞችና አነስተኛ የየራሳቸው ፓርቲ ፍላጎቶች የፈጠሩት በመሆኑ፣ እንደ ሟቹ ደመ-ቀዝቃዛ አምባገነን አይነት በጠንካራ መዳፍ ሥር የሚያሰባስባቸው ባለመገኘቱ በየጊዜው የኃይል መሸጋሸጎች ሊከሰቱ እንዲችሉ አድርጓቸዋል፤ አሁንም እየተስተዋለ ያለው ይኸው እውነታ ነው፡፡ በዚህ አውድ ላይ ቆመን ሊፈጠሩ የሚችሉ የቢሆን ሃሳቦችን ስናስቀምጥም በጠረጴዛው ላይ የምናገኘው ሁለት ዕድሎችን ይመስለኛል፡፡

የመጀመሪያ ሲናሪዮ የሚሆነው ከላይ የጠቀስኩት ቡድንተኝነት እንዳለ ሊቀጥል ይችላል የሚል ነው፤ ይህም የሚሆንበት ምክንያት ባለኝ መረጃዎች መሰረት የፖለቲካውን መስመር የያዘው ቡድን መሪ አባላት፣ አሁን ያላቸውን መንግስታዊ ሥልጣን ጠብቀው መቆየትን መሰረታዊ መሰባሰቢያ አጀንዳ ማድረጋቸው ነው፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ የሳሞራና ጌታቸው ጥምረት ህወሓትን ወደ ቀደመው ዘመኑ ለመመለስ ቢሻም፣ ሊሄድበት የሚችልበት መንገድ አደገኛ መሆኑ (ወታደራዊ ላዕላይ መዋቅሩንና የደህንነት ኃይሉን ከመያዙ አኳያ) ሁኔታዎችን ባሉበት ይዞ መቀጠልን በትርፍ-ኪሳራ ስሌት የተሻለ አማራጭ አድርጎ ይወስደዋል ብዬ አስባለሁ፡፡
ሁለተኛው የቢሆን ዕድል፣ ዳግመኛ የኃይል መሸጋሸግ ሊፈጠር መቻሉ ነው፤ ሰዎቹ ጥቅመኛ በመሆናቸው የቋንቋ ተናጋሪነት ልዩነቶቻቸውንና የኋላ የመቆራቆስ ታሪኮቻቸውን ተሻግረው፣ አንዳቸው ከአንዳቸው ጋር ሌላ መልክ ያለው ስብስብ ሊፈጥሩ ይችሉ ይሆናል፤ ይህ አይነቱ አዲስ የኃይል አሰላለፍም፣ ከቀጣዩ ሀገራዊ ምርጫ በፊት በማይታወቀው ተሰዊና ሰዊ ሊጠናቀቅም ይችላል፡፡
በመጨረሻም ምንም ይፈጠር ምን፤ እኛን ሊያግባባን የሚገባው ጭብጥ፣ የትኛውም ቡድን በግንባሩ ውስጥ ቢነሳ፣ የማዕከላዊ መንግስቱን ህልውና ወደሚበታትን ሂደት መግባቱ ሊሰካለት አለመቻሉ ነው፤ ምክንያቱም በዚህ መልኩ ሄዶ የሚጣሉበትን ጠረጴዛ መስበሩ ምን እንደሚያስከትል ያውቁታልና ወደዚህ ምዕራፍ እንደማይሻገሩ አምናለሁ፡፡ ይሁንና ከፓርቲው ዝግነት እና ከፖለቲከኞቹ አቋም የለሽነት አንፃር አሁንም ሆነ በቀጣይ ጊዜያት ከማንም ግምት ውጪ ያሉ ክስተቶች እንደ ደራሽ ውሃ ድንገት ሳይታሰብ ግንባሩን ሊያተራምሱት ይችላሉ ብሎ መገመቱ አግባብ ይመስለኛል፡፡

Hiber Radio: በደቡብ ሱዳን የተከሰተው የጎሳ ግጭት በኢትዮጵያ እንዳይከሰት የሚመለከታቸው ሁሉ ትኩረት ሰጥተው እንዲሰሩ ተጠየቀ

$
0
0

የህብር ሬዲዮ ታህሳስ 13 ቀን 2006 ፕሮግራም

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

<... ሻምበል ፍቅረ ስላሴ ወግደረስ አዳዲስና ከዚህ በፊት የማናውቃቸውን ጉዳዮች በመጽሐፋቸው አንስተዋል ...ራሳቸው ሁለት ጊዜ ሕይወታቸው አጣብቂኝ ውስጥ የገባበት ሁኔታን ጨምሮ የተለያዩ ወሳኝ መረጃዎችን አንስተዋል። ይህም መጽሐፍ ለታሪካችን አንድ ማስረጃ ነው...>

አቶ ኤልያስ ወንድሙ የጸሐይ አሳታሚ ባለቤትና ስራ አስኪያጅ ከሶስት ቀን በሁዋላ ለገበያ ስለሚቀርበው የሻምበል ፍቅረ ስላሴ <<እኛና አብዮቱ>> መጽሐፍ ከህብር ሬዲዮ ተጠይቆ ከሰጠው ማብራሪያ የተወሰደ ሙሉውን ያዳምጡት

<<... በኢትዮጵያ ያለው አገዛዝ በዘር ላይ የተመሰረተ የአፓርታይድ ስርዓት ነው። ...በኢትዮጵያ ያለው የጎሳ ችግር ከደቡብ ሱዳን የበለጠ ነው። ተቃዋሚዎች ብቻ ሳይሆኑ ሚዲያው፣የሐይማኖት አባቶች በአጠቃላይ ሁሉም ዜጋ በሱዳን የተከሰተው የዘር ግጭት እንደ ትልቅ ማስተማሪአ ወስደን በኢትዮጵያ እንዳይከሰት መስራት አለብን...>> አቶ ኦባንግ ሜቶ ስለ ደቡብ ሱዳን የሰሞኑ ግጭት ለህብር ከሰጡት የተወሰደ

የሱዳኑ አልበሽር ኢትዮጵያና ኤርትራን በእርግጥ ለማስማማት ወይስ ሁለቱ መንግስታት በተቃዋሚዎቻቸው የሚደርስባቸውን ለመከላከል? እውነት ይስማማሉ? አቶ መለስ የሰጉበትን የጓዶአኤርትራን ፍላጎት ዕውን ሕወሃት ማሟላት ይችላል ? የተቃዋሚዎቹስ ሚና(ትንታኔ)

የኦባማ ኬር የመጀመሮያ ዙር ምዝገባ ሰኞ(ከአቶ ተካ ከለለ ጋር ከአትላኢታ ቲኪ ዲሴምበር 23 ይጠናቀቃል።…ኢንሹራንስ ያለውም ተመዝግቦ የገበያ አማራጩን ማየት አለበት? (ስለ ኦባማ ኬር ከአቶ ተካ ከለለ ጋር )

ሌሎችም ዝግጅቶች

ዜናዎቻችን

- በደቡብ ሱዳን የተከሰተው የጎሳ ግጭት በኢትዮጵያ እንዳይከሰት የሚመለከታቸው ሁሉ ትኩረት ሰጥተው እንዲሰሩ ተጠየቀ

- ማንዴላን ያሰለጠኑት ኢትዮጵያዊ መኮንን ለቀብሩ ለመሔድ ቪዛ መከልከላቸውን በምሬት ገለጹ

- ኢትዮጵያ በደቡብ ሱዳን ጉዳይ እጇን እንዳታስገባ ተጠየቀ

- በጋዜጠኛ ርዮት ዓለሙ ላይ የተሰጠው የፍርድ ውሳኔ የዳኛው የእጅ ጽሑፍ ሳይሆን የሌላ ሰው መሆኑ ተገለጸ

- ምስጢሩ ሰኞ በርዮት የ30ኛ ወራት እስራት ይፋ ይሆናል

- በሳውዲ በሸሚሴ መጠለያ ያሉ ኢትዮጵያውያን ተቃውሞ አቀረቡ

- ከሳውዲ የመጡ እና በአገር ቤት ያሉ ወጣቶች ተፋጠዋል

ሌሎችም ዜናዎች አሉን

በእስር ላይ የሚገኙት የህዝበ ሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎች መግለጫ በድምፃችን ይሰማ ይፋ ሆነ

$
0
0

በእስር ከሚገኙ የህዝበ ሙስሊሙ የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት የተሰጠ መግለጫ
ሰኞ ታህሳስ 14/2006

ኢትዮጵያ ከአንድ ሺህ አራት መቶ አመታት በፊት የ21ኛው ክፍለ ዘመን ማህበረሰብ ካሰፈነው ፍትህ የላቀ ፍትህ ማስፈን ችላ ነበር። የወቅቱ የኢትዮጵያ ንጉስ በነቢዩ ሙሀመድ (ሰ.ዐ.ወ) አንደበት ‹‹በሐበሻ አንድም ሰው የማይበደልበት ንጉስ አለ›› ተብሎለታል። እንዲህ አይነት ፍትህ በዚህ መልኩ ለማስፈን ምን ያህል ፍትሀዊ፣ እውነተኛ እና የሰለጠነ ማህበረሰብ መገንባት እንደሚጠይቅ ግልፅ ነው። በሀገራችን የነበረው ፍትህ በጊዜው ነፃነት እና ፍትህ ፍለጋ ይዋትቱ የነበሩትን ማስጠለል የቻለ እና ዘመናትን ተሻጋሪ ነበር። ግና የዛሬው አሳዛኝ እውነታ ‹‹ሰዎች ስለ ፍትህ ግንዛቤ ባልነበራቸው በዚያ ዘመን የፍትህ ጥግ የደረሰችው አገራችን ሰዎች ሁሉ ወደ ዲሞክራሲ እና ፍትህ ፊታቸውን ሲያዞሩ ለምን ጀርባዋን ሰጠች?›› ብለን እንድንጠይቅ አስገዳጅ ሆኗል።
muslim1
ፍትህ ዘመን፣ ቦታና ሁኔታ የማይገድበው፣ በሃይማኖት፣ በሃገርና በብሔር ልዩነት የማይደረግበት፣ ሁሉም ለሁሉም እውን ሊያደርገው መጣር ያለበትና ሰው የመሆናችን ሚስጥር የሚፈታበት ጥልቅ እውነታ ነው። ግና ምድራዊም ሆነ ሰማያዊ ህጎች ፍትህን ቢደግፉትም ቅሉ በተጨባጩ ዓለም ግፍና በደል ተንሰራፍቶ ይገኛል። ቀደም ሲል አምባገነኖች በአደባባይ ይፈፅሙት የነበረውን ግፍ በዘመናችን ቅርፁን ቀይረው ፍትህ፣ ነፃነት እና እኩልነትን እየሰበኩ በተግባር ግን የህዝባቸውን ኑሮ የስቃይ ያደርጉታል።

መንግስት በሚዲያና በየስብሰባው ስለፍትህና ዴሞክራሲ በተደጋጋሚ ቢያነሳም መሬት ላይ ያለው ተጨበጭ ፍፁም ለማመን አዳጋች ነው፡፡ በማንኛውም ዘመን አምባገነኖች እንደሚያደርጉት ሁሉ ሰብዓዊነት የጐደለው ኢ-ፍትሃዊ ተግባር እየፈጸመ ሳለ ‹‹ህዝቡ ቦታ የሚሰጣቸው ሥነ-ምግባሮች፣ ህግጋትና መልካም እሴቶችን ለማስጠበቅ›› ሲባል የተሰራ እንደሆነ አድርጎ ለማቅረብ ይሞክራል። በመብት ትግላችን ሂደት ለሃይማኖታቸው ታማኝ በመሆን የፍትህና የነፃነት ጥያቄ ያነሱ ወገኖቻችን ሁሉ በመንግስት አካላት ስደት፣ እስራትና ሞት የደረሰባቸው ህብረተሰቡ የሚያከብራቸውን ስነ-ምግባሮች፣ እሴቶችና ህግጋት ሽፋን በማድረግ መሆኑ በእርግጥም ምጸት ነው።

ሙስሊሙ ህብረተሰብ ያነሳቸውና በወከላቸው ኮሚቴዎች አማካኝነት ለመንግስት ያቀረባቸው ጥያቄዎች ግልጽ፣ ቀላል፣ ሃይማኖታዊና ህገ-መንግስታዊ መብቶች መሆናቸውን መላው ኢትዮጵያዊና ዓለም ዓቀፉ ማህበረሰብ ያውቀዋል። መንግስት ግን ለሰው እምነት ከባለቤቱ በላይ ተቆርቋሪ፣ ለሃገር ደህንነትና ሰላም የሚያስብ ብቸኛ አካል እና ህገ-መንግስቱን አክባሪና አስከባሪ እንደሆነ በመደስኮር የመብት ጥያቄያችንን የሀሰት ቅርፅ ሊያስይዘው ሞክሯል። በመሰረቱ መንግስት ኃይልና ጉልበት ያለው አካል ሆኖ ሳለ በተቃራኒው ደግሞ ህዝብ ጉልበት ስለሌለው ሰላምንና ደህንነትን አጥብቆ የሚፈልገው ከመንግስት በላይ ህዝብ ነው። ህገ-መንግስት ደግሞ መንግስት ያለውን ኃይል በመጠቀም ህዝብ ላይ ግፍ እንዳይፈፅም የሚገድብ ህግ እንደመሆኑ በመንግስት እንጂ በህዝብ ሊጣስ አይችልም።

ከጅምሩ መንግስት የሙስሊሙ የመብት ጥያቄ ከጀርባው ምንም ሴራ እንደሌለው የሚያውቅ መሆኑን ብንረዳም በአባላቱም ሆነ በማህበረሰቡ ላይ ብዥታ እንዳይፈጥር ዓላማችንን እና ጥያቄዎቻችንን ለሁሉም ግልፅ አድርገናል። ይህም ሆኖ ግን በተለያዩ ብሄሮችና ሃይማኖቶች መካከል መከባበር እንዲኖር የማድረግ ከፍተኛ ኃላፊነት ያለበት መንግስት ሙስሊሙን እርስ በእርስ፣ እንዲሁም ሙስሊሙን እና የሌላ ሀይማኖት ተከታዩን ህብረተሰብ ለግጭት የሚዳርጉ ተግባራትን ሲፈጽም ቆይቷል። አሁንም እያደረገ ይገኛል። ይህ አደገኛ አካሄድ ሊከሽፍ የቻለው በህዝባችን ብስለት እና ጨዋነት ብቻ ነው። ኩሩው የኢትዮጵያ ህዝብ ከህዝበ ሙስሊሙ የመብት ጥያቄ ጋር በተያያዘ የመረጠው በሳል አካሄድ ሊመሰገን የሚገባው ነበር። ይህ በሳል የህዝብ ምላሽ ሙስሊሙን እና ክርስቲያኑን ሊያጋጭ ይችል የነበረውን የመንግስት እንቅስቃሴ ቀልብሶ የህዝባችንን ጨዋነት፣ ተከባብሮ የመኖር ብቃት እና አስተዋይነት ዳግም ማሳየት ችሏል። ክስተቱም በታሪክ መዝገብ ውስጥ በወርቃማ ጽሁፍ የሚሰፍርበትና ለትውልድ የሚተረክበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም።

በህዝበ ሙስሊሙ ላይ የፈጸማቸው በደሎች በህዝቡ ብስለት የከሸፉ ቢሆኑም ለህዝቡ ደንታ የሌለውና ስህተቱን አምኖ መቀበልን ውርደት አድርጐ የሚቆጥረው መንግስት ግን ህዝብ እየተቃወመው ህገወጥነቱን ቀጥሎበታል። በዚህም ምክንያት ‹‹መንግስት በሀይማኖታችን ጣልቃ አይግባብን! ያልመረጥናቸው ህገ-ወጥ የመጅሊስ አመራሮች ወርደው ፍትሀዊ ምርጫ ይካሄድ! የማናምንበት እምነት በግድ አይጫንብን!›› ብሎ የጠየቀውን ህዝብ ከነወኪሎቹ ለእስር፣ ለስደት፣ ለእንግልት እና ለሞት ዳርጓል።

የኢፌደሪ ህገ-መንግስት አንቀጽ 17 ንዑስ አንቀጽ 2 ‹‹ማንኛውም ሰው በህግ ከተደነገገው ስርዓት ውጪ ሊያዝ፣ ክስ ሳይቀርብበት ወይም ሳይፈረድበት ሊታሰር አይችልም›› ይላል። ነገር ግን ለፀጥታ ተግባር የተሰማሩት አካላት ህጉን በመጣስ ሰላማዊ ግለሰቦችን ሲይዙ የታጠቀ የጠላት ኃይል ላይ እንኳ ሊፈፀም የማይገባውን ግፍ፣ ድብደባ፣ ወከባ እና ስቃይ ይፈፅማሉ። ከፍርድ ቤት የመያዣ ትዕዛዝ ሳያገኙና ለባለቤቱ ሳይሰጡ ያስራሉ። ህግ ጥሰው ከምሽቱ አስራ ሁለት ሰዓት በኋላ የግለሰቦች ቤት ላይ ብርበራ ያካሂዳሉ። በብርበራው ወቅት በሚፈጥሩት ሁከት በቤተሰብ ላይ ከፍተኛ ስጋት እና ድንጋጤ ይፈጥራሉ። ይህ ሁሉ የሚካሄደው ህዝቡ በፍርሃት ከመብት ጥያቄው ወደ ኋላ እንዲል ቢሆንም ውክቢያውና እንግልቱ ግን የመብት ጥያቄው ይበልጥ እንዲፋፋም፣ ህዝቡ ፍርሃቱ ለቅቆት ለነፃነት የሚከፈል መስዋዕትነት ያለውን ልዩ ጣዕም እንዲያጣጥም እና ሙሉ መብቱን ወደ መጠየቅ እንዲሸጋገር ነው ያደረገው።

የህገ-መንግስቱ አንቀጽ 18 ንዑስ አንቀፅ 1 ‹‹ማንኛውም ጭካኔ ከተሞላበት፣ ኢሰብዓዊ ከሆነ ወይም ክብርን ከሚያዋርድ አያያዝ ወይም ቅጣት የመጠበቅ መብት አለው›› ይላል። ህገ-መንግስቱ ይህን ቢልም ዜጐች መሆናችንን ጥርጣሬ ውስጥ በሚከት መልኩ ከያዙን በኋላ በማእከላዊ በክረምት ቀርቶ በበጋ እንኳን ቅዝቃዜው በማይቻለው ‹‹ሳይቤሪያ›› ተብሎ በሚጠራው ጨለማ ክፍል ለ3 ወራት አጉረውናል። መቋቋም የሚያዳግተውን የማሰቃያ ስልታቸውን በመጠቀም ያላሰብነውንና ያልሰራነውን ‹‹እመኑ! ተናገሩ! ፈርሙ!›› ብለው አስገድደውናል።

ለቀጠሮ ፍርድ ቤት ስንቀርብ የደረሰብንን ሰቃይ አሳይተን ቢያንስ ፍርድ ቤቱ ስቃዩን እንዲያስቆምልን ጠይቀን ነበር። ያገኘነው ውጤት ግን ወደ ማዕከላዊ ስንመለስ ከመርማሪዎቹ በቀልና ተጨማሪ ስቃይ ነበር። ፍርድ ቤቱ የደረሰብንን ስቃይና የተከሰስንበትን ጉዳይ አግባብ እንዳልሆነ አይቶ ዋስትና ሰጥቶን ሳለ ፖሊስ የፍርድ ቤትን ትዕዛዝ ጥሶ ዋስትናውን በመከልከል ክስ መስርቶብናል። አሰቃዮቻችን ስለ ህገ-መንግስት እና መብት ስንናገር ‹‹ህገ-መንግስቱን ቀደህ ጣለው!›› እና ‹‹እኛ መሰዋዕትነት ከፍለን ነው እዚህ የመጣነው!›› ወ.ዘ.ተ በማለት ለህግም ሆነ ለሰው ክብር ደንታ እንደሌላቸው አሳይተውናል። ይህ ሁሉ መከራ በተቃራኒው ህገ-መንግስቱን ለማስከበር መታገል የሚያስፈልግበት ትክክለኛ ወቅት ላይ መሆናችን እንዲሰማን፣ እውነተኛ ፅናትና ወኔ እንዲኖረንም አድርጎናል።

በህገ-መንግስቱ አንቀጽ 19 ንዑስ አንቀጽ 5 ‹‹የተያዙ ሰዎች በራሳቸው ላይ በማስረጃነት ሊቀርብ የሚችል የእምነት ቃል እንዲሰጡ፣ ወይም ማናቸውንም ማስረጃ እንዲያምኑ አይገደዱም። በማስገደድ የተገኘ ማስረጃ ተቀባይነት የለውም›› የሚለውን ድንጋጌ መሠረት በማድረግ እዚያው ማዕከላዊ የምርመራ እስር ቤት እያለን የደረሰብንን ስቃይና እንግልት ገልፀን ክስ አቅርበን ነበር። በምርመራ ጣቢያው ቃላችንን የሰጠነውም ሆነ የፈረምነው ተገደን መሆኑን ገልፀን ውድቅ እንዲደረግ ጠይቀናል። ሆኖም ግን ክሳችን ተዳፍኖ እና ተድበስብሶ እንዲቀር በመደረጉ በጊዜው ምላሽ ሳናገኝ ቀርተናል። ክስ ተመስርቶብን ወደ ከፍተኛው ፍርድ ቤት አቅርበን በኋላም በድጋሚ ጉዳዩን ያስረዳን ሲሆን አሁንም ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን ሙሉ ለሙሉ የሚያደምጥበትንና ምላሽ የሚሰጥበትን ቀን እየተጠባበቅን እንገኛለን።

ከቤተሰብ፣ ከጠበቃና ከሀኪም ጋር እንዳንገናኝ አድርገው የፈፀሙብን የህግ-ጥሰት እና አስገድደው በማስፈረም እና ድምፅና ምስላችንን በመቅረፅ የፈፀሙብን በደል በወንጀለኛ መቅጫ ህግ ቁጥር 424 መሰረት እስከ አስር አመት የሚያስቀጣ ኢ-ሰብዓዊ ተግባር ነው። ነገር ግን የፖሊሱም፣ የዐቃቤ ህጉም፣ የፍርድ ቤቱም አለቃ በሆነውና የፍትህ ስርዓቱን ሰብስቦ በያዘው ገዚው ፓርቲ አምባገነንነት በተቃራኒው እኛ ተከሳሾች ሆነን ጉዳያችን ‹‹በፍርድ ቤት›› በመታየት ላይ ይገኛል።

በማዕከላዊ እስር ቤት ውስጥ ከፍተኛ የሆነ ስነ-ልቦናዊ እና አካላዊ ስቃይ አድርሰውብናል። ከአስራ አራት ሰዓታት በላይ ያለ እረፍት ቀጥ ብለን እንድንቆም በማድረግ፣ ጀርባችን ሰንበር እስኪያወጣ እና እስኪገሸለጥ ራቁታችንን በሽቦ በመግረፍ፣ በሰንሰለት በማሰር እና ዓይናችንን በጨርቅ በመሸፈን የውስጥ እግራችን እስከሚላጥ ገልብጦ በመግረፍ፣ ቀንና ማታ አሰቃቂ በሆነ ምርመራ እና ድብደባ እንቅልፍ በመንሳት፣ ሃይማኖታችንንና ክብራችንን በመንካት፣ ፂማችንን በመንጨትና እንድንላጭ በማስገደድ፣ እንዲሁም ሰላት በመከልከል፣ ቤተሰብ፣ ጠበቃ፣ ሀኪምና የሃይማኖት አባት እንዳናገኝ በማድረግ፣ ከአቅም በላይ የሆነን ስፖርት በግድ በማሰራት፣ ብልት በመግረፍ፣ ‹‹ልጅህን እንገለዋለን! ሚስትህን አስረን በፊትህ ቶርች እናደርጋታለን! ብልትህ ላይ ሀይላንድ በማንጠልጠል መሀን እናደርግሃለን!›› ሲሉ በማስፈራራት ከፍተኛ የሆነ እንግልትና ስቃይ አድርሰውብናል።

ይህም አልበቃ ብሏቸው በሃገሪቱ የቅጣት ጣሪያ የመጨረሻ የሆነውን የወንጀል አንቀፅ ጠቅሰው ከሰሱን። ‹‹ህገ-መንግስት ይከበር!›› ብለን በጠየቅን ህገ-መንግስትን ለመናድ በመንቀሳቀስ ወነጀሉን። ተቃውሟችን ፍፁም ሰላማዊ ሆኖ ሳለ ‹‹ከእኛ ውጪ ያሉ እምነቶች ከሃገሪቱ መጥፋት አለባቸው ብለዋል›› ሲሉ ከሰሱን። ሃይማኖታዊ የመብት ጥያቄያችንን ‹‹ድብቅ የፖለቲካ አጀንዳ ነው›› በሚል ሊያጠለሹ ሞከሩ። ‹‹ህዝብ ያልመረጣቸው የመጅሊስ አመራሮች በህገ-ወጥ መንገድ መጥተው አይመሩንም! ፍትሀዊ ምርጫ ይካሄድ!›› ባልናቸው ‹‹መንግስት ይውረድ! መንግስት አያስተዳድረንም! ብለዋል›› በሚል ወነጀሉን።

ያዘጋጁት ክስ የህግ ባለሙያ ቀርቶ ማንም የህግ ግንዛቤ የሌለው ሰው በሚረዳው ደረጃ በህግ ስህተቶችና አመክኖአዊነት በጐደላቸው ሃሳቦች የተሞላ፣ በህግ ወንጀል ያልሆኑ አረፍተ ነገሮች እና ቃላት ወንጀል ተደርገው የተጠቀሱበት ፍፁም ተራ እና የሃገሪቷን የፍትህ ሁኔታ የሚያስገምት ክስ ነው። ምንም እንኳን ‹‹ክሱን ዳኞች ስርዓት ሊያስይዙት ይገባል›› በሚል የፀረ-ሽብር አዋጁን በመቃወም እና ክሱ ላይ ያሉ ስህተቶችን ሁሉ ነቅሰን በማውጣት የክስ መቃወሚያ ያቀረብን ቢሆንም የዳኞች ብይን ክሱን ይበልጥ የማይገባና ውስብስብ አደርጎታል።

ከታሰርን ጀምሮ የደረሱብን የህግ ጥሰቶች እና የፍትህ እጦቱ ከፍርድ ቤት ሂደት ራሳችንን ሙሉ ለሙሉ እንድናገል የሚገፉ ነበሩ። ሆኖም ግን የተወነጀልንበት ክስ ምን ያህል ከእውነት የራቀ፣ ጥያቄያችን ሃይማኖታዊ እና ህገ መንግስታዊ መሆኑን እና እንቅስቃሴያችንም ፍፁም ሰላማዊ እንደነበር ለህዝባችን በፍትህ አደባባይም ጭምር ለማሳየት ስንል የፍርድ ሂደቱ ውስጥ መግባቱ የተሻለ መሆኑን በማሰብ ሃሳባችንን ቀይረናል።

መንግስት በአግባቡ ሊተውነው ያልቻለውን አሳፋሪ የፍርድ ቤት ድራማውን ህዝብ እንዳያይበት ለመሸሸግ በመገደዱ ‹‹የተከሰሱ ሰዎች ክስ ከቀረበባቸው በኋላ ተገቢ በሆነ አጭር ጊዜ ውስጥ በመደበኛ ፍርድ ቤት ለህዝብ ግልፅ በሆነ ችሎት የመስማት መብት አላቸው›› የሚለውን ህገ-መንግስታዊ መብት በመጣስ ችሎቱ ዝግ እንዲሆን ተደርጎ ቆይቷል። በዝግ ችሎቱ የምስክር መስሚያ ጊዜ ብዙ አስገራሚ ድራማዎችን አይተናል። ዓቃቤ ህጎች ዳኞች የሚሰጡትን ብይን እንደማይቀበሉ እስከመግለጽ የደረሱበትን እና ምስክሮችን ማለት ያለባቸውን አሰልጥነዋቸው እንደሚያመጡ አምልጧቸው የተናገሩበትን አጋጣሚ ታዝበናል። በወቅቱ ‹‹ጋዜጠኞች፤ ዲፕሎማቶች እና ህዝባችን ምነው ይህንን አይተው በነበር?›› ብለን ከመመኘት ውጭ ምርጫ አልነበረንም።

ማንኛውም ታራሚም ሆነ ተጠርጣሪ በማረሚያ ቤት ሊያገኛቸው የሚገቡ በህግ የተደነገጉ መብቶች አሉ። መብቶች ግን እንደተለመደው ከወረቀት ዘለው መሬት ጠብ ማለት አልቻሉም። የፖለቲካና የህሊና እስረኞች ላይ ሲሆን ደግሞ መብቶች በቅጣት ይተካሉ። ካለው የጋራ ችግር በተጨማሪ በእኛ ላይ በተለየ መልኩ በጥላቻ እና በበቀል ስሜት የደረሰብን እንግልት ህሊና ያለውን ሁሉ የሚጎዳ ነው። ከቤተሰቦቻችን መካከል ከጥቂቶች ጋር በስተቀር እንዳንገናኝ ተደርጓል። የምንጠየቅበትንም ሰዓት ከእስረኞች ሁሉ በመለየት በቀን ለሃያ ደቂቃ ብቻ እንዲሆን በማድረግ አድሎ እና መገለል ተፈፅሞብናል። በመካከላችን ልጆቹና ቤተሰቦቹ እንዳይጠይቁት የተደረገም አለ። ከሁሉም በላይ ከባድ ህመም ያለባቸው፤ ሆስፒታል ሄደው እንዲታከሙ የታዘዘላቸው፤ ቀዶ ጥገና እንዲደረግላቸው የተመራላቸው እና በማእከላዊ የደረሰባቸውን ድብደባ ለመታከም የጠየቁ ለዓመት ከአራት ወር በላይ መፍትሄ ሳያገኙ ስቃዩን ይዘው ‹‹የፍትህ ያለህ!›› እያሉ ይገኛሉ። ማረሚያ ቤት የደረሱብን እና እየደረሱብን ያሉ አድሎዎችንና እንግልቶችን ሁሉ ዘርዝረን ጉዳያችንን ለሚመለከተው ፍርድ ቤት ብናቀርብም የማረሚያ ቤቱ ኃላፊዎች ፍርድ ቤት እንኳ ለመቅረብ ፍቃደኛ ሳይሆኑ ሶስት ጊዜ ቀጠሮ አሳልፈዋል።

ሙስሊሙ ማህበረሰብ የመብት ጥያቄ እንቅስቃሴውን ከጀመረ በኋላ መንግስት በነጋዴውና በተማሪው፣ በመንግስት መዋቅር ውሰጥ በሚሰሩ አካላት፣ በሃይማኖት አባቶች እና በአስተማሪዎች፣ እንዲሁም በኢስላማዊ ተቋማት ላይ ሰብዓዊነት የጎደለው እና ህገ-መንግስቱን የሚጻረር የመብት ጥሰት መፈጸሙን ቀጥሎበታል። በበርካታ የክልል ከተሞችና ሙስሊሙ ደስታውን በሚገልጽበት የዒድ ዕለት በአዲስ አበባ ፈጽሞ ልንረሳው የማንችለውና ጭካኔ የተሞላበት ግፍ ፈጽሞብናል። የምንሳሳላቸው እና የምንወዳቸው ወገኖቻችንን እና ቤተሰቦቻችንን ለእስር፣ ለሞትና ለአካል ጉዳተኝነት ዳርጎብናል። ይህ ሁሉ ስቃይ እና መከራ በአንድ በኩል የመንግስትን ግፍ እና ለህግ ተገዢ አለመሆን ሲያጋልጥ በሌላ በኩል የህዝባችንን ፅናት እና ቁርጠኝነት አሳይቶናል። በየትኛውም ሃይማኖት፣ ባህል እና ልማድ ግፍ የተጠላ ሲሆን ለመብት ሲሉ መሰዋት ደግሞ ክብር ነው። ስለዚህ ለሃይማኖታችሁ፣ ለክብራችሁ እና ለደህንነታችሁ ለተሰደዳችሁ፣ ለታሰራችሁ፣ ለተደበደባችሁ እና ቤተሰቦቻችሁን ላጣችሁ ሁሉ ያለንን ክብር እንገልጻለን፤ በሀገራችን ለሚሰፍነው የሃይማኖቶች ነፃነት እና እኩልነት የመሰረት ድንጋይ የሚሆነው ዛሬ እናንተ የከፈላችሁት መስዋእትነት ነውና!

ለሁለት ዓመታት ያለ ምንም መሰላቸት እንግልቱ፣ ማስፈራሪያው፣ እስሩ፣ ድበደባው እና ግድያው ሳይበግራቸው እና ሰላማዊውን የተቃውሞ መስመር ሳይለቁ ለሃይማኖታቸው ያላቸውን ፍቅር ላሳዩ፣ እንዲሁም ይህን ድንቅ ታሪክ ለሰሩ አባቶች፣ የሃይማኖት መሪዎችና አስተማሪዎች /በተለይ ደግሞ ወጣቶች እና ሴቶች/ ያለንን ከፍ ያለ ክብር እና ምስጋና ልናቀርብ እንወዳለን። በሰራችሁት ሁሉ ተደስተናል፤ ኮርተንባችኋልም!

መንግስት የሃይማኖት ግጭት ለመፍጠር ያደረገውን ሙከራ ንቆ በመተውና ጉዳዩን በብስለትና በሰከነ መንፈስ በማየት፣ እንዲሁም እውነታውን ለመረዳት ጥረት በማድረግ ረገድ ሌሎች ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን፣ በተለይም ህዝበ ክርስትያኑ ላደረጋችሁት ትብብር ሳናመሰግን አናልፍም። በእውነቱ የሃይማኖት ልዩነት ሳያግደን በህዝብ ደረጃ ተከባብረን ስለመኖራችን ከተነሱ ምሳሌዎች ሁሉ በዚህ ሁለት ዓመት ውስጥ ያሳየነው መከባበር እና አንድነት ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ነው። ይህ ብሄራዊ አንድነት የበለጠ ተጠናክሮ በጋራ ለምንገነባት ሃገራችን ታላቅ ብርታት እንደሚሆን ጠንካራ እምነት አለን።

በተጨማሪም የፕሬስ ነፃነት በተነፈገበት ተጨባጭ የመብት ጥያቄያችንን እውነታ ለመገንዘብ ማስፈራሪያዎችን እና ዛቻዎችን አልፋችሁ፣ የመንግስትን የተሳሳተ እና ኢ-ህገመንግስታዊ አካሄድ ለይታችሁ ሂደታችን ላይ አዎንታዊ አስተያየቶች እና ገንቢ ትችቶችን ለሰጣችሁ ጋዜጠኞችና በሚዲያው ዘርፍ ለተሰማራችሁ ባለሙያዎች ሁሉ ልባዊ ምስጋናችንን እናቀርባለን።

ወገኖቻችሁ ያጡትን ፍትህ እና ነጻነት በሃገራችሁ ለማየት በመጓጓት የበኩላችሁን አስተዋጽኦ ለማበርከት የምትጣጣሩ በስደት የምትገኙ ሙስሊሞችና የሌሎች ሀይማኖቶች ተከታይ ወገኖቻችን በሙሉ ላደረጋችሁት ሁሉ ምስጋናችን ላቅ ያለ ነው። በሀገር ውስጥ ለተጠናከረው የአጋርነት ስሜት የእናንተ አስተዋጽኦ የመጀመሪያውን ድርሻ ይይዛል።

በአጠቃላይ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ፣ ነጋዴው፣ አርሶ አደሩ፣ አርብቶ አደሩ፣ ተማሪው፣ ሴቱ፣ ወንዱ፣ ወጣቱ፣ አዛውንቱና ሌላውም፣ እንዲሁም በመንግስት መዋቅር ስር ሆናችሁ የመንግስትን የተሳሳተ አካሄድ ስትቃወሙ የነበራችሁ ዳኞች፣ ዓቃቤ ህጎች፣ አባቶች፣ ፖሊሶች፣ የጦር ሰራዊትና የፓርላማ አባላት በሙሉ ከፍ ያለ ምስጋናችንን እናቀርብላችኋለን። የጥረታችሁን ፍሬ በቅርቡ ያሳያችሁ ዘንድም አላህን እንለምናለን!

መልእክታችን

1/ በሙስሊሞች መካከል እና በሙስሊሙና በክርስትያኑ መካከል የታየውን አንድነትና መከባበር ሁላችንም በጋራ እንድንጠብቀው፣ እንዲሁም መሰረቱ የፀና ሆኖ እንዲቀጥል ለማድረግ እንድንጥር አደራ እንላለን። ሀገራችን ከእርስ በእርስ ሽኩቻዎች ወጥታ የእድገትና ብልጽግና ጉዞ እንድትጀምር ከተፈለገ ትክክለኛ የሃይማኖት ነፃነት፣ እኩልነት እና መከባበር በቅድሚያ እውን መሆኑ አማራጭ የሌለው ግዴታ ነው። የሃገራችንን እድገት የጋራ አላማ አድርገን፣ የጋራ ተጠቃሚ ሆነን መኖር የምንችለው ስጋትና ጥርጣሬውን በፍቅርና መተማመን ስንተካው ነው።

2/ በፅናት ሰላማዊ የመብት ትግሉን የምንቀጥል መሆኑንና የሚያስከፍለንን መስዋዕእትነት ሁሉ ለመክፈልም ዝግጁ መሆናችንን ለህዝባችንም ሆነ ለመንግስት መልእክት ለማስተላለፍ እንወዳለን። ለቀጣዩ ሰላማዊ የመብት ትግል እርከንም እኛም ህዝባችንም በሙሉ ዝግጅት ላይ መሆናችንንና ለመብታችን ተግተን ሰርተን መስዋዕት ከመሆን ወደኋላ የማንል መሆኑን ስንገልጽ በከፍተኛ ወኔ ተሞልተን ነው!

3/ መንግስት እየፈጸማቸው ያላቸውን ኢ-ህገ መንግስታዊ ተግባራት፣ በህዝበ ሙስሊሙ ላይ እየፈጸመ ያለውን እስራት፣ ግፍ፣ መስጂድ ነጠቃ፣ የሀሰት ውንጀላና የሃይማኖት ሰዎችን፣ ጋዜጠኞችንና የመብት ጠያቂዎችን በሽብርተኝነት መፈረጅና መሰል ህገ መንግስታዊ የመብት ጥሰቶችን በአስቸኳይ እንዲያቆም ጥሪያችንን እናቀርባለን። በማእከላዊና በተለያዩ እስር ቤቶች የሚፈጸሙት ኢ-ሰብዓዊ ድርጊቶች እንዲቆሙና የህሊና እስረኞችም መለቀቅ እንደሚገባቸው ለመግለጽ እንወዳለን። መላው የኢትዮጵያ ህዝብ የእውነተኛ ሰላም፣ ፍትህ፣ ዴሞክራሲ እና ልማት ባለቤት ሆኖ ማየት የዘወትር ህልማችን መሆኑንም ሳንገልጽ አናልፍም፡፡

በመጨረሻም በቃል ኪዳናችን ጸንተንና መነሻው ላይ ከነበረው በተሻለ ሁኔታ ተንቀሳቅሰን ፍጹም በሰለጠነና በተጠና መልኩ የተሟላ ፍትህ እና ነፃነት ለማግኘት በጽናት እና በቆራጥነት ሁሉም ባለድርሻ አካል እንቅስቃሴውን ከዳር እንዲያደርስ አደራ ለማለት እንወዳለን። የእንቅስቃሴው ማብቂያ ድልና ስኬት እንደሚሆን አንጠራጠርም!

አላሁ አክበር!

ግልባጭ፡- እዚሁ አገር ውስጥ እና በውጭ አገራት ለሚገኙ የህትመትና የኤሌክትሮኒክስ ሚዲያዎች


ከርዕዮት ዓለሙ ችሎት ጀርባ ያለው ጥቁር ዳኛ ማነው? – የሰነድ ማስረጃ የያዘ ጥብቅ ምስጢር

$
0
0

ከጋዜጠኛ ስለሺ ሐጎስ

ክፍል አንድ

የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ጥር አስር ቀን 2004 ዓ.ም በእነ ርዕዮት አለሙ ላይ ያስተላለፈው የጥፋተኝነት ውሳኔ በችሎቱ የተሰየሙት ዳኞች በነጻ ህሊና የሰጡት ፍርድ ነው ብሎ ያመነ ሰው አልነበረም፡፡ እዚህም እዚያም ሲወራ የነበረው ውሳኔው በመንግስት ፍላጎት ላይ የተመሰረተ መሆኑ ነበር፡፡ ፕሮፌሰር መስፍንን ጨምሮ በርካታ ሰወች ይህንኑ በአደባባይ ጽፈውታል፡፡ ቆየት ብሎ ግን ዳኛው የተጻፈለትን እንዳነበበ የሚገልጹና ተጨማሪ ነገር ለማወቅ የሚገፋፉ መረጃዎች ወደኔ መምጣት ጀመሩ፡፡

እርግጥ የኢትየጵያ የፍትህ ስርአት በተደጋጋሚ ተፈትኖ የወደቀና ነጻነቱ ጥያቄ ውስጥ የገባ ከመሆኑ አንጻር እንዲህ አይነት የጥርጣሬ ድምጾች መሰማታቸው በራሱ ብዙ የሚገርም አይደለም፡፡ በመሆኑም በጉዳዩ ላይ የምር እንዳስብ የሆንኩት ዳኛው የተጻፈለትን እንዳነበበ በመስማቴ ብቻ አይደለም፡፡ ይልቁንም ከዚያ በፊት በነበረው የፍርድ ሂደት ያስተዋልኳቸው ሦስት አጠራጣሪ ክስተቶቸ ናቸው እንደ ጋዜጠኛም ሆነ እንደ ርዕዮት የቅርብ ሰው ስለ ጉዳዩ ብዙ ለማወቅ እንድታትር የገፋፋኝ፡፡

የመጀመሪያው፣ ርዕዮት በማዕከላዊ ምርመራ ላይ እያለች የታዘብኩት ነው፡፡ ርዕዮት በተያዘች በማግስቱ አራዳ ፍርድ ቤት ቀርባ ፖሊስ የ28 ቀን የምርመራ ጊዜ ሲጠይቅ አባቷና ጠበቃዋ የሆኑት አቶ አለሙ ደግሞ ቤተሰብ እንዲጠይቃትና የህግ ምክር እንድታገኝ አመለከቱ፡፡ ዳኛዋም ፖሊስ ይህንኑ እንዲፈጽም አዘውና የ28 ቀን የምርመራ ጊዜ ሰጥተው ችሎቱ አበቃ፡፡ በዚህ ጊዜ ግን ርዕዮት፣ ጠበቃም ሆነ ቤተሰብ ሳታገኝ 28ቱ ቀን አለፈ፡፡

የነበረው አማራጭ የቀጠሮው እለት ጠበቃዋ ገብተው ድጋሜ እንዲያመለክቱ ማድረግ ብቻ ነበር፡፡ እኛም ፍርድ ቤት ስትመጣ ጠብቀን ቢያንስ አይኗን ለማየት ጓጉተናል፡፡ በዕለቱ የሆነው ግን በጣም አስገራሚም አሳዛኝም ነበር፡፡

ቀጠሮው ከሰዓት በኋላ 8 ሰዓት ነበረ፡፡ በዚያን ዕለት ጠዋት 2፡30 ቁርስ ላደርስላት ወደ ማዕከላዊ ስሄድ ከዚያን ዕለት በፊትም ሆነ በኋላ አይቻት የማላውቃት አንዲት ልጅ “ርዕዮትን በሌሊት ወደ ፍርድ ቤት ወስደዋታል ሮጠህ ድረስባት” ብላኝ ካጠገቤ ብን አለች፡፡ ለአቶ አለሙ በስልክ ይህንኑ ነግሬ ወደ ፍርድ ቤቱ አመራሁ፡፡ ቦታው ቅርብ በመሆኑ 10 ደቂቃ ባልሞላ ጊዜ ደረስኩ፡፡ እኔ ወደ ግቢው ስገባ ርዕዮት በፒካፕ መኪና ተጭና እየወጣች ነበር፡፡

የፍርድ ቤቱ የቀጠሮ ሰዓት የተለወጠው ባጋጣሚ ወይም በስህተት ሊሆን ይችላል በሚል ይህ ለምን እንደሆነ መዝገብ ቤቱን ጠይቀን የተረዳነው ኬዙን ያየችው ዳኛ በህመም ምክኒያት ለረጅም ጊዜ ስራ የምትገባው ከሰዓት በኋላ ብቻ መሆኑንና ሁኔታው ለእነሱም እንግዳ ነገር መሆኑን ነው፡፡ ስለዚህም የቀጠሮው ሰዓት ለውጥ በፖሊስ ፍላጎት ሆን ተብሎ ተፈጽሟል ለማለት ይቻላል፡፡ ይህ ማለት በፍርድ ቤቱና በፖሊስ መሀከል ሊኖር የሚገባው መስመር ላይ ችግር አለ ማለት ነው፡፡

ሌላው የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ለ5 ወራት ያህል ግራና ቀኙን ሲያከራክር ሰንብቶ ታህሳስ 17 2004 ዓ.ም የመጨረሻውን ፍርድ ለመስጠት በተሰየመበት ዕለት የነበረው ሁኔታ እንዲሁ ጥርጣሬውን የሚያጠናክር ነው፡፡ ቀጠሮው ከጠዋቱ 3፡00 የነበረ ቢሆንም በዚያን ዕለት ይሰጣል የተባለውን ፍርድ ለመስማት የተገኙ ሰዎች የችሎቱን አዳራሽ የሞሉት ቀደም ብለው ነበር፡፡ ዳኞቹ 1 ሰዓት አርፍደው 4፡00 ላይ ችሎቱ ተሰየመ፡፡ ወዲያውኑ ውሳኔው ማለቁንና ይሁን እንጂ በኮምፒውተር ተጽፎ ስላላለቀ ከሰዓት በኋላ እናርገው አሉ፡፡ በዚህ ጊዜ የእነውብሸት ጠበቃ አቶ ደርበው “ከሰዓት ሌላ ቀጠሮ ስላለኝ አልችልም” ብለው ከአራት ቀን በኋላ ለታሀሳስ 21 እንዲሆን አማራጭ አቀረቡ፡፡ ዳኛው ግን አልተቀበሉትም፡፡ “እነዚህ ሰወች ያሉት በማረሚያ ቤት ነው፤ ቀጠሮው ከሚራዘም 7 ሰዓት እንገናኝና እስከ 8፡00 እንጨርሳለን” የሚል አማራጭ አቅረቡና በዚሁ ተስማሙ፡፡

የዳኛው ንግግር የሆነ ጥሩ ነገር ሊኖር ይችላል የሚል ተስፋ ስላጫረብን ሁላችንም ከዚያው ሳንወጣ ሰዓቱ እስኪደርስ መንቆራጠጥ ያዝን፡፡

አይደርስ የለ ሰዓቱ ደርሶ ችሎቱ በሚሰየምበት አዳራሽ ተኮለኮልን፡፡ ዳኞቹ ግን በሰዓቱ የሉም፡፡ ግማሽ ሰዓት አለፈ፤ አልመጡም 8 ሰዓት ሲሆን ሁላችንም ቀጠሮ አለኝ ያሉትን ጠበቃ ደርበውን እያየን መሳቀቅ ያዝን፤ ሰዓቱ እየነጎደ ነው፤ 9 ሰዓት ሆነ፡፡ ዳኞቹም አልመጡም ጠበቃ ደርበውም አልሄዱም፡፡ 9፡45 ላይ ዳኞቹ መጡ፡፡ አቶ ደርበው ግን ቀሩ፡፡

ዳኛው ስለማርፈዳቸው ምንም ሳይሉ አሁንም ጽሁፉ ስላልደረሰ በሚል ተለዋጭ ቀጠሮ ለመስጠት አጀንዳቸውን ማገላበጥ ያዙ፡፡ “አራት ቀን ምን ሲደረግ ይራዘማል” ያሉት ዳኛ ከ23 ቀን በኋላ ለጥር 10 2006ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥተው ዕለቱና ችሎቱ አበቃ፡፡ ተስፋችንም እንዲሁ፡፡

ይህ ሁኔታ አንዳች ደስ የማይል ነገር እየተከናወነ እንዳለ የሚናገር መሆኑ እንዳለ ሆኖ ቀደም ሲል ያነሳነውን ጥርጣሬ ወደ እውነት የሚገፋው ተጨማሪ ክስተት፣ ለቀጠሮው መራዘም ምክኒያት ሆኖ የቀረበው ነገር ነው፡፡ የታህሳስ 17ቱ ቀጠሮ ወደ ጥር 10 የተሻገረው ውሳኔው በኮምፒውተር ተጽፎ አለማለቁ ሆኖ ሳለ ዳኛው ጥር 10 ያነበቡት በኮምፒውተር ያልተተየበ የእጅ ጽሁፍ ነበር፡፡ ስለዚህም የቀጠሮ ለውጡ የተካሄደው ከችሎቱ ጀርባ ባለ ሌላ ምክኒያት እንጂ ዳኛው እንዳሉት የኮምፒውተር ጽሁፍ ጉዳይ አይደለም ለማለት ይቻላል፡፡

እነዚህ ከላይ የተጠቀሱትና ሌሎችም ትንንሽ የሚመስሉ በርካታ ትዝብቶች ዳኛው የተጻፈለትን እንዳነበበ ከሚገልጸው መረጃ ጋር ተደምረው ሲታዩ የሚሰጡትን ትርጓሜ በማስረጃ ለማረጋገጥ መጠነኛ ጥረቶች ተደርገዋል፡፡

ይህን ለማረጋገጥ ሁነኛና ቀላል ዘዴ ሊሆን የሚችለው በእለቱ ዳኛው ያነበበውን የእጅ ጽሁፍና የዳኛውን ትክክለኛ የእጅ ጽሁፍ አግኝቶ ማመሳሰል ነው፡፡ በዚሁ መሰረት ይህን ለማድረግ የሚያስችሉ ማስረጃዎች ተገኝተዋል፡፡ ማስረጃዎቹ ዳኛው በዕለቱ ያነበበው ጽሁፍ በራሱ በዳኛው የተጻፈ አለመሆኑን የሚያሳዩ ናቸው፡፡

ቀጣዮቹን ሁለት ምስሎች ይመልከቱ
reyot alemu 1

reyot alemu 2

ኢትዮጵያ የጋራችን ኤርትራ የግላችን! “ከ 40 ግድብ አንድ የአሰብ ወደብ” –ከሰመረ አለሙ

$
0
0

ኤርትራዉያኖች ተበልጠዉ በኢትዮጵያ ተንደላቅቀዉ የሚኖሩበትን ሁኔታ ከተነጠቁ በሗላ እንደገና እጃቸዉ ለማስገባት በተለያየ ዘዴ ቢጠቀሙም ህዋአት እና ሻቢያ “እባብ ለባብ ይተያያል ካብ ለካብ” አይነት ሆነና ኤርትራዉያን የፈለጉትን ያህል ሳይሆንላቸዉ ቀርቶ እዚሀ ላይ ተደረሷል። የጸሀየ ግብአተ መሬት ፉከራ ከከሸፈ በሗላ ኤርትራዉያን ኢትዮጵያን ሊበትንልን ይችላል የሚሉትን ሀይል እና ዘዴ ቢበደሩም መላ ቢመቱም ቢያሰባስቡ እና ቢያሰለጥኑም፤ የኢትዮጵያ አንድነት ፍንክች ሳይል ቀርቶ እዚህ ላይ ይገኛል። የኤርትራ ምሁራን ኢትዮጵያ ያስተማረቻቸዉ ተራ ወርደዉ የሚያስገምት ጽሁፍ ቢጽፉም፤ በቀይ ባህር ማተሚያ ቤት የእዉሸት ፋብሪካቸዉ ተረት መሰል የኢትዮጵያ ታሪክ ቢያሳትሙም፤ ቅጥፈት የተሞላዉ ወረቀት ቢጽፉም ድካማቸዉ ሁሉ ያለምንም ፍሬ ልፋት ብቻ ሁኖ ቀርቷል
ታድያ ለሁሉም ብልሀት አለዉ እንዲሉ ይህ ዘዴ ያለመስራቱን የተረዱ ኤርትራዉያን አቶ መለስንና ለኤርትራ ስስ ልብ ያላቸዉን የህወአት ባለስልጣኖች በመጠቀም ዛሬም ከዜጋዉ በላይ የኢትዮጵያን በረከት እየተጎናጸፉ ይገኛሉ። በተለይ ከአቦይ ስብሀት አለንላችሁ መግለጫ በሗላ ብዙ ኤርትራዉያን ባላቸዉ ንክኪ አማካኝነት በብዛት ወደ ሀገር ጎርፈዋል ከኢትዮጵያ ሳይባረሩ የቀሩትን ወገኖቻቸዉንና በዉጭ ሀገር በሚኖሩ ኤርትራዉያን አማካይነት የዉስጥ ለዉስጥ ግንኙነታቸዉን በማጠናከር ኢትዮጵያ ዉስጥ የቀድሞ ቦታቸዉን ይዘዋል።
በቅርቡ በወጣዉ ጽሁፍ ወደ 1700 የሚሆኑ የኤርትራ ተወላጆች ከኢትዮጵያዉያን ወጣቶች በላይ ቅድሚያ ተሰጥቷቸዉ ወደ ዩኒቨርሲቲዉ ጎርፈዋል ይህ አፊሲያላዊ ቁጥር ነዉ በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ከፍተኛ ቁጥር እንዳላቸዉ እማኝነት ያላቸዉ ዜጎች በቁጭት ይገልጻሉ። እንግዲህ ልብ ይበሉ እንደ አይን ብሌን በምናያቸዉ የትምህርት ተቋማት ኢትዮጵያዊዉ ወጣት በጫት የቀን ህልም ሲያልም ትላንት ኢትዮጵያ ላይ የተኮሱ ዛሬም ለኢትዮጵያ ክብር እና ፍቅር የሌላቸዉ ኤርትራዉያን በኢትዮጵያ ዩኒቨርስቲዎች ሲማሩ በእጂጉ ያሳዝናል።እነሱ እንዲማሩ ሌላዉ ኢትዮጵያዊዉ ቦታዉን ለነሱ መልቀቅ አለበት ማለት ነዉ።
ethiopias-planned-renaissance-damይህ በትምህርት ዘርፍ የተገኘዉ መረጃ ነዉ። በንግድ፤እርሻ፤ፐሮፐርቲን በተመለከተ ከሀገሬዉ ነዋሪ በላይ እዛ ያሉትም ከኤርትራ፤ከአዉሮፓ እና አሚሪካ እየጎረፉም በከፍተኛ ሁኔታ በመጠቀም፤በመጠቃቀም፤ከባንክ በመበደር እና በማምታት ህገ ወጥ ጥቅም በማግኘት ላይ ይገኛሉ። ገንዘብ ማሸጋገር ዋናዉ አገር መጉጃቸዉ ነዉ በዚህም ሂደት ገንዘብ አገሩን እየለቀቀ በባህር ማዶ ባንክ እና በዉጭ ሀገር ኢንቨስትመንት ላይ ይዉላል። እነሱም በዚህ ህገ ወጥ ስራ አንድም ጠላታቸዉ ኢትዮጵያን ይጎዳሉ አንድም ትርፋቸዉን ያደልባሉ። በህጋዊ መንገድ ቀረጥ ከፍለዉ ከመስራት ይልቅ ህገወጥ የሆነዉ መንገድ ባያተርፋቸዉም ይመርጡታል።
የሚያሳዝነዉና አንጀት የሚያበግነዉ እኛዉ መሀል ስንት ቤት ሰርተሀል? ሰሞኑን ምን ልከሀል? ትንሺ ገንዘብ ሰጥተህ በትግራይ በኩል ዘመድህን አስመጣ እያሉ በድፍረት ሲያወሩ በጣም ልብ ይሰብራል። ይህች ሀገር መች ነዉ ለዜጎቿ የምትሆነዉ? መች ነዉ ዜጎቿን የምታከብረዉ? መች ነዉ ዜጋዉ ከእንደዚህ አይነት ጥቃት ድኖ ሀገሩ የእርሱ መሆኑን የሚረዳዉ ብዬ አንዳንዴ እራሴን እጠይቃለሁ። እንደዉም ደግሞ የድፍረት ድፍረት ከህዋአት ጭቆናም ነጻም የሚያወጡን እነሱ ሁነዉ ተገኝተዋል ጆሮ የማይሰማዉ የለ። የአለሙ ሚዲያ አምነስቲ ኢንትርናሽናልን ጨምሮ በወር 3000 ኤርትራዊ አገሩን ይለቃል ሲባል አቶ ኢሳይያስ አፈወርቂ ከህዝቡ ፍቅር የተነሳ ያለ አጃቢ ነዉ የሚሄዱት ብለዉ ተቃዋሚዎቻችንን ሊያሳምኑን ይከጂላቸዋል ታዲያ ይህ ሁሉ ፍልሰት ነጻነት ፍለጋ ካልሆነ ፍለሰቱ አድቬንቸር ነዉ ማለት ነዉ ወይስ አቶ መለስ እንዳሉት ኤርትራዉያን እግር እንጂ አገር የላቸዉም የሚባለዉ አባባል እዉነት ሊሆን ነዉ?
በመሰረቱ አፍቃሪ ኢትዮጵያ ኤርትራዉያን ኢትዮጵያ ዉስጥ መኖራቸዉ ቅር የሚለኝ ሰዉ አይደለሁም ባለፈዉ ጽሁፌም እንደገለጽኩት ሀገሪቱ ዛሬ በስልጣን ላይ ቁጭ ብለዉ ከገደሏት በላይ ለሀገራቸዉ ኢትዮጵያም የሞቱ ታላላቅ የኤርትራ ተወላጆችንም ገልጫለሁ ምንም እንኳን ዛሬ በህይወት ባይኖሩም ለነሱ ያለኝ አድናቆትና ክብር ከጊዜዉ ጋር የሚደበዝዝ አይሆንም። እኔም የምኖረዉ በዉጭ ሀገር ነዉ ልዩነቱ እኔ ዛሬ የምኖርበትን ሀገር በክብር እና በፍቅር የማገለግል ነኝ በሀገሩ ተጠቃሚ ሁኜ ለሀገሩ ጥፋት የምመኝ አይደለሁም። ይህ ነዉ የእኔና የዘመኑ ኤርትራዉያን ልዩነት።
ዛሬ ሰዉ ምን ይለኛልም ቀርቶ ኤርትራዉያን በግላጭ ኢትዮጵያ የጋራችን ኤርትራ የግላችን፤ የአባትህ ቤት ሲዘረፍ አብረህ ዝረፍ የሚል ፌዝ የሚመስል ፌዝ ያልሆነ ቋንቋ በብዛት ሲጠቀሙ ይሰተዋላሉ። የሚገርመዉ ሀገር ዉስጥ ኑሮዉን ዘርግቶ የሚገኘዉ ኤርትራዊ ወይም ደግሞ ወደ ኢትዮጵያ በፍልሰት የሚገባዉ ኤርትራዊ ስለ አሰብ ምን ታስባለህ ስለ ባድሜ ምን ታስባለህ ተብሎ ቢጠየቅ መልሱ ለማያዉቃት፤ ላልኖረባት ፤ ላልተጠቀመባት፤ ለተንገላታባት አገሩ ኤርትራ ነዉ።

ኤርትራዉያን ኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያዉያን ሰፈር እንዴት ተንሸራተዉ እንደገቡ ግንዛቤ ቢያስፈልግ አንድም የህዋት ንክኪያቸዉን በመጠቀም፤ማንነታቸዉን በመለወጥ ሲሆን ሌላዉ ደግሞ በግንዛቤ የተጎዳዉን ኢትዮጵያዊ እየመረጡ በመጠቀም ነዉ። አንበሳዉ አለማየሁ መሰለንማ ማን ይደፍረዋል ተጠቃሚዉን ይጠቀምበታል እንጂ። እንግዲህ ወደፊት በስፋት ብመለስበትም ጀግና በጠፋበት ዘመን እንደ ቀድሞቹ ጀግኖች አያቶቹ በጠላት ሜዳ ተረማምዶ ግዳይ ጥሎ የቁርጥ ቀን ሲመጣ ኢትዮጵያዊነት ምን ማለት እንደሆነ አስመስክሮ ኢትዮጵያዉያን ሰፈር እንደገና የተሀድሶ መንፈስ ለሰጠዉ አለማየሁ መሰለ በያለንበት ዋንጫችንን እንድናነሳ በትህትና እጠይቃለሁ ገድሉም ከጊዜዉ ጋር ሊደበዝዝ አይገባም። በእዉነቱ አለማየሁ ያነን የመሰል ገድል ሲሰራ ዉቅያኖስ ጠልቆ ዉሀ ሳይነካዉ እንደወጣ ዋናተኛ ነዉ የምቆጥረዉ። ከጀብድ ስራዉ በላይ ደግሞ ንግግሩ የቀድሞዎቹ አንበሶች አያቶቹን መንፈስ የሚያንጸባርቅ ነበር። አለማየሁ በአንድ ቃለ መጠይቅ “ተስፋዬ ምንም እንኳን የሻቢያ ሰላይ ቢሆንም እኛም ከእሱ በላይ መስራት እንችላለን በሚል ጽኑ ኢትዮጵያዊ መንፈስ ስራዬን ተያያዝኩት” ነበር ያለዉ። ቆፍጣናዉ አለማየሁ በእዉነት የዘመናችን በላይ ዘለቀ ቢባል ብዙም ማጋነን አይሆንም ሰዉ የሚለካዉ እንደየዘመኑ ነዉና።

ኢትዮጵያ ጥንታዊ እና ገናና አገር ነች በዚህ በረጂም ዘመኗ ረጅም ስርን ተክላለች በረጂም ዘመኗም ብዙ ጠቃሚ እዉቀቶችን፤እምነቶችን፤መረጃዎችን ለዜጎቿ እና ለአለም አበርክታለች ከዚህ እና ከሌላም ስንነሳ ኢትዮጵያ እንደሀገር ኢትዮጵያዉያንም እንደተከበረ ዜጋ በቀጣይነት መኖር አለባቸዉ። ኢትዮጵያ ትላንት በግርግር እንደተፈጠረች ሁሉ አንዳንድ ብሄረተኞች አንድም የበታችነት መንፈስ በተጠናወታቸዉ በሌላም በባእድ ሀይሎች እየተገፉ ኢትዮጵያን እና ኢትዮጵያዉያንን ለመፈታተን የሚያደርጉት ጥረት ያለ ይሉኝታ ሊመከት ይገባል እላለሁ።
እንግዲህ እንዲህ ያለዉን አልፎ ሂያጅ የግርግር መንፈስ ሳይበግረዉ በእዉቀቱ ስዩም እንዳለዉ ወጣቱ ኢትዮጵያ አገሩን ከአባቶቹ በበለጠ ከፍ ያለ ደረጃ ላይ ማድረስ ይገባዋል እላለሁ። ዛሬ እንዲህ አደርግልሀለሁ እንዲህ ብናደርግ የምድር መንግስተ ሰማያት እንኖራለን በሚል ቀቢጸ ተስፋ የሰፈሮቻቸዉን ልጆች እያማለሉ ኢትዮጵያዊነት ላይ ወገኖችን የሚያስኮርፉ ነገ ሀሳባቸዉ ተሟልቶ እነሱ ኢትዮጵያን ቢከፋፈሉ እንደ ደሀ አጥር ሁሉም እየጣሳቸዉ ይሄዳል እንጂ እነሱም ተጠቃሚ እንደማይሆኑ በልምምጥ ሳይሆን በድፍረት ሊነገራቸዉ ይገባል። ፍቅርን የሚያዉቅ ጀግና ብቻ ነዉ እነሱ ግን ፍቅርን ልምምጥ ያደርጉታል። እነሱን ትልቅ ያደረገ እንዲህ የማኩረፍ ነጻነት ሁሉ የሰጣቸዉ ኢትዮጵያዊነት ነዉ። በአንድ ወቅት ፕሮፌሰር ጌታቸዉ ሐይሌ የዘረኞች እብሪት ሲበዛ አይተዉ ለአንዱ ዘረኛ በሰጡት መልስ ምንሊክ ባይሰበስቡህ እራስህን አንዱ የጎረቤት አገር ታገኝዉ ነበር ያሉት ዛሬም በባዶ ሜዳ ለሚያብዱ ነገር ለጠፋባቸዉ ዘረኞች በግልጽ ሊነገር ይገባል እላለሁ። እነዚህ የምንሊክን ታላቅ ስራ የማያዉቁ ደካሞች ምንሊክ ባይሰበስቧቸዉ ስማቸዉ ሌንጮ/ሀጎስ/ጫላ/ለማ… ከመሆን ይልቅ ሪካርዶ/ሮበርት/ዴቢድ ሲሆን ሀይማኖትም በልካቸዉ ይሰፋላቸዉ ነበር። የሚያሳዝነዉ የፕሮፌሰሩ ጽሁፍ ከግማሽ ቀን በላይ በድረ ገጾች ላይ አልዋለም ምክንያቱም የታወቀ ነበር።
እዚህ ላይ ላልፈዉ የማልፈልገዉ ስለ ታላቁ የኦሮሞ ህዝብ በኢሳይያስ ታግተዉ ጻፉ በሚባሉ ዘረኞች በነ አስመሮም ለገሰና 12ኛ ክፍል ባልጨረሰ መሀይም ተጽፎ ለንባብ ሲበቃ ማየት በእጅጉ ያሳዝናል ዛሬ በኢትዮጵያ ምስረታ በኢትዮጵያ ስነጥበብ በኢትዮጵያ አስተዳደር የኦሮሞ አሻራ ያላረፈበት አንድም ነገር አይገኝም። በሀገር እና ከሀገር ዉጭ ታላላቅ የኦሮሞ ጠቢባን ባሉበት አለም ስለ ኦሮሞ ህዝብ ታላቅነት፤በደል፤ጭቆና ከኤርትራ ኤክስፖርት ሲደረግ ከምንም በላይ የሚያሳፍረዉና የሚያዋርደዉ የኦሮሞን ህዝብ እንጂ ሌላዉን አይሆንም። የኦሮሞ ህዝብ ሞግዚት የሚያስፈልገዉም አይደለም የኦሮሞ ህዘብ በደሉን እና ጥቅሙን በሚገባ ያገናዝባል የኦሮሞ ህዝብ ህመም ከአማራዉ፤ጉራጌዉ፤ወላይታዉ…. በላይ እነ አስመሮም ለገሰንና ተስፋዬ ገ/አብን ለምን እንዳመማቸዉ ነገሩ ግልጽ ነዉ እነሱን ያቃታቸዉን ሀይል እነሱ እንዲሞክሩላቸዉ ታስቦ ነዉ ታዲያ ኦሮሞ ይህን አጣ? የምን ንቀት ነዉ? ከኦሮሞ እና አማራዉ የተወለደ 10 ሚሊዮን ህዝብ ከመኖሩም በላይ የአንዱን ደም አጥርቶ አንተ ከዚህ ነህ አንተ ከዚያ ነህ የሚያሰኝ ሁኔታም አይኖርም። አሁንም የኦሮሞን ህዝብ አታላግጡበት አርፋችሁ ቁጭ በሉ ሊባሉ ይገባል። ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ምነዉ ተስፋዬ ገ/አብ ከኦሮሞ በላይ ኦሮሞ ሆነ ያሉት እነ አስመሮም ለገሰን አፍ አዘግቶ እዛዉ እስር ቤታቸዉ ሊያስቀምጣቸዉ በቻለ ነበር ታድያ እነሱ ለክብር ስላልተፈጠሩ በተቻላቸዉ መጠን ቶሎ ትርፍ ያመጣልናል ብለዉ የሚሉትን ብቻ መሞከር ስለሆነ ሊማሩ አይችሉም። እንደ እዉነቱ ከሆነ በዛሬዉ አለማችን ከማንም በላይ በባርነት ቀምበር ስር ያለ ህዝብ ቢኖር ኤርተራዊ በመሆኑ ፍትህ እና ዲሞክራሲ ካማራቸዉ እዛዉ በእስር ቤት የሚኖረዉ ህዝባቸዉንና እራሳቸዉን ነጻ እንዲያወጡ ይጠየቃሉ ለዛም ካልታደሉ ተራ የኢሳይያስ ካድሬ መሆናቸዉ ቀርቶ በክብር እንዲቀመጡ እናሳስባለን 90 ሚሊዮን ህዝብን መናቅ የጤንነት አይመስልም።
ለማጠቃለል በስልጣን ላይ የተቀመጡት ህዋቶች በአቶ መለስ ምንጠራ አክራሪ ትግሬዎች ተነስተዉ በአብዛኛዉ ኤርትራ እና አፍቃሪ ኤርትራዉያን ቦታዉን በመያዛቸዉ የትግራይ ወንድሞቻችን ነገ ከሚመጣዉ ጥፋት እራሳቸዉን ለመከለከል ከወገናቸዉ ጋር ሰልፍ እንዲቆሙ ጥሪዬን አስተላልፋለሁ። ትላንት የትግራይ ወንድሞቻችንን ነፃ ለማዉጣት፤ የትግራይ ክልል ባድሜ እና ሌሎች የኢትዮጵያ ድምበሮች እንዲከበሩ በዛ የፈሰሰዉ ደም ከንቱ ሁኖ ቀርቷል። ባድሜም ለኤርትራ ሊመለስ ዉስጥ ለዉስጥ ዲፕሎማሲዉ ተጧጡፏል ኤርትራዉያንም ያለምንም ችግር በኢትዮጵያ የቀድሞ ቦታቸዉን በመያዝ ላይ ናቸዉ። ትላንት የትግራይ ህጻናትን በቦምብ የፈጀ ሀይል ዛሬ ለትግራይ ህዝብ ወዳጂ የሚያደርገዉ ምንም ነገር ሊኖር አይችልም ህዝቡም አስተዳደሩም ትላንት የነበረ ነዉና። የኢትዮጵያም ህዘብ በችግሩ ጊዜ የችግሩ ተካፋይ ካልሆናችሁ የችግራችሁ ጊዜ ብቻ ድረሱልን ብትሉ የኢትዮጵያ ህዝብ ደግነቱና እርዳታዉ ቀጣይነት ሊኖረዉ ስለማይችል ካሁኑ ማሰብ አግባብ ነዉ እላለሁ።

እንግዲህ በእነ ገበየሁ ባልቻ፤በላይ ዘለቀ፤በላይ ቃለአብ፤ኡመር ሰመታን፤ታከለ ገ/ሀዋያት፤አብዲሳ አጋ በነ አፈወርቅ ወ/ሰማያት እና ዛሬ ደግሞ እንደ ጎሹ ወልዴን

አለማየሁ መሰለን የመሰሉ ጀግኖቻችን ባሉበት አገር ወገን ዉርድተን መቀበል በእጂጉ ይከብደዋል። እንግዲህ የተኛዉ ወገን ነቃ ብሎ እንዲጠበቅ መሰሪዎችም እንዲጠነቀቁ ያህል ነዉ እንጂ ምን ያልተጻፈ አለ ሰሚ፤ አንባቢና አገናዛቢ ከተገኘ። ይህችን ጽሁፍ ከከተብኩ በሗላ በህዋትና በሻቢያ መሀከል በራቸዉን ዘግተዉ ኢትዮጵያንን አግልለዉ ከዚህ በፊት እንዳደረጉት ሁሉ በተዋራጅነት የሚያስቀምጥ አንዳንድ ድርድሮችን በማድረግ ላይ እንደሆኑ ጠቋሚ ጽሁፎች በብዛት ተሰራጭተዋል። ኤርትራ ኢትዮጵያ ኮሚቴም የሚባል የማወናበጃ ስብስብም በየቦታዉ እንደ አሸን ብቅ በቅ እያለ ነዉ። ብዙ ለግላጋ የኢትዮጵያ ህጻናት ያለቁበት የትግራይ ከልል ባድሜም በተዋራጂነት ለኢሳይያስ አፈወርቅ በእጅ መንሻነት ህዋአት ሊያስረክበዉ እንደሆነ ይገመታል። እንግዲህ ይህንና ሌላዉን አጠቃለን ስንመለከተዉ ኳሷ ያለችዉ የትግራይ ወንድሞቻችንን ክልል ስለ ሆነ ወደ ወገናቸዉ ተጠግተዉ የሚጠበቅባቸዉን ግዴታ እንዲወጡ አሳስባለሁ ለራሳቸዉም ጥቅም ሲባል። ከላይ እንደገለጽኩት የህጻናት ትምህርት ቤት በቦምብ ያጋየ ለትግራይ ህዝብ ወደፊት ወዳጂ ይሆናል የሚል እምነት ስለሌለኝ ከህዋአት ዉጭ ማሰብ እንዲችሉ በድጋሚ አሳስባለሁ።
እስከዛዉ በቸር ይግጠመን ሰመረ አለሙ ነኝ ከባህር ማዶ መልካም የፈረንጂ ገና
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር

ሴቶች ጥሩ ነገር አላቸው ጊዜ እሲኪሰጣቸው ድረስ ጠብቀው ይይዙት ዘንድ እለምናቸዋለሁ።

$
0
0

ሥርጉተ ሥላሴ 21.12.2013

በሴቶች ስሜት ውስጥ መሆንና በስሜቱ ውስጥ ሴቶችን ሆኖ ማሰብ ከባድ ነው።

sreate1እኔን ተብድሬው አላውቅም። እኔንም ተውሼው አላውቅም። እኔንም ሸቅጬው አላውቅም። እኔንም መስዬው ሳልሆን ሆኘው ስለምጽፈው በስሜቴ ውስጥ ያሉ ነገሮች ሁሉ በአብዛኞቹ ሴት እህቶቼ ስሜት ውስጥ እንደሚኖር አስባለሁ። የድምፄ ምት ከማህጸኔ ይነሳል። የመንፈሴ ትንፋሽ ደግሞ የልቤን ክናድ ይንተራሳል። መንፈሴ ሰግሮ ሁነኛ ማረፊያ ወይንም ድልዳል ሲያጣ ትካዜ ሲዋኝበት የኖረ ቢሆንም፤ አሁን ከዘሃበሻ ጋር መታደሙ የመገለው ስቃይ ተግ ብሎለት ህምሙም ታግሶ፤ በስክነትና በቅደም ተከተል ማሰብና ከረመጥ ላይ የበቀለውን ጸጋ ማቆለማመጥ ጀመርኩኝ። ስለሆነም እኔ ራህብ ላይ ሆኜ ሌላ ራህብተኛ ለማስናገድ አቅሜን በሙሉ ቀን መርቆ የሰጠኝ አምላኬ፤ ምክንያት ፈጥሮ የመተንፈሻ ቀዳዳ ለፈቀደለኝ የዘሃበሻ ድህረ ገጽ ምስጋናዬን በሐሴት ጠልፌ ተቀበሉኝ በማለት እነሆ ጀመርኩኝ …

ሴቶች የመኖር ቋንቋ ናቸው። የኑሮ አይደለም። ኑሮ ቅርንጫፍ መኖር ግንድ። ውድ ወገኖቼ አጠቃላይ የነፃነት ትግሉን የአቅም ግንባታ፣ ጥበቃ፣ ያለውን ሃብት በቋሚነት ማዝለቅ እንዲሁም ስምሪት በተመለከተ ያላችሁበት በመሆኑ እሱን ተወት አድርጌ በዚህ ዙሪያ አንስት እህቶቻችሁ ያላቸውን ልዩ መክሊት አትኩሮት ብትሰጡት ሁሉም አካባቢ ያሉ ክፍተቶችን እንዴት ሊያበጅና ሊያሳምርም እንደሚችል በአላቸው  ዙሪያ  ትንሽ ነገር ለማለት ፈለግሁ። 

 

ሀ.       ሴቶች ችግርን ለመፍታት ቁርጠኝነት ጠረናቸው ነው።

 

የሴቶች ተፈጥሮ መግለጫ ከሆኑት መሰረታዊ ጉዳዮች እንብርቱ ሴቶች ችግርን የማይፈሩ ደፋሮች መሆናቸው ብቻ ሳይሆን ችግሩን ለመፍታት ቁርጠኝነትን በአጽህኖት የተካኑ ከመሆናቸው ላይ ነው። እንዲያውም ሴቶች ወስነው ችግር ወደ አለበት ፈጥነው የሚገሰግሱ መሆናቸው የተፈጥሯቸውን ብቃት ያመሳክራል። ስለዚህ ሴቶች ማናቸውንም ችግር ከቤት እስከ አደባባይ ያለውን ሁሉ አሳር ዳፍረው ከመፍቻው ቁልፍ ጋር መፍትሄ የሚያስገኙ ድንቆች ናቸው። የፈለገ ዓይነት፣ በፈለገ ሁኔታ፣ በፈገ መጠን፣ በፈለገ ጊዜ፣ በፈለገ ግንኙነት፣ በፈለገ ልኬታ፣ ችግር በቅሎ ይጠብቃቸው አብዛኞቹ እንደ አመጣጡ መክተው፣ መንገዱን ጠርገው ለጥ ያለ አስፓልት በማድረግ፤ ወጣ ገቡን የሚታድጉ የመፍትሄ ማሃንዲሶች ናቸው። አቅርቧቸውና ፈትኗቸው ወኔው ካላችሁ ….

 

ለዚህ ማገናዘቢያ ይሆን ዘንድ …. እኔ በተመስጦ የኩርድሽ ሴቶች የጫካ ትግል እከታተላለሁ። ወንዶች ከተማ ሆነው የሎቢ ተግባር ይሰራሉ፤ ሴቶች ጫካ ሆነው የጀግንነት ግሩም ድርጊት ይከውናሉ። ጦር አዛዧ ሴት፤ የግንኙነት ኃላፊዋ ሴት፤ የሎጅስቲክስ ስምሪት አስተዳዳሪዋ ሴት፣ የጓድ መሪዋ ሴት፣ አዝማች ሴት … ወዘተ  ከትንግርት በላይ ነው። ጥንካሬያቸው፣ ብርታታቸው፣ ትብብራቸው፣ ጽናታቸው፣ የጫካ ህይወት ፍቅራቸው ንዑድ ነው። አምላኬን የምለምነው እንዲህ እንደ ጨው ዘር የተበተነውን ለእነሱ ቅንነት ሲል እንኳን በጉልበተኞች የተወሰደባቸውን መሬት አግኘተው ለሀገራቸው እንዲበቁ ነው። የአርበኝነት ውሏቸው ሰው መሆንን ይመረምራልና። ዓላማችውን አሳክቶ፤ አርበኛነታቸውን ለፍሬ አብቅቶ መሬት አልባነት ትሞ እማዊ የተግባር ሰውነት ምን ያህል ፍሬ ስለመሆኑ በ21ኛው ምዕተ – ዓመት በዓለም ዓቀፍ ዕውቅናውን እንዲያስጌጥ የዘወትር ፀሎቴ ነው።

 

ለ.       ሴቶች ስልት ተፈጥሯቸው ነው።

 

የሴቶች የአያያዝ ጥበብ በስልት ነው። ስልቱ ደግሞ ሩቅ ዓላማን ሰንቆ የቅርብ ፍላጎትን ሳይዘል አስማምቶ፣ አስመችቶም የመከወን ጠንካራ አቅም አላቸው። አሁን የቅርብ ምሳሌ ባነሳ በሳውዲ ላይ የተፈጠረው ችግር ጊዜያዊ መፍትሄ ለመስጠት መረባረቡን ሴቶች ከልብ ያምኑበታል። ነገር ግን ይህ የመከራ ዘመን የሚመክንበት ጉዳይ ላይ በርትቶ መስራትን ያሰምሩበታል። ለዚህም ዕድሉ ቢኖራቸው ቅደም ተከተል ሰጥተው የአቅም ክፍፍሉን አሳምረው ይቀይሱታል እንጂ ሳቢያዎች በሚፈጥሩት ውጤቶች ላይ ብቻ ጊዜያቸው እንዲላ አይፈቅዱም። በፍጹም። ነገም ሌላ ችግር በባሰ እንደሚበቅል ጠንቅቀው ያውቁታል። ስለሆነም አትኩሮታቸው በሳቢያ ላይ የሚያጠነጥን ብቻ ሳይሆን ይልቁንም በምክንያት ውጤቶች ላይ የተሳላ ነው። ተግባባን?

የችግሩ መፈልፈያ ከምንጩ መድረቅ አለበት። መነቀል አለበት – የሥራዓት መሰረታዊ ለውጥ ላይ አብዝቶ ከተሰራበት አብዛኞቹ የዛሬ ችግሮቻችን በሂደት በራሱ ጊዜ ያስተካከለዋልን።

ሐ.      የሴቶች ቀድሞ የመተንበይ አቅም ዓይነታ ነው።

 

አንድ ጊዜ በ90ዎቹ አጋማሽ ውጭ ሀገር አንድ የሥራ ባልደረባዬ፤ አለቃችን ሳይኖር አለቃዬም ነበር ለነገሩ  አዛውንት ጋዜጠኛ ታዋቂ በድንገት ሞቶ ቀብሩ ላይ ነበርኩኝ። አስከሬኑ ተቃጥሎ በትንሽ ነገር መያዙን አላስተዋልኩትም ነበር። እኔ እምጠብቀው ሳጥን ስለነበረ ከአጠገቤ ላላው ባልደረባዬ የተግባር መምህሬም ነው፤ መቼ ነው አስከሬኑ የሚመጣው? ስል ጠዬኩት ሂደቱን አጫወተኝ። ባለቤቱ የውጭ ዜጋ እንደ ሆነች እንደ እምነቷ፣ ቦታም ገንዘብም ለመቆጠብ እሬሳው እንዲቃጠል መወሰኗን አብራርልኝ። ይህን አሰቃቂ  ትዕይንት ስሰማም፣ ሳይም የመጀመሪያ ቀኔ ስለነበር አካባቢው እራሱ ቀፈፈኝ። ከአጠገቤ ደግሞ አንዲት አበባ የመሰለች ውብ ሴት እጅግ አምርራ ታለቅሳላች። ወደ እሷ ዞር አልኩኝና ጠጋ ብዬ እንድትታገስ ነገርኳት። ከዛ ምን እንዳለችኝ ታውቃላችሁ“ለራሴ ነው የማለቅሰው“ እንዴት? ስል ጓጉቼ ጠዬኳት። ለዛውም ሰው ፈቅዶ ካልነገረኝ ስለምንም ነገር መጠዬቅ አልወድም።

 

… ብቻ ጠዬኳት „ እኔ ተሰደድኩ፤ የስደቱን ፈተና ስላልቻልኩት የውጭ ዜጋ አገባሁ፤ ወለድኩኝ። አዬሽ አይደል መመለሻ የለኝም፤ አስከሬኔም የሀገሬ አፈር አያገኝም – በሁለት ምክንያት። ቀድሜ ብሞት ባለቤቴ የሚያደርገው ይህንኑ ነው። እንደ ባህሉ ያቃጥለዋል። ልጆቼም በዚህ ውስጥ ስለሚያድጉ ያፀድቁለታል አለችኝ“ ምንም እንኳን ሁሉም ጋብቻ ላይ ይህ ባይደርስም ዛሬ ላይ ሆኜ የትናት ትንበያዋን፤ ያ ሁለቱ የተፈጥሮ መስኮቶቿ ተከፈተው ገድቡን ጥሶ ሙላቱን ይለቀው የነበረው ፍላሎት ዛሬ ላይ በምልሰት ስቃኘው ሚስጢሩ ተገለጠልኝ። ሴቶች ነገን የማየት አቅማቸው ብጡል* (ጥንካሬው የደመቀ ልዩ) ነውና። ይህን ዘመን በድርብ ስመዝነው ደግሞ አይደለም ውጪ ሀገር … ሀገር ውስጥም መሰሉ ሊፈጸም እንደሚችል ምልክቶች ይጠቋቁማሉ። አስፓልቶች የኢትዮጵያ መሬት አይመስሉም፤ የገጠር መንደሮችም እንዲሁ …. ተወራላች ሀገራችን …. ውርርሱ የመሬት ብቻ ሳይሆን የዕምነት አፈጻጸም የተጋደመ ባህልም … እንዳይሆን ስጋቴ ነው።

 

… በዛው የቀብር ሥርዓት ያቺ ፔርሙስ በምትመስል ሰፋ ባለች ጎድጓዳ ማህል እጅ ላይ ተቀምጣ የነበረችው አዬኋት። አፈሩ ጫረጫር ተባለላትና እንደ ሀገሬው ባህል ወጉ ደራሳት። መሬቷ አንድ ስንዝር ብትሆን ነው። ያን ዕለት ከጎኔ ላላው ለማከብረው የቅርብ አለቃዬ ጠጋ አልኩና እኔ ደግሞ „በሰው እጅ የሞተ ይመስለኛል አልኩት።“ በጣም ፍጥነት የተሞላበት ነገር ነበር የተመለከቱት። እሱም “እናንተ ሴቶች መቅደም ተፈጥሯችሁ ነው። አብረን በኖርንባቸው ወቅቶች የታወቀ ምንም ዓይነት በሽታ አልነበረውም። ሁልጊዜም የህክምና ቁጥጥር ያደርጋል። ባለቤቱን ስለሁኔታው ደውዬ ስጠይቃት በመረጋጋትና  በአሸናፊነት መንፈስ ነበር ያጫወተችኝ። አሁን አንቺ ይህን ስትይ ግን የተሰወረ ግን ልንድርስበት ያልቻልነው ነገር አለበት ብዬ አስባለሁ። ለዚህም ይሆናል ብቻዋን ወሰዳ እንዲቃጠል ካስደረገች በኋላ የቀብር ሥርዓት ላይ ብቻ እንድንገኝ የነገረችን“ አለኝ። ከዚህ ላይ እኔ ትንቢተኛ ነኝ ለማለት አይደለም። ሴቶች ደራሽ ችግሮችን በተለያዬ አቅጣጫ እንደሚያዩት ለማጠዬቅ እንጂ …

 

ወገኖቼ … ሴቶች ንደ ወረደ የሚያስተናግዱት ምንም ነገር የለም በፍጹም። ይበልቱታል። የበለቱትን ክፍል ሰጥተው ይደለድሉታል። የደለደሉትን ንክኪና ግንኙነት ያላቸውን ነገሮች ሁሉ ከአገናኙ በኋላ ይፈታትሹታል በዬ አቅጣጫው፣ በዬዞኑ። ፍተሻው ጠንከር ያለ የራ ፊድ ባክ ወይንም ምላሽ ይሰጣቸዋል። ያ ፊድ ባክ ወይንም ምላሽ ዕርገታቸውን ያሳካላቸዋል …. እህታችሁን፤ የትዳር አጋራችሁን፤ እናታችሁን ለናሙና ወስዳችሁ መመዘን ይቻል ይመስለኛል።

 

መ.      ሴቶች በተፈጥሯቸው የተደራጁ ናቸው።

 

በሙያዬ አደራጅም ስለነበርኩ ብዙ ሳልጓዝ ብዕሬ በተወሰነ ጉዳይ ላይ ብቻ እንድታጠነጥን እለምናታለሁ። የሴቶች የመደራጀት ሂደት ከዬት የሚጀምር ይመስላችኋል። ከማህል? ከጠርዝ? ከማዕዘን? ከቀኝ – ከግራ – ከፊት – ከበስተኋላ? የሴቶች መደራጀት የሚጀመርው ከመንፈሳቸው አስኳል ነው። እንቅስቃሴያቸው „ሀን“ ዘሎ „ለን“ አይጀምርም – በፍጹም። እራሳቸውን አደራጅተው ነው የሚኖሩት። የሴቶችን እንቅስቃሴ የሚመራው በተደራጀ፣ በተሰናዳና በተከወነ መንፈስ ነው። ስለዚህ ከመደራጀት የሚገኘው ዕሴት ሁሉ ተጠቃሚ ናቸው። በዓለም የመጀመሪያው የድርጅትን ዋጋ አውቆ ጥቅም ላይ የዋለ ፍጥረት ቢኖር ሴቶች ናቸው። በሴቶች ህይወት ውስጥ ምን ያልተዳረጀ ነገር አለና? ስለሆነም አቅማቸውን በሥርዓት መርተው ለአቀዱት ዓላማ ጥቅም ላይ በአግባቡ ያውሉታል /ኢንቤስት/ ያድረጉታል …. ኃይላቸው ብክነት የለበትም። የፍሬ ነገሩ ኩላሊት ያለው ተዚህ ላይ ነው። ኃይላቸው ጥግና መጠለያ ምንጊዜም አለው። አሁን በዚህ የነፃነት ትግል የሚባክነውን ገንዘብ? ጊዜ? የሰው ኃይል ቁጭ ብዬ ሳዬው የነፃነት ራህብተኛ ነንኝና እስላላሁ … እንደ እኔ ሚሊዮኖችም …. አቅም እኮ አድመጭ ያጣ ቅምጥ ሃብት ነው። ለነፃነት ትግሉ ግን ጆሮም የለም ጊዜም በኩርማን ተቆንጥጣ … ለዛው ከተገኘ … በጠብታ ….

 

ሠ.       የድምጽ እንቁጢ የሴቶች መክሊት።

 

ሰሞኑን አንድ ሁለት መጣጥፍ ላይ ስለ ድምጽ አንስቻለሁ። ተወቅሸበታለሁም። እሱን በደስታ አስተናግጄ … በሰለጠነው አለም እኮ ድምጽ የሚሰለጥኑበት ሙያ ነው። ድምጽ ከምንም ነገር በላይ ቀልብን የመግዛት ሙሉ አቅም አለው። አዎን እኔ ሥርጉተ የውብ ድምጽ ቃና ፍቀረኛ ነኝ። አውዳለሁም። ነፃነት መጋፋት ኃጢያትም ወንጀልም ነው። በነፃነት ሀገር ነፃነቴን ማንም እንዲነጥቀኝ አልፈቅድም። ስለሆነም ነው የታሰረውን እዬተጋልኩ ተስፋ ሳልቆርጥ በተገኘው አጋጣሚ የምተነፍሰው። የተሰበረ ሞተር ወይንም ኮሳሳ ወይንም የሩጫ ፍልሚያ የሚጋብዝ ፋታ ነሽ ወይንም የታፈነ …. ለታላቁ የነፃነት ጉዞ አልመኝለትም። ምን በወጣው ….? በራሱ የሚተማማን፤ እውነትን የተንተራሰ፤ ለህግ የበላይነት የቆረጠ ዓለምን የሚየስደምም ኢትዮጵያዊነትን የሚታደግ ባለ ግርማ ሞገስ ድምጽ ናፍቆቴ ነው … እንዲመራኝ።

አሁን ወደ ቀደመው ነገር እንደ አቨው ….ካለ ዓመት የማትመጣው ብሄራዊ አበባችን እንቁጣጣሽ። እንቁጢ ተናፋቂ ናት። እንቁጢ ተስፋ ድውለቷ ነው። እንቁጢ አዲስነት ቅልጥሟ ነው። እንቁጢ ፍቅር ብርንዷዋ ነው። ታጥቦ የፈጠራት፣ ተናፍቃ ትመጣላች ሳትጠገብ ደግሞ ሽው …. እሷን ባደረገኝ።

የሴቶች ድምጽም እንቁጢ ነው። ድምፃቸው በደመቀ – በለሰለሰ – በሰከነ  – ልዩ ቃና የጣፈጠ ነው። ደወሉ የመንፈስ ድህነት ነው። ምቱ … የተዘጋ ይከፍታል። የታመመ ይፈውሳል። ተስፋን ላጣ በገፍ ተስፋን ይቸራል። የደከመን ያበረታታል። የጎበጠን ያቃናል። መፍቻ ያጠን ያፍታታል። ምን የማይሆነው አለ? የሴቶች ድሪያማ ውብ የርህራሄ፣ የቸርነት፣ አበረታች ለስላሳ ቀለማም ቅላፄ ይጠጣል።  ይጎረሳል። ይዋራረዳል። ያግራል። ያፍለቀልቃል። ያጽናናልም …. ይብቃ አይደል ወራጅ አለ በሉኝ።

ለማንኛውም ይህ ሃብት ግን ከቁጥር የማይገባ … ከፋይዳ የተዘለለ፤ ከመርኃ – ግብር የተፋቀ የተረሳ ጸጋ ነው። ዘንቦ ተባርቆ የሚዲያ የራዲዮ ሆነ የቴሌቪዥን ሰራተኛ ካልተሆነ ምክንት አብዝቶ የሚጨፍርበት አንጡራ ሃብት። በዬትኛውም ቤታ የአሸናፊነት መንገዱ ሁሉንም አካባቢ ዳስሶ በታቀደና በተደራጀ ሁኔታ በመንቀሳቀስ ኢትዮጵያዊነትን መታደግ ሲቻል … ፀጋው ውሃ ሲሄድበት የከረመ አለት ሆኖ ኤሉሄ አሉሄ ይላል …. ሞገዳማ ተንቀሳቃሽ ድምጽ የአጥቂነት ትጥቅ፤ የአሳማኝነት በትረ ሞገድ ነበር ላወቀበት ግን እንዴት? የታነቀ እውነት ….

 

ረ.      እናትነት።

 

ይህ እንግዲህ ለተባዕት የተከለከለው መንገድ የራሳችን ብቸኛው አንጡራ ሃብት ነው። ተቀናቃኝን በራሱ ጊዜ የመከተ። በፌክም ከማስመሰል በስተቀር መሆን የማይቻልበት ለሴቶች ብቻ የሰማዩ ዳኛ መርቆ የሰጠን የጸጋዎች እጬጌ ነው።  እናትነት የድርብርብ ፍቅር ክታብ። እናትነት በልቡ ውስጥ ልብ። የእናትነት ነገር ሲነሳ ወላዊና አውንታዊ እድምታ ላይ እንደርሳለን። እናትነት ሚስትነት ነው። የጡት ባህረ መዝገብ ሲገለጥ እናትነትን ከነክብሩ ይመጣል። ፍቅር ይከተላል። እናትነትን ሚስጢር የሚለው ቃል ሊገልጸው የሚችለው አይመስለኝም። የተከደነ ታምር ወይንስ የገድላት ቅዱስ መጸሐፍ ልበለው። እናትነት አይደለም ለሰው ልጆች እንሰሳ ላይ እንኳን ሲታይ ታምሩን የሰው ልጅ በጥበቡ ሁሉ ያልደረሰብት መክሊት ነው። እናትንት በተን ግን ጠቅላል ያሉ ሰንደቃዊ ቃሎችን ወይንም ኃብታቱ …

አለሁነት …. መቅድምነት …ቤተሰባዊነት … ታማኝነት … ተሳታፊነት …ቅርብነት … እቅፍነት …ተከታታይነት … አራራቢነት … አቀናባሪነት …ቀጥተኝነት … ዕንባመነት …ማራኪነት … ቻይነት … መሪነት … ሃላፊነትን በፈቃድ መውሰድ … ርህርህና … ስብዕዊነት … ሚዛናዊነት … ፍቅር … ቅንነት … አዎንታዊነት … አርቆ አሳቢነት … መምህርነት … ማህበራዊነት … ታማኝነት … ግልጽነት … ቀጥተኛነት … አድናቂነት … አክባሪነት … ተንከባካቢነት …. ኪዳንነት …. ለችግር ቀድሞ ደራሽንት … አጉራሽነት … አጽናኝነት … እውነትነት … ፈጣንነት … ባለሙያነት …. መሪነት …  አስተዳዳሪነት … መስዋዕትነትን ፈቅዶና ቆርጦ ተቀባይነት … አደራጅነት … አስተባባሪነት … ተጠያቂነት … ለጋስነት … ቸርንት …. አድማጭነት … አዛኝነት … ፈቃደኝነት … ቀዳሚነት … ኑሮነት …. ሁለመናነት … የሁሉዬነት …. መሆንነት … ሎሌነት …። በጣም በእርግጠኝነት እናት ለልጇ፣ ለትዳሯ፣ ለወገኗ፣ ለኃላፊነቷ ሁሉ ሎሌ ናት።

እያንዳንዱ ሥነ ተፈጥሯዊ ገፀ ባህሪ ደግሞ የራሱ ጭብጥና አምክንዮ አለው። እንደ እራሱ የመኖር ነፃነትና ከሌሎች ጋርም በመፈቃቀድ የሚያስተሳስረው ወርቃዊ ሃዲድም አለው። ድንበርና ወሰንም። ይህ ተፈጥሯዊ የገነት ህይወት ያለው የጸጋ ጅረት የራሱም ሥነ ምግባር፣ የራሱ አርትና ጣዕም አለው። ዬራሱ ዜማና ቃና አለው። የራሱ ማንነትና መግለጫ አለው። የራሱ አናትና ልብ አለው። የራሱ ፋይዳና ዕሴት አለው … የራሱ መተዳደሪያ ደንብና ሰነድም አለው። ይህ ሁሉ ተዝቆ የማያልቅ ጥሪትና እምቅ ቋሚ ሃብት ተዘሎ ይታቀደላል ሁል ጊዜ ግን ታቱ ዥግራ …

 

ሰ.      ሴቶች ብልህነት ወስጣቸው ነው።

የሴቶች ጸጋ ልጥፍ አይደለም። ከውስጣቸው በመሆን ያታተመ እንጂ። ሴቶች እጅግ ሲባዛ ብልሆች ናቸው።  በእያንዳንዱ የዓለም ታዋቂ ወንድ በሉት፤ ጀግና – ሳይንቲስት በሉት፤ ተመራማሪ በሉት፤ ተወዳጅ መሪ፤ በስተጀርባ አንዲት ብልህ ሴት በቅርበት አለች። አብዛኛውን ጊዜ የትዳር አጋራቸውን የሰሙ፤ ያዳመጡ፤ የተከበሩ መሪዎች ሆኑ፤ ለሽልማት የሚበቁ የስኬት ቁልፋቸው በእጃቸው መኖሩን ይቀበሉና ያረጋጋጡ ። እርማጃቸውን አንድ ብለው ከመጀመራቸው በፊት። የሁሉም ነገር መፍቻ ስልትና ብልሃት የመዳፋቸው እርስና እርት ሆኗልና እንኳንም ደስ አላቸው። የንጉሦች ንጉሥ የአፄ ቴውድሮስ ጠቅላላ ታሪክ በዛ መልክ የተጠናቀቀው እቴጌ ምንትዋብ በሞት ስለተለዮዋቸው ብቻ ነበር እንጅ እቴጌ በህይወት እያሉማ ድል በድል እዬተነባባረ የአሸነፊነትም የመሪነቱ እርክን አንቱ ነበር። እስከ እስራኤል ድረሰም ነበር ምኞታቸው።

እቴጌ ጋር የዐጤው መንፈሳቸው በድል ሰረገላ ላይ ያሸበሽብ ነበር። እቴጌ ለንጉሡ መዳህኒት ነበሩ ….  በብልህነት ሴቶች ተዝቆ የማያልቅ ፍጹም ልዩ ሥጦታ ነው ያላቸው። ደግሞም ስልታቸውን ተክትሎ ለሚጓዝ ህልሙ ቅርብ ነው። ድሉም ከፊት ለፊቱ ….

እስቲ ጠይቁልኝ እርቃ ሳትሄድ

እቴጌ ተዋበች ሚስትናት ገረድ

እጅግ „ሥራ አዋቂ“ ትናንትና ሞተች

መዳህኒቱን „ምሳ“ ታበላኝ ነበረች።

/ምዕራፍ 19 ከዐፄ ቴውድሮስ እስከ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ተክለ ጻድቅ መኩሪያ መጸሐፍ የተወሰደ።/  እጅግ „ሥራ አዋቂ“ ይህ ኃይለ ቃል የሴቶች ሥነ – ተፍጥሮ ተግባር ስለመሆኑ ብቻ ሳይሆን ዕውቀታዊ – አንስታዊ ውስጥንም አሳምሮ ይገልጠዋል። ሴቶች ለቧልት ጊዜ የላቸውምና። ሁለተኛው „ምሳ“ ታበለኛለች የሚለው ሰምና ወርቅ ነው። ሰሙ የማዕከላዊ የምግብ ክፈለ ጊዜን ማዕደኝነት ሲገልጽ፤ ወርቁ ሁለት ጥንድ ትርጉምን ይዟል። አንደኛው ቀደም ባለው ጊዜም ሆነ አሁን በገጠሩ ሀገረ-ሰብዕዊ መዳህኒቶች ከተክል ሥር ወይንም ከዕፅ ተቆፍሮ የሚገኝ ስለመሆኑ፤ ዶሱ ወይንም መጠኑ በጣት ተለክቶ እንደ ዕድሜው መሰጠቱን ይገልፃል። ስለዚህ ዐፄ ቴወድሮስ ህምም ሲሰማቸው ፈርማሲያቸው፣ ሃኪማቸው ከቤታቸው ነበሩ – እመቤት እቴጌ ምንትዋብ። ሌላው የወርቁ መጠነ ሰፊ ክፍለ አካል በዘመናችን ቁብ ያልተሰጠው ፍሬ ዘር ወይንም ነገረ ሚስጢር ግን ዐፄ ቴውድሮስ በንግሥና ዘመናቸውም ሆነ ሃሳባቸውን ሲወጥኑት ከልጅ ካሳነት ዘመናቸው ጀምሮ አስተዳደራዊ ብቃታቸው  ከእቴጌ ይቀዳ እንደነበር ለማጠዬቅ ነው።

በሌላ በኩል የአልጋቸው ጽኑ ጠባቂ የፕሮቶኮል ሹማቸው አማካሪያቸው እቴጌ መሆናቸውን ያመሳጥርልናል። ከዚህ ላይ የጉዳዩን ኩላሊት ከልብ ስንፈታትሽው ደግሞ ቀደምት ንጉሦቻችን የሴቶችን ተፈጥራዊ ልክ የማይወጣለት ብቃት ለመዳህኒትነት፣ ለችግር መፍቻነት፤ ለጭንቅ መበተኛነት፣ በአግባቡ ጥቅም ላይ ያዋሉና በዚህም ፈውስና ድህነት ማግኘታቸውን ቁልጭ አድርጉ ያስተምረናል ….

ከዚህ ጋር በተያያዘ የደህንነት እና የልጅነት ሚስጢርን በእናትነት ፀጋ ጎልምሶ የምናዬው ክፍል ደግሞ እቴጌ ሲሞቱ  …. የነበረውን አብረን እንመልከት።

እቴጌ ለባለቤታቸው አድልተው ወደ ትዳራቸው ፍላጎታቸው ቢመዝንም፤ እንደ ቤተሰባዊ ጸጋቸው በሴት ልጅነታቸውም አባታቸው በነበሩበት የግዞት ዘመን ሁሉ ከጎናቸው ነበሩ፤ ትዳራቸውን ሳያስከፉ በጥንቃቄ የልጅነት ድርሻቸውን በስውር ተወጥተዋል። ሊደረግላቸው የሚገባውን ተግባር ሁሉ አድርገዋል። እጥፍ ጸጋ። ሴት ልጅና ወንድ ልጅ ለወላጆቹ እኩል ተግባር ላይ አይገኙም። በቤተሰብ አያያዝና ክህሎትም ቢሆን  እኩል የመሆን አቅም የላቸውም - ፈጽሞ ። ለዚህ ነበር ራስ ዐሊ ልጃቸውን ሞት ሲነጥቅባቸው …. እንዲህ ብለው ቅኔውን የዘረፉት …. የጎደለ ሞይነት – ሁለመናነት … ሁሉዬ ሴት!

 

ጠጅ አማረኝ ስላት ማሩን ትሰዳለች (ለተጠማ ሆነ ለአምሮት ደራሽነት)

ራበኝም ስላት እኽሉን ታስጭናለች (ለራህብ ፈጥኖ ደራሽነት)

በረደኝም ስላት ሸማ ትሰዳለች      (ለታረዘ አልባሽነት)

ሌባዬ ተይዛ ባልጋ ትሄዳለች        (የድህንነት ጥበቅ ተግባር በስውርና በጥበብ)

የት አባቷን ዐውቃ ታሳዝነኛለች    (ችግርን ተጋሪ ሲርቅ ረመጥ ስለመሆኑ)

የጣቴን ቀለበት አንተ አድርገው ካሳ (ኪዳንህን ጠብቅ አደራ፤ ጽና!)

በኔማ ጣት ገብቶ አስጨነቀኝሳ (የሃዘኑ ቋያ ረመጥ ልኬታ አለመኖሩን) ያመላክተናል

( ከዐፄ ቴወድሮስ እስከ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ከተክለ ጻድቅ መኩሪያ መጽሐፍ ገጽ 20) የተወሰደ

ሴት ልጅ – እናት፤ እህት – ጓደኛ – አክስት –  ስትሆን ሚስጢሩ ሆነ ትርጉሙ ጣና ዘገሊላ ነው ….. ዛሬስ አቶ ወንዶች ይህን የማመሳጥር አቅም አላችሁን?

 

ሸ.      ሴቶች የተረጋጋ መንፈስ።

 

ይህ የሴቶች ተፈጥሮ ተግባር ላይ የሚውለው በትዳራቸው፤ በእናትና ልጅ ዙሪያ ወይንም በስብዕዊነት ዙሪያ አይደለም። ስለምን? በዚህ ዙሪያ ለሚመጡ ሰቀቀኖች ሴቶች ስሜታቸው ስስ ነውና። ነገር ግን ኃላፊነትን በሚጠይቁ የመወሰንን የመቁረጥ ሂደቶች፤ ሂደቶችን ተከትለው በሚመጡ አጣብቂኝ ፈተናዎች ዙሪያ ሴቶች የሰከነና መሬት ያዬዘ የተረጋጋ መንፈስ አላቸው። በመጀመሪያ ነገር ጉዞውን ሲጀምሩትም በአመዛኙ ይመጣል ብለው ካላሙት ችግር ውስጥ ያፈነገጠ አይሆንም። ስለሆነም በታቀደ እንቅስቃሴ ውስጥ የተጠበቀን ፈተና ለማስተናገድ ሴቶች ተረጋጋግተው የማስተናገድ ሆነ የመራመድ አቅማቸው ማገርፒላር ነው። በተፈጥሮ ሊቅነት። … ሥጦታው በትምህርት በተመክሮ ሲታክልበት እንዲሁም የተከበረ ተደማጭነት ሲያገኙ … መስፈርቱን ሆነ ዕሴቱን ለመለካት አይችልም … ዝልቅ ነዋ!

 

ቀ.      ማስተዋል ሴቶችን ይገልጣቸዋል።

 

ሴቶች አጋጣሚዎች የሚመራቸው ፍጥረቶች አይደሉም። ወይንም ሴቶች አጋጣሚን ተጠልለው አያቅዱም። መርኃ ግብራቸው እራሱን የቻለ እና ግብታዊነት የማይመራው በመሆኑ አትኩሮታቸው በጭብጡ ማዕክላዊ ዙሪያ ስለሚሆን ለግቦች ቅርብት ሆነ ለውጤቶች አስተማማኝ ግብዕት ናቸው። የሴቶች የፍላጎት ትልም ለወጀብ ሆነ ለአውሎ የተጋለጠ አይደለም  … እሳተ ጎመራን የመቋቋም ብቃቱ መካች ነው።

 

በ.      የሴቶች ነፃነት ናፈቂነት፤

 

ይህ የሴቶች በኽረ ህልም ነው። ምክንያቱም ውስጣቸውን ጠንቅቀው ስለሚያውቁት ድርሻቸውን ለመወጣት ተድቦልቡሎ ግን ተስውሮ የሚፈታታናቸውን የትምክህት ቲወሪ የሚመክት ነፃነት ይሻሉ። ለዚህ ነፃነትም ትርጉም ያለው፣ ድርጊተኝነትን በማስቀድም በግንባር ቀደምትነት ይጋፈጣሉ። እርግጥ ዘመንና ጊዜ የሚጠበቁ ነገሮች እንዳሉ ቢገነዘቡም፤ አጋጣሚዎችን ሳይዘሉ የምልክት ደወል መደወላቸውን ግን አያቋርጡም። ከናፍቆታቸው ጋርም ለመገናኘት ተግባር እንደሚያሸንፍ ስለሚያምኑ ድምጻቸውን አጠፍተው ከድርጊት ጋር ይባትላሉ – ይመስናሉ … በታሪክ ጊዜ የሌላቸው ቢዚ ፍጥረቶች ቢኖሩ ሴቶች ናቸው። በሁሉም ቦታ በተጫነ ጉልበታም ትምክህት ሥር ወድቀው፤ ግን ተሳትፏቸውን በትጋት ይወጣሉ። ፈተናው ሲጠናባቸው ሲስፈልግዞር ወይንም ለቀቀ አድርገው ግን ቀዳዳ ፈልገው ይተጋሉ። እንግሊዘኛው ስለሚገልጽልኝ ሙሉ ፓኬታቸው ትንታግ ነው – ። ለዚህም ነው ዕርሴ መጠበቅን ጽላቱ በማድርግ ሴቶች ጥሩ ነገር አላቸው ጊዜ እሲኪሰጣቸው ድረስ ጠብቀው ይይዙት ዘንድ  እለምናቸዋለሁ ያልኩት።

 

ጠቅለል ይበል …

 

የተፈጥሮ ውብ ዘላቂ ጥሎሽ የሴቶች ብቃት ነው። ዝም ብዬ ቁጭ እልና ሴቶችን ፊት ለፊቴ አስቀምጬ ሁለመናቸውን እፈትሸዋለሁ። እንደ ሰርጀሪ ነገር …  ሁለመናቸውን አስተውለዋለሁ። እያንዳንዱን ቅመማዊ ተፈጥሮ እዬነጠልኩም አናግረዋለሁ። ሁለመናቸውን እዬተነተንኩም እመካበታለሁ። ሁለመናቸውን እያፍታታሁ እጽናናባቸዋለሁ። ሁለማናቸውን እያስተዋልኩ አደንቃቸዋለሁ። ሁለመናቸው እዬዳሰስኩ እበረታታባቸዋለሁ – እውዳቸዋለሁም። ሁለማናቸውን በዓይኔ ወስጥ አስቀምጬ መንፈሴ እንዲደለው ፈቅጄ ነገን አልመበታለሁ። ቀደም ባለው ጊዜ „ እረኛ ምን አለ“ ይባል ነበር። አሁን ሰሞኑን የኢትዮጵያዊነት ስሜትን ፍላጎትን ሳወጣና ሳወርድ ከአንድ ጥቅል ፍላጎት ላይ ደረስኩ“ጣይቱ“ የሚለው አዲሱ  የአንስት ወላዊ፣ ትንቢታዊ፣ ፍላጎታዊ፣ ፈቃዳዊ፣ ጠያቂያዊ … ዜማ … እርገቱ በታዳጊ ወጣት የተስፋ ጠቅላይ ሚ/ር ቃለ ምልስልስ ሲጠናቀቅ ጨዋው ህዝባችን፤ ፈረኃ እግዚአብሄር ያለው ህዝባችን፤ ለእምነቱ ዶግማና ቅኖና ሞቱን የሚመርጠው ህዝባችን አንድ ነገር መንፈስ ቅዱስ እንደ አቀበለው ልብ አልኩኝ …. እንኩይ ….. የናፈቀው የሰከነ ፖለቲካዊ አመራር ከአንስት ነውና …

 

ከዚህ ጋር በተያያዘ ደግሞ መራኂት አርቲስት አለምጸኃይ ወዳጆ „የጣይቱን የሥነ – ጥበብ ማዕከል“ አሜሪካን ላይ አደራጅታ ጥበብን ተጠዬቅ ስትል፤ ቀድሞ የታያት ወርቅ እንደነባራትም ተገለጠልኝ። …. እሷም እኮ አለች … የጀመሪያው የተውኔት ባላሙያዎች ማህበር ብሄራዊ ሊቀመንበር … አስታዋሽ አርቲስት ታማኝ ባጠገቧ በመኖሩ ምክንያትም ቢሆን ኢሳት ይመስገን ተዚህ ላይ። … በሶስተኛ ጉባዔው ላይ ገላጭ አድርጓት አይቻለሁ፤ ግን ይህ በቂ አይደለም … ማስታወሱ መልካም ሆኖ ግን ሩቅ መጓዝ፤ ትብትቡን ፈቶ ቅኔዊ ውስጧን በቋሚነት ጥቅም ላይ መዋል ይገባል … ስብሰባ እኔ የምተረጉመው ገብያ በማለት ነው።

 

እናቴ ስትነግረኝ በልጅነቷ ጓደኛ ታበዛ ነበርና መሞታቸውን አውቀው፣ ሰኔልና ቹቻ አዘጋጅተው፣ ልጆቻቸውን መርቀውና ተሰነባተው ጸሎት ቤታቸው በሰላም ያረፉት ሊቀ – ሊቃውንቱ አያቷ መላክ ብርኃን ልሳንወርቅ ኃይለ ሥላሴ ቤተሰብ „ገብያነሽ“ ያላትን ስም አስቀሩት። ስለምን ገብያ ተሎ ይፈታል። ልጄ ዕድሜዋ ተግባሯም አጭር ይሆናል በማለት ሌላ ድንቅ ስም አወጡላት። አሁንም ሰው ወዳጅ ስለሆነች ተከባ ተከብራም አለች በባዕቷ። ምን ለማለት ነው እጅግ የፍቅሯን ንጥር ቅቤ ጠጥቶ ባደገው የልቤ ሙዳይ ውስጥ ብቸኛ ቦታ የሰጣት መራኂት ዓለምጸኃይ ወዳጆ … ቶሎ ለሚፈታ ጉባዔ ብቻ አትታጭ ዘለግ – ዘለቅትርጉም ላላው ተሳትፎ፤  አቅሙ ጉልበታም ለሆነ የኃላፊነት ቦታም ትታሰብ እንላለን … እንጮኃለን …. ተፈጥሮ እንዲያምርበት ማጣፈጫ አምላክ ፈጠረለት ሴትን

 

ሉሲ የ21ኛው ምዕተ ዓመት የሰው ልጅ ምንጭ ሆነች … ሳይንስም የኢትዮጵያዊነትን ሚስጥር ሳይነቅፍ ከሃቅ ጋር እርቀ ሰላም አወረደ። አመሳጠረ። ታዲያ ድንቅነሽ ማለት እኮ ሴት ናት … ተዚህ ማዕከል ይኮንና በኩነኔ ተፈርጆ ገሃንም የተወረወረው የሴቶች ብቃት ባሊህ ይባል እንላላን። የተከረቸመው በርም ይነቅነቅ እንላላን ///  እኔና የተከበረችው ብዕሬ – መንፈሴም ይታከል ….  ከዓውደ ምህረቱ ሆኖ  እንቢልታውን እያስነካ ውስጡን ላከ … ለጆሮ ….

 

ለነበረን የመደማማጥ ሸጋ ጊዜ ኢትዮጵያዊ ዘንካታ ምስጋና አቅርቤ ለዛሬ ልሰናበት። ቸር ያሰንብተን፤ ቸር ያሰማን አምላካችን አሜን።

 

ሴቶች የድርጊት ጀግኖች ናቸው!!!!!

የሴቶች ተሳትፎ በማለት የሰከረ ሳይሆን መሆንን የሰነቀ ነው!!!!

 

ይቅርታ በትህትና አክብሮትም ታክሎበት አንዳንድ ቦታ ላይ እንግሊዘኛውን ቃል ወስጃለሁ፤ ውስጤ አቅም አንሶት አይደለም ፍላጎቴን የበለጠ አስረግጦ የሚገልጸው እንግሊዘኛው ሲሆንብኝ ነበር … ትንሽ ዲቃላ ነገር የሆኑት ገለፃዎቼ …

 

እግዚአብሄር ይስጥልኝ።

 

ጥቁር ነኝ … ነገር ግን ውብ ነኝ

$
0
0

ሙሉጌታ አሻግሬ

mulugetaashagre@yahoo.com
ማህበር እየደገሰች ዘመድ የምትሰበስበዋ አክስቴ ‘አገር የጋራ ነው ሃይማኖት የግል ነው’ ትላለች። ይህን አባባል ለአክስቴ መስጠቴ አይደለም ሙስና እንዳይሆንብኝ። ህዝቡ ሁሉ እንደዛ ይላል። አክስቴ ምን ታድርግ መስመርና አብዮት የተባሉ ሰው ሰራሽ ጭራቆች ወንድሞቿን በልተውባታል። ይህ አባባል በፖለቲካ ምክንያት እሳት እና ጭድ የሆኑ ቀሪ ዘመዶቿ የተለመደውን ንትርክ እንዳይጀምሩ የምትጠቀምበት ዘዴ ነው። እኔ ግን ስተረጉመው ‘ዝምድና የጋራ ነው ፖለቲካ የግል ነው’ ማለቷ ነበር። በአክስቴ እምነት ፖለቲካ ጥሩ አይደለም። ሞት ያስከትላል።
ግን ሃይማኖትና ፖለቲካ እውነት ለየቅል ናቸው? ይህን አስተያየት ለመፃፍ ያነሳሳኝ ሰሞኑን አንድ ወዳጄ ጀባ ያለኝ የስብከት ሊንክ ነው።

ምንም እንኳን እንደአባባሉ ሃይማኖት የግል አገር የጋራ ቢሆንም የወያኔ ገዥ ቡድን አገርም የእነርሱ፤ ሃይማኖትም የእነርሱ እንደሆነ ህቅ እስኪለን ድረስ አሳይተውናል።
የእስለምና መሪዎች ሹመት በቀበሌ ምርጫ ካልሆነ ምኑን ሃይማኖት ሆነው ሊሉን ዳርዳር ያሉ የወያኔ ካድሬዎችን ታዝበናል። ማንን ፈርተው እንደተዉት ባይታወቅም ‘የመጅሊስ ተመራጮች ምርጫ ቦርድ መመዝገብ አለባቸው’ የሚል የደደቢት ቀጭን ትዕዛዝ ይተላለፋል ብዬም ጠብቄ ነበር። ኦርቶዶክሱንም ቢሆን ያልተመቻቸውን ሽረው፣ የተመቻቸውን ሾመው ፣ ኽረ ወግ እየተናደ ነው ብለው ቅሬታ ያሰሙ አባቶችን ደብድበውና አስደብድበው ሲኖዶሱ የእነሱን መስመር የሚከተል እንዲሆን ሰርተዋል። በአደባባይ በመውጣት ሚዲያ በመጠቀምም የኦርቶዶክስን አከርካሪ ሰብረናል ብለዋል። ስለዚህ ፖለቲካ ከእኛ በላይ ለአሳር ያሉት የወያኔ ገዥ ቡድን አባላት ይህን ካደረጉ እና ከተናገሩ፤ የእኔ የተራው ዜጋ ሁለት መስመር አስተያየት ሃይማኖት እና ፖለቲካን እንደማታቀላቅል እጅግ እርግጠኛ ነኝ።
ስብከቱ ከአንድ ሰዓት በላይ ነው። ትዕግስቴ አፍንጫዬ ላይ እንደሆነ የሚያውቀው ወዳጄ ግን አዳራ ጨርሰህ እንድትሰማው ብሎ መክሮኝ ነበር፤ አይገርምም አንዴ አይደለም ደግሜ ሰማሁት። በዚህ አስተያየት ውስጥ የሃይማኖት ክፍሉን ለሃይማኖቱ ተከታዮች በመተው ወቅታዊ የአገሪቱን ችግር የተመለከተውን ብቻ ለማሳየት እሞክራለሁ። የሰባኪውንም ማንነትም ሆነ የሃይማኖትን ጉዳዮች ሳልነካካ ማለት ነው። የወዳጄም ትልቁ ፍላጎት ይህ ነው።
ሰባኪው ይናገራል። በጥንቱ መፅሐፍ ቅዱስ እያጣቀሰ የኢትዮጵያን የዛሬ መከራ እና ችግር ይተረትረዋል። ወጣትነት፣ ስደት፣ ሙስና ፣ አድልዎ፣ ተጠያቂነት ምንም አልቀረውም። ሰባኪው የቤተክርስትያኗን አንደበት የሸበበውን በረዶ ሰብሮታል። ልክ ‘ICE Breaker’ እንደሚባለው ማለት ነው። ይህ መጀመሪያው ነው፤ አምናለሁ በርካቶች ሊከተሉ እንደሚችሉ እርግጠኛ ነኝ። አሸባሪ ተብሎ ክስ ካልተመዘዘበት በቀር። ግን ደጋግሞ ‘መናገር ካለብኝ እናገራለሁ፣ አልፈራም ’ ይላል ሰባኪው።
ወያኔ ድሮም በሃይማኖት ጣልቃ የመግባት ምስጢር መንግስተ ሰማያት አሊያም ጀነት የመግባት ፍላጎት አሳስቦት አይደለም። ወያኔ የኢትዮጵያን ህዝብ ያውቀዋል። ኢትዮጵያዊው በሃይማኖቱ ስነምግባርን ብቻ ሳይሆን መስዋዕትነትም የተማረ ህዝብ ነው። ስለዚህ ወያኔ ስልጣኑን ለማስጠበቅ ትላልቅ የሚባሉ ሃይማኖቶችን ወደራሱ መንገድ መጠምዘዝ ነበረበት። ህዝቡ የሃይማኖት አባቶችን ፣ የእምነት ተቋማቱን ያዳምጣል። ከልቡ። ስለዚህ ወያኔ በዚያ በኩል ሊመጣ የሚችለውን ‘የስልጣን አደጋ’ ለመከላከል የዘየደው ዘዴ የሃይማኖት ቁንጮዎችን ማወየን አሊያም መቆጣጠር ነበር።
እንደስብከቱ ግን ሃይማኖትን በአግባቡ ለማምለክ አገርና ማንነት ያስፈልጋል የሚል ግልጽ መልዕክት ተላልፏል። አትዝረፉ። ኽረ ሙስና ይብቃ።ተጠያቂነት ወዴት ነሽ? እያለ ሰባኪው ይጠይቃል። በቃ፣ በቃ፣ ይበቃል። ይላል ሰባኪው። ወያኔዎች በዚህ መልኩ ከተረዱት ትምህርት ይወስዳሉ። እራሳቸውንም ከጥፋት መልሰው ህዝቡን ማዳመጥ ይጀምራሉ። ይህን መልዕክት የትምክህተኞች እና ያለፈ ስርዓት ናፋቂዎች ነው ብለው የተለመደውን ነጠላ ዜማ ከለቀቁ ግን ከእግራቸው ስር ያለው መሬት እየተሰነጠቀ መሆኑን ለመረዳት እንደረፈደባቸው ያሳያል።
ህዝቡ በሃይማኖት በኩል ማጉረምረም ከጀመረ …. ኦሮማይ።
ጥቁር ነኝ … ነገር ግን ውብ ነኝ
ሰባኪው በክሊፑ ከ18፡00 እስከ 19፡15 ስደትን እየነገረን ለሚደርሰው ግፍ እና ኢሰብዓዊ ድርጊት ተጠያቂ የለም ይለናል። ከ 28፡33 እስከ 29፡35 ስለ ኢትዮጵያውያኖች ጀግኖች፤ ስላልተዘመረላቸው የኢትዮጵያ እንቁ ጀግኖች ይጠይቃል። ይናገራል። የእኛ ጀግኖች ብዙ እንደሰሩ ግን እንደተደበቁ ያስታውሰናል።
ከ42፡20 ጀምሮ ስለ ኢትዮጵያ ጥቁር ህዝብ ማንነት ይናገራል።የኦርቶዶክስን አከርካሪ መስበር ኢትዮጵያን ለመስበር መሞከር እንደሆነ በማስረጃ ይተነትናል። ቤተክርስቲያኗ ትምህርት ቤት፣ የህክምና ቤት፣ የፍርድ ቤት እንደነበረች ይነግረናል። አከርካሪዋ መሰበር ሳይሆን መመስገን ይገባታል ይለናል።
ከ46፡50 ጀምሮ ስለ ሞራል፣ ስለ አገር ተረካቢነት ይጠይቃል። ሙስና ከቤተመንግስት እስከ ቤተክህነት መንደሯን በስፋት እንደሰራች በግልጽ ይነግረናል። ህዝቡን እርስ በእርስ የማበላላት ፕሮግራም የኢትዮጵያን የወደፊት ማንነት ጥያቄ ውስጥ እንዳስገባ በመጠየቅ፤ መብላት እና መበላላት መወገድ አለበት ይላል። አጽንኦት በመስጠት።
ከ58፡30 ጀምሮ ሰባኪው ወደማንነታችን እንመለስ ይለናል። ወደ እውነት እንምጣ ይለናል።እምቢ፣ እምቢ እንበል ይለናል፤ ኢትዮጵያውያኖች ነንና። ኢትዮጵያውያኖች ነንና ነውር የሆነውን ትተን ወደክብራችን እንመለስ ይለናል።
ከ 1፡00፡50 ጀምሮ ስለነፃነት አባቶች ፣ ከባርነት ላወጡን አርበኞች ክብርና ምስጋናውን ያቀርባል።

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!!

የጥራት እና ደረጃ መዳቢ ባለስልጣን መ/ቤት እና ሕ.ወ.ሓ.ት (ልዩ ትንታኔ)

$
0
0

ጥራት እና ደረጃዎች
ነጻነት ይበልጣል (ከጀርመን)

tplfዛሬ ላስነብባችሁ ያሰብኩት  ቀደም ሲል የጥራት እና ደረጃዎች መዳቢ ባለስልጣን መስሪያ ቤት ተብሎ ይጠራ ስለነበረው  አሁን ለአራት ተከፋፍሎ እንዲጠፋ ስለተደረገ ተቋም ነው፡፡ መስሪያቤቱ ምርት እና አገልግሎችን  በመቆጣጠር የሸማቹን ደህንነት እና ጤንነነት ማስጠበቅ ፤ የገቢና ወጪ ምርቶችን  ጥራት በመከታተል ጉልህ ድርሻ እንዲያበረክት ታስቦ የተቋቋመ ነው፡፡ መስሪያቤቱን ለረጅም ዓመታት በበላይነት ይመሩ የነበሩት አቶ መሳይ ግርማ ሲባሉ በውስጡ የፍተሻ እና ካሊብሬሽን አገልግሎት ዳይሬክትሬት፣የሰርተፊኬሽ አገልግሎት ዳይሬክትሬት፣የኢንስፔክሽን አገልግሎት ዳይሬክትሬት፣የደረጃዎች ዝግጅት ዳይሬክትሬት፣ የስልጠናአገልግሎት  ዳይሬክትሬት እና የፋይናንስ ዳይሬክትሬት እና ሌሎች የአገልግጎች ዘርፎች ነበሩት፡፡አቶ መሳይ መስሪያቤቱን ከ16 ዓመት በላይ አስተዳድረዋል፡፡ ድንገት ባልተጠበቀ ሰዓት ከአቶ መሳይ እውቅና ውጭ 3 ሰዎች  አቶ ተክኤ ብርሀኔ ከመቀሌ፣አቶ ደቻሳ ጉሩሙ ከጅማ እና አቶ ዳንኤል ዘነበ ከሀረርጌ ተመልምለው  ወደ መስሪያቤቱ ተመደቡ፡፡

ሰዎች ሳይፈለጉ መመደባቸው ብቻ ሳይሆን በወቅቱ እንዲከፈላቸው የተፃፈላቸው የደመወዝ መጠንም በመስሪያቤቱ የደመወዝ ስኬል የሌለ፤ ካላቸው የትምህርት እና የስራ ልምድ ጋር ምንም አይነት ዝምድና ስለሌለው አቶ መሳይ መክፈል አልችልም በማለት አንገራገሩ፡፡ እነሱ መች የዋዛ ቢሆኑ እና እስከ ጠቅላይ ጽ/ቤት የተዘረጋ ሰንሰለት ስለነበራቸው በስልክ ተደውሎላቸው ሳይወዱ በግድ መክፈል ጀመሩ፡፡ እነዚህ ሰዎች በ2002 ዓ.ም ለሚካሄደው  ምርጫ ቅድመ ዝግጅት እንዲረዳ ከየክልሉ ተፈልገው የአብዮታዊ ዲሞክራሲ ሀዋርያ ሁነው ወደ ፌዴራል መንግስት የመጡ ናቸው፡፡ተክኤ በስፓርት ፣ደቻሳ በሂሳብ እና ዳንኤል በማኔጅሜንት ተመርቀዋል፡፡ ሲመጡ የሚያርፉበት የኪራይቤቶች የሚያስተዳድረው ሰፋፊ ግቢ የተዘጋጀላቸው ሲሆን ዳንኤል ከአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ጽ/ቤት አጠገብ፤ተክኤ እና ደቻሳ ደግሞ 22 አካባቢ ባለ ሰፋፊ ግቢ እንዲኖሩ ተመቻችቶላቸዋል፡፡

ዋናው  የቅርብ ጊዜ አላማቸውም በ2002 ለሚደረገው ምርጫ የመንግስት ሰራተኛውን ከኢህአዴግ ጎን ማሰለፍ እና ቀጣይ አመራሮችን ማዘጋጀት ነው፡፡ በዚህም መሰረት ባሉበት ቀበሌ በምርጫ ጣቢያ ሀላፊነት ተመድበው ይሰራሉ፡፡በተጨማሪም መንግስት በቢ.ፒ.አር.(business process re engineering) ብሎ ወደፊት ሊዘረጋ ላቀደው የሰራተኞች ማፈኛ መንገድ የራሱን  ታማኝ  የስለላ ሰዎች ወደ መሲሪያቤቱ ያስገባል፡፡ የአዲሶቹን ተመዳቢዎች አመጣጥ ተከተሎ በመስሪያ ቤቱ ከፍተኛ የፍረሃት  ድባብ ተፈጠረ፡፡እነሱ ሰራተኞችን ወደሚጭነው ሰርቪስ ሲገቡ አንድም ሰው ትንፍሽ አይልም፡፡የአውቶቡሱ ሰው ሁሉ በጸጥታ ይዋጣል፡፡ጆሮ ጆሮ እያሉ ያንሾካሽካሉ፡፡ በእረፍት ሰሀት እነሱ በተቀመጡበት አካባቢ አብሮ ተቀምጦ ሻይ ቡና የሚል የለም፡፡ሲመደቡ የኮሙኒኬሽን ሰራተኞች ተብለው ሲሆን ከመስሪያቤቱ እውቅና ውጭ ከነአቶበረከት ሰምኦን ጋር በየሳምንቱ ስብሰባ እና የመረጃ ልውውጥ ያደርጋሉ፡፡ከሳይንስና ቶክኖሎጂ ሚኒስትሩ አቶ ጁነዲን ሳዶ ጋር ከፈለጉ በአካል መኪና አዝዘው ካልፈለጉ በስልክ በቀጥታ መገናኘት ይችላሉ፡፡

አቶ መሳይ እና ሌሎች የመስሪያቤቱ ከፍተኛ አመራሮች የማያውቁት መረጃ ከነሱ ጋ ይገኛል፡፡በዚህ የአንድ አመት ቆያታቸው በመስሪቤቱ ደጋፊዎችን ማፍራት አልቻሉም፡፡

በ2003ዓ.ም የቢ.ፒ.አር ጥናት ሲጀመር አዲስ የመጡት ካድሬዎች  የጥናት ቡድን መሪ እየተባሉ ተመደቡ፡፡ ቢ.ፒ.አር ለመስራት ቀርቶ ስለመስሪቤቱ አሰራር በቂ እውቀት የሌላቸው ሰዎች መስሪያቤቱን አፍርሶ እንደ አዲስ የማደራጀት ስራ በእነዚህ ሰዎች ስር ወደቀ፡፡በዚህም ተቀራራቢ ስራዎችን በጋራ ማደራጀት በሚል ሰበብ ከብሄራዊ የጨረር መከላከያ አንዱን መምሪያ በማፍረስ፤የክሊነር ፐሮደክሽን መስሪያቤትን ሙሉ በሙሉ፤የሳይንስ መሳሪያዎች መስሪያቤትን ሙሉ በሙሉ አፈራርሰው አነዚህን መስሪያቤቶች ከደረጃ መዳቢ ባለስልጣን መስሪያቤት ጋር በማዋሀድ አራት የተለያዩ መስሪያቤቶችን ለመፍጠር ጥናቱ ተጀመረ፡፡ አዲስ የተጠኑት መስሪያቤቶች

1.Meterology institute,

2.Accreditation biro,

3 .Standards agency

4. Conformity assessment enterprise ይባላሉ፡፡

እነዚህ መስሪያቤቶች በተጠኑበት ወቅት ለጥናት ቡድኑ በየሳምንቱ በጣም ውድ በሆኑ ሆቴሎች የእራት ግብዣ  እየተዘጋጀ ለ6 ወር ያክል ተደከመበት፡፡ወደ መጨረሻው ምእራፍ ሲቃረብ  የጥናት ቡድኑ ሙሉ በሙሉ ናዝሬት ውስጥ ከ10 ቀን በላይ ሆቴል ውስጥ ተቀምጠው እንዲሰሩ ተደረገ፡፡በመጨረሻም የጥናቱን መጠናቀቅ አስመልክቶ  በአቶ ጁነዲን ሳዶ አማካነት አርባምንጭ ለሶስት ቀናት ድል ያለ ግብዣ ተደረገ፡፡ከአርባምንጭ መልስ ሁሉም በሳይንስ እና ቴክኔሎጂ ሚ/ር ስር የሚገኙ ሰራተኛ  ለገሀር በሚገኘው የመንገድ እና  ትራንስፖርት መሰብሰቢያ አዳራሽ ጠቅላላ ስብሰባ ተካሄደ፡፡በስብሰባው የየጥንት ቡድኑ ሀላፊዎች የጥናታቸውን ውጤት ይፋ አደረጉ፡፡የሀገራችን ችግሮች ተዳሰሱ፡፡ለችግሮች መፍትሄ ይሆናሉ የተባሉ አማራጮች ከየአቅጣጫው ጎረፉ፡፡

አብዛኞች ወጣቶች ተስፋ ያደረጉትን በየመስሪያቤቱ ያለውን ብልሹ አሰራር እንዴት ማስወገድ እንደሚቻል አስተያየታቸውን ሰጡ፡፡በዚህ ውይይት ከተነሱት ውስጥ እስካሁን የማሰታውሳቸው አቶ ገብረጊዳን ገብረመስቀል በቅጽል ስሙ(GG) “በየመስሪያቤቱ ያለውን የተማረ የሰው ሀይል  እጥረት ለመቅረፍ መንግስት በውጪ የሚኖሩት ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ገብተው እንዲሰሩ ቢደረግ መልካም ነው፡፡ለምሳሌ እንደ ኢንጅነር ቅጣው እጅጉ አይነት ሰዎች ነበሩዋት ሌሎችም እንዲህ አይነቶች ይኖራሉ ብሎ ተናገረ፡፡”በእረፍት የንግድ ሚኒስትሩ የአቶ ታደሰ ሐይሌ ባለቤት ወ/ሮ አልማዝ ካህሳይ ይህን የተናገረውን ልጅ ጠራቸው እና ስሙን ጠይቃ “አንተማ የእኛው ነህ እየውልህ ኢ/ር ቅጣው በመንግስታችን ላይ ሊሰራ አቅዶት የነበረውን ስለማታውቅ ነው እንዲህ ያልከው፡፡በቶሎ ቀጨው እንጂ ቢቆይ በጣም አደገኛ ነበር፡፡እንዲህ አይነቱን ሰው ስሙን መጥራት የለብህም” አለችው፡፡

ይቅርታ ወ/ሮ አልማዝ እኔ እሱን አላውቅም ነበር ሲል መለሰላት፡፡ሌላው ከጠቅላይ ሚ/ር ጽ/ቤት የመጣ  አቶ ጸጋዬ የሚባል አንድ ተናጋሪ በንግግራቸው መሀል ጣል ያደረጉዋት ቀልድ መሰል መልክት ሁሌም ትከነክነኛለች፡፡አቶ ጸጋዬ “አማርኛ እጅዋን አገኘች በግል ትምህርት ቤት ውስጥ አማርኛ መናገር እና ድንጋይ መወርወር ያስቀጣል ተብሎ በጉልህ ተጽፎ አንድ ትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ አንብቤያለሁ” ብለው አረፉ፡፡ ሌላው ጠያቂ አብዲ ዱጋ ይባላል፡፡አብዲ ጥያቄውን ያቀረበው ለሚኒስትር ጁነዲን ሳዶ ነው፡፡ጥያቄው “ኦሮሚያ ክልል ውስጥ አየተካሄደ ያለው የአበባ እርሻ ልማት የአካባቢውን አፈር እና ውሃ እየበከለው ነው፡፡በዚህም የተነሳ እንስሳት ይሞታሉ ሰዎች ይታመማሉ፡፡የሰራተኞችም ህይወት አደጋ  ውስጥ ነው  የሚከፈላቸውም ገንዘብ እዚህ ግባ የሚባል አደለም፡፡እንዲያውም  ባለ ሀብቶች ከሌሎች ሀገሮች ሲባረሩ ነው ወደዚህ ሀገር የመጡት ይባላል እና ይህን እንዴት ያዩታል? ሲል ጠየቀ፡፡አብዲን የገጠመው ከፍተኛ ውግዘት ነው፡፡ለውግዘቱ መነሻም በወቅቱ የአበባ እርሻ ልማት ሲጀመር አቶ ጁነዲን የኦሮሚያ ርእሰ መስተዳድር ስለነበሩ እሳቸውን እንደተቃወመ ተቆጠረ፡፡አብዲም ያጠናው ባዮሎጂ ስለነበር ሙያዊ ትንታኔ መስጠቱን ቀጠለ፡፡ክርክሩ እየከረረ ሲሄድ ጓደኞቹ ዝም እንዲል አደረጉት፡፡ስልጠናው ለ5 ቀናት በፍረሃት እንደተዋጠ ተጠናቀቀ፡፡ከዚህ ሰብሰባ መልስ በቀጥታ ሁሉም መስሪያቤት ወደ ሰው ኃይል ምደባ እንዲገባ መመሪያ ተላላፈ፡፡

Woyanes shoud face justice

ስብሰባው አርብ ተጠናቆ ሰኞ ጠዋት አቶ መሳይ ከመስሪያቤቱ በፍቃዳቸው እንዲለቁ  ትእዛዝ እንደተሰጣቸው  ለሚቀርቡዋቸው ሰዎች  ሲናገሩ የኮሚኒኬሽን ሰራተኞቹ እነ ተክኤ ደግሞ  ምደባውን እንዳያስተጉዋጉል በማሰብ አስቀድሞ መባረሩን በየቢሮው እየዞሩ ያውጃሉ፡ይህን ተከትሎ መስሪያቤቱ ሰው የሞተ ያክል በኡኡታ በልቅሶ ታመሰ፡፡አብዛኖች መልካም ተግባሩን ለሰራተኛ አዛኝነቱን እያሰቡ አባታቸውን በሞት የተነጠቁ ያክል ከልብ አዘኑ፡፡በዚሁ እለት የንግድ ሚኒስትሩ የአቶ ታደሰ ሀይሌ ባለቤት ወ/ሮ አልማዝ ካህሣዬ መስሪያቤቱን እንዲያስተዳድሩ ተሾሙ ፡፡የተለያዬ ዳይሬክተሮችን ሹመት ሰጡ፡፡በዚህ ወቅት ቀደም ሲል ወያኔን እንደሚቃወሙ የሚታወቁት እና ከአቶ መሳይ ጋር ቀረቤታ አላቸው የተባሉ ነባር ዳይሬክተሮች ተነስተው በምትካቸው የኢህአዲግ አባላትን መመደብ ተጀመረ፡፡ ምደባውም የሚካሄደው እያንዳንዱ ሰራተኛ እየተገመገመባለው ችሎታ ነው ይባል እንጅ ነገር ግን አስገራሚው እና ያን ያክል የተደከመበት ጥናት የግምገማውን 75% የሚይዘው  ከስራው ጋር ምንም ግንኙነት የሌለው አመለካካት የሚባል ነገር ነው፡፡ሰራተኞች በወቅቱ ያነሱት የነበረው ጥያቄ አመለካከት በምን ሊለካ ይችላል የእኔን አመለካካት ምን እንደሆነ ማን ያውቀዋል የሚል ነበር፡፡

ግምገማውን የሚሞሉት ቀደም ብየ የጠቀስኳቸው እነ ተክኤ፣ደቻሳ እና ዳናኤል ናቸው፡፡እነዚህ ሰዎች እንደመሰላቸው የግምገማ ነጥቡን መስጠታቸው ሳያንስ ምደባውን በዋናነት የሚመሩት እነሱ ናቸው፡፡ወደ ደረጃ መዳቢ መስሪያቤት የመጡትን የሌላ አዳዲስ  መስሪያቤት ሰራተኞች መልካቸውን ሳይቀር የማያውቁዋቸውን ሰዎች ግምገማ በድፍረት ይሞሉ ነበር፡፡በመሀል በተቃዋሚነት ያልተፈረጁትን እና አባል መሆን የሚፈልጉ ካሉ በምደባ እና በእድገት አያባበሉ ወደ ድርጅቱ የማግባባት ስራ ተከናወነ፡እኔ ስራየን እንጂ የፓርቲ አባል መሆን ፍላጎት የለኝም ያሉት ደግሞ ቀደም ሲል በተለያዩ የውጭ ሀገራት ሳይቀር ከፍተኛ ስልጠናዎችን ተከታትለው ስራቸውን በብቃት ሲወጡ የነበሩ በርካታ ባለሙያዎች አብዮታዊ ዲሞክራሲን ባለመቀበላቸው ብቻ  ዘራቸው እየታየ ከስራቸው ከተባረሩት መካከል ከዚህ  በታች የተዘረዘሩት ለማሳያ ያክል የቀረቡ ሲሆኑ አንድም የትግራይ ብሄር  ተወላጅ አለመባረሩን አንባቢያን ሊገነዘቡት ይገባል፡፡ሌላው እና አስገራሚው ነገር በወቅቱ  የኦሮሞ ብሄር ተወላጆችን እያገለለ እየተካሄደ ያለው ምደባ ያሳሰባቸው የኢህዴድ አባላት ጥያቄያቸውን ለሚኒስትር ጁነዲን ሳዶ ቢያቀርቡም ወ/ሮ አላማዝ ካህሳይ እያንዳንዱን ኦሮሞ እቢሮአቸው ጠርተው አርፈው እንዲቀመጡ አለዚያ እንደሚባረሩ በዛቻ ገልጸውላቸዋል፡፡በወቅቱም ከፍተኛ ተቃውሞ ያሰማው አቶ ሙሉጌታ መኮነን ያለስራ ለአንድ ዓመት ደመወዝ ብቻ እየተከፈለው ሊሰራ በማይችል ዘርፍ የቡድን መሪ ሁኖ ሲመደብ በስሩ ግን ምንም ሰው አልነበረም፡፡

ተ.ቁ            ስም     የነበራቸው ሀላፊነት

ብሄር

1 አቶ መሳይ ግርማ የጥራት እና ደረጃ መ/ቤት ዋና ዳይሬክተር

ኦሮሞ

2 አቶ ጋሻው ወርቅነህ የጥራት እና ደረጃ መ/ቤት ምክትል ዳይሬክተር

አማራ

3 አቶ ተፈራ ማሞ የኤሌክትሪክል ላብራቶር  ሃላፊ

ኦሮሞ

4 አቶ ሀይሉ የመሳሪያ ጥገኛ አገልግሎት ሃላፊ

ኦሮሞ

5 አቶ ደሬሳ ፉፋ የሰርተፊኬሽን አገልግሎት ዳይሬክተር

ኦሮሞ

6 አቶ መስፍን የስልጠና አገልግሎት ዳይሬክተር

አማራ

7 አቶ አዱኛው መስፍን የጥራት ማኔጅሜንት አሰልጣኝ

አማራ

8 አቶ እንዳ የኢንፎርሜሽን አገልግሎት ሀላፊ

አማራ

9 አቶ አመሃ በቀለ የጥራት ማኔጅሜነት አሰልጣኝ

አማራ

10 አቶ ሂርጳ የጥራት ማኔጅሜነት አሰልጣኝ

ኦሮሞ

11 አቶ መረሳ የሰርትፊኬሽን ኤክስፐርት

ኦሮሞ

12 አቶ ቴወድሮስ ዘካሪያስ የፍተሻ ላብራቶር ኤክስፐርት

አማራ

13 አቶ  ልኡል የባህርዳር ቅርንጫፍ  ሀላፊ

አማራ

14 የሰርትፊኬሽን ሲስተም ኦዲተር የነበሩት

ኦሮሞ

15 የድሬደዋ ቅርንጫፍ ሀላፊ የነበሩት አማራ
16 የናዝሬት ቅርንጫፍ ሀላፊ የነበሩት ኦሮሞ
17 የሀዋሳ  ቅርንጫፍ ሀላፊ የነበሩት ደቡብ

ታማኝ የህወአት አባላት  በባትሪ  ከሌላ ቦታ ተፈልገው ያለ ልምድ  እና ችሌታቸው  በከፍተኛ አመራርነት ሲመደቡ የተለሳለሰ አቋም ያላቸውን እና የአባልነት ጥያቄ ሲቀርብላቸው ጥያቄውን የተቀበሉ ነባር የመስሪያቤቱ ሰራተኞች የፍርፍሪው  ተቋዳሽ ሁነዋል፡፡በዚህ ምደባ እስከቡድን መሪ ያለው ሀላፊነት ያለ ፓርቲ አባልነት ወይም ያለ ትግራይ ተወላጅነት በምንም መልኩ ለተራው ሰራተኛ አይሰጥም፡፡

ተ.ቁ  ስም   ቀደም የነበራቸው ሀላፊነት አሁን የተሰጣቸው ሀላፊነት ብሄር
1 ወ/ሮ አልማዝ ካህሳየ የኢንስፔክሽን አገልግሎት ዳይሬክተር የደረዳዎች ዋና ዳይሬክተር ትግሬ
2 አቶ ወንዶሰን ፍስሃ የካሊብሬሽን አገልግሎት ሀላፊ  የሜትሮሎጂ ኢንስቲቲዩት ዋና ዳይሬክተር ትግሬ
3 አቶ አርአያ መከላከያ ኢንጅነሪንግ የአክረዲቴሽን ጽ/ቤት ዋና ዳይሬክተር ትግሬ
4 አቶ ጋሻው ተስፋዬ የፍተሻ ላብራቶር ኤክስፐርት የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ትግሬ
አቶ ገብሬ ኝግድ እና ኢንዱስትሪ ኤክስፐርት በደረጃዎች ኢጀንሲ ዳይሬክተር ትግሬ
6 አቶ ብርሀኑ ተካ ረዳ የፋይንነስ አስተዳደር ዳይሬክተር የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የፋይናንስ ዳይሬክተር ጉራጌ
7 ወ/ሮ ገነት ገ/መድህን የፍተሻ እና ካሊብሬሽን  አገልግሎት ዳይሬክተር የአክረዲቴሽን ጽ/ቤት ዳይሬክተር ትግሬ
8 ወ/ሮ ብርሀን ብሂል የአዋሳ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ጸሀፊ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የሰው ሀብት እስተዳደር ሀላፊ ትግሬ
9 አቶ ብርሀኑ ተካ የሰርቪስ ሹፌር የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የተራንስፖርት መምሪያ ሀላፊ ትግሬ
10 አቶ ተክኤ ብርሀኔ የኮሙኒክሽን ሰራተኛ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ትግሬ
11 አቶ ዳዊት  የሰርቪስ ሹፌር የሜትሮሎጂ ኢንስቲቲዩት የትራንትፖርትመምሪያ ሀላፊ ትግሬ
12 አቶ ጸጋዬ ኢንስፔክተር የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ሀላፊ ትግሬ
13 አቶ ዘነበ ኢንስፔክተር የገበያ ጥናት ሀላፊ ትግሬ

ቀደም ሲል እንደማናኛውም ኢትዮጵያ ውስጥ እንዳሉ የመንግስት መስሪያቤቶች የሚታዩ ችግሮች ቢኖሩም የተወሰደው እርምጃ ግን የወቅቱን የትግሬዎች የንግድ እንቅስቃሴ ያላንዳች ተቆጣጣሪ እንደፈለጉት ለማሽከርከር ታስቦ አንደሆነ ይታወቃል፡፡ለዚህም መነሻ የሚሆነው በተለያዩ ጊዜያት በቆርቆሮ፣በብረታብረት፣በማዳበሪያ፣በሳሙና፣በከብሪት፣በሲሚንቶ ፣በዘይት፤በጨርቃ ጨርቅ ፣ በባትሪ ድንጋይ፣በኤሌክትሪክ ገመዶች የመሳሰሉት ምርቶች ላይ ተደጋጋሚ ችግር ተከስቶ በበላይ አካል የስልክ ትእዛዝ ደረጃቸውን ያልጠበቁ ምርቶች ለህብረተሰቡ እንዲሰራጩ ተደርጉዋል፡፡ለአብነት ያክል የአቢሲኒያ ሲሚንቶ ፋብሪካ በጥራት ጉድለት ምክንያት እንዳያመርት አገዳ መስሪያቤቱ ሲያስተላልፍ በወቅቱ የከተማ ሚኒስትር የነበሩት ዶ/ር ካሱ ኢላላ  ፍተሻውን ያከናወኑ ባለሙያዎችን በግላቸው ቢሮ ድረስ በማስጠራት ትክክል አደላችሁም፤ልማታችንን እያደናቀፋችሁ ነው፤ኢንቬስተሮች ወደ ሀገራችን እየመጡ እንዳይሰሩ መሰናክል እየፈጠራችሁ ስለሆነ አቁሙ ሲባሉ የመስሪያቤቱ ሀላፊዎች እገዳውን ባስቸኩዋይ አንዲያነሱ ቀጭን ትእዛዝ አስተላለፈዋል፡፡መስሪያቤቱም እንዲፈርስ የተደረገው ባለሞያዎችም የተፈናቀሉት ሆን ተብሎ ያለ አግባብ  መሆኑን የኢትዮጵያ ህዝብ እንዲረዳው ያስፈልጋል፡፡

በስዊድን ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ላልተወሰነ ጊዜ ተዘጋ

$
0
0

ስዊዲን
(ዘ-ሐበሻ) “ባለፉት ወራት በቤተክርስቲያናችን ውስጥ ክርስቲያናዊ ያልሆኑ ሥነምግባራቶች በመከሰታቸውና ያለመግባባት በመፈጠሩ፤ ይህን ተከትሎ በማህበረ ምህመናኑ (አባቶች፣ እናቶች፣ ወንድሞች፣ እህቶችና ህፃናት ላይ ሊደርስ የሚችለውን አደጋ ግምት ውስጥ በማስገባት ከነገ ታህሳስ 13 ቀን 2013 (December 21,2013) ጀምሮ መንፈሳዊ አገልግሎቱን ለጊዜው እንድናቋርጥ ተገደናል” ይላል በስዊድን ስቶክሆልም ከተማ ውስጥ የሚገኘው የመንበረ ጸባዖት ቅድስ ሥላሴ ቤ/ክ ደጃፍ ላይ የተለጠፈው ማስታወቂያ።

የዘ-ሐበሻ የስዊድን ዘጋቢ ባስተላለፈው መረጃ መሠረት ቀድሞ ገለልተኛ ሆኖ የተመሠረተው ይህ ቤተክርስቲያን በአንዳንድ መዘምራን እና የማህበረቅዱሳን አባላት አማካኝነት በተነሳ ጥያቄ የዛሬ ሁለት ዓመት የአቡነ ጳውሎስ ስም በቅዳሴ ላይ እየተጠራ ግን በገለልተኛነቱ እንዲቆይ ተወስኖ አቡነ ጳውሎስ ካረፉ በኋላም የ6ኛው ፓትሪያሪክ አቡነ ማቲያስ ስም እየተጠራ በገለልተኛነት ቆይቶ ነበር። እንደ መረጃ ምንጫችን ገለጻ ከ2 ወራት በፊት እንደገና፤ በቤተክርስቲያኑ አንዳንድ መዘምራን እና የማህበረ ቅዱሳን አባላት ባነሱት ጥያቄ ቤተክርስቲያኑን ወደ ኢትዮጵያው ሲኖዶስ ስር ለማስገባት እንስቃሴ ተጀምሮ አሁን ያለው የቤተክርስቲያኑ ቦርድ በአዳዲስ ሰዎች እንዲተካ፣ የሰበካ ጉባኤውም አስተዳደር በአዲስ መልክ እንዲዋቀር፤ እንዲሁም ቤተክርስቲያኒቱ በካህናቱ እንድትመራ ጥያቄ አቅርበዋል።

በእንደዚህ ያለ ሁኔታ ውስጥ ያለው የስቶክሆልሙ መንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ቤ/ክ ከገለልተኛነት ወደ ኢትዮጵያው ሲኖዶስ ለማስገባት ውሳኔ እንዲሰጥ ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ባለበት በዚህ ወቅት ይህን ተከትሎም በቤተክርስቲያኒቱ ውስጥ ቦርዱ በመግለጫው ላይ እንዳለው ክርስቲያናዊ ያልሆኑ ሥነምግባራቶች መከሰትና ያለመግባባትም መፈጠር ጀምሯል።

የቤተክርስቲያኒቱ አስተዳደር ቦርድ እና ሰበካ ጉባኤው ይህን አለመግባባት ለማብረድ ቤተክርስቲያኑን ላልተወሰነ ጊዜ መዝጋቱን ያሳወቀ ሲሆን “ወደፊት ያለውን ሂደት ለማህበረ ምዕምናን እና ምዕመናቱ እናሳውቃለን” ብሏል።

በኮራ የሙዚቃ አዋርድ ሃገራችንን ያስጠራችው ድምፃዊት ሚካያ በኃይሉ አረፈች

$
0
0

mikaya (ዘ-ሐበሻ) “ሸማመተው” በሚለው የሙዚቃ አልበሟ ባሳየችው ብቃት በተለይም በቀጣይነት በኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃ ላይ ነብስ ሊዘሩበት ይችላሉ የሚል ግምት ከሚሰጣቸው አርቲስቶች ውስጥ ገብታ የነበረችው ድምፃዊት ሚካያ በኃይሉ በ37 ዓመቷ ከዚህ ዓለም ተለየች። የቀብር ሥነስርዓቷም ዛሬ በለብይ መካነ መቃብር መፈጸሙን ከአዲስ አበባ የመጡ መረጃዎች አመልክተዋል።

ላለፉት 3 ሳምንታት ያህል ለጊዜው ምንነቱ ባልተገለጸ ሕመም ስትሰቃይ እንደነበር የደረሰን መረጃ አመልክቶ ትናንት ማምሻውን ግን ህመሙ አላላውስ ሲላት ወደ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል በቤተሰቦቿ አማካኝነት ብትወሰድም ሕይወቷ ሊተርፍ እንዳልቻለ ተገልጿል።

አንድ ሙሉ የሙዚቃ አልበም እንዲሁም ነጠላ ዜማዎችን በመልቀቅ ታዋቂነትን ያተረፈችው ሚካያ ትምህርቷን የተከታተለቸው በቤተልሔም አንደኛ ደረጃ እና በአብዮት ቅርስ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ እንዲሁም የመጀመሪያ ዲግሪዋን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አግኝታ ሁለተኛዋን ዲግሪ ለመጨረስ ጥቂት በቀራት ሰዓት ሞት እንደቀደማት በሕይወት ታሪኳ ላይ ተቀምጧል።

ድምጻዊት ሚካያ በኃይሉ በአፍሪካ ኮራ የሙዚቃ አዋርድ ላይ ተሳትፋ፤ በተሳተፈችበት ምድብ በ2010 ዓ.ም ከምርጥ 20 ድምፃውያን መካከል አንዷ ሆና በመመረጥ እስከ ውድድሩ ግማሽ ፍጻሜ ድረስ ደርሳ እንደነበር ይታወሳል።

የአንዲት ሴት ልጅ እናት የሆነችው ድምጻዊት ሚካያ ወዳጅ ዘመዶቿ በተገኙበት ዛሬ በለቡ መካነ መቃብር፤ የቀብር ሥነ ስር ዓቷ ተፈጽሟል። ዘ-ሐበሻ በድምፃዊቷ ሞት የተሰማውን ሐዘን ትገልጻለች።


በአረና መጠናከር የሰጉት ህወሓቶች ‘ዕርቅ’ፈፀሙ

$
0
0

አብረሃ ደስታ ከመቀሌ

ህወሓቶች ለሁለት ተከፍሎው የደብረፅዮን (የአዲስ አበባ) ና የአባይ ወልዱ (የትግራይ) ቡድን ተሰይመው ሲነታረኩ መቆየታቸው ይታወቃል። ከወራት በፊት ጀምሮ ደግሞ ሁለቱም ቡድኖች ‘ለማስታረቅ’ ጥረት እየተደረገ መሆኑ ጠቅሼ ነበር።

ትንቅንቅ

ትንቅንቅ

አሁን አቶ ስብሃት ነጋ (ከቢተው በላይ ጋር በመሆን) ሁለቱም ባላንጣ ቡድኖች ‘ማስታረቅ’ ችለዋል። ዕርቁ የተፈፀመው በነ ደብረፅዮን ቡድን አሸናፊነት ነው። የነ አባይ ወልዱ ቡድን በመሸነፉ ምክንያት አቶ አባይ ወልዱ ከነ ስብሃት ነጋ ጋር እንዲስማማ ምክንያት ሁነዋል። የነ አባይ ቡድን የተዳከመበት ምክንያት ለሁለት በመከፈሉ ነው። አቶ አባይ ወልዱ ከአቶ ቴድሮስ ሐጎስ፣ ኢያሱ ተስፋይ፣ ተክለወይኒ አሰፋ፣ ኪሮስ ቢተው፣ በየነ መክሩ ወዘተ መግባባት ባለመቻሉ ከአዲስ አበባዎቹ ጋር ለመስማማት ተገደዋል።

tewedrosበስምምነቱ መሰረት ህወሓት በአዲስ አበባዎቹ ፕላን ይጓዛል። በ’መለስ ራእይ’ ስም ህዝብ መጀንጀን ይቀራል። በሙስና ሰበብ ባለስልጣናት ማሳሰርም ይቀራል። ከአሁኑ በኋል ከፍተኛ የህወሓት ባለስልጣናት በሙስና ሰበብ አይታሰሩም። በቀጣዩ የኢህአዴግ ጉባኤ የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስተር ከህወሓት እንዲሆን ጥረት ይደረጋል (ዶር ቴድሮስ አድሐኖም)።

ይህ የህወሓቶች የ’ዕርቅ ሂደት’ ባብዛኛው የብአዴን አመራር አባላትና በተወሰኑ የኦህዴድ መሪዎች ቅሬታ አስነስተዋል። ህወሓቶች ለመታረቅ የተገደዱበት ምክንያት በተቃዋሚዎች ስልጣን እንዳይነጠቁ በመስጋት ነው። ዓረና ፓርቲ ለህወሓቶች ትልቅ ስጋት በመፍጠሩ ነው። የፀጥታ ሃይሉ መፈራረስም ሌላ ህወሓቶች ያስደነገጠ ጉዳይ ነው። በዕርቁ ሂደት ከፍተኛ ሚና የተጫወተው አቶ ስብሃት ነጋ ነው።

የዕርቅ ሂደቱ በኢህአዴግ አባል ድርጅቶች ከፍተኛ አለመግባባት ሊፈጥር ይችላል። ኢህአዴግ በዉስጥ ለውስጥ የስልጣን ሹክቻ ምክንያት የሚዳከምበት አጋጣሚ መፈጠሩ አይቀርም። ዕርቁ ግዝያዊና ስትራተጂካዊ ብቻ ነው። የታረቁት መግባባት ስለ ፈጠሩ ሳይሆን የጋራ ጠላትን ለመከላከል ብቻ ነው።

ኢኮኖሚያችን ሲያድግ የህዝቡ ኑሮ ለምን አሽቆለቆለ?

$
0
0

Question-Markላለፉት 8 እና ዘጠኝ ዓመታት የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በሁለት አሃዝ አያደገ ነው ሲባል እንሰማለን፤  የእድገት ፍጥነቱ  ላይ የሚነሱ በርካታ ጥያቄውች  ቢኖሩም መንግስት  የመንገድ ግንባታ ፣ የኃይል ማመንጫ ግንባታወችን እና መሰል ነገሮችን  በመጥቀስ እድገት እንዳለ አስረግጦ ይከራከራል::  በሌላ በኩል የኢኮኖሚ እድገቱ ተመዘገበ በሚባልባቸው ዓመታት በዋጋ ንረት የህዝቡ ኑሮ ከጊዜ ወደጊዜ እያሽቆለቆለ  እንደሆነ በግልፅ የሚታይ ነገር ነው:: ታዲያ  የኢኮኖሚ እድገት አለ በተባለባቸው ዓመታት የህዝቡ ኑሮ ለምን አሽቆለቆለ? ይህን ጥያቄ ከ 7 ዓመት በፊት ሟቹ ጠቅላይ ሚኒስቴር መለስ  ተጠይቀው የሰጡት መልስ የዋጋ ንረቱን የኢኮኖሚ እድገቱ እራሱ የፈጠረው ጉዳይ ነው ነገር ግን ቀስ በቀስ እድገቱ ሲቀጥል ራሱ እድገቱ ችግሩን ይፈታዋል ብለው ነበር፤ ነገር ግን ከሰባት ዓመት በዃላም እንኩአን ሊሻሻል  የህዝቡ የኑሮ ሁኔታ ከቀን ወደቀን እየባሰበት ሂዷል::  ችግሩ የተለያዩ  ምንጮች ቢኖሩትም በዋናነት በ 2 ከፍሎ ማየት ይቻላል::

፩. የኢኮኖሚ እድገቱ ምንጭ

፪. የሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ መዋቅር

የኢኮኖሚ እድገት ማለት በአጭሩ ኢኮኖሚዉ ዉስጥ ተጨማሪ ሀብት መፍጠር ማለት ነው::  በመጀምሪያ ላለፉት 8  እና ዘጠኝ ዓመታት ኢትዮጵያ ዉስጥ  የተፈጠሩት ተጨማሪ ሀብቶች ምንድን ናቸው ብሎ መጠየቅ ያስፈልጋል ፤  በአብዛኛዉ ሀገሪቱ ዉስጥ የተፈጠሩት ሀብቶች ከመንገድ ፣ ከሕንፃ እና ከ ከኃይል ማመንጫ ከግንባታ ጋር የተያያዙ ናቸው:: በመቀጠልም የዚህ ሀብት የገንዝብ ምንጭ ምንድን ነው ብሎ ማየት ያስፈልጋል፤ የገንዘቡ ምንጭ በዋናነት ከብድር እና እርዳታ የተገኘ ሀብት ነው ፣ በተለይም በኢትዮጵያ አቆጣጠር ከ 1998 ዓም ጀምሮ በሶማሊያ በመጀመሪያ የእስላማዊ ፍርድ ቤቶች ህብረት በመቀጠልም የአልሻባብ እንቅስቃሴ መጠናከር ለኢትዮጵያ ትልቅ ሲሳይ ይዞ ነው የመጣው:: በሶማሊያ ያለዉን ሁኔታ  ለመቆጣጠር ምዕራባዉያኑ የሚያደርጉትን ጥረት በመደገፍ  በዋና አጋርነት የተሰለፈችዉ ኢትዮጵያ ላለፉት ስምንት ዓመታት በየዓመቱ በቢልየን ዶላር የሚቆጠር ገንዘብ በእርዳታ መልክ ከምዕራብ ሃገራት እንድታገኝ አድርጓታል:: ይህም ማለት ሀገሪቱ ዉስጥ የጎላ  የኢኮኖሚያዊ መዋቅር ፣ የአሰራር ስርዓት  እና የቴክኖሎጅ ለውጥ ሳይኖር ከፍተኛ ገንዘብ ወደኢኮኖሚው ፈሰስ እንዲሆን አድርጓል:: በሌላ አገላለፅ  የቆየው የሀገሪቱ  ኢኮኖሚ የጎላ የምርት ጭማሪ ሳይኖረው ከዉጭ የተገኘ ብድር እና እርዳታ ኢኮኖሚዉ ዉስጥ ተጨመረ እና የኢኮኖሚዉ መጠን አደገ ማለት ነው::  ስለዚህ የህዝቡን የኑሮ ሁኔታ እና የሀገሪቱን ተወዳዳሪነት ሊያሻሽል የሚችል የግብርና እና የኢንዱስትሪ ዘርፎች ላይ የጎላ  ለዉጥ ሳይታይ ለመሠረት ልማት ኢኮኖሚዉ ዉስጥ ፈሰስ የተደረገው ገንዝብ የገንዘብ አቅርቦትን (Money Supply) በመጨመር እና  የአገልግሎት ዘርፉ ( Service sector) ከሌሎቹ የኢኮኖሚ ዘርፎች ተነጥሎ እንዲለጠጥ እንዲሁም ዋጋ እንዲንር በማድረግ አብዛኛዉን ሕዝብ ለችግር አጋለጠ ::

ከብድር እና እርዳታ የተገኘው ገንዘብ መሰረተ ልማት ላይ ሲዉል ከላይ የተገለፀው ችግር ቢኖርበትም በአንፃሩ የመሰረተ ልማት መስፋፋት የማምረቻ ወጭ ( cost of production) እንዲቀንስ በማድረግ የሚያስገኘው ጥቅም አለ ፤ በተጨማሪም ገንዘብ ገንዘብን ይፈጥራል “ money creats money” በሚለው የኢኮኖምክስ  መርህ መሰረት ኢኮኖሚዉ ዉስጥ የተረጨው ገንዘብ በአብዛኛዉ አገልግሎት ዘርፉ ላይ የፈጠረው ተጨማሪ ሀብት አለ:: ነገር ግን ይህ የተፈጠረ ተጨማሪ ሀብት በጠንካራ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ መዋቅር ስላልተመራ ወደጥቂት ሰወች እጅ እንዲገባ ሁኗል::  ሃብቱ እጃቸው የገባ ሰወችም የኢኮኖሚዉን መዋቅር ሊለዉጡ የሚችሉ እንደኢንዱስትሪ አይነት ዘርፎች ላይ ከመሰማራት ይልቅ ከሙሰኛ ባለስልጣናት ጋር በመመሳጠር ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያለዉን የከተማ ቦታ በኢንቨስትመንት እና በሊዝ ስም በመዉሰድ ህንፃ በመገንባት እየተለጠጠ ላለው የአገልግሎት ዘርፍ በማከራየት በአቁአራጭ ከፍተኛ ገቢ ለመሰብሰብ ተጠቀሙበት::

በሌላ በኩል የሀገሪቱ የመሬት አስተዳደር ስርዓት በሙስና የተጨማለቀ እና ወጥ ስላሆነና አዳዲስ ብቅ ለሚሉ ባለሀብቶች መሬት ማግኘት ከባድ ስለሆነ ሀገሪቱ አሁን ባለችበት ተጨባጭ ሁኔታ ወሳኝ ሀብት (strategic resource) የሆነዉን የከተማ ቦታ ቀድመው የያዙ ባለሀብቶች የገቢያ ዉድድሩን ሚዛናዊ እንዳይሆን በማድረግ አዲስ የሚፈጠሩ ተወዳዳሪያቸውን በቀላሉ ከገቢያ ያስወጣሉ:: በተጨማሪም እንደነዚህ አይነቶቹ  ባለሀብቶች በአብዛኛው የፖለቲካዉ እና የግዥዉ ፓርቲ ጥገኛ ስለሆኑ የሚጠበቅባቸዉን ያክል  ግብር እና ታክስ አይከፍሉም:: ሥራቸዉን ስለሚያውቁም በሀገሪቱ በረጅም ጊዜ ሊከሰት ይችላል ብለው የሚፈሩትን ፖለቲካዊ አለመረጋጋት ስለሚሰጉ የሚያገኙትን ትርፍ ወደዉጭ ያሽሻሉ ፤ በጎን ሙሰኛ ባለስልጣናትም የሚዘርፉትን ገንዘብ ከሀገር ያሸሻሉ:: ከዚህ ላይ ፋይናንሽያል ትራንስፓረንሲ ኳሊሽን  ያወጣዉንና ኢትዮጵያ በህገወጥ የገንዘብ ፍሰት (illicit financial flow) በፈረንጆቹ ከ 2000 እስከ 2009 ያጣችዉን 11. 7 ቢልየን ዶላር ልብ ይሏል::

ለማጠቃለል የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ጤናማ ሁኖ እንዲያድግ ከተፈለገ ከላይ የተጠቀሱት  የሀገሪቱ የኢኮኖሚ እና የፖለቲካ መዋቅር ድክመቶች መስተካከል የሚገባቸዉ ሲሆን ፤ በዉጭ ብድር እና እርዳታ ላይ መንጠልጠሉን ቀንሶ ከሀገር ቤት በፍትሃዊነት ከሚሰበሰብ ግብር ሊሆን ይገባል:: ከዉጭ የሚገኘዉን ሀብትም  በብዛት መሰረተ ልማት ላይ ብቻ ማዋሉ የሚያስከትለዉን ችግር ጥልቅ ጥናት በማካሄድ  መመርመር እና  ገንዘቡ ከመሰረተ ልማቱ ጎን ለጎን የኢንዱስትሪው እና የእርሻዉን ዘርፍ መዋቅር ወደተሻለ ደረጃ እንዲደርስ ለማስቻልም መሰራት አለበት:: ከሁሉም በላይ ግን የኢኮኖሚ ነቀርሳ የሆነዉን ሙስና ለማስወገድ ከአንድ ፓርቲ የበላይነት ወደ መድብለ ፓርቲ ስርዓት መሸጋገር እንዲሁም ተጠያቂነትን ሊያጠናክሩ የሚችሉ እንደገለልተኛ ፍርድ ቤቶች ፣ የግል መገናኛ ብዙሃን  የመሳሰሉትን ተቋማት መፍጠር ያስፈልጋል:: ይህ ካልሆነ ግን ሀገሪቱ ሽህ ጊዜ ብታድግ የኢኮኖሚውን ፍሬ ጥቂቶች እየበሉ የአብዛኛዉ ሕዝብ  ኑሮ ማሽቆልቆሉ ይቀጥላል::

 

 

 

የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ከዩኒቨርስቲ ተባረሩ

$
0
0

ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ እንደዘገበው፦ የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርስቲና የጤና ነክ ተማሪዎች ለውዝግብ የተዳረጉት በሚሰጠው ድግሪ ሲያሜ እንደሆነ ከቦታው የደረሰን ማስረጃ ያስረዳል፡፡ ከ1ኛ እስከ 4ተኛ ዓመት ያሉ ተማሪዎች ሲመደቡ ዲግሪያቸው የጤና ሳይንስ መኮንን (Public Health Officer) እንደሚባል እንደተነገራቸው ገልፀው ነገር ግን ዩኒቨርሲቲው አሁን የህብረተሰብ ጤና (Public Health) ብቻ የሚል ስያሜ እንደሰጣቸው ተናግረዋል፡፡ ተማሪዎቹ ጉዳዩን በማሳወቅ ማብራሪያ የጠየቁ ሲሆን “‹የህብረተሰብ ጤና አጠባበቅ› የሚለው እናንተን አይመጥንም” እንደተባሉ ገልጸዋል፡፡
Debre_Markos
በመልሱ ያልረኩት የዲፓርትመንቱ ተማሪዎች ተጨማሪ ማብራሪያ ለማግኘት ከህዳር 28 ጀምሮ ደረጃውን ጠብቀው ለሚመለከተው የዩኒቨርስቲው ኃላፊዎችና ለፕሬዚደንቱ ጥያቄ ቢያቀርቡም “ብትማሩ ተማሩ ባትማሩ ግቢውን ለቃችሁ ትወጣላችሁ” የሚል ማስፈራሪያ እንደተሰነዘረባቸው አሳውቀዋል፡፡ ታህሣስ 05 ቀን 2006 ዓ.ም የተሰበሰበው የዩኒቨርስቲው ሴኔት 173 ተማሪዎች ከግቢ እንዲባረሩ ወስኗል፡፡

ከሰኞ ታህሣስ 7 ቀን 2006 ዓ.ም ጀምሮ መታወቂያቸውን በፖሊስ ተቀምተው ከግቢው እንዲባረሩ የተደረጉት 173 ተማሪዎች በአሁኑ ሰዓት ሜዳ ላይ ተበትነው እንደሚገኙና ለከፍተኛ ችግር እንደተጋለጡ በምሬት ተናግረዋል፡፡
ጉዳዩን ለማረጋገጥ የጤና ዲፓርትመንት ኃላፊ ወደ ሆኑት አቶ ዱቤ ጃራ ስልክ ደውለን የተባለው ነገር መከሰቱን ጠቅሰው ነገር ግን “ውሳኔው በአግባቡ ነው የተላለፈው፤ ይህ ስያሜ ከ1954 ዓ.ም ጀምሮ የነበረ ነው፤ ካሪኩለሙ ላይ ያለው የህብረተሰብ ጤና (Public Health) እንጂ የህብረተሰብ ጤና መኮንን (Public Health Officer) አይደለም” ብለዋል፡፡

አቶ ዱቤ በተደጋጋሚ የዲግሪው ስያሜ “አዲስ የተሰጠ ስያሜ አይደለም” ካሉ በኋላ በተጨማሪም “ተማሪዎቹ ያለ ትምህርት ለ11 ቀናት ግቢ ውስጥ መቀመጣቸው ተገቢ ስላልሆነ ከግቢ እንዲወጡ ተደርጓል” ብለዋል፡፡ በተያያዘ ጉዳይ ከጊቢው የተባረሩ ተማሪዎች ከፍተኛ ችግር ላይ መሆናቸው ታውቋል፡፡ ስሙ እንዲገለፅ ያልፈቀደ አንድ ተማሪ “መጠለያ፣ ልብስና ምግብ” እጅግ እንደቸገራቸው ገልፆ በተለይ ሴት ተማሪዎቹ መጠለያ እንዲሰጣቸው ለምስራቅ ጎጃም ዞን የሴቶች ጉዳይ ቢያመለክቱም “ዩኒቨርሲቲው ያባረራቸውን ብንረዳ እንጠየቃለን፤ ስለዚህ ልንረዳቸው አንችልም ማለታቸው ታውቋል፡

ሰበር ዜና ከሳውዲ አረቢያ ! ሮብ ምሽት በመንፈሃ ዙሪያ መጠነ ሰፊ ጥብቅ ፍተሻ ተጀመረ !

$
0
0

ነቢዩ ሲራክ

* በሪያድ የኢትዮጵያ ኢንባሲ የተጀመረውን ፍተሻ በማረጋገጥ ህጋዊ ሰነድ የሌላቸው ዜጎች በሰላማዊ መንገድ በአስቸኳይ ለጸጥታ አስከባሪዎች እጅ በመስጠት ወደ መጠለያ በመግባት ወደ ሃገር እንዲገቡ ማምሻውን ባወጣው ማስታወቂያ አሳስቧል ። ካለፉት ሳምንታት ወዲህ በሪያድ መንፉሃ በኢንባሲውና በሃገር ሽማግሌዎች የተቋቋሙ የመረጋጋት ኮሚቴ አባላት ወደ መንፉሃና ኢትዮጵያውያን በሚበዙባቸው ምንደሮች በመንቀሳቀስ ዜጎች ያለ ምንም ጉዳት እጃቸውን ሰጥተው ወደ ሃገር ለመግባት እንዲዘጋጁ የመከረ ቢሆንም ጥረቱ አልተሳካም ነበር ።  የሪያድ ኢናባሲ የሽማግሌዎች ኮሚቴ አባላት ባደረጉት ቅስቀሳ ወደ ሃገር ለመግባት ባልተጨበጠ ተስፋ የተዘናጉ ህጋዊ መኖሪያ ፈቃድ ያልያዙ ወደ ሃገር በመግባቱ ላይ እንዳያቅማሙ መምከራቸው ይጠቀሳል !

* አሁን በተጀመረው የመንፉሃ ፍተሻ ማዋከብ የለበትም ። ህጋዊ መኖርያ ፍቃድ የሌለውን ብቻ እንደሚይዙና ከአሰሪው (ከከፊሉ) ጋር ይሰራል አይሰራም የሚባል ማጣራትም ሲካሔድ አልተስተዋለም ተብሏል ።

* ከአሰሪው ጋር የማይሰራ እንደ ህገ ወጥ እንደሚቆጠር የሳውዲ ህግ በግልጽ ያሳወቀ ሲሆን የጅዳና የሪያድ ኢንባሲ ይህ ህግ እንደሚጸና ተደጋጋሚ ማስታወቂያ በማውጣት “በሰላም ወደ ሃገራችሁ ግቡ!” በማለት ሲመክሩና ሲወተውቱ ሰንብተዋል።

* በቀጣዩ መጠነ ሰፊ የማጣራት ዘመቻም ከአሰሪው (ከከፊሉ) ጋር የማይሰራ እንደ ህጋዊ ስለሚቆጠር የሳውዲ መንግስት በፈቃደኝነት እጃቸውን የሚሰጡት ወገኖች ወደ ሃገር መስደድ እንደተጠናቀቀ አንወጣም ባሉት ላይ ፍተሻ በማድረግ በእስራትና በገንዘብ እንደሚቀጣ በኢንባሲና በቆንስል መስሪያ ቤቶች በኩል ባስተላለፈው ማስጠንቀቂያ አስታውቋል ።

*  ቁጥራቸው በሽዎች የሚገመቱ ዜጎች እስካሁንም ድረስ ወደ ሃገር ግቡ የሚለውን ጥሪ ባለመቀበል የተዘናጉበት ሁኔታ ይስተዋላል ። ይሁን እንጅ ካለፉት ሁለት ቀናት ወዲህ መንቀሳቀስ  ያልጀመረው የጅዳ አካባቢ በርካታ ነዋሪዎች ወደ ሃገር ቤት ለመግባት ወደ ተዘጋጀው መጠለያ በመግባት ላይ ናቸው ። ከአሰሪያቸው ጋር ስለማይሰሩ ህገ ወጥ የተባሉት ግን አሁንም እንቅስቃሴ አለማሳየታቸው ይመለከታል ።

* የጅዳ ቆንስልና የወገን ለወገን ደራሽ ኮሚቴውም አውቶቡስን በአፋጣኝ እንዲቀርብ በማድረጉ ረገድ ከቆንሰሉ ሃላፊዎች ጋር በመተባበር ለነዋሪው ድጋፍ በማድረግ ላይ ናቸው ። ህጋዊ ሰነድ የሌላችሁ አስፈላጊውን ውሳኔ መውሰድና በእድሉ መጠቀም ይጠበቅችኋል። እድሉን መጠቀም መቻል ብልህነት ነው !

554190_613712818703643_1441333089_n

ጀሮ ያለው ይስማ

ነቢዩ ሲራክ

የለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ጉዳይ ለወያኔ እጅ መስጠት ወይም ነጻ የመዉጣት ትግል ነዉ፤ ምዕመናን በድምጽ የማሸነፍ ሙሉ መብት አላቸዉ

$
0
0

ከአጥቃዉ ቦጋለ

የለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ጉዳይ ለወያኔ እጅ መስጠት ወይም ነጻ የመዉጣት ትግል ነዉ። ምዕመናን በድምጽ የማሸነፍ  ሙሉ መብት አላቸዉ። በድምጽ ያሸነፈ ብቻ ይረከባል፦ይህ መብት የእንግሊዝ አገር ዲሞክራሲ  ነዉና፤ ግን ሰዉ ያልዘራዉን ማጨድ አይችልም።

londonየለንደን የደብረ ጽዮን ቅድስት ማሪያም በሁለቱም ጎን ከወያኔ ጋር እከከን ልከክህ እያሉ የዉጩን ህጋይዊ ሲኖዶስ ሙሉ በሙሉ በመርሳት ብሎም ለማዳከም በቃወም  በርከት ያሉት ዉስጥ ዉስጡን የወያኔ የልማት አጋር ሁነዉ የቆዩ ናቸዉ። አንዱ ለተፈጠረዉ ችግር ምክንያት ይህ ሳይሆን አይቀርም። ወያኔ የሚሰራዉን ግፍ ጥቂት ምዕመናን ከተቃዋሚዉ ጎን ያሉ አባላት ቢያወግዙም  በልማት አጋሮች  አስተባባሪነት አብዛናወቹ ህዝበ ክርስቲያን  ወያኔ የሚሰራዉን ግፍ ጀሮ ዳባ ልበስ ብሎ ቆይተዋል።አሁን በአንድነት የቆሙት አባላት እንኳ ቀኖና ተጥሶ በመሳሪያ አፈሙዝ ግፍ የተፈጸመባቸዉን ስደተኛ የኦርቶዶክስ አባት በጽሁፋቸዉ እንኳ ማንሳት አይፈልጉም፤ ይህ የትቢት ይሁን የጎጥ ወይም የሃይማኖት ልዩነት ግልጽ አይደለም፤ ግፍን ከማዉገዝ ገለልተኛ የሆነ ትዉልድ የለምና። ወያኔም ይህ የደለላቸዉን ብዙ የወዳጆቹን  አቋም  በገንዘብ በዉስጥ መሰሪ ካድሬወችን አሰማራ ፤የልማት ተዋናኞችም ደስተኛ ሆኖ፤ አሁን ግን ደረቅ ችሆት ይጮሃሉ። ዛሬም የወያኔ የድብቅ ነጋዴዎች  መንታ መንግድ ላይ መሆናቸዉ ጥርጥር የለዉም፤ ስለወያኔ ወንጀለኛነት በአንድ ድምጽ ሲያወግዙ አይሰማም፤ የሚሰድቡ ካድሬዉን ካህን ብቻ ነዉ፣ አህያዉን ፈርቶ ዳዉላዉን ይላሉ ይህ ነዉና። ይልቅስ አባላት ጸረ ወያኔ አቋም ይዘዉ ወንጀለኛ መንግስት ከቤተ ክርስቲያናችን እጁን  ያንሳ ማለት መቻል አለባቸዉ። የተሰደዱ አባቶች የወያኔን በደል እንዲመሰክሩ ከምዕመናኑ ፊት ባይርቁ ጥሩ ነዉ።። ወያኔ ነብስ አጥፊና  የሃይማኖት አባቶችን አሳዳጅ እንደሆነ በመረጃ አስረግጠዉ ካድሬወችንና ኢምባሲዉን ያዉግዙ፤ ይክሰሱ።ግፉ እየተፈጸመ ያለዉ በኦርቶዶክስ የሃይማኖት ዕምነት ተከታይ ክርስቲያኖች ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያ ዉስጥ በሁሉም ዘርግ በዕምነት መገደል, መታሰር ለስደት መዳረግ መኖሩን በመረጃነት አቅርቡ። የአቡነ መርቆሪወስና የሌሎች አባተች ቀኖና ተጥሶ በወያኔ ግፍ  ጭካኔ የተሞላት ድርጊት ተሣደዉ መሰቃየታቸዉን ሳትሸማቀቁ በመረጃነት ጥቀሱ፤  የሃይማኖት ጉዳይ በመሀል ሰፋሪነት ፍጹም ሊሆን አይችልም። በሃይማኖት  ዋናዉ ቁም ነገሩ የቤተ ክርስቲያን ህንጻ በብዙ ሚሊዮን መገንባት  ብቻ ሳይሆን  ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ከአንድ አምላክ በታች  ሁልጊዜም እራስ አላት ብሎ መጽናት እዉነተኛ መንገድ ነዉ። በተለይ የኛ ቤተ ክርስቲያን ብትሰደድም ገለልተኛ ሁና አታዉቅምl። ወደፊትም በአስቸኳይ ወያኔን ማስወግድ ገዘገየ ከተሰደዱ ህጋዊ አባቶች ጋር የጽድቅ ጉዟችን መቀጠል  የሃይማኖት ግዴታችን ነዉ።  ሌላዉ መንገድ ለእግዚአብሔሩ ቀርቶ ለአለማዊ የአንድነት ኑሮ አላመቸም፤  ይልቅስ የወያኔ ጅቦች  በቀዳዳዉ ይገባሉ በሚል ፍራቻ እርስ በእርስ እየተጠራጠርን ለፍርድ አናስቸግር። የዉስጥና የዉስጭ ሲኖዶስ እስቲታረቁ ከሆነ የምንጠብቀዉ እንደዚህ አይነት የሃይማኖት እምነት የለም። ኢትዮጵያ ያለዉ መንግስት ሃይማኖትን ተቆጣጥሮ ኢትዮጵያዉያንን እያሳደደ ከሆነ  ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስና ሌሎች አባቶች ጭምር እየተሳደዱ ነዉ። ይህንን በደልም ከመጥቀስ ወደኋላ አትበሉ፤ ግፍን በመረጃ ማቅረብ እኮ የአባ መርቆሪዮስ ደጋፊ አያሰኝምl፤ እኒህ የኦርቶዶክሳዊያን አባት  ለሁላችንም ሃያ አራት ሰዓት በመጸለይ ላይ እንደሆኑ አትዘንጉ፤ አስታዉሷቸዉ፤ ከህንጻዉ ይበልጣሉና።

አወ ለፍርድ ቤት በመጨረሻ ጉዳዩ ቢቀርብ ከኛ በበለጠ የኛን ቤተ ክርስቲያን የአስተዳደር መዋቅር ቁልጭ አድርገዉ ፍርድ ቤቶች ያዉቃልና ሌሎች ቤተ ክርስቲያናትም  ከእምነታችን አስተዳደር ዉጭ ገለልተኛ ነን እያላችሁ  የምትዝናኑ ችግሩ በራችሁን ላይ በአጭር ጊዜ ያንኳካል በእዉነት ስለ ዕዉነት አስቡበት። ለመሆኑ በአሁኑ ሰዓት አገር እየጠፋ ከምኑ ገለል እደምትሉ የሚጨበጥ ቁም  ነገር ጠፍቷል። ጉዳዩ በጽዮን  ብቻ አያበቃም፤ የሃይማኖት ቤታችን ወደ ንግድ ተቋም የመሸጋገር አደጋ እዬገጠመዉ ነዉ፤ እግዚአብሔር ወደ እዉነቱ ቦታችን ይመልሰን። ሌላዉ የዚህ ዓለም መንግስታዊ ፍርድ ቤት በህዝብ ድምጽ ያምናልና ለወያኔ ጊዚያዊ  የልማት ተጠቃሚ የሆናችሁ ወያኔን ካዱትና ድምጻችሁን ስጡ። የለደን ደብረ ጽዮን አባላት ብዙ ምሁራን እና የቤተ ክርስቲያን ሊቃዉንት እያሉበት  ግን በልማት ስምና ጎንደሬ ፓትራሪክ አቡነ መርቆሪዮስ ለመቃዉም ሲባል  የገለልተኛ ከበሮ አታድምቁ  ሲሆን የተበደለዉ ሁሉ ተባብሮ ማሸነፍ ፤ካልሆነም ገለል ከማለት በዓላማ ጸንቶ አወዳደቅን ማሳመር ተገቢ ነዉ። ወያኔም  ይህን የወላዋይ አቋም ይዘዉ መክረማቸዉን አስተዉሎ ጭራቸዉን በመያዝ  ፊታቸዉን መልሰዉ ወያኔ ገዳይ ነዉ ፤ጠላትም ነዉ ብለዉ መናገር እንዳይችሉ አደረገ። ምርጫዉ የኛ ነዉ፤ ለፍትህ ፤ ለሃይማኖት መቆም ወይስ ሁለት ባላ ላይ ለመቆም ወያኔ መንደር የተሰራዉን  ከንቱ የልማት ቤት በህልም እያዩ ወያኔ የጠለፋ ገመድ ታስሮ ባርነትን መምረጥ ፤ የቆጡን አወርድ ብሎ የ…..ማለት እንዲህ ነዉ። ሁሉም አባላት  ማለትም አብዛኛዉ ከተስማሙ መፍትሄዉ ቀላል ነዉ በአንድ ድምጽ የሚሰራዉን ግፍ ስናወግዝ ያኔ የወያኔ አደራጆች /ጠርናፊወች ጓዛቸዉን ጠቅለዉ ይሄዳሉ። በአሜሪካ ሚኒሶታ ደብረ ሰላም መድሃኒአለም የሆነዉ እንደዚህ ነዉ፤ የወያኔ ጠርናፊወች በስድስት ወራት 700 አባላትን አስመዝግበዉ በድምጽ ለማሸነፍ  በጉባኤ ሲቀመጡ ኢትዮጵያዊ ኢትዮጵያዊነቱን ነብር ዝንጉርጉርነቱን አይቀይርምና  አብዛኛዉ አባላቱ አቋማቸዉን አንድ አድርገዉ ወያኔ በመካድ  ኢትዮጵያ ዉስጥም ሆነ በየአለማቱ ወያኔ ሲሰራ የቆየዉን የሃያ ሁለት ዓመታት ግፍ አስረግጠዉ በመንገር፤  ከወያኔ ስር የምንወድቀዉ ምን አዲስ የሃይማኖትም  ወይም የህዝብ ነጻነት ተገኘ በማለት  ከሆዳሞች በቀር አብዛኛዉ ምዕመናን በጸረ ወያኔ አቋሙ ወስዶ  መድሃኒአለምን እጅ መንሻ ከመሆን አዳነ።  የለንደን ጽዮን ምዕመናን ትኩረታችሁ በቻሪቲ ጉዳይ ብቻ አታድርጉ ከዉስጣችሁ የመሸጉትን የልማት አባዉራወች በመነጸር እዩ ፤ በደም የተጨማለቁ በመዋለ ንዋይ የሰከሩ ወያኔወች ገለልተኛነት የወያኔ መሸጋገሪያ መንግድ አድርገዉ የተጠቀሙ ካድሬዎች ከዬቤተ ክርስቲያን ተመንጥረዉ ያለ እሉኝታ መባረር አለባቸዉ። በሚኒሶታ የተሰገሰጉት ንፍቀ ወያኔወች የወደፍቲ እጣ ይህ ነዉ። አሁን  ቢወድቁም ሙቶ የመፈራገጥ የወያኔ ባህሪያቸዉ አይጠፋምና  ምዕመናኑ ጠንቅቆ ስለሚያቃቸዉ በሚቀጥለዉ ምርጫ ከሚኒሶታ መድሃኒዓለም ግቢ ጨርሶ እንደሚያስወጣቸዉ እርግጠና ነኝ። ዘረኛዉ ወያኔ በለደን አካባቢ መሽጎ የሚተበትበዉ የሴራ ገመድ በአጭር ቀን ይበጣጠሳል። ምዕመናኑ በአንድነት መቆም ብቻ ሳይሆን የችግሩ ዋና ምንጭ የሆነዉን ወያኔን በማጋለጥ l ማለትም የሚያካህደዉን የዘር ማጥፋት ወንጀል በአማራዉ፤ በኦሮሞዉ, በጋምቤላዉ፤ በአፋሩ ሁሊንም ብሔሮች በመክፋፈልና በማጋጨት በዘረፋ ላይ መሰማራቱን መላዉን ኢትዮጵያዉያን የዕምነት ነጻነት መንፈጉን በአ,ደባባይ ተናገሩ። የወያኔዉን ተላላኪ ካህን ብቻ ማዉገዙ ፋይዳ የለዉም፤ አህያዉን ፈርቶ ዳዉላዉን ነዉና፤ ወደቁንጮዉ አነጣጥሩ። የሰዉ ዘር አጥፊና የሃይማኖት አባቶቻችን በማሳደድ ላይ እንዳለ ለለንደን ህዝብና ለእንግሊዝ መንግስት  አስረዱ። የወያኔ መንግስት ተባባሪ እነማን እንደሆኑ አጋልጣችሁ ከስርዓቱ ጋር ተጠያቂ መሆናቸዉን አስተምሩ፤ ከዉስጣችሁ ገና በህዝብ መብት ጉዳይ በወያኔን ጠላትነት ጉዳይ የጠራ  አቋም ያልያዙ ያሉ ይመስለኛል፤ ሁላችሁን ማለቴ አይደለም፤ ገለልተኛ ነን፤ ብዙ ገንዘብ አዉተን ህንጻ ገንብተናል ማለት ብቻ በቂ አይመስለኝም፤ ይህ በሃይማኖት ቤት ብዙ አይስተናገድም። ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሪዮስ በግፍ የተሰቃዩ አባት መሆናቸዉን ጭራሹን  አትርሱ፤ ከቀኖናም ሆነ ከሃይማኖት አንጻር መሰረታችሁ መስመሩን መዉጣት የለበትም፤ አባ መርቆሪዮስን ወያኔ በመሳሪያ ማዉረዱን ታዉቃላችሁ። እናንተን ግን በልማት ስም ወያኔ ሊያዋርዳችሁ በአንድ ለአምስት ጥርነፋዉ በገለልተኛ መርሆ ገብቶ ህገ ቤተ ክርስቲያን እያፈረሰ ነዉ። በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ  መፍትሄ የሚገኘዉ  የእዉነቱን በመናገር እንጂ ንብረቱን ለመቆጣጠር የሚደረገዉ የሽቅድድም እሩጫ የአምላክ መልካም ፈቃድ አይጨመርበትም። አወ ወያኔ ባወጣዉ የጎጥ መስፈርት  አቡነ መርቆሪዮስ ጎንደር ክፍለ ሃገር የተወለዱ ናቸዉ፤ ሃቁ ግን ወያኔ ሊቀ ጳጳሱ ትግሬ ቢሆኑ  አያባራቸዉም።  ይኸዉ አሁንም ደግሞ ደጋግሞ የሚሾመዉ የትግሬ ፓትራሪክ፤ የትግሬ ጀኔራል ነዉ። በእርግጥ ይህ ስልቱ ትግሬዉን ከሌላዉ ህዝብ እያራራቀ የስልጣን ዘመኑን አስረዝሞ ለመዝረፍ ነዉ። ሃቀኛ የትግራይ ልጆች አሁንም በወያኔ እዬተገደሉ እዬተሳደዱ ነዉ፤ ዉሎ አድሮ የትግራይ ህዝብ በቃ ይላቸዋል፤ አዎ ብዙ ገንጣይ ወያኔን ታገሉት ግን አፍኖ አዳከማቸዉ፤ የዕራያ ህዝብ ዛሬ ከሞቱት በላይ ካሉት በታች ነዉ፤ የተንቤን ህዝብ ከተረሳ ዓመታት አልፈዋል። ኢትዮጵያን ቆራርሶ ወያኔ ለባዕድ አግር በመስጠት ያዋረዳት እየከነከነዉ ቆሽቱ ያረረዉ  የትግራይ ህዝብ ከመላዉ ኢትዮጵያ ህዝብ ጋር ሁኖ  ወደክብሯ ለመመለስ ትግሉን ቀጥሏል። አየ ጉድ ጽሁፌን የወያኔ የዘር ጣጣ ጠልፎ ወሰደብኝና ብዙ ተናገርኩ፤ በሉ የጀመርኩትን ልጨርስ። አባ መርቆርዮስ ጎንደር ቢወለዱም እዉነተኛ ኢትዮጵያዊ እና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ/ክ  አባት ናቸዉ፤ በእርሳቸዉ የደረሰዉ ስቃይና መከራ እየረሳን  ማህበረ ቤተ ክርስቲያን ማጠናከር ወይም ባለቤት መሆን እግዚአብሔርም ሆነ ቀኖና አይደግፈንም። ሁላችን ሁሉን ህግ የሚጥሰዉን ወያኔን  ዘረኛ፤ ነብሰ ገዳይ፤  ዘራፊ ነዉ ብለን፤ ትግሬዉ፤ ኣማራዉ፤ ኦሮሞዉ፤ ሃድያዉ፤ ማለትም መላዉ ኢትዮጵያዊያን በዉጭ የዘረጋዉን የዘር መረብ በአንድነት መበጣጠስ አለብን። ችግሩ  በአሜሪካም እንዳንዣበበ ነዉ ። የዋሽንግተን የማሪያም  ቤተ ክርስቲያን እጣ ፈንታም  ተመሳሳይ ነዉ። እጀ እረጅሙ ወያኔ ለስላ ከመደበዉ 40MILLION ዶላር ብዙዉን ይህችን ትልቅ ካቴድራል አንቆ ለመያዝ የተጠቀመበት ነዉ። የልማት ሚሊዬነሮች በመቶ ሺህ በሚቆጠር ገንዘብ እዬደለሉ  ከካህናት ጋር እየተጋሩ ወያኔ መስመሩን  አንድ በአምስት በማደራጀት መርሆ ዘርግቶ በልማት ባላንባራሶቹ አማካይነት ዘርጥጦ ለመጣል ትልቅ ምሽግ ይዞ  60 ሚሊዮን የሚገመት  ንብረት በመጨረሻ የወያኔ ጦር ሜዳ ይሆናል። ቢያንስ በአቡነ መርቆርዮስ ማለትም በስደደተኛ አባቶች አስመዝግበዉ ቢቆዩ መልካም ነበር። ችግሩ ግን ከወያኔ ጋር በልማት የተቆራኙ ብዙ ሃብታሞች  ስላሉ  ከወያኔ ስዉር ሰንሰለት ነጻ የሚሆኑበት መንግድ እየጠበበ ሳይመጣ አይቀርም፤ በአቋራጭ እግዚአብሔር ከወያኔ እንደሚገላግለን  ግን ሙሉ ተስፋ አለኝ። ማሪያምን ከሆዳሞች ሽያጭ ያድናት። በሉ ሃይማኖታችሁንንና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን መሳሪያችሁ አድርጉ፤ ስደተኛ አባቶቻችሁን አትርሱ፤ አባ መርቆርዮስም አይባርኩን፤ አባ ማትያስምም አንፈልግም እንዲያዉ ከንቱ ምክንያት አልባ ህዝቡን ኦርቶዶክሳዊ ባልሆነ መንገድ አታድክሙት። የግፍ አገዛዝ በቃ በሉ፤ በከንቱ ዳር ዳርና የገለልተኛ ማሃል ሰፋሪነት  በሃይማኖት መሪነታቸዉ ብቻ የተሰቃዩ አባቶችን ከመርሳት ደረጃ አያደርስም።  ለህዝብ መብትና ለቤ/ክ የአስተዳደር ነጻነት ታገሉ፤ የአንድነት መድሃኒታችን የጎጠኛነት መርዝን ይነቀል። እግዚአብሔር ለዕዉነትl ለፍቅር ለቆሙ ሁሉ ዘወትር አይለይምና ለሃይማኖታችሁና ለአገራችሁ ያላችሁን አቋም  ከስጋዊ ኑሮና ከባለጸጋነት  በላይ አድርጉ፤ እግዚአብሄር ሁሌ ከተበደሉ ጎን አይለይማና ሰይጣኑን ወያንን የሚያሸንፍ ሃይል ይስጣችሁ።

መልካ ገና እና የምዕራቡ ጥሩ አመት ያድርግልን

አጥቃዉ ቦጋለ

ወስብሃት ለእግዚአብሔር

Viewing all 8745 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>