Quantcast
Channel: ዘ-ሐበሻ – Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 8745 articles
Browse latest View live

የወቅቱ ጥያቄ ራስን በወታደራዊ አቅም ማጎልበት ነው (ከአይናዲስ ተሰማ)

$
0
0

ethiopian-genocide-on-amharaአማሮች አማራ በመሆናቸው ብቻ በየአካባቢው እየተለቀሙ ሲሳደዱና ሲገደሉ አማራውን እወክለዋለሁ የሚለው ድርጅት ትንፍሽ አለማለቱን ሳስብ ዘወትር ይገርመኛል:: ለአማራው እልቂት መባባስ የብአዴን አመራሮች ምክንያት መሆናቸው ደግሞ ከግርምትም በላይ የሆነ ስሜት ይፈጥራል (አቶ ታምራት ላይኔ በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ተገኝተው ያደረጉትን ንግግር ምሳሌ ማድረግ ይቻላል)::  ከሌሎች ጎሳወች ጋር ተዋልዶና ተመሳስሎ የሚኖረው አማራ በዘሩ ብቻ ሲባረርና ሲገደል የብአዴን አመራሮች የተባረሩት አማሮች ግብር ለመክፈል ያልፈለጉ አጭበርባሪወች እንደሆኑ ሲናገሩ ነበር (አቶ አዲሱ ለገሰ ከኦሮሚያ ክልል ሀብታቸውን ተነጥቀው ስለተባረሩት አማሮች የተናገሩትን በምሳሌነት ማንሳት ይቻላል):: ሕጻን ሽማግሌ ሳይል: በብዙ ሽህ የሚቆጠር አማራ: ለዘመናት ሲኖርበት ከነበረ አካባቢ አንዲት ነገር ሳያንጠለጥል እንዲባረር ሲደረግ: ለዚህ እወክለዋለሁ ለሚለው መከራ ተቀባይ ሕዝብ አቶ አዲሱ ሊሟገትለት ሲገባ “ወንጀል የፈጸመ ስለሆነ መባረሩ አግባብ ነው” የሚል እንድምታ ያለው ንግግር ማሰማቱ ከጉድም ጉድ ያሰኛል:: ወንጀል  የፈጸመ ሰው ሰብአዊ ክብሩ ሳይነካ በህግ አግባብ መጠየቅ እንደሚገባው በህገመንግስቱ ላይ በግልጽ ሰፍሯል:: እንደተባለው አማሮች ወንጀል ፈጽመው ተገኝተው እንኳ ቢሆን ህጉ ላይ በተቀመጠው መንገድ መጠየቅ እንጅ ለዚያ አይነት መከራ እንዲጋለጡ መፈቀድ አልነበረበትም:: በዚያ ላይ አማራው ራሱ ሲያፈናቅሉት ህመሙን በሆዱ ችሎ ሲፈናቀል: የግድያ ወንጀል ሲፈጽሙበትም ድምጹን አጥፍቶ ሞቱን ሲቀበል ማየት አላስችል ቢለኝ የዘመኑን ትውልድ ወቅሸ የሞቱት አርበኛ እናትና አባቶቻችንን ከሞት ልቀሰቅስ “ይድረስ ለነፍጠኞች” ስል የብሶት ግጥም ሞነጫጨርሁ::

 

ግጥሙ የግጥምን መሰረታዊ ባህሪያት የተከተለ ሊሆን እንደማይችል ይገባኛል:: እኔም ለዚያ አልተጨነቅሁም:: በመሰረቱ እኔ የስነጽሁፍም ሆነ የጋዜጠኝነት ትምህርት ወይም ሙያ ያለኝ ሰው አይደለሁም:: የእኔ ፍላጎት በምንም ይሁን በምን የውስጤን እሳት አውጥቶ መተንፈስ: ትውልዱን መጎንተል: መቀስቀስ ነበር:: የጫጫርሁትን ግጥም ለብዙወች ሜዲያወች የላክሁ ቢሆንም ማንም  ቀንጭቦና አስተካክሎ እንኳ መልእክቴን ሊያደርስልኝ የሚፈቅድ ባለመገኘቱ ሀሳቤ መና ቀረ:: ቆይቶ የመጣልኝ ሀሳብ በደብረማርቆስ: በጎንደር እና በወሎ ስም የተመሰረቱ የቡድን ፌስቡኮች (Group) አባል በመሆን ግጥሜን ፖስት ማድረግ ነበር:: ነገር ግን አንዳንድ ቡድኖች ፖስት ያደረግሁትን ግጥም ስላጠፉብኝ ተናድጀ ከሁሉም ቡድኖች ጋር የነበረኝን አባልነት ሰረዝሁ:: በእርግጥ ግጥሙ ቢሉት ቢሉት የማያልቅ: የግጥም አመሰራረት እና ውበት የሌለው በመሆኑ ሜዲያወች ባያወጡት እውነት አላቸው:: ከዚያ በኋላ ባሉት ጊዚያቶች ሌሎች ብዙ ግጥሞች እና አርቲክሎች ልኬ የነበረ ቢሆንም ለንባብ የበቁልኝ ግን በጣም ጥቂቱ ብቻ ናቸው:: አንዳንዶቹ ሜዲያወች ጭራሹኑ ተሳስተው አንድ ጊዜ እንኳ ሊቀበሉኝ አልፈቀዱም:: እንዳልሁት ባለሙያ አይደለሁም:: ነገር ግን ያነሳኋቸው ጭብጦች ጠብታ ቁም ነገር የሌላቸው ፍሬከርስኪ እንዳልነበሩ ይሰማኛል::

 

ጽሁፎቸ በሜዲያ ላይ ለንባብ ሊቀርቡ ያልቻሉት ከሁለት ነገሮች በአንዱ ወይም በሁለቱም ምክንንያት ሊሆን ይችላል ብየ አስባለሁ:: አንደኛው የስነጽሁፍ ለዛ እና ደረጃ ያልጠበቁ በመሆናቸው ሊሆን ይችላል:: ሌላው ደግሞ ድህረገጾች በሚፈልጓቸው መንገዶች ያልተቃኙ ወይም የማይፈልጓቸውን ነገሮች የነኩ በመሆናቸው ሊሆን ይችላል:: እንደ Zehabesha, EmF, Ethiopian review እና ቋጠሮ የመሳሰሉት ድረገጾች የሚያወጧቸውን ጽሁፎች ከራሴ ጽሁፎች ጋር ለማነጻጸር ብዙ ጊዜ ሞክሬአለሁ:: አንዳንድ ጊዜ እኔ ከጻፍሁት ያነሰ መልእክት ያላቸው: ሰዋሰዋዊ አጠቃቀማቸውም ሆነ ስነጽሁፋዊ ውበታቸው እዚህ ግባ የማይባሉ ጽሁፎች በነዚህ ድረገጾች ላይ ወጥተው ሳነብ ለምን የእኔስ? ብየ መጠየቄ አልቀረም:: የሆነው ሆኖ በራሴ ጥረት የደረስሁበት አንድ እውነት የሚመስል ነገር አግኝቻለሁ::

 

ሁሉም በነጻ ሜዲያ ስም የሚታወቁት የሬዲዮ: የቴሌቭዥን እና የህትመት ሜዲያወች ሊያወሩባቸው የሚፈልጓቸው እና እንዲነኩባቸው የማይፈልጓቸው ጉዳዮች እንዳሉ ለመረዳት ችያለሁ:: ተቃዋሚ መነካት የለበትም በሚል ምልከታ የተቃዋሚ ፖለቲካ ድርጅቶችን በተናጠል ወይም በጅምላ ለመተቸት የሚነሳ ግለሰብ ወይም ድርጅት ላይ የህዝብን ትግል ለመግደል እንደተነሳ የወያኔ ተላላኪ አድርገው የሚወነጅሉና የጥቃት ኢላማ እንዲሆን የሚቀሰቅሱ ሀላፊነት የጎደላቸው ሜዲያወች መኖራቸው ሀቅ ነው:: አንዳንዶች የፈለገው የወረደ ጽሁፍ ቢቀርብም የቀረበው ጽሁፍ መንግስትን የሚቃወም እስከሆነ ድረስ ለመቀበል የማያመነቱ ናቸው:: ግንቦት 7ን የሚቃወም ጽሁፍ የሚወዱ ወይም የማይወዱ: ኢሕአፓ እንዲነቀፍ የሚፈልጉ ወይም የማይፈልጉ: ኦነግ በጥሩነቱ ብቻ እንዲነሳ የሚፈልጉ ወይም በመጥፎነቱ ብቻ እንዲነገርለት የሚፈልጉ –  –  – እንዳሉ ተረድቻለሁ:: ከሁለት ቀናት በፊት አቶ ይገርማል የሚባሉ ሰው ከመቶ አመት የቤት ስራወቻችን አንዱ የሆነው ኦነግ በሚል ያቀረቡት ጽሁፍ ቁምነገር ያለው መሆኑን ተረድቸ ወደ ፌስቡኬ ሸር ላደርግ ስል ከድረገጹ ላይ ላገኘው አልቻልሁም: ሰርዘውታል:: የመንግስት መገናኛ ብዙሀንን በአፋኝነት የሚከሱት ነጻ የሚባሉት ሜዲያወች የአቶ ይገርማልን ጽሁፍ ካወጡ በኋላ መልሰው መሰረዛቸው የተለያዩ ሀሳቦች እንዳይንሸራሸሩ እንቅፋት የሚፈጥሩ ማለትም ራሳቸውም አፋኝ መሆናቸውን ያሳያል::

 

ያም ሆነ ይህ ነፍጠኛ ማለት ከስድብ አልፎ የሚያሳፍር: የሚያስጠይቅ እና ለጥቃት የሚያጋልጥ መጠሪያ ተደርጎ ይታሰብበት በነበረበት ወቅት “ይድረስ ለነፍጠኞች” ብየ በፌስቡክ ላይ በማስነበቤ አሁን ላለው በነፍጠኛ አባት እናቶቻችን ታሪክ ለመኩራት እና ብሎም “አዎ ነፍጠኛ ነኝ” ብሎ ለመውጣቱ የራሴ የሆነ እገዛ አድርጌ ይሆን? ብየ አስብ እና ለህዝቤ ትንሽም ቢሆን በጎ ነገር አበርክቻለሁ በማለት ጮቤ እረግጣለሁ:: የአሁኑ የአማራ ወጣቶች በድፍረት አደባባይ ወጥተው መፋለም እንዲችሉ አንድ ምክንያት እንደሆንሁ: ብርታት እንደሰጠሁ አድርጌ አስብና በደስታ እሰክራለሁ:: የሞቱትን  እናትና አባቶቻችንን ቀስቅሸ “ይድረስ ለነፍጠኞች” የሚል ጥሪ በማድረጌ ሙት መንፈሶቻቸው ሰምተውኝ ህዝቡንና ሀገሩን ከጥቃት ለመከላከል ግንባሩን የማያጥፍ ወጣት ይኸው በአይኔ ለማየት በቃሁ::  ለዚህም ፈጣሪየን ከልብ እያመሰገንሁ የሞቱትን ወገኖቸን “ነፍስ ይማር! በሰላም እረፉ!” እላለሁ::

 

ኦነግ ለብዙ ኦነጎች የተከፈለ ቢሆንም ሁሉም ንዑስ ኦነጎች ዞረው ዞረው ያው የኦሮሞን ነጻነት ማለት መገንጠልን የሚደግፉ መሆናቸው የአደባባይ ሚስጥር ነው:: አንዳንዶቹ አሁንም በዚያው  በዱሮው የመገንጠል አቋማቸው ጸንተው የኦሮሚያ ሪፓብሊክን ለመመስረት የሚያልሙ ናቸው:: አንዳንዶቹ ደግሞ ኦሮሞው በኢኮኖሚው: በፖለቲካውም ሆነ በስልጣን እንደህዝቡ ብዛት ተመጣጣኝ ድርሻ እንዲሰጠው እና ራሱን በራሱ እንዲያስተዳድር ለማስቻል የሚታገሉ እንደሆኑ ሲያስመስሉ ይቆዩና ተመልሰው ያንኑ የመገንጠል ጥያቄያቸውን ሲያራግቡ ይገኛሉ:: እነጃዋር የተናገሩት የሽግግር መንግስት እና የመከላከያ ሀይል ምስረታ አላማ የሚነሳው ከዚህ የመገንጠል ፍላጎት ነው:: ጃዋር እና አንድ ፕሮፌሰር BBN ከተባለ ሬዲዮ ጣቢያ ጋር ያደረጉትን ቃለመጠይቅ ተከታትያለሁ:: በዚህ ቃለመጠይቅ ላይ የተገነዘብሁት ነገር ቢኖር “ምንም ልታመጡ አትችሉም” የሚል ድብቅ መልእክት ያለው በሽፍንፍን የቀረበ ሊቀር የማይችል የኦሮሚያ ነጻ መንግሥት ምስረታ ፍላጎት መኖሩን ነው:: ማንም ደገፈውም አልደገፈውም ለውጡ አይቀርም ብሎናል ጃዋር:: የሽግግር መንግስት ስለሚል ነገር አልሰማሁም ብለውናል ፕሮፌሰሩ:: ሌላ አንድ ዶ/ ር ደግሞ እናውቅላችኋለን አትበሉን ብለውናል:: የሚያደርጉት ነገር ከሌሎች ወገኖች ጋር በሚናበብ መልኩ ሳይሆን እነርሱ በሚፈቅዱት መንገድ እንደሚሆን ነው እየነገሩን ያሉት:: በጋራ ግዴታ መታሰር እንደማይፈቅዱ ነው ሊያስገነዝቡን የፈለጉት::

 

የአማራ ልጆች ምን ዝግጅት እያደረጉ እንደሆነ አላውቅም:: አቅራሪ “እዚያ ማዶ ሆኖ ክፉ ሰው ተጣራ እዚህ ማዶ ሆኖ ክፉ ሰው ወይ አለው ጎበዝ ተጠንቀቁ ይህ ነገር ለኛ ነው” ያለው ካለ ነገር አይደለም:: ኦነጎች የኦሮሞ ካርታ አላቸው:: እኔም  የአማራን ካርታ አውጥቸ በልቤ ይዣለሁ:: ሞረሽ: ቤተአማራ: ዳግማዊ  መዐህድ: የአማራ ዴሞክራሲያዊ ሀይልና ሌሎችም ሳያስቡበት አይቀርም ብየ አስባለሁ::

 

ለነገሩ ኦነግን ያተበተው ተቃዋሚ የአንድነት ሀይል የሚባለው ነው:: የኦሮሞ ህዝብ አሁንም ቢሆን ከአማራው ወንድሙ ጎን ተሰልፎ እንደዱሮው ሁሉ ኢትዮጵያን ለመከላከል ወደኋላ የሚል አይደለም:: ለኢትዮጵያ ሲሉ ያላቸውን ነገር ሁሉ አሳልፈው የሰጡ ወላጆቻቸውን አርማ አንስተው ለአንድነቷና ለሉአላዊነቷ የሚሰለፉ ኦሮሞወች ከኦነግ ጀሌወች በእጅጉ የበለጡ መሆኑ እየታወቀ የአንድነት ኃይል ነኝ የሚለው ወገን ህዝቡን ማእከል አድርጎ መስራት ሲገባው ኦነግን ወደመለማመጥ በመውረዱ የ50 አመት ጩጬው ኦነግ ሲገለማምጠን: በትእቢት ሲወራጭብን እያየን እየሰማን ነው:: ኦነግን በሰላ አንደበት እና በበሰለ ጽሁፍ የሚተቹትን አስተዋይ ሰዎች የሚያረክሱ የኦነግ ተከታዮች ሊመጣ የሚችለውን አስከፊ ውጤት አስቀድመው ማየት የተሳናቸው ናቸው:: ኦነግ አደብ ገዝቶ ከሌሎች ኢትዮጵያውያን የፖለቲካ ድርጅቶች ጋር ተሰልፎ ወያኔን ለማስወገድ እና ከወያኔ ውድቀት በኋላም የጋራ የሽግግር መንግስት እንዲመሰርት የሚመክሩትን ሁሉ እያበሻቀጡ እንደሆነ ከሚቀርቡ አስተያየቶች እየተረዳን ነው::

 

ስለመጭው የምንጨነቅ እኛ ብቻ ልንሆን እንደማይገባ ሁሉም እንዲገነዘበው ያስፈልጋል:: እስካሁን የጮህነው ጩኸት ከፍርሀት የመነጨ ሳይሆን ከማስተዋል የመነጨ እንደሆነ ማንም ሊረዳው ይገባል:: ስለዚህ ድንገት አስቸጋሪ ሁኔታ ቢከሰት መደነጋገር እንዳይፈጠር ሲባል አማራው ተጠንቅቆ መጠበቅና ራሱን መከላከል ይኖርበታል ብለን ስለምናምን የተጠናከረ ወታደራዊ ኃይል ማቋቋም እና የምንሞትለት ካርታ ማውጣት ግድ ይለናል:: ይህን ስል መአት ነገር እንደምባል አይጠፋኝም:: የአማራን እና የኦሮሞን አንድነት ለማደናቀፍ እንደተነሳሁ የሚያስቡ የዋሆች ሊኖሩ ይችላሉ:: የወያኔን ዕድሜ ለማስረዘም ቆርጨ የተነሳሁ አድርገው የሚወነጅሉኝ አይጠፉም:: ማንም ያለውን ይበል መሆን ያለበት ግን ይኸው ነው::  አማሮች ወገኖቸ ስጋቴ ይገባቸዋል:: እንደ እስስት የሚለዋወጡ ቡድኖችን አምኖ እጅና እግርን አጣጥፎ ተዘናግቶ መቀመጥ አግባብ አይሆንም:: ይነስም ይብዛም ኦነግ እና ወያኔ የረጅም ጊዜ ፖለቲካዊና ወታደራዊ እውቀትና አደረጃጀት አላቸው:: ሁለቱንም የሚያስተሳስራቸውና የሚያስማማቸው ደግሞ አማራ ጠላት ነው የሚለው አመለካከታቸው ነው:: እኛ ወታደራዊ ኃይል እናቋቁማለን ስንል ምንም ያላጠፉትን አማራ ያልሆኑ ወገኖቻችንን ለመደብደብ አይደለም:: እንዲህ አይነት ትምህርት ከወላጆቻችን አልተማርንም:: በንጹሀን ላይ ግፍ ለመፈጸም የሚያስችል በክፋት የተበከለ ህሊና ኖሮን አያውቅም: ወደፊትም ሊኖረን አይችልም:: ነገር ግን ጠላቶቻችን ናቸሁ የሚሉን: ሞትና ስደታችንን የሚመኙ ቡድኖች እንዳሉ እናውቃለን:: የኢትዮጵያ አንድነት በአንድ ወገን ፍላጎት ብቻ የሚመጣ አይደለም:: ሁሉም ቡድኖች ወደስምምነት መጥተው የጋራ ሀገራችንን ዴሞክራሲያዊት ለማድረግ ፍላጎቱ ካለ የመጀመሪያው ምርጫችን ይሆናል:: ካለበለዚያ ግን ራሳችንን ለመከላከል የሚያስችል አቅም ሊኖረን ግድ ነው::

 

ፈረንጆች might is right የሚሉት አባባል አላቸው:: በአለም ላይ ያለው እውነታም የሚያሳየው ይህንኑ ነው:: ጉልበት ያለው ሰው ማድረግ የሚፈልገውን የማድረግ ያልተጻፈ መብት አለው:: ለምሳሌ አሜሪካ ፓናማን ወርራ የፓናማን ፕሬዚደንት በምርኮ ወስዳ ስታስር ለምን ብሎ የጠየቃት አልነበረም:: የኢራቅን መንግስት የኒዩክሊየር ሀይል በማቋቋም ወንጅላ በአመራሯ ስር የተባበሩት መንግስታትን ጦር አሰልፋ ኢራቅን በሀይል ወርራ ፕሬዚደንት ሳዳም ሁሴንን ይዛ በሞት ስትቀጣ ልክ አይደለም ብሎ የሞገታት:  ከርምጃዋ እንድትቆጠብ ያደረገ አልነበረም:: ኢራቅ እየገነባች ነው ሲባል የነበረው የኒዩክሊየር ጣቢያ ሀሰት ሆኖ ሲገኝ ደፍሮ የወቀሳት እስካሁን በኢራቅ ውስጥ እየታየ ላለው ሁከትና ለሀገሪቱ ውድመት ምክንያት ነሽ ብሎ የጠየቃት የለም:: ብዙ ሽህ ኪሎሜትር ተጉዛ በቬትናም ሕዝብ ላይ ጦርነት ከፍታ ከአንድ ሚሊዮን ሕዝብ በላይ ስትገድል ማንንም ሳትፈራ ነው:: የአሁኑን እስላማዊ አክራሪ ኃይል መሰረት የሆነውን ታሊባን የተባለውን የአሸባሪ ድርጅት በአፍጋኒስታን ስትመሰርት አይሆንም ብሎ ያስቆማት አልነበረም:: በሊቢያ: በሶሪያ: በየመን በሶማሊያ – – –  ላይ ቦንብ እያዘነበች ሕዝብ ስትጨፈጭፍና ንብረት ስታወድም ትክክል ነበረች:: ሌላው ቀርቶ የኛዋ ኢትዮጵያ እንኳ በአቅሟ አልሸባብ ዝቶብኛል ብላ ጦር ሰብቃ ሶማሊያ የገባችው ጉልበት አለኝ ከሚል እብሪት በመነሳት ነው:: ለዚያም ነው Might is right! የሚባለው:: ጉልበት ካለህ ትፈራለህ: ትከበራለህ:: ድሀ ብትሆንም ምንም ማለት አይደለም:: ያለው ካለው ፈቅዶም ይሁን ፈርቶ ያካፍልሀል:: ራስህ የፈለከውን ያህል ተምነህ ብትወስድም ጠያቂ የለህም:: አቅም የሌለህ ደካማ ከሆንህ ግን እጣ ፈንታህ የሚወሰነው በአንተ አይሆንም::ራስን በወታደራዊ አቅም ብቁ አድርጎ መገኘት ሁልጊዜም አስፈላጊ ነው:: ለሕዝባቸው ከሚያስቡት ነፍስ ያላቸው የብአዴን አባላት ጋር በተጠና መንገድ ግንኙነት መፍጠር ይጠቅማል:: ያ ካልሆነ ግን እንደባለፈው ጊዜ ሁሉ ትንሹም ትልቁም እየተነሳ የሚያሳድደንና የሚገድለን መሆናችን አይቀርም::

 

አማራ መሆን እንደወንጀል ተቆጥሮ በተለያዩ ክልሎች በግፍ የተገደሉት ወገኖቸ ከሞታቸው በላይ ነፍስ ከስጋቸው እስክትለይ ድረስ ያዩትን ስቃይ ማስታውስ አንጀትን እሳት ውስጥ እንደወደቀ ላስቲክ በሀዘን ጭምትርትር ያደርጋል:: እያዩ እየሰሙ በእሳት የተቃጠሉት ወገኖቸን ስቃይ ሳስብ የምሆነውን አጣለሁ:: ሳያውቅ በተዳፈነ እሳት ላይ ለአፍታ እግሩን ያሳረፈ ወይም የፈላ ውሀ ተደፍቶበት በዚያች ትንሿ የአፍታ ቃጠሎ የተንሰፈሰፈ ሰው ከነነፍሱ በእሳት እንዲቃጠል የተደረገ ሰብአዊ ፍጡር ነፍሱ እስክታልፍ ድረስ ሊሰማው የሚችለውን ስቃይ ሊያስብ ይከብደዋል:: እንደእኔ በድህነት በባዶ እግሩ እየሄደ ያደገ ሰው እንቅፋት ሲመታው የተሰማውን ጥዝጣዜ ሲያስታውስ ወገኖቻችን በገጀራ ተገዝግዘው ሲታረዱ ያሳለፉትን ስቃይ ለማሰላሰል አቅሙ አይኖረውም:: የራሳቸው ቤት እና ኑሮ የነበራቸው ቤት ያፈራውን ለተቸገረ ሲመጸውቱ የነበሩት ወገኖቸ የነበራቸውን ተነጥቀው ሲባረሩ የሚሰማቸውን ግራ መጋባትና ተስፋ ማጣት ማሰብ አንጀትን በሀዘን ያላውሳል:: ታያላችሁ አይደል አሁን እየሆነ ያለውን? እየተካሄደ ባለው የህዝብ አመጽ የትግራይ ሰዎች ተጎጅ ሊሆኑ ይችላሉ በሚል ጥርጣሬ እነርሱን ከአመጹ አካባቢ ለማሸሽ እስከ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማወጅ የደረሰ ጥንቃቄ ተደርጓል:: የእኛ ወገኖች በየጉራንጉሩ ሲታረዱና ሲሳደዱ ማን ደረሰላቸው? ከእንግዲህ በኋላ ይህ አይነት ሁኔታ እንዲፈጸም መፍቀድ የለብንም:: ራሳችንን መከላከል ከማንችልበት ደረጃ ላይ ከተገኘን በክልሉ የሚኖረውን ሕዝባችንን ሳይቀር አባረው ከኦሮሚያ እየተፈናቀሉ ያሉትን ትግሬወች ሊያሰፍሩበትም ይችላሉ:: ህልውናችንን እና መብታችንን ለማረጋገጥ ነው የመከላከያ ኃይል የሚያስፈልገን:: አሁን የምንገኘው በሽግግር ዋዜማ ላይ ነው:: እንዲህ አይነት ጊዜ ደግሞ ፈታኝ ነው:: የቀዳማዊ ኃ/ሥላሴ ንጉሳዊ የአስተዳደር ስርአት ሲፈርስ በተለያዩ አካባቢወች የሚኖሩ አማሮች ላይ ጥቃት እንደተፈጸመ ከታሪክ እናስታውሳለን:: ሌላው ቀርቶ በወላይታ ሶዶ ይኖሩ የነበሩት አማሮች ላይ ምን እንደደረሰባቸው የሚያውቅ ያውቀዋል:: ደርግ ሲወድቅ የተፈጠረውንስ የማያውቅ ይኖር ይሆን?

ለእኛ ያለነው እኛው ነን!


 ዞኖች ተቀላቀሉ፤ ቀበሌዎች ተጨናነቁ  –ማስተዋል በለጠ (ከአዲስ አበባ)

$
0
0

 

“ሰላም ባይኖርም ሰላም ልበላችሁ” ይላል ያ ኪሩቤል በቀለ የተባለ ወዳጄ፤ እናም ‹ሰላም ለኩልክሙ› ብዬ ዘመነ ዲቁናየን በእግረ መንገድ ላስታውስ፡፡

ሰሞኑን ቀበሌዎች በሰው ብዛት እየተጥለቀለቁ እንደሆነ በቅርብ የማውቃቸው ነግረውኛል፡፡ ቀበሌዎቹ በሰው የሚጨናነቁባቸው ብቸኛ ምክንያትም ትግሬ ወያኔዎች መታወቂያቸው ላይ ያለውን ብሔር ከትግሬነት ወደ ኦሮሞነትና አማራነት ለመለወጥ ነው ተብሏል፡፡

 

Demonstrators chant slogans while flashing the Oromo protest gesture during Irreecha, the thanksgiving festival of the Oromo people, in Bishoftu town, Oromia region, Ethiopia, October 2, 2016. REUTERS/Tiksa Negeri

Demonstrators chant slogans while flashing the Oromo protest gesture during Irreecha, the thanksgiving festival of the Oromo people, in Bishoftu town, Oromia region, Ethiopia, October 2, 2016. REUTERS/Tiksa Negeri

አንድ ከቀበሌ መጣሁ ያለኝ የማይዋሸኝ ትልቅ ሰው – ትልቅ ፈጣሪ ብቻ መሆኑ በታሳቢነት ተይዞልኝ – እንደነገረኝ ከሆነ እጅግ በርካታ ትግሬዎች በሰሞኑ የኦሮሚያና የዐማራ ግርግር ከመደናገጣቸው የተነሣ መታወቂያቸውን ወደሌሎች ዘውጎች እየቀየሩ ነው፡፡ በዚህ የመታወቂያ ለውጥ ሰበብ የአዲስ አበባ ቀበሌና ወረዳ ጽ/ቤቶች ቅጥረ ግቢ ጠጠር ቢወረወር ማረፊያ የለውም ይባላል፡፡

“ፊቱን ነበር እንጂ መጥኖ መደቆስ…” ይባላል፡፡ ቀና ቀናውን ደጋግሞ ማሰብ ቀድሞ ነው፡፡ አንድ ነገር ከሆነ በኋላ መሯሯጥ ብዙም አይጠቅምም፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ መረን የለቀቀ ጠባይን በጊዜው ማረምና ማስተካከል ይገባ ነበር፡፡ በፊት “እዩኝ እዩኝ” ከማለትና ኋላ ላይ አሁን እየታዬ እንዳለው “ደብቁኝ ደብቁኝ” ከማለት አስቀድሞውኑ በትክክለኛ አቅጣጫ መጓዝ ይቻልና ይገባም ነበር፡፡ አሁን በጣም የመሸ ይመስለኛል፡፡ ለ25 ዓመታት እላዩ ላይ ሲጨማለቁበት የከረመ ሕዝብ አሁን ሲብስበትና ሞትና ስደቱ፣ ስቃይና እንግልቱ ሲበዛበት የመከራና የስቃይ ምንጮቹን ሀብትና ንብረት ማቃጠል ይቅርና እነሱ ራሳቸውንም በዘነዘና አናት አናታቸውን ቢጨፈልቃቸው አይፈረድበትም – የደረሰበት ግፍ ወደር የለውምና፡፡ ሕዝቡ ተናግሯል፤”በምታምኑት ይሁንባችሁ ማሩን፣ ድሃም ሆነን በቀያችን እንድንኖር ፍቀዱልን፣ ሀብትና ንብረታችንን ግዴለም ውሰዱት – በሕይወት የመኖር መብታችንን ግን እባካችሁ አክብሩልን” እያለ ግማሽ ምዕተ ዓመት ለሚጠጋ ጊዜ ፈሪና ቦቅቧቋ ተብሎ እስኪሰደብና መሣቂያ መሣለቂያ እስኪሆን ድረስ ተንበርክኮ ወያኔ ትግሬዎችን ለምኗል፤ አስለምኗልም – ስለዚህም በዚህ በአሁን እርምጃው “አይዞህ፤ በርታና ግፋበት! ለነዚህ የሲዖል ትል ወያኔዎችና ደጋፊዎቻቸው ይህም ሲያንሳቸው ነው!” ብሎ ሊያደፋፍር የሚቃጣ ወገን አይኑር እንጂ “ለምን እንዲህ አደረግህ” ብሎ ማንም ሕዝቡን ሊወቅሰው አይገባም፤ እንኳንስ በጨዋ ደንብ እየመረጠ ለሚያወድመው የመዥገሮች ንብረት ከዚህ በላይ ቢሄድም የግፈኞቹ ጥጋብ ያስከተለው መርገምት ስለሆነ ማንም በሕዝ መፍረድ አይችልም – ጎርጉረህ ጎርጉረህ ለምታወጣው ግማት ተጠያቂው አንተ ራስህ እንጂ ሌላ ወገን አይሆንም – በምን ዕዳው? በጊዜው ሰሚ አጣን እንጂ እኛም ብዙ ጩኸናል፡፡ አንጎላቸውን ሞራ የሸፈነባቸው ጥጋበኛ ወንድሞቻችን ይሠሩትን አጥተው ሕዝብና ሀገር ላይ ያን ያህል የበደልና የግፍ ደለል ሲከምሩ መቆየታቸው ምን ሊያስከትል እንደሚችል ለነሱ ቢሰወር ለኛ ግልጽ ነበር – ማንኛውም ጨለማ ሌሊት ሳይነጋ እንደማይቀር የማወቅን ያህል ቁልጭ ብሎ የሚታይ ሃቅ ነበርና፡፡

አሁንም የግፍ ብድሩ መከፈል ተጀመረ እንጂ አላለቀምና እግዜሩ በቀላሉ ይማረን፡፡ ደግሞም አንድ አይደለም 30 ዐዋጅ ቢያውጁ ከላይ የታዘዘን መቅሰፍት ሊያስወግዱት አይችሉም – ብቸኛው የመዳኛ መንገድ የሕዝብን ጥያቄ በአግባቡ መመለስና እውነተኛ ድርድር ማድረግ ነው – ከወያኔ ጋር ድርድር ሊኖር እንደማይችል ግን ነጥብ ይያዝልኝ – እንዲህ የምለው በየዋህነትና ምናልባትም በተዘዋዋሪ አንዳች ዘዴ ካለ ብዬ ነው – ለምሣሌ ለነገብሩ አሥራትና ለነአረጋሽ አዳነ ጉዳዩ ተላልፎ የሚሰጥና በነሱ አማካይነት ምናምን ነገር…፡፡ ከዚያ ውጪ ያለው የኃይልም በሉት ጊዜ ለመግዛት የሚደረግ የማጭበርበር ሥልት ሁሉ ለበለጠ መላላጥና ለሕዝብና ሕዝብ መቃቃር በር ከመክፈት ባለፈ ፋይዳ የለውም – መጽሐፍ ምን አለ? “ኢይድኅን ንጉሥ በብዝኃ ሠራዊቱ” – ንጉሥ በሠራዊቱ ብዛት አይድንም – ሌላስ? “ቦዕ ጊዜ ለኩሉ” – ለሁሉም ጊዜ አለው፡፡ ለዚህ ለዚህማ ቁጥር ሥፍር የሌለው የደርግ ሠራዊትስ ያን ሁሉ ዘመናዊ መሣሪያ ይዞ መች እግር አውጭኝ ይፈረጥጥ ነበር? ቀን አያዘምብልብህ – ካዘነበለ አዘነበለ ነው፤ መመለሻም የለው፡፡ ለማንኛውም በወያኔ የደረሰው ጭቆና ዓለም የማታውቀው እጅግ ከባድ ነበር – የሚደርሰው የዕዳ ክፍያም እንዲሁ ዓለም የማታውቀው እጅግ አሰቃቂ ይሆናልና ይህን የድሃ ምክር የሚሰማ ይስማ!! ሳይቃጠል በቅጠል ከተቻለ ደግ ነው፡፡ አለዚያ በኔና በናንተ ይቅር እንጂ “እንዲህ ጨሶ ጨሶ የነደደ እንደሆን፤ ያመዱ ማፍሰሻ ሥርፋው ወዴት ይሆን” እያለ የጎንደርና የጎጃም ገበሬ እየፎከረ መሆኑን ሹክ ያለኝ ሰው አለና የወደፊት ጉዟችን እሾሃማ ነው፤ እንዲያውም የዚህ ፉከራ የኦሮምኛ ትርጉም በኦሮሞው ገበሬ መሀልም ተስፋፍቶ እንደቀጠለ ሰምቻለሁ፡፡

መታወቂያን በሚመለከት እኔ እንኳን በቅርብ ጊዜ የጻፍኩት አንድ አቤቱታ አለ፡፡ “በመታወቂያ ላይ ብሔራዊ ማንነት ይጻፋል እንጂ ጎሣና ነገድ አይጻፍም፤ እንዲያ ከተደረገ ለዘረኞች ጥቃት ግማሽ ሥራ እንደመሥራትና እነሱን እንደመርዳትም ነውና ዜጎችን በቀላሉ ለጥቃት መዳረግ ነው…” ብዬ አቤት ብያለሁ፡፡ ይሄውና ጊዜው ደረሰ፤ ዕብሪተኞቹ የዘሩትንም ማፈስ ጀመሩ፡፡ ግን ማን ተጎዳ? ማንስ ተጠቀመ? በመሠረቱ በዚህ ሂደት የሚጎዳ እንጂ የሚጠቀም የለም፡፡ በወረት ፍቅር የታወሩ፣ በዘረኝነት ዛር የሚያጎሩ፣ በጎጠኝነት የስሜት ስካር የደነዘዙ ቆሻሻ ሰዎች በተከሉብን የብሔር ፖለቲካ ምክንያት እየተላለቅን ነው፤ አሁን ከመሸ በኋላ መታወቂያ ቢቀየር አንደበት አይለወጥም፤ መታወቂያ ወረቀት ቢቀየር እውነት አትሰረዝምና ማንም ቢሆን ዘርቶ ካሳደገው ጌሾና አርሞ ኮትኩቶ ለመኸር ካበቃው እንክርዳድ የተዘለለ ጠላ መቃመሱ አይቀርም፡፡ ወዮ ለምሥኪን ዜጎች! ወዮ ምንም ጥቅም ሳይደርሳቸው መከራና ፍዳው በስማቸውና በዘውጋቸው ምክንያት ለሚደርስባቸው! ለኢትዮጵያ ወዮ በሉ ወገኖቼ፡፡

በልማድ ዞን ዘጠኝ  ይባል የነበረው የብዙዎቻችን ትልቁ እሥር ቤት ከትናንትናው የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ በኋላ ወደ ስምንቱ ዞኖች ተቀላቀለ፡፡ በቃሊቲው ዘብጥያ ስምንት ዞኖች እንዳሉና እኛ ከጠባቦቹ እሥር ቤች ውጪ የምንኖረው ዜጎች በዘጠንኛው ዞን መመደባችን የሚታወስ ነው – እንደቀልድ ግን እውነት የሆነ እውነት፡፡ አሁን ግን ሁላችንም እኩል የምንሆንበት ሁኔታ ተፈጥሯል፡፡ ይህም ከአሁን በኋላ እስካሁን ጭል ጭል ትል የነበረችው በአንጻራዊ አነጋገር እንደመልካም አጋጣሚ የምትጠቀስ ትንሽዬ በነፃነት የመንቀሰቅ መብት በዚህ ዐዋጅ መሠረት ድራሽዋ ጠፍቷል፡፡ ከእስካሁኑ በከፋ ሁኔታ የምንገደልበት፣ የምንሰቃይበት፣ የምንታሰርበት፣ የምንበረበርበት፣ እንደዐይጥ በየተገኘንበት ሥፍራ የምንጨፈጨፍበት፣ ያለችን ሀብትና ንብረት በጠራራ ፀሐይ የምትዘረፍበት … አዲስ ዐዋጅ ታውጆ ለተግባራዊነቱ አጋዚዎች ነቅተው የሚጠባበቁበት ጊዜ ላይ እንገኛለን፡፡

ብቻ ለማንኛውም እግዚአብሔር ይሁነን፡፡ ኢትዮጵያዊቷ አርማጌዴዎን ሰተት ብላ እየመጣች ነው፡፡ ሀገርና ሕዝብን በገንዘብ የምትለውጡ ሁሉ ወዮላችሁ! ለእውነት ያልቆማችሁ ወገኖች ሁሉ የምትበጠሩበት፣ ያጠራቀማችሁትን ገንዘብ የማትበሉበት የመከራ ዘመን እየመጣ ነው፡፡ አስታውሱ – ይሁዳ በዘመኑ አንቱ የተባለ ትልቅ ክፍያ – 30 ዲናር – ከክርስቶስ ጠላቶች ከጻፎች ፈሪሣውያንና ሰዱቃውን ተቀብሎ ጌታውን በመሳም አሳልፎ ሸጠ፡፡ ኋላ ላይ ግን ተፀፀተና ከገንዘቡ አምስት ሣንቲም እንኳን ሳያጎድል ራሱን ሰቅሎ ገደለ፡፡ ያም ገንዘብ በአይሁዶች እጅ ገባና መሬት ተገዛበት – የደም መሬት ተባለ – አኬልዳማ! አለቀ፡፡ ተበልቶ ዕዳሪ፣ ተጠጥቶ ሽንት ለሚሆን ምድራዊ ሀብት ብለን ዘላለማዊት የሆነች ነባቢት ነፍስን፣ በአርአያ ሥላሤ የተገነባ ተክለ ሰውነትን አለጊዜው ብናጠፋ ወይም ለመጥፋቱ ምክንያት ብንሆን ጌታ በቀላሉ የሚለቀን ወይም ሂሳባችንን ሳናወራርድ እንዲሁ የሚምረን እንዳይመስለን፡፡ የጌታ መሐሪነት የማይቀጣጠቡት ሆኖ ነገር ግን የእጃችንን የማግኘቱን ጉዳይ ማናችንም ልንዘነጋ አይገባም፡፡ ጌታ ሌላ ምን ሥራ አለው? ሥራው ይሄው ነው – መፍረድ፡፡

ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያውንን በመሸጥ በሀብት የከበራች አሁኑኑ ንስሃ ግቡና ወደሕዝብ ተመለሱ፡፡ ይህችን ጠባብ ዘመን የሚያልፍ እጅግ ጥቂት ሰው ነው – ያም የታደለና ከወንጀልና ከክፉ ሥራ ራሱን የገታ ነው፡፡ ወደ ሆድ ወርዶ የመሸገ ጭንቅላት በአስቸኳይ ወደቦታው ይመለስ – የሰማ ያሰማ፡፡ ይህን መልእክት በቻላችሁት መንገድ ሁሉ ለሁሉም አዳርሱልኝ፡፡ ይህ መልእክቴ ራዕይ ወይም ንግርትና ሟርት ወይም ትንቢት አይደለም – ማንም የዋህ ልቦና ያለው መሬት ላይ በጉልኅ ቀለማት ተጽፎ ሊያነበው የሚችል ግልጽ አውነት ነው፡፡ አጉሊ መነጽር ሳያስፈልገን በግልጽ በምናየው አደጋ መጠቃት የለብንምና ለሁላችንም አስተዋይ ልቦና ይስጠን፡፡

አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ:- የወያኔ ሰራዊት ቀኝ ሁዋላ ወደ ደደቢት –ታሪኩ አባዳማ

$
0
0

ታሪኩ አባዳማ መስከረም 2009

 

hailemariam_desalgn-6-satenaw-newsህወሀት ተልዕኮው በከፊል ሰምሯል ፤ ለብሔር ብሔረሰቦች መብት እስከ መገንጠል ቆሜያለሁ ብሎ ነበር ፣ ዲሞክረሲ ሳይሽራረፍ አረጋግጣለሁ ፣ ሰብአዊ መብት አሰፍናለሁ ብሎ ነበር ፣ ያለፍርድ አንድም ዜጋ ህይወቱን ቀርቶ መታሰር አይደርስበትም ብሎ ነበር ፣ ከጎረቤት አገሮች ጋር በማይናወጥ ሰላም እንኖራለን ብሎም ነበር… ከፖለቲካ ስርአት ምህዳር እና ሰማይ በታች ሁሉንም በጎ ነገሮች በኔ አገዛዝ ስር ትጎናፀፋላችሁ ሲል ቃል ገብቶ ነበር። ቃሉን በሰነድ ላይ አስፍሮ ህገ መንግስት አድርጎ – እሰከዚህ ድረስ ተጉዞ ነበር።

 

ራዕዩ ቃል ፣ ቃሉም ሰነድ ሆኖ ነበር… በቃ ፣ ከዚያ ማለፍ አልቻለም። ሰነዱ ሳይነበብ ብል በላው ፣ ምስጥ መዘመዘው ፣ አረም ዋጠው። ቃሉ ስጋ ወ ደም ሳይዋሀድ ጨነገፈ… በመጨረሻም እነሆ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አወጀ። የተባባሰ ግድያ አዋጅ ፣ የላቀ ጅምላ መብት ጥሰት አዋጅ ፣ የጫካ አዋጅ ፣ የአራዊት አዋጅ ፣ የደደቢት አዋጅ አወጀ። ህወሀት ከሀያ አምስት አመታት የግፍ አገዛዝ በሁዋላ ቀኝ ሁዋላ ወደ ደደቢት አለ ፤ ጫካውን ናፈቀ። ተጠያቂነት እና ግልፅነት የማያውቀው የደደቢት ፖለቲካ ህይወት እጅጉን ናፈቀው።

 

መጀመሪያ ያኔ ወደ ደደቢት ሲጓዝ የህዝብ ብሶት ሰንቆ ለጋ ወጣት ሳለ የተመኘውን ሊከውን ነበር – ይብዛም ይነስ ብሩህ አይምሮ ፣ ያልተልከሰከሰ መንፈስ እና ምኞት ነበረው። አሁን ወደ ደደቢት ለመጓዝ የተነሳው ደግሞ በህዝብ ልጆች ደም የጨቀየ እጆቹን ፣ በሙስና የበከተ ህሊናውን ፣ በውሸት እና ቅጥፈት የተባ ምላሱን አንዘላዝሎ ፣ ታሪክ ይቅር የማይለው ፣ ትውልድ አሳፋሪ ታሪኩን አንግቦ ነው። ህወሀት ቀኝ ሁዋላ ወደ ደደቢት አለ – አስቸኳይ ጊዜ አወጀ። ገድለው በህግ የማይጠየቁበት ፣ ዘርፈው የማይጠግቡበት ፣ ባሻቸው ውለው የሚያድሩበት ደደቢት ናፈቀው። ወንድም ወንድሙን ገድሎ የሚፎክርበት ፣ ሀውልት የሚገትርበት ፤ ድልድይ አፍርሶ ፣ ባንክ ዘርፎ ፣ ድሀ አስለቅሶ እለት ጉርሱን ሳይቀር ቀምቶ ወደሚያድርበት ደደቢት ቀኝ ሁዋላ ዙር አለ – አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አወጀ። ህወሀት እንደገና ኢትዮጵያ ለምኔ አለ ፣ ኢትዮጵያዊ ገድሎ ፣ ክብሯን አዋርዶ ፣ ባንዲራዋን እንደ ጨርቅ በሶ እየቋጠረ ወደማይጠየቅበት ደደቢት ፊቱን አዞረ።

 

ትናንት በቃሉ መሰረት የሰጣቸውን ሰነድ የተማመኑ ፣ ተማምነውም መብታቸውን የጠየቁ አሸባሪ ተብለው አደባባይ በጥይት እሩምታ ታጨዱ ፣ በየወህኒው ታጎሩ ፣ ተሰደዱ። ያልተሸራረፈው ዲሞክረሲ ቀርቶ መሰረታዊ እና ተፈጥሯዊ መብታችን ይከበር ያሉ በወንጀል ተከሰው ወህኒ ተወረወሩ። በታጎሩበት ወህኒ እሳት ነደደባቸው። እሱም አልበቃ ብሎ ዛሬ ለሌላ ጅምላ ፍጅት አዋጅ ታወጀባቸው – አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ።

 

ህወሀት ትግራይን ነፃ ለማውጣት ተልሞ ድፍን ኢትዮጵያን ተቆጣጥሯል – ህዝቧን በከፋፍለህ ግዛ መርህ በጎጥ ሸንሽኖ አንድነቷን አናግቷል። አንድነቱ በተናጋ እና በተከፋፈለ ህዝብ ትከሻ ላይ ተደላድሎ እጅግ መጠነ ሰፊ የሆነ ሀብት መዝብሮ ቢጠሩት የማይሰማ ቱጃር ሆኗል። በጎጥ የከፋፈለውን ህዝብ በወረፋ አንዱን ዛሬ ሌላውን ነገ እየነጠለ ሲገድል ፣ ወህኒ ሲያግዝ ፣ ለስደት ሲዳርግ ፣ ንብረት ሲቀማ ሀያ አምስት አመታት አስቆጥሯል።

 

ግን ዛሬ ህዝብ በቃ አለ – አለም ይህን ጅምላ ፍጅት መርምሮ ተጠያቂውን ለፍርድ ማቅረብ ግድ ይላል ሲል ሰምቶ ህወሀት ደነበረ ፣ ፊቱን ወደ ደደቢት አዞረ። አንዳችም ተጠያቂነት ወይንም ግልፅነት ወደሌለበት ወደ ደደቢት አለም ለመጓዝ ተጣደፈ። ኢትዮጵያን በታትኜ ፣ እንደ ሩዋንዳ የዘር ፍጅት አቀጣጥዬ ደደቢት ገባለሁ አለ። ይህም አይሆንም ሲል ህዝብ አንድነቱን አጥብቆ ከዳር እስከ ዳር ተሰለፈ – ህወሀት ግን አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አወጀ – ደደቢትን ከነ አተላው እግታችሁዋለሁ አለ፤ ህዝብን ምን ያህል እንደ ናቀ ለማሳየት አዋጅ አወጀ። የአንዲት አገር ልጆችን በጎጥ ሸንሽኖ ፣ በክልል በረት አጉሮ እንኳ መግዛት ተሳነው።

 

የትግራይን ሪፐብሊክ ለማወጅ የረቀቀው ሰነድ ከተቀበረት ዋሻ አቧራው ተራግፎ ወደ አደባባይ ብቅ እያለ ነው። ወያኔ/ህወሀት ‘በብረት አስገብረን ፣ ደም አፍሰን ፣ እንደ ገል ቀጥቅጠን እንደ ብረት አቅልጠን መግዛት ካልቻልን እናንተን በታትነን እኛ ሪፐብሊካችንን እናውጃለን’ በሚል እየተጋበዘ ቆይቷል። ህዝቡ አንተ እንደፍጥርጥርህ ለእኛ ግን አንድነታችን ፣ ሰብአዊ መብታችን ዋስትናችን ነው በሚል ፅኑ ተቃውሞ ማድረጉን ቀጠለ። ህወሀት ደደቢት ላይ ሲያደርግ እንደ ነበረው ጭፍን ጥላቻን በህዝብ ለመርጨት ሲል ሀውልት እስከ ማቆም ደረሰ። ህዝብ ግን ህወሀት ሰራሽ የሆነ አንዳችም ነገር እንደማይበጀው ይፋ አደረገ። Down down woyane እያለ መልካው እስኪናጋ ድረስ አስተጋባ። ህወሀት ግን ፊቱን ወደ ደደቢት አዞረ ፣ ተጠያቂነት ፣ ግልፅነት የሌለበትን ስርአት ናፈቀ – አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አወጀ።

 

አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ይፋ ሆኗል – የደደቢት ስርዓት በመላው አገር በይፋ ይረጋገጣል ብለዋል። ከቶውንም ህግ ባልነበረበት አገር ፣ ስርአት ባልተጠበቀበት ምድር አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የሚያመጣው ምን አዲስ ነገር አለ? እስከ ዛሬ እንደ ጅረት ስላፈሰሱት ደም ፤ እስከ ዛሬ ከአፅመ ርስቱ ስላፈናቀሉት ዜጋ ፤ እስከ ዛሬ ህልውናውን ፣ ስብእናውን ክደው ስላዋረዱት ህዝብ ጉዳይ መልስ እየጠየቅን እንጂ መቸ ሌላ ዙር ፍጅት ጠየቅን።

 

ሳይውል ሳያድር ለጥያቄአችን መልስ እንፈልጋለን። እስከ ደደቢት ድረስ እናንተን የምንሸኝበት አቅም ፣ ዝግጅትም ሆነ ፍላጎት የለንም ፤ አስቸኳይ ጊዜ አዋጃችሁን የምንሸከምበት ዕዳ ፣ በዚያም የምንገዛበት ትከሻ የለንም። ደደቢትን ወደ እኛ እንዳመጣችሁ ሁሉ መልሳችሁ እንድትረከቡ ህዝብ ድምፁን ከፍ አድርጎ ይጮሀል። Down down woyane ይላል።

ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ 2 ህንጻዎችን ማን አቃጠላቸው? –አብዱረህማን ሀበሸ

$
0
0

debremarkos-university-satenaw-newsበዚህ ተግባር ላይ የተሰማሩ የወያኔ ተላላኪዎች አሉ። እስር ቤቶችን እያቃጠሉ እስረኞችን እንደ በቆሎ ሲጠብሱ ነበር። አሁንም ይህንኑ ተግባር በዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ማደሪያ ላይ ፈጽመውታል። በእሳቱ የተጎዳ ተማሪ እንደሌለ ታውቋል። ሆኖም ግን አሸባሪዎች ህንጻችሁን አቃጠሉላችሁ በማለት የከተማውን ህዝብ ከወያኔ ጋር እንዲወግኑ ለማድረግ ሆን ተብሎ ታቅዶ የተደረገ ነው።

በተማሪዎች ለማሳበብ ነው መስከረም 30 የተመረጠው። በዚህ ቀን ዩኒቨርሲቲው ነባር ተማሪዎችን ተቀብሏል። እነዚህ ተማሪዎች በቁጥር እጅግ ጥቂት ናቸው። የሚገርመው ነገር ከሩቅ ቦታ መጥተው በደከሙበት ሰአት ይህን ያደርጋሉ ብሎ መገመት ይከብዳል። ስለዚህ ወያኔ ተቋማትን የማቃጠል እቅዱን አጠናክሮ ቀጥሏል።

ስለዚህ ተማሪዎች ጥንቃቄ አድርጉ። በተለይ ወደተቃጠሉበት አካባቢዎች አትጠጉ። እሳት እናጠፋለን ብላችሁ በየዋህነት አትቅረቡ። #ምክንያቱ_አልታወቀም የተባለው ለዚህ ነው። ሆን ተብሎ ታቅዶ የተፈጸመ ነው።

 

የአዲስ አበባው ደህንነት ቢሮ ተዘረፈ።ሕወሓት በመጨረሻው ሰዓት ማሟጠጥ ይዛለች።(ምንሊክ ሳልሳዊ)

$
0
0

Getachew-Assefaአዲስ አበባ ከኣፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን ጀርባ በቅርብ ርቀት ከሚገኘው የደህንነት ቢሮ ውስጥ 14 ሚሊዮን ዶላር መዘረፉን የውስጥ ኣዋቂ ምንጮች ተናግረዋል፤ ምንጮቹ እንዳሉት ላለፉት ሶስት ኣመታት ከኣየር መንገድ ከፖሊስ ኢግዚቢት እንዲሁም ከኮንትሮባንድ ተይዘው በኣዲስ ኣበባ ደህንነት ቢሮ የተከማቹ ዶላሮችን የዘረፈው ኣካል ማን እንደሆነ ኣልታወቀም ሲሉ ምንጮቹ ለምንሊክ ሳልሳዊ ገልጸዋል።

በኦሮሚያና ኣማራ ክልል ተቃውሞ ከተነሳ ጀምሮ ለስብሰባዎችና ለጉዳይ በሚል ሃያ ኣራት ሰኣት የሕወሓት ባለስልጣናት እንደሚመላለሱ ሲታወቅ እነዚህ ባለስልጣናት በሚሰበሰቡበት ለሊት በኣከባቢው ጥበቃ የሚያደርጉት ልዩ የደህንነት ሃይሎች ሲሆኑ ሌሎች ወደ ቢሮው እንዳይደርሱ እንደሚደረግ እና እረፍት እንደሚሰጣቸው ታውቋል ሲሉ ምንጮቹ ለምንሊክ ሳልሳዊ ተናግረዋል።

ከዚህ ቀደም ይኸው ቢሮ መዘረፉ ሲታወቅ የሕወሓት የደህንነት ባለስልጣናት በየግላቸው የሚመሯቸው ማፊያ ቡድኖን ያሏቸው ሲሆን ምናልባት እንደባለፈው ዘረፋው በቡድኖቹ የጋራ ቅንጅት ተተግብሮ ይሆናል ሲሉ ምንጮቹ ኣክለው ሲገልጹ በባለፈው የቤተ መንግስቱ ተኩስ በሕወሓት ጄኔራሎች ተገደለ የተባለው የደህንነት ሚኒስትሩ በሕይወት ያለ ሲሆን የማፊያ ስራውን በመስራት ላይ ሲገኝ የደህንነት ሚኒስትሩ ተገደለ የሚለው የሃሰት ዜና በደህንነቶች የተፈበረከ ውዥንብር መሆኑን ምንጮቹ ገልጸዋል።

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ –ምናባዊው አጥር ለምን አስፈለገ –መላኩ ወልደስላሴ

$
0
0

stateofeme-1እንደሚታወቀው የብሄራዊ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የሚታወጀው በህዝብ ህይወት ጤናና ደህንነት ላይ የተጋረጠ አደጋ ሲያጋጥምና ያንንም በተለመደው በመደበኛው የህግ ማስከበር ስርአት መቆጣጠር አይቻልም ተብሎ ሲታመን ነው።ከዚህ በፊት ያልነበረው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ከተለመደው የመደበኛው የአስተዳደር ቅኝት በተለየ መልኩ እንዲተገበሩ የሚደነግጋቸው ጉዳዮችን ይዘረዝራል።ልብ ማለት የሚገባን ከተለመደው የመደበኛው የአስተዳደር ቅኝት በተለየ የሚለውን ቃል ሲሆን ምንም አዲስ ለውጥ የማያመጣ ከሆነ አዋጁ ትርጉም  አይኖረውም።

ህንዶች ካስተናዷቸው የአስቸካይ ጊዜ አዋጆች አንዱ ከጁን 1975 እስከ ማርች 1977 ለሃያ አንድ ወራት የቆየው በጠቅላይ ሚንስትሯ ወይዘሮ ኢንድራ ጋንዲ የተደነገገው በይዘቱ ለየት ያለ ነበር።ያም አዋጁ የወጣው ህንድ በራሷ የውስጥ የፖለቲካ ቀውስ በተነሳ ችግር ውስጥ በነበረችበት ጊዜ መታወጁ ነው።የኢንድራ ጋንዲም የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የሚከተሉት አበይት ይዘቶች ነበሩት።

  1. ነፃው ፕሬስ ላይ እቀባ /ሲንሰርሺፕ ማድረግ
  2. የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎችን ማሰር
  3. የክልሎችና የፓርላም ምርጫዎች ወደፊት ላልተወሰነ ጊዜ ማሸጋገር
  4. አዳዲስ ህጎች ማውጣት
  5. መሃይምነትንና ድህነትን ለመዋጋት ብሎም የሃገሪቱን የእርሻና የኢንዱስትሪ ምርት ለማሳደግ ባለ ሃያ ነጥብ ፕሮግራም መንደፍ
  6. ሀገሪቱን በአዋጅ መምራት

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ከመውጣቱ በፊት ህንድ ውስጣ ገደብ የለሽ ነፃ ፕሬስ ነበረ፣ፍርድ ቤት ከፖለቲካ ተፅእኖ ነፃ ነበር፣ታዋቂ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች ቀርቶ ማንም ሰው ከህግ ውጪ አይታሰርም አይንገላታም ነበር፣በሁሉም ደረጃ ያሉ የክፍላተ ሃገራትና የማእከላዊ መንግስት የፓርላማና ሌሎች ምርጫዎች ጊዜያቸውን ጠብቀው ትክክለኛና ፍትሃዊ በሆነ መልኩ ይካሄዱ ነበር፣ከህግ አውጪው ክፍል ውጪ ህጎች በዘፈቀደ አይወጡም ነበርና በአስቸኳዩ አዋጅ ምክንያት ኢንድራ ጋንዲ ከፍተኛ ትችትና ተቃውሞ የደረሰባት አዋጁ በፊት የነበሩ መብቶችን በማገዱ ነበር።

ወደሀገራችን ሁኔታ ስንመለሰ የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሆኑት አቶ ጌታቸው አምባዬ እንደገለፁት በህገ መንግስቱ አንቀፅ 93 መሰረት ህገ መንግስቱ አደጋ ላይ ሲወድቅ የሚለውን በመጥቀስ በተለመደው የህግ ማስከበር ስርአት የተፈጠረውን አደጋ ለመከላከልና ሁኔታውን ለመቆጣጠር አዋጁ መውጣቱንና ይህም ህገ መንግስታዊ መሰረት እንዳለው በመግለፅ ጀምረዋል።ጠቅላይ አቃቤ ህጉ እንደገለፁት በንኡስ እንቀፅ ሁለት መሰረት ዝርዝር ስልጣኖች ያሉት አስፈፃሚ ኮማንድ ፖስት መፈጠሩን ሲያስረዱ አያይዘውም የገለፁት የአዋጁ ይዘት በሚከተለው ሊጠቃለል ይችላል።

ወንጀሎች

  1. ማንኛውም ሁከት ብጥብጥና በህዝቦች መሃከል መጠራጠርና መቃቃርን የሚፈጥር ይፋዊ ይሁን የድብቅ ቅስቀሳ ማድረግ።

 

  1. ፅሁፍ ማዘጋጀት ማተምና ማሰራጨት ትእይንት ማሳየት በምልክት መግለፅ ወይም መልእክትን በማናቸውም መንገድ ለህዝብ ይፋ ማድረግ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ተግባራዊ በሚሆንባቸውና ለህዝብ ይፋ በተደረጉ ቦታዎች ላይ እነዚህን መፈፀም ።

የኮማንድ ፖስቱ ስልጣን

  1. ማናቸውንም የመገናኛ ዘዴዎች እንዲዘጉ ማድረግ መቻል።
  2. ስብሰባና ሰልፍ የማድረግ ጉዳዮችን ሊያግድ ይችላል መደራጀትንና በቡድን መንቀሳቀስን ሊከለክል የሚችልበት ሁኔታም በአዋጅ ውስጥ ተቀምጧል
  3. የህዝብን ሰላምና ፅጥታ በማደፍረስ ላይ ተግባር ላይ ተሳትፏል ተብሎ በሚጠረጠር ማንኛውም ሰው አለፍርድ ቤት ትእዛዝ መያዝ መቻሉ።
  4. ወንጀል የተፈፀመባቸው ወይም ሊፈፀምባቸው የሚችሉ እቃዎችን ለመያዝ ሲባል ማናቸውንም ቤት የብርበራ ትእዛዝ ሳይወጣ መበርበር ማንንም ሰው ማስቆምና መፈተሽ መቻሉ
  5. የሰአት እላፊ ተፈፃሚ የሚሆንበትን ቦታ ይወስናል ተግባሪዊ የሚሆንባቸውን ቦታዎች ተግባራዊ ያደርጋል

አስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የሚያስከትላቸው ቅጣቶች

አቃቤ ህጉ አዋጁ ተግባራዊ የሚሆንበት ጊዜ  ስድስት ወር እንደሆነና እንደሁኔታው ሊያጥር ወይም ሊረዝም መቻሉን ገልፀው ማንኛውም ሰው ማንኛውም ዜጋ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የተቀመጡ እርምጃዎችን የማክበርና የመተባበር ግዴታውን ካልተወጣ የሚከተሉት ቅጣቶች እንደሚከተሉ ገልፀዋል።

  1. የኮማንድ ፖስቱን ወይም የህግ አስፈፃሚዎችን አለመተባበረ እስከ ሶስት አመት የእስር ቅጣት እንደሚያስከትል

 

  1. አዋጁን በቀጥታ ተላልፎ መገኘት እስከ ስድስት ወር እስር የሚያስቀጣ መሆኑን አስረድተዋል።

 

ከህንድ በተለየ ሁኔታ አዋጁን አነጋጋሪ ያደረገው ከህግ ውጪ ህዝብ በአደባባይ በጥይት እየተቆላ ባለበት ሁኔታ ልክ እስካሁን የተደረገው የህዝብ ጭፍጨፋ በህገ መንግስቱና በፍርድ ቤት ትእዛዝ መሰረት እንደተከናወነ በማስመሰል ካሁን በሁዋላ  የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ታውጇል መባሉ ነው።ህወሀት የሚሊቴሪ የፖለቲካና የኢኮኖሚ የበላይነቱን ያሰፈነው ከፋፍለህ ግዛ የሚባለውን የአስተዳደር ዘይቤ እየተጠቀመ በመሁኑ ነው እይተባለ፣ ለማስረጃም የመንግስት የኮሚኒኬሽን ሚንስትር የሆኑት አቶ ጌታቸው ረዳ ራሳቸው እሳትና ጭድ እያሉ የሃገሪቱን ሁለት አውራ ብሄረሰቦች የሚያፋጅ ሃሳብ በአደባባይ እየተናገሩ ማንኛውም ሁከት ብጥብጥና በህዝቦች መሃከል መጠራጠርና መቃቃርን የሚፈጥር ይፋዊ ይሁን የድብቅ ቅስቀሳ ማድረግን ወንጀል ነው ብሎ እራሱ መንግስት አዋጅ ሲያወጣ እነ አቶ ጌታቸው ምን ቅጣት ደረሰባቸው ብሎ መጠየቅ ተገቢ ነው።እንደምንሰማው ከሆነ ኦህዴድ እራሱ ሌላውን በሄረሰብ ከኦሮሞ ብሄርሰብ ማጣላቱን ተያይዞታል እየተባለ ነው።

ፅሁፍ ማዘጋጀት ማተምና ማሰራጨት ትእይንት ማሳየት በምልክት መግለፅ ወይም መልእክትን በማናቸውም መንገድ ለህዝብ ይፋ ማድረግ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ካሁን በሁዋላ የተከለከለ ነው ማለት እስካሁንስ መቼ ተፈቅዶና ያስብላል።በተለያዩ የኦሮምያና የአማራ አካባቢዎች ኢትዮጵያውያን የተተኮሰባቸው በዚሁ አይደለም እንዴ።እስካሁን የማይከለከል ተግባር ከነበረ ይህን ተላልፈው የግድያ፣የድብደባና ፣የማሰር ወንጀል የፈፀሙ መች ለፍርድ ቀረቡ ብሎ መጠየቅም አግባብ አለው።ይህ ማለት ግን አስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ምንም ትርጉም የሌለው ነው ማለት ሳይሆን የሚከተሉት እንደምታዎችን አሉት።

  1. ሆነ ብሎ የህዝብን ጥያቄ ጠምዝዞ መረዳት ህወሀት/ ኢህአድግ እራሱ ያወጣውን ህገ መንግስት አያከብርም ሲባል የህገ መንግስት ጥሰቱ የሚጀምረው ገዢው ፓርቲ ከህጉ ውጪ ፓርላማውን መቶ በመቶ መቆጣጠሩ እንጂ ግድያዎችን ፓርላማው በመጀመሪያ ያፅድቅ ወይንም አያፅድቅ አይደለም። ፓርላማውና ህወሀት/ ኢህአዴግ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገፅታዎች ናቸው። መልሱ ያለው የፓርላምውን ህዝባዊነት ማሳየት ላይ ነው። ማንኛውንም የመንግስት እርምጃ የፓርቲው የአንድ ሳንቲም ገፅታ በሆነው ፓርላማ በመፅደቁ ወይም አለመፅደቁ ለህዝብ ብዙ ትርጉም የለውም።ህዝብ እያለ ያለው ህወሀት እጁን ይሰበስብ ፣አንድ ሰው አንድ ድምፅ የሚለው ዲሞክራሲያዊ መርህ ይተግበር ፣የህግ የበላይነት ይረጋገጥ ሲሆን የዚህ ማሳያው በመጀመርያ አሁን ያለው ፓርላማ የኢትዮጲያውያንን የአመለካከት ብዝሃነት የማያነፀባርቅ መሆኑን መዋጥና የህዝብ የተለያዩ አመለካከቶች ውክልና ያለው ፓርላማ እንዲኖር በአስቸኳይ መንቀሳቀስ ነው። የጀርመኗ ወሮ መርክል ከፓርላማው ፊት ለፊት ቀርበው መነጋገር እምቢተኛ የሆኑት በዚሁ ጉዳይ ነው።

 

  1. ሃላፊነትን ማውረድ ባይቻል ተጠያቂነትን ማስፋት.እየተመለከትን ያለነው እራሳቸውን ከህግ በላይ ያደረጉ የህወሀት ባለስልጣናት ሁሉን እንደፈለጉ ካቦኩና ጋግረው ካሳረሩ በህዋላ የራሳችሁን ህገ መንግስት አታከበሩም የሚለው በጆሯቸው እልፍ ሲል ታድያ ምን ችግር አለው ፓርላማው የኛ ሎሌ አይደል እንዴ የሚል ተራ ብልጠት ውስጥ ሲገቡ ነው።ህሳቤው የተሰራ ወንጀልን ለማስተሰረይ ፕርላማውን እንደ ፀበል ለመጠቀም የተደረገ ሙከራ ነው። ሀምሳ ሎሚ ለሃምሳ ሰው የሚል አባባል አለ ግን ሃምሳ ወንጀል ለሃምሳ ሰው የሚለውን እስካሁን አልሰማሁም።ፓርላማው የህዝብ መጠቃት ጥቃቱ የሆነ ፣መንግስት የወሰደውን የሃይል እርምጃ ህጋዊነት የሚሞግት ፣መንግስትን ጥፋተኛ ሆኖ ካገኘ ጠቅላይ ሚንስትሩንና ካቢኔውን ሊሽርና ለፍርድ ሊያቀርብ የሚችል የአመለካከት ብዝሀነት ያለው ጥርሳማ የሀገሪቱ ከፍተኛ ስልጣን መሆኑ ሳይረጋገጥ ዝም ብሎ እጅ ማጨብጨብ ለተፈፀመው የህዝብ ፍጅት ተጠያቂነት እነደእሳት እራት ዘሎ በመግባት እራሱን አየተሰራ ላለው ወንጀል ተጠያቂ አድርጓል።በሃገሪቱ በተለያዩ ቦታዎችም የግድያ ትእዛዞችን ያስተላለፉት ገዳዮች አሁን ሙሉ የፓርላማውን አባላት ጭምር ለወንጀሉ ተጠያቂ በማድረጋቸው የሰሩትና የሚጠየቁበትን የወንጀል መጠን አይቀንሰውም ከተጠያቂነትም ሊያመልጡ እይችሉም።ለመሆኑ ያ ሁሉ እልቂት ህዝብ ላይ ሲወርድ ፓርላማው የት ነበረ ።ከራሱ ህዝብስ የበለጠ ሌላ አስቸኳይ ስብሰባ የሚያስጠራ ጉዳይ አለውን።

 

  1. የህዝብን ጥያቄ በሀይል ለመጨፍለቅ ከመሞከር አለመታቀብ አሁንም እየተመለከትን ያለነው እየተካሄደ ያለውን ህዝባዊ አመፅ ልዩ ኮማንድ ፖስት በማቋቋም በሃይል ለመጨፍለቅ የሚደረግ ሙከራ ነው። ግድያውን፣ድብደባውንና እስራቱን እየፈፀመ ያለወ አግአዚ የሚባለው ሰራዊት ይሁን፣ሌላ ሚሊሽያ ሃይል ወይም ምናምን ፖስት ለህዝብ ግድያ ግድያ ነው።ጭፍጨፋውን እንዴትና በየትኛው ሃይል እንፈፅመው የሚለው የህወሀት ፊታውራሪዎቹ የውስጥ አሰራር ነበር።ያን ህዝብ አወቀው አላወቀው መንገድ ላይ ፊት ለፊት የሚገናኙት እስናይፐር ተኳሽና ዱላ ያልያዘ ሰላማዊ ተቃዋሚ ህዝብ ናቸው።የህዝብ አመፁን መፍታት የሚቻለው ሰላማዊውን የህዝብ ጥያቄ በፍጥነት በመረዳት ፈጣን መልስ በመስጠት ነው።ህዝብም ከፕሮፌሰር መስፍን እስከ ጄኔራል ፃድቃን ሁሉም የየበኩሉን አስተያየት እየሰጠ ነው።እኔም በበኩሌ ‘Rock Bottom Benchmark for the comprehensive Renewal of TPLF/EPRDF’ የምትል መጣጥፍ ወርውሬ ነበር።የኔ ሃሳብ እንደፕሮፌሰር መስፍን መሆን ያለበት ብዬ ሳይሆን ከህወሀት /ኢህአዴግ ባህሪ አንፃር ጥልቅ ተሃድሶ አደርጋለሁ ካለ ይህ ጥልቅ ተሃድሶ ቢያንስ ቢያንስ ሊያመጣ የሚገባው ለውጥ ብዬ የምጠበቀውን ነበር። ምን እናድርግ ከተባልኩ ግን የፕሮፌሰር መስፍን መፍትሄ ፍቱን መድሃኒት ይሆናል።ግን ህወሀት /ኢህአዴግ ያን ያህል ይሄዳል ብዬ አልጠብቅም።ከዚህ ሁሉ የህዝብ እልቂትም በሁዋላ የህዝብን ጥያቄ በሃይል መጨፍለቅ ይቻላል ብዬ አላምንም።

 

  1. አምቢተኛ የመከላከያና የፖሊስ ሃይላትንና ሌሎችን መክሰሻ እስካሁን ከተለያዩ የዜና ምንጮች የምንሰማው በመከላከያና በፖሊስ ሰራዊትና በአንዳንድ መንግስታዊ ተቋማት ውስጥ ያሉ በህዝብ ላይ እየተወሰደ ያለውን እርምጃ በመቃወም ስርአቱን አናገለግልም እያሉ መሆናቸው እየተደመጠ ነው።የነዚህ ሰዎች አቋም በነፃ ፍርድ ቤት ቢታይ የሚተላለፉት ህግ አለ ተብሎ ሊቀጡ አይችሉም። ህዝብ ላይ መተኮስ ህገ መንግስታዊ ሊሆን ስለማይችል። አሁን ግን በዚህ ጊዜያዌ አዋጅ የአሰራሩ ተባባሪ አልሆኑም ወይንም አሰራሩን ተቃውመዋል በሚል በየትኛውም ፍርድ ቤት እየቀረቡ ከሶስት እስከ ስድስት አመት ሊፈረድባቸው ይችላል። ከዚህ መለስ የህዝብ እምቢተኝነት አፈናው ሃይል የሚፈልገውን ለማድረግ እስካሁን ያጋጠሙትን ችግሮች ከግንዛቤ በማስገባት በራሱ እምነት በልዩ ልዩ የመንግስት መስርያ ቤቶች የጋራ ግንዛቤ ለመፍጠርና በይበልጥ ለመንቀሳቀስ የሚያስችሉትን ድንጋጌዎች ለማካተት ያስችለዋል።

 

  1. ምናባዊ የፍርሃት አጥር ህዝብ ላይ መጫን የአምባገነን መንግስታት ዋና መሰረት ህዝብን ማስፈራራትና ያቺንም የፍርሃት ድባብ በመጠቀም ህዝብ መንግስትን እንዳይጠይቅ ፣ሃሳቡን እንዳይገልፅ፣የመብት ጥያቄ እንዳያነሳና መንግስት እየቸረቸረ የሚሰጠውን መብት ብቻ እሺ እርሶን ሺህ አመት ያኑርዎ እያለ እንዲቀመጥ ማድረግ ነው። የአዋጁም አላማ ህዝብን አስፈራርቶ ማቆም ነው።አሁን በአብዛኛው የኦሮምያ የአማራና አንዳንድ የደቡብ ኢትዮጰያ አካባቢዎች የምንመለከተው የነበረው የፍርሃት ድባብ መሰበሩን ነው።አቶ ሃይለማርያም ለመከላከያው የሰጡት የነፃ እርምጃ ሙሉ ስልጣንም ተቃውሞውን አልገታውም።በዚህ ሁኔታ ከዚህ በፊት ከነበረው የተለየ ምንም አዲስ ነገር የማይጨምር አዋጅ ማውጣት ምናልባት ተጨማሪ የስነ ልቦና ጫና በህዝብ ላይ በመፍጠር ምናባዊ የሆነ አዲስ የፍርሃት አጥር በህዝብ ስነ ልቦና ላይ ለመጫን የታሰበ ይመስላል።ከዚህ በፊት በተቃዋሚ ሰልፈኞች ላይ ሲወሰድ ያየነው ከፍተኛው እርምጃ ግድያ ነበር አሁን ደግሞ አዋጁ ከፍተኛው ቅጣት የስድስት አመት እስራት ነው ብሎናል። እስር አሉን አቶ አቃቤ ህግ ከዛስ በሁዋላ የሚመጣው የእስር ቤት ቃጠሎ ጌታው። ስድስቱ አመት ቃጠሎውን ህሳቤ ያደረገ ነው እንበል።

 

  1. የሰው ህይወት መጥፋትና የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለአለም አቀፍ ማህበሩ እንደምታው. የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መታወጁ በራሱ የሰላምና የመረጋጋት ችግር እንዳለና ለኢንቨስትመንት አመቺ ሁኔታ አለመኖሩን ያሳያል።ያም ሆነ ይህ ለኢትዮጰያውያን ከኢትዮጲያውያን ህይወት የበለጠ ምንም ነገር ጭራሽ እይኖርም።የሰው ህይወት መጥፋት አሁንም ችግሩን በሃይል ለመፍታት የሚኬደው አካሄድ ህዝቡን የበለጠ ያነሳሳዋል መንግስትንም በአለም አቀፉ ማህበረሰብ ያለውን ተቀባይነት ይሸረሽረዋል።

 

በቅርቡ በኢሬችው በአልና በሌሎች የሃገራችን አካባቢዎች በግፍ ለተገደሉ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን ጠበቃ ሆነን መቆም ይኖርብናል። የሞቱት ለግል ጥቅማቸው ሳይሆን ለህዝብ ብለው መሆኑን ልብ እንበል።ህዝባዊ አመፅ በሃይል ሊቆም እንደማይችል ልብ ያለው ልብ ይላል።

 

 

ኢትዮጲያ ለዘላለም ትኑር

 

መላኩ ወልደስላሴ

ከአትላንታ

የኢትዮጵያ ሴቶች የመብት ማዕከል (CREW) ለሰብዓዊ መብቶች መከበር፣ ለሴቶች የእኩልነት መብት

$
0
0


crew
ጥቅምት ፪ ቀን ፳፻፱ ዓም

የኢትዮጵያ ሴቶች የመብት ማዕከል (CREW) ለሰብዓዊ መብቶች መከበር፣ ለሴቶች የእኩልነት መብት መረጋገጥ፣ ለዲሞክራሲ ሥርዓት እውን መሆን፣ ለሰላምና ለሕግ የበላይነት ተግባራዊ መሆን የሚታገል ሕዝባዊ ድርጅት ነው።

እኛ በኢትዮጵያ ሴቶች የመብት ማዕከል የተሰባሰብን ሴቶች በሀገራችን እየተካሄደ ያለውን ሕዝባዊ እንቅስቃሴና የመንግሥትንም በሕዝቡ ለተነሱት ጥያቄዎች የሚሰጠውን የጥይት ምላሽ እየተከታተልን ነው። ለመብታቸው ሲታገሉ መስዋዕት የሆኑትን ወገኖቻችን ነፍሳቸው በሰላም እረፍት እንድታገኝ፤ የተሰዉላት ሀገራቸውም ስቃይና መከራዋ በአጭር ሆኖ ትንሣኤዋን ለማየት እንዲያበቃን እየተመኘን ለቤተሰቦቻቸውና ለኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን በሙሉ መጽናናትን ያድልልን እንላለን።

በሀገራችን በኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች ሁኔታ በጣም አስከፊ ደረጃ ላይ ደረሷል። የኢትዮጵያ ሕዝብ የመናገር፣ የመጻፍ፣ የመሰብሰብ የመደራጀት፣ ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ መሠረታዊ መብቱ ተረግጦ በገዛ ሀገሩ የበይ ተመልካች ሆኖ፣ ወጣቶች የተሻለ ኑሮና ሕይወት ፍለጋ ወደ ማያውቋቸው ሀገሮች በበረሃ፣ በባህር፣ በዱር በገደሉ እየተጓዙ የአውሬና የአሣ ነባሪ ቀለብ ሆነዋል። ላለፉት 25 ዓመታት ያለማቋረጥ ሀገራቸው የምድር ሲኦል ሆናባቸው በድህነት፣ በሥራ አጥነት፣በማንነት ጥያቄ፣ መተንፈሻ በማጣታቸው ትዕግሥታቸው ገንፍሎ በቃን ተበደልን፣ በደል አንገፈገፈን ብለው በሰላማዊ መንገድ ለመብታቸው ባደረጉት ትግል ከመንግሥታቸው ጥይት እየዘነበባቸው ከፍተኛ የሆነ ቁጥር በመላው ሃገሪቷ ሕዝብ እየረገፈ ነው። ላለፈው አንድ ዓመት በፊት ጀምሮ በኦሮሞ ወገኖቻችን የተነሳው ሕዝባዊ እንቅስቃሴ ዛሬም እንዳለ ነው፤ የወልቃይት  የማንነት ጥያቄን መሠረት አድርጎ በጎንደር በጎጃም የተቀሰቀሰው ሕዝባዊ እንቅስቃሴ በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ የሀገሪቷን ጎልማሳ ሽማግሌ፣ ሴት ወንድ፣ ህፃንና ወጣት ሳይለይ በሞት እየቀጠፈ ነው። በኮንሶ፣ በቤንሻንጉል፣ በደቡብ፣ በሰሜን፣ በምስራቅና በምዕራብ መላው ሀገሪቷ በሕዝብ ደም ማዕበል እየተጥለቀለቀችና በመንግሥት ታጣቂዎች ጥይት እየታመሰች ትገኛለች።

ይህ ሁኔታ በአግባቡ ከአልተያዘና በአስቸኳይ ካልቆመ ሀገሪቷንና የአካባቢውን ሀገራት ጨምሮ ወደ አልተገመተ አስከፊ የፖለቲካ የማህበራዊና የምጣኔ ሀብት ቀውስ ውስጥ ሊያስገባ ይችላል። ምንም እንኳን መንግሥት በጎሳና በሃይማኖት እየከፋፈለ ላለፉት 25 ዓመታት በእጥፍ እያደገነው የሚለው የምጣኔ ሀብት እድገት ለጥቂቶች መከበሪያ ከመሆነ አልፎ የሕዝቡን የኑሮ ሁኔታ ሊቀይረው አለመቻሉ ግራ የሚያጋባ ስሌት ቢሆንም  የሀገሪቱ የኤኮኖሚ ግሽበት ከ90% በላይ የሚሆነው ሕዝብ ከድህነት በታች እንዲኖር አድርጎታል። በ2009 መንግሥት አትራፊ ያልሆኑ ሕዝባዊ ድርጅቶችን የሚገድብ ህግ ደንግጓል። ይህ ህግ ሕዝባዊ ድርጅቶችን፣ ሰብዓዊ መብቶችን ለማስጠበቅ የቆሙትንና ተቆርቋሪ ድርጅቶችን ለሕዝቡ እንዳይደርሱ አምክኗቸዋል።

በዚሁ ሥርዓት ተወልደው የጎለመሱት የነገዋ ኢትዮጵያ ተረካቢ ትውልድ ቀደም ሲል በመካከለኛ ምሥራቅ በስደት ፍዳቸውን ያዩና ያለቁት ቁጥር ስፍር የላቸውም። አሁን ደግሞ ተስፋ በማጣት መረረኝ ብለው በሀገራቸው በስላማዊ ትግል ብሶታቸውን  በማሰማታቸው መንግሥት ምላሹ ጥይት ሆኖ በየቀኑ እንደ ጉድ እየረገፉ ነው። በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንዲሉ ይባስ ብሎ መንግሥት በሀገሪቱ ላይ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በማውጅ በገዛ ሕዝቡ ላይ አመጹን የሚያባብስ እርማጃ ወስዷል።

  • ይህ አዋጅ የሀገሪቷን መጻኢ ዕድል ከፍተኛ አደጋ ላይ የሚጥል፣ ሕዝቡን ለከፋ ቀውስ የሚዳርግ በመሆኑ አጥብቀን እንቃወማለን።
  • የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ እየደረሰበህ ያለው አስከፊ የመብት እረገጣ፣ ግድያና እሥራቱን ለመቋቋም አንድነት ኃይል ነው፣ የሕዝብን የአንድነት ትግል የሚያሸንፈው ኃይል የለምና ትግላችሁን ከዋናውና ከጋራ ጠላታችሁ ጋር ብቻ በማድረግ  ይችን ክፉ ዘመን በጋራ በአንድነት በመቆም  እንድትወጡት ወገናዊ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
  • የተቃዋሚ ኃይሎች ልዩነታችሁን አጥብባችሁ በየቀኑ በሚያለቀው፣ እንታገልልሃለን በምትሉትና ልትሰዉለት በተዘጋጃችሁት ሕዝብ ስም ከምንግዜውም በላይ ዛሬ በሚያግባቧችሁ መሠረታዊ ጥያቄ ላይ በማተኮር በጋራ ቆማችሁ ኢትዮጵያን ለማዳን ለሕዝባችሁ እንድትደርሱለት በአንክሮ እንጠይቃለን።
  • የተለያያችሁ ሕዝባዊ ማህበራት፣ የእምነት የሃይማኖት ተቋማት፣ የዕድር የእቁብ፣ አትራፊ ያልሆናችሁ ወገናችሁን በመርዳት ላይ ያላችሁ ተቋማት ሁላችሁም የወገናችን ዕልቂት በአስቸኳይ እንዲቆምና ሕዝባዊ መሠረት ያለው ሁሉም ኢትዮጵያውያንና የህብረተሰቡ አካሎች የተሳተፉበት ሕዝብ የመረጠው ሕዝባዊ መንግሥት እንዲመሰረት የበኩላችሁን ተሳትፎ እንድታደርጉ እንጠይቃለን።
  • የዓለም አቀፍ ህብረተሰብ በተለይ የአሜሪካንና ኃያላን አገሮች፣ በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ ያላቸውን ፖሊሲ እንድትመረምሩና የገዛ ሕዝቡን በጥይት ከሚጨርስ ከወያኔ ኢህአድግ መንግሥት ጋር ሳይሆን ከኢትዮጵያና ሕዝቧ ጎን እንድትቆሙ አጥብቀን እንጠይቃለን።

 

ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነት ለዘላለም ትኑር።

የኢትዮጵያ ሴቶች የመብት ማዕከል (CREW)

መለስ ዜናዊ ኦሮሞን አንደ ህዝብ ጠባብ ነው የሚል ሰነድ አዘጋጅተው እንደነበር አቶ ጁነዲን ሳዶ ገለጹ

$
0
0

ኢሳት (ጥቅምት 2 ፥ 2009)
junedinየቀድሞ ጠ/ሚ/ር መለስ ዜናዊ ኦሮሞን አንደ ህዝብ ጠባብ ነው የሚል ሰነድ አዘጋጅተው እንደነበር አቶ ጁነዲን ሳዶ ገለጹ። በሁኔታው የተቆጩ በዝቅተኛ ዕርከን ላይ የሚገኙ የኦህዴድ ካድሬዎች ሰነዱ እንዲቃጠል መጠየቃቸውንም አስታውሰዋል።
የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ከአዲስ አበባ ወደ አዳማ ከተዛወረ በኋላ ወደ አዲስ አበባ እንዲመለስ የተደረገው ቅንጅት አዲስ አበባ ላይ በማሸነፉ እንደሆነም ተመልክቷል።
የምርጫ 97 ማግስት ለኢህአዴግ ሰዎች እጅግ አስጨናቂ እንደነበር ያስታወሱት አቶ ጁነዲን ሳዶ፣ ዕርሳቸውና አቶ አባዱላ በምርጫ ክልላቸው ኢተያ ላይ በትክክል መሽነፋቸውን አምነዋል።
ኦሮሚያ ክልልን 4 አመታት ያህል በፕሬዚደንትነት ያገለገሉትና በተለያዩ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች በሚንስትርነት ሲሰሩ የቆዩት አቶ ጁነዲን ይህንን የገለጹት ከኢሳት ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ ሲሆን፣ በስርዓቱ ውስጥ የነበረውንና አሁንም እየቀጠለ ያሉት የህወሃትና የትግራይ የበላይነት በየአጋጣሚው ተቃውሞ ሲቀርብበት መቆየቱን አስታውሰዋል።
በተለይም በህወሃት ክፍፍል ማግስት በጠ/ሚ/ሩ ጽ/ቤት ባደረጉት ስብሰባ በዚህ ረገድ ጠንካራ ተቃውሞ እንደቀረበባቸው አስታውሰው፣ ከዚያ በኋላ በነጻነት የሚናገሩበትና ተቃውሞ የሚያቀርቡበት መድረክ እንዳልነበርም አብራርተዋል።
የህወሃት ንብረት የሆነው ኤፈርት ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ገንዘብ እየወሰደ ሲፋፋ፣ ሌሎች ዲንሾን የመሳሰሉ የኦህዴድ ኩባንያዎች ስለመጫጨታቸው ለአቶ መለስ ጥያቄ መነሳትንም ያስታወሱት አቶ ጁነዲ ሳዶ፣ አቶ መለስ ለዚህ የሰጧቸው ምላሽ ኤፈርት የተቋቋመው ጆንያ ሽጦ ነው የሚል እንደነበር ገልጸዋል።
ለድርቅ ተጎጂዎች የመጣውን እህል ካደልን በኋላ ጆንያውን ሸጥን፣ በዚያም ኤፈርትን አቋቋምን ማለታቸው ተመልክቷል።
አቶ ጁነዲን ሳዶ በስልጣን ዘመናቸው በፌዴራል መንግስትና በኦሮሚያ ክልል ውስጥ ያለፉበትን ሁኔታ በተመለከተ ከኢሳት ጋር ያደረጉትን ሰፊ ቃለምልልስ ከነገ ጀምሮ በተከታታይ እናቀርባለን።


ሁሉን አቀፍ የምክክር ጉባኤ መካሄድ ሊዘገይ የማይችል ተግባር ነው

$
0
0

ቀን፤ ጥቅምት 3፣ 2008 ኦክቶበር 13፣ 2016


shengoENTCEthiopian_Youth_Movement_Logo
በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ለ 25 አመታት ተጭኖ የኖረው የህወሀት/ኢህአዴግ የአፈናና የከፋፍለህ ግዛው ስርአት እነሆ በህዝባችን ታላቅ ተጋድሎና መስዋእትነት መሰረቱ ተናግቶ በመንገዳገድ ላይ ይገኛል:: ዛሬ ባለው ሁኔታ ስርአቱ ተንኮታኩቶ እንዲወድቅ አሁን በተለያየ ቦታ ከሚከናወነው ህዝባዊ ተጋድሎ በተጨማሪ፣ የስርአቱ መፈራረስን ተከትሎ ምንም ክፍተት እንዳይፈጠርና በህዝባችንም ሆነ በሀገራችን ላይ ምንም አይነት አደጋ እንዳይደርስ ምን መደረግ አለበት የሚለው ሁሉም ዜጋ፣ የፖለቲክ ድርጅቶች፣ ሲቪክ ማህበራት፣ ያገባናል የሚል ሁሉም ባለድርሻዎች ሊያስቡበትና የመፍትሄውም አካል ሊሆኑ የሚገባበት ወቅት አሁን ነው። — የሚቀጥለውን ያንብቡ በዲፍ …..

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ማስፈፀሚያ ደንብ ወጣ –አዲስ አድማስ

$
0
0

stateofeme-1 የሰዓት እላፊ ተግባራዊ የሚሆንባቸው ቦታዎች አሁንም ይፋ አልተደረጉም
– በሁከቱና ብጥብጡ ተሳታፊ የሆኑ ሰዎችን  በአንድ ማዕከል በማሰባሰብ እንደጥፋታቸው    መጠን እርምጃ የመውሰድ ሥራ ይሰራል
– በስራ ማቆምና በቤት ውስጥ መቀመጥ አድማዎች ላይ ተሳታፊ መሆን በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ያስቀጣል
– በኢንተርኔት ስራ ላይ የተሰማሩ ሰዎች፣ በአፍራሽ ተግባር ላይ ተሰማርተው የቆዩ በመሆኑ ገድቦ ማቆየቱ ተገቢ ነው

የሰዓት እላፊ ተግባራዊ የሚሆንባቸው ቦታዎች አሁንም ይፋ አልተደረጉም
በሁከቱና ብጥብጡ ተሳታፊ የሆኑ ሰዎችን በአንድ ማዕከል በማሰባሰብ እንደጥፋታቸው መጠን እርምጃ የመውሰድ ሥራ ይሰራል
በስራ ማቆምና በቤት ውስጥ መቀመጥ አድማዎች ላይ ተሳታፊ መሆን በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ያስቀጣል
በኢንተርኔት ስራ ላይ የተሰማሩ ሰዎች፣ በአፍራሽ ተግባር ላይ ተሰማርተው የቆዩ በመሆኑ ገድቦ ማቆየቱ ተገቢ ነው
በኦሮሚያና በአማራ ክልሎች የተነሳውን ተቃውሞና አመፅ ተከትሎ መስከረም 28 ቀን 2009 ዓ.ም የወጣውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል የማስፈፀሚያ ደንብ  የሚኒስትሮች ምክር ቤት በትላንትናው ዕለት ማውጣቱ ተገለፀ፡፡
ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ አቶ ጌታቸው አምባዬ ትናንት ለጋዜጠኞች በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደተናገሩት፤ መንግስት የህዝብን ሰላምና ፀጥታ ለማስከበር የሚያስችል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አውጥቶ ለህዝብ ይፋ አድርጓል፡፡ ይህንኑ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለማስፈፀም ተግባራዊነቱነ ለመከታተል የሚያስችል ዝርዝር ደንብ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ማውጣቱንና በሥራ ላይ እንዲውል ማድረጉን ገልፀዋል፡፡ ደንቡ ከያዛቸው ዝርዝር ጉዳዮች መካከል አዋጁ የያዘቸውንና ተግባራዊ የሚደረጉትን ዝርዝር ሃሳቦች ለህዝቡ ይፋ ማድረግ፣ አስቸኳያ ሁኔታ በተጋረጠባቸው አካባቢዎች ልዩ ገደቦችን በመጣል ለህዝቡ ማሳወቅ፣ የተከለከሉ ጉዳዮችን ህዝቡ በዝርዝር እንዲያውቃቸው ማድረግና፣ ተላልፎ መገኘት የሚያስከትላቸውን ቅጣቶች ለህዝቡ ማሳወቅ ይገኙበታል፡፡ ማንኛውም ህብረተሰብ መረጃ የመስጠትና የመተባበር ግዴታ እንዳለበት በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ውስጥ የተደነገገ ሲሆን መረጃ በመስጠቱ ምክንያት ለጉዳት የሚጋለጥ አካል ከለላ የመስጠት ሥራ ተግባራዊ እንደሚደረግ አቶ ጌታቸው በመግለጫቸው ጠቁመዋል፡፡
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በሁከትና በብጥብጡ ውስጥ ተሳትፎ አላቸው የተባሉ ሰዎችን ለመቅጣት የሚያስችል ህጎችን ያቀፈ መሆኑን የተናገሩት ጠቅላይ ዐቃቤ ህጉ፤ ዜጎች ባጠፉት ጥፋት ልክ ቅጣታቸውን የሚያገኙበት አሠራር ተግባራዊ እንደሚያደርግ ተናግረዋል፡፡
የጥፋታቸው ክብደትና መጠን አነስተኛ የሆኑና በሁከትና ብጥብጡ አስተዋፅኦና ድጋፍ የነበራቸው ወገኖችን በአንድ ማዕከል ውስጥ በማሰባሰብ እንደ ጥፋታቸው ደረጃ ተሃድሶና ትምህርት በመስጠት፣ ወደ ህብረተሰቡ እንዲቀላቀሉ የማድረጉ ሥራ ተግባራዊ እንደሚደረግና የጥፋታቸው መጠን ከፍተኛ የሆኑትን ደግሞ በህጉ መሰረት ወደ ፍርድ ቤት ቀርበው በፍርድ ሂደት የሚዳኙበት አሠራር ተግባራዊ ይደረጋል ብለዋል፡፡ ይህንን ሁኔታ ፀረ ህዝብ ኃይሎች በራሳቸው መንገድ ተርጉመው፤ ለራሳቸው የፖለቲካ ፍጆታ ማዋላቸው አይቀሬ ነው ያሉት አቶ ጌታቸው፤ በቀንደኞቹ ላይ የምንወስደው እርምጃ ሌሎችን የሚያስተምርና ለጥፋታቸው ተመጣጣኝ የሆነ ነው ብለዋል፡፡ የጥፋት ኃይሎቹ እያካሄዱት ያለውን የሽብር ተግባር በመደበኛ አዋጅና ህጎች መቆጣጠር ባለመቻሉ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ለማውጣት ተገደናል ያሉት ጠቅላይ ዐቃቤ ህጉ፤ የፀጥታና የሰላሙ ሁኔታ እየታየ ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የምንወጣበት ሁኔታ ይኖራል ብለዋል። ጥፋት ሊደርስባቸው ይችላሉ ተብሎ የሚታሰቡ ቦታዎችን በመለየት፣ ጥፋት ሊያደርሱ ይችላሉ የተባሉ አካሎችን በአንድ ቦታ በማስቀመጥ ጥፋት እንዳያደርሱ መከላከልና ጥፋቱ ያደርስባቸዋል በተባሉ አካባቢዎች ላይ የሚኖሩ ሰዎችን ከጥፋት ለመታደግ ጥበቃ አድርጎ እዛው ማቆየት አሊያም ወደ ሌላ ቦታ እንዲዛወሩ የማድረግ ሥራም ተግባራዊ ይሆናል ብለዋል፡፡
በሁከትና ብጥብጥ ተግባር ተሳታፊ መሆን ተጠያቂነትን እንደሚያስከትል ሁሉ በሥራ ማቆምና የአገልግሎት መስጫ ተቋማትን በመዝጋት ተግባር ላይ ተሳታፊ መሆን በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ መስራት ለቅጣት እንደሚዳርግም አቶ ጌታቸው ተናግረዋል። ሰሞኑን የኢንተርኔት አገልግሎት ከመቋረጡ ጋር በተያያዘ፣ ይህንኑ አገልግሎት ለህብረተሰቡ በመስጠት የሚተዳደሩ አካላት ጉዳት እንደደረሰባቸውና ይህ ሁኔታ እስከመቼ እንደሚቀጥል ለቀረበላቸው ጥያቄም አቶ ጌታቸው ሲመልሱ፤ ‹‹የኢንተርኔት አገልግሎት መስጫ ተቋማት ገንቢ በሆነ ሥራ ውስጥ ተሰማርተው ከሚሰሩበት ይልቅ አፍራሽ እንቅስቃሴና በህዝቦች መካከል ሁከትና ብጥብጥ መጠራጠርና ጥላቻ እንዲዘራ በማድረግ የነበራቸው ሚና ቀላል ግምት የማይሰጠው ነው፡፡ በዚህ የተነሳም በአገራችን ቀላል የማይባል ውድመት ደርሷል፤ ህገ መንግስታዊ ስርዓቱ አደጋ ላይ እንዲወድቅ ሆኗል፡፡ ስለዚህም ለእንደዚህ አይነት አገልግሎት የሚውሉና የማይውሉትን ለይቶ አስፈላጊውን እርምጃ መውሰድ እስከሚቻል ድረስ አገልግሎቱን ገድቦ ማቆየት አማራጭ የሌለውና የአገርንና የዜጎችን ህልውና የሚታደግ ጉዳይ ነው ብለዋል፡፡

ለመለስ የተፃፈ ደብዳቤና የመለስ መልስ

$
0
0
ከፍቃዱ ጌታቸው ለመለስ
(ፍቃዱ ጌታቸው)

Meles-Zenawi_head1.jpgእንደምን አለህ ጋሼ እንደምን ነህ መለስ
ትመጣለህ ስንል ቀረህ ሳትመለስ
እኛማ ይሔውልህ
ባንተ ሌጋሲና ባንተ ትልቅ
ራዕይ
በየአደባባዩ እንላለን ዋይ ዋይ
ዛሬም ጀነራልህ ተኩስ ነው ትዕዛዙ
ወገን ያጋድማል የግፍ አፈሙዙ
ለምንድን ነው ስንል ስምክን አስቀድመው
ከክርስቶስ በላይ ምስልህን አትመው
ቅዱስ መጽሐፍ ይመስል
ባንተ ራዕይና በሌጋሲህ ምለው
ቢረፈርፉንም አላለቅንምና
ደብዳቤ ላክንልህ ከሞት የተረፍነው!
የሆነስ ሆነና ግን አንተ ደህና ነህ
እኛማ ይኸውልህ
ደርሰህ ስትናፍቀን
አይሞትም የምትል ሙዚቃ ሞዝቀን
መቃ
ብርህን ልንስም አበባ ልናኖር ሥላሴ ብንመጣ
ፌደራል ያይሃል እስረኛ ይመስል ሾልከህ እንዳትወጣ
መቼም ሥላሴ ውስጥ
ባለስም ነውና የሚቀበርበት
አንተን አየት አርገን ዞር ስንል ድንገት
እነፊታውራሪ
ግራ’ዝማች
ቀኝ’ዝማች
ፊተኛ ባለስም የሆኑት አባቶች
ያለዘብ ቆመዋል እነ አብዲሳ አጋ
ጀግና መሃል ሳለህ ምነው በድንህ ሰጋ!
የሆነስ ሆነና
ኃየሎም ደህና ነው
እዛም ትግል ይመራል
እስር ቤት ሰባብሮ ታራሚ
ያስፈታል
እዛም ከፊት ሆኖ ጭቁን ያታግላል
እዛም በጀግንነት በለኮሳት ሻማ
ነፃ ነኝ ባለባት ርዕሰ ከተማ
ትንሽ ግሮሰሪ ይገባ ይሆን ደፍሮ
እዛስ ጀማል ያሲን ፈጠረ አምባጓሮ
ኃየሎምን ሰዋው በሐሺሽ ናላው ዞሮ
እኛማ ይኸውልህ ብዙ ኃየሎሞች ፈጥረን ስናበቃ
እልፍ ጀማል ያሲን ይሆናል ጥበቃ
ይኸው ባደባባይ የጀግኖቻችን ደም በየቦታው ፈሶ
አለ ጀማል ያሲን ሞት ሚበይንበት ፍርድ ቤቱ ፈርሶ!!
ግን አንተ
ደህና ነህ
አቡነ ጳውሎስስ ብፁው እንዴት ናቸው
እዚያም እንደምድሩ አንድ አንቀጽ ያክላል መጠሪያ ስማቸው
ደረታቸው ግድም “ሽጉጥ” የሚያደርጉት አለ መስቀላቸው
እኛማ ይኸውልህ
ዳያስፖራ ጳጳስ ሾመን ባደባባይ
ከበዓል ቀን ውጪ ፊታቸውን አናይ
ሰው ሲሞት
ህዝብ ሲያልቅ
እምነት ሲተራመስ አያውቁም ግሳጤ
ዝም ዝም ናቸው
ቆባቸው የጳጳስ ነብሳቸው የአጤ!!

እንደምን አለህ ጋሼ እንደምን ነህ መለ

ትመጣለህ
ስንል ቀረህ ሳትመለስ
ከቻልክ ፃፍልን ለደብዳቤያችን መልስ!!
***
ከመለስ ለፍቃዱ ጌታቸው
(ወለላዬ)
ደብዳቤህ ደርሶኛል ሰሞኑን የላከው
እንዴት! ከረምክልኝ? ፍቃዱ ጌታቸው
ነበልባሉ መሃል፣ በሲዖል አዳራሽ
በተነጠፈልኝ ሠፊ የእሳት ፍራሽ
እየተጠበስኩኝ፣ በቁጭት በምሬት
ጽሑፉን በሙሉ አንብቤ ጨረስኩት
ምነው ቀረህ ያልከኝ በዛው ሳትመለስ
አጣድፎ ወስዶኝ ነው አባቴ ዳቢሎስ
ያስጨኹኛል ያ
ልከው በየአደባባዩ
ባላስጮኹኽ ነበር እዚህ እኔን ቢያዩ
ውሸት ቦታም ብሆን እውነት ለመናገር
መከራ እየቀመስኩ እያየሁ ነው አሳር
ሥላሴ በመሄድ እኔን የፈለከኝ
እንደው ለፋህ እንጂ እዛ የታለሁኝ
ለሥልጣን ዕድሜያቸው ለማወናበጃ
ርገው አስቀምጠውኝ እኔን መቀለጃ
ሌጋሲው እያሉ እያወናበዱ
ሰማሁኝ በስሜ እንደሚነግዱ
እንኳንስ የተውኩት ዕራይ ሊኖረኝ
የራሴው ራዕይ ለራሴም አልበጀኝ
አስራ ዘጠኝ ዓመት በከተማ
መሃል
አስራ ሰባት ዓመት በበረሃ ትግል
ሃያ አንድ ዓመታት ሀገር ሳተራምስ
ሳላየው ከርሜ የኔን ጉድጓድ መማስ
ከሄድኩበት ቀረኹ በዛው ሳልመለስ
ሌሎቹም አይቀሩም ተጠርቷል ስማቸው
አንተስ! እንደምነህ ፍቃዱ ጌታቸው?
የህወሓት አባላት ኃየሎም ምናምን
አሰፋ ማሞና ክንፈ ገ/መድህን
በደህና ጊዜ ነው ወደዚህ የመጡት
ይብላኝ በአሁን ሰዓት በሥልጣን ላይ ላሉት
በህዝብ ተይዘው ልክ! እንደጋዳፊ
እየተወገሩ በርግጫ
በጥፊ!
ይመጣሉ እዚሁ አይቀርም ሞታቸው
ይፈንጩ ግድ የለም እስከዛ ተዋቸው
እንደው ለመሆኑ በረከት ስምኦን
እንዴት አደረጋት የቆየች ህመሙን?
እንዴትስ! ዘገየ እስካሁን ሳይመጣ?
ፊቱስ ምን መሰለ? ጠቆረ ወይ ነጣ?
እነ አቦይ ስብሓት፣ እነ ስዩም መስፍን
እነ ገነት ዘውዴ፣ እነ ደብረጽዮን
እነ አባይ ፀሓዬ፣ ቴዎድሮስ አድኃኖም
ሳሞራ፣ አባዱላ፣ እነ ኃይለማርያም
ወርቅነህ ገበየሁ፣ እርካበ እቁባይ
እያወናበዱ
ተቀምጠው አንድ ላይ
እስከመቼ ድረስ ሊኖሩ አስበዋል?
ከኔ ከተለዩ ስንት ሰው ገድለዋል?
ምን ያህል ገዘፉ፣ ምን ያህል ከበሩ?
ስንት ብር አሸሹ? ስንት ፎቆች ሠሩ?
የተማከርነውን የአማራንስ ማጥፋት
ከኦሮሞ ጋራ ማስነሳቱን ግጭት
እንዴት አደረጉ ከምን አደረሱት?
ዕቅዱ ተሳካ እነሱው ጨረሱት?
እንደው በከንቱ ነው መግደል ማሰራቸው
በቅርብ ይመጣሉ ግዴለም ተዋቸው
አንተስ እንደምነህ ፍቃዱ ጌታቸው?
አባ
ጳውሎስንም ያነሳህ መሰለኝ
ወደዛ ተዋቸው አሁን ምን ሊረቡኝ
አክብሬ አስመጥቼ ጎኔ ሳደርጋቸው
ሳጠፋ ገስፀው በአባትነታቸው
ምናለበት ነበር ቢመክሩ ቢቆጡኝ
ልጄ ልጄ እያሉ ለዚህ ከሚያበቁኝ
አሁንማ አብረውኝ የሲዖልን ስቃይ
እየቀመሱ ነው ከኔ ጋር አንድ ላይ
የራሳቸው ጉዳይ ሁሉንም ተዋቸው!
ፊትም እማይረቡ ወራዳዎች ናቸው
ደግሜ ልናገር ወራዳዎች ናቸው
አንተስ እንደምነህ ፍቃዱ ጌታቸው

ከመለስ ይልቅ በጥልቅ መቃብር ያለው ሰላዩ ልደቱ –ካሳሁን ይልማ

$
0
0

ይኼ ቅጥረኛ አንቅረን ከተፋነው 10 ዓመታት በኋላም ይለፈልፋል። “ተቃዋሚዎች ኢህአዴጎች በሕዝብ ዘንድ እንድትጠሉ ብዙ ጥረት አድርገናል” ይላል:: እሱ ተቃዋሚ? ደንቆሮህን ፈልግ።
ምርጫ ሲመጣና ህወሓት አደጋ ውስጥ ሲገባ ወደ ቴሌቪዥን መስኮት፣ ወደ ልሳኖቻቸው አምጥተው የተቃዋሚ ተውኔት ይሰጡታል።

ህወሓትን የማደንቀው በባሪያ አመላመል ላይ ያለችውን ችሎታ ነው። አገልጋይ መምረጥ ተክነውበታል። ጥሩ ሆዳም ያውቁበታል። ኃፍረተ የማያውቅ ኅሊና ቢስ ባንዳ ጠፍጥፈው መስራት ይችሉበታል።

ደግነቱ የኢትዮጵያ ሕዝብም ከልቡ አውጥቶ ሕይወታቸውን የምድር ሲኦል ማድረግ ይችለበታል። በቁም ሞተው የሚራመዱ ያደርጋቸዋል። ልደቱም የፖለቲካ ሞትን ሞቶ ከመለስ ይልቅ በጥልቅ መቃብር ሆኖ ይቃዣል::


ከመለስ ይልቅ በጥልቅ መቃብር ያለው ሰላዩ ልደቱ

በአገሪቱ የበጀት ውዥቀት ተከሰተ፤ በባሕር ዳር 67 ሆቴሎች የባንክ ብድር መመለስ አንችልም ብለዋል –ሙሉቀን ተስፋው

$
0
0

bahir_dar_city_03መንግስት በከፍተኛ ሁኔታ ኪሳራ ውስጥ ገብቻለሁ አለ፡፡ የ2009 ዓ.ም የካፒተል በጀት እስካሁን ድረስ አልተለቀቀም፡፡ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ለስራ ማስኪጃ እና ለፅህፈት መሳሪያዎች መግዥያ የሚገለገሉበት በሀገሪቱ የሚጠበቀው የካፒታል በጅት በ2009 ዓ.ም ሊለቀቅ አይችልም፡፡ ሲሉ የአማራ ክልል ገንዘብ እና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ አየነው በላይ ተናግረዋል፡፡
መንግስት በዚህ ስዓት ለድንገተኛ አደጋዎች መከላከያ በሚል ከመንግስት በጀት ለሚልሻዎች ቀለብ እና ለወታደሩ የምግብ ሂሳብ ወጭ ያደረገ ሲሆን ይህም የወረዳዎችን በጀት እንዳናጋባቸው እና በአሰተዳደራዊ ስራው ላይ ተፅዕኖ እያሳደረ መሆኑን በበአዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ስብሰባ ላይ አንስተዋል፡፡
በተያያዘ በአማራ አካባቢ በተነሳው ህዝባዊ አመፅ ጋር በተያያዘ በአሁኑ ሰዓት በክልሉ የሚገኙ ኢንቨስትምንት እና ሆቴሎች በቀን ሻሂ እንኳን መሸጥ አልቻልንም ሲሉ አቤቱታ አሰምተዋል፡፡
ባህር ዳር ጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ (ቴክስታይል)፣ ፒፒ የፕላስቲክ ቀረጢት ፋብሪክ፣ ፀሐይ ቀለም ፋብሪካ፣ አማራ ፓይፕ ፋብሪካ፤ በግብፆች እና በብአዴን የሚመራው ዳሸን ቢራ፣ አማራ ችፑድ እና ፕላስቲክ ፋብሪካ ገበያ ጠፍቷል አላመርትንም፤ መሸጥም አልቻንም ብለዋል፡፡
በባህ ዳር የሚገኙ ትልልቅ ሆቴሎች ደግሞ መንግስት ያበደረንን እስከ 300ሽህ ብር የሚደርስ ገንዘብ አሁን ምንም የመመለስ አቅም የለንም፡፡ በቀን ሻሂ እንኳን መሸጥ አልቻልንም ሠራተኞቻችንንም ለመበተን እየተገደድን ነው ብለዋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ በባህር ዳር የስርዓቱ አቀንቃኝ ተብሎ በህዝባዊ አመፅ ጉዳት የደረሰበት ጋሳ ባለ አምስት ፎቅ ሆቴል፤ የወያኔ ተላላኪ እና የዳሸን ወኪል አከፋፋይ በመሆኑ፤ ህዝቡ ላለመጠቀም በወሰደው እርምጃ ሆቴሉ ሙሉ ለሙሉ አገልግሎት መስጠቱን አቆሞ፤ ሰራተኞችን እንደበተነ ከባለቤቱ አረጋግጠናል፡፡
በአሁኑ ሰዓት የወሰድነውን ብድር መመለስ አልቻልንም ሲሉ ለመንግስት እንቅጩን በመናገር ቅሬታ ያሰሙ ሆቴሎች ዝርዝር 67 ሲሆኑ እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡

1 ቦስተን ሎጂ ባ/ዳር 28 (የምኝታብዛት) 0582264868 0582264280
2 ፓፒረስ ሆቴል ” 100 0582205100 0582205047
3 ብሉ ናይል ሬስቶራንት (ጣና ሆቴል) ሆቴል ” 64 0582200554 0582202042
4 ብሉ ናይል ሆቴል ” 55 0582202028 0582263958
5 ጋሳ ሆቴል ” 31 0918766107 –
6 አዝዋ ሆቴል ” 41 0582203820 –
7 ኒውላይት ሬስቶራንት ” – 0918241801 –
8 ሌክ ሾር ሬስቶራንት ” – 0918340666 –
9 አባይ ምንጭ ሎጂ ” 44 0582281039 0582182223
10 ድብ አንበሳ ሆቴል ” 60 0582201436 0582201818
11 ሆምላንድ ሆቴል ” 28 0582204545 0582220209
12 ሰመርላንድ ሆቴል ” 40 0582206565 0582221091
13 ጊዮን ሆቴል ” 30 0582200111 0582200303
14 ኢትዮስታር ሆቴል ” 68 0582202026 0582209442
15 ስታርባክስ ሬስቶራንት ” – 0918007370 –
16 ዴዘርት ሎጅ ሎጅ ” – 09218282575 –
17 አሉዋቅ ሆቴል ሆቴል ” 30 0582265565 –
18 አቫንቲ ብሉናይል ሆቴል ” 135 0582264566 –
19 ባ/ዳር ቁጥር 2 ሆቴል ” 36 0582203820 –
20 ኒውላንድ ፔኒሲዮንፔኒሲዮን “82 0582200876 /0918341054 –
21 አዲስ አምባ ሆቴል ሆቴል ” 69 0911220608 –
22 መነን ሆቴል ሆቴል ” 54 0582202800 –
23 ጃካራንዳ ሆቴል ” 28 ዐ5822ዐ9899 –
24 ጨጨሆ ሬስቶራንት ሬስቶራንት ” – ዐ911181937 –
25 ኢትዮ ላንድ ሆቴል ሆቴል ” 58
26 ራህን ሆቴል “ – ዐ5822ዐ7575 –
27 ቤተ ዳንኤል ሆቴል “ – ዐ582266161/22ዐ1414 –
28 ኤንጅጅ ሆቴል ሆቴል “ 42 ዐ5822ዐ6363 –
29 ጣና ሆቴል ጎንደር 18 ዐ918786132 –
3ዐ ሰሜን ፖርክ ሆቴል “ 32 ዐ58111ዐ3ዐዐ –
31 ግራንድ ሪዞርትና ሰፖ ሪዞርት ባ/ዳር – ዐ5822663ዐ3/ ዐ5822ዐ7833 –
32 አሲኗራ ሆቴል ሆቴል “ – ዐ5822ዐ7299 –
33 ኪትስል ሆቴል “ “ – ዐ5822663ዐዐ –
34 ዲላኖ ሆቴል “ “ – ዐ5822ዐዐ622 –
35 ታዬ በላይ ሆቴል “ 79 ዐ58111218ዐ ዐ581112175
36 አምባራስ ሆቴል “ 4ዐ ዐ581111181 –
37 ኩይንስ ሆቴል “ 18 0581141297 –
38 ጐሀ ሆቴል “ 66 ዐ58111ዐ634 ዐ58111192ዐ
39 ሴንትራል ጎንደር ሆቴል “ 18 ዐ581117ዐ2ዐ –
4ዐ አፄ በካፋ ሆቴል “ 24 ዐ581117711 –
41 ቋራ ሆቴል ጎንደር 5ዐ ዐ58111ዐዐ4ዐ ዐ581111144
42 ሰርክል ሆቴል “ 24 ዐ581111991 ዐ58112ዐ599
43 ሬድ ፎክስ ሆቴል “ 14 ዐ58114ዐ581 –
44 ህብረት ሆቴል “ 42 ዐ58112ዐ4ዐዐ ዐ58112ዐ4ዐ1
45 ጐልደንጌት ሬስቶራንት “ – ዐ58111769ዐ –
46 ኤልሼኘ ሬስቶራንት “ – ዐ91877ዐ272 –
47 ላመርጌር ሆቴል ሆቴል “ 2ዐ ዐ58112ዐ599 –
48 ኤጅ ሆቴል ሆቴል “ 45 ዐ581126ዐዐ7 –
49 ጃንተከል ሆቴል “ 39 ዐ918776ዐ68 –
5ዐ ሴንትራል ጎንደር ሆቴል ሆቴል “ 2ዐ ዐ58153762ዐ –
51 ተሜና ኪም ሎጅ ሎጅ ጎርጎራ 12 ዐ92ዐ336671 –
52 ዩኒክላንድ ስኬኘ ሆቴል ደባርቅ 21 ዐ58117ዐ152 –
53 ሰሜን ፖርክ ሎጅ “ 22 ዐ58231ዐ741 –
54 ጃይንት ሎቢሊያ ሆቴል “ 39 ዐ58117ዐ56ዐ –
55 እሚት ጐጐ ሆቴል “ 27 ዐ58117ዐ634 –
56 ጃስመን ሆቴል ሆቴል “ 27 ዐ58117ዐ563 –
57 ሰሜን ፖርክ ሆቴል ሆቴል “ 5ዐ ዐ58117ዐዐ55 –
58 ይምርሃ ሆቴል ላሊበላ 42 ዐ33336ዐ862 ዐ116299259
59 ማውንቴን ቪው ሆቴል “ 3ዐ ዐ33336ዐ8ዐ4 ዐ33336ዐ649
60 ፍቅሩሰላም ሆቴል “ 25 ዐ33336ዐዐ47 ዐ33336ዐ55ዐ
61 ሰቨን አላይቭስ ሆቴል ” 27 0333360020 –
62 ቤተአብርሃም ሆቴል ” 49 0333361065 0333361213/2
63 አያት ሮሃ ሆቴል ” 64 0333360009 0333360156
64 ሆሊ ላንድ ሬስቶራንት ” – 0911481948 –
65 ላል ሆቴል ” 210 0333660008 0333660008
66 አማን ሆቴል ” 56 0333360076 0333360214
67 ግራንድ ሪዞርትና ሰፖ ሪዞርት
68. ራህ ናይል

#AmharaResistance

‹‹በጌዴኦ የደረሰው ችግር የብሔር ግጭት አይደለም›› (ወ/ሮ ሂክማ ኬይረዲን፤ የደቡብ ክልል መንግሥት ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ኃላፊ)

$
0
0

አዲስ አድማስ
screen-shot-2016-01-10-at-18-11-24-800x425-e1452496751407
  የችግሩ ምክንያት በዲላ የንግዱ ማኅበረሰብና የጌዴኦ ዞን ሕብረት ሥራ ዩኒየን መካከል የቦታ ይገባኛል ክርክር ነበር፡፡ ባለፉት ጊዜያት ፍ/ቤቱ አክራክሮ ውሳኔም አስተሳልፎ ወደ አፈፃፀም ሂደት ሊገባ ነበር፡፡ በዚህ ሂደት ውስጥ ቦታው ለዩኒየኑ ይገባል በሚል የተወሰኑ አካላት ማኅበረሰቡን አነሳስተው በንግዱ ማኅበረሰብ ላይ ጉዳት ደርሷል። የፍ/ቤቱን ውሳኔ መነሻ አድርጎ ነው ግጭቱ የተከሰተው፡፡ ከግጭቱ ጋር በተያያዘ የሰው ሕይወት ጠፍቷል፣ ንብረትም ወድሟል፡፡ 23 ሰዎች ሞተዋል፤ ቤት ንብረት የተቃጠለባቸውና የወደመባቸው አሉ፤ ጉዳቱ ሰፊ ነው፡፡
በዚሁ ሂደት መካከል ችግሩ ሲከሰት ደንግጦ ከቤቱ የወጣ፤ ቤትንብረቱ ሲቃጠል ከቤቱ የወጣ  ሰው አለ፡፡ አንዳንድ ሰዎች የብሔር ግጭት ነው ይላሉ፡፡ ግን አይደለም፡፡ ጉዳቱ የደረሰው ከአካባቢው ብሔረሰብ ውጭ ብቻ አይደለም፡፡ ከአካባቢው ተወላጅ ሕይወቱ ያለፈ አለ፡፡ ስለዚህ ከሁሉም ኢትዮጵያዊ ብለን ነው መውሰድ የሚቻለው፡፡ የንግዱ ማኅበረሰብ ውስጥም የአካባቢው ተወላጆች አሉ፡፡ ንብረታቸው የወደመው የሁሉም ነው፡፡ ስለዚህ ግጭቱ የተወሰነ ብሔረሰብ ላይ በፍፁም ያነጣጠረ አይደለም፡፡
ለተጠቂዎቹ ቀድሞ የደረሰላቸውና ሕይወታቸውን የታደገው የአካባቢው ማኅበረሰብ ነው፡፡ አንዳንዶቹ የሃይመናት ተቋማት ውስጥ ተጠልለው ነው ያመለጡት፡፡ ሌሎቹ ደግሞ በአርሶ አደሩ ጓሮ ነው የተጠለሉት፡፡ ቤቱን በማጋራት ከቤቱ በላይ ሲሆንበት የአካባቢውን ማኅበረሰብ አስተባብሮ ድንኳን በመደኮን፤ ውሃ፣ ምግብ፤ በማቅረብ ቀድሞ የደረሰላቸው የአካባቢ ማኅበረሰብ ነው፡፡ ከቤት ንብረቱ የተፈናቀለ ሰው ከ20-25ሺህ ይደርሳል፡፡ መንግሥት ችግሩ ከዞኑ አቅም በላይ መሆኑን ካረጋገጠ በኋላ የፀጥታው ኃይል ገብቶ ሰላም የመፍጠርና የማረጋጋት ሥራ ሰርቷል፡፡ በመቀጠል ደግሞ ለተፈናቀሉ የማኅበረሰብ ክፍሎች የሚያስፈልጉ ነገሮችን ከለየ በኋላ ቁሳቁሶች ገዝቶ እያሰራጨ ነው፡፡ አብዛኛው ሕዝብ ደርሶታል፤ ያልደረሳቸውም ያሉ ይመስለኛል፡፡
በመሠረቱ ችግሩ ይህን ያህል ይሆናል ተብሎ አልተጠበቀም፡፡ ሲነሳ በተደራጀ መልኩ ቀደም ብሎ የተሠራበት አይደለም፡፡ ለንግዱ ማኅበረሰብ ተወስኗል የሚል ነገር ነው ለኅብረተሰቡ ተሰራጨው። አብዛኞቹ የኅብረት ሥራ ዩኒየኑ አባላት በአርሶ አደሩ መሃከል ያሉ ናቸው ወሬውን ያሰራጩት፡፡ ውሳኔው ተላላፊ እንጂ ወደ አፈጻጸም አልተገባም፡፡ የዞኑ አመራርም በአንድ ጊዜ ችግሩ በዚህን ያህል ይሰፋል፤ ኅብረተሰቡ በአንድ ጊዜ ይህን ውሳኔ ይሰማል የሚል ግንዛቤ አልነበረውም። ጥፋቱ ከአካባቢ አካባቢ ይለያል፡፡ ዲላ በስፋት ተጎድቷል። ወናጎ ላይና ይርጋጨፌ ላይ በጣም በስፋት ጉዳት ደርሷል፡፡ ሌሎች ወረዳዎች ላይ መጠነኛና ቀላል ነበር፡፡ መነካካቱ አለ፡፡ ግን ችግሩ አጠቃላይ ነው ብሎ መውሰድ አይቻልም፡፡
በአሁኑ ወቅት ይህንን ችግር ፈጥረዋል የተባሉ የተጠረጠሩ ሰዎች ተይዘዋል፡፡ የሕግ ሂደት መጠበቅ ስላለበት እነዚህ ሰዎች ናቸው ብሎ መደምደም አይቻልም፡፡ ከኅብረተሰቡ ጋር ስለጉዳዩ ውይይት ሲደረግ እነዚህ እነዚህ ናቸው ብሎ የሰጣቸው ሰዎች አሉ፡፡ ቁጥራቸው ሊጨምርም ሊቀንስም ይችላል፡፡
ከዝግጅት ክፍሉ
የይርጋጨፌ ወረዳ አስተዳዳሪ ስለጉዳዩ ለመጠየቅ ደውለንላቸው ሞባይሉ አይሰማም፣ በቢሮ ስልክ ደውሉ ብለውን ቁጥር ሰጡን። ስንደውል አይነሳም፡፡ መልሰን ደውለን ስልኩ አይነሳም አልናቸው፡፡ ቆይ እኔ እደውላለሁ ብለው ሳይደውሉ ቀሩ፡፡ ዞኑ አስተዳዳሪ ጋ ደውለን ስለጉዳዩ ልናናግራቸው መፈለጋችንን ስንነግራቸው አሁን አልችልም ስብሰባ ላየ ነኝ አሉን፡፡

ሕወሓት በአሰቸኳይ ጊዜ አዋጁ ሊያሳካ ያሰበው ግልፅ እና ድብቅ ግቦች

$
0
0

ጉዳያችን / Gudayachn
ጥቅምት 7፣2009 ዓም
www.gudayachn.com
=====================

achamየአሰቸኳይ ጊዜ አዋጅ በኢትዮጵያ ላይ ከታወጀ ጥቂት ቀናት ውስጥም በሕወሓት ላይ የሚደረገው ተቃውሞ የመቀነስ አዝማምያ አላሳየም።በባህር ዳር የስራ ማቆም አድማ የተደረገው ከአዋጁ በኃላ ነው፣ አሁንም ከአዋጁ በኃላ በሰሜን ጎንደር የትጥቅ ትግሉ ቀጥሏል፣ ባለፈው ዓርብ በጎንደርም የስራ ማቆም አድማ እንዲደረግ ጥሪ ቀርቧል።ይህ ሁሉ የሚያሳየው የአዋጅ ጋጋታው ያመጣው ለውጥ አለመኖሩን ነው።እርግጥ የኢትዮጵያን ሕዝብ መስዋዕትነትን ሊጨምረው ይችላል።ይህ በእንዲህ እንዳለ ግን አዋጁ በወጣ በሳምንቱ አዋጁ ምን ምን እንደሚከለክል የመከላከያ ሚኒስትር በሚል ስም ስር በሚገኙ ግለሰብ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ተገልጦለታል።እዚህ ላይ የተከለከሉ እና ያልተከለከሉ የተባሉትን የገዢው ስርዓት መገናኛ ብዙሃን ያሉትን መድገም አያስፈልግም።ባጭሩ አዋጁ በአዲስ አበባ የሚገኙ የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቦች ከአዲስ አበባ 40 ኪሎ ሜትር በላይ እንዳይርቁ ተነግሯል።በተጨማሪም መሰረታቸውን ውጭ ያደረጉ የቴሌቭዥን እና የራድዮ ጣብያዎችን ኢሳት እና ኦኤምኤን ጨምሮ መስማት የተከለከለ መሆኑም ተነግሯል።አሁን ጥያቄው ሕወሓት ይህንን አዋጅ ያወጣበት እና እግረ መንገዱን ሊያሳካው ያሰበው ግልፅ እና ድብቅ ግብ ምንድነው? የሚለውን ጥያቄ መመለሱ ነው።
ሕወሓት በአዋጁ ሊያሳካ ያሰበው ግልፅ እና ድብቅ ግቦች
1ኛ/ ግልፅ ግብ
አዋጁ በዋናነት ለሁሉም ግልፅ እንደሆነው የሚታየው ዓላማ የሕወሐትን የስልጣን ዘመን ማራዘም ነው።ይህም የሚቃወሙትን በሙሉ አንገት አስደፍቶ እና አሸማቆ በስልጣን ዘመኑ መቆየት ነው። ማሸማቀቅ እና አንገት ማስደፋት ብቻ አይደለም ጎን ለጎን በፈረሰው የኦህዴድ እና የብአዴን ድርጅቶች ምትክ አዲስ አሽርጋጆች እና መስሎ አዳሪዎችን ወደ መድረኩ እያመጣ የተቀባቡ ግለሰቦች እና ድርጅቶችንም ይፈጥርበታል።ለእዚህም ነው እንደ ልደቱ አይነቶቹን መድረክ መስጠት የፈለገው።በእዚህ ሂደት ውስጥ ግን መንገዱ አልጋ በአልጋ እንዳልሆነ በእርግጠኝነት አብዛኛው የሕውሓት አቀንቃኝ ያውቀዋል።ሆኖም ግን ተስፋ መቁረጥ እና ከወንጀል ነፃ ሆኖ ለመኖር እንደ ብቸኛ መፍትሄ የተወሰደው ዛሬ እየገደሉ እና እያሰሩ ነገን በተስፋ መጠበቅ ነው። ይህ ሁኔታ ግን ተቃውሞው እየጠነከረ ሲመጣ እና የበላይነት መያዝ ሲጀምር ለሕወሓት የበለጠ ወደ አዘቅት ብቻ ሳይሆን እርስ በርሱም የመከፋፈል ዕጣ እንደሚገጥመው የሚያጠራጥር አይደለም።
2ኛ/ ድብቅ ግብ
ሕወሓት በአዋጁ ዋናውን እና ግልፅ ግቡን ለማሳካት ከሚሄድበት መንገድ በተጨማሪ ሁለት ድብቅ ግቦችን ማሳካት ያስባል።

አሰቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንደ አካባቢ ስጋት እንዳልሆነ የሚነገረው በትግራይ አካባቢ ነው።በተቀረው የኢትዮጵያ ክፍል ከስጋት አልፎ ለበለጠ ትግል መነሳት አስፈላጊ ብቻ ሳይሆን ብቸኛ አማራጭ ሆኖ ቀርቧል።የአዋጁ አፈፃፀም ለምሳሌ የአደጋ ቀጠና ተብለው ከተጠቀሱት መንገዶች ውስጥ አንድም የትግራይ ክልል መንገድ የለም።ይህ ማለት ሕወሓት በአንደኛ ደረጃ ስጋት አለብኝ የሚለው ያውም ተቃዋሚዎች መሽገውባታል የምትባለው ኤርትራ ጋር የሚያዋስን መንገድ ለምን አንዱም ቀይ መስመር አልተባለም? ብሎ መጠየቅ ያስፈልጋል።ይህ ብቻ አይደለም አዲስ አበባ ዙርያን ለዲፕሎማቶች የስጋት ከተማ አድርጎ ያስቀመጠበት አግባብ እንደተባለው ሕዝባዊ ተቃውሞው የውጭ ሀገር ዜጎችን ኢላማ አድርጎ ነው? ባለፈው በሰበታ መስመር መገደሏ የተገለፀው አሜሪካዊት በእውነት በተቃዋሚ ሕዝብ ነው የተገደለችው? ከእዛ በፊት የሚኒባስ ጥቃት ያውም ተሳፋሪ ባለበት ተደብድቧል? እነኝህ ሁሉ ጥይቄዎች በአግባቡ መመለስ አለባቸው። በሌላ በኩልም መጠየቅ ያለብን ጉዳይ አለ በኦሮምያ እና በአማራ የተቃጠሉት ፋብሪካዎች እና እርሻ ቦታዎች በእውነት ሁሉም በተቃዋሚ ነው የተቃጠሉት? በጎንደር ገበያ ላይ የተፈፀመው እና በኃላም ሌላ የጎንደር ቦታዎችን ልታቃጥል ስትል የተደረስባት ከትግራይ የመጣች ነች የተባለችው ሴት ሰሞኑን ከሚቃጠሉት ቃጠሎዎች አንፃር ምን ይነግረናል? ይህችው ወንጀል ለመስራት ሙከራ ላይ እንደሆነች የተነገረው ሴት በወታደር ታጅባ እጇ ላይ ሰንሰለት ሳይገባ እንድትሄድ የሆነበት ጉዳይስ ምን ያሳየናል?

ከላይ ከተነሱት ጥያቄዎች አንፃር አዋጁ ሊያሳካ የሚያስባቸው ድብቅ አላማዎች እንዳሉት እና እነኝህ ድብቅ አላማዎች ደግሞ ከሕወሐት የረጅም ጊዜ ስልቶች ጋር ሁሉ የተቆራኙ እንደሆኑ መረዳት ይቻላል።በእዚህ አዋጅ ሕወሓት ግልፅ ከሆነው ስልጣኑን ማስጠበቅ በተጨማሪ ሁለት ድብቅ አላማዎች (ግቦች) አሉት። እነርሱም ; –
ሀ/ የመሃል ሃገሩን እና የደቡብ አካባቢን በአዋጁ አማካይነት ሙሉ በሙሉ በመምታት ኢኮኖሚያዊ እና ማኅበራዊ መሰረቱን ማናጋት እና የበለጠ ማደህየት።
በእዚህ አዋጅ መሰረት በሕወሓት መዘውር ውስጥ በሚገባ ያልገቡ የንግድ ድርጅቶች በሰበብ አስባቡ እና የሽብርተኛ ታቤላ እይተለጠፈባቸው ይዘጋሉ፣ይወረሳሉ ወይንም ከገበያ እንዲወጡ ይደረጋሉ።
በእዚህም የሕወሓት ሰዎች እንዲቆጣጠሩ ይደረጋሉ።የበለጠ ድሃ እንዲሆን የተደረገው ሕዝብ የበለጠ የእነርሱ ተገዢ እንዲሆን እና አመፁን ዝም ማሰኘት ይቻላል ብለው ያስባሉ።ለእዚህ ነው የሚቃጠሉት ድርጅቶች ሁሉ የሕወሓት ሳይሆኑ እንደ ጎንደር ገበያ ሕወሓት እራሱ የሚያቃጥላቸው ድርጅቶች እንዳሉ ማወቅ ያለብን።

ሌላው የማደህየት ሥራው የሚገልጠው የአዋጁ አስፈፃሚ ኮማንድ ፖስት ስር ያሉ ወታደሮቹ እንዲዘርፉ የውስጥ በጎ ፈቃድ አሳይቷል። ለእዚህም ማስረጃው በአዲስ አበባ በተደረጉ አሰሳዎች የውጭ ምንዛሪ እና ሞባይል ስልኮች መዘረፋቸው እና ወታደሮቹ በግላቸው መውሰዳቸው ነው።ይህ በትንሹ የተጀመረ ሂደት ነገ ኮማንድ ፖስቱ የእገሌ ድርጅት በሽብር ተግባር ሊሰማራ ሲል ተይዞ ድርጅቱ ተወረሰ ሲል እንደምንሰማ መጠራጠር የለብንም።
ለ/ የትግራይን ምጣኔ ሃብታዊ እና ማኅበራዊ ልዕልና በቀረው የኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ በሚገባ መስፈኑን ዋስትና ለመስጠት
ሕወሓት ከመነሻው ዋና ግቡ መሃል እና ደቡብ ኢትዮጵያን ከቻለ ለሚገነባው የትግራይ ኢምፓየር በግብዓትነት እንዲያገለግሉ ማድረግ እና የተወሰነ ልማት እያሳዩ የቀረውን ግን ማጋበስ ነው።ይህ የሚሆነው ግን ሕዝብ በተቃውሞ እስካልተነሳበት ድረስ ነው።ሕዝብ በተቃውሞ ከተነሳበት ግን ሊያደርግ የሚያስበው መሃል ሃገሩን እና ደቡብን በብሄር ግጭት እና በምጣኔ ሀብት ቀውስ አተራምሶ ቀጥሎም ማውደም እና የትግራይ ምጣኔ ሀብት የመሳብ (puling role) ወይንም የማዕከላዊ ሚናውን(central role) እንድትጫወት ማድረግ ነው። ይህም የአዲስ አበባን የዋና ከተማነት እና የኢንዱስትሪ ማዕከልነት በተለያየ መንገድ አውድሞ ልማቱ ወደ ትግራይ ማዕከልነት እንዲቀየር ማድረግ ነው። ይህ ደግሞ የእረጅም ጊዜ ሂደት ነው።ሆኖም ግን የእዚህ አይነቱ ግርግሮች እንደ አንድ አጋጣሚ ሕወሓት ይመለከተዋል እና የእረጅም ጊዜ ሂደቱን ያፋጥናል ብሎ ያስባል።

ባጠቃላይ ሕወሓት በአዋጁ ግልጥ እና ድብቅ ዓላማዎች እንዳሉት መረዳት ይገባል።ብዙ ሕዝብ የሚያወራው ስለ ግልጡ እና የስልጣን እድሜውን ለማራዘም ነው የሚለውን እንጂ እግረ መንገዱ እየሰራ ያለው የእረጅም ጊዜ ግቡ የተከሰተለት አይመስለኝም።የፖለቲካ መፍትሄዎችን የማይሰጥበት ዋናው ምክንያት ድብቅ አላማውን እንደሚያሳኩለት ስለሚያምን ነው።የጎንደርም ሆነ የኦሮምያ ተቃውሞዎች ከመጀመርያው ፍፁም ሰላማዊ ነበሩ።በጎንደር በመቶ ሺህ የሚቆጠር ሕዝብ ታሪካዊውን ሰልፍ ሲያደርግ አንዳች ኮሽታ አላሰማም።ነገር ግን ሕወሓት ቀላል መነሻ የነበራቸውን ጉዳዮች እያከረረ እና የህዝቡን ሰላም እየነሳ እዚህ አድርሶታል።በእዚህም የአማራ እና የኦርሞ አካባቢዎች የስጋት ቀጠና አድርጎ ትግራይ ግን ሰላማዊ ቀጠና አድርጎ አቅርቧል።ይህ ማለት አንድ ቱሪስት ጎንደር ከምትጎበኝ መቀሌ ብትሄድ የተሻለ ነው እያለ የሕዝብ ምጣኔ ሀብት እድገትን በማቀጨጭ የእረጅም ጊዜ የእድገት ማዕከልን የመቀየር ሂደቱን ያጧጡፍበታል።በተመሳሳይ መንገድም መሃል ሀገር ያለውን ባለ ሀብት ለ25 አመታት ያህል ከከተማ ይዞታው ከማፈናቀል ጀምሮ ከገበያ እንዲወጣ እያደረገ እና የንግድ መስመሮቹን በሙሉ በእራሱ ሰዎች በማስያዝ የምጣኔ ሀብቱንም ሆነ የማኅበረሰባዊ የበላይነትን ለመቆጣጠር ይጠቀምበታል።

ስለሆነም እንደ ኢትዮጵያዊነት መኖር ካለብን እኩልነት በቅድምያ መምጣት አለበት።ይህ እኩልነት ደግሞ የጥቂቶች (minority ) መንግስት የሆነው የሕወሓት መንግስት ስልጣኑን ለሕዝብ ማስረከብ እና የሁሉንም ሕዝብ ውክልና ያገኘ መንግስት ኢትዮጵያ ውስጥ መመስረት የእያንዳንዱ ዜጋ ግዴታ ነው።ከእዚህ ውጭ አዋጁ በእራሱ ከፋሺዝም አዋጅ ያልተለየ እና ከፍተኛ ጦርነት የሚቀሰቅስ አደጋውም በበለጠ ለሕወሓት ህልውና ቆምያለሁ በሚለው ላይ እንደሚሆን ምንም ጥርጥር የለውም።ይልቁንም እነኝህ አደጋዎች ከመድረሳቸው በፊት የሕወሓት ደጋፊዎች በመጨረሻው መጨረሻ ሰዓት ላይም ሆነው ሊያስቡበት ይገባል።የማይስኬድ መንገድ ለጊዜው የሚያራምድ ይመስላል እንጂ በማንኛውም ሰዓት ይርዳል።ይህ ደግሞ ያለፉት ጥቂት ወራቶችም በሚገባ አስተማሪ ናቸው።

 


በሰሜን አሜሪካና ካናዳ የሚንገኝ የወላይታ ተወላጆች በወቅታዊ የሀገራችን አሳሳቢ ጉዳዮችን አስመልክተን የተሰጠ መግለጫ

$
0
0

ቀን ጥቅምት 6, 2008     ኦክቶበር 16, 2016

welyta-satenaw-news

እናት አገራችን ኢትዬጵያ የበርካታ ህዝቦች መኖርያ የሆነች ጠንካራ ሃይማኖቶች፤ ጥንታዊ ቅርሶችና፤የበለጸገ ታሪክ ያላት፤ የጥቁር ህዝቦች የነጻነት ተምሳሌት ናት። በኢትዮጵያችን ከሚኖሩ ህዝቦች አንዱ የሆነዉ የወላይታ ህዝብ ለኢትዮጵያ ሉዓላዊነት እንዲሁም ለህዝቦች የጋራ መኖር ከፍተኛ አስተዋኦ ሲያደርግ የቆየ በደቡብ የሃገራችን ክፍል ከሚኖሩ የኢትዮጵያ ህዝቦች አንዱ ነው። ከታሪክ እንደምንረዳው ወላይታ የሚለዉ የብሄረሰብ መጠርያ በወላይትኛ ቋንቋ “ወላሄታ” ወይም በአማርኛ “የተቀላቀለ” ከሚለዉ ቃል የተገኘ ሲሆን ይህም የወላይታ ህዝብ አንድ ዘዉግ ወይም የዘር ግንድ ሳይሆን ከኦሮሞ፤ ከአማራ፤ ከጋሞ፤ ከዳዉሮ፤ ከትግራይ፤ ከሃድያ፤ ከሲዳማ፤ ከአፋር፤ ከሶማሌና፤ ከተለያዩ አካባቢዎች በንግድ፤ በጦርነት፤ በጋብቻ፤ በስደት፤ ወዘተ የመጡ ሰዎች አካባቢዉን በለምነቱና ለኑሮ አመቺ በመሆኑ መርጠዉ ቀደም ሲል በስፍራዉ ይኖሩ ከነበሩ ሰዎች (natives) ጋር ተዋህደዉና ተዋልደዉ በአንድ ወላይትኛ ቋንቋ ተጠቅመው ጠንካራ ባህል ገንብተው የራሳቸዉን ንጉስ ተጠቅመው ቤተ መንግስት፤ የጦር ሃይል፤ የፍርድ ስርዓት፤ የመገበያያ ገንዝብ ፈጥረው ለብዙ ዘመናት የኖሩበት አካባቢ ነዉ።

በጥንታዊት በኢትዬጵያ አንዱን ንጉስ ሌላውን ንጉስ ለማስገበር አንደኛው መንገድ ጦርነት በመሆኑ በወቅቱ አፄ ምኒሊክ ማዕከላዊ መንግሥት ለመመስረት በነበራቸው ህልምና ምኞት ለማዕከላዊ መንግሥት  በሰላም አንገብርም ያሉትን በጦርነት ማስገበራቸው ይታወቃል ። በሄሆኑም የወላይታን ህዝብ ለማስገበር ጦርነት ከከፈቱ በኋላ በወቅቱ የወላይታ ንጉስ በነበሩት ንጉሥ ጦና የሚመራ የወላይታ ጦር 6 ጊዜ የሚኒሊክን ጦር አሸንፎ አባረረ። በዚህ ሽንፈት የተናደዱት አፄ ሚኒሊክ ራሳቸው ጦራቸዉን አጠናክረው በራስ አሉላ አባነጋ አዝማችነት ለ 7ኛ ግዜ ከወላይታ ህዝብ ጋር ተዋግተዉ በማሸነፍ ነጉስ ጦናን ማርከዉ የወላይታን ህዝብ ለማእከላዊ መንግስት አስገብረዋል። ጦርነቱ በህዝቡ ላይ ከባድ ጉዳት ያደረሰ ከመሆኑ በላይ ሃብትና ንብረቱን ዘርፈዉ በአፄ ሚኒሊክ ፈቃድ የጦር ምርኮኞችንና ጉልበት ያላቸዉን ማንኛዉንም የወላይታ ተወላጆች ሠራዊታቸው የዘረፈዉን ንብረት አሸክመው እንዲወስዷቸው ተደረገ። በዚህም ሁኔታ በርካታ ወላይታዎች በመላዉ ኢትዮጵያ እንዲብትኑ ተደርጓል።ለመጥቀስም ያክል አዲስ አበባ ሲቆረቆር ከነበረዉ ነዋሪ ውስጥ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ የወላይታ ተወላጆች ነበሩ ። በደሴና አንዳንድ የኢትዮጵያ ከተሞችም የወላይታ ሰፈር እየተባሉ የሚጠሩት በጦርነቱ ተማርከዉ የተወሰዱት የወላይታ ተወላጆች ይኖሩበት የነበሩባቸዉ ሠፈሮች መጠርያዎች ናቸዉ።

አፄ ምኒሊክ ንጉስ ጦናን ማርከዉ ከወሰዱ ብኋላ የክርስትናን ሀይማኖት እንዲቀበሉ በማድረግ በመጥመቅና የክርስትና ስም በመስጠት ከእሳችዉ በፊት የወላይታ ነጉስ የነበሩት አማዶ ያገዱትን  የክርስትና እምነት ወደ ወላይታ እንዲገባየልዑላን ቤተሰብ የነበረችዉን “ሸዋንግዬ” የተባለችዉን ሴት ለንጉስ ጦና በመዳር የወላይታ ባላባት እንዲሆኑ መልሰዉ ልከዋቸዋል። የወላይታ ህዝብም ንጉሥ ጦናን ከተቀበለ በኋላ እንደሚስት ሆና አንድ ላይ የተላክችዉን ሴት “ሸንገቴ” ብለዉ ይጠሯት ነበር። የወላይታ ህዝብም የጣልያንን ወረራ ለመመከት በአድዋ ጦርነትንና  በግንባር ቀደምትነት በአዝማችነትና ዘማችነት ተዋግቷል ፣ የወላይታ ህዝብ በተለያዩ ወቅቶች ታሪካዊ ጠላቶቻችን ሃገራችንን ሲወሩ ለኢትዮጵያ አንድነትና ሉዓላዊነት ተዋድቋል። በቅርቡ ኢሃዴግ ደርግን አሸንፎ የኢትዮጵያ ሰራዊትን ሲበትን በተካሄደዉ የቀድሞ ሠራዊት ምዝገባ የት እንደገቡ ያልታወቁትንና በጦርነቱ የተሰዉትን ሳይጨምር በቀይ መስቀል የተመዘገቡት ከተራ ወታደር እስከ ከፍተኛ መኮንን 75ሺህ የወላይታ ልጆች በመከላከያ ሠራዊትነት የኢትዮጰያን አንድነትና ዳር ድንበር ሲያስክበሩ ቆይተዋል። በቅርቡም ህወአት/ በኢሃዴግና በሻቢያ መካከል በተካሄደዉ ዉጤት አልባ የባድሜ ጦርነት ከ 10ሺህ በላይ የወላይታ ልጆች ከሌሎች ኢትዮጵያዉያን ጋር በመሆን ትዋግተዋል።

የዛሬ ሃምሳ በዓመት ገደማ ለለም መሬትና ለተሻለ ኑሮ ፍለጋ ከጎንደር ፣ ጎጃም ፣ ከሸዋና ወሎ አካባቢዎች የመጡ ወገኖቻችን ወላይታ ውስጥ በአባያ ኃይቅ ዳርቻ አበላ በምትባል ለም አካባቢ ሰፍረው እዝያው ወልደው ፣ ተጋብተውና ከብረው ሃብትም አፍርተው ቋንቃውንም ለምደውና የራሳቸውንም ነዋሪውን አስለምደው እስከዛሬም ተባዝተው መኖራቸውና እንደዚሁም በሥራ ዝውውር የመጡ በርካታዎች ሁሉ ህዝቡንና አገሩንም በመውደድ ቤታቸው ማድረጋቸው የወላይታ ህዝብ ለኢትዬጵያዊነት ትስስርና አብሮነት ተምሳሌት  ስለመሆኑ ጥሩ ማሳያ ነው።

ዛሬም ታሪኩን አስከብሮ  ለዓመታት የተነዛውን የዘረኝነት አባዜ በመዋጋት ከሁሉም ወገኖቹ ጋር በትስስርና በፍቅርእንደሚቀጥል ሙሉ እምነታችንን ነው።

ከላይ ያስቀመጥነዉ የወላይታ ህዝብ ታሪክ የመጥፎም ሆነ የጥሩ የኢትዮጵያ ታሪክ አንዱ አካል መሆኑንና ሟቹ ጠቅላይ ሚኒስትር የአክሱም ሀዉልት ለወላይታ ምኑ ነው ብለዉ የተናገሩት ለወላይታ ህዝብ ከፍተኛ ስድብ መሆኑን ለመጥቀስም ጭምር ነው።

፩  በወያኔ አኢሃዴግ የሚመራው በወላይታው የኢሃዴግ ክንፍ “ወህዴድ” በወላይታ ህዝብ ላይ ያደረሰው ግፍና በደል

1ኛ) 1985 በአረካ ገበያ ላይ ተኩስ በመክፈትና የእጅ ቦንብ በመወርወር ከ 100 በላይ ንጹሃን ዜጎች ሲገደሉ በርካቶች ደግሞ አካለ ስንኩል ሆነዋል። ይህም ሆኖ ወያኔ ወንጀለኞችንና ገዳዮችን ፈጥኖ ከአካባቢው እንዲሰወሩ በማድረግ ለሞቱትም ሆን ለቆሰሉ ተጠያቂ ሳይኖር በዋዛ ቀርቷል፤

2ኛ) በ 1991 ወጋጎዳ የተባለ በ 4 ቋንቋዎች የተዳቀለ አዲስ ቋንቋ በመፍጠር በሰላም ይማር የነበረዉን ተማሪና ወላጅ በማሸበር ከአጎራባች ጋሞና ጎፋ ህዝቦች ጋር ከማጋጨቱም በላይ በከፍተኛ የመንግስት ወጪ መጽሃፍ በማሳተም ህዝቡ በግድ አዲስ ቋንቋ እንዲማር ጫና በመፍጠሩ የወላይታ ህዝብ እምቢ በማለትና የዞን መስተዳድር ደረጃ ለመጠየቅ ሰልፍ በመውጣቱ የአጋዚ ጦር ታዞ የወላይታ አውራጃ ዋና ከተማ የሆነችዉን ሶዶ አፍንጫው በታጠቀ ሰራዊት በመክበብ የወላይታን ህዝብ ጨፍጭፏል፤ መምህራንና ሠራተኞች ከስራቸዉ አፈናቅሏል። ጉዳዩን እንዲከታተሉ በህዝብ የተመረጡትን ሽማግሌዎች በደህንነት በማደን ከቤት ንብረታቸዉ አፈናቅሏል። የጉዳዪ ጠንሳሾች ናቸዉ ያላቸዉን አስሮ ከፍተኛ ቶርቸር በማድረግና በማሰቃየት በሽተኛ ሆነዉ እንዲሞቱ አድርጓል። የዞን ጥያቄ አቀራቢና የወላይታ ነጻነት ታጋይ አቶ ሰለሞን ሴታ ሲሆን በእስር ተሰቃይቶ ሞቷል። 12 ግለሰቦችም በአጋዚ ወታደሮች ጥይት ተገድለዋል። በርካታ ግለሰቦችም አካለ ስንኩል ሆነዋል። የዚህ ወንጀል ፈጻሚዎችና መመሪያ አስተላላፊዎች እስከ ዛሬ ድረስ በወላይታ ህዝብ ተወካይ ነን በማለት በወያኔ የስልጣን ኮርቻ ላይ ተቆናጠው ይገኛሉ።

3ኛ) በ 1997 ምርጫ ሰፊዉ የወላይታ ህዝብ በነቂስ ወጥቶ የተቃዋሚ ፓርቲ ተወካዮችን በከፍተኛ ድምጽ ከመረጠ በኋላ በሶዶ በቦዲቲ፤ በሁምቦ፤ በባዴሳ ፤ በጋሱባ ፤ በአረካ ፤ በባሌ ከተማና በአንዳንድ ቀበሌዎች የአሸናፊዎች ስምና የቆጠራ ዉጤት ከተለጠፈ በኋላ በወቅቱ የደቡብ ክልል ፕሬዝዳንት የነበሩት አቶ ኃ/ማርያም ደሳለኝ ከአቶ መለስና በረከት ስምኦን በተሰጣቸዉ ትዕዛዝ በሌሊት በመላዉ ወላይታ ካድሬዎችን ከፍተኛ አበል ከፍለዉ በመንግስት ተሽከርካሪ በማሰማራት የወላይታ ህዝብ ድምጽ እንዲሰረቅና ኮሮጆ ተገልብጦ ኢህአዴግ እንዳሸነፈ ተደርጎ በህዝቡ ያልተመረጡ ግለሰቦች ሥልጣን በሌብነት እንዲይዙ ተደርጓል።  እነዚህ የዉሸት ባለስልጣኖች የወላይታ ህዝብ በጥቂቱም ቢሆን ብሶቱን እንዳይተነፍስ የተቃዋሚ ድርጅቶችን ቢሮዎች በማሸግ አመረሮችን በማሰር የኑሮ ዋስትናቸዉን በማሳጣት ንብረታቸዉን በመቀማት እየተከታተሉ በማሳደድ አጥፍተዉ ለብቻቸዉ የወላይታን ፖለቲካ ጠቀልለዉ ይዘዋል።

  • በአሁኑሰአትወላይታዉስጥየኢህአዴግአባልወይምጆሮጠቢያልሆነግለሰብተምሮሥራአያገኝም፤ነግዶወደፊትእንዳይወጣይደረጋል፤አርሶበነጻነትእንዳይኖርበካድሬዎችጫናይደርስበታል።
  • ወላይታከፍተኛየህዝብብዛትያለበትናየመሬትጥበትያለበትመሆኑእየታውቀየገበሬዉይዞታለከተማመስፋፋትእየተባለአለበቂካሳክፍያይወሰዳል።በገጠርደግሞታዳጊማዘጋጃቤትእየተባለየገበሬዉመሬትይነጠቃል።የመሬትነጠቃዉንየተቃወሙግለሰቦችይታሰራሉይደበደባሉይባረራሉ።
  • የአርሶአደሩንመሬትበGPS እየለኩከአቅምበላይየሆነግብርበመጫንመክፈልካልቻለመሬቱንይነጥቃሉ።
  • ለገበሬዉበኮታማዳበሪያበማደልበአንድኩንታልክ 1 ሺህእስክ 2 ሺህበመተመንመክፈልካልቻለከብቱንነጥቀዉወደገበያበመዉሰድሸጠዉገንዘቡንለማዳበርያክፍያያዉላሉ።
  • በከተማዉነጋዴላይከአቀምበላይየሆነግብርበመጫንነግዶእንዳይበላያፈናቅላሉ፤ግብሩምእጅግየተጋነነነዉብሎየተናገረነጋዴየንግድፈቃዱተቀምቶቤቱይታሸጋል።
  • የከተማመሬትበከፍተኛዋጋበሊዝዝስለሚሸጥየመንግስትሠራተኞችምሆንአነስተኛኑሮያለዉዜጋየቤትባለቤትመሆንአቅቶአቸዋል።
  • በሌላዉየኢትዮጵያእንደሚፈጸመዉሁሉየወላይታህዝብበኑሮዉድነት፤በመኖርያቤትችግር፤በዉሃናበመብራትእጦት፤በመሬትዘረፋናንጥቅያ፤በኢህአዴግ“ወህዴድ”የፖለቲካጫናበድሮጉልተኛሥርዓትከደረሰበትጭቆናበላይወያኔበመደባቸዉየራሱንቋንቋበሚናገሩሆዳሞችታፍኖይገኛል።በሌላበኩልየወያኔጆሮጠቢዋችመዋቅርዘርግተዉህዝብንናመንግስትንበመዝረፍሰባዊመብቱንረግጠውናአፍነውይገዛሉ።

፪ በመላዉ ኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለዉ የህዝብ ንቅናቄና የኢትዮጵያ ጠቅላይ ምንስቴር ምላሽ በተመለከተ

አቶ ኃ/ማርያም ደሳለኝ ከወላይታ ህዝብ ከመልካም ቤተሰብ የተወለዱ፤ በጥሩ ሥነምግባር ያድጉ፡ ከፍተኛ የቀለም ትምህርት የቀሰሙና ወጣት ሲቪል ፖለቲከኛ በመሆናቸው ህወሃት በጠቀላይ ሚኒስትርነት ሲመድባቸዉ ኢትዮጵያዉያን ወደተሻለ ዴሞክራሲ፤ የጋራ መግባባት ያለዉ የሰከነ ፖለቲካ፤ የህግ የበላይነት ያሰፍናሉ፤ የሰዉን ሰብአዊ መብት ያስከብራሉ፤ የህዝብን እምባ የሚያብስ ፖለቲካ ሥርዓት ያመጣሉ የሚል ተስፋ መላዉ የኢትዮጵያ ህዝብ እንደጣለባቸዉ እኛም የወላይታ ተወላጆች አንዳዶቻችን በግል ጓደኝነት ሌሎቻችን በአካባቢ ልጅነትና በትምህርትና በስራ አጋጣሚ ስለምናዉቃቸዉ ተደስተን ነበር። ሆኖም ቤተ መንግስት እንደገቡ ሙሉ በሙሉ ለህወሃት እጃችዉን ሰጥተዉ ህሊናቸውን ሸጠዉ የሟቹን ጠ/ሚኒስትር ራዕይ አሳካለሁ ማለት ጀመሩ።

የመጀመሪያዉ 2 የስልጣን ዘመን የዉከልና ነዉና ይሻሻላል በሚል ሲጠበቁ የመለስ ራዕይ የሚሉትን እንደ እግዚአብሄር ቃል ሙጭጭ አድርገዉ በመያዝ የመለስን የምርጫ ማጭበርበር፤ የተቃዋሚ ፓርቲ አፈና እስርና ግድያ፤ የጋዜጠኞች እስርና ስደት ደረጃዉን ከፍ አደረጉት። ኮሮጆ እየሰረቁም ቢሆን በመለስ ዜናዊ 10% ከዚያም አንድ ለእናቱ በሚል የሚታወቀዉን የፓርላማ ወንበር ጨፍልቀዉ ፓርላማዉን 100% ተቆጣጠሩት። በአረካ ከእርሳቸዉ ጋር የተወዳደሩትን እዉቁን ነጋዴ በካድሬዎቻቸዉ አማካኝነት የተቃዋሚ ደጋፊዎች የምረጡኝ ዘመቻቸውን በነፃነት እንዳያካሂድ በማዋከብና በማስፈራራት አሰናክለው ምንም ህፍረት ሳይሰማቸዉ 100 ለ 0 አሸነፍኩ አሉ። የህወሃትን የከፋፍለህ ግዛ ተልኮ ለመፈጸም በደቡብ የወላይታን ብሄረሰብ ከሲዳማ ጋር ለማጋጨት ከብላቴ ወንዝ ማዶ የነበረዉን የሲዳማ መሬት ብላቴን አሻግረዉ የወላይታ መሬት ለሲዳማ እንዲሰጥ በማድረግ ሁከት እንዲፈጠር አመቻችተዋል።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ሰላማዊ ሰልፍ ባደረጉት የኦሮሚያ ህዝቦች፤ የመብት ጥያቄ ባነሱ የዓማራ ህዝቦች እንዲሁም በኮንሶ፤ በቁጫ፤ በአርባ ምንጭ፤ በቤኒሻንጉል፤ በጋምቤላና በቴፒ ወዘተ የተነሱትን የተነሱትን ጥያቄዎች የጥይት ምላሽ እንዲሰጥ የዉጭ ወራሪ ሃይል ባልተነሳበት ሁኔታ የመከላከያ ሠራዊት እርምጃ እንዲውስድ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል።

የመሬት ባለቤትነት ቢረጋገጥ ገበሬዉ መሬቱን ሸጦ ወደ ከተማ ይፈልሳል የሚለዉን የህወሃት ፕሮፓጋንዳ ፍጽም መሠረት የሌለው መሆኑን እየጠቆምን ለመረጃም ያህል  በደርግ ዘመን መሰረታዊ የተማሪው ጥያቄ የነበረው የመሬት  ላራሹ ምላሽ በማግኘቱ ሠፊው ህዝብ ከመሬት ጭሰኝነት ተላቆ የመሬት በለቤትነት በሚገባ ተረጋግጦ ነበር ። ታድያ   ህወአት /ኢህአደግን የምናሳስበው የኢትዬጵያ አርሶ አደር መሬቱን ያለማል ለልጅ ልጅ ያወርሳል ፣ ህይወቱና የኑሮ ዋስትናው መሆኑን በማወቅ ይንከባከባል እንጁ በቀላሉ አይሸጥም ለምሳሌም ወላይታን ብንመለከት ሄምቤቾ ፤ የአድማንቾ ፤ የወይቦ ቀበሌ ገበሬዎች መሬታቸዉን ሸጠዉ አረካ ወርደዉ ነበር? የኦፋ ሴሬ፤ የዋጃ ቄሮ ፤የኮካቴና ሌሎችም አካባቢ  የሚኖረውረው  ገበሬ  መሬቱን ሸጦ ሶዶ ከተማ ወርዶ ነበር ? ገበሬዉ ቢቸገር እንኳን ዘመዱን ወይም ቅርብ ጓደኛዉን ፈልጎ ለአንድ ወይም ሁለት ዓመት ኮንትራት ይሰጣል ። የወላይታ ቀበሌዎችን እንደምሳሌ  አነሳን እንጂ የትም ቦታ ገበሬዉ የኑሮ ዋስትና የሆነዉን መሬት በቀላሉ አይሸጥም። ይህ እኛ እናዉቅልሃልን የሚሉ የህወሃት ፖለቲከኞች የኢትዮጵያን መሬት ተቀራምተዉ ለዘመድ አዝማድ በማከፋፈል በአቋራጭ ለመክበር ያወጡት ዘዴና አርሶ አደሩን አሳንሶ ማየት ነዉ። ከዛሬ 45 ዓመት በፊት  የወላይታ ተወላጅ የነበረዉ በወቅቱ ከቀዳማዊ ኃይለሥላስሴ ዩንበርስቲ የሦስተኛ ዓመት ተማሪ የነበረው ጀግናዉ ሰለሞን ዋዳ ከዩንበርሲትው በሰርቢስ አገልግሎት ወይላታ ተመድቦ በዚሁ ህይወቱን የሰዋዉ መሬት ላራሹ የሚል መፈክር አንግቦ ነዉ። በታሪክ አጋጣሚ ከወላይታ ህዝብ በአሁኑ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር የሆኑት በተቃራኑው የኢትዬጵያ ህዝብ እስትንፋሱና መሰረታዊ ጥያቄው የመሬት ባለቤትነት ጥያቄ መሆኑን በመረዳት ከሰፊው ህዝብ ጎን መቆም ተስኗቸዋል ።

የኢትዮጵያ ህዝብ አንኳር ጥያቄ የአንድ ብሄር የበላይነት ይቁም ሲሆን እርስዎ ግን የብሄር የበላይነት የለም ይሞግታሉ ! በማሳያነትም በአጭሩ ቢገለጽ  የመከላከያ ኢንጂኔሪንግን የሰዉ ሀይል ብንወስድ ከዘበኛ ጀምሮ እስከ ከፍተኛ ባለስልጣን ቢመለከቱ  ከትግራይ አንድም ሰዉ የቀረ አይመስልም። የደህንነት መስርያ ቤትንና ማዕከላዊ ምርመራን ገራፊዉ፤ አሳሪዉ፤ አዛዡ ሲቪል ልብስ ለብሰዉ በየመንገዱ ዜጎችን አፍኖ ወዳልታወቀ ስፍራ ወሳጁ ከእርስዎ አጃቢዎች ጀምሮ እስኪ አስተውሉ! የኢትዬጵያ አየር መንገድ 80% ሠራተኞችስ? ቴሌኮም ፣ የኢትዬጵያ ቴለብዥንና ራድዬስ ?

በሌላ በኩል በየፕሮጀክቶች ተቋራጭ የሆኑት፤ ዕቃ አቅራቢዎችና የመጓጓዣ ከባድ መኪና በለ ንብረቶች በሙሉ የአንድ ብሄር ተወላጆች አይደለምን? ለምሳሌ የወይጦ ስኳር ፋብሪካን እናንሳ አንድ የትግራይ ተወላጅ ግለሰብ እስከ 100 ከባድ መኪና ወይም ሎው ቤድ አለዉ። ይህ ከየት እንደመጣ ያጣራ ከፍል አለን?  ከጀቡቲ ወደብ መሃል አገር የኮንስትራክሽን ዕቃ የሚያመላልሱ የማን ተሽከርካሪዎች የማናቸው? አዲስ አበባ ካሉት ከፍተኛ ፎቆች አብዛኛዎቹ የህውሃት በለሥልጣንና ዘመድ አዝማዶቻቸው እንዲሁም በጋብቻና በአምቻ የተገናኙ ግለሰቦች ሀብት መሆናችው አይታወቅምን? ይህ ነው ይህች ሃገር የማን ናት አስብሎ የዜጎች እኩልነት የለም የሚያሰኘን። ከዚህም በላይ ኢህአዴግ እራሱ በየጊዜዉ በሚያካሂደዉ የምክር ቤትም ሆነ ሥራ አስፈጻሚ ስብሰባዎች ስለመልካም አስተዳደር እጦት ስለ ኪራይ ሰብሳቢነት ያነሳል ብልሹ አሰራረም እንዳለ በየመግለጫዎ በተደጋጋሚ ያስቀምጣል።

ኪራይ ሰብሳቢነት ችግር እንደሆነና ለመታገል አቅጣጫ ተቀምጧል ሲባል ቆይቷል። ሆኖም እየተሻሻለ ሳይሆን እየባስ ሄዷል። ኢሃዴግ ቁልፍ ችግር እንጂ ቁልፍ መፍትሄ ለኢትዬጵያ ህዝብ አልፈጠረም። ለህዝባችን ጥያቄ  ቁልፉ መፍትሄ 1ኛ) የመሬት ባለቤትነትና ንብረት ማፍራት 2ኛ) ነጻ ፕሬስ፤ 3ኛ) ነጻ ምርጫ፤ 4ኛ) የህግ የበላይነት፤ 5ኛ) በሰላማዊ ሰልፍም ሆን በተለያዩ መድረኮች ያለመሸማቀቅ ሃሳብን በነፃ መግለጽ  6ኛ) ከተቃዋሚ ፓለቲካ ድርጅቶች በጠረጴዛ ዙሪያ ተቀምጦ መነጋገርና ፖለቲካ ምህዳሩንም ማስፋት፤ 7ኛ) የመንግስ ባለስልጣናትና የፖልቲካ ድርጅት አመራርና አሰራርን መለየት፤ 8ኛ) በአገሪቱ መተማመንን ለመፍጠር ሁሉንም የፓለቲካ እስረኞች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ መፍታት ሌሎችን ማሸማቀቅና ማሰርን ማቆም።

፫) ዉድ እናት ሀገራችን ኢትዮጵያ በአሁኑ ጊዜ አሳሳቢ በሆነ መስቀለኛ መንገድ ላይ መሆኗን በመገንዘብ ካላይ ያስቀመጥናቸዉን ሁኔታዎች በጥልቀት አይተን የሚከተለዉን የአቋም መግለጫ አዉጥተናል።

1ኛ) ከአንደኛ  ደረጃ ጀምሮ በታሪክና በጂኦግራፊ ስንማር ወልቃይት ጠገዴ የጎንደር እንጂ የትግራይ ሆኖ ስለማያዉቅ ለበርካታ ግዜያት ከትግራይ ተወልደዉ የትግራይ ክፍለ ግዛት ገዠና አስተዳዳሪ የነበሩት ራስ መንገሻ ሰዩም በመሰከሩት መሰረት የወያኔ እንካ ሰላንተያ ቆሞ የአማራ ህዝብ ጥያቄ ተገቢዉን ምላሽ እንዲያገኝ እንጠይቃለን፤

2ኛ) የወያኔ ሰራዊትና የደህንነት ኀይል በሰላማዊ መንገድ እምነቱን ለመግለጽና የእሬቻ በአልን ለማክበር በወጣዉ  ህዝብ ላይ ያደረሰዉን ጭፍጨፋ የሰዉ ዘር ማጥፋት ድርጊት በመሆኑ በጣም አዝነን እያለቀስን ይህን አረመኔያዊና ሴይጣናዊ ተግባር አጥብቀን እናወግዛለን፤

3ኛ) የወያኔ ሰራዊት በአማራ፤ በኦሮምያ፤ በጋምቤላ፤ በኮንሶና፤ ወዘተ የሚያፈሰዉ የንጹሃን ኢትዮጵያዉያን ደም የወላይታ ህዝብ ደም ስለሆነ ደርጊቱን እናወግዛለን፤

4ኛ) ሰሞኑንም በዲላና አካባቢው ብዙ ብሔረሰቦች በሰላምና በፍቅር ይኖሩ የነበሩት ሃያ አምስት ዓመታት ህዋአት ኢህአዲግ አገዛዝ በረጨው የዘረኝነት መርዝ ሳቢያ እርስ በርስ መጠቃቃታቸውንና በዚህም የንጽሐን ወገኖቻችን ህይወት  ማለፉና የአካልና የንብረት ውድመት መድረሱ እጅግም ልባችንን ነክቶታል ። አገዛዙም  የተቃጣበትን አገራዊ እምቢተኝነት ትኩረት ለማዛባት ሲል ራሱም ጭምር የለኮሰው መሆኑን በአሜሪካ ድምጽና ሌሎች መገናኛዎች ከሥፍራው ከተጠቂዎች አንደበት ስንሰማ በእጅጉ እያዘንን ድርጊቱን በጽኑ እናወግዛለን።

5ኛ) በአሁኑ ጊዜ የኢትዮጵያ ጠ/ሚኒስትርና የኢሃዴግ ሊቀመንበር የሆኑት የወላይታን፤ የሲዳማን፡ የጋሞን፤ የቁጫን፤ የኮንሶን ደም ያፈፈሱትን የመካላከያ ሠራዊት ሲያዙ ቆይተዉ ይህ ሳያንስ አሁን በመላ ኢትዮጵያ የተነሳውን የመብት ፣ የነጻነትና የህዝባዊ እምቢተኝነት ጥያቄ ለማዳፈን ጦር አዘዋል ፣ ይህንን ለማርገብ ያገባናል ከሚሉ ኃይሎች ጋር በጠረጴዛ ዙሪያ  ውይይት አገሪቱን ከእልቂት ማዳን ሲቻል ይባሱኑ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በማውጣት በህወአት ወታደራዊ መዳፍና የደህንነት ኮማንድ ፓስቴ አፈናውን ለማስፋት መወሰኑ ስላሳሰበንና ስላሳዘነን በእጅግ እርምጃውን  በጽኑ እናወግዛለን፤ኣ።

6ኛ) ከወላይታ ህዝብ አብራክ ወጥተው ለህዝባቸዉ ጥቅም ሳይሆን ለሆዳቸዉና ለስልጣናቸው አድረው ሰፊዉን ሕዝየሚያተራምሱ ካድሬዎች ነገ በታሪክና በህዝብ ፊት ተጥያቂ ከመሆናችሁ በፊት እጃችሁን ከጥፋት መንገድ በአስቸኳይ እንድታነሱ እንጠይቃለን፤

7ኛ) ሰፊዉ የወላይታ ሕዝብ ትናንትናም ዛሬም ነገም ጅግና ነህ፤ ሃጤሮ አንቼ  የተባሉ የወላይታ ጀግ የመልከኛው ሥርዓት  አንገሽግሾት ህዝብን አንቼ ድርባ በምባለው ተቃውሞ  ዘመቻ ለወላይታ ሕዝብ መብትና ክብር ታግሎ እንድተሰዋ ሁሉ ንብረታችሁንና መሬታችሁን ለመቀማት ለሚመጣውና ለሚያፍናችሁ የወያኔ ካድሬ ጸጥ ብላችሁ እንዳትገዙና ለኦሮሞ፤ ለአማራና፤ ለኮንሶ ሕዝቦች የአጋርነት ድምጻችሁን እንድታሰሙ እንጠይቃለን። በህዝብ እገዛና ድጋፍ ተምራችሁ በተለያዩ የመንግስት ሥራ የተሰማራችሁ ወገኖች በኑሮ ዉድነት መከራችሁን እንድታዩና ልጆቻችሁን የማብላትና የማልበስ አቅም ያሳጣው በፕሮፓጋንዳ ሆዳችሁን እየሞላ ያለዉን የወያኔ ኢሃዴግ አገዛዝ ሕዝቡ እምቢ እንዲል የራሳችሁን አስተዋጽኦ እንድታደርጉ እንጠይቃለን፤

8ኛ) ወያኔ በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ እየፈጸመ ያለዉን ጭፍጨፋ መልኩን ለማስቀየርና ሕዝባዊ ድጋፍ ያለው ለማስመሰል በየቦታው የሚጠራውን የድጋፍ ሰልፍ እንኳን ገደላችሁ ብሎ የሚወጣ የወላይታ ሰው አለመኖሩን በተግባር እንድታሳዩ እንጠይቃለን፤

9ኛ) አምባገነኑ ህወአት ኢህአደግ ሥርዓት በወገኖቻችን ላይ የሚያደርሰውን መጠነ ሰፊ ሰቆቃ አስመልክቶ በአሁኑ ወቅት መላው ዓለም አገዛዙን በማውገዝ ላይ ይገኛል በዚህም ዓለም አቀፉ የሰባዊ መብት ድርጅቶች ፣ የተባበሩት መንግሥታት የአውሮጳ ህብረት ኃያላን መንግስታትን ጨምሮ አሜሪካና በሰሞኑ ኢትዬጵያን እግረመንገዳቸው የነበሩት የጀርመኗ ቻንስለር አንግላ ማርኬም አገዛዙን በመንቀፍ ለፓርላማው እንዲናገሩ የተጋበዙትን በአንድ ድርጅት ለተቀፈደደውየኢትዬጵያ ፓርላማ ንግግር አላደርግም በማለት ቅሬታቸውን ለማሳየት ውድቅ ማድረጋቸውን በጽኑ እንደግፋለን።

10ኛ) እኛም በአሜሪካና ካናዳ የምንኖር ( 69 ) ሰላሳ ዘጠኝ የምንሆን ኢትዮጵያዉያን የወላይታ ተወላጆች አገራችንችንን ከልባችን የምንወድ ከማንኛውም አፍራሽ ሃይል ጋር ግንኙነት ኖሮን ሳይሆን በአገር ቤት የሚገኘው ኢትዬጵያዊ ወገናችን ዛሬም በድጋሚ በአምባነኖችና ጨቋኞች መዳፍ ሥር በመውደቁና አፈናው ፣ ሰቆቃውና ግዲያው ህዝባችን ሊሸከመው ከሚችለው በላይ በመሆኑና ትዕግስታችንም በመሟጠጡ የወገናችን ሰቆቃ ሰቆቃችን መሆኑን በመገንዘብ የእዚአብሄር ቃል በመጽሃፍ ቅዱስ በተለያዩ ቦታዎች ለተጎዱ ጩሁ በየቦታዉ ድምጻችሁን አሰሙ ባለዉ መሰረት ድምጽን ለለታፈነው የኢትዬጵያ ሕዝብ አንደበት በመሆን ይህንን መግለጫ በጋራ አውጥተናል።

ኢትዬጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!!!

በአሜሪካና በካናዳ የምንኖር የወላይታ ተወላጅ ኢትዬጵያዊያን!

ሀሳብና ንባብ=== [ክፍል ፩] –አቻምየለህ ታምሩ

$
0
0
achamyeleh

አቻምየለህ ታምሩ

ሀሳብ ማለት በውስጡ እንደ ባሕር ጥልቀት ያላቸው ጉዳዮች የያዘ ቁም ነገር ማለት ነው። ተጨንቆ ያሰናሰለ ሀሳብ ያፈልቃል። አብዛኛው ሃሳብ ደግሞ ልክ እንደ ጉም ነው። ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ከጭንቅላት ተንኖ ሊጠፋ ይችላል። አንዳንዱ ተንኖ የማይጠፋ የሚመስለን ሀሳብ መለስ ብለን ስንመለከተው ቀደም ብሎ ጥሩ ይመስለን የነበረው ቁም ነገር የማይረባ ሆኖ እናገኘዋለን። ትልቅ ቁም ነገር የተሸከመ የመሰለን ሀሳብ ከአፍታ ቆይታ በኋላ ሽምድምድ ያለ ደካማ ይሆናል።

እንዴት ከጥቂት ደቀቃዎች በፊት ዓለምን የሚያበራ የመሰለን አንድ ሀሳብ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ጭልጭል የሚል ብርሃን እንኳን የሌለው ወይንም አይን የሚያቃጥል ጭስ ይሆናል? ብለን ራሳችንን እንጠይቃለን።

ይህ ሁኔታ ሁለት ጥያቄዎችና ያጭራል። የመጀመሪያው ከደቂቃዎች በፊት ተራራ የሚያክል ሀሳብ አጭረን የት እንደገባ ሳናውቀው ተኖ የት ጠፋ? ብለን እንጠይቃለን! ሁለተኛው ደግሞ ከቅጽበት በፊት ተራራ የሚንድ የሚመስለው ሀሳብ እንዴት ሊሽመደመድ ቻለ? የሚለው ነው። እነዚህ ሁለት ተጠይቆች መፍትሄያቸው ምንድነው? ወደሚለውና መናገር ወደምፈልገው የጽሁፌ ክፍል ይወስዱኛል።

ከመፍትሔው በመጀመሪያው ልጀምር።

ኃሳፊነት ለሚሰማው ሰው ጥሩ ሀሳብ አደራ ነው። ጥሩ ኃሳብ አሳልፍ ተብሎ የተሰጠን አደራ ነው። እኛ ውስጥ ብልጭ ብሎ ቢጠፋና ብንረሳው አደራ በላን ማለት ነው። አደራ የበላ ሰው ሊቆጭ ይገባል። «አሁን ይህንን ብል ይሳቅብኝ ይሆን??? በሚል ራሳቸውን የሀሳብ መቃብር የሚያደርጉ አሉ። አብዛኛው ሰው እንደዚያ ነው። አብዛኛው ሰው ጥሩ ኃሳብ በውስጡ እንዲሞት ያደርጋል። የባሱት ደግሞ ይህንን ሀሳብ እንዴት ባደርገው ትርፍ ያመጣልኝ ይሆን ብለው ሌላ ነገር ሲያስቡ ሀሳቡ ይጠነዛል። ይህንን ሲያወጡ ሲያወርዱ ሀሳቡ ከባህር ወጥቶ የቆየ አሳ ይሆናል። ሀጢያት ማለት አደራ የተሰጠን ሀሳብ መግደል ቢሆን ለነዚህ ሰዎች ሲዖል ይገባቸዋል።

ሀሳብ የሚያሳዝን ነገር ነው። ለመኖር ብዙ ነገር አይፈልግም። ሀሳብ አፍ አውጥቶ «አካፍለህ ስጠኝ» ብሎ ህሊናን ይሞግታል። ያለዚያ «እሞትብሃለሁ» ብሎ ይፈታተናል። ያሰናሰለውን ሀሳብ ላያጎል፤ ትርፍ ካላገኝሁበት ብሎ በሀሳብ ታንቆ ሳይተነፍስ ሀሳቡን አንቆ የሚገል ሰው ምህረት ሊደረግለት አይገባም። ይህ ታንቆ የሞተ ሀሳብ ከኒውተን በላይ አለምን የሚያነቃንቅ ሀሳብ ሊሆን ይችላል። አልበርት አንስታይን አሜሪካ ሳይሰደድ ቀርቶ በሂትለር ቢገደል ኖሮ አለምን የለወጠው ሀሳቡ አብሮት ይሞት ነበር።

ስለዚህ አንድ ሰው ለሀሳብ ደፋርና ሩህሩህ መሆን አለበት። ይህ ማለት ያ ሰው ሀሳብ እንደመጣለት፣ ሳይቆይ፣ ሳይጠነዛ ወዲያው ማካፈል ወይንም በወረቀት ማስፈር አለበት ማለት ነው። ያ ከስቅላት የተረፈው ሀሳብ ጥሩ ሊሆን ወይ ላይሆን ይችላል። ይህንን ፍርድ መስጠቱ የሌላው እንጂ የሀሳብ ባለአደራው ፈንታ አይደለም። የሀሳቡ ባለቤት ይህንን ሚዛን ላይ የሚያወጣ ከሆነ ስራ ይበዛበታል። ስለዚህ ያለህን ሃሳብ ያለምንም ማሽሞንመን እንዳለ ከፈነዳ ካንዱ ወዳንዱ ሲሄድ ይጸዳል።

ሁለተኛው የሀሳብ ተንኖ የመጥፋት ጉዳይ ያለመዘጋጀት ችግር ነው።

መዘጋጀት ማለት በአብዛኛው ማንበብ ማለት ነው። አንድ ሰው «አነበበ» ማለት ሀሳብ አፍላቂ ሆነ ማለት አይደለም። አንድ ሰው «አነበበ» ማለት ለሀሳብ ማፍለቅ ሁኔታዎችን አመቻቸ ማለት ነው። ማንም ሰው ሀሳብ ይመጣለታል። ህጻናትም ቢሆኑ ሀሳብ ይመጣላቸዋል። ግን የሀሳብን ጥሩነት ደረጃ በትክክልና በፍጥነት ለመገመት ከቀድሞው አንብቦ መዘጋጀት ያስፈልጋል።

ሀሳብ ማለት መንገድ ላይ የሚገኝ ወርቅ ማለት ነው። ወርቅን ካላወቅን ድንጋይ ብናገኝ ወርቅ ብናገኝ ልዩነት የላቸውም። ስለዚህ ሁል ጊዜ በውቀት የታነጸ የሀሳብ ባለቤቶች ለመሆን ራሳችንን በንባብ ማዘጋጀት አለብን። በንባብ ራሳችንን ካላዘጋጀን ግን ሀሳብ እንኳ ቢመጣልን ተንኖ ይጠፋል እንጂ ጥቅሙን ልናውቀውና ልናደረጀው አንችልም። ወርቅ ብናገኝ ወርቅነቱን ካላወቅን በስተቀር ከድንጋይ ልንለየው እንደማንችል ሁሉ ሀሳብም ያለ ንባብ ጠቀሜታ የለውም። ያላነበበ ሰው አለምን የሚለውጥ ሀሳብ እንኳ ቢያፈልቅ የሀሳቡ አለም ለዋጭነት ሊታወቀው አይችልም። ስለዚህ የምናመነጨውን ሀሳብ ጠቀሜታ ለማወቅ በንባብ የበቃን መሆን አለብን! በንባብ የበቃ ሰው የሀሳብን ክብደት ማወቅ ይቻለዋል።

ይቀጥላል. . .

ድንቄም …”ጥራት ያለው የቴሌኮም አገልግሎት ለሁሉም!!”–ኤልያስ ገብሩ

$
0
0

አቤት ቃላት ማሳመር ሲችሉበት?!
——–

ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ

ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ

ትናንት ረፋድ ላይ ቦሌ መድሃኒያለም አከባቢ ወደሚገኝ ኢትዮ-ቴሌኮም ቅርንጫፍ ቢሮ ለጉዳይ ገባሁ። ጉዳዬም፡- እንዴት የኢንተርኔት አገልግሎት በተግባር ማግኘት እንደሚቻል በግልጽ ባለሙያዎቹን ለመጠየቅ ያለመ ነበር።

አንዲት ሴት የድርጅቱ ሰራተኛ ጋር ተቀምጬ ጥያቄዬን አቀረብኩ። “CDMA ጭራሽ አይሰራም አይደለ?” አልኳት።
“አዎ፣ አይሰራም” መልሷ ሆነ።
“ካለሰራ ታዲያ CDMA ለምን ካርድ (የተለያየ የገንዘብ መጠን ያለው) ይወስዳል?!” ስል ጠየኳት። አፈር እንደማለት ብላ “ይቅርታ አላውቅም” አለችኝ። (ገፋፊዎች አልኩኝ በልቤ።) የአቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ የቴሌ የምትታለብ ላም አገላለጽ እዚህ ጋር በተግባር ትመጣለች።

[አውራምባ ታይምስ ጋዜጣ ላይ ስሰራ፣ አቶ ደብረጽዮን ገ/ሚካኤልን ሻራተን ሆቴል በአንድ ስብሰባ ላይ አግኝቻቸው ለቃል ምልልስ እንደምፈልጋቸው ከነገርኳቸው በኋላ የቢሮ ስልክ ሰጥተውኝ ከ10 ቀናት በኋላ ፈቃደኛ ሆነው እኔና ባልደረባዬ አቤል ዓለማየሁ በጋራ በቢሯቸው ቃለ-መጠይቅ አድርገንላቸው ነበር። “ኢቲዮ-ቴሌኮም የሚያስከፍለው ታሪፍ ውድ በመሆኑ ተቋሙ ዜጎችን ገፋፊ መሆኑ ይገለጻል። ለዚህ ምን ምላሽ አለዎት?” ብዬ ስጠይቃቸው ከተቀመጡበት የምቾት ወንበር ላይ በንዴት ተንስተው ጠረጼዛቸውን መምታታቸውን አስታውሳለሁ። በወቅቱ ከጉኔ የተቀመጠው አቤልም ተረጋጋ ብሎ በእጁ ቆንጠጥ አድርጎኝም ነበር።]

“እና አሁን ዋይ ፋይ ብቻ ነው የሚሰራው?” ስል ባለሙያዋን ጠየኳት። “እሱም እኮ በደንብ አይሰራም። እኛም ለአሰራር ተቸግረናል። …” አለች።

“መቼ ነው በደንብ የሚሰራው?” በማለት የመገረም ጥያቄ አነሳሁባት።
“አላውቅም!” አለች በፍርሃት አዘል ፍጥነት። …ሳንነጋገር ተግባብተናል።

“ስለአሰራችሁ የሚገልጽ ብሮሹር ስጪኝ” ስል በድጋሚ ጠየኳት።
ከተቀመጠችበት ተነስታ “የኢትዮ-ቴሌኮም የተገልጋዮች ቻርተር” የሚለውን በጥራት የተሰራ በለ 42 ገጽ አነስተኛ መጽሃፍ ሰጠችኝ። ከዚህ በላይ ከእሷ ጋር መነጋገር ብዙም አስፈላጊ ስላልነበረ አመሰግናለሁ ብያት ከቢሮው ወጣሁ።

መጽሐፉን ስገልጠው ግን እንዲህ የምታዩትን የተቋሙን ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አንዷለም አድማሴ መልዕክት አንብቤ በማዘን ፈገግ አልኩ።

አቤት ቃላት ማሳመር ሲችሉበት?! ….ሌላ ምን ይባላል …

1

ሳምሶን ማሞ የሕገወጥ ሰንደል ኣምራች እና የሕገወጥ ኣገዛዝ መስላል

$
0
0

b922e6286-1አርዓያ ተስፋማርያም

ሰበታ መግቢያ ስትደርስ ወደቀኝ ታጥፈህ በግምት 500 ሜትር ገባ ብለህ በአንድ ሺህ ካሬ ሜትር መሬት በቆርቆሮ ታጥሮ ታገኛለህ። በግቢው በቆርቆሮ የተገነባው መጋዘን መሰል ውስጥ…ህገወጥ ሰንደል ይመረታል። ከህንድ መጣ እየተባለ ነው የሚታዋወቀው። እናቶች በወር በማይረባ ደመወዝ አደገኛውን ኬሚካል በእጃቸው ሲያቦኩና እንጨቱ ላይ ሲጠቀልሉ ይውላሉ።

የዚህ ህገወጥ ድርጅት ባለቤት ሳምሶን ማሞ እንደሆነ በሚገባ አውቃለሁ። ታናሽ ወንድሙ ነው ስራውን የሚመራው። በአካል ተገኝቼ አይቼዋለሁ። ሳምሶን አንድ ካሬ ሜትር አልወሰድኩም ብሎ ሲቀጥፍ ገረመኝ። እሱን ጨምሮ ሌሎች ጋዜጠኞችና አርቲስቶች በነፃ ሰበታ ላይ መሬት የወሰዱት በአንድ ባለስልጣን ትእዛዝ ነው።

በኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ ኣስጊና ኣደገኛ መሆኑን የኣሜሪካ የውጪ ጉዳይ መስሪያ ቤት ለዜጎቹ ኣወጀ

$
0
0

በኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ ኣስጊና ኣደገኛ መሆኑን የኣሜሪካ የውጪ ጉዳይ መስሪያ ቤት ለዜጎቹ ኣወጀ።በኣሜሪካ ዲፕሎማቶችና በወያኔ ሰዎች መካከል የተጀመረውን ውይይት ኣስታኮ መስሪያ ቤቱ እንዳለው እጅግ ኣስፈላጊና ኣስገዳጅ ጉዞ ካልሆነ በቀር በፍጹም ዜጎቹ ወደ ኢትዮጵያ እንዳይሄዱ ኣስጠንቅቆ ተናግሯል።

et-maphttp://www.zehabesha.com/ethiopia-travel-warning-u-s-department-of-stat/

 

 

 

Viewing all 8745 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>