Quantcast
Channel: ዘ-ሐበሻ – Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 8745 articles
Browse latest View live

መድረኮቻችንን ከሃይማኖታዊ ቅኝቶች እናርቅ!- ኡመር ካሊድ

$
0
0

religionኢትዮጵያውያን ዛሬ ላሉብን ችግሮች ጅማሮው ትናንት ህውሃት ስልጣን ከያዘ ጀምሮ የመነጩ ናቸው የሚል መደምደምያ ላይ የሚያደርሰን አመክንዮ ያለ አይመስለኝም። ያ ከሆነ ዘንድ ከዛም ቀደም ሲል ችግሮቹ ነበሩ ወደ ሚል ይወስደናል። ታድያ እዚህ መሰረታዊ ሃሳብ ላይ ከተስማማን ደግሞ ችግሮቻችን ምን ምን ነበሩ ወደ ሚሉት ዝርዝር ጉዳዮች በሂደት ያሸጋግረናል ማለት ነው። ይህን ተከትሎ ችግሮቻችንን በመቅረፍ ላይ መተማመን መድረስ ሌላኛው ሂደት ነው። በዛም አያበቃም ቀጣዩ እርምጃ በጋራ ተሳስበን እና ተከባብረን ልንኖርባት ስለምናስባት የጋራ ሃገር የጋራ የሆኑ እሴቶቻችንን ልናጎለብትባቸው የሚያስችሉንን የጋራ መድረኮች ልንፈጥር ግድ ይላል ማለት ነው። እናስተውል。。 የጋራ ቤታችንን ለመገንባት በሚያስችለን ጉዳይ ላይ የጋራ መወያያ መድረክ እና መድረኮች ነው ያልኩት።

እነዚህ የጋራ መድረኮቻችን ደግሞ የፖለቲካው ፣ የስፖርቱ ስብስቦች ፣ የባህል ስብስቦች እና ኤግዝቢሽኖች ወዘተ ተብለው ሊዘረዘሩ ይችላሉ። እነዚህ የእምነት ፣ የብሄር ፣ የቋንቋ ፣ የፆታ እና ሌሎች የአመለካከት ልዩነቶች ጨምሮ እንደተጠበቁ ሆነው በኢትዮጵያዊነት ብቻ ዜጎች ሚስተናገዱባቸው ሊሆኑ ይገባል። እነዚህ ስፍራዎች ደግሞ አግላይ ሳይሆኑ አቀራራቢ ፣ ሚጎረብጡ ሳይሆኑ የተደላደሉ ሊሆኑ ሚገባቸው ቦታዎች ናቸው። እኩልነቱ ከአንደበት አልፎ በውስጣችን ከሰረፀ ማለት ነው። ታድያ እነዚህ ከየትኛውም አድሏዊ አስተሳሰቦች ፣ መገለጫዎች ፣ መንፈሶች ፣ እና በተግባር ከሚገለፁ ጉዳዮች ሁሉ በተቻለ መጠን የፀዱ ሲሆኑ ነው። በዋነኝነት መፍትሄው ደግሞ የእኩል ተሳታፊነት እና አሳታፊነት ሚዛናቸው ሲጠበቅ እና ግልፅነት ሲታከልባቸው ነው። ከየአቅጣጫው አንድነት አንድነት ሲባል በተደጋጋሚ ይነገራል።  አንድነት ማለት ምን ማለት ነው?  አንድነት ስንል ተመሳሳይነት ማለት ነውን ?  አንድነት ለምን ያስፈልጋል ?  አንድነት በምን ላይ ? 。。。ወዘተ ዝርዝር ሃሳቦች ሊነሱ ይችሉ ይሆናል። ሆኖም ዛሬ ግን በነዚህ ዝርዝር ጉዳዮች ላይ ረዥም እና አሰልቺ የሆነ ፅሁፍ ከማስነብባቹ በይደር ትቼ ወደ ዋና የተነሳሁበት መልእክት በአቋራጭ ሃሳቡን መንደርደርያ አድርጌው ልግባ። ብዙ ግዜ አንድነት ስንል ተመሳሳይነት ማለት እንዳልሆነ ልብ ልንል ይገባል። ሰዎች በዘር ፣ በቋንቋ ፣ በሃይማኖት ፣ በፆታ ፣ በመደብ ደረጃ፣ በቀለም እና አካባቢ ወዘተ ቢለያዩም ማሳረግያው የሰው ልጆች ነን አንድ ነን የሚለው ነው። ይህ ጠቅል የወል መጠርያ ሰው የሚለው ቃል ወደ ሃገርም ሲመጣ ሁላችንም ኢትዮጵያውያን ነን ወደ ሚለው ወደ አንድ የወል መጠርያ ሊያደርሰን ይችል ይሆናል። ይህ ማለት የተለያየን አይደለንም የሚል የተዛባ አስተሳሰብን ሊያጭር አይገባውም። ኦሮሞ ኢትዮጵያዊ ፣ ከምባታ ኢትዮጵያዊ ፣ ሃድያ ኢትዮጵያዊ ፣ ስልጤ ፣ አፋር ፣ ትግሬ ፣ ጉራጌ ፣ ሲዳማ ፣ ቀቤና ፣ ሶማሌ ፣ አማራ ኢትዮጵያዊ 。。。 ወዘተ በሚል ሌላ የቡድን መጠርያ ደግሞ የተላበስን ነን። በደርግ ግዜ የወጣቶች ማህበር ፣ የሴቶች ማህበር ፣ የጡረተኞች ማህበር የሚሉ ነበሩ። እነዚህ ማህበራት ያስፈለጉበት አብይ ምክንያት እነዚህ አካላት በጥቅል የወል መጠርያቸው ሰው በሚለው ወይም ደግሞ በሌላኛው መጠርያቸው ኢትዮጵያዊ በሚለው ሊጠቃለሉ ባስፈለገ ነበር። ነገር ግን ወንዶች ከሴቶች ያሏቸው ፍላጎቶች ስለሚለዩ። ወጣቶች እድምያቸው ከገፉ አዛውንቶች ፍላጎቶቻቸው ስለሚለይ ወዘተ ነው። ስለሆነም በኛ በሚሉት ስር በመደራጀት ፍላጎቶቻቸውን ይፈፅማሉ ወይም ያሟላሉ ማለት ነው። ማንነትን የዘነጋ ሁላችንንም እንደ አንድ አድርጎ የሚወስድ የአስተሳሰብ ዝንባሌ እየጎላ ከመጣ ለምናልመው አንድነት ከፍተኛ የሆነ አሉታዊ ተፅእኖ ይፈጥራል። የሌሎችን ማንነት እየደፈጠጠ የራሱን ማንነት እያጎላ የሚመጣው አስተሳሰብ በብዙዎች ዘንድ ተቀባይ የመሆን እድሉ የመነመነ ነው። ይህ ደግሞ ለምናልመው አንድነት ጋሬጣ በመሆን ሁሉም የየራሱን ፅንፍ ይዞ እንዲገለል ያረጋል። ዛሬ ዛሬማ አንዳንዶቻችን በመድረኮች እና ስብስቦች ላይ ሁሉ የመታደም ፍላጎቶቻችን ከእለት ወደ እለት እየሞቱ እንዲመጡ እየተደረጉ ይመስላል። ለዚህም አንዱ ምክንያት ሆኖ የሚታየው የአንድ ወገን የቆየ ወግ እና ልማድ አጉልቶ ለማሳየት በሚደረግ በሚመስል እሽቅድድም ውስጥ ግንባር ቀደም መሪነቱን ዳግም እንዲያንሰራራ የመመኘት ሂደት ስለሚንፀባረቅበት ነው። እርግጥ ነው ሃገራችን የሲሶ መንግስት ከነበረችው ቤተ-ክርስትያን ከተገነጠለች የ40 አመታት እድሜ ብቻ ነው ያስቆጠረችው። ቢሆንም ዓለም እየተጓዘበት ያለበትን የሴኩላር አስተሳሰብ ፍጥነት መከተል ጀምርያለሁ ካለችም ያው እሩብ ክፍለ ዘመን ቢሞላም ገና ከራሳችን ጋር የተዋሀዳ አይመስልም። ሆኖም ግን ይህ የሴኩላር አስተሳሰብ መሰረታዊ ፅንሰ ሃሳብ ሃይማኖት እና መንግስት የተለያዩ ናቸው የሚለው ነው።

መንግስት በእምነት ጣልቃ አይገባም እምነትም በመንግስት አሰራር ጣልቃ አይገባም ሲሆን የመንግስት መዋቅር ውስጥ ያሉ ግለሰቦች እምነት አልባ ይሆናሉ ማለትን አያሳይም። ሌላኛው ገፅታው ደግሞ የአንድ ሃገር ዜጎች ከነሱ የተለዩ እምነት ያላቸውን ዜጎች እምነት ፣ ባህል እና ወግ አክብረው እና እውቅና ሰጥተው በመከባበር ላይ መኖር ሲችሉ ነው። መንግስት ከሚያረቃቸው ህጎች በተሻለ ዜጎች በሚያጎለብቷቸው የመቻቻል ባህሎች ሰላም የተሻለ ዘላቂ ነው። ይህ መሰረታዊ የሴኩላር ህሳቤ እንደ ኢትዮጵያ የሃይማኖቶች ብዝሃነት ባሉባቸው ሃገራት ውስጥ ብቸኛው ዴሞክራስያዊ የመንግስት መዋቅር መፍጠር የሚያስችል የተሻለ መንገድ ነው የሚል እምነት አለኝ። ይህ ማለት ታድያ ሰዎች እምነት አልባ ብቻ ሆነው ወደ ፖለቲካ መድረኮች ይግቡ የሚል እንዳልሆነ ልብ ሊባል እወዳለሁ።

እንደ ኢህአዲግ / ህውሃት የተለያዩ ሳንቃዎችን በመደንቀር ሙስሊሙን ዛሬ ከፖለቲካ እንደሚያገለው ሁሉ አንዳንድ የፖለቲካ መድረኮችም ሂድ አትበለው እንዲሄድ አድርገው ብሂልን በመከተል የመግፋት ስራ ሲሰሩ የምናስታውስበት ግዜ እሩቅ አልነበረም ዛሬም እያገረሸ ይመስላል። የልብ መሻከር እንዳይኖር እና በእምነታችን ተከባብረን እንድንዘልቅ የፖለቲካ እና ሌሎች ማህበራዊ ስብስቦች እንደ ስፖርት በአላት ወዘተ ከቤተ እምነቶች ሰበካ ፣ መንዙማ እና ቅዳሴ ማፅዳት ያስፈልጋል። ስብስቦቻችን በነሱ ባይባረኩ ምንም የሚጎላቸው ነገር አይኖርም። ተባርከውም የተጨመረ ነገር የለም ። በመባረካቸውም ሳብያ ከጭቅጭቅ አልዳንም ፣ ልዩነቶችን ከማጉላት አልተቆጠብንም ፣ ፍትህ እና ሰላምም አልሰፈነም። ስለሆነም መድረኮቻችንን የሰበካ እና የቤተ እምነቶች ግቢ ከሚያስመስላቸው አሰራር ማፅዳት ያስፈልጋል ባይ ነኝ። ሰሞኑን ያጋጠመኝ አንድ ክስተት ይህን አምርሬ እንድቃወም ምክንያት ሆኖኛል። በስዊዘርላንድ በምትገኝ አንድ ከተማ በተደረገ ስብስብ ላይ ተገኝቼ ነበር። ስብስቡ ለኢትዮጵያውያን በሃገር ጉዳይ ላይ ፖለቲካዊ ንቃተ-ህሊና(political awareness)ን የማጎልበት እና የመፍጠር ዘመቻ ላይ ያተኮረ ነበር። በሂደቱ እንደ አንድ የመድረክ ተጋባዥ(Panellist)ሆኜ ቀርቤ ነበር። የውይይት ርእስ ይሆናል ተብሎ የተነገረኝ ጉዳይ “የእምነት ተቋማት በመብት ዙርያ ሊኖራቸው ስለሚገባ ድርሻ” በሚል ሃሳብ ላይ ያጠነጠነ ነበር። በትክክል ቃል-በቃል አላስቀመጥኩት ይሆናል። በዚህም ስብሰባ እኔ የእስልምና እምነት ተከታይ እንጂ የሃይማኖት አባት /ሸህ አይደለሁም ብዬ ለጋባዦቼ ምላሽ ሰጠሁ። እንደ እምነት አዋቂ ሆኜ እንዳማልናገር አስረገጥኩ። ሆኖም እንደ እምነቱ አማኝ ሆኜ ግን በፖለቲካ እና ሰብአዊ መብቶች ጉዳይ ላይ እንደሚጨነቅ አንድ ኢትዮጵያዊ አክቲቪስት ልቀርብ እችላለሁ በሚል ፈቃደኛ ሆኜ ቀረብኩ። መድረኩን ያዘጋጁት ወጣቶች ቀናኢነት እና ያላቸው ቁርጠኝነት እንዲሁም መስተንግዶው ይህ ነው ተብሎ በቃላት የሚገለፀ አይደለም።

እንዲሁ ግሩም ነበር ብቻ ባይበቃውም 。。እንለፈው። የነዚህ ወጣቶች አላማ ግልፅ እና ግልፅ ለመሆኑ አያጠራጥርም። ሆኖም በተለያዩ መድረኮች ላይ ጎልተው እንደሚወጡት ሁሉ መድረኮቹን በቅዳሴ መጀመር ብቻ ሳይበቃ ቤቱን ሁሉ በመዝሙር ወደ ቤተ-እምነትነት የለወጡት የእምነት አባት ግን እጅግ አሳዝኖኛል። በእርግጥ ብዙ ክርስትያኖችም ደውለውልኝ ማዘናቸውን ሳይሸሽጉ የገለፁልኝም አሉ። ቀርቦላቸው የነበረው ጥያቄ ሌላ ሆኖ እርሳቸው ያደረጉት ሰበካ እና ዝማሬ እኔ ፈጣሪ አለ ብዬ ማምነውን እንዲህ ካበሸቀኝ ፈጣሪ የለም ብሎ ከኔ እና እኔን ከመሰሉ አማኞች ጋር በጋራ እንወያይ/እንምከር ብሎ የመጣው እምነት አልባው ኢትዮጵያዊ እንዴት እንደሚበግን አሰብኩት። ይህ እኔ በግሌ የታዘብኩት ሂደት ግን አዲስ ክስተት አይደለም። ”የኛው ኢሳት የህዝብ ጆሮና አይን“ በየሄደበት መድረክ ሁሉ አስባርኮ እና አስቀድሶ የሚያስከፍተው ዝግጅቱ ሁሉም የሚያውቀው እውነታ ነው።

በአውስትራልያ የተለያዩ ግዛቶች ፣ የካናዳው ሰልፍ ፣ ሰሞኑን በአማራ እና ኦሮሞው ክልል በህውሃት ጥይት ለተጎዱ ተጎጂዎች በተደረገ የእርዳታ ማሰባሰብያ ጥሪ ፕሮግራሞች ያው ተመሳሳይ ሂደቶች ናቸው። ግን ለምን እስከ መቼ ? እዚህ ጋር ግልፅ ላረገው ምፈልገው ተቃውሞዬ እነዚህ እምነቶች መስጅድ እና ቤተ ክርስትያን አለላቸው እዛ ይስበኩ ነው። እኔ የተለየ እምነት ያለኝን ኢትዮጵያዊ ከኔ የተለየ እምነት ካለው ኢትዮጵያዊ ጋር ብሎም ከማያምነውም ጋር የምገናኝበት ነጻ መድረክ ነው ልቀቁልን የሚል ጥሪ ነው። የወል ጉዳዮች አሉን ስለሆነም እነዛን በነጻነት እና የኔም የሱም ሌሎች መገለጫዎች እሽቅድድም ውስጥ ሳይገቡ በገለልተኛ ቦታ ላይ በነጻነት እናውራበት እንጂ የሃይማኖቶችን ቃኖና ከመቃረን ጋር እንዳልሆነ ልብ በሉልኝ። በተመሳሳይ ሁኔታ ሰሞኑን በቪዥን ኢትዮጵያ እና ኢሳት ዙርያም የተነሳው አነጋጋሪ ጉዳይም ተመሳሳይ ነው። ምን አልባት አንዳንድ ሰዎች ጉዳዩን በማጠፍ ስብስቡ የሃይማኖት አይደለም የሃገር ጉዳይ ነው ወዘተ በሚል ቁንፅል እውቀት የሰሞኑን ቁጣ ሊያጠለሹት ይሞክሩ ይሆናል። መጠኑ ላይ ልንነጋገር እንችል ይሆናል ነገር ግን ጉዳዩ አዋራ ማስነሳቱ አግባብነት ያለው ነው የሚል እምነት አለኝ። ከዚህ ቀደም በተደረገው የቪዥን ኢትዮጵያ ሁለተኛው ዙር ስብሰባ ላይ ተመሳሳይ ወቀሳዎች አልተነሱም ነበር። ዛሬ ለምን? የሚለውን ጥያቄ መጠየቅ አግባብነት ያለው ይመስለኛል። ፕሮፌሰር መሳይ ከበደ በባለፈው ማርች በተደረገው የቪዥን ኢትዮጵያ ስብስብ ላይ የተናገሩት እጅግ ቁልፍ ሃሳብ ነበር። ይህም ሃሳብ “የዘውግ ፖለቲካ (የብሄር ፖለቲካ) ባለባቸው ሃገራት ሊበራል ዲሞክራሲ ብቻውን በቂ ምላሽ አይሰጥም ከዛ በተጨማሪ ውክልናን የሚያረጋግጥ ሂደት ያሸዋል” በሚል ያስቀመጡት አንኳር ነጥብ ነበር። አዘጋጆች ይህን ቁልፍ ንግግር እንዴት እንደዘነጉት አላውቅም። ይህ መሰረታዊ መርሆ በየትኛውም መልኩ ሊጣስ ሲታሰብ የሚያስከትለው አፀፋዊ ምላሽ መኖሩ እምብዛም አይገርምም።

እዚህ ጋር የእምነት ተዋፅኦን ከግምት ያስገባ ይሁን ሲባል እና የእምነት ተቋማት በስብስቡ ይገኙበት ማለት ሁለቱ እጅግ የተራራቁ ጉዳዮች ናቸው። የእምነት ተቋማት እንደ ማንኛውም የሙያ ይሁን ሌሎች የማህበራት ስብስብ የተወሰነ ድርሻ ሊኖራቸው ይችል ይሆናል። ነገር ግን ሃገር አቀፋዊ ጉዳዮች ላይ የሚመክሩ የፖለቲካ መድረኮች እና ጉባኤዎች ግን የሁሉንም ውክልና ያንፀባረቁ ሊሆኑ ይገባል ሲባል ግን የተለየ ነው። ለምሳሌ የቪዥን ኢትዮጵያ ስብስብ መድረኩ የብሄር ስብስብ ጉዳይ ሚወራበት ስለሆነ አይደለም የብሄር ተዋፅኦው ይጠበቅ ሚባለው። እንደዛች ሃገር አንድ የማህበረሰብ ክፍል የዛን ብሄር ፍላጎት ፣ ስሜት ፣ እና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮችን የሚመለከቱ በግንባር ቀደምትነት እነሱ ስለሆኑ ነው። የዛን ማህበረሰብ ፍላጎት እና ጥቅም የሚያስጠብቁት ነገሮችን በቅርበት በመሳተፍ እና በቅርበት ጉዳዩን በማየት ነው ። የእምነት ተዋፆኦንም ከግምት ያስገባ በሚባልበት ግዜ እንደ ብሄሩ ሁላ የእምነቱንም ተከታዮች ፍላጎት እና ጥቅም ከግምት ያስገባ ስለሚሆን ነው።

ስለሆነም የፖለቲካ መድረኮቻችንን ከእምነት የሰበካ ቦታ በማፅዳት ሴኩላራዊ በማድረግ እና የጋራ እ ሴቶቻችንን በጋራ ፣ በእኩልነት እና በመተማመን በመገንባት የኔነት ስሜቱን ፈጥረን ወደ እውነተኛ አንድነት እና መቀራረብ እንጓዝ። የህዝቦችን ውክልና ማስተናነስ ወይም ቦታ ያለመስጠት ደግሞ ለዘለቄታዊ የፍትህ መጓደል አደጋ ይሆናል። ሰላም እና መረጋጋት ብሎም ለምንሳሳላት ሃገራችን ከቃላት በዘለለ እና በውስጣችን በሰረፀ እኩልነት ላይ ተመርኩዘን መጻኢት ኢትዮጵያን ዲሞክራስያዊ እና ፍትሃዊ ልናደርጋት ግድ ይለናል።


ለወያኔ እድሜ ማራዘሚያ በተዘጋጀ መድረክ  ተቀዋሚዎች ምን ይሰራሉ ?  –ይገረም አለሙ

$
0
0

Tensaye የፖለቲካ ድርጅት  የመገናኛ ብዙሀን ባለቤት አንዳይሆን የመከለክለውን  ህግ በመተላለፍ ወያኔ ያቋቋመው  ፋና  ሰሞኑን አንድ  የውይይት መድረክ አዘጋጅቶ ነበር፡፡ ውይይቱን  በቀጥታ ስርጭት ሳይሆን ለእኛ ይገባቸዋል ብለው የመጠኑልንን አቀናብረው አስተላልፈውልን ተመልክተነዋል፡፡ ጽሁፍ አቅራቢዎቹ ተወክለው ይሁን ወክለው ባይታወቅም ከምሁራን ከባለሀብት ከተቀዋሚና ከኢህአዴግ ተብለው ነው የቀረቡት፡፡ ከኢህአዴግ አቶ በረከት ከተቀዋሚ አቶ ልደቱ፡፡ ዶ/ር መረራንና ኢ/ር ይልቃልን ጨምሮም ጥቂት የፓርቲ ሰዎችንም በአዳራሹ ተመልክተናል፡፡ የባለሀብቶች ተወካይ የተባሉት ጽሁፍ አቅራቢ   ለመድረኩ መዘጋጀት ምክንያት በሆነው ህዝባዊ አመጽ ለተገደሉት ሀዘናቸውን በመግለጽ ብቸኛ ሰው ሆነዋል፡፡ ከዚህም ሌላ  ኢህአዴጎች መታደስ ሳይሆን ፈርሶ መሰራት ነው ያለባችሁ በማለት ፖለቲከኞቹ ያልደፈሩትን ተናግረዋል፡፡ አቦ እግዜአብሄር ይባርክዎት፡፡

ተቀዋሚ ፖለቲከኞች በሀገራዊ ጉዳይ ላይ ምክክር በሚደረግበት በማናቸውም መድረክ ተጋብዘው አይደለም ራሳቸው ጠይቀው ሊገኙ አንደሚገባ አምናለሁ፡፡ ነገር ግን በተለያየ ግዜ የወያኔን ግብዣ ፋይዳ ቢስ እያሉ አለመቀበላቸውን ሲነገሩን  የነበሩ ሰዎች  የህውኃትን  ህልውና ለመታደግ በተዘጋጀ በዚህ መድረክ ላይ መታየታቸው ለምን አሰኝቷል፡፡

በዚህ መድረክ  መገኘት ያለባቸው ሰዎች ወያኔ  በጥገናዊ ለውጥና በጥልቅ ተሀድሶ ራሱን አርሞ  በሥልጣኑ አንዲቀጥል የሚሹና ምክር ሰምቶ  የሚታዘዝለትንም መድሀኒት ወስዶ ለህዝብ ጥያቄ ተገቢና ትክክለኛ መልስ መስጠት ይችላል ብለው የሚያምኑና  ምክር ለመለገስና መድሀኒት ለማዘዝ የተዘጋጁ መሆን አለባቸው፡፡

ከዚህ አንጻር  የተቀዋሚ ተወካይ በሚል ሽፋን ጽሁፍ ለማቅረብ የበቃው አቶ ልደቱ  ተገቢ ቦታው ላይ ነው የተገኘው እላለሁ፡፡ ከተሰብሳቢው በኩል ሆነው ሲናገሩ ያየናቸው  ዶ/ር መረራና ኢ/ር ይልቃል ግን ያለቦታቸው ነው የተገኙት ብየ ስላመንኩ ለምን የሚል ጥያቄ አነሳለሁ፡፡ ከስሜት ሳይሆን ከምክንያት ተነስተን መድረኩ የሚገባቸውንና ያለ ቦታቸው የተገኙትን ለይቶ ማወቅና የመገኘታቸውን አንዴትነት መረዳት የህዝቡን ትግል ቀጣይ ተግዳሮቶች ለመለየት የሚያስችል  ይሆናል፡፡

አቶ ልደቶ ፤

አቶ ልደቱ ከተቀዋሚ ፓርቲ ተብሎ ከመነገሩ በቀር ተቃዋሚዎችን አይደለም አባል የሆነበትን ኢዴፓን ስለመወከሉ አልተገለጸምና አነጋጋሪ ሆኖ የሰነበተው ንግግሩ የግል አቋሙ ይሁን   የኢዴፓ አልታወቀም፡፡ ፓርቲውም አላስተባበለም፡፡ የተገኘው በግሉም ይሁን በኢዴፓ መድረኩ የሚመጥነው ነውና  በተገቢው ቦታ ነው የተገኘው ፡፡ይህን ደግሞ ከተመደበለት  በላይ 10 ደቂቃ አስጨምሮ ለ40 ደቂቃ ባሰማው ንግግሩ  ያረጋገጠው ነው፡፡  አቶ ልደቶ በብዙ መንገድ ወያኔን አድንቆና አጀግኖ የህዝቡን ትግል አናንቆና ወያኔን በሚገባው ቋንቋ ማነጋገር የሚሉ ወገኖችን አክራሪዎች እያለ በዘለፈበት ንግግሩ አስቀድሞ ለሚያውቁተ የበለጠ ማረጋገጫ ሰጥቷል፡፡ እስካሁን ላላወቁትና በተለይ ከምርጫ 97 ወዲህ ለአቅመ ፖለቲካ ለደረሱት ወጣቶች ደግሞ ራሱን በግልጽ አሳይቷል፡፡ ወያኔዎች በዛ መድረክ ሲያቀርቡት ማንነቱን ተረድተውና ፍላጎቱን አጢነው ይሁን ወይም ለመድረኩ እንዲስማማ አዘጋጅተውት ባይታወቅም የልደቱ አድራጎት ግን ለእነርሱም ሆነ ለራሱ የሚጠቅም አይመስለኝም፡፡ የእነርሱ ፍላጎት ሊጠቅሙትና ሊጠቀሙበት ሳይሆን ለመጨረሻ ሊገሉት ከሆነ ግን የሚሳካላቸው ይመስለኛል፡፡

ትናንት ዛሬ አይደለም በሚል እሳቤ ልደቱ ካደረሰውም ከደረሰበትም ተምሮ ይሆናል የሚል እንጥፍጣፊ አዘኔታና ተስፋ  የነበራቸው ሰዎች ሁሉ አንቅረው እንዲተፉት ያደረገ መድረክ በመሆኑ ፤ለምን በተቀዋሚ ካባ ቀረብክ እንጂ ለምን እዛ  መድረክ ተገኘህ አንዴትስ አንዲህ ለመናገር ደፈርክ ልንለው አይቻለንም፡፡ ወያኔ የራሱ ሰዎች እየጠሉትና እየከዱት ባለበት ሰአት ህዝብ የጠላኝ እውነቱን ሳያውቅ ነው የሚለው አቶ ልደቱ ከወያኔ ጋር ይበልጥ ለመጣበቅ ይህን ያህል መሄዱ ምን ለማግኘት አስቦ ወይንም ምን ቃል ተገብቶለት አንደሆነ ወደ ፊት የሚታይ ይሆናል፡፡

ዶ/ር መረራ

ዶር መረራ የኦፌኮና የመድረክ መሪ ቢሆኑም በዛ መድረክ የተገኙት በየትኛው ፓርቲ ውክልና አንደሆነ ግን አልተነገረም፡፡ በተለይ አንደ ኦፌኮ ሊቀመንበርነታቸው በዛ መድረክ ላይ መገኘት ቦታቸው ነው ወይ የሚል ጥያቄ አንስቶ በቂ ምክንያት ካላቸው እንዲነግሩን አለበለዛም የተገኙት አለቦታቸው እንደነበር አምነው ለወደፊቱ አንዲታረሙ መንገር ያስፈልጋል፡፡ የወዳጅን ስህተት እየሸፋፈኑ ማለፍ ወይንም አትንኩት ብሎ በተከላካይነት መሰለፍ ሰውየውን ጭምር ነው የሚጎዳው፡፡

ከገዳይ አስገዳዮች ጋር በአንድ መድረክ፤

ባሳለፍነው አንድ አመት በኦሮምያ ከአንድ ሺ በላይ ሰላማዊ ዜጎች መገደላቸውን  በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ መታሰራቸውንና ለአካል ጉዳት መዳረጋቸውን ከራሳቸው ፓርቲ ሲወጡ ከነበሩ መግለጫዎች ሰምተናል፡፡ ያ አልበቃ ብሎ ሌላ ግድያ ሌላ አስር ሌላ ማሰቃየት ለመፈጸም የአስቸኳይ ግዜ አዋጅ ታውጇል፡፡  ለዶ/ር መረራ በአንዲህ አይነቱ መድረክ መገኘት  ግድያና እስራቱ መቆምና ያለፈው በገለልተኛ አንዲጣራ ስምምነት ላይ መደረስ ነበረበት፡፡ ነገር ግን ይህ ሊሆን ቀርቶ  የተ.መ.ደ የሰብአዊ መብት ኮሚሽን ጉዳዩን ለማጣራት ላቀረበው ጥያቄ አዎንታዊ ምላሽ ተነፍጎት ባለበት ወቅት ያውም ለህውኃት ትንሳኤ  ሊመክር በተጠራ መድረክ የዶ/ር መረራ መገኘት ምን ለመፈየድ ነው?  ሺዎች ኦሮሞዎችን ከገደሉና ካስገደሉ ሰዎች ጋርስ ምሳ አብረው መብላታቸውን   በመገናኛ ብዙሀን መናገራቸውስ ምግቡ እንዴት ቢዋጠላቸው ነው?  ይሄ መቼም ዲፕሎማሲም ዴሞክራሲም ሊባል የሚችል አይመስለኝም፡፡

ጥያቄአችን የሥርዓት ለውጥ ነው፡፡

የሥርዓት ለውጥ እየጠየቀ ያለውን  የህዝብ ትግል የዶ/ር መረራ ፓርቲ  ባይመራውም  እወክለዋለሁ የሚለው ሕዝብ ጥያቄ ነውና መደገፉ ግድ ነው፡፡ የፖለቲካ ሳይንስ መምህሩ ወያኔ በሥልጣን ላይ እያለ የሥርዓት ለውጥ ተግባራዊ የሚሆንበት መንገድም ዘዴም አለ ካላሉ በስተቀር  ከሥልጣን መልቀቅ የሚጠይቅ ነው፡፡ ታዲያ የሥርዓት ለውጥ እየጠየቁ ለወያኔ እድሜ ማራዘሚያ መድሀኒት ፍለጋ በተጠራ መድረክ ላይ መገኘት ምን ይሉታል ?

ወያኔ አፍ አንጂ ጆሮ የለውም

ዶ/ር መረራ ከሚታወቁባቸው ንግግሮች አንዱ ወያኔ አፍ አንጂ ጆሮ የለውም የሚለው ነው፡፡ ታዲያ ወያኔ የሚናገር አንጂ የሚሰማ ካልሆነ ርሳቸው በዛ መድረክ የተገኙት ወያኔን ለመስማት ነው? ወይንስ በራሱ መድረክ ሲሆን ጆሮ ይኖረዋል ብለው ወይንም የህዝቡ ቁጣ ጆሮ እንዲኖረው አድርጎታል ብለው አምነው ለጥገናዊ ለውጡ ሀሳብ ለመለገስ፡፡ ከላይ ባነሳኋቸውም ሆነ በሌሎች ምክንያቶች የዶ/ር መረራ በፋና መድረክ መገኘትን  ተገቢ የሚያደርግ ምክንያት አላገኘሁምና  አለቦታቸው ነው የተገኙት እላለሁ፡፡ ምክንያት ካላቸው ማስረዳት ከሌላቸው ደግሞ ነገም ሚሆነው አይታወቅምና ተመሳሳይ ነገር በመስራት ለወያኔ ምርኩዝ የሚሆንና ትግሉን የሚጎዳ ተግባር ከመፈጸም ሊታቀቡ ይገባል፡፡ አናለባብስ!

ኢ/ር ይልቃል ጌትነት

ሰማያዊ ፓርቲ ጠቅላላ ጉባኤ አካሂጄ የሊቀመንበር ለውጥ አደርጌአለሁ ማለቱን ሰምተናልና ኢ/ር ይልቃልን በሚመለከት የሚነሳው  የመጀመሪያ ጥያቄ ማንን ወክሎ ነው የተገኘው የሚለው ነው፡፡ ሁለተኛው ብዙ መድረኮችን አልገኝም እያለ መሰረዙን እናውቃለንና ዛሬ ምን ተገኘ የሚል ሲሆን ሶስተኛው በዛ ቦታ መገኘነቱ በተለያየ ግዜና መድረክ ሲናገራቸው ከነበሩትና የፓርቲው አቋሞች ናቸው ብለን ከተቀበልናቸው ጉዳዮች ጋር የሚቃረን መሆኑ ነው፡፡ ጥቂቶቹን አንይ፡፡

ትግሉ የነጻነት ነው፤

በምርጫ 2007 ሰሞን ትግሉ የነጻነት ነው እያለ ሲናገር ሰምተናል፡፡ ይህንኑ አቋሙን በማጠናከርም ካናዳ በሄደበት ወቅት የምርጫ ፖለቲካ አብቅቶለታል ሲል ተናግሯል፡፡ እነዚህም ሆኑ  ሌሎች  ንግግሮቹ የሚያሳዩት የሥርዓት ለውጥ ያስፈልጋል የሚል እምነት አንዳለው ነው፡፡ ወያኔ በስልጣን ላይ እያለ ነጻነትን የሚያቀዳጅ የሥርዓት ለውጥ የሚገኝበትን ዘዴም ሆነ መንገድ  የነገረንም ሆነ ያሳየን የለምና በእስካሁን ግንዛቤአችን የምንረዳው እነ ይልቃል የሥርዓት ለውጥ ሲሉ ወያኔ ስልጣን መልቀቅ/ መወገድ አለበት እያሉ አንደሆነ ነው፡፡  ታዲያ ኢ/ር ይልቃል ለመገናኛ ብዙኃን ፍጆታ የሚናገረውና የሚያምነው የተለያየ ካልሆነ በስተቀር  የወያኔን እድሜ ለማራዘም መድሀኒት ፍለጋ በተጠራ መድረክ ላይ መገኘቱ ምን ለማትረፍ አንደሆነ ግልጽ አይደለምና ምክንያት ካለው ማስረዳት ካልሆነም ዳግም መሰል ድርጊት አንዳይፈጽም በተለይ ወዳጁ አድናቂው ተከታዩ ወዘተ ነን የምትሉ ልትመክሩትም ልትገስጹትም ይገባል፡፡ህዝብ አንዴ አንቅሮ ከተፋ መመለሻ የለም፡፡

ወያኔ የሥልጣን እድሜውን ለማራዘም ይጠቅማል እስካለ ድረስ መድረክ መጋበዝ አይደለም ትንሽ ትንሽ ሥልጣን እስከመስጠት ሊሄድ ይችላል፡፡ በዚህ ወቅት እየተንገዳገደ ያለውን ወያኔ ተጋግዞ ከመግፋት ይልቅ በየግል ፍላጎት ምክንያት በወያኔ ድርጊት እየተታለሉም ሆነ እየማለሉ ጥያቄውን በመመለስም ሆነ ስጦታውን በመቀበል ምርኩዝ መሆን የኢትዮጵያ  ህዝብ በባርነት አንዲኖር ተባባሪ መሆን ነውና ያስጠይቃል፡፡ ስለሆነም ወያኔ ከዚህ በኋላም ብዙ ነገር ሊያደርግ መቻሉን ታሳቢ በማድረግ  ህዝብ በደሙ ያቀለመውን ትግል ማገዙ ቢቀር አንዲኮላሽ ተባባሪ ከመሆን መቆጠብ ይገባል፡፡  ላለፈው ክረምት ቤት ባይሰራም ለመጪው ማሰብ ግን ተገቢ ነው፡፡

 

ሰምሃር መለስ የገባት መተካካት –ተቃዋሚዎች ያልገባቸው መታደስ! –ክንፉ አሰፋ

$
0
0

የአፈና ግዜ አዋጁን ተከትሎ፤ የሕወሃቱ ፋና ብሮድካስቲንግ በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ያስተናገደው “የውይይት መድረክ”  አዳዲስ  ኩምክናዎችን ይዟል። ልደቱ አያሌውን በመሪ ተዋናይነት ያሳተፈውን ይህን  አዲስ የበረከት ስምኦን  ድራማ ብዙም ሰው አላየውም። ሕዝቡ ፋና ሚባል ነገር እንደሬት መርሮታል። ገሚሶች ደግሞ በ “ቃና”ው “ጥቁር ፍቅር” ድራማ ተጠምደዋል። በዚህ ድራማ ልደቱ አያሌው መሪ ገጸ-ባህሪይ ተላብሶ ይተውን እንጂ እንደወትሮው ቀልብ ሊስብ አልቻለም።  በኢትዮጵያ ታሪክ ወያኔ መድብለ ፖርቲን የፈቀደ ድርጅት እንደሆነ በሙሉ አፉ ሲናገር እሱ አላፈረም። ከሱ ይልቅ የተሸማቀቁት እነ በረከት እና ስብሃት ናቸው።  በልባቸው አበስኩ ገበርኩ እያሉ… ጌታዎቹ ሃዘን ሲሰማቸው እሱ ያለቅሳል። በዚህ አቋሙ ከሶስተኛው መንገድ ወደ አንደኛው የተሸጋገረ ይመስላል ልደቱ።  ለነገሩ እንጂንለሱ መገለባበጥ አዲስ ጉዳይ አይደለም!

semere-meles ልደቱ አያሌው ከተቃዋሚ ፓርቲ መሪነት ወደ ልማታዊ ባለሃብት እንደገባ ነበር የምናውቀው – የሃብቱ ምንጩ ግልጽ ባይሆንም። እንደ ፕ/ር ኤፍሬም ይሳቅ የሕወሃት የመከራ ጊዜ ደራሽ እና አስተንፋሽ  ለመሆን መጣሩ አይደንቅም።  ሕዝባዊ አመጹን ማውገዙ ግን ከሃይለኛ ማእበል ጋር አላትሞታል።”ጥናታዊ ጽሁፍ”  ያቀረበው የአስታራቂነትን ሚና ለመጫወት ከሆነም ማስታረቅ፣  የተበደለን ሕዝብ እየኮነኑ አይደለም። ህወሃት ሕዝብን በጅምላ ገድሏል። አንዴ የተገደለውን ሕዝብ ደግሞ መግደል ምን ይሉታል? መጨረሻውን ፈጣሪ ያሳምርለት።

የዚህ ውይይት አላማ ግልጽ ነው።ችግሩን ከመፍታት ይልቅ በግብጽ እና ሻእቢያ ላይ ጣት ማውጣቱ ያዋጣቸው አልመሰለም። ስለዚህ የተወጠረውን  ለማስተንፈስ፣ የተለመደ አቅጣጫ ማስቀየስ፣ እና ሕዝብን ለማዘናጋት መሞከር ከመጣር አልተኙም ። በውይይቱ የተገኙትም አይነተ ብዙ ናቸው። ጉዳዩ የገባቸው፣ ጉዳዩ ያልገባቸው እና ግራ የገባቸው ሰዎች ተሳትፈዋል።

ሃይሌ ገብረስላሴ እና ሳምሶን ማሞ የነበረከት ደባ በደንብ ከገባቸው ተሳታፊዎች ዋነኞቹ ናቸው። የኢትዮጵያ ችግር በውይይቱ እጅግ ተጋንኖ እንደቀረበ በቀልድ እያዋዛ ተናገረ ሃይሌ።  አንዴ ተኑሮ ለሚታለፍባት አለም እንዲህ አጎብዳጅ  መሆን ለምን እንዳስፈለገ አይገባኝም። የማያልፍ ነገር የለም። ይህ ስርዓትም በእርግጠኝነት ያልፋል። እንደ ሃይሌ እና ቀነኒሳ  ያሉ አድርባዮች ይህ ያከበራቸው  ህዝብን  ነገ እንዴት ቀና ብለው እንደሚመለከቱት ወደፊት የምናየው ይሆናል። በፈጣሪ አምሳል የተሰራን ሰው አትግደሉ ብሎ የመርናገር ሞራል ከሌላቸው፣  ዝምታም እኮ መፍትሄ  እንኳን ባይሆን አማራጭ ነበር። ዝምታ ወርቅ ነው። እነሱ ግን እንደበቀቀን ህወሃቶች የሚሉትን  የ”መልካም መስተዳደር” አሲዮ ቤሌማ  ደጋግመው ይዘፍኑልናል።

ሳምሶን ማሞ  ሲናገር  የክበበው ገዳን አዲስ ቀልድ ያስታውሳል።

በአሜሪካ ሃገር ዋይት ሃውስ በር ላይ ቆመህ “ኦባማ ይውረድ”  እያልክ ብትውል የሚነካህ የለም።  ሲባል  የሰማው ክበበው ገዳ እኛስ ሃገር ቢሆን አራት ኪሎ ቤተ መንግስት በር ላይ ቆመህ  “ኦባማ ይውረድ!” እያልክ ብትጮህ ማን ይነካሃል? ብሎ ነበር ክበበው ገዳ።

“እኔ አቶ በረከት ስምዖን ቢሮ ገብቼ እንደፈለኩ ተሳድቤ እወጣለሁ። ይህንን ያህል ነፃነት አለ።” ይለናል ይህ የስርዓቱ ተደጋፊ  ሳምሶን ሞሞ። አዎ ይህ ሰው ይሳደባል።  አቶ በረከትን ቢሮ ድረድ ሄዶ ተሳድቦ ቢሆን ኖሮ ግን 34 ጥርሶቹን አናያቸውም ነበር። ደፋሩ ሳምሶን ባለፈው ሳምንትም በዚሁ መድረክ ላይ ቀርቦ ሕዝብን በጅምላ ተሳድቧል።  አቶ በረከትን ሊሳደብ እንደማይችል ግን ሕጻን ልጅም ይገምታል። የሚደንቀው ታዲያ በስድብ እና በመብት መካከል ያለውን ልዩነት እንኳን አጥርቶ የማያውቅ  ይህ ሰው መድረኩን ይዞት ሲቀልድ ማየቱ ነው። እርግጥ ነው። ዝሆን ላይ የሚጮህ ሞኝ ውሻ ብቻ ነው።  ሆድ ከፊት ለመሰለፍ አይፈራም ይሉ የለ አፍሪካውያን።

ሕዝብ መሬት ላይ ነው። እነሱ ሰማይ ላይ።  መሬት ላይ የተኛ ግዜው እስኪያልፍ ሊረጋገጥ ይችላል። መሬት ላይ የተኛ  እወድቃለሁ ብሎ አይሰጋም። ዛሬ ሰማይ ላይ ያሉት ግን እዚያው አይቀሩም። ነገ መውረዳቸው የተፈጥሮም ህግ ነው።

የመለስ ዜናዊ ልጅ ሰምሃል መለስ ግራ የተጋባች ተሳታፊ ትመስላለች። ግን አጠር ብላ የረዘመች መልእክት አላት። በህወሃት ውስጥ ያለውን የስልጣን ሽኩቻ ብቻ ሹክ ብላ አላለፈችም። ስልጣንችሁን ላለማስነካት ከምትንደፋደፉ ስልጣኑን ለኛ ስጡን ብላለች።

አባትዋ ከማለፉ በፊት ስለመተካካት ብዙ ተናግሮ ነበር። ሰምሃር ይህንኑ ቃል እንደ ፈጣሪ ቃል አምና ተቀብላለች። ይህ ብቻ አይደለም። የህወሃት ስልጣን እንደ ርስትና ጉልት በውርስ እየተላለፈ ይቆያል ተብሎም ተነግሯታል። ጸጉርዋን የሽፍታ አስመስላ ስልጣኑን ከነበረከት ለመቀበል  ብዙ የጠበቀች ነው የሚመስለው።  በዚያ ሰሞን ጠመንጃ ይዛ የቶክስ ልምምድ ስታደርግ የተነሳችው ፎቶም ተለቆ ነበር። ይህም በህወሃት መመዘኛ ከርክክብ ቅድመ ሁኔታዎቹ አንዱ መሆኑ ነው።

የመተካካት እና የቅብብሎሹ ወሬ ከአቶ መለስ ጋር ተቀበሮ በጥልቅ ተሃድሶ አዲስ ዜማ መተካቱን ግን ሰምሃር የሰማች አይመስልም። ይህች ወጣት ስብሰባው ላይ የተሳተፈችው የእናቷ አዜብ ጎላን ሃሜት ይዛ ነው የሚለው ንግግራቸው የሚያስኬድ ቢሆንም፤ መልእክትዋ ግን ግልጽ ነው። እስዋም ገና የለውጥ ሳይሆን የጥገና መፍትሄ ላይ ናት።

እንደ ሰምሃር ነገሮችን ሳያላምጡ እየዋጡ፣  ቅዠት ሁሉ ህልም መስሎ እየታያቸው፤ ሕወሃትን እንደ ንጉሳዊ ስርዓት ለማስቀጠል የሚፈልጉ ደፋሮች  ጥቂት አይደሉም።

ዶ/ር መረራ ጉዲና እና ኢንጅነር ይልቃል በዚህ ስብስብ የተሳተፉበት ምክንያት ግን አልገባኝም። ድራማውን ለማሟሟቅ ከልሆነ በስተቀር የእነሱ በዚያ መገኘት ፋይዳ አይታይም። እርግጥ ነው ሁላችንም ይህንን ውይይት እንድንመለከት ያደረገን የ እነሱ መሳተፍ ነበር።ግና  ከምርጫ ክርክር ግዜ የተናገሩትን ያህል እንኳን በዚህ ውይይት ሲናገሩ አልሰማንም።  እነሱ እዚህ እያወሩ ባሉበት ቅጽበት  አጋዚ ጦር በጠራራ ጸሃይ የቤት ለቤት ዘረፋ፣ አፈና እና አስገድዶ መድፈር ላይ ተሰማርቷል። ከውይይቱ በፊት – እንደ ተቃዋሚ ፓርቲ መሪ  ቅድመ ሁነታዎችን ማስቀመጥ ነበረባቸው።

ሕዝብ ጥገና ወይንም ተሃድሶ ሳይሆን ለውጥ ነው የፈለገው።  ሕወሃት፣ የማይታደስ፣ የማይሻሻል፣  ከስህተት የማይማር እንደሆነ ብዙ ግዜ ነግረውናል። ጅምላ ግድያ እየፈጸመ ካለ ከዚህ ስርዓት ጋር ቁጭ ብለው ዲስኩር ማድረግ ምን ሊጠቅም እንደሚችል ከእኛ በላይ እነሱ ያውቁታል። ሕዝብ እና ሕወሃት የማይታረቅ ቅራኔ በዚህ ወሳኝ ወቅት፣ እነሱ ራሳቸው የውይይት ግዜ አብቅቷል ሲሉ  የሰማን መስሎኝ ነበር።በረከት ስምኦን እና ልደቱ  “ብቃት ያለው ተቃዋሚ ልንፈጥር አልቻልንም” የሚሉን ይህንን እያስተዋሉ ይሆን?

አቦይ ስብሃት እንደተባለው ቀምቅመው መድረክ ላይ ይውጡ እንጂ፣  የሚናገሩት ሁሉ ቅኔ አዘል ነበር። ሰምና ወርቅ ያለው ቅኔ። “መረራ እና ይልቃል ጓደኛሞች ናቸው። የፖለቲካ ፓሪቲ አይደሉም!” ያሉት ያለምክንያት አልነበረም። ያንን ሁሉ ተናግራችሁ ስታበቁ እዚህ በኛ ጉባኤ ላይ ምን ትሰራላችሁ? ማለታቸው ይመስላል።  ሆድ ያባውን ብቅል ያወጣዋል እንዲሉ  ሕወሃት ለፍትህ እንጂ ለድርድር እና ለውይይት የሚቀርብ ስር ዓት እንዳልሆነ ነው የቅኔው ወርቅ የሚጠቁመን። የህወሃት መክሠም እና መጥፋት ምኞታቸው መሆኑን የማብሰራቸው ቅኔ ግን ሰምም ሆነ ወርቅ የለውም።

ሽማግሌው ስብሃት ቀጠሉ “እናንተ ሕዝቡን አታውቁትም። እኛ እንኳን ግማሹን የኢትዮጵያ ሕዝብ አናውቀውም!” ብለው አረፉ።   የማያውቁትን ሕዝብ ለ 25 አመት የሙጥኝ ይዘውት ኖሯል።

“ከፊትህ የሚጠብቅህን መንገድ ለማወቅ ተመላሾቹን ጠይቅ።” ይላሉ ቻይናውያን። ላስተዋለው ትልቅ አባባል ነበር። ለተመክሮውም የደርግ ውድቀት ብቻ በቂ ነው። እነሱ ግን ከታገሉት ደርግ በመቶ እጥፍ ብሰው ተገኙ።  ወትሮውን ቁጭ ያሉበት መጥበሻ ሲግል እንደማሽላ መፈንዳት ግድ ነውና እስከመጨረሻው እስትንፋሳቸው ይናገራሉ። እኛም እንደ ኮሶ እያንገሻገሸን የሚሉትን መስማቱን አልተውንም።

… በሚቀጥለው ጽሁፌ ሰለ አፈና ግዜ አዋጁ እና ሰለ አጋዚ አ የምለው አለኝ። እስከዚያው ቸር እንሰንብት።

 

ሰሚ ያጣ ሕዝብ –ዶ/ር ዘላለም እሸቴ

$
0
0

በሕዝብ ማመላለሻ መኪናዎች ውስጥ የጎጃምና ጎንደር ሙዚቃዎችን መክፈት ተከለከለሕዝብ ተነሳ። ይህ ከወትሮው የተለየ አነሳስ ይመስላል። ከአንዴም ሁለት ጊዜ ይህ ሕዝብ ተነስቶ ሲያበቃ እድሉን ለልጆቹ በአደራነት ሰጥቶ ሲቀመጥ፥ መሪዎቻችን የስልጣን ርክክብ አካሄደው ሕዝቡን በዜሮ እየሰደዱት ስልችቶታል። ቁጭ ብድግ ማለቱ በቃኝ ያለ ይመስላል። አሁን ላንዴና ለመጨረሻ ጊዜ መነሳቱ፥ የስልጣን ርክክብ ለማካሄድ ሳይሆን፥ ዳግም እንደገና መነሳት በማያስፈልገው ሁኔታ ስልጣኑን ራሱ ወስዶ ተረጋግቶ ለመቀመጥ ነው።

ቀድሞ ነገር ባለጉዳዩ ሕዝብ ቁጭ ብሎ መሪዎቻችን ሲተራመሱና ሕዝቡን ራሱን ሲያተራምሱት ምንም ያለማድረጉ በውጭ ለተመልካች ሲታይ ምንም እንደማያውቅ ያስመስለው ይሆናል። እውነቱን ብንመረምር ግን የምናስተውለው ሁሉን አዋቂ እንደሆነና፥ ዝም ያሰኘው ትዕግስቱ መሆኑ በገባን ነበር። የኢትዮጵያ ሕዝብ ሲታገስ መሬት ነው። ይሸከማል፥ ይችላል። ረዥም ጊዜ ይሰጣል። ፅዋ ሲሞላና ጊዜው ሲደርስ ይህ ሕዝብ ጠያቂ ነው። በውጭ ሲታይ ሕዝቡ ጉዳይ ፈፅሙልኝ ብሎ አቤቱታ የሚያቀርብ ይመስላል። ግን አሁን እንደዚያ አይደለም። ቀረብ ብለን፥ አጥልቀን ብናይ ይህ ህዝብ በመልካም አስተዳድሩኝ እያለ መንግስትን እየተማፀነ አይደለም። ደግሞም ስም ጠርቶ እከሌ ይግዛኝ ብሎም እየተሟገተ አይደለም። ሕዝቡ እያለ ያለው ስልጣን የሕዝብ ነውና ለሕዝቡ የስልጣን ባለቤትነቱን የሚያረጋግጥ ድምፁ እንዲሰማ ነው።

መንግስት የሕዝብ ጥያቄ መልስ እሰጣለው ብሎ ጥልቅ ተሃድሶ ላካሂድ ብሎ ተነስቷል። ተቃዋሚ የሕዝብ ጥያቄ እመልሳለው ብሎ ሕገ መንግስት ለማርቀቅ ተነስቷል። በፊት ለፊት የማይታየውን እውነት ለማየት ብንጥር ግን ሕዝብ እያለ ያለው፥ ጊዜው የሁለቱም ተፎካካሪዎች የመምራት ጉዳይ ሳይሆን ሕዝቡ ራሱ የሚመራበት ወቅት መሆኑ ነው። ጊዜው መሪዎቻችን ስፍራቸውን ለሕዝቡ ምሪት የሚለቁበት እንጂ በየፊናቸው በነፍስ ወከፍ ለመምራት ሽር ጉድ የሚሉበት ጊዜ አይደለም። ይልቁንስ ሕዝብ መሪዎቹን ለመምረጥ የስልጣን ባለቤት ሆኖ፥ ድምፁ የሚሰማበትና የሚከበርበትን መድረክ ለማመቻቸት እንወያይና እንግባባ። መንግስትም ሰምቶ ይታዘዝ፥ ተቃዋሚም ሰምቶ ይቀናጅ።

የሕዝቡ ቆራጥነት የትዕግስቱ ውጤት ነው። ጊዜው እስኪደርስ ትዕግስቱ ሲገርም፥ ጊዜው ሲደርስ ደግሞ ቁርጠኝነቱ የሚደንቅ ነው። ውሎ እንዲያድር ፋታ አይሰጥም። በውጭ ሲታይ ለብዙ ጊዜ የታየው ትዕግስቱ አሁንም አለ ብለን እንታለል ይሆናል። ሕዝቡ ከዝምታውና ከመቀመጫው ሲነሳ ቶሎ ብሎ መታዘዝ ማስተዋል ነው። የለመደች ጦጣ ሁልጊዜ ሽምጠጣ ብለን እንደለመድነው እንቀጥል ብንል፥ መሬት የሆነው ሕዝብ እሳት ሆኖ ይበላናል። ስልጣኑን የያዘው የሙጥኝ ማለቱን ትቶ፥ ተቃዋሚዉም ስልጣኑን መቋመጡን ትቶ፥ ሕዝቡ ልምራ ሲል በእሽታ ሁሉም የየግል ምኞቱን ለቆ ይመራ። ለዚህም ዓላማ ይህ ሕዝብ በእውነት የስልጣኑ እውነተኛ ባለቤት የሚሆንበትን መፍትኤ በአስቸኳይ ይመከርበት።

አሁን ልተርክ የተነሳሁት ፊት ለፊት ያለውንና ሁላችንም ያሰለቸንን፥ ግን እውነት ስለሆነው ታሪካችንና ተጨባጭ ሁኔታዎቻችን አይደለም። ደግሞም እውነቱ አድክሞኝ የሌለ ነገር ፈጥሬ አፈታሪክ ለማውራትም አይደለም። ዓላማዬ ፊት ለፊት ከሚታየው እውነት ጀርባ ያለውን ግዙፉን የማይታየውን እውነት አስተውለን፥ የሚገርመውን ነገር እንድናውቅ ነው። እንዴት ማለት ጥሩ ነው።  እንግዲህ ከስር መሰረቱ እንጀምር።

1ኛ/ ሕዝቡ የሚገርም ነው።

የሕዝቡ ማንነት የሚገርም ነው። በመሪዎቻችን ማንነት ሕዝቡ ማንነቱን ተጠልፎ መነጋገሪያ የሆነው የመሪዎቻችን ማንነት ነው። ማን ያውራ ስለ ደጉ ሕዝብ? ማን ያውራ በፍቅር ስለሚተሳሰበው ሕዝብ። ሲራብ አብልቶ፥ ሲጠማ አጠጥቶ፥ አብሮ ተቻችሎና ተጋብቶ ለዘመናት የሚኖረውና የሚያኖረው ሕዝብ ማን ማንነቱን ያራግብለት? ያደከመን በመሪዎቻችን ማንነት ላይ የተመሰረተ የፊት ለፊት እውነት እያወራን ስጋታችን መብዛቱ ነው። ሁሉም ዓላማውን የሚያራምደው ኢትዮጵያን የመሪዎቻችን ነፀብራቅ አድርጎ በመውሰድ ነው። ከላይ ላይ ከሚታየው እውነት ጀርባ የተደበቀውና በጊዜ ተፈትኖ ያለፈው ትልቁ ጥልቅ እውነት ግን የኢትዮጵያ ሕዝብ ቤተሰብነት ነው።

2ኛ/ የሀገር ልጅ የሚገርም ነው።

መሪዎቻችን ሁሉ ሲታዩ ለየቅል ናቸው፦ ኢአዴግ፥ ግንቦት ሰባት፥ መድረክ፥ ሰማያዊ፥ ኦነግ፥ ወዘተረፈ። እንደገና ግልፅ ከሆነውና ከምናውቀው እውነት ጀርባ ያለውን የማይታየውን እውነት ለማየት ብንጥር ሁሉም የሀገር ልጆች ናቸው። ይህም በራሱ ክብር ነው፥ ምክንያቱም ከታላቁ ሕዝብ አብራክ የወጡ የሕዝቡ ልጆች ስለሆኑ ነው። የሀገር ልጆች ስለሆኑም በውስጣቸው ያለው እስከ ዛሬ ያልታየው ችሎታቸው ታሪክ ለመስራት አቅም አለው።

እነዚህ የሀገር ልጆች ድንቅ የሆነው ችሎታቸውና እምቅ አቅማቸው እስካልተገለጠ ድረስ አንዱ ሌላኛውን ለማጥፋት መሮጣቸውን አያቆሙም። ይህ ያልተገለጠው አቅም በውስጥ የሀገር ልጅነት እውን እንደሆነ ሁሉ በገሀዱ ዓለም እውን ሆኖ እንዲወጣ ተአምር ይጠይቃል። ተአምር ማለት ሲደረግ ታይቶ የማይታወቅና፥ ይሆናልም ተብሎ ሊታሰብ የማይችል ነገር ሲሆን ነው።

3ኛ/ ውይይትና መግባባት የሚገርም ነው።

በሀገር ልጆች ያለው እምቅ አቅም የሚገለጠው፥ በሕዝቡ ቆራጥ ግፊት መሪዎቻችን ውይይትና መግባባትን የችግራችን መፍቻ አድርገው መጠቀም ሲችሉ ነው። ይህ ተአምር የአገር ልጆችን እርስ በርሳቸው ተጨፍልቀው አንድ ወጥ እንዲሆኑ የሚያደርግ ሳይሆን፥ እያንዳንዳቸው ውይይትና መግባባትን ተክነውበት፥ ስልጣኑን ባለቤት ለሆነው ሕዝብ ማስረከብ የሚችሉበት መድረክ የሚፈጥር ነው። ተአምሩ ዲሞክራሲና እኩልነት አይደለም። እነዚህ እሴቶች ተአምራት ከሆነው ውይይትና መግባባት የሚገኙ ውጤቶች ናቸው። ይህም እንደ ድሮ በጠጉረ ልውጥ አሳላፊነት የሚካሄድ ሳይሆን በሀገር ልጆች ሽማግሌነት እውነትን ብቻ ዋና መሰረት አድርገው የሚተገብሩት ጉዳይ ነው።

ፊት ለፊት ያለውን የውጭውን ብቻ ለሚያይ ሰው፥ ውይይትና መግባባት መንግስትን በስልጣን የሚያስቀጥል ጊዜ መግዣ እኩይ ተግባር፥ ወይም ተቃዋሚን በአቋራጭ ስልጣን ላይ የሚያስቀምጥ መሰሪ ድርጊት አድርጎ ይወስዳል። የማይታየውን እውነታ ጠጋ ብሎ ለማየት የታደለ ግን፥ ውይይትና መግባባት እስከ ዛሬ ያልተፈተነ ተግባር ሆኖ፥ የሀገር ልጅነትን ውበት ከመሪዎቻችን ውስጥ አውጥቶ እንደ ብሩህ ብርሃን የሚያስፈነጥቅና፥ ለሕዝብ የስልጣን በላይነት ተገዥዎች እንዲሆኑ የሚያደርግ ነው።

4ኛ/ የሚጠበቀው ነገር የሚገርም ነው።

ከእንግዲህ ውሃ ቅዳ ውሃ መልስ የለም። ማንም ላይታመን፥ ሕዝቡ ራሱን ብቻ ሊያምን ተነስቷል። ስልጣን የሕዝብ ነው እያሉ በስሙ የሚነግዱ ከእንግዲህ በቃችሁ ተብለዋል። ስልጣን የሕዝብ መሆኑን የሚናገር ሳይሆን በሕዝቡ ለመመራት ራሱን የሕዝቡ ተከታይ የሚያደርግ ብቻ ይፈለጋል። ከትልቅ ትዕግስት በዋላ ላንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ሕዝቡ የተነሳው፥ ለመንግስት ስልጣኑን የሚያስረዝምበትን መላ ለማፈላለግ፥ ወይም ለተቃዋሚ የስልጣን ውርስ እንዲያደርጉ ለማመቻቸት ሳይሆን፤ መሪዎቻችን የሕዝቡን ድምፅ እንዲሰሙ እና ስልጣንን ለባለቤቱ (ሕዝብ) ማስረከቢያውን መንገድ እንዲፈጥሩ ነው።  ፈሪሃ ፈጣሪ ያለው ይህ ሕዝብ አምላክ እንዳለለት ይታወቅለት።

ኢሜል አድራሻ፦ ethioFamily@outlook.com

አመጽ የተጨቆኑ ህዝቦች ቋንቋ ነው –ዳዊት ዳባ

$
0
0

አርእስቱን ከፌስ ቡኬ ላይ ያገኘሁት ነው።

ዳዊት ዳባ።

Saturday, October 15, 2016

Demonstrators chant slogans while flashing the Oromo protest gesture during Irreecha, the thanksgiving festival of the Oromo people, in Bishoftu town, Oromia region, Ethiopia, October 2, 2016. REUTERS/Tiksa Negeri - RTSQF70

በቀለ ገርባን አይነት  ብዙ ምርጥ የህዝብ ልጆች  የታሰሩበት የቂሊንጦ እስር ቤት ላይ እሳት ተነስቶ ብዙ እስረኞች እንደተቃጠሉ ወያኔዎች ባልተለመደ መንገድ በራሳቸው መገናኛ ነገሩን። ክህዝብ አልገዛም ባይነት ጋር በተያያዘ የታሰሩ የኦሮሞ ህዝብ ታጋዬችና አመራሮች፤ የስልምና እምነት ተካታይ ዜጎች ወኪሎቻቸው በቅሊንጦ እስር ቤት ታሳሪዎች ናቸው።   በቃጠሎው ማን ሞተ  ማን ተረፈ የሚለው ግን አይደለም ለህዝብ የቅርብ ቤተሰብም ሳያውቀው ሳምንት እንዲያልፍ ተደረገ። ጥብቅ የሆነ ሚስጢር ተደረጎ ተይዞ ነበር። ይባስ ብሎ ድህንነታቸውን የጠየቁ ቤተ ዘመዶች እስር ድብደባና ማዋከብ ተፈፀመባቸው። ፍጅቱን ከፈፀሙ በሗላ ከሳምንት በላይ ቢጠብቁም ህዝብ  አልገዛም ባይነቱን በጀመረው ሰላማዊ በሆነው መንገድ አጠንክሮ ቀጠለበት።  ቆያይተው እቅዳቸው ከታሰበበት አላማ ውጪ እንዳይወጣና ህዝባዊ እንቢተኛነቱ አዲስ አባባ ላይ እንዳይፈነዳ በመስጋት ይመስላል ቀድሞ ያላግባብ በቅሊንጦ ታስረው የነበሩ የድምፃችን ይሰማ አመራሮች ድህንነት ቀስ በቀስ  እንድናውቅ ሆነ። ቆያይቶም ተፈቱ። በሗላ ግልፅ እንደሆነው አመራራቹ ደህና ቢሆኑም  እሳት ለኩሰውባቸው የገደሏቸው ብዙዎቹ ኦሮሞዎች መሆናቸውን አውቀናል።

የቅሊንጦ እስር ቤት ቃጠሎ ለአንድ አመት ሙሉ የቀጠለው የህዝብ  ሰላማዊ ትግል ጉልበት እያገኘ እየሰፋ አለማቀፋዊ ድጋፍንና ትኩረትን በእጅጉ እያገኘ አገዛዙን እለት በእለት እየገዘገዘው እየሄደ ባለበት ጊዜ ላይ የተፈፀመ አስደንጋጭ ክስተት ነው ። ሌሊሳ ፈይሳ የውጪውንም የአገሩንም ሜዲያ ሙሉ በሙሉ የተቆጣጠረበት ጊዜ ነበር። ለአንድ አመት በዘለቀው ትግል  ቀን በቀን ዘግናኝ በሆነ ሁኔታ የሚገደሉ ንፁሀን ዜጎች ጉዳይና የናቶች ለቅሶ መላውን ዜጋ ሲቃ ውስጥ የሚከትና  እልህ ውስጥ ያሚያሰገባ አልነበረም ማለት በጭራሽ አይቻልም። በእልህ ምክንያ የትግል ስልት መቀየር አለበት የሚሉ ድምፆች መሰማት  ጀማምረው ነበር። ከቅሊንጦው ፍጅት እና ወያኔ ፍጅቱን የያዘበት ጠቅላላ ሁኔታ ለተከታተለ ወያኔ ህዝብን ሴሜታዊ ለማድረግና ወደ ለየለት አመፅ ውስጥ ለማስገባት  እየሰራ እንደሆነ ግልፅ ነበር። በግሌ ልፅፍበት አስቤ ከሌሎች ጋር ስወያይበት ቆይ ቆይ ወያኔ ስላደረገው ብቻ ለምን መጥፎ ይሆናል?  ትግሉ ላይ ጥቅሙንና ጉዳቱን ስናሰላው  ጠቃሚነቱ የበዛ ስለሆነ ይታለፍ አለን። እርግጠኛ ነኝ ትግሉ ላይ በቅርብ ያሉትም  ይህንን ጉዳይ አይተውታል።  ወያኔዎች በፈለጉት መንገድ እንዲያስኬዱት እንደተዉላቸው እርግጠኛ ነኝ። ይህን ለማለት የሚያስችሉ ምክንያቶችም አሉ።።

ቀጠለ የኦሮሞ ህዝብ ጥያቄ አግባብ ያለው ነው። አልፎም ሊመለስ የሚችል ነው። መንግስት መመለስ አለበት። የትግራይ ህዝብ የኦሮሞን ህዝብ ትግል ደግፎ ሊሰለፍ ነው። ከአማራ ተጋድሎ ጋር በማፎካከር መሆኑ ነው። ማዘናጊያ ፕሮፓጋንዳ ጦዘ። ከአርባ አመት በሗላም ይህቺን የውሸት ፕሮፓጋንዳ እንደተሰጣቸው  የዋጧት ነበሩ።  ለወደፊቱ እንንቃ ትግሉ አገራቀፋዊ ሆኗል። ጥያቄው ወደስርአት ለውጥ አድጓል። የትኛውም ጥያቄ ወያኔ ስላጣኑ ላይ ባለበት ሊመለስ የሚችል አይደለም።  የትኛውም የኦሮሞዎች ጥያቄ ወያኔ ሊመልሰው የሚቻላውም አይደለም።  ሲጀመር ጥያቄው አንድ ብቻ አይደለም። ቀለል ተደርጎ የተገለፀው የአዲስ አባባ ማስተር ፕላን ጥያቄ ራሱ ለመመለስ እንደምንለው ቀላል አይደለም።   ከቅሊንጦው ፍጅት በሗላ በቀጣይ ምን ተሳቦ ይህቺ ቀልድ መጣች ብሎ መጠየቅ ለሁላችንም የተገባ ነበር።  ጫወታው ወደዚህ ነበር።

የቅሊንጦው ፍጅት አልሰራላቸውም በቀጣይ ምን ያደርጋሉ የሚለወን ስንወያይ የተለያዩ መላ ምቶችንም አስቀምጠናል። በግሌ ግን በቀጣይ ሊያደርጉት የሰቡትን  ማወቅ እችል ነበር። ከፈፀሙት በሗላ ደደብ ነኝ ነው ለራሴ ያልኩት።  በፈረንጆች አቆጣጠር 1989 እንግሊዝ ውስጥ የሊቨር ፑል የእግር ኳስ በድን ደጋፊዎች እልቂት በተመለከተ በጊዜው ሜዲያዎች በሙሉ ተቀባብለው እንደዘገቡት በደጋፊዎቹ ስርአት አልበኛነት ምክንያት ሳይሆነ የፀጥታ አስከባሪዎች በሰሩት ተራ በሆነ ስህተት የተፈጠረ እልቂት መሆኑን የሚያሳይ አስገራሚ ጥናታዊ ፊልም  ሲኤን-ኤን ላይ የዛኑ ሰሞን ተላልፎ አይቼ ነበር።  ይህቺኑ በቀጥታ ቀድተው ይጠቀማሉ ብዬ ግን እንዴት ይታሰበኝ።

ላለፈው አንድ ኣመት ሙሉ  አገዛዙ የተነሳበትን ህዘባዊ አልገዛም ባይነት ለመቀልበስ ብዙ ጥሯል። መሪ ብሎ ያሰባቸውን ሰብስቦ ማሰር፤ ፍጅት፤ ጀምላ እስር፤ የርስ በርስ ግጭትና በዜጎች ዘንድ መፈራራትን መፍጠር፤ ማስፈራራት፤ እስረኞችን እስከነብሳቸው በእሳት ማቃጠል፤ የመሳርያ ትግላቸውን እርግፍ አድርገው ትተው ህገመንግስቱን አክብረው ለመታገል ስለወሰኑ ድርጅቶች … ብዙ ብዙ። ግብፅ፤ ኤርትራ፤ አክራሪ የሚሉ ማሸማቀቂያዎችን ማጦዝ…።  ይህ ሆሉ ጥረት ግን እንደቀድሞው ህዝባዊ እንቢተኛነቱን ሊያቆመው አይደለም ትግሉን ይጠቅማል ብሎ ሊገፋው ወዳሰበው አመፅና ውድመት ያለበት መንገድ  ሊወስደው አልቻለም። ይባስ ብሎ መላው ዜጋ አገዛዙ  ሟች መሆኑን አውቆ ስለቀጣዩ እጣ ፋንታው ወደማውራት  ተሻገረ። በውጪ  ብቻ እንዳይመስለን በመላ አገሪቷ በይበልጥም አዲስ አበባ ላይ ዋናው መወያያ ቁም ነገር ሆኖ ነበር።

የኢሬቻን ፍጅት በተመለከተ። {1989 የሊቨር ፑል ደጋፊዎች እልቂት ፊልም ላይ በዚህም መንገድ ፍጅት መፈፀም እንደሚቻል ወያኔዎች በእርግጠኛነት ግንዛቤ ወስደዋል}። የእሬቻ በዓል።

  1. በትንሹ ከሁለት ሚሊዬን በላይ ህዝብ የሚታደምበት በዓል ነው።
  2. በዓሉ በተከበረባቸው የቀደሙ አመታት ሁሉ ህዝብ በበዓሉ ላይ ላገዛዙ ያለውን ተቃውሞ ያሰማ ነበር። ምን አልባት የትግሉ መነሻ  በየዓመቱ የሚደረገው ይህ ታላቅ በዓል ነው ማለት ይቻላል።
  3. የኦሮሞ ህዝብ ተቃውሞ ከደረሰበት ደረጃ አኳያ በዚህም ዓመት ጠንካራ ተቃውሞ በበዓሉ ላይ እንደሚኖር የሚጠበቅ ነበር።
  4. ከባድ ተቃውሞ እንደሚኖር ስላወቁም ታንክ፤ከባድ መሳርያና ብዙ ወታደር ቦታው ላይ አዘጋጅተው ነበር።
  5. በዓሉ የሚከበርበት ቦታ መልካ ምድርና ከህዘቡ ብዛት አኳያ በቀላሉ እወካን በመፍጠር ህዘብ ሲገፋፋ ገደል ውስጥ እንደሚገባና፤ በጭሱ ሊታፈንና ተረጋግጦ ሊሞት እንደሚችል ይህን ተጠቅሞ እልቂት እንዲደርስ ማድረግ እንደሚችል አስልተዋል።
  6. በእለቱ የነበረው ጠንካራ ተቃውሞ ቢሆንም ፍፅም ሰላማዊ የነበረ መሆኑ በግንዛቤያችን እናስቀምጥ።
  7. በዓሉ ከሚከበርበት ቦታ አኳያ ተቃውሞው ለስልጣን፤ ለሰው ሆነ ለንብረት ውድመት ብቻ በየትኛው ሁኔታ ላገዛዙ አስፈሪ ሊሆን የሚችልበት ሁኔታ ማጣቀስ ለማንም አይቻልም። ታቃውሞው ፍፁም ስላማዊ ስለነበረም  ታላቅ በዓል ከመሆኑ ጋር ደምሮ ፍጅት ለመፈፀም ቀድሞ ለተዘጋጀ አካል ካልሆነ በቀር ለምንም አይነት ሀላፊነት ለሚሰማው ክፍል  አግባብ ያለው ሁኔታውን መቆጣጠርያ መንገድ ተቃውሞው እንዲቀጥል መተው፤  የተቻለውን ያህል ጣልቃ አለመግባትና  ያሰማራቸውን ወታደርና የመገደያ መሳርያዎች ከዛ አካባቢ ማራቅ  ነበር።
  8. በተቃራኒው ያገዛዙ ተንኳሽነትና አስጨናቂ ድባብ መፍጠር ነበረበት። ታነክ በቦታው ነበር፤ ከባድ መሰራያ ነበር። መሰርያ የታተቁ ወታደሮች በመኪና ሆነው በዓሉን ለማክበር በተሰበሰበው ህዝብ ውስጥ ይመላለሱ ነበር። ተደብቀውም በተዘጋጅ የሚጠብቁ ብዙ ወታደሮች ከጀርባ ነበሩ። ከነዚህ በተጨማሪም መሳርያ ያልያዙ ብዙ ወታደሮች ከፊት ተደርድረው ነበር። ህዝቡ  አመቱን ሙሉ ሲገድሉ በየቀኑ ልጆቹን እየቀበር ሲቃወማቸው እንደነበረ እየታወቀ የመንግስት ባለስልጣናት በዓሉ ላይ ንግግር ለማድረግ ማሰባቸው ተንኳሽነት ነው። ይህ ሙከራቸው ለተቃውሞው መጠንከርና ቦታው ላይ ንትርክን ያስነሳ  ነበር። በድርጅታዊ ስራ ብዙ የኦፒዲዬ አባላት በዓሉ ላይ እንዲገኙ ተደርጓል። ተለይተው እንዲታዩ ባንዲራ ይዘው ነበር። ይህ ድርጊት በራሱ የርስ በርስ ግጭት ለማስነሳት ነበር። የእቅድ አነድ አካል ነበር ማለት ይቻላል። አስገራሚውና ሁላችንም መዘንጋት የሌለብን ሀላፊነት ከሚሰማቸው ክፍሎች ቀድምው በዓሉን አገዛዙ ለፖለቲካል ፍጆታ ለመጠቀም መሞከሩ ሊያስከትል የሚችለውን አደጋ በማስረዳት እንዲታቀብ  አስጠንቅቀውት የነበረ መሆኑንም ክግንዛቤ እናስቀምጥ።
  9. ከባድ መሳርያን ጨምሮ ተኩስ ነበር፡ አስለቃሽ ጪስ ተተኳሷል። በቦታው ሂሊኮፕተር ነበር። በቀደሙት አመታት  በእሬቻ በዓል ላይ የመልካም በዓል መልእክት የያዘ ወረቀት  በሂሊኮፕተር ይበተን የነበረ መሆኑ ገና መመርመር ያለበት ነው። እነዚህ ሂሊኮፕተሮች አስለቃሽ  ጪስ ወደህዘብ ተኩሰዋል። ወረቀትም አስለቃሽ ጪስም ሁለቱንም ለምን ቀድምው ተዘጋጁበት ? የሚለውም።
  10. አገዛዙ ከእሬቻው ፍጅት በሗላ እንግዳና ባልተለመደ ሁኔታ ፈጣን መግለጫ አውጥቷል። ከፍጅቱ በፊት የተዘጋጀ መግለጫ ነው የሚመስለው። መግላጫው ላይ የተካተቱት ቁም ነገሮች በሙሉ አንድ በአንድ ሲመረመሩ ቅድመ ዝግጅት እንደነበረ ተጨማሪ አስረጅነት አላቸው። በሗላ ላይ የፅጥታ አስከባሪዎቼ ምንም አይነት ተኩስ አላደረጉም የሚለው የጠቅላይ ሚንስትር ተብዬው ውሸት ሚሊዬኖች በቦተው ሆነው በአይናቸው ያዩትና የሰሙት ሆኖ እያለ ህዝቡን በማናዳድ ስሜታዊ ለማድረግ ሆን ተብሎ እንዲናገረው የተደረገ ነው ።
  11. እልቂቱ ከመፈፀሙ ከትንሽ ደቂቃዎች ቀደም ብሎ ባካባቢው የነበሩ የሜዲያ ሰዎች ሁሉ ካካባቢው እንዲርቁ በፀጥታ ሀይሎች ተገደዋል።

 

አሁን ላይ በእሬቻ በዓል ላይ ሂወታቸውን ያጡና የተጎዱ ዜጎች ዝም ብለው ተረጋግጠው አለመሞታቸውንና አለመጎዳታቸው ለማንም ግልፅ ሆኗል። ተረጋግጠውም ሆነ ገደል ገብተው ወይ ባስለቃሽ ጪሱ ምክንያት አየር አጥተው ይሙቱ   መንግስት በወሰደው እርምጃ  ምክንያት የተፈጠረ ፍጅት መሆኑ የማያከራክር ሆኗል። እልቂቱ በስህተት ምክንያት የተፈጠረ ነው ወይስ አገዛዙ ቀድሞ አቅዶበት የፈፀመው ነው የሚለው ግን ገና ጎልቶ አልወጣም። ትክክለኛ ድምዳሜ ላይ ለመድረስ የቅሊንጦንና የእሬቻውን እልቂት አጣምሮ ማየት ተገቢ ነው። ከትግሬ ወያኔዎች የሗላ ተመሳሳይነት ያለውና ብዙ ንፁሀንን የመፍጀት ታሪክና መፈጸሚያ መንገዶቹን አካቶ ማየትም አስፈላጊ ነው። አሁን ላይ እያየን እንዳለነው የገጠመውን የህዝብ ተቃውሞ ለመወጣት ያዋጣል ብሎ ያስቀመጠው እቅድና እየወሰደ ያለው እርምጃንም ጨምሮም ማየት ያስፈልጋል። ከላይ አንድ ሁለት ተብለው የተዘረዘሩትን መክንያቶች ከነዚህ ቁም ነገሮች ጋር አብሮ ለጨመቀ  መረጃዎች የሚያስረግጡት ፍጅቱ በአግባቡ የታቀደና አስበውብት ተፈፃሚ ያደረጉት መሆኑን ነው። በተፈጠረ ስህተትና ቀድሞ በታቀደ ሁኔታ የተፈፀመ ፍጅት  የሚለው የሰማይና የምድር ያህል ልዩነት አለው። ይህን የንፁሀን ፍጅት እየመረመሩ ያሉ አካላት ሁሉ ቢፈልጉ ምክንያት ዘርዝረው ቀድሞ በታቀደ መንገድ መንግስት የፈፀመው አይደለም ማለት ይችላሉ። ግኝታቸው ላይ በስህተት ወይስ ቀድሞ ታቅዶ በአገዛዙ የተፈፀመ ነው የሚለው ላይ ልዩነት ባደረገ ጥርት ያለ መደምደሚያ ከሌለው  ግን  ሀላፊነት በተሞላበት አልቀረበም ወይም ሽፍጥ እንደሆነ አሁኑኑ መናገር ይቻላል። ይህ  ቁም ነገር ፍጅቱን መርምሮ ግኝቱን ለህዘብ ይፋ ለማድረግ እየሰራ ላለ የትኛውንም ክፍል ይመለከታል። በዋንኛት የገዳው ስርአት መሪዎች ሀላፊነት አለባቸው። በቦታው ነበሩ የተፈፀመውን ፍጅት በአካል ተገኝተው አይተዋልና።

ሞት እስር መደብደብ እያንዳንዱ የኦሮሞ ቤት ውስጥ ገብቷል። የህዝቡ ቁርጠኛነት ጽናት አስገራሚ መሆኑ እንዳለ  ተጠቂነት እልህና ቁጭት አዝሏል።  ወገኖቹን አስረው እሳት ለኩሰውባቸው ጠብሰው እንደበሏቸው ሰምቷል። ከሰባት መቶ በላይ ንፁሀን አራት ሚሊዬን ህዘብ  እቦታው ኖሮ እማኝ በሆነበት ፈጅተዋቸዋል። በዚህ እውነታ ውስጥ ህዘብ ስሜታዊ ሆኖ በንብረት ላይ ውድመት መፈፀሙ አስገራሚ አይደለም። አመፅ የተጨቆነና የተገፋ ህዝብ ድምፅ ነው። ይህ በሰው ልጆች ታሪካ ውስጥ ሁሌም የነበረና ወደፊትም የሚኖር ነው። የወደመው ለአገዛዙ የመጨቆኛ ጉልበትና የባለስልጣናቱ ንብረት ነው።  ስራችንን ወያኔዎችዩ  ቀሙን እንጂ እነዚህን ንብረቶች ዶጋ አመድ ማድረጉ ትግሉ ላይ አንዱ ስራችን ነበር።

ህዘብ ስሜታዊ እንዲሆን ምን ያህል እንደሰሩበትና ፍጅት መፈፀም ድረስ እንደሄዱ ከለይ  አይተናል።  ንዴት ውስጥ ገብቶ የንብረት ውድመት እንዲፈፀም አጥበቀው ፈልገዋል። ግን ለምን?። ይህ ፍላጎታቸው በእሬቻው እልቂት ምክንያት ተፈፃሚ በይሆን ኖሮ በእርግጠኛነት ሌላ አይነት ደግሞ ፍጅት ፈፅመው መሞከራቸው አይቀርም ነበር። መላ አሮሚያን በሰባት የፀጥታ ዞን ከፍለው በወታደራዊ አስተዳደር ስር ከዋሉት ቆይተዋል። ይህ ሁሉ የፈሰሰ ጦር ሰራዊት የህዝብን ደህንነት ሊጠብቁ አይደለም እዛ ያለው። ውድመቱ ባይፈለግ ኖሮ በደንብ መከላከል ይቻለው ነበር። ንብረቱን መጠበቅ የሚችል እጅግ ቁጥሩ የበዛ ፀጥታ አስከባሪ በቦታው ነበር። ለጊዜው ግልፅ ያልሆነው ቆያይቶ መታወቁ ግን የማይቀረው ወያኔዎች በዚህ ውድመት ላይ ከፍላጎትና የህዘብን ትግል ወደዛ ከመግፋት ባለፈ ቀጥተኛ በሆነ መንገድ በመሬት ላይ ምን አይነት ድርሻ ነበረቻው? የሚለው ነው። ይህን ጥርጣሬ የሚያጠናክረው ሌላ ጉዳይ ደግሞ ጠቅላላ  የአገሪቷ ፖለቲካ ባልተለመደ መንገድ ላሁኑ  አገዛዙን በፈለከው ደረጃ ማሳጣት፤ መውቀስ መስደብ ተፈቅዷል። ተናጋሪው ግን ሳይረሳ  “እንዴት ንብረት ይወድማል” የሚለውን በሆነ አገላለፅ ንግግሩ ውስጥ  እስካስገባ ማለት ነው።

ለማጠቃላያ ወያኔ ትግሬዎች የተነሰባቸውን አልገዘም ባይነት ለመቆጣጠር ተፈፃሚ እያደረጉ ያሉት እቅድ ሁሉም አይሰራም። አያዋጣምም።

  1. የጭንቅ ጊዜ አዋጁ። ዋና አላማው “አስቸኳይ”ና “አዋጅ” የሚለው ነገር ላይ ያለን የህዘቡ ስነልቦናና ያለፈ ተሞክሮ በመጠቀም ማስፈራራት ነው። የሚያስፈራ ግን አልሆነም።  እንደውም የተከለከሉትን ነገሮች በቀላሉ ህዘብ በብዙ ቁጥር በተራ በተራ በማፍረስ ቀላል መታገያ አድርገን ልንጠቀምባቸው የምንችልባቸውን ቁም ነገሮች ሰጥቶናል። ይህ ተጀምሯል ይቀጥላል።
  2. በተጓዳኝ በጠረቤዛ ዙሪያ በሚደረግ ወይይት መፍትሄ ለመስራት ተነሳሽነት ያለ የሚመስል የተጠናና በደንብ የታሰበበት ቲያትር በመስራት ማዘናጋት ነው። ቲያትሩም ተዋናዬቹም ጥሩ ሊከውኑት ግን አልቻሉም። ተሳክቶላቸውም ቢሆን አይገባቸውም እንጂ ህዝብ የዚህ አይነት ቲያትር ሁሌም ለህዝብ ካለ ንቀት የሚመጣ እንደሆነ ስለሚያውቅ የተማረረበትና ስልችት ያለው ነገር ነው። በነገራችን ላይ የመለስ ልጅ ንግግርም የቲያትሩ አካል ነው። በአጠቃላይ ወይይቱ ያንድ ጊዜ ነው። እንደተባለው ወደህዝብም አይወርድም። ምክንያቱም ህዝብ መፍራት አቁሟል። ፍርጥ አድርጎ ይናገራል። በጥልቅ ለመታደስ ማሰባችሁ ጥሩም ችግራችሁም ነው። እኛ ላይ ሆናችሁ ግን አታስቡት ማለቱ አይቀርም። ለፈፀሙት የንፅሀን ፍጅት ምክንያት ህዝብ መድርክ ላይ የሚቀርቡትን ባለስልጣናት ጉሮሮ ለማነቅ መነሳቱ አይቀርም። ልጄን ገድላችሗል ውለድ። ልጄን ያለአግባብ አስራችሗል በአስቸኳይ ፍቱ በሚል የቅርብ ዘመዶቻቸው ሊጋፈጧቸው እንደሚችሉ ያውቃሉ።
  3. የደረሰውን የንብረት መውደምና የኦሮሞ ህዘብ ትግል ላይ ያለን ጥርጣሬና ፍራቻ በማጦዝ የፈፀሙትንና የቀጠሉበትን የንፁሀን ፍጅት በህዝብ ዘንድ ዋና ትኩረት እንዳይሆንና ወንጀላቸውን  ተቀባይነት ያለው ለማድረግ መጣር ነው። ህዝብ እውነተኛውን መረጃ የሚያገኝበትን መንገዶች ሁሉ ዘግተው አጠንክረው እየሰሩበት ያለ ነው። በቀላሉ የዚህ አይነት ወጥመድ ውስጥ የሚወድቁ ፈዛዛ ሙህራኖች ተቃዋሚዎችና ተሰሚነት ያላቸወን ሰዎች መጠቀማቸው አይቀርም። ይህም ቢሆን አካሄዳቸው ከታወቀ መላ የሌለው አይደለም። ሲጀመር አልገዛም ባይነቱ በመላው አገሪቱ በጠቅላላው ህዝብ ዘንድ ስለሆነና የአማረው ተጋድሎ በሰሜን ባየለበትና አገዛዙ በተመሳሳይ  ጊዜ ንጹሀን ዜጎችን እየፈጀ ባለበት ይህቺ እቅዳቸውም እንደወትሮው አትሰራላቸውም።
  4. መላ አገሪቷን የመረጃ ጨለማ ውስጥ መክተት ነው። ይህ ለኛም ለነሱም ሁለት ጎን ስለት ያለው ቢሆንም አሳሳቢ ነው። ለጊዜው አውሪዎች እነሱ ብቻ ናቸው። እዚህ ጉዳይ ላይ ህዝብም የለውጥ አንቀሳቃሾችም የሚቻላቸውን ያህል መላ መፋላለግና ይህን ችግር መገዳደር ወና ስራ መሆን አለብት። በቀጥታ መታገል ባይቻል እንኳ በትላልቅ ህዝባዊ እንቢተኛነት ከበፊቱ በጠነከረ መንገድ አከታትሎ በማድረግ ማፈን እንደማይችል ተስፋ ማስቆረጥ ያስፈልጋል።

 

ምክር ቢጤ።

ህዘብ ግርግዳ አስደግፎ ማንቁርት ይዟል። ውጤት እያመጣ ያለ ትግል በደም ፍላት ስለገደሉ ስላሰሩ ተብሎ አይቀየርም። ከዚህ በፊትም ሁሌም በዚህ አይነት ሁኔታ ተገፍቶ የሚደረግ የትግል መስመር ለወጥ ፍዳችንን ሲያበዛው ነበር። ሊገልህ የመጣን አካል መከላከል አግባብም መገላገያም ሊሆን ይችላል። የማይካደው ግን ጉልበታም የሆነው በመግደላችን ሳይሆን በብዙ ቁጥር ሆነን አንፈልግም ማለት በመቻላችን ነው። ትልቁ ጉልበታችንም በቀላሉም ልናደርገው የሚቻለንም ይህው ነው። ያንኛው መንገድ እየተሰማንን ያለውን ጉልበተኛነትና የደረስንበትን በራስ መተማመን ገድሎ ነፃ አውጪ ጠባቂ ነው የሚያደርገን። ትግል በዋናነት የጭንቅላት ጨዋታ ነው። አዋጩ መንገድ አሁን ደግሞ ቀዝቀዝ አድርጎ ፍፁም ሰላማዊ ወደሆነ እንቢተኛነት መአቀፍ ውስጥ በቶሎ መልሶ ማጫወት ነው።  ይህን ስናደርግ ውስብሰም በቀላሉ  አሸናፊም እንሆናለን። ያዋጣል ካለ ለሁለተኛ ጊዜ ወደሀይልና ውድመት እሱ ይግፋው። ያኔ ለትግሉ የሚጠቅም ወይ የሚጎዳ መሆኑን የምናየው ይሆናል። አንድ ክልል ህዘብ ወይ የአንድ ከተማ ህዘብ ተነጋግሮ ላንድ ሳምንት እቤት መቀመጥ ከቻላ ሊያደርግ የሚችለው ብዙ ነግሮች ይኖራሉ። ፋታ መስጠት ግን ጥሩ አይደለም። እንደውም በአገር አቀፍ ደረጃ አዲስ አበባንም ጨምሮ አገር አቀፋዊ ተቃውሞ ተጣምሮ በቶሎ መጥሪያ ጊዜ ነው። የትግሉን አርማ  በእኩል ሰዓት ለደቂቃዎች በያለበት ቀጥ ብሎና ሁሉን ነገር ቀጥ እደርጎ በማሳየት የጭንቀት አዋጁን አንድ ሁለት እያሉ ከማፈራረስ  መጀመር ነው። ይህን ፅሁፍ ከመላኬ በፊት ከደቂቃዎች በፊት ይህን ጨመርኩ። የኢትዬጵያን ፖለቲካና አንድነት የሚያተረማምስ፤ ይህን ያህል መሰዋትነት የተከፈለበትና ቀና ያለ የህዘብ ትግል በቂጡ የሚያስቀምጥ፤ ሀላፊነት የሚባል ነገር በማይሰማቸው የሆነ ጊዜ ላይ አፍሮ ያበጥሩ የነበሩ አሮሞ አቢዬተኞ አባቶች   እየሰማው ነው። ታግሶ የመጨረሻውን ድምዳሜ መጠበቅ ተገቢ ይሆናል ልባል ላሁኑ እየተሰማኝ ያለው ግን ጥልቅ ሀዘንና ተስፋ ቢስነት ነው። በደም ፍላት ብዙ ላለማለት እዚህ ላይ ላቁመው።

 

 

 

 

 

የኢትዮጵያ ታሪክ! (ያለፈውን ታሪክ ለማስተካከል ዛሬ እኛ ነፃ መውጣት አለብን)

$
0
0

ሥዩም ወርቅነህ(LLB)

ታሪክ ብዙ ጠቀሜታ እንዳለው ግልፅ ነው። ጠቀሜታ የሚኖረው ግን ትክክለኛውን ታሪክ በማወቅ ጥሩውን ወስዶ ስህተቱን በማረምና እንዳይደገም ትምህርት በመውሰድ ነው። ትምህርት መውሰድ ብቻ ሳይሆን ስህተቱን እንዳይደገም አበክሮ በመስራትና ግንዛቤ በማስጨበጥ ነው።

syumየኢትዮጵያ ታሪክ የተፃፈው ያለፉትን ስርዓት ገዢዎች በሚመቻቸው ሁኔታ ነው። በወቅቱ የነበሩ የስርዓቱ ገዢዎች የማያስደስት ነገር የፃፈ ሰው ብዙም ተቀባይነት አልነበረውም። የስርዓቱን ገዢዎች የሚያስወቅስ ነገር የፃፉ ሰዎች የህይወት መስዋዕትነት ከፍለዋል። ከነዚህም ውስጥ አቶ በዓሉ ግርማ እንደ ምሳሌ መጥቀስ ይቻላል። በደርግ ዘመን “ኦሮማይ” የሚል መፅሃፍ በመፃፋቸው ስርዓቱን የካዱ ተደርገው በመፈረጃቸው ብዙ ነገር ደርሶባቸዋል። በመጨረሻም እስከዛሬ እውነቱን በማይታወቅ ሁኔታ የደረሱበት አይታወቅም። ነገር ግን ይህን ሸፍጥ ያቀናበሩት የስርዓቱ ቁንጮ ባለስልጣናት መሆናቸው የሚያሳይ ብዙ ማስረጃዎች አሉ።

ያለፉት ስርዓቶች በኢትዮጵያ ሕዝብ ይሁንታ ያልተመረጡ እንደነበሩ ግልፅ ነው። ምርጫ የሚባል ነገር ስላልነበር። እነዚህ ገዢዎች ዲሞክራሲያዊ አልነበሩም። ሆኖም በኢትዮጵያ ሕዝብ ዘንድ ጥሩም መጥፎም አሻራ ጥለው አልፈዋል። እነዚህ ስርዓቶች በዲሞክራስያዊ ስርዓት ለመተካት ብዙ የህይወት መስዋዕትነት ተከፍሏል። ሆኖም ሁሉም በሚባል ደረጃ የስርዓትና የመሪዎች ለውጥ ከማምጣት ውጪ የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚፈልገውን ነፃነት ሊያጎናፅፉት አልቻሉም። ዛሬም በስልጣን ላይ ያለው ስርዓት ያለፉትን ስርዓት ችግሮች ለማስተካከል የታገልኩ ነኝ ብሎ የሚገዘት ቢሆንም በተግባር ሙሾ ከመሆንም አልፎ ካለፉት ስርዓቶች የባሰ ሆኖ አግኝተነዋል። በመሆኑም የህን ስርዓት አስወግደን በዲሞክራስያዊ ስርዓት ለመተካት ትግሉ የሚጠይቀውን መስዋዕትነት ሁሉ እየከፈልን በመታገል ላይ እንገኛለን። ይህን የምናደርገው እኛም ከአንባገነን ስርዓት ያልተላቀቅን ነፃ የወጣን ሰዎች ባለመሆናችን ነው።

ያለፉት ስርዓቶች በደል አላደረሱም ብሎ ጥብቅና መቆም በጣም ከባድ ነው። በኢትዮጵያውያ ሕዝብ በደል አላደረሱም ማለትም በጣም ይከብዳል። ባለፉት ስርዓት በግፍ ለተበደሉት ጥብቅና መቆምና ደማቸውን ማጥራት እንዳለብን ይሰማኛል። ሆኖም እኛ እራሳችን ነፃ ባልሆንበትና በማንስማማበት በአለፈው ታሪክ ላይ እየተከራከርን ዛሬ ላይ ያለውን ትግላችን ማሰናከል ያለብን አይመስለኛም። በግፍ ስለተበደሉት እየተከራከርን ዛሬም በአንባገነን ስርዓት የንፁሃን ዜጎች ነፍስ እየተነጠቅን ስለሆነ።

የአለፈውን ታሪክ በተለይ ያለተማመንበትን ለመነጋገር እውነቱን ለማውጣት በማስረጃ የተደገፈ ውይይት ማድረግ ያስፈልጋል። ለዚህ ደግሞ ነፃ የውይይት መድረክ መዘጋጀት አለበት። የአገራችን ህዝብ  ሁሉም መብቱን በተነጠቀበት በዚህ ወቅት ይህን ማድረግ በጣም የሚከብድ ይመስለኛል። ስለአለፈው እየተከራከርን ዛሬም የአንባገነኑን እድሜ እናራዝማለን የንፁሃን ዜጎች ነፍስም እንነጠቃለን። ስለዚህ መጀመርያ አሁን በህይወት ያሉ ወገኖቻችን ነፍስ እንዳንነጠቅ ይህን የወያኔ/ኢህአዴግ አንባገነን ስርዓት አስወግደን ዲሞክራሲያዊ ስርዓት ለመገንባት በአንድ ላይ መረባረብ ይኖርብናል።

ነፃ ዳኝነት በሌለበትና በማያስማማን ታሪክ ላይ ቆመን እየተከራከርን የፋሽስትና አንባገነኑ የወያኔ/ኢህአዴግ ስርዓት በማርዘም የወገኖቻችን ስቃይ ከምናበዛ ጠላታችን የሆነውን ስርዓት ገርስሰን ሁላችንም ነፃ በማውጣት ያለፈውን ታሪክ ለማስተካከል ተግተን ለመስራት ቃልኪዳን መግባት ይኖርብናል።

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!

“የዉበት እስረኞች” ግራ ተጋብተዋል –ዋዜማ ራዲዮ

$
0
0

yellow-cab-in-addis-300x155ዋዜማ ራዲዮ- የትራንስፖርት ሚንስትር የነበሩትና በቅርቡ ወደ ኦሮሚያ ክልል አመራርነት የመጡት ወርቅነህ ገበየሁ መስቀል አደባባይ ተገኝተው “ለአዲስ አበባ ሕዝብ የአዲስ ዓመት ስጦታ ይዤ መጥቻለሁ” ያሉት ጳጉሜ፣2008 ነበር፡፡ የሚመሩት መሥሪያ ቤት በበኩሉ በነገታው ጋዜጠኛ ጥሩልኝ አለ፡፡ በመስከረም መጀመርያ ታሪፍ ተምኜ፣ ታርጋ አስለጥፌ መልከኞቹን ታክሲዎች በሙሉ ኃይል ወደሥራ አሰማርቼ የትራንሰፖርትን ችግር ድራሹን አጠፋለሁ ሲል ለሕዝብ ቃል ገባ፡፡

አሁን አዲስ ዓመት ገብቶ፣ ጥቅምት እየተገጋመሰ ነው፡፡ ወፍ የለም!

እርግጥ ነው ቢጫዎቹ ታክሲዎቹ በያደባባዩ ዉርወር ይላሉ፡፡ በየጎዳናው ሽው እልም ይላሉ፣ ይምነሸነሻሉም፡፡ ሙሽራ እንደቀረበት ሚዜ ትክዝ ብለው በየጥጋጥጉ የሚቆሙም አሉ፡፡

ወፍ የለም!

ወያላና ከራር ፀሐይ ያለርህራሄ የሚረባረቡበት የሸገር ሕዝብ መልከኞቹን ታክሲዎች ቁልጭልጭ እያለ ከመመልከት ዉጭ “ታክሲ!” ብሎ በሙሉ አፉ ሊጠራቸው፣ የኔ ብሎ ሊሳፈርባቸው አልደፈረም፡፡ይጠጌ- አይነኬ” ናቸው ይላሉ የተማሩ ተሳፋሪዎች፡፡ “የዉበት እስረኞች” ይሏቸዋል ፊልም አዘውታሪዎች፡፡

“እኔምልህ? ለምንድነው “የዉበት እስረኞች” የተባላችሁት ግን?” አልኩት ቴድሮስን፣ ፡፡

“ያው ምን መሰለሽመሸጥ መለወጥ አንችልም፣ እናምራለን ግን ባለ እዳ ነን፡፡ ለዚያ ይመስለኛል” አለ፣ መሪዉን በቄንጥ እያሾረ፡፡

ቴዲን ያገኘሁት እስጢፋኖስ ጋ ነበር፡፡ ላንድ አጣዳፊ ጉዳይ ጀሞ መድረስ ነበረብኝ፡፡ ከ300 ብር ብሞት አልወርድም አለ፡፡ ሰዓቱ ቀትር ስለነበር ፀሐይዋ ናላዬን አዞረችው መሰለኝ ከጠራው ሒሳብ 50 ብር ብቻ አስቀንሼ ተሳፈርኩ፡፡

“ቤተሰብ! ፈታ ብለሽ ቁጭበይ! በማስተዋወቂያ ዋጋ ነው የጫንኩሽ፡፡ ጀሞ በዚህ ዋጋ አይታሰብም” አለኝ፣ እንደ አምባሳደር ከኋላ ተደላድዬ መቀመጤን በዉስጥ ስፖኪዮ ከተመለከተ በኋላ፡፡

እውነት ለመናገር የቴዲ ሊፋን ትመቻለች፡፡ አዲስ ስለሆነች ነው መሰለኝ አዲሱ ኤይርባስ ላይ የተሳፈርኩ ያህል ተሰማኝ፡፡ ቴዲም የዋዛ አይደለችም፡፡ ብርቅ ሆናበት ነው መሰለኝ የወንበሯን ላስቲክ እንኳ አልላጠውም፡፡ ፈራ ተባ እያልኩ ለምን ላስቲኩን እንዳላጠው ስጠይቀው ግን ተከዘ፡፡ ነገሮች ካልተስተካከሉ መኪናውን ለመሸጥ እንደሚያስብ ነገረኝ፡፡

“ቅድም መሸጥ መለወጥ አንችልም አላልከኝም እንዴ?”

“የአክስዮን ድርሻህን እኮ ነው የምትሸጠው፡፡ የሚገዛው ሰው የሉሲ ታክሲ ማኅበር አባል ይሆናል፡፡ መኪናውንም አብሮ ይወስዳል፡፡ እስከነእዳው ማለቴ ነው፡፡ 100 ሺ ለእጄ ባገኝ አይኔን አላሽም! ማርያምን፡፡”

ከተሳፈርኩበት እስጢፋኖስ እስካሁን ሦስት መብራት ይዞናል፡፡ የአብዮት፣ የስቴዲየም ቤተዛታና የኮሜርስ መብራት፡፡ በቁርጥ ዋጋ ባልነጋገርና በኪሎ ሜትር የምከፍል ቢሆን ኖሮ በቆምንበት ሁሉ እኔ ላይ ነበር ማሽኑ ይቆጥር የነበረው? ወይስ ምንድነው ብዬ ማብሰልሰሌ አልቀረም፡፡ ጥያቄዬን አሳደርኩት፡፡

“ሥራ ግን እንዴት ነው? ለምዶላችኋል?” ሜክሲኮ የፌዴራል ፖሊስ ሕንጻ ጋር ወደ ሳርቤት ገብሬል መስመር ሲታጠፍ ያነሳሁለት ጥያቄ ነበር፡፡

“ወፍ የለም ባክሽ!”

“እውነትህን ነው?”

Addis Ababa Yellow cab

Addis Ababa Yellow cab

“አዎ!ሰው ለምን እንደሆነ አላቅም ቢጫ ታክሲ ይፈራል፡፡ ኮማንድ ፖስት እያሉ ሙድ የሚይዙብን አሉ፡፡ ዋጋችን ዉድ ስለሚመስላቸው መሰለኝ፡፡”

ሳቅኩኝ፡፡ ቴዲ ዝም ብሎ የሚነዳ ሾፌር አይደለም፡፡ ተጫውቶ የሚያጫውት አይነት ነው፡፡

“ገና እኮ ዋጋ ሳይጠይቀን ነው ሰው ዝም ብሎ የሚሸሸን፡፡”

“እኔ እንደውም ብዙ ሰው እንደወደዳችሁ ነው የሰማሁት”

“አይምሰልህ! ያዲሳባ ሕዝብ ድሮም ወረተኛ ነው፤ አይገር ባስ ሲመጣም እንዲህ አድርጎት ነበር፣ ባቡሩ ሲመጣም ቆልቶት ነበር፡፡ ከዚያ ዞር ብሎ አያይህም፡፡አንተ ነህ ፍዳህን የምትበላው፡፡”ደርሶ ሆድ ባሰው፡፡

“ላዳ ታክሲ ግን አበቃለት ማለት ነው?”

“አይመስለኝም፡፡ እንዲያውም አሁን ሳስበው እኛንም አንደኛውን ሰማያዊ ቢቀቡን ይሻለን ነበር፡፡”

እንደገባኝ ቴዲ ቢቀልድ ቢጫወትም ዉስጥ ዉስጡን ድምጹ ስጋት የተጫነው ይመስላል፡፡ በመኪናዋ አዲስነት ደስተኛ ነው፣ የባንክ እዳው ግን ፍርሃት ለቆበታል፣ የገበያ መጥፋት ደግሞ ግራ አጋብቶታል፡፡ በወር 5850 ብር መቆጠብ አለበት፡፡

“በዛች ከርካሳ ማዝዳ ቢሆን እኮ እስካሁን አንድ አምስት መቶ ሸቃቅዬ ነበር፣ ማርያምን!”

“ማዝዳ ነበር የነበረችህ??”

“መዓዚ ነበር የምላት፡፡ ትዳር በለው፡፡ ከ97 ጀምሮ 10 ዓመት ነድቻታለሁ፡፡”

አዘንኩለት፡፡ከመአዚ ጋር ጥልቅ ፍቅርና ጠንካራ ቁርኝት እንደነበረው ከድምጹ ያስታውቃል፡፡

ጀርመን አደባባይ ተዘጋግቶ ጠበቀን፡፡ ትራፊክ የለም፡፡ ሁሉም መኪኖች ቀድመው አደባባይ ለመግባት ይሞክራሉ፡፡ ቴዲ አዲሷ ሊፋን እንዳትጋጭበት የሰጋ ይመስለኛል፡፡ እንደ ታክሲ ሾፌር አይደለም የሚነዳው፡፡

***

በሁሉ ነገር ግራ የሚገባው መንግሥት የአዲስ አበባን የትራንሰፖርት ጭንቀት ለመፍታት ብስክሌት ሳይቀር ሞክሯል፡፡ ተሳክቶለት ግን አያውቅም፡፡ ግንቦት መጀመርያ፣ 2008 ዓ.ም 08/2008 ተብሎ የሚጠራ መመሪያ አወጣ፡፡ በዚህ መመሪያ መሰረት ቀድሞ በላዳ ታክሲ ተሰማርተው የነበሩ ወይም በብሔራቸው የቦሌ ታክሲ የነበሩ ሁሉ በአክሲዮን ተደራጅተው ከመጡ አዳዲስ ታክሲ ያለቀረጥ እንዲያስገቡ እፈቅዳለሁ አለ፡፡ ይህ መመሪያ እንደተሰማ 79 ማኅበራት ትራንስፖርት ቢሮን አጣበቡ፡፡

አንድ ሕጋዊ አክሲዮን ማኅበር፣ ወይም ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር በትንሹ 50 ታክሲ ማዝገባት አለበት ሲባል 79ኙም ማኅበራት ደነገጡ፡፡ አንድ ሀምሳ ማኅራት ወዲያዉኑ ጠፉ፡፡ መንግሥትም ደነገጠ፡፡ በአንድ ማኅበር መግባት ያለባቸው ትንሹ የታክሲ ቁጥር ከ50 ወደ 35 ዝቅ እንዲል አደረገ፡፡

መመሪያው በሚያዘው መሰረት እያንዳንዱ አክሲዮኑ በባንክ ሒሳብ የመኪናውን 30 በመቶ ብር ተቀማጭ እንዲያደርጉ አዘዘ፡፡ ይህን ጊዜ ተንደርድረው ከመጡ 79 ማኅበራት 53 የሚሆኑት የገቡበት አልታወቀም፡፡ 26ቱ ብቻ የተባሉትን ገንዘብ አስቀመጡ፡፡

“ብዙዎቹ መንግሥት መኪናውን ገዝቶ በስጦታ እንዲያበረክትላቸው ጠብቀው ነበር መሰለኝ” አለኝና በረዥሙ ሳቀ፣ ቴዲ፡፡

“አሁን ከተማዋ ዉስጥ ስንት የዉበት እስረኛ ነው ያለው ግን? በዛችሁብኝ፤ በየቦታው ነው የማያችሁ፡፡”

“በዝተን አይምሰልሽ ቀዮ፤ የጠጅ ቀለም ቀብተውን ከየትም ስለምንታይ ነው የበዛንብሽ፡፡” በድጋሚ ዘለግ ያለ ሳቅ ሳቀ፡፡ ጤንነቱን መጠራጠር ጀመርኩ፡፡ ለምንድነው ይሄ ልጅ አብዝቶ የሚስቀው?

ከዉጭ አገር ከተገዙት 1163 ታክሲዎች 826 ገብተው አገልግሎት እየሰጡ ነው፡፡ 821 የሚሆኑትን ገንዘብ ያበደራቸው ብርሃን ባንክ ነው፡፡ ቀሪዎቹን ንግድ ባንክና ንብ ባንክ ደርሰውላቸዋል፡፡ ያኔ ነገሩ ሲጠነሰስ “አገልግሎቱ በኪሎ ሜትር ይሆናል፡፡ እያንዳንዱ ማኅበር የተማከለ የጥሪ ማዕከል ይኖረዋል” ተብሎ ነበር፡፡ እንደ ኡበር መሆን የቃጣቸው ወጣት የሶፍትዌር ሊቃውንትም በታክሲ አገልግሎት ዙርያ አዲስ ግኝት አለን ሲሉ በሚዲያ ወጣ ወጣ ማለት ጀምረው ነበር፡፡ ትራንስፖርት ሚኒስቴርና የዉበት እስረኞቹ ግን በታሪፉ ጨርሶ ሊግባቡ አልቻሉም፡፡

“ሼም አያቅም እንዴ መንግሥት? በከተማ አውቶቡስ ዋጋ ሊያሰራን ይፈልጋል እንዴ? የማነው በናታቹ?” ቴዲ የታሪፍ ጉዳይ ሲነሳባት ደርሶ ቱግ ይላል፡፡

“ስንት ወሰኑላቹ?”

“በኪሎ ሜትር ዴች”

“10 ብር? ዘርፈሽኛላ ቴዲ?” ከእስቲፋኖስ ጀሞ የተስማማሁበት ዋጋ ደርሶ ጎኔን ሰቀዘኝ፡፡

“አንሰማውም ባክሽ! ከቦሌ ጊዮርጊስ 10 ኪሎ ሜትር ነው፡፡ በመቶ ብር ልንጭለት ይፈልጋል እንዴ? ላሽ በለው?”

ቴዲ እውነቱን ነው፡፡ መንግሥት ያስኮረፈውን የአዲስ አበባን ሕዝብ በታክሲ ታሪፍ ሊክሰው እየሞከረ ይመስላል፡፡ 10 ብር አሁን ፓኮ ኒያላ አይገዛም፡፡ አንድ ስፖኪዮ ቢሰበር አንድ ሺ ብር አይበቃም፡፡ ሰርቪስ አለ፡፡ ፍሬን ሸራ አለ፡፡ የትራፊክ ቅጣት አለ፡፡ ከሁሉ በላይ ደግሞ የባንክ እዳ እነ ቴዲን ግሮሯቸው ላይ ቆሟል፡፡ እንዴት ነው በ10 ብር ታሪፍ ይህን ሁሉ የሚሸፍኑት? እርግጠኛ ነኝ አይሰሩለትም፡፡

“ሊፋኖቻችሁ እዚህ ነው አይደል የተገጣጠሙት?”

“ኸረ አይደለም! ከዉጭ ነው የመጡት፡፡ ሊፋን መሆናቸውን አይተሸ ነው?” ቴዲ ጮኸ፡፡ በስፖኪዮው ገላመጠኝ፡፡ “ቀለሙን ጨምሮ አንድ ነገር ሳይቀር ከዉጭ ነው የገባው፡፡ ታርጋ ብቻ ነው ከአገር ዉስጥ” በራሱ ቀልድ ዘለግ ያለ ሳቅ ሳቀ፡፡

“እኮ ያው ስሪታቸው ቻይና ነው፡፡”

ቴዲ ከቻይና መሆናቸውን ቢያውቅም እንዲነሳበት አይፈልግም፡፡ የገቡት ከዉጭ ነው፣ በቃ፡፡ ከብዙ መተከዝ በኋላ ጀርመን አደባባይን እንዳለፍን፣ ዋናውን የጀሞን መንገድ እንደያዝን ሊፋን በመግዛቱ እንደሚጸጸት ተናዘዘ፡፡

“ሊፋን የቻይና መኪና ነው፡፡ ጥሎበት ቶሎ ይገረጅፋል፡፡ ይኸው አይገር ባስ የአሮጊት መስሎ አታየውም? ቢሾፍቱ ባስ እንዴት ማስጠሎ እንደሆነ አታይም? ቻይና እድሜዋ አጭር ነው፡፡መሪዉን በቡጢ ነረተው፡፡”

“ማርያምን ተገነተርኩ፡፡ መባነን ነበረብኝ”

ላጽናናው አልፈለኩም፡፡ ይዉጣለት፡፡

***

ሊፋን ከቤቱ 365ሺ ብር ነው፡፡ መንግሥት ቀረጥ አነሳለቸውና ዋጋውን ወደ 220ሺ ብር አወረደላቸው፡፡እስከነ ኢንሹራንሱ 98 ሺህ ብር ከፍለዋል፡፡ ኾኖም የባንክ ወለድ አለባቸው፡፡ 80 ሺ ብር ወለድና የመኪናው ቀሪ ብር 130ሺ በድምሩ 210 ሺ ብር በ2 ዓመት ገቢ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል፡፡ ለዚያ ነው እነ ቴዲ አብዝተው የሚጨነቁት፡፡

ምናልባትም እነ ቴዲ የሊፋንን እዳ ከፍለው በሚጨርሱበት ወቅት ሊፋኗ ራሱ አብራ ከእዳው እኩል ታልቅ ይሆናል፡፡ በዚህ እርግጠኛ መሆን ይቻላል፡፡ የሆላንድ ካር አባይን፣ የመስነፍን ኢንጂነሪንግ ጂሊን የገዙ ወዳጆቼ መኪኖቻቸው እንደ ጭስ ተነውባቸዋል፡፡ ለቴዲሻ በድጋሚ አዘንኩለት፡፡

እስከነአባባሉ ልፋ ያለው ሊፋን ይገዛል ነው የሚባል፡፡

የጀሞን አደባባይ ለመሻገር አንድ 25 ደቂቃ ቆምን፡፡ መንገዱ ተቆላልፏል፡፡ ቴዲ የሊፋንን ግለ ታሪክ ጨርሶ ወደ አቫንዛ ታሪክ ገባ፡፡

ቢጫዎቹ ታክሲዎች ሁሉም ደም ግባታቸው ልዩ ነው፡፡ በተለይ ሽንጣሞቹ አቫንዛ ቶዮታዎች ከዉብም ዉብ ናቸው፡፡ 460ሺ ብር ከቀረጥ ነጻ እንደወጣባቸው ቴዲ አጫወተኝ፡፡

“ነገሩን የቆሰቆሱት እኮ የቦሌ ታክሲዎች ናቸው፡፡ በተለይም አዲስ ሜትር ታክሲ የሚባል ማኅበር አለ፡፡ የፖለቲካ ማኅበር በለው፡፡ መሪዎቹ መሬ* ናቸው፡፡ ከለታት አንድ ቀን መንግሥት ጋ ሄዱና “ይሄ እኛ የምንነዳው ከርካሳ ታክሲ የአገር ገጽታ እያበላሸ ነው፡፡” የቱሪዝም መዳከም ዋናው መንስኤ የቦሌ ታክሲዎች ሞተር መድከም ነው ብለው ተቀደዱ፡፡ ወዲያውኑ ተፈቀደላቸው፡፡ ምን አይነት መኪና እናስመጣ በሚለው ብዙ ክርክር ካካሄዱ በኋላ የ2016 አቫንዛ ቶዮታ ይሁንልን ብለው ወሰኑ፡፡ ይሄ ሙድ ያለው መኪና የሀብታም መኪና እንደሆነ ነው የሚታወቀው፡፡ ለታክሲነት በጭራሽ የሚታሰብ አይደለም፡፡ ማኅበሩ እንዴት እንደመረጠው አላውቅም፡”

“ከሊፋን መቼስ የትናየት ይሻላል” አልኩኝ፡፡ ሳላስበው የከረመ ቁስል ቀሰቀስኩ፡፡

“ፍሬንድ! ምን ነካሽ!? ባጃጅና ሊሙዚን ታወዳድሪያለሽ እንዴ?” አቫንዛ እኮ አንድ ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ነው ከቤቱ የሚገዛው፤ ዜሮ ዜሮ፣ ያለጠፈ፡፡” በዉስጥ ስፖኪዮ አፈጠጠብኝ፡፡

“ታዲያ አንተ ከሊፋን እሱ አይሻልህም ነበር?”

“ቀላል ይሻላል እንዴ! ያኔ አልባነንማ፡፡ ቅድመ ክፍያው 120 ሺ ብር ነው ሲሉኝ ደንግጬ ይብራብኝ አልኳቸው፡፡ለሊፋን በከፈልኩት ብር 22ሺ ብጨምርበት ዛሬ የአቫንዛ ጌታ ነበርኩ፤ ማርያምን!”

ቴዲ እውነቱን ነው፡፡ አቫንዛ ቶዮታ የተቀናጣ የሀብታም መኪና ነው፡፡ እንዲያውም ሀብታሞች እንዴት የኛ መኪና እንደ መናኛ ለታክሲነት ይፈቀዳል ብለው መንግሥት ላይ አቂመዋል አሉ፡፡ እጃቸው ላይ ያለ አቫንዛን ባገኙት ዋጋ መሸጥ ጀምረዋል ይባላል፡፡ በዚህ ምክንያት የለጠፈ አቫንዛ ዋጋው ዘጭ ብሏል ይባላል፡፡ ከባለጸጋነት ወደ ታክሲ ሾፌርነት ያወረዳቸው መንግሥት ደጋፊዎቹን ሳያስቀይም አልቀረም፡፡

እነዚህ 2016 አቫንዛ ቶዮታ አውቶሞብሎችን በግል ወደ አገር ቤት ለማስገባት አንድ ሚሊዮን ሁለት መቶ ሺ ብር ይፈጃል፡፡ ኾኖም በመንግሥት ቸርነት ማኅበሩ በ460ሺህ ብር ነው አጠናቆ ወደ አገር ቤት ያስገባቸው፡፡

በዚያ ላይ ቴዲ እንደሚለው አቫንዛ በአንድ ጊዜ 7 ቀጠን ያሉ ሰዎችን መያዝ ይችላል፡፡ ሻንጣ ያለው ሰው ከመጣ የኋላው ወንበር ይታጠፍና ሰፊ የሻንጣ ቦታ ይፈጠራል፡፡

“ወፍራም አረቦች በድሮ ላዳ ታክሲ ሲገቡ የተወሰነ ቦርጫቸው ዉጭ ይቀራል፡፡ ስለዚህ አቫንዛን ነው የሚመርጡት፡፡” አለኝ ቴዲዮ እየሳቀ፡፡

ጀሞ ደረስኩ፡፡ የቴዲ ሳቅ ዘላቂ አልመስልህ አለኝ፡፡ እዳው ሲያልቅ ሊፋኑም አብራ የምታልቅ መሰለኝ፡፡

ወያኔን በመቃወም ኢትዮጵያውያን በጀርመን ጎዳናዎች ለሰልፍ ወጡ –ቪዲዮ ዘርይሁን ሹመቴ

$
0
0

ወያኔን በመቃወም ኢትዮጵያውያን በጀርመን ጎዳናዎች ለሰልፍ ወጡ – ቪዲዮ ዘርይሁን ሹመቴ

ወያኔን በመቃወም ኢትዮጵያውያን በጀርመን ጎዳናዎች ለሰልፍ ወጡ – ቪዲዮ ዘርይሁን ሹመቴ


ወታደራዊ መረጃ እና የጌታቸው አሰፋ “ልጆች” እጣ ፈንታ -ከዶ/ር ታደሰ ብሩ

$
0
0

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የሳሞራ የኑስ ቡድን የበላይነት መያዙ የሚያረጋግጥ ነው። ይህ በህወሓት የስለላ ተቋማት ሥራ ላይ የሚኖረው ተጽዕኖ ምንድነው?

Tadesse-Kersmo-290

ዶ/ር ታደሰ ብሩ

ህወሓትን በቅርበት የሚከታተሉ ሰዎች እንደሚያውቁት ከመለስ ዜናዊ “መሰዋት” በኋላ ድርጅቱ ውስጥ ሁለት ቡድኖች ጎልተው ወጥተዋል። አንደኛው ቡድን ማንኛውም ዋጋ ተከፍሎ ቢሆን የህወሓት ፈላጭ ቆራጭነት መጠበቅ አለበት የሚሉ፤ ህወሓት እና የትግራይ ሕዝብ አንድ ናቸው እያሉ በአደባባይ የሚሰብኩ፤ የይስሙላ ስልጣን ቢሆንም እንኳን የኃይለማርያም “ጠ/ሚኒስትር” ተብሎ መጠራት ምቾት የማይሰጣቸው፤ ለአገሪቱ የፓለቲካ ችግሮች ሁሉ መፍትሄው ጉልበት ነው ብለው የሚያምኑ ከፍተኛ የአስተሳሰብ ችግር ያለባቸው ሰዎች የተሰበሰቡበት ነው። የዚህ ቡድን መሪ ሳሞራ የኑስ ነው። ሌላኛው ቡድን ደግሞ የህወሓትን የበላይነት ለማቆየት የሚቻለው በዘዴና በጥበብ እንጂ በጉልበት አይደለም፤ ስለሆነም ትንሽ እንለሳለስ ባይ ነው። የዚህ ቡድን መሪ ጌታቸው አሰፋ ነው።

በመግቢያዬ እንዳልኩት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የሚነግረን ነገር ቢኖር የጌታቸው አሰፋ ቡድን በሳሞራ የኑስ ቡድን መሸነፉን ነው። አሁን አገራችን ድርና ማጋቸውክፋት ብቻ በሆኑ ሳሞራ የዩኑስና ፀጋዬ በርሄን በመሳሰሉ የአዕምሮና ድኩማን እየተመራች መሆኑን ነው።

ሳሞራ የሚመራው የጦር ሠራዊት ብዙ የሚገርሙ ነገሮች አሉበት። ጄኔራሎች እስካሁን መዋጮ ከፋዮች የህወሓት አባላት ስለመሆናቸው ብዙ የተባለበት ስለሆነ ደግሞ ማንሳት ዋጋ የለው። ዛሬ በትንሹ ልዳስሰው የምፈልገው የወታደራዊ መረጃ ዋና መምሪያን ነው።

መከላከያ ሚኒስቴር ውስጥ ለጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙ ተጠሪ የሆኑ አምስት ዋና መምሪያዎች አሉ፤ ከእነዚህ አንዱ ወታደራዊ መረጃ ዋና መምሪያ ነው። ይህ ዋና መምሪያ ሰዋዊ (human) መረጃ፣ ኤሌክትሮኒክስ መረጃ (INSAም እዚህ ውስጥ ይገባል)፣ ፀረ-መረጃ፣ የእዞች መረጃ፣ የክልሎች መረጃ፣ የድንበር ክትትል፣ የውጭ አገራት መረጃዎችን የሚባሉ መምሪያዎች፣ ዋና ክፍሎችና ክፍሎች አሉት። ወታደራዊ መረጃ ሲባል የሚሊታሪ ኢንተለጀንስ ሊመስል ይችላል። እውነታው ግን ከዚህ በጣም፣ በጣም የተለየ ነው። የሳሞራ “ወታደራዊ መረጃ” የማይመለከተው ጉዳይ የለም። የወታደራዊ መረጃ human intelligence ለምሳሌ በሁሉም የሴክተር መሥሪያ ቤቶች ውስጥ ኤጀንቶች አሉት። በሌላ አገለጽ የሳሞራ ሰላዮች የግብርና ሚኒስቴርንም የትምህርት ሚኒስቴርንም፣ መስጊዶችንና ቤተክርስቲያኖችን፣ ሆቴሎችንና ዮኒቨርስቲዎችን ይሰልላል። ይህ የጌታቸው አሰፋ ተቋም ሥራ ቢሆንም የወታደራዊ መረጃ “ባለሙያዎች” “የኛ ያልሆነ የስለላ ሥራ በአገሪቱ ውስጥ የለም” ባዮች ናቸው። ከሁሉ የሚብሰው በክልሎች፣ በዞንና በወረዳዎች ነው። በመከላከያ ስር 4 እዞች አሉ፤ ሰሜን እዝ፣ ማዕከላዊ እዝ፣ ምዕራብ እዝ እና ደቡብ ምስራቅ እዝ ይባላሉ። የክልሎች ወታደራዊ መረጃዎች የሚሄዱት ለእዝ አዛዦች ነው። ይህ አሠራር የእዝ አዛዦች ከክልሎች ፕሬዚዳንቶች በላይ መረጃና ስልጣን እንዲኖራቸው አድርጓል። በውጭ አገራት ኤምባሲዎችም ውስጥ የሚሊታሪ አታሼዎች ሥራ ከዚህ ዋና መምሪያ ጋር የተሳሰረ ነው።

የወታደራዊ መረጃ ዋና መምሪያ አዛዥ ሜ/ጄ/ ገብሬ ዴላ ይባላል። ዴላ እውነተኛ የአባቱ ስም አይደለም፤ የትውልድ ሥፍራዉ ትግራይ አምባላጌ ያለ የአካባቢ መጠሪያ ነው። ሜ/ጄ/ ገብሬ ዴላ የሳሞራ የቅርብ ወዳጅ ነው፤ ስለ ኢንተለጀንስ እውቀት ባይኖርም ከሳሞራ ያላነሰ ክፋት አለው፤ በሳሞራ መልካም ፈቃድ ከክፍለ ጦር አዛዥነት ወደ ወታደራዊ መረጃ ዋና መምሪያ ኃላፊነት የተተኮሰ ሰው ነው።

ከገብሬ ዴላ ጋር ሲነፃፀር ጌታቸው አሰፋ የተሻለ ግንዛቤ አለው፤ የህወሓት አገዛዝ ችግር ውስጥ መግባቱ ያውቃል፤ ሆኖም ግን በደነዞች ተበልጦ ተሸንፏል። አሁን ሳሞራ የአገዛዙን መሪ ጨብጧል፤ ከመረጃ አንፃር ደሞ መሪነቱን ገብሬ ዲላ ወስዷል። ድሮም የገብሬ ቢሮ በጌታቸው ቢሮ ሥራዎች ጣልቃ ይገባ ነበር፤ አሁን “ጣልቃ መግባት” ሳይሆን በአዋጁ መሠረት ህጋዊ ሥራው ሆኗል።

የገብሬ ዲላ ሰዎች ቀጥለው ምንድነው የሚያደርጉት? ጌታቸው አሰፋ ቀጥሎ የሚመጣውን ገምቶ መንቀሳቀስ ከአሁኑ ጀምሯል ብዬ አምናለሁ። ራሳቸውን “የኢንተለጀንስ ባለሙያዎች” አድርገው የሚቆጥሩ፤ ሁሉ በእጃቸው የሚመስላቸው የጌታቸው አሰፋ “ልጆች” አደጋ ውስጥ ናቸው፤ ገብሬ ዲላ ተፎካካሪ አይወድም፤ ሶሞራ ደሞ ከእርሱ በላይ ሰው በዓለምም ላይ ያለ የማይመስለው ግብዝ ነው። የሶሞራ መንግሥት የህወሓት አገዛዝን ውድቀት ያፋጥናል፤ ከመሞቱ በፊት ግን የሁልጊዜ ተፎካካሪውን የጌታቸው አሰፋ ቢሮ ሰላዮችን ይበላቸዋል። የጌታቸው አሰፋ ቢሮ ሰዎች ራሳችሁን ለማዳን ያላችሁን አጭር ጊዜ ተጠቀሙበት።

የፕሬዝዳንት ሙላቱ ሪፖርት እና የፋና ውይይት…. ግርማ ሠይፉ ማሩ

$
0
0

girmaseifu32@yahoo.com, www.girmaseifu.blogspot.com

Girma-Siefu.jpgታሪከኛው የ2007 ምርጫ ተጠናቆ ገዢው ፓርቲ `መንግሰት` መስርቻለሁ ባለ ማግስት በተጀመረ ህዝባዊ እንቅስቃሴ ሲናወጥ የከረመው መንግስት የሁለተኛ ዓመት ስራውን ለመጀመር ማሟሻ ንግግር የሚያደርጉት ፕሬዝዳንት ሙላቱ ተሾመ መሰከረም 30/2009 ንግግር አድርገዋል፡፡ ተከትሎም የግንባሩ ልሣን ፋና ብሮድካሰቲንግ ማስመሰያ ውይይት አዘጋጅቷል፡፡ ከፕሬዝዳንቱ ሪፖርት እና ከፋና ውይይት ምን እንጠብቅ የሚል ጥያቄ ለራሴ አቅርቤ ትዝብቴን አሰቀምጫለሁ፡፡ የፕሬዝዳንቱ የመክፈቻ ንግግር እና የፋና የውይየትት ፕሮግራም በተለመደው መስመር ማዘናጋት እና አሁንም ገዢው ፓርቲ ህወሃት/ኢህአዴግ መሆኑን አረጋግጦ ማለፍ ነው፡፡ የተወሰኑ ነጥቦችን አንስተን ለመመልከት እንሞክር፡፡

እንደ መነሻም በሰሞኑ ለነበረው የህዝባዊ እንቅስቃሴ ሞተር ለነበረው ወጣት ትውልድ ማዘናጊያ የሚሆን 10 ቢሊዮን ብር መመደቡን አብሰረዋል የዚህ ዓመት በጀት ጉዳይ በሰኔ 30 መጠናቀቁን የሚያስታውስ ሰው ያለ አልመሰላቸውም፡፡ ቀደም ሲል የኦሮሚያ ፕሬዝዳንት የነበሩት አቶ ሙክታርም ለኦሮሚያ ቀወስ 3 ቢሊዮን በጀት ዓመቱ ሊጠናቀቅ ሶሰት ወር ሲቀረው ለወጣቱ ሰራ ፈጠራ መድነበናል ብለው ነበር፡፡ ይህ በጀት የኦሮሚያን ችግርም አላበረደም አቶ ሙክታርንም በስልጣን ሊያቆይ አልቻለም፡፡ 10 ቢሊዮን ብር በጀት የወጣቱን ጥያቄ ለመመለስ የወሰዱትን እርምጃ በአስገራሚነቱ ተወዳዳሪ ሊኖረው አይችልም፡፡ ምን ማለት ነው “ወያኔ ይውደም!!” ብሎ መፈክር ለሚያሰማ ወጣት መልሱ “አርፈህ ወደ ስራ ግባ!!” እንደማለት ነው፡፡ ወጣቱ የጠየቀው የስርዓት ለውጥ ነው፡፡ የስርዓት ለውጥ የሚያመጣውን ማነኛውንም እድል የስራ ዕድልን ጨምሮ ለማየት ይፈልጋል፡፡ 25 ዓመት ተሞክሮ ያልተሳካለት አብዮታዊ ዲሞክራሲ ትንተና መልስ እንደማይሰጠው ነው ወጣቱ የተናገረው፡፡ ለዚህ መልስ መስጫው መንገድ ተዘዋዋሪ የብድር ገንዘብ ተዘጋጅቶዋል የሚል ፌዝ ያዘለ መልስ ያስቃል፡፡ ህወሃት/ኢህአዴግ ጉዳዩን የምር እንዳልያዙት የሚያስታውቀው በቅርቡ ሬዲዮ ፋና በጠራው ስብሰባ ላይ የተጋበዙት የወጣቶች ተወካይ የኢህአዴግ አደረጃጀት ወጣት ናቸው፡፡ እነዚህ ወጣቶች ሰልፍ አልወጡም ጥያቄም አላቀረቡም፡፡ ይልቁንም ጥያቄ ያነሱትን ወጣቶች ፀረ-ሰላም እያሉ የሚከሱ ቡድን ተወካይ ናቸው፡፡ ምን አልባትም የተመደበው በጀት ለዚህ ቡድን ሊያገለግል ይችላል፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ ከአንድ ጓደኛዬ ጋር ስናወራ ይህ የስርዓቱ ትክክለኛ መገለጫ ነው፣ ችግሮች የሚፈቱት በገንዘብ ይመስላቸዋል፡፡ ሙሰኛ ስርዓት ህዝብንም ሙሰኛ አድርጎ በማየት በገንዘብ ለመደለል ይሞክራል ነው ያለኝ፡፡ እኔም ተሰማምቼበታለሁ፡፡ ገንዘብ ካለ በሰማይ መንገድ አለ ከሚል የዘራፊዎች ቡድን ከዚህ የተሻለ የመፍትሔ አቅጣጫ አይገኝም፡፡ የወጣቱ ጥያቄ የስርዓት ለውጥ ነው፡፡ መልሱም እንዴት በተረጋጋ ሁኔታ የስርዓት ለውጥ እናምጣ የሚለው ነው፡፡ መልሱን ከወጣቱ ጋር በግልጽ መወያየት ነው፡፡ ወጣቱ ተወካይ የለውም እንዳትሉን ከዚህ በፊት እንደዳልኩት እኔ ዞን ዘጠኝ የሚባሉትን ወጣቶች ወክያለሁ ……. ሌላም መጨመር ይቻላል፡፡ ከፎረም ውጭ ……

በፕሬዝዳንቱ ንግግር ውስጥ ትኩረት አግኝቶ በተለያየ መንገድም ትኩረት የሳባው የምርጫ ህግ ማሻሻል የሚመለከተው ነው፡፡ የምርጫ ህግ ማሻሻል ሲባል ብዙ ሰው “ህገ መንግሰት ማሻሻል” መሆኑንም ዘንግቶታል፡፡ ከብዙዎቹ አንዱ ፕሬዝዳንት ሙላቱ ናቸው፡፡ የኢትዮጵያ ህገ መንግሰት አንቀፅ 54/2 በአንድ ምርጫ ክልል አብላጫ ድምፅ ያገኘ ያሸንፋል በሚለው መስረት ይመረጣል ነው የሚለው፡፡ ሰለዚህ ሌላ የምርጫ ስርዓት ማድረግ አይቻልም፡፡ ህገ መንግሰቱ ሳይሻሻል ማለት ነው፡፡ ሌላው ህወሃት/ኢህአዴግ ማስተላለፍ የፈለገውን መልዕክት ብዙ ሰው የተቀበለው ይመስለኛል፡፡ ይህ መልዕክት “ህውሃት/ኢህአዴግ እና አጋሮች አሸንፈዋል” የሚለው ነው፡፡  ይህ ማለት ግን “ሁሉም ሰው መርጦናል ማለት አይደለም” የሚለውን መልዕክት ነው፡፡ ይህ ደግሞ ምርጫው ነፃ፣ ፍትሃዊና ታማኝነት ነበረው ለማለት ነው፡፡ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚያስፈልገው ነፃ፣ ፍትሃዊ፣ ግልፅነት ያለው ምርጫ እንጂ የምርጫ ስርዓት ለውጥ አይደለም፡፡ የምርጫ ስርዓት ለውጥ የሚጠቅመው በቢሮ ቁጭ ብለው የፓርቲ ሰርተፊኬት እና ማህተም በፌስታል ይዘው የብሄር ተወካይ ነን በሚል የውክልና ስልጣን ለማግኘት ለሚፈልጉ ጥቂት ግለሰቦች ነው፡፡ አሁን ባለው ምርጫ ስርዓት ኢትዮጵያ ውስጥ የብዙሃን ፓርቲ ስርዓትን ማረጋገጥ ይቻላል፡፡ ከዚህ የተለይ የምርጫ ህግ የሚመክሩን የውጭ አማካሪዎችም ሆኑ ኢትዮጵያዊያን ልሂቃን በኢህአዴግ ምርጫ አሸንፊያለሁ ችግሩ የምርጫ ስርዓቱ ነው በሚለው መታለላቸውን ማስታወስ ይኖርብኛል፡፡ በመደራጅት መብት ስም ማንም ሱሰኛ የፓርቲ ሰርተፊኬት ይዞ ዕጩ የሀገር መሪ ቡድን ነኝ ሲል ዝም ሊባል አይገባም፡፡ በምርጫ ስርዓት ማሻሻል ሰምም የህዝብ ውክልና ማገኘት ዕድል ሊመቻች አይገባም፡፡

በኢትዮጵያ ሀገራችን ውይይት አጅግ በጣም አስፈላጊ እና በእጅጉ የጎደለን የሰልጣኔ መንገድ እንደሆነ ይስማኛል፡፡ ውይይት ሲባል ደግሞ ገዢዎች ንግግር ሲያደርጉ የሚያዳምጣቸውን የፎረም ተወካዮች ሰብሰቦ ሲሞጋገሱ መዋያም መድረክ አይደለም፡፡ ውይይት ሲባል ሃሳብ ተለዋውጦ የሃሳብ ሽግሽግ ለማድረግ መዘጋጀትንም ይጠይቀል፡፡ የሃሳብ ሽግሽግ የሚደረግበት የውይይት መድረክ ሀገራችን በእጅጉ ያስፈጋታል፡፡ በሰብሰባ ውስጥ የህዝብ ሰሜት የሚኮረክሩ ንግግሮች ከተደረጉ በኋላ ሹሞች ያሻቸውን በማጠቃለያነት ተናግረው፣ ሲፈልጉም ዘለፋ አክለውበት ምን ታመጣላችሁ፣ ከቻላችሁ ተደራጅታችሁ እራሳቸሁን አጠናክራችሁ መጥታችሁ ግጠሙን በሚል ፉከራ የሚጠናቀቅ መሆን የለበትም፡፡ ይህ ዓይነቱ መድረክ የውይይት ሳይሆን የፉከራና ቀረርቶ ነው ሊባል የሚችለው፡፡ ተጠናክሮ መጥቶ ለመጋጠም የሕወሃት/ኢህአዴግ ምክር አስፈላጊ አይመስለኝም፡፡ መጋጠሚያ ቦታውን እና የመጋጠሚያ ህጉን ማስተካክል ነው፡፡ የብረት ቦክስ ይዞ ሜዳ እየገቡ ባዶ እጅ ያለን ተጋጣሚ ማድማትና ማቁሰል ጉብዝና ሳይሆን ህገወጥ መሆን እና ውንብድና ነው፡፡

ሌላው የሪፖርቱ አስገራሚ ነጥብ የዜጎች መፈናቀል የሚመለከተው ነው፡፡ ዜጎችን ማፈናቀሉ ትክክል እንዳልሆነ ተገንዝቢያለሁ ያለ የሚመስለው ገዢው ፓርቲና መንግሰት በተዘዋዋሪ ማፈናቀል እቀጥላለሁ ነገር ግን የሚሰጠውን ካሳ ከጊዜው የዋጋ ንረት፣ የምርት ዋጋ እና ምርታማነት እድገት ጋር ተገናዝቦ ይሻሻላል የሚል መግለጫ እየሰጠ ይገኛል፡፡ አታፈናቅሉኝ ያለን ዜጋ ዋጋ ጨምረን እናፈናቅልህ እያሉት ነው፡፡ ህውሃት/ኢህአዴግ ችግሩን ከመስረቱ መፍታት ሳይሆን አሁንም ዙሪያ ጥምጥም መሄድ መርጠዋል፡፡ የህዝቡ ጥያቄ የመሬት ባለቤትነት ጥያቄ መልስ ያግኝ ነው፡፡ የያዘውን መሬት ለልማት ሲባል እንዴት እና በምን ዓይነት ሁኔታ እንደሚለቅ በኋላ የሚደረስበት የውይይት ነጥብ ነው፡፡ ይህ ጉዳይ እንደ ምርጫ ሰርዓቱ ህገ መንግሰታዊ ጉዳይ ነው፡፡ ገዢው ፓርተ የመሬት ነገር በመቃብሬ የሚለውን ነገር ወደ ጎን ትቶ መሬት ለባለመሬቱ ማስተላለፍ ይኖርበታል፡፡ ቀሪውን ስንደርስ የምንጫወታው ይሆናል …… ድልድዩን ሰንደርስ እንሻገራለን እንደሚባለው መሆኑ ነው፡፡

የህወሃት/ኢህአዴግ ጥልቅ ተሃድሶ ፍልስፍና ፈርሶ እስከ መሰራት እንደማይደርስ አቶ አባይ ፀሃዬ ነግረውናል ባይነግሩንም የሚታወቅ ሀቅ ነው፡፡ ፈረሰው ይሁን፣ በአሸዋ ላይ ፓርቲያቸውን መስራት የእነርሱ ምርጫ ነው፣ ይህን ምርጫቸውን የምናከብርላቸው ቢሆንም አሁንም የኢትዮጵያን ህዝብ በካበኔ ሹም ሽር ለመሸንገል ተጨፈኑ እናሞኛችሁ ብሎ ማሰብ መፍትሄ ፍለጋ እና ችግሩን መረዳት ላይ እጅግ ልዮነት እንዳለን ማሳያ ነው፡፡ የኢህአዴግ ካቢኔ ማንንም ይዞ ቢመጣ መስመሩን እስከ አላስተካከለ እና በመድበለ ፓርቲ ስርዓት ውስጥ ቁጥጥር የሚደረግበት ካልሆነ ትርጉም የሌለው ድካም ነው፡፡ ምን አልባትም በራሳቸው ስር ሌላ አኩራፊ ከመጨመር ውጭ የተለየ ፋይዳ አይኖረውም፡፡ አቶ ጁነዲን ሳዶን የመሰለ የአብዮታዊ ዲሞክራሲ ፈላስፋ (በሀገር ውስጥ እያለ) አሁን በግልፅ ምንም ስልጣን አልነበረኝም ስልጣኑ የህወሃት ነው ማለቱን ማስታወስ ያስፈልጋል፡፡ ተራው የማን ነው? መጠበቅ ነው፡፡

በመጨረሻ በቅርቡ ይወጣል የሚባለውን “የኦሮሚያን ልዩ ጥቅም በአዲስ አበባ” የሚመለከት አዋጅ ነው፡፡ ይህ አዋጅ ምን ያህል የተደከመበት ቢሆን ህወሃት/ኢህአዴግ በለመደው መልኩ አዋጅ አድርጎ ካወጣ በኃላ ንትርክ የሚፈጥር እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡ ቢያንስ በቅርቡ ይወጣል ሲባል እንኳን ለህዝብ ለውይይት የሚረዱ አንኳር ነጥቦችን ማጋራት አልቻሉም፡፡ ጉዳዮንም የኦሮሚያ ክልል ብቻ በማድረግ የአዲስ አበባ ነዋሪ ግብር ከፋይ ምንም መረጃ እንዲኖረው እየተደረገ አይደለም፡፡ ሰለዚህ ይህ አዋጅ ምን ይዞ ይመጣል ወደፊት የምናየው ነው፡፡ ፕሬዝዳንቱ ግን በቅርቡ ይታወጃል ብለዋል ….. ቅርብ መቼ ነው? በነገራቸን ላይ ሀረሪ ክልል በሚባለው ውስጥስ ቢሆን ኦሮሚያ ልዩ ጥቅም አያስፈልጋትም ትላላችሁ፡፡ ወይም ክልሉ ለኦሮሚያ ተሰጥቶ የሀረሪ ልዩ ጥቅም የሚባል ነገር በሃሳባችሁ መጥቶ አያውቅም፡፡ እጅግ በቁጥር አነስተኛ የሆኑ ሀረሪዎች ሁልጊዜ አሸናፊ የሚሆኑበት ምርጫ ኢትዮጵያችን ውስጥ ላለው አሳፋሪ የምርጫ አፈፃፀም ጉልዕ ማሳያ ነው፡፡ ሰለምርጫ ከላይ ያነሳሁትን ነጥብ እዚህም ማስታወስ የግድ ይላል፡፡ አዲስ አበባ መቼ ነው በነዋሪዎች ቀጥተኛ ምርጫ ከንቲባ የምትመርጠው የሚል ጥያቄ አሁንም አለኝ፡፡

ይህ ፅሁፍ በምንም መልኩ ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ጋር እንደማይጋጭ እራሴን ሳንሱር አድርጌ ነው የፃፍኩት፣ቢጋጭም ይጋጭ ብዬ ለጥፌዋለሁ፡፡

ቸር ይግጠመን!!!!

ኢትዮጵያን ከአደጋ ለመታደግ አስቸኳይ መፍትሔ ለመፈለግና ለሰላማዊ ሽግግር የሸንጎ ራእይ

$
0
0

ጥቅምት 12 ቀን 2009 ዓ.ም

shengoኢትዮጵያ አገራችን ከፖለቲካ ቀውስ ውስጥ ተማግዳ የቆየችበት ወቅት ገደቡን አልፎ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ሕዝባዊ እንቅስቃሴ ለመውለድ በቅቷል። በሙስሊም እምነት ተከታዮች፣ በኦሮሞ ክልል፣ በአማራው ክልል በጎንደርና ጎጃም የተቀሰቀሰውና የተቀጣጠለው ሕዝባዊ እምቢተኝነት የዚሁ ነጸብራቆች ናቸው።

የህወሃት መራሹ የኢሕአዴግ አገዛዝ እንዳለፈው ሁሉ ያረጀ ያፈጀ የ25 ዓመት ስልቱን፣ ሃይልና ጭካኔን በመጠቀም ሕዝባዊ እምቢተኝነቱንና አመጹን ለማፈን ከመቸውም ጊዜ በበለጠ ደረጃ የሞት የሽረት እንቅስቃሴ እያደረገ ይገኛል። የሕዝቡ ትግል ግን እየከረረና እየተጠናከረ እንጂ እየተዳከመ አልመጣም። ይህ አዲስ ክስተትና አዲስ የፖለቲካ አካሄድ መጣኝ የሆነ ምላሽን ይጠይቃል። ይህንንም አዲስ አካሄድና አቅጣጫን ለመንደፍ ሁሉም የሚሳተፍበት የፖለቲካ ሂደት መወጠን ከምን ጊዜውም በላይ በጣም አስፈላጊ ነው። ከዚያ ውጭ ግን የህዝብን ጥያቄ በተለመደ መልክ አፍኖ ለመቀጠል መሞከር የበለጠ ትርምስና አቅጣጫውን መገመት ወደሚያስቸግር ቀውስ የሚወስድ ይሆናል።

በሚያሳዝን ሁኔታ አምባገነኖቹ መሪዎች ከተጠናወታቸው የክህደትና የጨለምተኝነት ባህሪ የተነሳ ያለውን ዕውነታ ማገንዘብና መረዳት ተስኗቸው የሕዝብን ተቃውሞና የለውጥ ፍላጎት በአግባቡ ለማስተናደግ የፖለቲካ ፍላጎትም ሆነ ብቃት አይታይባቸውም። ይህንን ማየት ቢችሉ ኖሮ ያለፉበትን መንገድና የሕዝቡን ጥያቄ ባጤኑና በጎ ምላሽም በሰጡ ነበር።

የ2005 ብሔራዊ ምርጫን ተከትሎ የተከሰተው እልቂትና ጭፍጨፋ በሽህ የሚቆጠሩ ዜጎችን ለሞት፣ ለእስራትና ለስደት በመዳረግ የልዩነቱ ደረጃና ጥልቀት ጎልቶ የታየበት ሲሆን፣ መንግሥት ተብየው ቡድን ግን ለሥልጣኑ ሟችና ለሕዝብ ፍላጎት ግደቢስ መሆኑን በወሰደው እርምጃና በመረጠው መንገድ በገሃድ አረጋግጧል። የተከተለውንም አጥፊ አቅጣጫ በተጠናከረ መልኩ ቀጥሎበት በተወሰነም ደረጃ ቢሆን የተቃዋሚ ድርጅቶችን ለማሽመድመድ ችሏል። አሁንም የሚጓዝበት መንገድ ከዚያ ቢብስ እንጂ የተለዬ አይደለም። የነጻ ሚዲያ ዘርፎችን አፍኗል፣ ነጻ የሆኑ የሙያና የመብት ተከራካሪ ድርጅቶችን ዘግቷል፣ “የጸረ ሽብርተኝነት” የሚል ሕግ አውጥቶም ከሱ ጋር ያልተሰለፉትንና የሚቃወሙትን ሁሉ አጥቅቶበታል። ይህም አድራጎቱ ሲሰብክ የነበረውን የመድብለ ፓርቲ ልፈፋ ባዶነትና የኢዴሞክራሲያዊነት ባህሪውን አጋልጧል። በአብዮታዊ ዴሞክራሲ ስምና ልማታዊ መንግሥት በሚል ካባ ታጅሎ የሚያጭበረብር ብቸኛ የሥልጣን ባለቤት መሆኑን  በገሃድ አሳይቷል። በዚህም አካሄዱ የሰላማዊ የስልጣን ሽግግር በርን በመዝጋቱ አሁን ወደምንገኝበት ሕዝባዊ ሰላማዊና ትጥቃዊ እንቅስቃሴዎች በየቦታው የተስፋፋበት ወቅት ላይ ተደርሷል። አገዛዙ በበኩሉ ይህንን ሕዝባዊ ተቃውሞና የለውጥ ፍለጋ ትግል ለመቆጣጠር የሃይል እርምጃ በመውሰድ ላይ ይገኛል። ውጤቱ ግን ይበልጥ ስርዓቱን ከድጡ ወደማጡ ከመሄድ አላዳነውም።

የኢትዮጵያን ህዝብ ዛሬ ለለውጥ እንዲነሳ ያደረጉ አያሌ የፖለቲካ፣ የኤኮኖሚና የማህበራዊ ምክንያቶች ቢኖሩም የሕዝቡን ቁጣና እምቢተኝነት ከቀሰቀሱት ውስጥ ዋናዋናዎቹ የሚከተሉት ናቸው፥

  1. ላለፉት 25 ዓመቶች በተከታታይ በአገዛዙ የተከናወነው፣ ጭቆና፣ አፈናና ግድያ፣
  2. የሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች አለመከበራቸው፣
  3. ሕዝብ ለዘመናት ከኖረበት ቦታ መፈናቀሉ፣ ንብረትና መሬቱን መነጠቁ፣ ከሥራ ምድቡ ያላግባብ መባረሩ፣ እንደ ዜጋ ለደህንነቱ ዋስትና ማጣቱ፣ ሕገ አልባ ሥርዓት መስፈኑ፣
  4. ሕዝብ በብሄሩ በጎሳውና በቋንቋው መሠረት እየተነጠለ ለጥቃት መዳረጉ፣ አንዱ በሌላው ላይ እንዲነሳ የጥላቻና ቅራኔ ቅስቀሳ አገዛዙ በኩል ሆን ተብሎ የፖለቲካ ስልት ተደርጎ መወሰዱ፣
  5. በገጠርና በከተማ ለመኖር የሚያስችሉ የሥራ ዕድሎችና መስኮች እንዲሁም ከፍተኛ የስልጣን እርከኖች በቅድሚያ ለገዢው ፓርቲ አባላትና ለደጋፊዎቹ መሰጠቱ፣ ሌላውን በማግለል የዝቅተኝነትና የተስፋ መቁረጥ ስሜት እንዲዳብር መደረጉ፤
  6. ተቃዋሚውን በጎሳና በእምነቱ እየመነዘሩ ከዚያም አልፎ ተርፎ፣ ጠባብ፣ አክራሪ፣ ትምክህተኛ፣ አሸባሪ…እያሉ መመደብና ያለማቋረጥ ጥቃት መፈጸሙ፤
  7. በተለያዩ ቦታዎች ያለህዝብ ፈቃድ ለፖለቲካ ተጠቃሚነትና ተስፋፊነት የሚደረግ ያስተዳደር ክልሎች ሽግሽግ ለምሳሌ(በወልቃይት ጠገዴ፣ ጠለምት፣ ራያ፣ ኮንሶ ወዘተ.) ከፍተኛ ግጭትና ተቃውሞ ማስከተሉ፤

አሁን በመሬት ላይ የሚታየው ሃቅ ለሃያ አምስት ዓመት ሳያሰልስ የተካሄደው ተቃዋሚን ደምስሶ የማጥፋት ስልት የሚፈለገውን ውጤት እንዳላመጣ ሕዝቡ ተደጋግፎ በሙሉ ልብ የሚያካሂደው ትግል ማስረጃ ነው። ይህ ክልል፣ ዕድሜ፣ ጎሳና ሃይማኖት ያለየው ሕዝባዊ ትግል ያነጣጠረው የሥርዓቱ ዋልታ በሆነው ህወሓትና የሱ ኮረጆ በሆነው ኢሕአዴግ ላይ ነው። ሥርዓቱ የእኔ ናቸው ብሎ ይተማመንባቸው የነበረው ተቋማት ሳይቀሩ አሁን ተቃውሟቸውን በግልጽ እያሰሙ መጥተዋል። ቀን በቀን አቅሙ እየዛለ ሥልጣንም ከእጁ እያፈተለከ መውጣቱን የተገነዘበው የገዢ ቡድን የሞት የሽረት የመጨረሻውን ነብስ አድን እርምጃ ለመውሰድ ተገዷል፤ ይህም አስቸኳይ ጊዜያዊ አዋጅ ማወጅ ነው። ይህ እርምጃ በአገሪቱ ውስጥ ያለው አለመረጋጋት ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱን ያመለክታል። ሁሉም እንደሚያሰታውሰው ተመሳሳይ አዋጅም የዛሬ አስራ ሁለት ዓመት የ1997 ዓመት ምርጫ ተከትሎ አሳሳቢ ቀውስ ላይ በነበረበት ጊዜ  አውጆ  ነበር። በተቃዋሚው ጥንካሬ ማጣትና የእርስ በርስ ሽኩቻ ሕዝብ የሚሻው ለውጥ ሳይገኝ አገዛዙ እንደገና ሊያንሰራራ ችሏል። አሁንም ተመሳሳይ ሁኔታ እንዳይፈጠር ተቃዋሚው የሕዝቡን ትግል ተከትሎ፣ ጥያቄውንም አዳምጦ፣ በይበልጥም አገራችን ያለችበትን አደገኛ ወቅት ተገንዝቦ የአገርን አንድነት የሚያስከብርና ለሚፈለገው ለውጥ የሚያበቃ የትግል አቅጣጫ መንደፍና የትግሉ አካል መሆን አለበት። በውሃ ቀጠነ ተለያይቶ ወይም ለሥልጣን ጉጉት ተነጣጥሎ መጓዙ በአገራችንና በሕዝቡ ላይ መቅሰፍት እንዲወርድ  ወይም ያለው የተጠላ አገዛዝ እድሜ እንዲራዘም እንደመፍቀድ ይቆጠራል።

በታህሳስ 2008 ዓ.ም.(ኖቬምበር 2015) በኦሮሞ ሕዝብ ክልል የተቀሰቀሰው ተቃውሞ ወደ አማራው ክልል ተሻግሮ አሁን በመልክና በይዘት የተለዬ አደረጃጀት የያዘ፣ ካለፈው የተሻለ ሕዝባዊ ተቃውሞ ከመሆን ደረጃ ላይ ደርሷል። ይህ ትግል ይበልጥ የተጠናከረና ለሚፈለገውም ድል እንዲበቃ ለማድረግ ብሔራዊ አቀነጃጀትና ራዕይ ያለው አመራር ያስፈልገዋል።

የአሁኑን ሕዝባዊ እንቅስቃሴ ካለፈው የተለየ የሚያደርገው በከፊል በሚከተሉት ምክንያቶች ነው፤

  1. ያለፉት የተቃውሞ እንቅስቃሴዎች በዋና ዋና ከተማዎች በተለይም በአዲስ አበባ ያተኮረና የተካሄደ ነበር፤ የአሁኑ ግን የተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች፣ የገጠር፣ ከተሞችና ወረዳዎችን ያጠቃለለ ነው።
  2. ያለፉት ትግሎች በዋናነት ከላይ ወደታች በፖለቲካ ድርጅቶች ዙሪያ የተካሄደ ሲሆን ገዢው ቡድን መሪዎቹን ነጥሎ በመምታት ለማዳከም የቻለ ነበር፤ የአሁኑ ግን ብዙሃኑን ሕዝብ ከታች ወደ ላይ የቀሰቀሰና ያሳተፈ በመሆኑ ለማፈንና ለመቆጣጠር ቀላል አልሆነም፣
  3. ባለፈው ጊዜ ከታየው ሁሉ በተለየ ሁኔታ አሁኑ ህዝቡ ይዟቸው የተነሳው ጥያቄዎች በመሬቱ ላይ የመኖርና ያለመኖር፣ መሰረታዊ ማንነት፣ ታሪክና የእለት ተለት ህይወት ጋር እጅግ የተቆራኙ በመሆናቸው ለጥያቄዎቹ ምላሽ ለማግኘት የህይወት መስዋእትነትም ቢሆን እየከፈለ እስከመታገል ቆርጦ እንዲነሳ አድርጎታል።
  4. ባለፈው አገዛዙ እንደ አንድ ማእከል በመንቀሳቀስ ሳይከፋፈል በሙሉ ልብ ጠንካራ ሆኖ የታየበት ወቅት ነበር፣ አሁን ግን የአገዛዙ ስርዓት በውስጡ ክፍተት ያለበት፣ አንድነቱን ያጣበትና የተጋለጠበት ወቅት ነው።
  5. ባለፈው ጊዜ ስርዓቱ ህዝብን ሃይማኖትን፣ ብሄርንና ጎሳን፣ የመለያያ ስልት ያደረገበትና የተጠቀመበት ነበር፤ አሁን ግን ሕዝቡ እጅ ለእጅ ተያይዞ በመቆም አገዛዙን የጋራ ጠላት አድርጎ እየተንቀሳቀሰ የሚገኝበት፤ የኦርቶዶክስ አባቶች ጭምር ድምጻቸውን ለማሰማት ደፍረው የተነሱበት ጊዜ ነው።
  6. አሁን የፍርሃት ድባብ ተገፎ ሕዝቡ አደባባይ ወጥቶ ለመታገል የደፈረበት ወቅት ነው።
  7. በቅርቡ በኢሬቻ ሕዝባዊ በዓል ላይ የተፈጸመው የጭፍጨፋ ወንጀል ሥርዓቱን በውስጥና በውጭ ይበልጥ አጋልጦታል። ይደግፉት የነበሩትም አንዳንድ መንግሥታት ጥያቄ እያነሱበት ነው። የጀርመን፣ የካናዳ፣ የስዊድን፣ የአውሮፓ ህብረት ከሚጠቀሱት መካከል ናቸው።

ከዚህ  በላይ የተዘረዘሩት የሕዝቡን ትግል ጥንካሬና የሥርዓቱን እየተዳከመ መሄድ ያበስራሉ። ህዝብም በስርአቱ ላይ እምነቱ ሙሉ በሙሉ እንደተሟጠጠና በህወሓት/ኢህአዴግ ስር ለመገዛት በፍጹም እንደማይሻ እያሳየ ነው። ሆኖም ግን ሥርዓቱ አሁንም የክህደት፣ የማጭበርበር፣ የሰለቸና የተጋለጠ ፕሮፓጋንዳውን በማስተጋባት፣ ለለውጥም እንደተነሳ በማስመሰል የሕዝቡን የትግል ስሜት ለማኮላሸትና ትጥቅ ለማስፈታት እላይ ታች እያለ ይገኛል።

ህወሀት መራሹ አገዛዝ ከዚህ ወዲያ እንደተለመደው ለመቀጠል እንደማይችል ተረድቶ ለመሰረታዊ ለውጥ ፈቃደኛ ካልሆነ፤ ሁሉንም የሚያሳትፍ አገራዊ እርቅና ሰላም የሚያመጣውን በር ካልከፈተ አገራችን ወደባሰና እጅግ ወደተወሳሰበ ቀውስ መግባቷ የማይቀር ይሆናል፤ ለዚህ ደግሞ ተጠያቂዎቹ የሥርዓቱ ተጠሪዎችና አራማጆ ች ይሆናሉ።

ተቃዋሚዎች በተደጋጋሚ ስለ አገሪቱ አሳሳቢ ሁኔታና መፍትሔ ማፈላለግ ላቀረቡት የውይይት ጥሪ የተሰጠው መልስ በሽዎች የሚቆጠሩ የጸጥታና የመከላከያ ኃይል አባላትን በማሰማራት በሕዝቡ ላይ ዘመቻና ጥቃት ማካሄድ ነው። በዚህም ሳቢያ በሽህ የሚቆጠሩ ህይወታቸው ሲያልፍ አያሌዎችም አካለስንኩል ሆነዋል፣ በሺዎቹ የሚመደቡ ደግሞ በእስር ቤት እየተሰቃዩ ይገኛሉ።

የህወሀት መራሹ አገዛዝ የያዘውን የአጥፍቶ መጥፋት፣ የእልህና የበቀል ጎዳና ካልቀየረ፣ ለሰላምና እርቅ ድርድር በሩን ካልከፈተ አገራችን የቀውስ መስክ ሆና ለተለያዩ የታጠቁ የሽብር ሃይሎች አመቺ ሁኔታ እንደሚፈጠር ያሳሰባቸው የውጭ ታዛቢዎች ሳይቀሩ ደጋግመው አስጠንቅቀዋል። የሸንጎም ስጋት ከዚህ የተለዬ አይደለም። አገሪቱ ለተደቀነባት ዘርፈ ብዙ ችግሮች የመውጫ መንገድ ዛሬ ነገ ሳይባል መቀየስ አለበት፤ የመውጫ መንገዱም በሰጥቶ መቀበል መንፈስ፣ በረጋና በሰከነ አስተሳሰብ የሕዝቡን ጥያቄና ችግሩን ተገንዝቦ በጋራ መፍትሔ ለመፈለግ መወሰን ነው። በመተማመን፣ ሁሉን ያቀፈና ያሳተፈ ፍትሃዊና ሃቅ የተመላበት፣ ይቅርታን መሰረት ያደረገ፣ ሁሉም የሚረካበት ሂደት መጀመር አማራጭ የሌለው ምርጫ ነው። በተለመደው መንገድ መንጎዱ ቀውሱን ያባብሰዋል እንጂ ማስወገድ ቀርቶ አይቀንሰውም።

ኢትዮጵያና አጎራባች አገሮቿ የሚገኙበት አካባቢ ውጥረትና ስጋት የሰፈነበት በመሆኑ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የፖለቲካ ቀውስ በዚሁ ከቀጠለ ደግሞ በአገሪቱም በውጭም ያለውን አለመረጋጋት ይበልጥ ያባብሰዋል። ስለሆነም በኢትዮጵያ ውስጥ በአፋጣኝ የሕዝቡን ጥያቄ መመለስ ለአካባቢው ቀጠናና ባጠቃላይም ለአህጉሩ ሰላምና መረጋጋት ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል።

ስለሆነም አሁን ሀገራችንና ሕዝባችን ከሚገኙበት ሁኔታ ለመውጣት ሸንጎ የሚከተሉት ሦስት ነጥቦች መሰረታዊ ናቸው ብሎ ያምናል፤

  1. መረጋጋትን ለመፍጠር እውነተኛ፣ አስተማማኝ፣ ሁሉን አሳታፊ፣ በሁሉም ተቀባይነት ያለው የፖለቲካ ሂደት መጀመር፤
  2. ሁሉንም ባሳተፈ ውይይት የቀውሱን መንስዔ አስወግዶ ለሕዝቡ ጥያቄ መልስ ለመስጠት የሚችል የሽግግር ሂደት ማካሄድ፤
  3. ጠንካራ መሰረት ያለው ሂደት ተግባራዊ በማድረግ፤ ዘላቂ የሆነ ለውጥና ዴሞክራሲያዊ ስርዓት መዘርጋትና ተመሳሳይ ቀውስ ወደፊት እንዳይከሰት መስራት፤

ከላይ የተጠቀሱትን እውን ለማድረግም የሚከተሉት አብረው የሚታዩ ተጓዳኝ ተግባሮች ናቸው፤

ከአመጽ ይልቅ አመጽ አልባ የሆነ ሽግግር ይመረጣል

የሚቻል ቢሆን የሰው ሕይወት ሳይጠፋ፣ የአገር ንብረትና ሃብት ሳይወድም በሰላማዊ መንገድ ለውጥ ቢመጣ የሚጠላ የለም። ይህም በመሆኑ ሰላማዊውን ሽግግር የሚመርጥ ሁሉ ለተግባራዊነቱ ከፍተኛ ጥረት ማድረግ ይጠበቅበታል፤ ለዚህም ነው ሸንጎ ሽግግሩ ሰላማዊ መሆኑ ለወደፊቱ የአገሪቱ ዕጣ ፈንታ ያለውን ወሳኝነት ግንዛቤ ውስጥ ያስገባ የትግል አካሄድን የሚከተለው።

አሁን ግን በአገዛዙ ጀብደኝነትና ጭካኔ የተሞላበት አካሄድ ሁኔታው ይበልጥ እየተካረረና ህዝቡም ሌሎች አማራጮችን እንዲወስድ አስገደዶታል። በኛ በኩል ሰላማዊ  ሸግግር የተሻለና አስተማማኝ ውጤትን እንደሚያስከትል ስለምናምን አሁንም ቢሆን የበለጠ አደጋና ውድቀት ሳይመጣ የእስከአሁኑ በቅቶ አገዛዙ ወደ ህሊናው ተመልሶ ወደሚሻለው አቅጣጫ ፊቱን እንዲያዞር የመጨረሻ ሰዓት የአደጋ ጥሪያችን እናሰማለን። የወቅቱ ሁኔታ ከቀውስ የጸዳ፣ ሁሉን ያቀፈና ያሳተፈ፣ ዴሞክራሲያዊ የሆነ፣ የፖለቲካ አቅጣጫን ይሻል። ሕዝቡ ያለውን ስርዓት አንቅሮ ተፍቶታል። ለተመሳሳይ አምባገነን አገዛዝም እንደማይመች ይፋ አድርጓል።

የሚያስገርመው ጉዳይ ግን አሁንም የቀውሱ ባለቤት የሆነውና በሥልጣን ላይ ያለው ቡድን እራሱን ብቸኛ የሰላም፣ የመረጋጋት፣ የእድገትና የልማት፣ የእኩልነትና የዴሞክራሲ ፈጣሪና አውታር፣ ሕዝብም ከዳር እስከዳር የሚደግፈውና የሚከተለው አድርጎ ማቅረቡ ነው። እዚህ ላይ “ለማያውቅሽ ታጠኝ” ከማለት በስተቀር እሰጥ አገባ ጊዜ ማባከን ይሆናል። በአጭሩ አገዛዙ የሚከተለው መንገድ አገሪቱን ከተዘፈቀችበት የቀውስ ማእበል የሚያወጣ ሳይሆን በቀውስ ላይ ቀውስ እየወለደ የኤኮኖሚና የማህበረሰብ ውድመትን የሚያስከትል ነው። ከዚያ ማዕበል ለመውጣት ያለው መንገድ አንድ ብቻ ነው። ሁሉን ያሳተፈ አዲስ የሽግግር ሂደት መጀመር!

ግልጽነት ያለው ሁሉን አቀፍ ሽግግር አስፈላጊና ወቅቱ የሚጠይቀው ነው

አሁን ያለውን ሁኔታ በኢትዮጵያ ውስጥ የተረጋጋ ስርዓትን ለማምጣት በህዝብ ተቀባይነትና ከበሬታ ሊኖረው ወደሚችል መንግስትና ስርዓት መሸጋገርን የግድ ነው። ህወሀት መራሹ አገዛዝ ሙሉ በሙሉ የህዝብን አመኔታና ክብር አጥቷል።

አሁን እየተካሄደ ያለው በአይነቱ በጣም የተለያየ አካሄድ ከቀጠለ ለሚፈለገው የተደላደለ አይነት ስርዓት የታደልን አንሆንም። ለዚያም የሚያበቃ ተስፋ የሚጣልበት ነጠላም ሆነ የቡድን ድርጅት አለመኖሩን አምኖ መቀበል ያስፈልጋል። የሕዝቡን ትግል የሚመራና የሚያስተባብር የጋራ የሆነ ድርጅት አለመኖሩም ሌላው ክፍተት ነው። እዚያና እዚህ ትግሉን እየመራነው ነው የሚሉ ባይጠፉም በገሃድ ግን በመሬት ላይ የሚታዬው እውነታ ከዚያ የተለዬ ነው። ስለሆነም አገር አቀፉን ሕዝባዊ ትግል ወክሎ በሁሉም ቦታ የሚመራ ብቸኛ ድርጅት የለም። አንዱ ድርጅት ባንድ አካባቢ የተሻለ ጥንካሬ ቢኖረው እንኳን በሌላ ቦታ ደግሞ ተመሳሳይ አቅምም ድገፍም ላይኖረው ይችላል።

ስለዚህም የሀገራችንን ችግሮች ለመፍታት ሁሉም ባለድርሻ የሚሳተፍበት፣ የውድቀቱም የስኬቱም ሂደትና ውጤት ባለቤት የሚሆንበት ሁኔታን  ለመፍጠር ጉባኤ መጥራትና መወያየት አስፈላጊ ነው። ይህ ካልሆነ ሊከሰት የሚችለውን አደጋ ለመከላከልም ሆነ ለማስወገድ ከባድ ይሆናል፣ አገራችንም ወደማያባራ ቀውስና ምስቅልቅል ሁኔታ ልትገባ ትችላለች። ያንን መፍቀድም አይኖርብንም። የሽግግር ወቅት ከመፍጠር የተሻለ አማራጭ የለም። ለዚያ ደግሞ ወቅቱ ነገ ሳይሆን ዛሬ ነው። ሁሉን አቀፍ፣ በግልጽነት፣ በመተማመንና፤ በመግባባት የሚፈጠረው የሽግግር ሂደት (የሽግግር መንግሥት) የሕዝብ ድጋፍና እምነት ብሎም ከበሬታ ያገኛል።

የሽግግር መንግስትና የሽግግር ምክር ቤት

በኛ አመለካከት ይህ ሁሉን አቀፍ ጉባኤ የሚወልደው የሽግግር መንግስት ሁሉንም የፖለቲካ ድርጅቶች፣ የለውጡ አንቀሳቃሽ የሆኑ የጎበዝ አለቆችን፤ የሲቪክ ማህበረሰብ ተወካዮችን፣ የሃይማኖት፣ የጾታ፣ የሙያ፣ የጎሳ፣ የምሁራን፣ ታዋቂ ግለሰቦችን፣ ወጣቶችን የሚያካትት (ሁሉን ያቀፍ hybrid model) መሆን ይኖርበታል እንላለን። ከሽግግሩ ወቅት ጀምሮ የጸጥታና የመከላከያ ክፍሎች እንዲሁም የፍትህ ተቋማት ከፖለቲካ ተሳትፎ ርቀው ለተሰለፉበት ሙያና ተግባር ብቻ ያደሩ ይሆናሉ። የሕዝቡንና የአገሪቱን ሰላምና ደህንነት አስከባሪዎች እንጂ የአንድ ድርጅት ታዛዦችና አገልጋዮች አይሆኑም። ተጠሪነታቸው ሕዝብ መርጦ በሥልጣን ላይ ላስቀመጠው መንግሥትና ለሕዝባዊ ምክር ቤቱ ይሆናል።

የሀገሪቱን እለት ተለት ተግባር ከሚመራው የሽግግር መንግስት የበላይ ሆኖ የሚያገለግል “የሽግግር ወቅት የብሄራዊ አንድነት የጋራ ምክር ቤት” (Transitional Assembly of National Unity) መመስረት አለበት እንላለን።

ይህ የሽግግር ምክር ቤት የፖለቲካ ድርጅቶች፣ ሲቪክ ድርጅቶች እና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን ያካተተ መሆኑ እጅግ አስፈላጊ ነው።

የሽግግር ሂደት(የሽግግር መንግሥት) በሚከተሉት ቁልፍ ተግባርና ግዴታ ላይ ያተኮረ ይሆናል።

  1. አገሪቱን ቋሚ መንግሥት ተመስርቶ እስከሚረከብበት ጊዜ ድረስ ይመራል፤ ያገልግሎት ዕድሜው ግፋ ቢል ከሦስት ዓመት አይበልጥም።

አፋኝና ጨቋኝ የሆነውን ሕገ መንግስት አስወግዶ በምትኩ በሽግግሩ ተሳታፊዎች የጸደቀ ጊዜያዊ የሽግግር ቻርተርን ተግባራዊ ያደርጋል፤ በሽግግሩ ወቅትም ሕገ መንግስት አርቃቂ ኮሚሽን መስርቶ ህዝብን ባሳተፈ ሁኔታ አዲስ ሕገ መንግሥት ያረቃል ለሕዝበ ውሳኔ አቅርቦም ያስጸድቃል።

  1. ነጻና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ እንዲካሄድ ያመቻቻል፣ አሁን ያለውን ቋሚ የምርጫ ቦርድ ሽሮ ሥራው በምርጫ ወቅት ብቻ በሚያገለግል በሕዝብ ምክር ቤት ስር በሚቋቋም አካል እንዲካሄድ ያደርጋል።
  2. የእርቅና መግባባቱ ሂደት እንዲጀመርና እንዲቀጥል ጥረት ያደርጋል። ወንጀል የፈጸሙ ሁሉ በህግ የሚዳኙበትን ሁኔታ ያመቻቻል።

የሰብአዊና የዴሞክራሲያዊ መብቶችን እውን ስለማድረግ፣

ለሽግግሩ ዋነኛ መሰረት የሚሆነው የሰብአዊና የዴሞክራሲያዊ መብቶች መከበር ነው። የመደራጀት፣ ሃሳብን በነጻነት መግለጽ፣ መደገፍና መቃወም፣ መምረጥና መመረጥ፣ ዜጋ በፈለገበት የአገሪቱ ግዛት የመኖር፣ የመስራትና ንብረትና ሃብት የማፍራት…ወዘተ ያካትታል። እነዚህን ለማረጋገጥና አስተማማኝ ሂደት ለመጀመር፤ ለሕዝቡና ለአገሪቱ መተማመንን የሚገነቡ ተግባራት በቅድሚያ መፈጸማቸው ወሳኝ ነው። ከነዚህም ውስጥ የፖለቲካ እስረኞችን መፍታት፣ የጊዜያዊ አስቸኳይ አዋጁን ማንሳት፣ የመገናኛ ተቋማትን ነጻነት ማክበርና የፖለቲካና የሲቪክ ድርጅቶችን ነጻነት በተግባር ማረጋገጥ ዋናዎቹ ናቸው።

እኩልነትን፣ እራስን የማተዳደርና የአገሪቱን አንድነት ለማረጋገጥ የሚረዳ  ሁኔታን ስለመፍጠር

በቋንቋና ክልል ረድፍ የማንነት ጥያቄ መነሳቱ የአገሪቱን አንድነትና የሕዝቡን ተሳስሮ፣ ተዋልዶና ተስማምቶ መኖር የሚፈታተን ሆኗል። ሁሉም ባለድርሻዎች በጋራ በመወያየት ለሀገራችን ምን አይነት የአስተዳደር መዋቅር እንደሚበጅ መመካከሩና መወሰኑ የተከሰተውንና ወደፊትም ከቁጥጥር ውጭ ሊሆን የሚችለውን የእርስ በርስ ግጭት ስጋት ሊያመክን ይችላል። ስለሆነም በሽግግር ሂደቱ ውስጥ የሚሳተፉት በእኩልነት ላይ የተመሰረተ፣ በሥልጣን ክፍፍል የመንግሥትና የአካባቢ አስተዳደር ተቀራርቦና የአገሪቱ አንድነት ተጠብቆ የሚሰራበት፣ የአካባቢ ነዋሪ ሕዝብ፣ መጤና ተወላጅ ሳይባል፣ በሁሉም አካባቢ መብቱ በእኩልነት የሚጠበቅበትና በተግባር የሚተረጎምበት አካሄድ አንዱ መፍትሔ ነው ብለን እናምናለን። የልዩነቱ ሳይሆን የአንድነቱና የጋራ እሴቱ እየጎላ የሚታይበት፣ ሁኔታ መፍጠር ሁሉንም ተጠቃሚ ያደርጋል። የእኔና የእኔ ብቻ የሚለው አስተሳሰብ የእኛና የጋራችን በሚለው አስተሳሰብ እንዲለወጥ ማድረጉ ለበለጠ እድገትና ጥንካሬ ይረዳል። ከክልል ፖለቲካ ወጥቶ አገር አቀፍ ፖለቲካ መከተሉ ያስከብራል፣ እድገትና ሰላምን ያስገኛል።

በሽንጎው በኩል በዚህ የሽግግር ሂደት ውስጥ ተሳታፊ የሚሆኑ ሁሉ ለእኩልነት፣ ለአካባቢ አስተዳደሮች አስፈላጊውን ስልጣን በማጋራትና የሀገሪቱን አንድነት በማስጠበቅ ላይ ለመሰለፍ ቃል ሊገቡ ይገባል እንላለን።

ለእርቅና ለመግባባት የሚረዱ ተግባሮች

የማህበረሰብና የፖለቲካ እርቅ ለማስፈን የአገራችን ህልውና ቀዳሚና ወሳኝ ነው። የነበሩና አሁን የተፈጠሩ ቁርሾዎችን እንደ ሁኔታው በሰላምና በውይይት ለመፍታት አለመቻል ችግሮቻችንን እጅግ የተወሳሰቡ እንዲሆኑ አድርገዋቸዋል።

እነዚህን ቁርሾዎች ባግባቡ መመርመርና መፍታት ተፈላጊውን ብሄራዊ እርቅ ለማምጣት እጅግ አስፈላጊ እርምጃ ነው። ይህን ማድረግ የሚቻለው ደግሞ፣ በመከባበር፣ በቅን መንፈስ፣ በእውነተኛነትና፣ በግልጽ አሰራር ላይ ተመስርቶ መሆን አለበት። ይህም እውን የሚሆነው በብሄራዊ እርቅ ሂደት ስንጓዝ ስለሆነ፣ የሽግግሩ መንግስት ይህን ሂደት በጥንቃቄ ግብ ይመታ ዘንድ መሰረቱን መጣል ስራውንም መጀመር ይጠበቅበታል።

ካለፉት የሽግግር ሂደቶች የሚቀሰመው ትምህርትና ተመክሮ

ኢትዮጵያ ካለፉት አርባ ሦስት ዓመታት ወዲህ በሁለት የተለያዩ የፖለቲካ፣ የኤኮኖሚ፣ የማህበራዊ ሽግግር ሙከራ ሂደቶች ውስጥ አልፋለች። ከንጉሡ ቀጥሎ የሰፈነው ወታደራዊ አምባገነንና እሱን ጥሎ የተተካው የአሁኑ ብሄርና ጎሳ ተኮር ስርዓት መሆናቸው ነው። ሁለቱም የሚመሳሰሉበት አሏቸው፤ ሌላውን ያሳተፉ አይደሉም፣ የነጠላና የጠበበ ፍላጎት ላይ የተመሰረተ ውሳኔ የሚተገበርባቸው ነበሩ፤ ሁለቱም የዲሞክራሲ ጸሮች ናቸው፣ በሁለቱም ስርዓቶች ሕዝብና መንግሥት ሆድና ጀርባ የሆነባቸው፣ አለመተማመን፣ ስጋት፣ ግፍ፣ ሽብርና ጭንቀት የሰፈነባቸው ናቸው። በእነዚህ ስርዓቶች ሰፍኖ የኖረው አጥፊና ጠባብ የፖለቲካ ባህል ተወግዶ በቦታው የሁሉም በሁሉም ለሁሉም በሆነ የተሻለ ስርዓት እንዲተካ ካለፈው ድክመትና ውድቀት መማር ተገቢ ነው እንላለን።

በ1983 ዓ.ም. የተከሰተው የለውጥና ሽግግር ድክመት

  1. ግልጽነት የሌለው፣ የተዘጋ አግላይ ቡድን የጠነሰሰውና የተሳተፈበት ሌላው ተገፍቶ ከዳር የቀረበት ሂደት ነበር።
  2. የሕዝቡን ይሁንታ ሳያገኝ ቋሚ መንግሥት ሊሰራው የሚገባውን ነጥቆ በአገሪቱ ዘላቂና ከፍተኛ ጉዳዮችና ጥቅሞች ላይ ጎጂ ውሳኔ ያስተላለፈ ጠባብ የሽግግር ሂደት ነበር።
  3. ያንድ ድርጅትን ፕሮግራም ብቻ በሽግግር ቻርተርነት ስም አቅርቦ በሀገሪቱ ላይ መጫኑ።

አሁንም ቢሆን ተመሳሳይ ስህተት እንዳይደገም ሁሉም መጣር አለበት።

ኤርትራን ከኢትዮጵያ የመነጠል ውሳኔና ያስከተለው ጉዳት

የኤርትራ ከኢትዮጵያ መለየት ጉዳይና በአስመራ የተመሰረተው የሻቢያ መራሹ አገዛዝ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ምን ሚና እንዳለው ማየቱ አወዛጋቢ ጉዳይ ነው። አሁን ባለው የሀገራችን የፖለቲካ መልክዓ ምድርም ቢሆን የኤርትራ ጉዳይ ሲነሳ ለየት ያለ ተጨማሪ ምስቅልቅልን ይጋብዛል።

አሁንም ቢሆን የኤርትራን በተመለከተ ያላለቀ ጉዳይ መኖሩን በመገንዘብ ይህን ጉዳይ አሁን ኢትዮጵያ ካለችበት ሁኔታ ጋር ማደባለቅ ነገሮችን እጅግ ማወሳሰብና መፍትሄውንም እጅግ ማበላሸት  እነደሆነ መገንዘብ ተገቢ ነው።

ስለሆነም በሁለቱም በኩል ያለውን ያልተዘጋ አጀንዳ በአዳሪ ማስቀመጥና የኢትዮጵያን ውስጣዊ ችግር በቅድሚያ መፍታት አስፈላጊነቱን ተረድቶ መጓዝ ተገቢ ነው እንላለን።

የህወሃት/ኢህአዴግ መንግስት ከስልጣን መውረድ እንዳለበት በአሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ ከተማ የተካሄደው የምሁራን ጉባዔ ጠየቀ

$
0
0

a12

ኢሳት (ጥቅምት 14 ፥ 2009)

በኢትዮጵያ በስልጣን ላይ የሚገኘው ገዢው የኢህአዴግ መንግስት የህዝቡን ጥያቄ በመቀበል ከስልጣን መውረድ እንዳለበትና በሃገሪቱ የሽግግር ስርዓትና የህገ-መንግስት ረቂቅ እንደሚያስፈልግ በአሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ ከተማ የተካሄደው የምሁራን ጉባዔ አስገነዘበ።

a11የቪዥን ኢትዮጵያ ፕሬዚደንት ፕሮፌሰር ጌታቸው በጋሻው የጉባዔውን መጠናቀቅ አስመልክተው ለኢሳት እንደገለጹት “ህወሃት የሚመራው መንግስት ህዝብን እየገደለና ሰብዓዊ መብት እየረገጠ በመሆኑ ስልጣኑን ሊለቅ ይገባል።
በቪዥን ኢትዮጵያና በኢሳት ትብብር በሳምንቱ መገባደጃ ቅዳሜና እሁድ የተዘጋጀው ኮንፈረንስ ሲጠናቀቅ እንደተገለጸው አሁን ባለው የኢትዮጵያ ሁኔታ የሽግግርና አዲስ ህገመንግስት ያስፈልጋል።
በኮንፈረንሱ ማጠቃለያ ላይ በኢትዮጵያ አዲስ ስርዓት ለማበጀት የሽግግር ካውንስል ማቋቋም እንደሚያስፈልግ መግባባት ላይ መደረሱ ተገልጿል።

የቪዥን ኢትዮጵያ ዋና ጸሃፊ ዶ/ር አሸናፊ ጎሳዬ ለኢሳት እንደገለጹት፣ የሰላም ሚና ያለውና ሃገሪቱን ወደ ሽግግር ሂደት የሚወስደው ካውንስል የተለያዩ አካላት እንዲወስኑበት ማድረግ ያስፈልጋል።
አሁን ያለው ገዢ ፓርት ህወሃት/ኢህአዴግ ግድያውን እንዲያቆምና ለሰላም በሩን በመክፈት ለድርድር ፈቃደኛ እንዲሆን ጥሪ መተላለፍን ገልጸዋል።

ዶ/ር አሸናፊ እንዳሉት በኢትዮጵያ በተካሄደው ግድያና የሰብዓዊ መብት ረገጣ እጃቸው ያለበት ባለስልጣናት ማንኛውም የገዢው ፓርቲ አባላት በህግ መጠየቅ ይኖርባቸዋል።

በቪዥን ኢትዮጵያ የተካሄደውን ስብሰባ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን በፌስቡክና በኢሳት ድረገጽ ቀጥታ ስርጭት መከታተላቸው ታውቋል። የአጠቃላይ የስብሰባውን መግለጫና የተደረሰበትን ድምዳሜ ቪዥን ኢትዮጵያ በቅርቡ ይፋ እንደሚያደርግ ተገልጿል።

ከቀልድ ቁምነገር እንማር እንጅ ቁምነገር የሌለው ቀልድ አንቀልድ (ከይገርማል)

$
0
0

ethnic-federalismበሕጻንነቴ ትዝ ከሚሉኝ ነገሮች ዋናው እንደእናት ተንከባክባ አዝላ: በዳውጃ ላይ አስቀምጣ እየጎተተች አጫውታ:  ሽንትና ካካየን ሳትጸየፍ አጸዳድታ: አስቸጋሪ ባህሪየን ችላ በተረት አዋዝታ: ጸጉሬን እያሻሸች የምታስተኛኝ የአክስቴ ሁኔታ ነው:: ከድሀ ቤተሰብ የተወለድኩ ብሆንም አስተዳደጌ ግን የቀበጥ ነበር: በትንሽ በትልቁ የማኰርፍ: ውሀ ቀጠነ ብየ የምናደድ: አፌን ከፍቼ ማልቀስ ከጀመርኩ ደግሞ መመለሻ ያልነበረኝ:: እናትና አባቴ እኔን ለአክስቴ እርግፍ አድርገው ትተው ካለሀሳብ በዋናው ቤት አለማቸውን ይቀጩ ስለነበር ገመና ከታቼ: ሞግዚቴ: ጓደኛየ: እናቴ: አክስቴ ነበረች:: ካልሁት ለምን ጎድሎ ብየ ወይም በሆነ ሰንካላ ምክንያት ማልቀስ ከጀመርኩ እንደሀምሌ ዝናብ እኝ-ኝ-ኝ እንዳልሁ መዋሌ ነው:: አባትና እናቴ የእኔን ልቅሶ በሰሙ ቁጥር “ይህን ልጅ ካለልክ አቅብጣው!” እያሉ አክስቴን ከመወንጀል: እኔን ባገኙት ነገር ከመጨርገድ: በቁንጥጫ ከመመዝለግ ውጪ እንደወላጅ አንስተው ታቅፈው እምባየን እየጠረጉ ያባበሉበት ጊዜ ትዝ አይለኝም:: ታዲያ ይህን መያዣ መጨበጫ የሌለውን ባህሪየን እና የወላጆቼን ምላሽ የምታውቀው አክስቴ: ለማልቀስ አፌ ከመከፈቱ በፊት የምፈልገውን አሟልታ: ኮራኩራ አሳስቃ: ከምታውቃቸው ተረቶች አንዱን: ፈጥራም ቢሆን እየነገረች ማረሳሳት የዕለት ከዕለት ተግባሯ ነበር:: አክስቴ ከነገረችኝ ተረቶችና ቀልዶች ውስጥ አንዱ እንዲህ የሚል ነበር:: “ሰማይና መሬት የወለልና የጣሪያ ያህል መቀራረብ ነበራቸው:: በቅሎ ናት በርግጫ ብላ ወዲያ አሽቀንጥራ የጣለችው:: ከዚያ ጊዜ ጀምሮ አምላክ ከሰው ርቆ መኖር ጀመረ:: በቅሎም በሰራችው ሥራ ተረገመች”

ተረቱን ስትነግረኝ በቅሎዋ በኋላ እግሮቿ ሰማዩን እንዴት አድርጋ እንደመታችው በእንቅስቃሴ ጭምር እያሳየችኝ ስለሆነ እግሯን ባፈራገጠች ቁጥር ሽንቴ ፊር ፊር እስኪል ድረስ በሳቅ እንከተከት ነበር:: እማማ:- ሳላውቅ በስህተት አውቄም በድፍረት ላስቀየምሁሽ ሁሉ ይቅርታ እንደምታደርጊልኝ ቅንጣት ታክል ጥርጣሬ የለኝም:: ብድሬን ለመክፈል አቅሜም ጥረቴም እዚህ ግባ የሚባል ስላልነበረ የዕውነት የፍቅር አምላክ በበኩሉ ይቅር ይበለኝ: ለእኔ የዋልሽውን ውለታ እርሱ ይክፈልልኝ:: ነፍስሽን በገነት ያኑርልኝ:: አሜን!

የአክስቴ ጨዋታ ሲተነተን እንዲህ የሚል ይወጣዋል:: ‘ዱሮ ዱሮ ሰማይ ለመሬት በጣም ቅርብ ነበር:: ታዲያ ያኔ በሰማይ የሚኖረው አባታችን የልብ ትርታችንን ሳይቀር ማዳመጥ ይችል ስለነበር የሰው ልጆች ብሶት ይሰማ: ችግራቸው በቀላሉ ይቀረፍ ነበር:: ይህ በእንዲህ እንዳለ ከእለታት በአንዲት ቀን በቅሎ ሆዬ ጥጋብ ንፍት አድርጓት የምትሆነውን ያሳጣታል:: ወዲህና ወዲያ የምትፈነጭበት ቦታውም ይጠባታል:: በዚህም ምክንያት አገጯን ወደመሬት ተክላ: የኋላ እግሮቿን እንደጉድ አንስታ: ሽቅብ ተስፈንጥራ: ባለ በሌለ ኃይሏ ሰማዩን ስትደልቀው ሰማዩ እያጉረመረመ የትየለሌ ሄዶ ተሰቀለ:: ከዚያ ወዲህ “ከዐይን የራቀ ከልብ ይርቃል” እንዲሉ ፈጣሪ በአካል ብቻ ሳይሆ በመንፈስም ራቀን:: የገጻችንን መዳመን የስሜታችንን መጎፍነን አስተውሎ: ጸሎታችንን ሰምቶ: የምንጠይቀውን ያሟላልን: የሚበጀውን ያደርግልን የነበረው አባት ዛሬ ላይ ብንጮህ ብናለቅስ አልሰማ ብሎናል:: የሰውን ልጅ ከፈጣሪ ያራራቀችው በቅሎ “ወልደሽ አትሳሚ!” ተብላ ብትረገም ይኸው የመወለድ እንጅ የመውለድ ጸጋን ተገፋ “ብዙ ተባዙ!” የሚለው የፈጣሪ ቃል ዘሏታል::’

በአንድ ወቅት ከአንድ አርብቶአደር ጋር ስናወራ ከሆነ ሰው ጋር በመጣላቱ የተጣላውን ሰውየ ልጅ ገድሎ ታስሮ እንደቆየ ነገረኝ:: ‘እንዴ! ልጁ ምን አድርጎህ ነው የገደልኸው? ሲሆን ሲሆን የበደለህን ሰው በህግ መጠየቅ በተገባ ነበር: ካልሆነ ደግሞ መቅጣት የሚኖርብህ ምንም ያላጠፋውን ልጁን ሳይሆን አጥፍቷል ያልኸውን አባቱን መሆን ነበረበት’ ስለው አርብቶአደሩ ወንድሜ እየሳቀ “አባቱ ውሻ ነበር:: የውሻ ልጅ ውሻ ነው” በማለት የወሰደው ርምጃ ትክክለኛ መሆኑን ሊያሳምነኝ ሞከረ:: እስካሁን ባለው እውነታ የውሻ ልጅ ውሻ መሆኑን የሚክድ አይኖርም:: የፈረስ ልጅ ፈረስ ስለመሆኑ ምን ያህል እርግጠኛ መሆን ይቻላል? ያም ሆነ ይህ በቅሎ የሰራችው ሥራ የሚያቀባብር አይደለም:: ግን ማንን ልኰንን? በቅሎዋን ወይስ አህያና ፈረስን አዳቅለው በቅሎን ያመጡብን ናቸው የሚባሉትን አገወች?

ጀብሀን: ሻዕቢያን: ኦነግን: ወያኔን: ኦብነግን: ሶማሌ አቦን:  – – -ማን ፈጠራቸው? ማንን ከማን አዳቅሎ? እኒህ ዲቃላወች ምን ጉዳት አደረሱ?

ግብጽ ጀብሀን ፈጠረ: ሻእቢያን ጀብሀን ወለደ: ሻእቢያ በበኩሉ የፈጠራቸው- – – እያልን እንቀጥል ወይስ የልብ-ወለድ ታሪክና የስልጣን ጥም ተዋህደው እኒህን ጉዶች ፈጠሩ እንበል? የሆነው ሆኖ አንዳንዶች “በለጋነታችሁ ይቅጫችሁ: ለቁምነገር አትብቁ!” ተብለው ተረግመው መንቦራቸት ሳይጀምሩ ሳያምርባቸው: ከተቀመጡበት መሬት ላይ ሳይነሱ አርፈው ተቀብረዋል:: አንዳንዶቹ ደግሞ “ህልማችሁ እንደጉም ይትነን: እንደባዘናችሁ ኑሩ!” ተብለው ይኸው የማይደርስ ህልም: የማይጨበጥ ተስፋ ይዘው ቀጥለዋል:: እምባና ደም እያፈሰሱ: ጤና አጥተው: ጤና ነስተው: እየኖሩ ያሉም አሉ:: በርግጠኝነት መናገር የሚቻለው የሞቱት ቡድኖች የማይሞት መጥፎ አሻራወቻቸውን ጥለው እንዳለፉ ሁሉ በህይወት አሉ የሚባሉትም እንዲሁ አሳፋሪ ታሪካቸውን ጥለው እንደሚያልፉ ነው:: ይህ የሚሆነው ከታወቀበት ብቻ ነው::

የጎሣ ድርጅቶችን አባብሎ ኢትዮጵያዊ መስመር እንዲከተሉ ለማድረግ ብዙ ተሞክሯል: ብዙ ተደክሟል:: ግን ያው “ውሀ ቢወቅጡት—” ሆኖ የተለወጠ ነገር የለም:: ሰማዩን አይተው የዝናቡን አቅጣጫ መረዳት የሚችሉ እነሱ በዝናብ ከመበስበስ ይድናሉ:: “እወቅ ያለው በአርባ ቀኑ ያውቃል: አትወቅ ያለው ግን በአርባ አመቱም አያውቅ” የሚለው አባባል ዝም ብሎ የተባለ አይደለም:: እናሳ! ሕዝቡን አስተምሩና አደራጁ እንጅ እኒህን ቡድኖች አትለማመጡ የሚሉትን ሁሉ እንደ ጸረ-አንድነት አድርጎ መመልከቱ ዛሬም አይበቃም! ካለፈው ስህተት መማር የማይችል ሰው ለወደፊቱ በጐ ነገር መስራት የሚሳነው ብቻ ሳይሆን የዐዕምሮ ጤንነቱም የሚያጠራጥር ነው:: አሁን ያለው የኃይል አሰላለፍ በዋናነት በሁለት የሚመደብ ነው: ጎሣዊና ሕብረ-ብሔራዊ:: የአንድነት ኃይል (ሕብረ-ብሔራዊ) ነን የምትሉ ሁሉ በአንድነት እንዳትቆሙ የሚያደርጋችሁ መሰረታዊ ልዩነት ይኖራል ተብሎ አይታሰብም:: የአረብ ገንዘብ የሚፈስላቸውን ጎጠኛ ድርጅቶች ለማባበል ከሄዳችሁበት ርቀት ግማሽ ያህሉን እንኳ ተጉዛችሁ ችግሩንም ሆነ ደስታውን ተካፍሎ የሚኖረውን ሕዝብ ለማቀፍ ብትሰሩ እዳው ገብስ ይሆናል::

ሰሞኑን የኦሮሞ ድርጅቶች ለንደን ላይ ተሰብስበው ከተነጋገሩት ውስጥ ተቀንጭቦ የሰማነው ኦሮሚያ የምትመሰረተው በኢትዮጵያ ከርሰ-መቃብር ላይ እንደሆነ ነው:: የኦሮሞ ድርጅቶች የሚሰሩት ኢትዮጵያን ለማፈራረስ እንጅ ለመደገፍ እንዳልሆነ ነው:: ከዚህ በላይ ምን ብለው ይንገሩን? እህሳ! እኒህን የዘረኝነት ቫይረስ ተሸካሚ ቡድኖችን መለማመጥ እንቀጥላለን ወይስ በኢትዮጵያዊነታቸው የማይደራደሩትን ወገኖቻችንን ይዘን ወደሕዝብ እንዘልቃለን?

አክስቴ ከነገረችኝ ተረቶች መሀል ትዝ የሚለኝ ሌላው የአንድ ባልና ሚስት ልብ-ወለድ ታሪክ ነው:: በአንድ ወቅት በአንድ አካባቢ የሚኖሩ ድሀ ባልና ሚስት ነበሩ:: ባልና ሚስቱ ጠንክረው በመስራት ኑሯቸውን ለማሻሻል ከመጣር ይልቅ እጃቸውን እና እግራቸውን አጣጥፈው ቁጭ ብለው በማይጨበጥ ምኞት የጎደለውን ሊሞሉ: የዘመመውን አቃንተው ህይወታቸውን ሊያደላድሉ የሚደክሙ የህልም እንጀራ ጋጋሪወች ነበሩ:: አንድ ቀን ባልና ሚስቱ እንደተለመደው ቁጭ ብለው ሲጫወቱ ሚስት “ሞሰብ ሰፍቼ: ሞሰቡን ለንጉሥ አበርክቼ: ንጉሡ በሚሰጡኝ ሽልማት ላም ገዝቼ: ላሟ ስትወልድልኝ ጥጃዋን ከመደብ ላይ አስራታለሁ” ብላ ምኞቷን ትናገራለች:: ይኸኔ ባል በንዴት ቱግ ይልና “ጥጃይቱን ከመደብ ላይ አታስሪያትም!” በማለት ይናገራል:: ሚስትም የዋዛ ስላልነበረች ከባልዮው በላይ እሳት ለብሳ እሳት ጎርሳ “ምን የቆረጠው ነው ጥጃየን መደብ ላይ እንዳላስራት የሚከለክለኝ?” በማለት ያዙኝ ልቀቁኝ ትላለች:: “አታስሪያትም ብያለሁ አታስሪያትም” ባል ከሚስት በላይ ጮሆ ያስጠነቅቃል:: ሚስት የምትረታ አልነበረችም: ባልዮውም ነገሩን ችላ ብሎ የሚያልፍ አልሆነም:: ‘አታስሪያትም! – አስራታለሁ’ የሚለው ጭቅጭቅ እየተካረረ ሄዶ በመጨረሻ ወደድብድብ ያድጋል:: ባል ሆየ በያዘው ከንተሮ ሚስቱን ኩኳን ሲላት እንደ እስክስታ ወራጅ እየተውረገረገች ወደ ታች ወርዳ ከመሬት ላይ ትዘረራለች:: ባል በበኩሉ ሚዛኑን መጠበቅ አቅቶት ከድንጋይ ላይ ወድቆ ሳይነሳ በዚያው ይቀራል:: በሌለ ነገር: ባጉል ተስፋ ባልና ሚስቱ ሕይወታቸውን አጡ::

በባዶ ስልጣን የሚራኮቱ የፖለቲካ ድርጅቶችን ባሰብሁ ቁጥር የባልና ሚስቱ ታሪክ ትዝ ይለኝና ፈገግ ያሰኘኛል:: ኢትዮጵያ በጎጠኞች እየተደገሰላት ያለውን ጥፋት እያዩና እየሰሙ ያሉት የአንድነት ተሟጋች ነን የሚሉት ድርጅቶች ከስህተታቸው ተምረው የግል ፍላጎታቸውን ወደጐን በማድረግ በአንድነት ለመቆም ፍላጎት ባለማሳየታቸው እንወዳታለን የሚሏትን ሀገር ዕጣ ፈንታ ለጐጠኞች አሳልፈው በመስጠት የእርስ በርስ የመጠፋፋት ስራ እየሰሩ ነው::

የሀገራችን ተረትና ምሳሌወች ከአዝናኝነት በላይ አስተማሪነታቸው አሌ የሚባል አይደለም:: ተረትና ምሳሌወች ሰዎችን እያዝናኑ ትምህርት ለማስጨበጥ ተመራጭ መንገዶች ናቸው:: ክርስቶስ እራሱ ሰዎችን ሰብስቦ ሲያስተምር ምሳሌወችን መጠቀም ያዘወትር እንደነበር ነው ከመጽሀፍ ቅዱስ የምንረዳው:: ከቀልዳ-ቀልዶችና ከተረትና ምሳሌወች ቁምነገር የሚቀስሙ ሰዎች ባይበዙም አይጠፉም:: በቁምነገር መሀል የጅል ቀልድ የሚቀልዱ ግን ሞልተዋል:: ደግሜ እለዋለሁ:: ልብ ያለው ሰው የሚነገሩትን ቀልዳ-ቀልዶችን: ታሪክና ምሳሌወችን ስቆ የሚያልፋቸው ሳይሆን ትምህርት የሚቀስምባቸው ናቸው:: አንዳንዶቹ ግን ከተረትና ምሳሌም ሆነ ከሚታየውና ከሚደረገው ተጨባጭ ክስተት ሊማሩ የማይችሉ የልማድ ደንበኞች ናቸው:: ሕዝብ በጎጠኞች ግራና ቀኝ ተወጥሮ ተይዟል:: የአንድነት ኃይሎች ነን የሚሉት ቡድኖች ግን በአንድነት መቆም ተስኗቸው የሀገር ጠላቶችን ከጎን አስቀምጠው በእርስ በርስ የቀዝቃዛ ጦርነት ተጠምደዋል:: ይህ ሊታረም ይገባል:: በጊዜ ያልተሰራ ስራ ለዐይን ሲይዝ (በአመሻሽ) ልስራህ ቢሉት ስለሚያስቸግር አሁኑኑ ተሰባስበን ደርሰናል እንበል::

ትንሳኤ ለኢትዮጵያ

የለውጥ ሃይሎች ግልጽና……. ክፍል ሁለት –ኤርሚያስ ለገሰ

$
0
0

ጆቤ እንኳን ደህና አልመጣችሁ!!

ለህዝብ ውይይት መድረክ የተዘጋጀ (ሂውስተን/ቴክሳስ)

                                       

   ኤርሚያስ ለገሰ

       የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቭዥንና ራዲዮ(ኢሳት)

    ጥቅምት/2016

                                

                  ማስታወሻ        

ይህ ጽሁፍ ከራሴ ውጭ የምሰራበትን የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቭዥንና ሬዲዮ (ኢሳት)ን ጨምሮ የማንንም አቋም አያንፀባርቅም::

 

 

መግቢያ

ermias copy“የለውጥ ሃይሎች ግልፅና ደፋር ውይይት ለመፍትሔና የጋራ ድል” በሚል አቢይ ርዕስ ተከታታይ መጣጥፍ እየቀረበ ነው። ከዚህ ቀደም “በክፍል አንድ” በተሰራጨው ጽሁፍ ሁለት ቁምነገሮችን ለመዳሰስ ተሞክሯል። የመጀመሪያው፦ ግልጽና ደፋር ውይይት የምናደርግባቸው መሰረታዊ ምክንያቶች ምን እንደሆኑ ለመዘርዘር ተሞክሯል። ዛሬ አገራችን ያለችበት ሁኔታ የሚያሳስበው ዜጋ ባለመኖሩና አገር አደጋ ላይ በወደቀችበት ሁኔታ በመተማመን ላይ የተመሰረተና የጋራ ድል (win- win) በሚያረጋግጥ መልኩ ምክክር መካሄድ እንዳለበት የተገለጠበት ነው። መጣጥፍ በኢትዮጵያ ውስጥ የስርአት ለውጥ መምጣት አለበት በማለት የሚንቀሳቀሱት ሁሉም የለውጥ ሃይሎች የዛሬና የነገን ኢትዮጵያ እጣ ፋንታ በሚወስኑ መሰረታዊ ጉዳዮች ላይ ምን እንደሚያስቡ ለህዝቡ ማቅረብ እንዳለባቸው የሚጠይቅ ነው።

ሁለተኛው፦ በተከታታይ ለሚቀርቡት ጽሁፎች መነሻ ከተደረጉ አምስት ታሳቢዎች ውስጥ ሦስተኛው ታሳቢ (“የአዲስ አበባ ነዋሪ የስርአት ለውጥ ይፈልጋል። ህዝባዊ ማዕበሉን ለማቀጣጠል ዝግጁነቱ ከፍተኛ ነው”) የሚለው ሃሳብ የተስተናገደበት ነው። ለማስታወስ ያህል “በክፍል አንድ” በቀረበው ጽሁፍ የቀረቡት አምስት ታሳቢዎች የሚከተለውን ይላሉ

 

ታሳቢ አንድ፦ የህዉሃት አገዛዝ ይወድቃል። የሚወድቀው ግን በከባድ መስዋዕትነት ነው። ከተከፈለው ያልተከፈለው መስዋዕትነት ይበልጣል።

ታሳቢ ሁለት፦ የኢትዮጵያ አንድነት እንደተጠበቀ ይቆያል። የለውጥ ሃይሉ በኢትዮጵያ አንድነት ላይ አይደራደርም።

ታሳቢ ሦስት፦ የአዲስ አበባ ነዋሪ የስርአት ለውጥ ይፈልጋል። ህዝባዊ ማዕበሉን ለማቀጣጠል ዝግጅነቱ ከፍተኛ ነው።

ታሳቢ አራት፦የለውጥ ሃይሉ ከህወሃት የቀድሞ የጦር ጄነራሎችም ሆነ አመራሮች ብዙ መጠበቅ የለበትም።

ታሳቢ አምስት፦ ከአጭር ጊዜ አኳያ የተገኘው ድል በብስለትና በፅናት ካልተያዘ ሊዳፈን ይችላል።

 

 

በመሆኑም በዚህ ጽሁፍ ላይ ለዋናው ሰነድ መነሻ ከሆኑት ውስጥ በ”ታሳቢ አራትነት” የለውጥ ሃይሉ ከህወሃት የቀድሞ የጦር ጄነራሎችም ሆነ አመራሮች ብዙ መጠበቅ የለበትም”) የሚለው ይቀርባል። በመጣጥፍ ሆድ እቃ ውስጥ የትግራይ ኤሊቶች በተለይም የቀድሞ የህዉሃት የጦር መኮንኖች መደ መድረኩ አሁን ለምን እንደመጡ፤ ይዘው የመጡት እጀንዳ ምን እንደሆነ፤ ወደፊት መምጣታቸው የሚያስገኘው ጥቅምና ጉዳት ለውይይት መነሻ በሚሆን መልኩ የቀረበበት ነው። ከዚህም በተጨማሪ ህሃትን ከመገርሰስ አኳያ ዋነኛ የትግል ማዕከሎችና ፓሎች (ምሰሶዎች) የትኛዎቹ እንደሆነ ለማሳየት ይሞክራል።

(“ክፍል አንድ” አግኝታችሁ ማንበብ ያልቻላችሁ ሰዎች በሳተናው፣ ኢትዮ-ሚዲያ ፎረም፣ ዘሃበሻ፣ ህብር-ሬዲዮ ድረ-ገጾች ላይ ማግኘት ይቻላል።)

 

 

(ታሳቢ አራት)

 የለውጥ ሃይሉ ከህወሃት የቀድሞ የጦር ጄነራሎችም ሆነ አመራሮች ብዙ መጠበቅ የለበትም።

 

 

ላለፉት ሩብ ክፍለ ዘመናት ህዉሃት በብሔር ብሔረሰቦች ዲሞክራሲያዊ መብቶች እየማለና እየተገዘተ ህዝቡን ለማታለል ብሎም ለመለያየት ቢሞክርም ያሰበውን አላማ ሊያሳካ አልቻለም። ለሁሉም ግልጽ እንደሆነው በአገራችን የሰላም እጦት ከጫፍ እስከ ጫፍ እየታየ ነው። የስርአት ለውጥና የነፃነት ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት የተለያዩ የትግል ስልቶች ተቀርፀው ወደ ትግባር ተቀይረዋል። እየተደረጉ ያሉት ትግሎች አስተሳስረን ስንመረምር አሁን ኢትዮጵያ ያለችበት ሁኔታ ሰላማዊ የፖለቲካ ትግልና ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር ወደ መቃብር የወረደበት ሆኖ እናገኘዋለን። ከዚህ በኋላ ህዉሃት መንግስታዊ የበላይነትን ባገኘበት ሁኔታ የምርጫ ፖለቲካ አጀንዳው ተዘግቷል። የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች እንዳሉት በምርጫ ፖለቲካ መቃብር ላይ ጥቁር አበባ ተቀምጦበታል። መቃብር ፈንቅሎ ትንሳኤ ይፈፀም ይሆን ለወደፊት የምናየው ይሆናል። ተስፋ አለኝ።

 

ከዚህ ጋ ተያይዞ ህዉሃት መራሹ ድርጅት በየጊዜው የሚሰጠው ድርጅታዊ መግለጫና እሱን ተከትሎ እየተወሰደ ያለው እርምጃ ተስፋ የሚያስቆርጠው የአገሬው ህዝብና የአለም መንግስታትን ብቻ አይደለም። የስርአቱ መስራችና ባለቤት የነበሩ እንዲሁም በተለያየ ከፍተኛ የፖለቲካና ወታደራዊ ስልጣን ላይ የነበሩትን ጭምር ነው። በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ የሚገኙ የኢትዮጵያ ሚዲያዎችን ያጨናነቁት ጄኔራል አበበ እና ጄኔራል ፃድቃን በስርአቱ ምላሽ ላይ ምን ያህል ተስፋ እንደ ቆረጡ መገመት ይቻላል። “የስርአት ችግር ስላለ፣ ኢህአዴግ የተቀባይነት ችግር ስላጋጠመው የስርአት ለውጥ መምጣት አለብት!” ብሎ የተናገረው አንደበታቸውና የከተበው ብዕራቸው ዞር ብለው ሲመለከቱ ማፈራቸው የሚቀር አይደለም። እነ ፃድቃን “ሀገሪቷ የመበታተን አደጋ ሊያጋጥማት ይችላል” ቢሉም የቀድሞ የትግል ጓዶቻቸውና የስልጣኑ ባለቤቶች “ህገ-መንግስታዊና ዲሞክራሲያዊ የፖለቲካ ስርአት በጽኑ መሰረት ላይ ተገንብቷል” የሚል ዲስኩር ያሰማሉ።

 

እነ ጆቤ “ህዝቡ በተስፋ እጦት ውስጥ ገብቷል” ብለው ሲፅፉ በተቃራኒው እነ አባይ ፀሀዬ “የአገራችን ህዝቦች በኢትዮጵያ የፈነጠቀውን የልማትና የዲሞክራሲ ጮራ ተማምነው በለመለመ ተስፋ ወደፊት ይመለከታሉ” የሚል ዘመን ተሻጋሪ ማብራሪያ ይሰጣሉ።  እነ ፃድቃን በቀኝ ሆነው የመቶ ፐርሰንት ምርጫ በህዝብ ማላገጥ ነው” በማለት ብዕራቸውን ሲያነሱ በግራ የተሰለፉት እነ በረከት “ኢህአዴግ ስራ በምርጫ ካርድ የተሰጠውን ሃላፊነት አደራ ለመወጣት ቆርጦ ተነስቷል” ይሉናሉ። አራንባና ቆቦ!!

 

እዚህ ላይ በሁለቱ የቀድሞ የጦር አዛዦችና የህዉሃት መራሹ መንግስት ሃይሎች መካከል በሁሉም ጉዳይ ተቃርኖ ውስጥ እንደገቡ የሚያስብ ካለ በደንብ ተሸውዷል። ሁለቱም ሃይሎች የህዉሃትን ብሎም የትግራይ ህዝብ ጥቅም ይነካል ብለው በገመቱት ጉዳይ ላይ ተመሳሳይ አቋም አላቸው። ከዚህ አንፃር በቅድሚያ ሊነሳ የሚችለው በቀድሞ በትግራይ አስተዳደር ስር ያልነበሩና ዛሬ የተካለሉት ወልቃይትን የመሳሰሉ ቦታዎች ናቸው። የጦር አዛዦቹም ሆነ የህዉሃት ታጋይ ባለስልጣናት መጀመሪያ ሰሞን የወልቃይትና ተመሳሳይ ቦታዎች ፈጽሞ አንዳይነሱ፤ የሚዲያ ትኩረት እንዳያገኙ አድርገው ነበር። በጽሑፎቻቸውም ሆነ በመግለጫዎቻቸው በየትኛውም ቦታ ከመግለጥ ተቆጥበው ነበር። የቅማንትን ጉዳይ አጉልቶ የገለጠው “ጆቤ” ወልቃይት ላይ ሲደርስ የብዕሩ ቀለም በሚያስፎግር ሁኔታ አልቆበት ነበር። በኦሮሚያ ጥያቄዎች ላይ በምናቡ ከፈጠራቸው የኦሮሞ ልጆች ጋር ማውራቱን ሊነግረን የፈለገው ጄነራል አበበ ጠገዴና ጠለምት ፀለምት(ጨለማ) ሆነውበት ግድግዳ ተስታኮና ተንፏቆ ሲያልፋቸው ተመልክተናል።

 

ሁኔታዎች እየገፋ ሲመጡና የትግሉ ማዕከሉ “ወልቃይት” መሆኑ ሲረጋገጥ እየተንፏቀቁም ቢሆን የወልቃይትን አጀንዳ ማንሳት ጀመሩ። ለምን ከዚህ በፊት ልታነሡት አልሞከራችሁም ሲባሉ “ይሔ ትልቅ ጉዳይ አይደለም። መደረግም አልነበረበትም” የሚል ምላሽ ሰጡ። ቁምነገሩ እዚህ ጋር ነው። ለእነ ጄነራል ፃድቃን የቅማንት ጉዳይ ትልቅ እንደሆነ አድርገው ሊያገኑት ሲሞክሩ የማያቋርጥ የህዝብ ደም እየፈሰሰበት ያለውን ወልቃይት ንቀው እንደተውት ሊያሳዩ ሞከሩ። እነዚህ ሰዎች ይህን ምላሽ ሲሠጡ ወልቃይት “የትግል ማዕከል” እና “የኢፍትሃዊነት ማሳያ” መሆኑን ጠፍቷቸው አይደለም። ልክ አቶ መለስ በኢትዮ- ኤርትራ ጦርነት ወቅት ካድሬዎች “ለምን ባድመን ለመሰለ ቁራሽ መሬት የ10ሺዎች ደም ይፈሳል?” ብለን ሥንጠይቀው እጁን እየጠበጠበ “ባድመ የትግላችን ማዕከል የሆነችው የኢፍትሐዊነት ማሳያ ስለሆነች ነው” በማለት የንዴት ምላሽ ሰጥቷል። በመሆኑም ባድመ የኤርትራ መንግስት በሃይል ስለወሰዳት መጀመሪያ ወደቀድሞው ቦታዋ ትመለስና ህጋዊ ውሳኔ ይሰጥባት እንደተባለ ሁሉ የወልቃይትም ተመሳሳይ ነው። ወልቃይት “ኢፍትሃዊነት ማሳያ” ስለሆነች መጀመሪያ ወደቀድሞው ታሪካዊ ባለቤቷ ትመለስና ሌሎች የህዝብ ጥያቄዎች ቂም በቀል በማይፈጥሩና የጋራ ድል (Win_Win) በሚያረጋግጡ መልኩ ይፈቱ ማለት የአባት ነው። ይገባልም። ይህ ካልሆነ ግን ምንአልባት ከባድመው ባልተናነሰ በ100ሺዎች የሚጠጋ ህይወት የሚወድቅበትና ደም መቃባቱ የሚያባራ ሊሆን ይችላል።

 

በመቶ ሺዎች ሊገደሉ ይችላሉ የሚለውም ተራ ማስፈራራት አይደለም። ህዉሃት በተለይም የአማራ ተወላጆች ላይ የቋጠረው የቂም ቋጠሮ ከዚህ በላይ ሊገድል እንደሚችል ፍንጭ የሚሰጥ ነው። የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር አሰፋ አቢዩ ከሳምንታት በፊት በሰጠው መግለጫ “99 ፐርሰንት ንፁህ ናቸው። እርምጃ የምንወስደው በተቀሩት ላይ ነው” በማለት ይፋ አድርጓል። አሁን ባለው የአማራ ክልል ንቅናቄ ከ5 ሚሊዮን የአማራ ተወላጆች በቀጥተኛ እየተሳተፉ እንደሆነ ዝቅተኛ ግምት ቢወሰድ እንኳን በኮሚሽነር አሰፋ ስሌት መሠረት ከ50 ሺህ በላይ ሠዎች እርምጃ ይወሰድባቸዋል። ህዝባዊ ማዕበሉ እየሰፋ ሲሄድ በአስቸኳይ የስርአት ለውጥ ካልመጣ እርምጃ የሚወሰድበት የአማራ ተወላጅ ሁለትና ሶስት እጥፍ ይሆናል። ስለዚህም፣ ለህዉሃት “የትግል ማዕከል” (centrifugal force) የሆኑትን ቦታዎች አሳልፎ መስጠት መቃብሩን በጥልቀት የመቆፈር ያህል ስለሚመለከተው በጅምላ ከመግደል የሚመለስ አይሆንም።

 

በእኔ እምነት ኢትዮጵያ ውስጥ የተቀጣጠለው ህዝባዊ ማዕበል ከህዉሃት ህልውና አንጻር በርካታ ዋልታዎች (Multi- Polar) ያሉት ቢሆንም፣ የዋልታዎቹ ምሰሶ ወልቃይት (Wolqayit Factor) ተደርጎ የሚወሰድ ነው። የኦሮሚያ፣ ጋምቤላ፣ ኮንሶ የተነሱት እምቢተኝነቶች ትላልቅ ዋልታዎች ቢሆኑም ህዉሃት ልቦና ገዝቶ በህይወት መቆየት ከፈለገ ወደ ምሶሶነት ሳያድጉ በተራዘመ ሂደት ሊያዳፍናቸው ይችላል። ለምሳሌ ህዉሃት ኤርትራ ላይ የሚያስበው (Eritrian-Factor፡ ኤርትራ በጦርነት ማሸነፍና አስመራ ላይ አሻንጉሊት መንግስት መመስረት) ከተሳካና ህዉሃት ኢትዮጵያን መምራት ከተነሳው የኦሮሚያን ጥያቄ እስከ ጫፍ በመውሰድ ምላሽ ሊሰጥበት ይችላል። ይህም በኦሮሞ ጉዳይ የተደራጁ የፖለቲካ ፓርቲዎችንና አክቲቪስቶችን የመከፋፈል እድሉ ሰፊ መሆኑ አይቀርም። ህዉሃት እስከ ጫፍ የሚወስደውን ፍላጎት ለመቀበል አዳዲስ ሃይሎች (Emerging Powers) የሚፈልቁበት ሁኔታ ይፈጠራል። በመሆኑም ህዉሃት በሚቀደው ሀገር የማፍረስ ቦይ የሚፈሱ ቁጥራቸው ቀላል ያልሆኑ ሰዎች ይኖራሉ። ከሰሞኑ የድል አጥቢያ አርበኛ ሆነው ብቅ ብቅ ማለታቸው አይቀርም። በጅምር ላይ ያለውን የትብብር መንፈስም ውሃ ሊቸልሱበት ይሞክራሉ።

 

ወደተነሳንበት ስንመለስ ሁለቱ የህዉሃት የቀድሞ ጦር አዛዦች በተለይም ሌ/ጄነራል ፃድቃን ወልቃይትና ሌሎች “የኢፍትሐዊነት ማሳያ” ቦታዎችና “የትግል ማዕከሎች” በተመለከተ ያስቀመጡት ምላሽ ህዝባዊ እምቢተኝነቱን የበለጠ ነዳጅ የሚጨምር ነው። ጄነራል ፃድቃን መጀመሪያ አካባቢ ባቀረባቸው ጽሁፎች በብልጣብልጥነት ሊያልፈው ቢፈልግም ቦታዎች ይበልጥ “የትግሉ ማዕከሎች” መሆናቸውን በህዝባዊ ማዕበሉ ሲመለከት ከድርቅና በተሻገረ አይን አውጣነት ለአዲስ አድማስ ጋዜጣ እርስ በራስ የተምታታ ምላሽ ሰጠ። ይህ የጦር መኮንኑ ምላሽ የአማራ ህዝብ ትግልና መነቃቃት ከደረሰበት ደረጃ ጋር ፍፁም የማይመጥን ነው። የአሁኑ የአማራ ትግል የደረሰበት ደረጃ ፍልሚያው ተጧጡፎ አድማሱን በመስፋት ቅኝቱ ሙሉ ለሙሉ ተቀይሯል። ከአስር አመት በፊት ሃሰን ዑመር አብደላ በመጣጥፋቸው እንደገለጡት ቅኝትና ምቱ ከተቀየረ እስክታውም መቀየር አለበት። በመሃመድ አህመድ የትዝታ ቅኝትና ምት ጥላሁን ገሠሠን “አንቺን ነው! ሰማሽ ወይ” የሚለው አይደነስም። በ “እምበር ተጋዳላይ” አጨፋፈር ስልት የይሁኔ “ሰከን በል” አይጨፈርም። እንደዚህ ከሆነ በአራዳ ቋንቋ ሽወዳ ይሆናል። አሁን ትግሉ በደረሰበት ደረጃ ደግሞ ውሽልሽል ምክንያት ሸውዶ ማለፍ የሚችልበት ወቅት ላይ አይደለንም። አለበለዚያም እውነት መድፈር ካልተቻለና የሚያስፈራ ከሆነ (ኮንስቲትወንሲያቸውን እንደሚያጡ ይገባኛል) ምላሽ አለመስጠት ይቻል ነበር። ፃድቃን ሊጠቀምበት የፈለገው “የሽወዳ ፖለቲካ” ህዝባዊ እምቢተኝነቱን አቀጣጥሎ መስዋዕትነቱን ከመጨመሩ ባሻገር በሌሎች ያቀረባቸው የመፍትሄ ሃሳቦችም ላይ በጥርጣሬ እንዲታይ ያደረገ ነው።

 

ለማንኛውም ሌ/ጀነራል ፃድቃን ገ/ትንሳይ “የትግሉ ማዕከል” በሆነው ወልቃይት ዙሪያ ለአዲስ አድማሱ ጋዜጣ የሰጠውን መግለጫ በመመልከት ፍርዱን እንስጥ። አዲስ አድማስ ጋዜጣ “በሰሜን ጎንደር አካባቢ ያለው ተቃውሞ በተለይ ከ “ወልቃይት አማራነት” ጋር የተያያዘ ነው። የወልቃይት የማንነት ጥያቄ ጉዳይ በምን አግባብ ነው መፈታት ያለበት?” ለሚለው ጥያቄ የሚከተለውን ምላሽ ሰጥቷል።

 

“እኔ የወልቃይት ጉዳይ ለአንዳንድ ፖለቲካዊ አላማዎች ሽፋን ነው ብዬ ነው የማምነው። እንዴት ነው የሚፈታው ላልከው እኔ የሚታየኝ ህገ- መንግስቱን መሠረት አድርጎ ነው። በመጀመሪያ ደረጃ ይሔ ትልቅ ጉዳይ መደረግ አልነበረበትም። ህዉሃትና ብአኤን ተመካክረው መፍታት የሚችሉበት ደረጃ ላይ መድረስ ነበረባቸው።…. በህጋዊ መንገድ ስንሄድም ህገ-መንግስቱን መሰረት አድርጎ መፍታት ያስፈልጋል ነገር ግን ክልሎች በሚወሰኑበት ወቅት ከፍተኛ የፖለቲካ ውሳኔ ሰጪ አካል ውስጥ ነበርኩ። በወቅቱ ቋንቋና የህዝብ አሰፋፈርን መሰረት አድርገን እንወሰን በሚል ነው የወሰነው። በዚህ መሰረት ደግሞ የተወሰነው ተወስኗል።”

 

አዲስ አድማስ ጋዜጣ ቀጥሎ የጠየቀው “በወቅቱ ወልቃይት እንዴት ነው ወደ ትግራይ የተላከው?” በማለት ነበር። ሌ/ጄነራሉ እንዲህ በማለት አስገራሚ፣ አሳዛኝና እርስ በራሱ የሚደባደብ ምላሽ ሰጠ።

 

“አሁን እየጠየከኝ ያለኸው መረጃ ነው። ይሄን መረጃ አሁን አላስታውሰውም። እንደዚህ  ሆኖ ነበር ብዬ ለማለት አልችልም። የተጠቀምንበት አቅጣጫ ግን የፌደራሊዝሙን መነሻ ነው። የህዝቦች ቋንቋና ባህልን መነሻ አድርገን ነው የከለከልነው። እኔ እስከማውቀው ድረስ እዚያ አካባቢ ያለው አብዛኛው ህዝብ ትግርኛ ተናጋሪ ነው። ባህሉ የትግራይ ነው። በትግራይ ውስጥ ሊካተት የሚችል ህዝብ ነው። የሆነውም በዚህ አግባብ ነው።”

 

በመሆኑም እነዚህ የህዉሃት ጦር ጄነራሎች “ህዉሃት አደጋ ላይ መውደቁን ሲያዩ ሊታደጉት መጡ” የሚለውን አባባል ለጊዜው እንተወውና የጎደላቸውን ነገር በጨዋ ቋንቋ እንንገራቸው። በእኔ በኩል  የጦር ጀነራሎቹ ወደፊት መምጣት ቢያንስ በአራት መሰረታዊ ጉዳዮች እደግፈዋለው።

አንደኛው ያልተገለጠ ማንኛውም አስተሳሰብ ስለማይታወቅ መገለጥ አለበት የሚል የፀና እምነት አለኝ። የሉቃስ ወንጌል (መዕራፍ 6 ቁጥር 45) በልብ ሞልቶ ከተረፈው አፍ ይናገራል።….. ክፉ ሰውም ከልቡ ክፉ መዝገብ ክፉ ውን ያወጣል። መልካም ሰውም ከመልካም መዝገብ መልካም ያወጣል” አንዲል አንደበታቸውና ብዕራቸው የተፋው ቁምነገር ከየትኛው ልብ እንደመነጨ ማወቅ የሚጠቅም እንጂ ጉዳት የሚያደርስ አይደለም።

 

ሁለተኛው ምክንያት እነዚህ የህዉሃት የጦር ጄኔራሎች የቀድሞ ድርጅታቸው ምን ያህል ኋላቀር፣ ለለውጥ ዝግጁ ያልሆነ ግትረኛ፣ ፈሪ ድንጉጥ እንደሆነ በቀላሉ መረዳት ይችላሉ የሚል እምነት አለኝ። እንደጠበኩት በጥቂት ቀናት ውስጥ በህዉሃት ስፖንሰርነት የሚንቀሳቀሱት የውጭ ድረ-ገጾቻቸው ዘመቻቸውን በተጠናከረ መንገድ ከፈቱ። የአየር ሃይል አዛዥ የነበረውን አበበ ተ/ሃይማኖት በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ወቅት የአውሮፕላን ግዥ ላይ ፈፀመ ያሉትን ሌብነት እየጠቀሱ  ወረዱበት። “የፈፀምከውን ሌብነት ዝም ስንልህ የረሳነው መሰለህ እንዴ?” በሚል ማስፈራራቱን ቀጠሉ። ጄኔራል ፃድቃንን ደግሞ “የስልጣን ፍላጎት የቀፈቀፈው ሃሳብ” በማለት አብጠለጠሉት። ይባስ ብለው በኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚና ማዕከላዊ ኮሚቴ ስም ባወጡት ድርጅታዊ መግለጫ የኢትዮጵያ ህዝብ በሁሉም የህይወት መለኩ (መንፈሳዊንንም ይጨምራል) ከፍተኛ ለውጥ እንዳመጣ፣ ህገ-መንግስታዊ ስርአቱ ጠንካራ መሠረት ላይ እንደተጣለ፣ በዲሞክራሲያዊ ምርጫ (100%) አሽንፈው የመንግስት ስልጣን እንደተቆጣጠሩ፣ ባለሁለት አሀዝ ተከታታይ እድገት አምጥተናል….ወዘተ የሚሉ አስደንጋጭ ቃላትን በመጠቀም የጦር መኮንኖችን ቆሌ ገፈፋ።

ሦስተኛው ምክንያት የህዉሃት የጦር ጄነራሎች የሚያቀነቅኑት ሃሳብ ምን ያህል የአገራችንን ችግሮች በጥልቀት ይዳሳሳል፤ ምን ያህል ተቀባይነት ይኖረዋል፤ ከመንግስትና የለውጥ ሃይሎች ፍላጎት አንፃር የተቃኘ ነወይ፤ የደበቋቸውና ለህዝብ ይፋ ቢደረግ ራሳቸውንም ሆነ የቀድሞ ድርጅታቸውን ተጠያቂ የሚያደርግ ነገር ይገልጡ ይሆን ወይ?….. ወዘተ የሚሉ ጥያቄዎች ምላሽ ያገኛሉ በሚል ነው። በግሌ የጠበኳትን አግኝቻለሁ። መኮንኖች የስርአቱ ችግር አለ መፍትሄው ስርአታዊ (systemic) መሆን አለበት ብለዋል። እርግጥ መፍትሄው አሁን ባለው የህዉሃት/ኢህአዴግ ህገ-መንግስት ማዕቀፍ ስር መሆን እንዳለበት ያስገነዝባሉ። አሁን ባለው ህገ- መንግስት እንዴት አድርጎ ስርአታዊ ለውጥ ለማምጣት እንደሚቻል እንቆቅልሽ ቢሆንም  እንደ ሃሳብ መነሳቱ የሚያበረታታ ነው። በተለይ ህዉሃት አሁን ከዚያው አቋም ሲነፃፀር ምን ያህል የሰማይና ምድር ልዩነት እንዳለ መገንዘብ ይቻላል። ሰሞኑን አቶ በረከት የኤፈርት ኩባንያ ንብረት የሆነው ሬዲዮ ፋና በጠራው ኮንፈረንስ ላይ አይኑን በጨው አጥቦ “18 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን መክረው የተጻፈ ህገ-መንግስት፣ በአለም ላይ ካሉ ጥቂት ምርጥ ህገ- መንግስቶች አንዱ የሆነ” በማለት ዲስኩር ሲያሰማ እንደነበር ለሁሉም ግልጽ ነው። ህገ-መንግስታዊ ፍርድቤት የሌለው፤ ፍርዱን የሚሰጡት እነ አባዱላ፣ ሙክታር አህመድ፣ አባይ ወልዱ፣ ገዱ አንዳርጋቸው…… ወዘተ የሆኑበት ህገ-መንግስት ምርጥነትን ለመናገር በበረከት የአስተሳሰብ ደረጃ ዝቅ ማለት ይጠይቃል።

አራተኛው ምክንያት፡ የህዉሃት የጦር መኮንኖች በአንዳንድ የለውጥ ሃይሎችና በአለም አቀፍ ተቋማትና ሀገሮች ያለው ግንዛቤ በጣም አደገኛ መሆኑ ላይ ነው፡፤ እነዚህ ግለሰቦችና ተቋማት የጦር መኮንኖች የውስጥ አዋቂ አድርገው ስለሚቆጥሩ እንደ ዋነኛ የመፍትሄ አካል አድርገው የሚወስዱበት ሁኔታ በተደጋጋሚ ይታያል። ይህ አረዳድ በጣም አደገኛ ከመሆኑም ባሻገር የተጀመረውን የለውጥ እንቅስቃሴ ወደኋላ የሚመልስበት እድል ሰፊ ነው። የም ዕራብ ሐገሮች በተለይም ሰሜን አሜሪካ (ለምሳሌ የውጭ ጉዳይ መ/ቤት) በተለያዩ ጊዜያቶች ህዉሃት አደጋ ውስጥ ሲወድቅ እነዚህን የጦር መኮንኖች እንደ አማራጭ የሚያማትሩበት ሁኔታ መኖሩ የሚታወቅ ነው። በምርጫ 97 ማግስት (አቶ በረከት ስምኦን ያጫወተኝ ስለሆነ በከፊል እመኑኝ) የቅንጅት አመራሮች ከአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መ/ቤት ጋር በሚወያዩ ሰዓት ጄኔራል ፃድቃን ገ/ተንሳይ እንዲያካትቱ ጠይቀዋቸው እንደነበረ በንዴት ውስጥ ሆኖ አውግቶኛል። ይሄ የበረከት አገላለጥ እውነት ይሁን ውሸት ታሪክ የሚገልጠው ቢሆንም ዊክሊክስን ያገላበጠና የአሜሪካ ኤምባሲ ከቀድሞ የህዉሃት አመራሮች ጋር ያደረጉትን ሚስጥራዊ ውይይት ለተመለከተ አሜሪካኖቹ የሚይዙት የተሳሳተ አመለካከት እንደሚኖር መገመት ይቻላል።

 

አንዳንድ የለውጥ ሃይሎች ነን የሚሉና አለም አቀፍ ተቋማትና ሀገራት የጦር መኮንኖቹን እንደዋና መፍትሄ የሚወስዱ ከሆነ በጣም አደገኛ ሁኔታ የሚፈጥርበት የተለያዩ ምክንያቶች አሉ። ከእነዚህ ውስጥ የመጀመሪያው የህዉሃት የጦር መኮንኖች ህዉሃት የኢህአዴግ የፖለቲካ አስኳል መሆኑን ሌሎች የኢትዮጵያ ማህበረሰቦችና የውጭ ሃይሎች እንዲያውቁ አይፈልጉም። ጄኔራሎቹ በጠመንጃ፣ በደህንነት፣ በኢኮኖሚና ፖለቲካ የበላይነት የአገሩ ባለቤት የሆነውን የትግራይ ነፃ አውጪ (ህዉሃት) ወደ ጎን ትተው የህይወት እስትንፋስ የሌለውን ኢህአዴግ እንደ መፍትሄ አመንጪና ተጠያቂ አድርገው ያቀርባሉ። ለስሙ ቦታውን የያዙትንና አንዳችም ስልጣን የሌላቸውን ከህዉሃት ውጪ ያሉ ባለስልጣናትን ከፍ ከፍ በማድረግ የተለየ ምስል ለመፍጠር ጥረት ያደርጋሉ። በተለይም የአየር ሃይል አዛዥ የነበረው ጄኔራል አበበ ተ/ሃይማኖት በሙት መንፈስ የሚመራውን ሃይለማርያም ደሳለኝ ብዕሩን ባነሳ ቁጥር ሲያንቆለጳጵስና ሲያሞካሽ ማየት የተለመደ ሆኗል። “ይድረስ ለክቡር አቶ ሃይለማሪያም ደሳለኝየጦር ሃይሎች ጠቅላይ አዛዥ” የሚል ርዕስ በመጠቀም “ለሰራዊቱ ግንባታ የተዘጋጀው መጽሀፍ አግዱልኝ!” በማለት ተማፅኖ ሲያቀርብ ይስተዋላል። ጀቤ ይሄን የሚያደርገው የሃይለማሪያምን “የህዉሃት ትሮይ ፈረስነት” አጥቶት አይደለም። ኢህአዴግ የሚባለው አደረጃጀት ለህዉሃት ጭምብልነት የተፈጠረ መሆኑን ዛሬም የሚመራበት መርሆ በጫካ የተቀረፀና ከዘመኑ ጋር የማይሄድ፤ ሸረሪት የሚሯሯጥበትና ያደረበት መሆኑን ጠንቅቀው ያውቃሉ።

 

ከጄኔራል ፃድቃን አስተያየት ሳልወጣ አድናቆቴን መግለጽ የምፈልግበት አንድ አረፍተ ነገር አለ። ጄኔራሉ በሌሎች የህዉሃት ታጋዮች ባልተለመደ መልኩ አሁን ያለውን ሁኔታ ሲገመግሙ “የትግራይ ህዝብ በተለይም በከተሞች አካባቢ በሌሎች ማህበረሰቦች የመገለል ሁኔታ አጋጥሞታል። መተማመኛውንም የስልጣን የበላይነት አስጠብቆ ማቆየትና በመከላከያና ሌሎች የፀጥታ ሃይሎች ተከልሎ መኖር” እንደሆነ ገልጧል። ይሄንን ግምገማ ሙሉ በሙሉ የምቀበለው ነው። ለረጅም ጊዜያቶች ይሄ ችግር እየመጣ እንደሆነ ደጋግመን ስንለፈልፍ በህዉሃት ጎራ ያሉ ሰዎች “ዘረኞች” የሚል ታፔላ ተለጥፎልን ነበር። ዛሬ የጦር መኮንኑ በግላጭ ሲያወጣው በህዉሃት መንደር የተፈጠረ ብዙም መንጫጫት አይታይም። ታዲያ! ጄኔራል ፃድቃን በዚህ ጉዳይ ላይ ይሄን ያህል ርቀት መጓዝ ከቻለ ከጥያቄው ጋር አብረው ለሚነሱት ሌሎች ጥያቄዎች ምላሽ ቢሰጥበት እኛንም ከስድብና ውርጅብኝ ያድነናል። ጥያቄው የትግራይ ህዝብ በተለይ በከተሞች ውስጥ በሌላው ማህበረሰብ እየተገለለ መሄዱ እውነት ሆኖ ሲያበቃ፤ የመገለሉ መንስ ኤና መሰረታዊ ምክንያት ምንድነው? መገለሉስ ከመቼ ጀምሮ የተፈጠረ ነው? ተጠያቂው ማነው?…. ወዘተ የሚሉ ናቸው። ይህንን ቁልፍ ጉዳይ መመለስ ከተቻለ ወደ ቁልፍ መፍትሄው የምንሄድበት መንገድ አልጋ በአልግስ ይሆናል።

 

ከዚህኛው ክፍል ከመውጣቴ በፊት ሁለቱን የህዉሃት የጦር ጄኔራሎችም ሆነ እነሱን ተከትለው ሃሳባቸውን በሰፊው ተቀብለው ያራመዱ የአገር ውስጥ ሚዲያዎች የቀጣይ እጣፈንታ ምን ሊሆን ይችላል የሚለውን የራስ ግምት አስቀምጬ መሄድ እፈልጋለሁ። ከልምድ ማየት እንደሚቻለው ህዉሃት በአንድ መሰረታዊ ጉዳይ ላይ አቋም ወስዶ መግለጫ እስኪያወጣ ድረስ የቀድሞ አባላቱንም ሆነ በግል ኤሌክትሮኒክስ ሚዲያ የሚንቀሳቀሱ (ሸገር 02) ድርጅቶች ትንሽ ለቀቅ ያለ ሃሳብ የሚያራምዱበት በር ገርበብ ይደረግላቸዋል። የዛን ሰሞን አፋችንን ይዘን በመገረም “በሸገር ካፌ” ላይ ወይዘሮ መዓዛ ብሩና ጓድ አብዱ የጄኔራል ፃድቃንን “የስርአት ለውጥ” አስተሳሰብ ተገቢ እንደሆነ በአድናቆት ሲነግሩን ነበር። እርግጥ የደርግ ዘመን ጥያቄና መልስ ላይ “አብዮታዊ” ማብራሪያ ሲሰጥ የምናውቀው ጓድ አብዱ በእያንዳንዱ ንግግሩ ሟቹ መለስ ዜናዊን ሲያንቆለጳጵስ መደመጥ ብዙዎችን አስገርሟል። በጣት ቆጠራ አልፈው ካልሆነ በስተቀር ጓድ አብዱ ከሰባት ጊዜ በላይ ባደርገው የሟች ጥሪ በስላሴ 24 ሰዓት ቁጭ ብለው መቃብር የሚጠብቁ የህዉሃት ዋርድያዎችን ሳያስበረግግ አይቀርም።

 

ወደ ገደለው ጉዳያችን ስንመለስ የህዉሃት የቀድሞ ጄኔራሎችም ሆነ እንደ ሸገር ያሉት የሚዲያ ተቋማት ህዉሃት/ኢህአዴግ መግለጫ ካወጣ በኋላ ቀስ በቀስ ወደ ኋላ መንሸራተታቸው የግድ ይሆናል። ያለ አንዳች ጥርጥር ጄኔራሎቹ ወደ አፎታቸው ይገባሉ። ሸገርና ተመሳሳይ ሚዲያዎች ደግሞ ወደ ሰገባቸው። ይህን ማድረግ ካልቻሉ “የአበራሽን ጠባሳ ያየ በእሳት አይጫወትም” የሚለው ብሂል ወደተግባር ተገልብጦ ለመመልከት ሩቅ አይሆንም። ለነገሩ ጆቤና ጓድ አብዶ በአክሮባት የሚታሙ ስላልሆነ ካናዳው ለማምለጥ እንደ አቦሸማኔ መሮጣቸው ሳይታለም የተፈታ ነው።

 

የትግራይ ኤሊቶች፣ የህዉሃት የቀድሞ የጦር ጄኔራሎችም ሆነ የቀድሞ ታጋይ ባላስልጣናት ከህዉሃት በፍጥነት ተፋተው ለአዲስ የስርአት ለውጥ ዝግጁ የማይሆኑባቸው ሌሎች ተጨማሪ መሰረታዊ ምክንያቶች አሏቸው። ከዚህ ውስጥ የቅድሚያ መስመር የምትይዘው ኤርትራ ናት (Eriteria-Factor)። ህዉሃት ከኢርትራ ጋር የገባበት ጦርነት ፍፃሜ የረጅም ጊዜ የመጠባበቂያ ህልሙን ያጨለመ ነው። ለሁሉም ግልጽ እንደሆነው ከጦርነቱ በፊት ከኤርትራ መንግስት ጋር ለአመታት የተካሄደው ድርድርም ሆነ የጦርነት ውሳኔ የተወሰነው በህውሃት ማዕከላዊ ኮሚቴ ነው። ወደ ጦርነት ከተገባም በኋላ የመሪነቱን ሚና የጨበጡት ህዉሃቶች ናቸው። በጦርነቱ ምክንያት የአገሪቱ ካዝና በተራገፈና ሙጥጥ ባለ ሰዓት መንግስት ከሶስት ቢሊዮን ብር ያላነሰ የተበደረው ከህዉሃት የኢኮኖሚ ኢምፓወ ከሆነው ኤፈርት (ትእምት) ነበር። ለጦርነቱ የሚሆነውን የጦር መሳሪያ (ታንክ፣ ሮኬት፣ ሚሳየል፣ የውጊያ አውሮፕላኖች……) በየአህጉራቱ የተሽከረከሩ የሚገዙት የህዉሃት አመራሮችና የጦር አዛዦች ናቸው።

 

(በነገራችን ላይ በአውሮፕላን ግዢ ላይ ከፍተኛ ተሳትፎ ከነበራቸው የጦር አዛዦች ግንባር ቀደሙን የሚይዘው የቀድሞ አየር ሃይል አዛዥ የነበረው ሜ/ጄኔራል አበበ ተ/ሃይማኖት ነው። አበበ የክፍፍሉ መጀመሪያ ወቅት እንቡር እንቡር ቢልም የአንጃዎቹ መጨረሻ ኩምሽሽ አድርጎታል። “አይተነው ጊዜ ወደሚያደላው” አይነት ባህሪ ያለው አበበ ገልብጦ የመለስን ቡድን ይቅርታ ቢጠይቅም የመለስን የቃሪያ ጥፊ ከማግኘት አልታቀበም። ከአዛዥነቱ በንፋስ ፍጥነት ተባረረ። ከዛ በኋላ ጆቦ በሚሊዮን ብር የሚጠጋ ገንዘብ ከኪሱ በማውጣት አሜሪካን ሀገር ተማረ። በትምህርቱም “የአሰብ ኢትዮጵያዊነት” ተገለጠለት። መገለጡ ቀልብ ይስባልና በኢትዮጵያ አየር ሃይል ላይ በተነው። ጆቤ! ዛሬ በወር 150ሺህ ብር የሚከራይ ቪላ አለው። ያውም በአዱገነት እምብርት! ለ100 አመት ይዞ ቢቆይና ከደሞዙ ሰባራ ሳንቲም ባያወጣ አሁን ያለውን ሀብት ሩብ አይኖረውም። እርግጥ ከርቀት እንደሰማነው ባለቤቱ ብቸኛዋ ሴት ጄኔራል ሆናለች።)

 

እዚህ ላይ የኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ውጤት ለህዉሃት የበላይነት መምጣትና የትግራይ ተጠቃሚነት ዋስትና የፈጠረው አደጋ ለህዉሃት መሰንጠቅ መሰረታዊ ምክንያት ቢሆንም ሌሎች ተጨማሪ ምክንያቶች አሉት። እነዚህ አደጋዎች ከህዉሃት አፈጣጠር፣ የዘረጋው ስርአት ባህሪና ውስጠ- ድርጅት ሁኔታ ጋር የተያያዘ ነው። ህውሃት የበላይነቱን ያረጋገጠባት ኢትዮጵያ ካልቀጠለችና የአገር መበተን ካጋጠመ “የትግራይ ሪፐብሊክ” ነፃ ሀገር ፈጥሮ መኖር እንደ መጨረሻ ግብ ያስቀመጠ ቢሆንም ከኤርትራ ጋር የገባበት ቁርሾና ደም መፋሰስ ይህን ፍላጎቱን ከሞላ ጎደል ዝግ አድርጎታል። Eriteria-Factor የተባለው አንዱ ገፅታ ይሄ ነው። የጎንደር፣ አፋር፣ ወሎ ህዝብ ከታች ኤርትራ ከላይ ሆነው ትግራይን ሳንድዊች የሚያደርጉበት ሁኔታ ስለሚፈጠር ከዚህ በኋላ “የትግራይ ሪፐብሊክ” ከህልም የዘለለ አይሆንም። ትግራይን ገንጥለን በሰላም እንኖራለን የሚባል ህልም ወልቃይት፣ ጠገዴ፣ ጠለምት፣……ወዘተ ወደ ትግራይ የተከለሉ ሰአትና የኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት በተነሳ ሰአት ወደ መቃብር ወርዷል።

የኢትዮ- ኤርትራ ጦርነት አጨራረስ በአንድ በኩል ነፃ ሀገር ለመመስረት ህልም የነበረችውን የህዉሃት አመራሮች ወሽመጥ የቆረጠ ሲሆን፤ በሌላ በኩል ኢትዮጵያዊነቱን አጥብቆ ለሚፈልገው የትግራይ ህዝብ ትልቅ ብስራት ተደርጎ ሊወሰድ የሚችል ነው። በአጭሩ ኢትዮጵያን ወዳድ ለሆነው የትግራይ ህዝብ የጦርነቱ አጨራረስ በመጥፎ ሁኔታ ውስጥ የሚፈጠር ጥሩ አጋጣሚ ነው። Blessing in disguise!!

 

የኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት አጨራረስ ህዉሃትን ለሁለት ሰንጥቋል የሚባልበት መሰረታዊ ምክንያት ይሄ ነው። የስዬ አብርሃ ቡድን የኢትዮጵያን ህዝብ ሀብትና ደም መከታ አድርጎ ኤርትራ በመደምሰስ አሻንጉሊት መንግስት ለመመስረት ሲያስብ ሌሎች አላማዎችን ለማሳካትም ጭምር ነበር። ህዳጣኑ ህዉሃት ከትግራይ ውጭ ያለው የኢትዮጵያ ህዝብ መግዛት ካቃተውና ህዝባዊ ማዕበሉ ካናወጠው ያለ ኤርትራ ስጋት “ነፃ የትግራይ ሪፐብሊክ” መመስረት ይችላል። የስዬ ቡድን ኤርትራ ላይ ለራሱ ተጠሪ የሆነ አሻንጉሊት መንግስት መመስረት አለመቻሉ በክፉ ጊዜ መጠጊያ የምትሆነውን “ሪፐብሊክ ትግራይ” የመመስረት ራዕይ ተጨናገፈበት። በተለይ በአሁን ሰዓት የኢትዮጵያ ህዝብ ልጆቹን በመገብሩ ቁጭት ላይ የወደቀ መሆኑና ከዚህ በኋላ ጋሻነቱ ባከተመበት ሁኔታ ከኤርትራ ጋር ጦርነት መግጠም ማለት የህዉሃት ፍፃሜ መሆኑ አይቀርም። በሌላ በኩል ጓድ መለስ በስልጣን ለመቆየት ካለው ጥማት በመነሳት ጦርነቱ ሊገፋበት አለመቻሉ እዛው ሳለ የትግራይን ነፃ መንግስት ህልም ባጭሩ የቀጨ ሆኗል። ይህ በመሆኑ ምክንያት በህዉሃት/ኤህአዴግ ህገ-መንግስት ውስጥ የሰፈረው አንቀጽ 39 ከህዉሃትና ትግራይ ህዝብ አኳያ ከወረቀት አንበሳነት የዘለለ አይሆንም። የህዉሃት አፈጣጠር መነሻ የሆነው “የትግራይ ነፃ ሪፐብሊክ” መመስረት እውን ሊሆን የሚችለው ሁለት መሰረታዊ ጉዳዮች ሲሟሉ ብቻ ነው። አንደኛው ወልቃይት፣ ጠገዴ፣ ጠለምት….. የመሳሰሉ መሬቶችን ለባለቤታቸው ሲመልሱ ይሆናል። ሁለተኛው ኤርትራ ላይ (Eriteria-Factor) ዳግም ጦርነት በመክፈትና ኤርትራን ወደ ዳግም ሱማሊያ መውሰድ፤ ከተቻለም ለህዉሃት ተጠሪ የሆነ አሻንጉሊት መንግስት በመመስረት በተራዘመ ጊዜ በኮንፌደሬሽን መዋሃድ። የወልቃይት፣ ጠገዴ፣ ጠለምትና ሌሎች ቀድሞ በትግራይ ክልል ያልነበሩ ቦታዎች ወደ ቀድሞ ቦታቸው ይመለሳል የሚለው ጥያቄ “በህዉሃት መቃብር” ላይ ብቻ የሚፈፀም ነው። ለዚህም ነው ከየትኛውም የኢትዮጵያ ቦታዎች በበለጠ ሁኔታ እነዚህ አካባቢዎች “የትግሉ  ማዕከል” ናቸው የተባለበት ምክንያት። ኤርትራን በጦር ገጥሞ ለህዉሃት ተገዢ የሆነ አሻንጉሊት መንግስት በአስመራ እናቋቁማለን የሚለውም ፍላጎት ያስቀና የደቀቀ ተደርጎ ባይወሰድም ወደ ዜሮ የቀረበ እድል (Probability) ተደርጎ ሊወሰድ የሚችል ነው።

 

እርግጥ ሌሎች ህዉሃትን ለሁለት የሰነጠቁ እንጭፍጫፊ ምክንያቶች እዚህ ላይ ሊጨመሩ የሚችሉበት ሁኔታ መኖሩ እሙን ነው። የህዉሃት የፍጥረቱ የመጨረሻ ግብ ከመኮላሸቱ ጎ ለጎን የዘረጋው ስርአት ባህሪና የውስጠ- ድርጅቱ ሁኔታ ለመሰነጣጠቁ ምክንያት ነው። ህውሃት የዘረጋው ስርአት የፓርቲውን የበላይነትና የትግራይን የተለየ ተጠቃሚነት ዝርፊያ (ሙስና) አንዱ መለያ ባህሪው ነው። መንግስት እንደመሆኑ መጠን ወረራና ዝርፊያው “መንግስታዊ” መሆኑ አይቀርም። “መንግስታዊ ሌብነት”…. “መንግስታዊ ዝርፊያ”…. “መንግስታዊ ሙስና”…. “መንግስታዊ ውንብድና!”…. በመሆኑም የህዉሃት አንዱ መሰረታዊ መለያ ባህሪ በአዋጅ፣ በህግ፣ በመመሪያ የሚፈፅም የቡድን ዝርፊያ (“መንግስታዊ ሙስና”) ነው። ህዉሃት ገና ከጠዋቱ ቁልፍ ቁልፍ የሆኑ የመንግስትና ድርጅታዊ የስልጣን ቦታዎችን በቁጥጥር ስር ያዋለው በዚህ ምክንያት ነበር። ጠቅላይ ሚኒስትር፣ ውጭ ጉዳይ፣ መከላከያ፣ ደህንነት፣ ፖሊስ፣ ሚዲያ፣ የድርጅት ቢሮ፣ የክልሎች ሞግዚት በመሆን አይናቸውን በጨው ያጠቡት ለዚህ ነው።

ይህም ሆኖ የህዉሃት ስርአት በትግራይ ህዝብና ልሂቃን ዘንድ ያለው አረዳድ ከሌላው አካባቢ ጋር ተመሳሳይ አይደለም። አሁን ባለው ነባራዊ እውነታ ከትግራይ ህዝብ የወጡት ህዉሓቶች በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ ፈላጭ ቆራጭ በሆኑበት፤ ገዳዩ አሳሪው ገራፊውና መርማሪው እነሱ በሆኑበት፤ የመንግስት ስልጣንን በመጠቀም ከፍተኛ የኢኮኖሚ አቅም በገነቡበት፤ በትግራይ ውስጥ ታይቶ በማይታወቅና ኢ-ፍትሃዊ በሆነ መንገድ እልፍ አእላፍ ፋብሪካና የኢኮኖሚ አውታሮች በተገነቡበት፤ በጠብታ ኢኮኖሚ መልኩ በትግራይ ክልል የተገነቡት፤ መሰረተ ልማቶችና ማህበራዊ ፍትህ ማምጫ ተቋማት….. ወዘተ በፍጥነት ወደ ህዝባዊ እምቢተኝነቱ ሊቀላቀላቸው አይችልም። ራሳችንን ማምሸት ካልፈለግን በስተቀር የትግራይ ህዝብ በህዉሃት አገዛዝና አፈና ተማሮ ሊሆን ይችላል እንጂ “አዲስ ስርአት” ለመቀበል ዝግጁነቱ አይታይም። የህዉሃት አገዛዝ በፓርቲ መዋቅሩ አማካኝነት የሚፈጥረው ጭቆና፣ የዘመድ አዝማድ አድሎአዊ አሰራር፣ ኋላቀርነት፣ “አህያ ቢራገጥ” የሚመስል አይነት ቂም በቀል፣… አሰልቺ ስብሰባዎች እና መዋጮ….. ወዘተ የትግራይን ህዝብ ሊያስመረምረው ይዝል ይሆናል እንጂ ለስር-ነቀል ለውጥ የተዘጋጀ አይደለም። ግፋ ቢል ከአጭር ጊዜ አኳያ “ላም እሳት ወለደች” ከሚለው ብሂል የሚርቅ አይደለም። ይህ የብዙሃኑ የትግራይ ተወላጅ ፍላጎት አድርገን ልንወስደው የምንችል ነው።

 

 

ኢትዮጵያውያን ወጣቶችን በጅምላ ማሰር፣ መሰወር፣ በግፍ መግደል፣ ማሰቃየት ለዚች አገር መፍትሄ አይሆንም!

$
0
0

elias-daniel

ኢትዮጵያውያን ወጣቶችን በጅምላ ማሰር፣ መሰወር፣ በግፍ መግደል፣ ማሰቃየት ለዚች አገር መፍትሄ አይሆንም!

በኢትዮጵያውያን ላይም የጦርነት አዋጅ ማወጅ ምንም ጠብ የሚል ፋይዳ አያስገኝም!

ጭቆናን፣ አፈናን፣ ግፍን፣ የዘር ማፅዳት እርምጃን እንቃወማለን – ሁሌም!


የሙታን ድምፅ ይጣራል? –ዴሬ አይሣ፤ አርባ ምንጭ ፤ኢትዮጵያ

$
0
0

 

59cbcc0b93dc457ea0f6f5000f4fef1d_18የመቶ አለቃ ጳዉሎስ ቦጋለ “የሕዝብ ምጥ” በሚል ካናዳ ሆነ የጻፈውን  Ethiomedia ላይ አነበበኩ። ጽሁፉ ረዥም ነው። መዝጊያው ላይ “የዘበዘብኩት” ይላል። እውነትነው! ስለምንና ስለማን  እንደጻፈ እንኳን እኔ ራሱም የተረዳው አይመስለኝም።ጳዎሎስ ቦጋለ መዘብዘቡ ሳይሆን ደፍሮ መጻፉ ገረመኝ! ተርቱ “ ጅብ የማያውቁት አገር ሄዶ ቁርበት አንጥፉልኝ አለ!” ነበር። የዛሬ ጅብ የሚያውቁት አገርም ሄዶ ቁርበት አንጥፉልኝ ማለት ቻለ። በዛሬ መገናኛ ካናዳ ከኢትዮጵያ የአንድ ቀን መንገድ ነው። በማህበራዊ ገጽ (Social Media,Internet) የደቂቃ መንገድ ነው። ስለዚህ ጳዉሎስ ቦጋለ የሚኖርበት ካናዳ  “የማያውቁት አገር” አይደለም።

የጳውሎስ ቦጋለ “ደፍሮ መጽፉ ገርመኝ!” ያልኩት ሌላ ተረት አስታወሰኝ። “የአቦን ስለት የበላ ያስለፈልፈዋል!” ሲባል “የት አለ እኔ የለፈለፍኩት!”አለ የሚባለውን። ድፍረቱ ገረመኝ ያልኩትን በሁለት ማስረጃ ለማስረዳት እሞክራለሁ። አንደኛው ከራሱ ከጳውሎስ አንደበት የስማሁትና ሁለተኛው በዚሁ በEthio Media  ላይ የያዛሬ ሁለት አመት ገደማ (February 18, 2015 ) ሽመልስ አበበ የጻፈውን በከፊል እዚህ በመለጠፍ ነው።

                                                  *

1.በዘመን ደርግ ፤በ1960ዎቹ ውስጥ ጳውሎስ ቦጋለ የጋሞ ጎፋ ክፍለ ሐገር ምክትል ዋና አስተዳዳሪ ነበር።። ሰው- በላው የደርግ አባል ሻለቃ ለአሊ ሙሳ አርባ ምንጭ መጣ።  በመቶ አለቃ ጳዎሎስ አዘጋጅነት የ11 የጎፋና የገለብና ሐመር ባኮ አውርጃ ነፍጠኞች ስም  በወቅቱ “አብዮታዊ እርምጃ!” ለሚባለው  ለአሊ ሙሳ ቀርበለት። ዋና አስተዳዳሪው የኦሮሞ ነጻ አውጭ ድርጅት አባል የሆነው መኮንን ገላን ነበር። ጳውሎስ  አቀረበ ያልኩት መኮንን ክፍለ ሐገሩንና ማን ምን እንደሆነ አያውቅምና  ተባባሪ እንጅ ጠንሳሽ ሊሆን አይችልም በሚል ነው። ከነዚህ 11 ስዎች ውስጥ አንዱ ዳኛቸው ከጥቂት አመታት በፊት በወ ቅቱ ለነበረው  የንጉሱ ፓርላማ ከጳውሎስ ጋር የተወዳደር ሰው ነበር። የግል ቂም በቀል ነበራቸው ይባላል።

በቀረበው መሠረት ሻለቃ አሊ ሙሳ “አብዮታዊ ውሳኔ!” አሳለፈ። “አብዮታዊ እርምጃ!” ማለት ይረሸኑ ማለት ነዉ።ብዙ ባለስልጣናት የነበርቡት ስብሰባ ስለነበር ውስኔው ወዲያውን አርባ ምንጭ ናኜ። ትልቅ ድንጋጤና መሸበረም ፈጠረ። “ማነው ተረኛው?” የሚለው በሁሉም ዘንድ ጭንቀትን ፈጠረ። ከተሰበሰቡት ባለስልጣናት አንዱ “እኔ እዚህ ውስጥ የለሁበትም!” ብሎ ስብሰባውን ረገጦ እንደወጣም ተወራ። ሒሊናውን እንጅ 11ዱን ሰዎች አላዳነም።የግለስቡን ስም እዚህ ማንሳት ለጊዜው አስፈላጊ አልመስለኝም።

11 “አብዮታዊ እርምጃ!” የተወሰነባቸው ሰዎች ሰዎች ጎፋ አውራጃ ዋና ከተማ የላ-ሳውላ በእስራት ላይ ነበሩ። በነጋታው ማታ ተረሸኑ። መረሽናቸው ሳይሆን ግድያው እንዴትና ማን አንደፈጸመው መስማቱ የበለጠ የሚዘገንን ነበር። 11ንም ግድያውን( መረሸኑን) የፈጸመው የመቶ አለቃ ጳውሎስ ቦጋለ ነበር። ይህንን የሰማሁት ከራሱ ከጳውሎስ አንደበት ነበር።

“አብዮታዊዊ  ውሳኔ!” በአሊ ሙሳ በተሰጠ ማግስት የመቶ አለቃ ጳውሎስ ቦጋለ በአውሮፕላን ወደየላ-ሳውላ በረረ ።ይህን የሚነግረን ጳውሎስ ነበር። ድርጊቱ ከተፈጸመ በኋላ በሁለተናኛው ቀን አርባ ምንጭ በቀለ ሞላ ሆቴል ጀርባ ፤ወደሐይቆቹና የእግዜር ድልድይ ፊቱን ያዞረው  ጉብታ ላይ ከጓደኞቼ ጋር ቢራ ስንጠጣ የመቶ አለቃ ጳውሎስ መቶ ተቀላቅለን። ወሬውን ማን እንዳነሳው በደንብ አላስታውስም ። ጳውሎስ ሳውላ ግድያው እንዴት እንደተፈጸመ ያወጋን ጀመርን። ያምስታውሰው  “ ሳውላ  ቀን ደርስኩ.. ከማውቃቸው ሰዎች ጋር ሆነን ስንቀመቀም ሞቅ ብሎኝ አመሸን። ከምሸቱ  ሁለት ሰአት ገደማ ወደወህኒ ቤት ሔድን። እስረኞቹ የፍጥኝ ታስረው መጡ። ግርግዳ አስደግፏቸው አለኩ። ከዚያ ኡዚያን አውጥቼ ተራ በትራ አርከፍኩባቸው። ግማሹን በደርቱ፤ሌላው ጭንቅላቱን ፤..የልፍለፋሉ ..ይናዘዛሉ ..ልጆቼን ሳላስድግ … ሳልናዘዘ.. ቤተሰቤን ሳልስናበት ። የደሙ ፍንጣሪ ልብሴን አበላሸው …”  የጦር ሜዳ ፊልም የሚያወራ ነበር የሚመስለው። ዜማ አይኑረው እንጅ ፉከራና ቀረርቶ ይመስል ነበር። የዚያን ቀን የደነገጥኩትን ያክል  ከዚያ በፊትም ከዚያ ወዲህም ደንግጨ አላውቅም።

                                                  *

  1. አሁን ደግሞ ሽመልስ አበበ በ Ethiomedia ላይ February 18, 2015 ከጻፈው ከዚህ ጋር ተዛማጅነት አለው ብዬ ያሰብኩትን ከዚህ በታች አቀርባለህ

“…..እ. ኢ. አ. በ1969 ዓ. ም. በአንድ ወቅት የአርባ ምንጭ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መማሪያ ክፍሎች ዴስኮች ላይ ለእያንዳንዱ ተማሪ ተብሎ በእጅ የተጻፉ የኢሕአፓ ወረቀቶች ተበትነዉ ነበር። ክፍል ስገባ ወረቀቱን አነበብኩ። ወረቀቱ የተሞላዉ በኢህአፓ መፈክሮች ነዉ። እያንዳንዱም ተማሪ አንብቦት ዝም ብሏል። ትምህርትም ተጀምሮ ሳለ የአርባ ምንጭ ወረዳ ፖሊስ ጣቢአ አዛዥ የነበረ ሻምበል ተስፋዬ የሚባል ከጠቋሚ ተማሪዎች ጋር በመሆን በየክፍሉ እየዞረ ማን ነዉ ወረቀት የበተነዉ እያለ ይጮህ ነበር።እኔ የነበርኩበት ክፍልም መጥቶ ጮኸብን። ብዙ ተማሪዎች ክፍል ለቅቀዉ ሲወጡ እኛም ወጣን። ብዙ ጠቋሚ ተማሪዎች በቦክስ ተመቱ። ቁጥሩ አንድ መቶ የሚሆን ማስ የሚባል (ፈረንሳይ የተሰራ አስር ጥይት ጎራሽ) ግማሽ አዉቶማቲክ ጠብመንጃ የታጠቀ የፈጥኖ ደራሽ ሀይል ትምህርት ቤቱን ከበበ። በዚህን ጊዜ ነበር አቶ አሰፋ ጫቦ ወደ ትምህርት ቤታችን የመጡት።

አቶ አሰፋ በጉርድ ላንድሮቨር ሲመጡ ተማሪዎች አሰገቧቸዉ ብለዉ ሲጮሁ ዋና መግቢያዉን በር ይጠብቁ የነበሩት ተማሪዎች አስገቧቸዉ። ከዚያም ሰንደቅ አላማ የሚከበርበት ቦታ መኪናዉን አቁመዉ ከመኪና ሲወጡ ተማሪዎች ከበቧቸዉ። ከዚያም ተማሪዎች ጪኸታቸዉን ማሰማት ጀመሩ። አቶ አሰፋ የላንድሮቨሩ ሞተር ኮፈን ላይ ቆመዉ ሳለ የድምጽ ማጉያ ተሰጥቶአቸዉ ከተማሪዎች ጥያቄ መቀበል ጀመሩ። ከዚያም መልስ መስጠት ጀመሩ። ተማሪዎች በጥሞና አዳመጧቸዉ። እርሳቸዉም “…ይህቺ የዴሞ ቅስቀሳ ነች። ትምህርታችሁን ብትከታተሉ ይበልጥ ትጠቀማላችሁ…” ብለዉ ተናገሩ። ሌሎች መልሶችም ባያረኩን እንኳ እሳቸዉ ምልስ ሊሰጡ እንደማይችሉ ተማሪዎች የተረዱትም ይመስለኛል። በቦክስ የተመቱና የደሙ ተማሪዎች በአምቡላንስ ወደ ሆሲፒታል ተላኩ። ጥቃቱን የፈጸሙ ተማሪዎች ከተጠያቂነት እንደማይድኑ አቶ አሰፋ ማሳሰቢያ ሰጡ። ይህ እየሆነ ሳለ የመቶ አለቃ ጳዉሎስ ቦጋለ መጥቶ አቶ አሰፋ እንዲናገር እድል ሲሰጠዉ ድምጽ ማጉያዉን ተቀበሎ መደንፋት ጀመረ። “…የአድሀሪያን ልጆች የሬሳ ሳጥን በሚያክል አገልግል ፍትፍትና ጭኮ እየተላከላቸዉ ተንደላቅቀዉ እየተማሩ የጭቁን ልጆች እንዳይማሩ ለማድረግ የተጠነሰሰ ሴራ ነዉ…” እያለ ደነፋ። ብዙ ዛቻዎችንም ዛተ። ከዚያም አቶ አሰፋ ከመቶ አለቃ ጳዉሎስ ጋር ለጥቂት ደቂቃዎች ተነጋገረ። የመቶ አለቃ ጳዉሎስ እየተቆጨ ሲናገር እንደነበር ታዘብኩ። ኮሎኔል ተስፋዬ የሚባል የፈጥኖ ደራሽ ሀይሉን መርቶ የመጣዉ ወደነርሱ ጠጋ ብሎ የነገሩትን ሰምቶ ሄደ። ከዚያም አቶ አሰፋ ለዚያኑ ቀን ትምህርት እንደሌለና ወደ ቤታችን እንድንሄድ ነገሩን። እኛም ወደ ቤት ስንሄድ የታዘብኩት ነገር ቢኖር የመቶ አለቃ ጳዉሎስ ቦጋለ ከአቶ አሰፋ ጋር ሲጨቃጨቅ እንደነበር ነዉ። በወቅቱ ከጓደኞቼ ጋር ስንነጋገር የደረስንበት መደምደሚያ ቢኖር የመቶ አለቃ ጳዉሎስ እርምጃ ለመዉሰድ ፈልጎ በአቶ አሰፋ እምቢተኝነትና ተጽእኖ ደም ላይፈስ እንዳልቻለ ነዉ። በወቅቱ ቁጥሩ አንድ መቶ የሚሆነዉ የፈጥኖ ደራሽ ሀይል የግድያ ትእዛዝ ቢሰጠዉ ኖሮ ምን ያህል ተማሪ እንደሚሞት መገመት አያዳግትም. በተማሪዎችም ዘንድ አቶ አሰፋ ክብር ሊያገኙም ችለዋል ይህችን ዉለታ ለተማሪዎች ስለዋሉ።

ከአቶ አሰፋ ጋር በርእዮተ አለም አመለካከት ብለያይም አንኳ በእርሳቸዉ ብርታት ከሞት ልድን ችያለሁ። በወቅቱ ከከበቡን ፈጥኖ ደራሾች ቢያንስ ወደ አስር የሚሆኑትን አዉቃቸዋለሁ። ተማሪዎች የነበሩ ናቸዉ። በሌላ ወቅት አግኝቼ ስጠይቃቸዉ በአቶ አሰፋ እምቢተኝነት የመቶ አለቃ ጳዉሎስ ቦጋለ ትእዛዝ ለመስጠት እንዳልፈለገ አዛዣቸዉ የነበረዉ ኮሎኔል ተስፋዬ እንደነገራቸዉ አጫወቱኝ። ትእዛዝ ቢሰጣቸዉ ኖሮ እኔንም ሊገድሉ እንደሚችሉ ነገሩኝ። እኔም የህችን የአቶ አሰፋን ዉለታ ሁል ጊዜ እንዳስታዉስ አደረገኝ። አቶ አሰፋን ወድጄ አላዉቅም። ግን ይህ ዉለታቸዉ እንዳከብራቸዉ አድሮጎኛል።

ብዙ ሰዎችን አስገድለዋል የሚል ክስና ስሞታ በተደረጉት ትችቶች ዉስጥ ተካትተዋል። አርባ ምንጭ ዉስጥ የተደረጉት ግርፊያዎች ናቸዉ የኢሕአፓን አባላትና ደጋፊዎች ለማጋለጥ ተብሎ። ፋሺስቱ አሊ ሙሳ በገዛ እጁ የገደላቸዉ አተ ተፈሪ (የእኔ ዘመድ የሆነችዉ አየለች ማመጫ ባለቤት)፣ ክፈተዉ (የአጎቴ ባለቤት ወንድም)፣ እና ኑሩ (አቶ አሰፋ ሲታሰሩ በእርሳቸዉ ምትክ የተመደበዉ) ሲሆኑ አርባ ምንጭ ዉስጥ ምንም የፖለቲካ ግድያ አልተካሄደም። አንድም የኢሕአፓ አባል አልተገደለም። ግርፋት ግን ተካሂዷል። በጎፋ አዉራጃ ዋና ከተማ ሳዉላ ከተማ የመቶ አለቃ ጳዉሎስ ቦጋለ ፊዉዳሎች ናቸዉ ብሎ የረሸናቸዉ ጥቂት ግለሰቦች ናቸዉ። የገለብና ሀመር ባኮ አዉራጃ ዋና ከተማ ዉስጥ አንድ የጊዶሌ ተወላጅ የሆነ ካድሬ አንድ ነጋዴ ገድሏል። እ. ኢ. አ. በነሐሴ ወር 1976 ዓ. ም. (August 1984 G. C.) ለትምህርት ኢትዮጵያን ለቅቄ እስከምወጣ ድረስ እዚያዉ ጋሞ ጎፋ የኖርኩ ስለሆነ ሁኔታዎችን ጠንቅቄ አዉቃለሁ። በአቶ አሰፋ ላይ የተደረገዉ አሳዛኝ ትችት ከእዉነት የራቀ መሆኑ በጣም አሳዘነኝ። ጸሀፊዎቹና ተቺዎቹ ከተባራሪ ወሬ የቀሰሙትን ነገር እንደ እዉነታ አድርገዉ ማቅረባቸዉ ዋጋ ቢስነቱን ከማጋለጥ በስተቀር የሚያመጣዉ ነገር ያለ አይመስለኝም። አቶ አሰፋ ቢጠየቁም እንኳ በኢሕአፓነት ተጠርጥረዉና ታስረዉ ለተገረፉት እንጂ በአስገዳይነት አይደለም። ብዙ ተማሪዎች በኢሕአፓነት ተጠርጥረዉ በተለያዩ ቦታዎች ታስረዉና ተገርፈዉ ወደ ሰላማዊ ኑሮና ትምህርት እንዲመለሱ ተደርጓል። ግድያ እንዳይካሄድ ካድሬዎች እንኳ አቶ አሰፋን ያሙ የነበረ ለመሆኑ ሲነገር ሰምቻለሁ። አቶ አሰፋ ኢሕአፓዎች እንዳይገደሉ አድርገዋል። ጋሞ ጎፋ ዉስጥ ባጠቃላይ እስራትና ግርፊያ ተካሄደ እንጂ የፖለቲካ ግድያ አልተካሄደም። ይህ ደግሞ በአዲሰ አበባና ሌሎች ከተሞች አንዳንድ የቀበሌ ሊቀመናብርት በቀይ ሽብር ወቅት ወጣቶች እንዳይገደሉባቸዉ ያስሯቸዉና ይገርፏቸዉ ከነበረዉ በምንም ተአምር አይለይም።

ኢሕአፓዎች ያደረጉትስ የከተማ ቃፊር የግድያ ዘመቻ እና በመካከላቸዉ በነበረዉ የፖለቲካ መከፋፈል እርስ በእርስ የተጋደሉት፤ እንዲሁም ወጣቱን ያስጨረሱት ተረሳና የአቶ አሰፋ ድርጊት ጎልቶ ታይቶ ነዉ ወይ እንዲህ አይነቱ ትችት የተደረገዉ? ትችት በትክክል መረጃ ተይዞ ሲቀርብ ያምራል። ያለበለዚያ ቂም መወጣጫ ወይም ለፖለቲካ ፍጆታ ይዉላል። ደርግም፣ ኢሕአፓም፣ መኢሶንም፣ ወያኔም ሆን ማንም ድርጅትም ሆነ ግለሰብ ከተጠያቂነት አይድንም።

ኢትዮጵያ ለሁላችንም እኩል እናት አገር ነች። ማንም ከማንም አይበልጥም። የበደሏት፣ የገደሏትና የሞቱላትም እንዲሁ አሉ። እያንዳንዱ ትዉልድ የራሱ የሆነ ባህርይ እንዳለዉ ሁሉ ለቀጣዩ ትዉልድ የሚያስተላልፈዉ ትምህርት ገንቢ ሀሳብና ራእይ ያለዉ ቢሆን ይመረጣል። ካልሆነም ደግሞ የታሪክ ተወቃሽ ሆኖ ይቀራል። አገር በቂም በቀል የሚመራ መሆን የለበትም። ታሪክም ቢሆን የሚጻፈዉ በቂም በቀል አይደለም። ወቀሳ፣ ትችትና ሂስ ገንቢ የሚሆኑት አግባብ ባለዉ ሁኔታ ሲፈጸሙ ነዉ። ታሪክም እንዳይወቅሰን ደግሞ ብናስብበት የበለጠ ጠቃሚነት አለዉ ብዬ አምናለሁ።

ሺመልስ አበበ shimelisabebe@gmail.com

*

ይህ በሆነ በሶስተኛው ወር ይሁን ጳውሎስ ቦጋለ ከምክትል አስተዳዳሪነቱ ተነሳ። ድርጊቱ ተደርሶበት በቁጥጥር ስር ውሏል የሚል ወሬ ናኝቶ ነበር። በቁጥጥር ስር ሳይሆን ንግድ ሚኒስቴር መዝገብ ቤት መደቡት። ከዚያም ዛሬ ነገ ቁጥጥር ስር ይውላል የሚል ወሬ ነበር። ጳውሎስም አመኖበት  በቁሙ የሚቃዥ ሁኖ ነበር ተብሎ ሲወራ እስማለሁ። ከዚያ ለማምለጥ አንድ የሚያውቀውን ሰው ተማጽኖ ለፖለቲካ ትምህርት ኩባ ተላከ። ለዚያ ለመሔድ የነበረው ቀዳዳ በወቅቱ ከነበሩት የፖለቲካ ድርጅቶች የአንዱ አባል መሆን ነበር። ኩባ  አንድ አመት ተኩል ቆይቶ ወደኢትዮጵያ ሲመለስ የሰደድ አባል ሁኖ ተመለሰ።  ይህ ደግሞ አዲስ አበባ እንደገባ  ሌላ ችግር ፈጠረበት። የሁለት ድርጅት አባል ሆኖ መገኘት በወቅቱ ሲበዛ ለሞት ሲያንስ ለእስራት የሚያበቃ ነበር። ሰደደ የነመንግስቱ ኃይለ ማርያም ፓርቲ መሆኑ ነው። በፖሊስነቱ የሚያውቀው፤የሰደድ አመራር አባል የነበረው  ሻለቃ ጌታቸው አግዴ ከዚህ ማጥ ውስጥ አስወጣው ሲባል ሰመቻለሁ።

ይህ ነው የሚባል  ስራም  ሳያገኝ ወያኔ ገባ። ወያኔ እንደገባ ሊጠጋቸው መንገድ በመፈላለግ ላይ እንዳለ ይህንን ኢሰብዐዊ ድርጊቱን ደርሱበትና በቁጥጥር ስር ሊያውሉት ሲፈልጉ በጅቡቲ በኩል ሾልኮ ካናዳ ገባ ተባለ። የሰማሁት ይህንን ያክል ነው እንጅ በተለየ ያጣራሁት አልነበረም። አሁን ካናዳ ሁኖ ለኢትዮጵያ ሕዝብ  ተቆርቋሪ ሁኖ “የሕዝብ ድምጽ” ብሎ  ጻፈ።እኒዚያ የረፈራፋቸው  ሰዎች የህዝብ አካል አልነበሩም? አርባ  ምንጭ ሁለተኛና ደርጃ ሊያስፈጃቸው የነበሩት   ተማሪዎች ሕዝብ ቁጥር ውስጥ አይገቡም? የሕዝብ ትርጉም ትላንት፤ተትላንት ወዲያ፤ ዛሬ፤ ነገ፤ ኢትዮጵያ ይሁን ካናዳ እንደ አመችነቱ የሚለዋወጥ ተለዋዋጭ ትርጉም አለው?  ፀፀት የሚሉት፤መሰቅጠጥ የሚሉት አንዳንዱ ቤት፤ጳውሎስ ቦጋለ ቤት  ሞቶ ቀበረ?አንድ ልዩነቱ ቢኖር፣ጳውሎስ ቦጋለ ሲያመልጥ  ሻለቃ አሊ ሙሳ ግን “የቁርጡ ቀን ሲመጣ” የገዛ ሹጉጡን ጠጥቶ ሞተ ! ይገርመኛል!

የመቶ አለቃ ጳውሎስ ቦጋለ “የሕዝብ ምጥ” በሚለው ጽሁፉ መግቢያ አካባቢ “አስጨናቂው ምጥ አገርንና ሕዝብን ከገጠማቸው አስከፊ አስተዳደር ለመገላገል ..”ይላል። ወደማጠቃለያው ላይ ደግሞ “እንግዲህ ለብዙ አመታት አምቄው የኖረውን እንዳለ ዘረገፍኩት” ይላል ። ጳውሎስ ንዳለ ዘርገፍኩት ማለቱን እንኳን እኔ ራሱም የሚያምነው አልመስለኝም።ጎፋ የላ-ሳውላ በኡዚ ያጨዳቸው 11 ሰዎች ጉዳይ አላነሳም። ይህ በአደባባይ፤ሳውላ ወህኒ ቤት፤ አገር ሲያየው የፈጸመው ነበር። ጳውሎስ ቢረሳው፤ቢዘነጋው፤ ወይም ሊረሳው ሊዘነጋው ቢፈልግም እኒያ  አይን ምስክር የነበሩ ሊረሱትና ሊዘነጉት የሚችሉት አይመስለኝም። እነዚህ 11 ስዎች እንደማንኛችንም ባል፤አባት፤ ወንድም፤ አጎት፤አክስት፣ጎሮቤት፣ዘመድ-አዝማድ አገር የሚያውቃቸው ዘመድ አዝማድ ፣ከሁሉም በላይ ልጆች ያላቸው ነበሩና ትላንትም፤ዛሬም ነገም ሊረሱ የሚችሉ አይመስለኝም።

የጳውሎስ ቦጋለ “የሕዝም ምጥ” ጽሁፍ መደመደሚያው “በቅርቡ የምለው አለኝ!” ይላል። ይህንን ወድጀዋለሁ! በቅርቡ ይህንን አስቃቂ ግፍ ታሪክ ይነገራናል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ። እኔም ሆንኩ ሌላው ከጳውሎስ ቦጋለ መስማት የምንፈልገው አንዳች ነገር ቢኖር የዚህን የየላ-ሳውላ ወህኒወኔ ቤት ግድያ ታሪክ ብቻ ነው።

ወይም አማራጭም አለ።ካናዳ የወንጀለኛና ፤የነፍሰ ገዳይ መሽሸጊያ፤መታጎሪያ ፤መሸፈቻ ጫካ አይደለችም። የአለም አቀፍ ወንጀለኞች ፍርድ ቤት ማቋቋሚያ ስምምነት(International Court of Criminal Justice,ICC )December 18,1998 በ  ፈርማ ተቀብላ  አጽድቃለች። በዚሁ መሠረት በየአገሩ የተሽሸጉ የሰው ዘር አጥፊዎች እየተፈረደባቸው ወህኒ ወረደዋል።  ለሰው  ዘር መዳን የሚሟገቱ ድርጀቶችና ግለሰቦች ተባብረው ማስረጃውን ለካናዳ መንግስት የማቅረብ ጉዳይ እንጅ ጳውሎስ ቦጋለን  ፍትሕ አደባባይ ማድረስ ዛሬ በጣም  ውስብስብ አይመስለኝም።

ጳውሎስ ቦጋለ “በቅርቡ የምለው አለኝ!” የሚለውን ለዚያ ፍርድ ቤት ይንገርና ከዚያ ብንስማው እምርጣለሁ!

 

 

ከሰሞነኛው የፌስ ቡኩ ግብግብ ምን እናስተውላለን? (ከሚ)

$
0
0

facebookከሰሞኑ የፌስቡክ ግብግቦች የማይናቁ የፖለቲካ ግንዛቤዎች ልንቀስም እንችላለን። ባንድ ወገን የወጣቱን የጋለ የሃገር ፍቅር ስሜት ስናስተውል በሌላ ጎኑ ደግሞ ግብግቡ ላይ የተንጸባረቁትን ስሜት የወለዳቸውን ብሶቶች ልብ እንላለን። ወጣቱ የሚጠቀምባቸው የቃላት ሃረጎች ለስላሳ፣ ግብረገባዊ አንዳንዱም አጸያፊ መሆናቸውም የወጣቱን ባህርይ ወይም ጠባይ ልክ ያሳያል። ግብግቡ ከአሜሪካ ምድር ተነስቶ በኢትዮጵያ አድርጎ አረብ አገርንና እስራኤልን ካካለለ በኋላ ተመልሶ አሜሪካ ይገባል። እስኪ ለዚህ ጽሑፍ መነሻ የሚሆኑ አራት ናሙናዎችን (sample) እንመልከት።

እነዚህን ጥቂት ናሙናዎች የምናየው ብሶት ከስሜት ጋር ሲትደባለቅ ሊፈጥር የሚችለውን ሁኔታ በጥቂቱ ለመቃኘት ነው እንጂ በጥልቀት ገብተን የነገር ለኳሹን (protagonist) ወይም ተጻራሪውን (antagonist)ባህርይ በቅጡ ለመመርመርና (assessing character of participants) ጥናታዊ ጽሑፍ ለማቅረብ አይደለም። ሁሉንም ውይይቶች፣ አታካራዎች፣ ሽንቆራዎችና ስድቦች ብንመለከት ሠፊ ግንዛቤዎች ልንቀስም በቻልን ነበር። ከነዚህ ናሙናዎቹ ግን ምናልባት የአመለካከት ልዩነቶችንና የአስተሳሰብ ደረጃዎችን ለመለካት ፍንጭ እናገኝ ይሆናል እንጂ እንደ ጥቅል እይታ (generalization) ልንወስድ አይገባም። ጽሑፉ በተጓዳኝ የማህበራዊ ሜዲያ ሥርዓትን፣ ከግብግቡ ያገኘናቸውን ግንዛቤዎችና የኢሕአዴግን ውስጣዊ ችግር ለመገንዘብ ጥረት ያደርጋል።

አራት ናሙናዎች (Four Samples)

አንዲት ልጅ አማራንና ኦሮሞን “አህዮች፣ ደደቦች” ስትል በስድ ንግግር በመዝለፏ ሳብያ የሁለቱ ታላላቅ ነገድ ስብዕና መነካቱ ያስቆጣቸው በርካታ ወጣቶች የቃላት ጦር ሠብቀው “ሆ” ብለው ተነሱባት። ለዚህች ልጅ መልስ ከሰጡት ወጣቶች መካከል አንዳንዶቹ እውጭ ሃገር ያደጉ የትውልደ ኢትዮጵያውያን ልጆች ናቸው። ምላሹ ምክርና ትምህርት ያዘለ ሲሆን አብዛኛው ግን በዘር ላይ የተመሰረተ ስሜታዊ የአጸፋ ስድብ ነበር። በአጸፋው ስድብ ወቅት በዚህች ልጅ ሰበብ የትግራይ ሕዝብ ስዕብና እንደ ሥጋ ተዘልዝሏል። የትግራይ ሕዝብ መዘለፍ ያስቆጣቸው ሰዎች ማለትም የእሷ ደጋፊዎች ብቅ ማለታቸው ደግሞ ፍልሚያውን ይበልጥ አጧጧፈው።

እዛው አሜሪካ የሚኖር አንድ ተፋላሚ የቃላት ሚሳይል ታጥቆ ብቅ አለ። የወያኔ ደጋፊ የሚላቸውን ሁሉ በመሸንቆጥ የሚታወቀው ይህ ሰው የሚሠነዝረው ስድብ በዓይነት በዓይነት ተደርድረዋል። በተለይም አንዲት ባህር ማዶ አረብ አገር የምትኖረውን የፌስ ቡክ ተሳታፊ “ትግሬ ነኝ” በማለትዋ “ወያኔ ነች” እያለ ካብጠለጠላት በኋላ በሌሎችም እንድትጠላ መንገዱን አመቻችቷል። ይልቁንም እሷነትዋን የሚነካ ብዙ ስድቦች ከወረወረ በኋላ “ገረድ – ሸሌ” ሲል አንቋሿታል።

አረብ አገር የምትኖረዋ ወጣት ፌስቡክን የምትጠቀመው ሌሎች ወገኖቿን ለመርዳትና በሚያጋጥሙ ችግሮች ላይ ተወያይቶ መፍትሄ ለማፈላለግ እንጂ ፖለቲካ ለማራመድ እንዳልሆነ ትናግራለች። ወጣቷ አለባበሷዋ ምናልባት ለብዙዎች የሚስማማ ላይሆን ቢችልም “ትግሬ ነኝ” በማለትዋ ግን በመንግሥት ደጋፊነት መፈረጅዋ ምቾት አልሰጣትም። “ትግሬ ሁሉ ወያኔን አይደግፍም፣ ያ ቢሆን ብዙዎች ለምን ተሰደዱ” የሚል ጥያቄ ካቀረበች በኋላ “ግርድና አያስነውርም፣ ሥራ ክቡር ነው፣ እዛም ያላችሁት (አሜሪካ ማለቷ ነውወንዱ ፈረስ አጥቦ ሴቷ የአሮጊት ዳይፐር ቀይራ ነው ደሞዝ የምታገኙት፣ ስደት የትም ያው ነው” በማለት ስደትን ባጭሩ ቃኝታዋለች። የኦሮሞም ወጣቶች ሊጎነታትሏት ጀምረው “ጃዋርን ለቀቅ አድርጊ” የሚል ማስጠንቀቅያ አዘል ንግግር አድርገዋል። ይህች ወጣት በመጨረሻ “የፈለጉትን በሉ እንጂ የፌስ ቡክ ተሳትፎዬን አላቆምም ኢሕአዴግም ጃዋርም ይዘቅዘቁ” ስትል አቋሟን ግልጽ አድርጋለች።

ሌላኛዋ የፌስ ቡኩ ተፋላሚ በዘለፋ አንጀቷ ያረረ እስራኤል ሃገር የምትኖር ወጣት ስትሆን ይህች ወጣት አማራነቷን እያንጸባረቀች፣ በባህል ቀሚሷ ዘንጣ መጥታ ወያኔ አግዓዚን በዘለፋና ተቃውሞ እሳሩን አብልታ በፋሲል ደሞዝ ቀስቃሽ ዘፈን እስክስታ ወርዳለች። ልጅቷ የዘር ልዩነትን የማትደግፍ ስለመሆኗ ብዙ ጊዜ ተናግራለች። ይህ በእንዲህ እንዳል “በአራት ቀናት ውስጥ ይቅርታ ካልጠየቅሽ ትሞቻለሽ” ሲሉ ባላጋራዎቿ ደብዳቤ ጽፈው እቤቷ ደጃፍ አስቀምጠዋል። “የመይሳው ዘር ነኝ” ያለችው ወጣቷ ተፋላሚ፣ ሞትን እንደማትፈራ ገልጻ እንደውም ከቆመችበት ዓላማ አንዳች እንደማይመልሳት ለወዳጅም ጠላትም አሳውቃለች።

ሥነ ምግባርን ተከትሎ ተሳታፊዎች ያንጸባረቁት መልዕክት ጠቅላይ ይዘት

ሁሉም ነገር ሥርዓት አለው። ሥነ ምግባር ሥርዓትን ይመራል። ማህበራዊ መገናኛም በስነ ምግባር መመራት አለበት። በሁለቱ መካከል ያለውን ዝምድና እንዲሁም ገደብ ማስቀመጡ የዚህ ጽሑፍ ዓላማ አይሁን እንጂ የማህበራዊ ሜዲያ ተጠቃሚዎችን ጠባይና አኳኋን ከመስመሩ እንዳያልፍ ሥነ ምግባር ገደብ ያስቀምጣል።

የችግሩ መንሥኤ ሆናለች የምትባለው ተፋላሚ ወጣት አማራን “አህያ” ኦሮሞን “ደደብ” ስትል ያለመሸማቀቅ ከተናገረች በኋላ ይቅርታ ጠይቃለች። አንድን ሕዝብ ነገዱን አህያ፣ ደደብ፣ ችግራም እያሉ መስደብ ኢትዮጵያዊነትን አያንጸባርቅም። ዘር ወይም ነገድ እግዚአብሄር በንጹህ እጁ የፈጠረው የአምላክ ዕቃ ነው። የሱን እቃ መስደብ እሱን ራሱን መቃወም ነው። ወንድሜን “አህያ”፣ እህቴን “ደደብ”፣ እናቴን “ችጋራም” ብዬ ብሰድብ – እኔስ ማነኝ። የአንድ እውቅ ጸሃፊን አባባል ልዋስና እንዲህ መሳደብ በራስ ላይ እንደ መጸዳዳት አሳፋሪና የሥነ ምግባር ድህነት ነው (to be unethical is absurd)

የአሜሪካ አገር ነዋሪው ተሳታፊ ብዙ ተከታዮች አሉት ነገር ግን ለእርሱ የማይስማሙትን ሰዎች ለመቃወም የሚጠቀምባቸው አነጋገሮችና ስድቦች ወይንም የአነጋገር ለዛዎች ኢትዮጵያዊ ጨዋነትን አያሳይም። አሳሳቅ፣ አነጋገርና አባባሎች ስነምግባራዊ መመርያዎች (social ethical rules) አሏቸው።

የአረብ አገሯ ልጅ ምናልባት ቄንጧን እንድታስተካክል ምክር መለገሱ ጤናማ ቢሆንም “ትግሬ ነኝ” በማለትዋ ልትሰደብ አይገባም። ትግሬ የሆነ ሁሉ በኢሕአዴግ ደጋፊነትም ሊፈረጅ አይገባም። በርካታ ሴት ወጣቶቻችን ሥርዓቱ በፈጠረው የስነ ልቦና ጫናና ሥራ ማጣት የተነሳ ወደ አረብ ሃገሮች በገፍ ተሰደዋል። አረብ አገር ያለችን እህት “ሸሌ” ብሎ መስደብ እህት ወይም እናት እንደሌለው መሆን ነው። የሃገራችንን ባህላዊ አለባበስንና ሃገራዊ የአነጋገር ዘይቤዎችን ይዞ በሕዝብ ፊት መቅረቡ ያስከብራል። ለተረዳ ሰው በየአጋጣሚዎቹ ኢትዮጵያዊነትን ማንጸባረቅ ብልህነት ነው።

የጎንደሯ ልጅ “ወያኔን እጠላለሁ” በማለትዋና አማራዊ ማንነትዋን በማንጸባረቅዋ የወያኔ ደጋፊ ነኝ ከሚሉ ሰዎች ማስፈራርያና ዛቻ ደርሷታል። ይህም ተገቢ አይደለም ምክንያቱም ወያኔን እንደ ፖለቲካ ሥርዓት የጠላችበት የራስዋ ምክንያት አላት። እንግዲህ ትጥቅ ቢኖራቸው ወይንም ሥርዓት ባይኖር ዛቾች በእርስዋ ላይ ምን ሊፈጥሩ እንደሚችሉ ይህን ብቻ በማየት መረዳት እንችላለን።

ስድብና ዘርን፣ ነገድንና ጎሳን ማንቋሸሽ ኋላ ቀር አስተሳሰብ ነው። ተሳትፏችን ለብዙሃኑ ጠቃሚ እንዲሆን ካሰብን የታዳሚውን ፍላጎት ማወቅ (know the audience) ብቻ ሳይሆን ከብዥታ የጠራ (stay away from bias) ጠቃሚና የሚያንጽ መልዕክት ልናስተላልፍለት ይገባናል። በማህበራዊ መገናኛዎች ስንጠቀም የግለሰብን ስብዕና ሆነ ግለሰቡን ሁለንተናዊውን መብቱን መንካት የለብንም (never compromise on privacy)። በተሳትፎ ወቅት ግልጽ ልንሆን (be transparent) ይገባናል። እውነትን መናገርና (speak truth) ሃሳባችንን በዓየር ከመልቀቃችን ወይም ከመጻፋችን በፊት ማሰላሰሉ ተወዳጅና በሳል ያደርገናል(think before you speak or tweet)። መለክቶቻችን ሁልጊዜ ተጽዕኖን ፈጣሪዎች ሊሆኑ ይችላሉ ብለን ከመገመቱ ባሻገርም ( imagine the impact) የሕዝብ ጉዳይ ትልቅ መሆኑን ልንገነዘብ ይገባልና (public perception matters a lot) ንጹህ ሆነን በጨዋ አለባበስ ቢቻል በባህል ልብሳችን ብንቀርብ የብዙዎችን ቀልብ እንስባለን።

አጭር ግንዛቤ

(1)የማህበራዊ መገናኛው ተገልጋዮቹ ወጣቶቹ ሲደጋገፉ ወይንም ሲስማሙ አንዱ አንዱን በእጅጉ ያቆላምጣል። የኔ እናት፣ የኔ ጌታ፣ የኔ ማር፣ ውድድ ነው የማደርግሽ፣ በርቺ የኔ ቆንጆ፣ የኔ ጀግና፣ ስኳርዬ፣ ወለላዬ፣ ወዘተ የመሳሰሉት ማወደሻ ቃላት የተለመዱ ናቸው። በሃሳብ ካልተስማሙ ደግሞ በባህርያቸው ልክ ቅዋሜ ይንጸባረቃል። መልካም ጠባይ ያሏቸው ለተነሳው ሃሳብ ለስላሳ ምክርንና ወቀሳን ወይም ጠቃሚ ሂስን ሲያንጸባርቁ ስሜታቸውን መቆጣጠር የማይችሉት ደግሞ ከግብረገብ ውጭ የሆኑ እጅግ ዘግናኝ፣ ስብዕናንና ዘርን የሚያንቋሽሽ ለመስማት የሚያጸይፍ ስድብ ይሠነዝራሉ። ይህ ሲሆን አንድ ነገር መገንዘብ እንችላለን። ስሜትን አለመቆጣጠርና በችኮላ መናገር ቀላል ያልሆነ ጥፋትና ግጭት ሊያስከትል ይችላል። “ትንሽ ምላጭ አገር ትላጭ” እንደሚባለው ትንሽ ስሜታዊ ዘለፋ የበርካታ ሰዎችን ናላ ታናውጣለች። ጥፋቱም መሪር ነው። በምዕራቡ ዓለም እየተኖረ ሌላ ሃሳብ ያመነጨን ግለሰብ ላይ ጥላቻን ማንጸባረቅ ገና እተሻለው አስተሳሰብ ደረጃ አለመድረስን ያሳያል።

(2)የሃገሪቱን ፖለቲካና ማህበራዊ ጉዳይ በተመለከት የወጣቱ ተሳትፎ እጅግ ጠቃሚ ነው። የፖለቲካ ባህል የሚዳብረው እንዲሁም ፖለቲካው የሁሉንም ወገን ጥቅም አስጠባቂ ሊሆን የሚችለው የመላ ሕዝቡ የውስጥ ስሜት በነጻነት መንጸባረቅ ሲችል ነው። ማህበራዊ መገናኛዎች (Social Media) ለዚህ ክቡር ዓላማ ተግባራዊ መሆን ወሳኙን ክፍል ይይዛሉ። ማህበራዊ መገናኛዎች ከዚህ በተቃራኒ ሲውሉ ደግሞ ብዙ ነገሮች ይበላሻሉ። ይልቁንም የሰው ልጅን ሃሳቡን ሰምቶ አላምጦ በተሻለ ሃሳብ መቃወም ሲገባ ስብዕናን በመንካት የማህበራዊ መገናኛዎችን አገልግሎት ማቃወስ የራስን ማንነት መልሶ ማንቋሸሽ ነው። ኢትዮጵያውያኖች፣ በጣም ጥቂት ካልሆንን በቀር አብዛኛዎቻችን ድሆች ነን። ወይንም ደግሞ ድሆች ዘመዶች አሉን። ሁላችንም የመጣንበት ዘር ወይም ነገድ አለን እንጂ፣ የመጣንበት ዘር ወይም ነገድ ለፈጸመው ጥፋት ሁሉ ተጠያቂ አይደለንም። ሥራ መተዳደርያ ነው። ሥራን ብንንቅ፣ የሰዎችን ሥራ ዝቅተኛ አድርገን ብንመለከት አምላክ ደስ አይለውም። እኛ ኢትዮጵያውያን እጅግ ብዙ የተደበቁ ዓለምን የሚያስደንቁ እሴቶችና ባህሎች እያሉን በተልካሻ ምክንያቶች ለምን እንቆራቆሳለን።

(3)የምዕራቡ ሃገር ወጣቶች የመሰዳደብን ደረጃ ከማለፍም ባሻገር ትዕግስትንና ጥንቃቄን እንደ ዓዕምሮ ቀበቶ ይጠቀሙበታል (high tolerance)። ለዚህም በተሳትፏቸው ጊዜ የሚሰነዝሩት ሃሳቦች ምስክሮች ናቸው። ምዕራብያኖች የሰው ዘር እኩል መሆኑን በመከባበር ያሳያሉ። በምዕራቡ ዓለም ማንኛውም ሥራ ክቡር ነው። ለምሳሌ ቀድሞ ከየሠፈሩ በመኪና ቆሻሻ የሚያነሱት ሰዎች ማለትም «garbage man»የሚባሉት አሁን የሥራውን ክቡርነት ለማሳየት «sanitary engineer» ይባላሉ። የጽዳት ሠራተኞች «building engineer» ይባላሉ። ሥራ ክቡርነቱ ካልታወቀ ዕድገት የለም። አንዳንዶቻችን ታድያ ከድህነት አስተሳሰብ አለመውጣታችን አንዱ ማስረጃ ሥራን መናቃችን ነው። ብንንቀውም ግን ሥራው ለብዙዎቻችን መተዳደርያ ነው።

(4)በአውሮፓ በአንድ ትልቅ መሥሪያ ቤት ውስጥ አብረው የሚሠሩት ሚኒስቴሩና እንግዳ ተቀባይዋ ምሳ ለመብላት ካፌቴርያ ውስጥ እኩል ተሰልፈው ነው የሚስተናገዱት። በምዕራቡ ሃገር ያደጉት የትውልደ ኢትዮጵያውያን ልጆች መልካም እሴቶችን ገና ከልጅነታቸው ስለሚማሩ (value learned as children) በሰው ልጅ እኩልነት ያምናሉ፣ ሲናገሩም፣ ሲራመዱም ሚዛናዊ ናቸው፣ ሥራን ያከብራሉ፣ ሃሳባቸውን ሌላውን በማያስቀይም መንገድ መሰንዘሩን ያውቁበታል። የምዕራብያኑ አብዛኛው ዜጎች ሰውን ማሳዘን አይፈልጉም፣ ሰው እንዲሸማቀቅ አይፈልጉም ይልቁንም ማበረታታትና ለሌላው ቅድሚያ መስጠት ሥርዓቱ ያስጨበጣቸው የእድገት ደረጃዎች ናቸው። በእርግጥ ድህነቱን በማንበርከካቸው ግለሰብ ከግለሰብ የሚቆራቆሱባቸው ምክንያቶች እጅግ ሊጠቡ ችለዋል። ኢሕአዴግ በድህነት ላይ ዘመትኩኝ ቢልም እንኳን በተዘዋዋሪ ድህነቱ የብዙ ሰዎችን በር በማንኳኳቱ ብሶትና ሃዘን የሰዎችን ስሜትን ነክቷል። ሕዝቡ “እምቢ ለሥርዓቱ” ያለው በዚህ ምክንያት ነው። የሰሞኑ የፌስቡክ ግብግብ የዚሁ እምቢተኝነት ነጸብራቅ ነው።

የኢሕአዴግ ችግር

ልማት ዘንቧል”፣ “ሁለት አሃዝ ዕድገት ተመዝግቧል” ቢባልም ኢሕአዴግን የሚቃወሙት፣ በራሱ በኢሕአዴግ ዘመን የተወለዱ ከሃያ አምስት ዓመት በታች የሆኑ ወጣቶች ናቸው። ምናልባት ሠላሳና አርባ ዓመት የሞላቸው ቢኖሩ እንኳን ያን ጊዜ ከአምስት እስከ አስራ አምስት አመት የነበሩ ትናንሽ ልጆች ነበሩ። ወጣቶቹን ልማቱም ዕድገቱም አላመረቃቸውም ማለት ነው። ይህ ጉዳይ እንግዲህ ወደ ፖለቲካዊ ሥነልቦናዊ ፍተሻ ሊያመራን ይችላል ማለት ነው።

ኢሕአዴግ የመነነች መንግሥት ተብላ ትጠራ ከነበረችው አልቤኒያ ርዕዮተ ዓለም ልክፍት ሳይፈወስ ደርግ ድንገት በመውደቁ ምክንያት ከመቅስፈት የከበርቴውን ሥርዓተ ማህበር እንዲቀበል ተደርጎ ተጠመቀ። ይህ ሳይፈልግ የአሜሪካ የጡት ልጅ የሆነው ድርጅት ለሁለት ተቃራኒ ውቃቢዎች መስገድ ግድ ሆነበት። ግትሩ ውቅቢ፣ አልባዊነቱን መተው አይፈልግም። ለስለስ ያለው ውቃቢ ደግሞ ሌሎቹ የሞቱለትን የዲሞክራሲውን መንገድ መከተሉን ቢያንስ በመርህ ደረጃ ይቀበላል። ግትሩ ውቃቢ፣ ተዋግተን ነው ሥልጣኑን የያዝነው የሚለው ወታደራዊ ኃይል ወይንም ጭፍኑ ኮሙኒስታዊው ውቃቢ “ልማታዊ” ነኝ የሚለውን ውቃቢ ይግደራደራል። ነጻና ፍትሃዊ ምርጫ ሊኖር ያልቻለው ጭፍኑ ኮሙኒስታዊው ውቃቢ ሥልጣኑን ለሕዝብ ማስረከብ ሽንፈት መስሎ ስለሚታየው ነው። “ልማታዊው” በከበርቴው ሥርዓት ፍልስፍና እየታገዝኩኝ ሃገሪቱን ወደ እድገት አሸጋግራለሁ የሚለው ውቃቢ በሁለት ተግዳሮቶች ይሰቃያል። አንደኛ፣ የኮሙኒስቶቹ ወታደራዊ ኃይላት ጫና የፈጠረው የፖለቲካ ሙስናና ብልሹው አስተዳደር ማህበራዊ ምጣኔ ኃብታዊውን ሥርዓት ጠምዛዛ (twisted socio-economic structure) እያደረገበት የፖለቲካ ምህዳሩን አጠበበ። ይህ ውቃቢ አድጎ አድጎ “ኮማንድ ፖስት” ሆኗል። ሁለተኛ፣ በልማት ስም መሬት የተሰጣው ባለሃብቶች ብዝበዛን እንጂ ከመሬቱ ላፈናቀሉት ጭቁን ሕዝን የነጻነትና የእድገት ጭላንጭሎች ሆነው አልታዩም። በሃገሪቱ የኃብት ክፍፍሉ (Wealth inequalities) መጠን እጅግ ማደጉ ብሶቱን አኑሮ እምቢተኝነቱን (public disobedience and violence) ባቀጣጠለ ጊዜ ግትሩ ውቃቢ “ኮማንድ ፖስቱ” ላይ ሲንጠለጠል ለስላሳው ውቃቢ “በቅጡ እታደሳለሁ” አለ። ተቃራኒ ውቃቢዎች ርህራሄ ቢስ ያደረጉት ሊለወጥ የማይችለው ኢህአዴግ የውስጥ ችግር ይህን ይመስላል።

ሉላዊነትን ተከትሎ የሚራመደውን ወጣት ለማርካት፣ በሁለቱ ውቃቢዎች የሚዋዥቀው ኢሕአዴግ ማለትም “ኮሙኒስታዊ ውስጡንና ልማታዊ ውጭውን በማምለክ የተጠመደው ኢሕአዴግ”፣ አቅሙ፣ ብስለቱና አስተሳሰቡ ያለው አይመስልም። ለምን?

– ኢሕአዴግ አዲሱንና ብልጭልጩን የከበርቴው ሥርዓት ተግባራዊ ሲያደርግ ሃገሪቱን መዝባሪዎች ተቀራመቷት።

– ሕወሃትኢሕአዴግ ለሥልጣን ያበቁትን ምዕራብያኖቹን ለማስደሰትና እንደልባቸው እንዲፈነጩ ሲያደርግ ነጻና ፍትሃዊ ምርጫ የተጠማው ሕዝብ ብሶት እያደገ ደሃው ዕንባው አልደርቅ አለ።

– ስግብግቦች ደግ በመምሰል የሚለግሱት ርጥባን ብሶትን እንዴት ሊያፍን እንደሚችል ኢሕአዴግ ከከበርቴው ሥርዓት በወሰዳት አነስተኛ ኮርስ ታግዞ ስለ ሊበራል ምጣኔ ኃብት ዘይቤ፣ ልማትና ዲሞክራሲ ያደሰኩራል እንጂ ማንም አይሰማውም።

– ኢሕአዴግ አስተሳሰቡ ከኢትዮጵያ ሕዝን አኗኗርና ስለልቦናዊ አመለካከት ጋር አብሮ አይሄድም።

– ኢሕአዴግ የተከተለው ሥርዓት የመጨረሻ ግብ በገቢና በኃብት እጅግ የተለያዩ መደቦችን እንደሚፈጥር ጥናቶች ይጠቁማሉ። ይልቁንም ይህ አሰራር ሃገሪቱን በትልቅ ዕዳ ውስጥ ዘፍቆ ጥቂቶች ብቻ የብድሩ ተጠቃሚዎች እንዲሆኑ ማድረግና ብዙሃን ግብር ከፋዩን የሚያደኸይ፣ ጥቂቶች ውጭ ሃገር እየተመላለሱ መታከም ሲችሉ ደሃ እናቶች በወሊድ፣ ልጆቻቸው በበሽታ እንዲሞቱ የሚያደርግ የጤና አጠባበቅ መርህን የሚነድፍ ሥርዓት ይደረጃል።

– ፍትህ ለጥቂቶች ብቻ እንድትሆን ሌላውን የሚያፍን ህጎችን የሚያረቁ አድር ባይ ምሁራንን መልምሎ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ኤሌክትሮኒክስ መሥሪያ ቤቶች እየከፈተ ሥልጣን በገፍ በማደል በሕዝብ የሚቀልድ የመሃይማን ሥርዓት ማደርጀት።።

– ባጠቃላይ ርካሽ የሰው ልጅ ጉልበትን መከመርና ለውጭ ባለሃብቶች ማደል፣ ሁሉ አልሆን ብሎት የመረረው ወጣት እንዳይታገል ማፈን አልያም ተሰዶ ባህር እንዲሰምጥ ወይም በምድረበዳ ዘራፊዎች እየተገደለ እንዲያልቅ የሚያደርግ፣ ያልተሰደደው ባንድ ለአምስት እታች በወረደ የስለላ አውታሮች ተጠርንፎ መሰቃየት ሥርዓቱ ያዳበረው ፖለቲካ ነው።

ሌላም ጉድ አለ። የሰሞኑ አመጽም ሆነ በፌስቡኩ ግብግብ ላይ በዋነኛነት የሚንጸባረቀው የዘር ክፍፍል ከየትም አልመጣም። የከተሞች ማደግና መንገዶች መዘርጋት ቅርጻዊ ሲሆን ከላይ በጠቃቀስኳቸው ምክንያቶች የኑሮ ውድነቱና ድህነቱ መቀረፍ አለመቻሉና ውስጣዊ ብሶት ማባባሱ ነባራዊው እውነታ (objective reality) የወለደው ሃቅ (truth) ነው። የችግሩ ዋነኛ መንሥዔ በፈረንጆቹ ግፊት ኢሕአዴግ የሚያራምደው የአፍሪካ አህጉር አሳፋሪው የፖለቲካ ባህል የሆነው የዘር ፖለቲካ የወለደውና ይህንኑ ተከትሎ የመጣው “የማንነት ጥያቄ” ነው። ኢሕአዴግ የሕዝቡን ጥያቄዎች ለማፈን፣ የማንነቱን ጥያቄ ለማርገብና እየጋለ የመጣውን ሕዝባዊ እምቢተኝነት ለመቆጣጠር “የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ” አውጇል። ኢሕአዴግ አዋጁን ተንተርሶ ፌስቡክንና ማህበራዊ ሜዲያዎችን መዝጋቱ እምቢተኝነቱ በራሱ ኅልውና ላይ ሊያደርስ የሚችለውን ጥፋት ገምቶ ነው። ይህ ግን ዘለቄታዊ መፍትሄ አይሆንም። መፍትሄው የሕዝቡን ጥያቄ መመለሱና የማንነቱን ቀውስ መፍታት ነው።

የቱንም ያህል አልሚ ሥራዎች ያከናወኑ፣ በሥልጣን ላይ ያሉ መሪዎች የዘር ፖለቲካን ካራመዱ፣ እንወክለዋለን የሚሉት ጎሳ ወይንም ነገድ በሌሎች ጎሳዎች ወይም ነገዶች ላይወደድ ይችላል። ይህ ስሜት ነው ጀግናውን የትግራይ ሕዝብ እንደ መንግሥት ደጋፊ ያስፈረጀው። እንዲህ ዓይነቱ የዘር አድልዎና “ዘርን እንደ ጋሻ የመጠቀም ፖለቲካ” (Tribe shield politics) አፍሪካን ቁልቁል ያስኬዳት። በደቡብ ሱዳን የሙርቴና (Murte) ኑወር (Nuer) ጎሳዎች መካከል ያለው መቆራቆስ ሙርቴውን የራሱን ነጻ መንግሥት የመመስረት ፍላጎት አሳድሮበታል። ከሰሜኑ የተከፈለችው ደቡብ ሱዳን እንደገና ልትከፈል ነው ማለት ነው። መንግሥት የፍትህ አካላትን እንደማስፈራርያና መጨቆኛ ሲጠቀምባቸው በጎሳዎች መካከል ልዩነቶች ይከሰታሉ። ሩዋንዳና ዚምባብዌ ውስጥ ይህ ሁኔታ ጎልቶ ይታያል። የደቡብ ኡጋንዳ ነዋሪዎች ምጣኔ ኃብቱን መቆጣጠራቸው አኮሊ (Acholi) የሚባሉትን የሰሜኑን ክልል ነዋሪዎች አስከፍቷል። ነባራዊ ሁኔታው (Lord’s Resistence Army Rebel Groups) ለሚባሉት አማጽያን ኃይል መፈጠር ምክንያት በመሆን አለመረጋጋቱን አብሷል። በደቡብ አፍሪካም በፕሬዚዳንት ጃኮብ ዙማ አስተዳደር ውስጥ ከፍተኛውን ቦታ የያዙት የዙሉ ጎሳዎች (Zulu Tribes) ናቸው። ይህም ሌሎቹን የተገፉ ጎሳዎች አስቆጥቷል። እነዚህን በመሳሰሉ ክልላዊና የጎሰኝነት አስተሳሰብ ሳብያ የሚፈጠሩ የኃብት ክፍፍል ልዩነቶች ደም አፋሳሽ ናቸው። የመጀመርያው ደረጃ መቆራቆስ በፌስ ቡኩ ላይ እንደምናየው በብሽሽቅ፣ መናናቅና መዘላለፍ ይጀምራሉ። የሚቀጥለው መጎሻሾሙ ነው። ይህ ዓይነቱ አሳፋሪ ፖለቲካ ኢትዮጵያ ውስጥ መስፈን አልነበረበትም። ኢትዮጵያውያኖች እንዲህ ልንሆን ባልተገባ ነበር። የእልፍ ዓመታት አኗኗራችንንና ታሪካችን በምድር ከሚኖሩት ሕዝቦች መካከል ልዩ ሥፍራን አሰጥቶን ነበር። እነ ሄሮዶቱስና ሆሜር ድንቅና እውነተኛ ሕዝቦች እንዳላሉን ኢሕአዴግ በአመራር ስህተት ሃገሪቱን አዋረዳት።

መደምደምያ

ድንገት የገነፈለው ብሶት በርካታ የፌስቡኩን ተጠቃሚ ወጣት “አሸናፊ” ሆኖ የመውጣት ስሜት ቢያሳድግም የመማርና የማስተማር፣ የማመንና የማሳመን ሂደትም ተንጸባርቋል። አንዳንዱ አድናቂና ቲፎዞ በበዙለት መጠን ይበልጥ ቢዋዥቅም በእርግጥ ዘለፋና ስድብ ከበዛበት የሰሞኑ ፌስቡኩ ፍልሚያ ቁም ነገርም አይታጣም። ጥቂት ወጣቶች ፖለቲካውንም አበጥረው ተንትነዋል። የኢትዮጵያም ወጣቶች በነጻ ሃሳባቸውን ማንሸራሸር ሲችሉ «DOWN DOWN TPLF» በማለት ተባብረዋቸዋል። ይህ የታመቀ ብሶት መግለጫ ነው። “አትናገር”፣ “አትተንፍስ” የተባለ ወጣት ቀዳዳውን ሾልኮ ከወጣ እንደ ነብር ኃይለኛ ነው። በሃገር ቤት የተደረጉት አመጾች ሳይደመሩ፣ የፌስቡኩን ናሙና ብቻ እንኳን ተመርኩዘን ያስተዋልነውን ብናስቀምጥ፣ ኢሕአዴግን ከሞላ ጎደል እጅግ በርካታ የወጣት ተቃዋሚዎች እንዳሉት ማወቅ ይቻላል። ስድሳ በመቶ የሚሆነውን የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚወክሉት ወጣቶች ኢሕአዴግን አይደግፉም። እነዚህ ወጣቶች በኢሕአዴግ ዘመን ያደጉ ወጣቶች ናቸው። መንግሥት “የሚቃወሙኝ የቀድሞ ሥርዓት ናፋቂዎች ናቸው” የሚለውን ሰበቡን ውድቅ ያደርጉበታል። ኢሕአዴግ “ለገጠሩ ሕዝብ አጋዥ ነኝ” የሚለውንም አባባል “የገጠሩ ወጣቶች ተሳትፎ” አፋልሶታል። ይህ ኢሕአዴግን ደጋፊ አልባ ለማድረጉ በቂ ማስረጃ ነው። የአስቸኳይ ጊዜው አዋጅ ውቃቢዎቹን ከዚህ ሁሉ ውርጅብኝ የሚከልሉት ላጭር ጊዜ ነው።

ኢትዮጵያን ከዚህ በኋላ ትመራ የምትችለው ሰከን ባለ ኃይል ነው። ሁሉንም ጎሳዎችና ነገዶች በአንድ ማዕድ የሚያሰባስበው “ኢትዮጵያዊነት” ከብስለት (prudence) ይገኛል። ደግና ትሁት የሆነው ኢትዮጵያዊ ቅን ይሁንለት እንጂ ለማንም ይገዛል። የፖለቲካ ባህላችን ባብዛኛው ይህን ይመስላል። ለብዙ ዓመት በብሔራዊ ነጻነት የኮራ ሕዝብን “የሥልጣን ጥማትን በማርካት ጥማት” ለባዕዳኑ የግራውም ሆነ ቀኙ ርዕዮተዓለም ተንበርካኪ ማድረግ አይቻልም። በስድሳዎቹ የተማሪዎች እንቅስቃሴ ዘመን ተማሪዎች እንዳይረብሹ አሜሪካኖች በስድስት ኪሎና አራት ኪሎ ዩኒቨርሲት ካምፓሶች ውስጥ አዳዲስ የመኝታ ቤቶችንና (new block) ኬኔዲ ላይብራሪን (Kennedy Library) አንጸው ነበር። እነዚህ ምቾቶች ተማሪውን ከትግሉ አላስቆሙትም። ኢሕአዴግም ለብዙ ዘመን ተከፍሎ በማያልቅ የዓለም ባንክ ብድር ፎቆችና ፋብሪካዎች ተክሏል፣ ከአዲስ ድሬዳዋ፣ ከአዲስ ትግራይ ዘመናዊ መንገድ አንጥፏል። ይህም የዛሬውን ወጣት በተለይም ደግሞ ዓለም አንድ በሆነችበት ዘመን (globalization) የሚኖረውን ወጣት ተቃውሞ አላዳፈነም። ላዲሱ ትውልድ ብዝሃነት (diversity) ከዓለማቀፍ ማህበራዊ ምጣኔ ኃብታዊ ትስስር ጋር አብሮ መራመድ እንጂ “ብሔር ብሄረሰቦች” የሚለው አሮጌው የማርክሲስቶች አባባል አይደለም።

ሃገራችን ከፖለቲካ ፓርቲዎች በተጨማሪ ሥነ ምግባርን የሚያስተምር ግብረገብነትን የሚያስፋፋ ከሁሉም የኃይማኖት አባቶች የሚውጣጣ አዲስ ኃይማኖታዊ ድርጅት ያስፈልጋታል። ይህ ድርጅት እንደ ፓርቲ ለሥልጣን የሚወዳደር ሳይሆን ለሕዝባዊ ግልጋሎት ራሱን የሚያዘጋጅ የሥነልቦና ተሃድሶ መስጫ ኃይል ነው። ይህ ድርጅት በሃገራችን ነባራዊ ሁኔታ ታግዞ ሕዝብን በግብረገብነት የሚያንጽ አስተሳሰብን የሚያሰፋና ዓዕምሮን ለሥራና ለስተሳሰብ እድገት የሚያዘጋጅ ስብስብ ነው። ይህ ድርጅት ለሕዝብም፣ ለመንግሥትም፣ ለፖለቲካ ፓርቲዎችም የሥነ ምግባር ምንጭና አጋዥ ኃይል ብቻ ሳይሆን የሥልጣንና ፖለቲካ ሙስናን (power and political corruption) ጭምር የሚዋጋ ኃይል ይሆናል። ጽሑፌን በዚህች ማሳሰብያ ልቋጭ።

ጋናዊው የምጣኔ ኃብት ምሁር የሆኑት ዶክተር ጆርጅ አይተይ (George Ayittey) አንድ ወቅት በስብሰባ ላይ ሲናገሩ ያሁኑን አፍሪካዊ ትውልድ “አነር” (Cheetah) ሲሉት በሥልጣኝ ላይ ያሉትን በልተው በልተው በቃኝ የማይሉትን ሙስናው ያወፈራቸውን ገዢዎች “ጉማሬ” (Hippos) ብለዋቸዋል። እርሳቸው በነዚህ “አነሮችና ጉማሬዎች” መካካል (African Cheetahs versus Hippos) ያለው ትግል ቀላል እንዳልሆነ አውስተው፣ ዞሮ ዞሮ ጉማሬ አነርን አባሮ መያዝም ሆነ ማሸነፍ ስለማይችል ሜዳውን ከወዲሁ ቢለቅለት ውሃ ውስጥ ለሚያሳልፈው ቀሪ ዘመኑ መልካም መሆኑን በማውሳት ምክራቸውን ለግሠዋል። እነዚህኑ አፍሪካዊ ጉማሬ ባለስልጣኖች ነው ፕሬዚዴንት ባራክ ኦባማ ኬንያን በጎበኙበት ወቅት “ይበቃችኋል፣ እርፍ በሉ፣ ሥልጣኑን ለቃችሁ ያጠራቀማችሁትን ብሉ” ያሉት።

ሠሚ ጆሮ ያለው ቢኖር እነዚህ ምክሮች የአፍሪካን አምባገነኖች ከስጋትና ነገ ከሚመጣው መቅሰፍት የሚያድናቸው ምክር ነበር። ምክሮቹ አህጉሪቱንም ከጥፋት ያድናሉ። ኢሕአዴግም ከእነዚህ ምክሮች ማስተዋል ያገኛል የሚል እምነት አለኝ።

ነጭ በሬ ሆኜ ቆሜልሃለሁ እና ጨፉጭፈኝ! –ደመቀ ገሰሰ የኔአየሁ (PhD)

$
0
0

Ethiopiaእንደሚታወቀው ህወዓት ፋሺስት ጣሊያን አያቱ ሊፈፅም አቅዶ ያልተሳካለትን ኢትዮጵያን የማፈራረስ ፕሮጀክት በ1983ዓም ይዞ ብቅ በማለት ፋሺስት ጣሊያን ኢትዮጵያን ከፋፉሎ ለመግዛት በብሄር ተከፋፉሎ የተሰራውን የፋሺስት ጣሊያን ኢትዮጵያ ካርታ ከወዳደቀበት ፉርስራሽ አቧራውን አራግፎ አያቱ ጀምሮ ያልተሳካለትን ኢትዮጵያን የማፉረስ አጀንዳውን ይዞ ብቅ በማለት አንቀፅ 39 የሚባል እስከመገንጠል መብት በህገ-መንግስቱ ውስጥ በማስቀመጥ የአያቱን ፋሺስት ጣሊያን ፕሮጀክት ከዳር ለማድረስ አልሞ እና አቅዶ መነሳቱ ይታወሳል።

ፉሺስት ጣሊያን ለከፋፉለህ ግዛው ፕሮጀክቱ ትልቅ ደንቀራ ሆኖ የገጠመው ሃይል ቢኖር በአገሩ እና በሃይማኖቱ ድርድር የማያውቀው የአማራው ነገድ ነበር። ፋሺስት ጣሊያን እኛ የመጣነው የአውሮፓን ስልጣኔ እና ጥበብ ልናስተምራቹህ ነው እያሉ በመደስኮር ነበር። ይህ ዲስኩር ገና ምእራባውያን እራቁታቸውን በጢሻ ሲኖሩ የአለም ስልጣኔ ቀንዲል የሆነ ህዝብ መሆኑን እና ይህን ዲስኩርህን አይገባኝም ብሎ አሻፈረኝ ያለው የአማራው ነገድ በጣሊያኖች እይታ “ይህ የማይገባው መንቻካ ህዝብ አህያ ነገር ነው” ሲሉ ማጥላላታቸውን ተያያዙት። በተቃራኒ ከፋሺስት ጣሊያን ጋር የወገኑ እና በባርነታቸው ውስጥ የገባውን ባንዳ ወይም አስካሪ ደግሞ “እናንተ ትምህርት ቶሎ የሚገባቹህ ስልጡን ህዝብ ናቹህ” እያሉ የሰሜን ዘመዶቻችንን ማቆላመጡን ተያያዙት።

“ስልጣኔ አልገባው ያለው” የአማራ ችኮ ህዝብ ግን በአገሩ እና በማተቡ ቀልድ የለም ብሎ በሚያመልከው አምላኩ ምሎ እና ተገዝቶ ወራሪው ፋሺስት ጣሊያንን አይቀጡ ቅጣት ቀጥቶ ሊያደባያቸው መላው የኢትዮጵያን ህዝብ ከዳር እስከዳር በማስተባበር ባርነትን ሊጭኑብን የመጡትን ባእዳን በአድዋ ተራሮች ስር አጥንቱን ከስክሶ እና ደሙን አፉስሶ አፈርድሜ በማስጋጥ ሃያልነቱን እና አልበገር ባይነቱን አሳያቸው።

የአማራው ህዝብ ኢትዮጵያ ሃገራችንን ባህር አቋርጠው የመጡትን ባእዳን ሁሉ ሌላውን ኢትዮጵያዊ ሁሉ እያስተባበረ እና ከሌላው ኢትዮጵያዊ ጋር እየተባበረ ይቺን አገር ለዚህ ትውልድ ዋጋ ከፉሎ ያቆየ ህዝብ ነው። የአማራው ህዝብ በታሪኩ አንድም ቀን ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ወገኖቹ ተለይቶ ብቻውን በመቆም የተዋጋው የውጭ ወራሪ ሃይል አልነበረም። የልቁንም እኒህ አርቀው የነገውን ያስቡ የነበሩት ቅደመ-አያቶቻችን በተናጠል የሚደረግ ትግል ውጤታማ እና ዘላቂ ትብብርን የማያመጣ እንደሆነ በመረዳታቸው ሁሉንም ኢትዮጵያዊ እያስተባበሩ ነበር ዳርድንበራቸውን ሲቆጣጠሩ የኖሩት።

በርካታ ጊዜ አገራችንን ቅኝ ለመያዝ የቋመጡት ፋሺስት ጣሊያንን በመመከት ዛሬ ላይ በአለም ህዝብ ዘንድ አንገታችንን ቀና ብለን እንድንሄድ አኩሪ ታሪክ ሰርተውልን አልፈዋል። በአደዋ ላይ አይቀጡ ቅጣት ቀምሶ የተመለሰው ጣሊያን ተመልሶ በሁለተኛው የአለም ጦርነት መባቻ ላይ አገራችንን ሲወር ከአደዋው ጦርነት እጅግ በተሻለ ዘምነው በሰማይ እየበረሩ እኛ ግን አሁንም የነበረንን እንደያዝን በመውዜር እና በአጋሰስ ብቻ ገጠምናቸው። ይህ የነበረው የትጥቅ አለመመጣጠን እንደማያዋጣን አብዝተው የተገነዘቡት አያቶቻችን ትልቁን ዲፕሎማሲ በመስራት እንግሊዝ ከጎናችን እንድትሰልፉ እና ለዳግም ድል እንድንበቃ አድርገውናል።

ይህን ታሪክ ወደኋላ ሂደን እንድናስታውስ አስፈላጊ የሆነበትም ምክንያት ዛሬ ላይ አማራው ምን ማድረግ እንዳለበት ለማስታወስ ነው። ህወዓት የትግራይን ሪፕብሊክ ለመመስረት አቅዶ ትግሉን ቢጀምርም እድል ቀንቶት የደርግን መንግስት ከሻብያ ጋር ተባብሮ እንደሚጥለው ሲገባው መገንጠሉ እንደማይጠቅመው በመረዳት ኢህዴግ የሚባል የድርጅቶች ስብስብ በመፉጠር ኢትዮጵያዊ መስሎ ከች አለ። ወያኔ ያኔ በለሱ እንደቀናው ትግራይን ገንጥሎ ቢሄድ ኖሮ ምን ሊደርስበት ይችል እንደነበር ለማወቅ ነብይ መሆን አያስፈልግም። የልቁንም ይህ ችግር የገባቸው ህወዓቶች ኢትዮጵያን ጌታቸው ፋሺስት ጣሊያን ለከፋፍለህ ግዛው አላማ ፈጥሮት የነበረውን የብሄር ካርታ አቧራውን አራግፎ አገሪቱን በብሄር ከፋፉሎ እየው እስከዛሬ ድረስ ኢትዮጵያዊ ካባ ለብሶ ሁሉንም ብሄሮች ለራሳቸው የውስጥ ባንዳ የሚሆኗቸውን የየብሄሩ ተወላጆች በፓርቲ ስም በማዋቀር እየገዙ ይገኛሉ። እዚህ ላይ ማስተዋል ያለብን ህወዓት 25ዓመት ሲገዛ ብቻውን በህወዓት ስም አይደለም። የልቁንም ብሄር ብሄረሰባችን መብት አስከብሬአለሁ በማለት የሁሉንም ዘውጎች ተወካዮች በመያዝ ነው። ብአዴን፣ደህዴን፣ኦህዴድ እና መሰል የብሄር ተቀፅላ ፓርቲወችን ከጎኑ በማሰለፉ ነው።

ህወዓት አሁን የሚደረገውን የነፃነት ትግል ለማፈን የቀረበው ህወዓት ብቻ ሆኖ አይደለም። የልቁንም አብዛኛው የመከላከያ እና ፓሊስ ሰራዊት ከትግራይ ውጭ በሆኑ ሌሎች ኢትዮጵውያን አደራጅቶ የመሪነቱን ቦታ ደግሞ ለሚያምናቸው የትግራይ ሰወች በመስጠት ነው እየወጋን ያለው። ህወዓት ብቻውን ከኢትዮጵያውያን ጋር የሚዋጋ ቢሆን ኖሮ ይህን ያህል ዋጋ ባልተከፈለ ነበር። እውነታው ግን ይህ አይደለም። ይህ ማለት ወያኔ ኢትዮጵያውያንን ይዞ ሲወጋን ወያኔን ልናሸንፉ የምንችለው እንደ ኦነግ ወይም የብሄር ድርጅቶችን በማዋቀር በብሄርህ ብቻ ስትደራጅ ሊሆን አይችልም። ከ25 ዓመት በላይ የአገሪቱን ጠቅላላ ሃብት በበላይነት በመቆጣጠር እና በስመ ፀረ-ሽብር አጋርነት ከምእራባውያን በሚደረግለት ልገሳ እና ስልጠና የፈረጠመን ሃይል እና ሌላውን ኢዮዬጵያውያን ይዞ በኢትዮጵያ ደረጃ ሲገጥመን እኛ አማራ ነፃ አውጪ ድርጅት፣ ኦሮሞ ነፃ አውጭ ድርጅት፣ወዘት እያልን በብሄር ጠበን ስንወርድለት የበለጠ ነጭ በሬ ሆነን ህዝባችንን ኑና ጨፉጭፉልን ከማለት ያለፈ ትርፉ ሊኖረው አይችልም። ትላንት ኢትዮጵያውያንን በማስተባበር የአገራችንን ዳር ድንበር ከጠላት ሲከላከል የነበረው ትልቁ የአማራ ነገድ ወያኔ በፈጠረለት የብሄር ቋት እንሶ በመደራጀት አማራውን ነፃ ሊያወጣ የሚችልበት ምድር ላይ ያለ እውነታ አይደለም። ይህ ዝም ብሎ ሳያሰላስሉ እና ኢትዮጵያ የተሰራችበትን የታሪክ ምህዳር ሳያገናዝቡ፣የቀጠናውን ጂኦ ፓለቲካል አሰላለፉ ምን እንደሆነ ሳያስተውሉ እና ወያኔ አሁንም በኢትዮጵያ ካባ ስር ሌላውን ኢትዮጵያዊ አስተባብሮ እየወጋህ እያለ አንተ ከነበረህ የታሪክ ደረጃ ወርደህ በአማራነት ስትደራጅለት ለወያኔ ድግስ እና ምላሽ ሆንክለት ማለት ነው። እንዲያውም ይኽውልህ እያለ የበለጠ ከሌላው ጋር ያላትምህ ይሰራል እንጂ እንዲህ በቀላሉ ሽር የሚባልበት መንገድ አይመስልም።

በአማራ ብሄርተኝነት ስም እንደራጅ ብለው የሚያስቡ ቡድኖች ሃሳባቸው ትክክል ሃኖ ሳለ አሁን ላለንበት እውነታ ውጤታማነቱ እጅግ አስቸጋሪ ነው። ወያኔ እና ሻብያ ብሄር ተኮር አጀንዳ ይዘው ሲታገሉ ድል የቀናቸው ትልቁ ምክንያት በዘመኑ የነበረው የቀዝቃዛው ጦርነት ትልቅ አስተዋዖ ነበረው። ዛሬ ላይ የጎረቢት አገሮች ሳይቀር በወያኔ ቀኝ እጅ ውሥጥ ባሉበት በአሁኑ ወቅት፣ በፀረ-ሽብር ምክንያት ህወዓት-ኢህዴግ ከምእራባውያን ሃያላን ጋር እጅ እና ጓንት ሆኖ እየሰራ ባለበት ወቅት፣ እራሱ ወያኔ ኢትዮጵያዊ ካባ ለብሶ እየታገለን ባልንበት በዚህ ሰዓት እንደ አማራ ነፃ አውጭነት፣እንደ ኦሮሞ ነፃ አውጭነት ወዘተ ሆነን ዳር ልንደርስ አንችልም። እያየነው ያለውም ሃቅ ይህ ነው። በብሄር ተደራጅቶ ሊሳካ የሚችል ቢሆን ኖሮ ኦነግ ከ40ዓመት በላይ ሚሊዮን ኣሮሞወችን ነጭ በሬ ሆኖ በመቆም ለእልቂት ዳረገ እንጂ ያተረፈው ትርፉ የለም። አማራውም የተለየ ሊሆን አይችልም ።ቅደመ አያቶቻችን ጠላትን በህብረት ተፋልመው አሸነፉት እንጂ በተናጠል አልሄዱም።

ዛሬ ላይ የተለየ እውነታ የለም። የልቁንም ዛሬ ላይ ወያኔ ያልገደልው እና ያላሰቃየው ህዝብ የለም። ሁሉም ህዝቦች የወያኔ ጭካኔ ደርሶባቸዋል። የኦሮሞው ወጣቶች አብዬት እና የአማራ ህዝብ ተጋድሎ እያሳየን ያለው ነገር ቢኖር ወያኔን ዘረኛ ቡድን አድርጎ በያሉበት እየተፋለሙት ይገኛሉ። ወያኔ ዛሬ ላይ በኢትዮጵያዊ ካባ የተጀቦነበት ካብ እየተናደ ተነጥሎ እየተመታ ነው። ይህ ሃቅ ሆኖ ሳለ ልክ እንደ ቅድመ-አያቶቻችን ተባብረን በአንድ ላይ ለፉትህ እና እኩልነት መታገል በእኔ እይታ ብቸኛ አዋጪ መንገድ ይመስለኛል። ነገር ግን የአለምን የፓለቲካ ሚዛን ሳይመረምሩ፣ምድር ላይ ያለውን ሃቅ ሳይመለከቱ በኢሞሽን ብቻ በመነዳት የአማራ ብሄርተኝነት የአማራውን ችግር ይፈታል የሚል እምነት የለኝም። የልቁንም በወያኔ ክፉ በትር የተጎዱ እና እየተጎዱ ያሉትን ሌሎች ወገኖቻችን ጋር በመተባበር ፉትህ የሰፈነባት ዴሞክራሲያዊ ኢትዮጵያን ለመገንባት መታገል አውጭው መንገድ ነው።

እስኪ አስቡት ወያኔወች ኢትዮጵያ ሆነው ሲገጥሙን በምን መስፈርት ነው አማራ በአማራነት ሆነን ልንገጥማቸው ያሰብን? እናም እናስተውል! የአንድ ድርጅት ስኬት የሚለካው ይዞት የተነሳው አላማው አዋጪነቱ(feasibility) ሲኖረው ነው። ለሚደረገው ትግል የአለም አቀፉ የትብብር ድጋፉ ሊያገኝ መቻል አለበት። የጎረቢት አገሮች ሚና ተለይቶ መታየት አለበት። የአማራው ስነ-ልቦና መታወቅ አለበት። እውነት ለመናገር ይህ በአማራነት ብቻ ተደራጅቶ የአማራንም ህዝብ ሆነ ኢትዮጵያን ነፃ ማውጣት የሚቻል እንኳ ቢሆን እጅግ እረጅም አመታትን የሚፈጅ እና ኪሳራውም የከፋ ነው የሚሆነው።

ይህን ስል አማራው መደራጀት የለበትም እያልኩ አለመሆኔ ሊሰመርበት ይገባል። አማራው አሁን እያደረገ ያለውን ተጋድሎ ተቀናጅቶ መቀጠል ይኖርበታል። ነገር ግን የአማራ ነፃ አውጭ ብሎ እራስን ነጭ በሬ አድርጎ ለጥቃት ማጋለጥ ሳይሆን እንደ ቅድመ አያቶቻችን ሌሎችን ብሄሮች ተባብሮ እና አስተባብሮ ወያኔ ነጥሎ ለመምታት ሲቻል ብቻ ነው። ወያኔ በህብረ-ብሄራዊ ጭንብል ኢትዮጵያዊ ሆኖ ሲገጥመን እኛ ወርደን አማራ ሆነን ልንገጥመው ማሰብ ለወያኔ የሞራል ልእልና ካርድን መሸጥ ብቻ ሳይሆን በራሳችን ወገን ሳይቀር ወያኔ አስተባብሮ ልክ በኦነግ እና ኦብነግ ላይ ያደረሰውን የጭካኔ በትር በእኛ ላይ እንዲዘምትብን ነጭ በሬ መሆን ነው።

አንድ አማራውን የሚወክል ፓለቲካል ፓርቲም ቢኖር መላክም እንጂ ችግሩ አይታየኝም። አንድ ጠንካራ የአማራ ፓለቲካ ፓርቲ ካለ ለሽግግር መንግስትም ሆነ በዘላቂነት የአማራውን ፉላጎት እና ጥቅም የሚያስከብር ፓርቲ ሊኖር ይገባል። በእኔ እይታ የአማራውን ህዝብ ችግር እና ትግል የሚዘክር እና የአድቮኬሲ ስራ የሚሰሩ እንደ ሞረሽ-ወገኔ አይነት ድርጅቶችን ማጠናከር፣ ህዝባችን ከሌሎች ኢትዮጵያዊ ወገኖቹ ጋር ሆኖ የሚያደርገውን ተጋድሎ መርዳት እና ማገዝ ወቅቱ የሚፈልገው አዋጪ መንገድ እንደሆነ አስባለሁ።

ቸር ይግጠመን!

ኢትዮጵያ ለዘላለም ከህዝቦቿ ጋር በክብር ትኑር!

 

የአሰቸኳይ ጊዜ አዋጅ ብርቅ ነው!!! –ግርማ ሠይፉ ማሩ

$
0
0

ግርማ ሠይፉ ማሩ girmaseifu32@yahoo.com, www.girmaseifu.blogspot.com

Girma-Siefu.jpgየአስቸኳይ ጊዜው ሴክፌታሪያት አዋጁ ግቡን መቷል ብለው መግለጫ መስጠታቸውን ሰምተናል፡፡ ይህ አዋጅ በአጭሩ ዝም ጭጭ አድርጎ ለመግዛት የተቀየሰ ዘዴ ነው ለምንል ሰዎች ዜጎች ዝም ጭጭ እንዲሉ ተደርጓል ማለት ነው፡፡ አሰገራሚው ነገር መስከረም 1967 “መለኮታዊ ንጉስ” የሚባሉትን አውርዶ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ደርግ ለምን አወጀ ብለው የሚከሱ፣ ሲከፋም በዚሁ ምክንያት ነው ጫካ የገባነው ብለው የሚፎክሮ የዲሞክራሲ አርበኞች በህይወት እያሉ አሁን “ዲሞክራሲያዊ” የተባለ የአስቸኳይ ጊዚ አዋጅ አውጀውልናል፡፡ ይህ አዋጅ በቴሌቪዥን ሲነበብ አደመጥኩት ክልከላዎቹ በሙሉ ድሮም በህግ የተፈቀዱ በተግባር ግን የማይቻሉ የነበሩ ናቸው፡፡ ለማረጋገጥ በጋዜጣ የወጣውን በጥሞና ደግሜ ደግሜ አነበብኩት ብዙዎች መመሪያው “ክልክል” ያላቸው ድሮም ወደፊትም ክልክል ናቸው፡፡ ለምሣሌ ንብረት ማውደም፣ ሰው መግደል፣ ያልተፈቀደ የሠራዊት ዩኒፎርም መልበስ፣ ህገወጥ ቅስቀሳዎች፣ ወዘተ በሙሉ መቼም ያልተፈቀዱ ወደፊትም የማይፈቀዱ ክልከላዎች ናቸው፡፡ ተፈቅደው ነገር ግን በተግባር ያልነበሩት የአደባባይ ሠልፍ እና ስብሰባ ዋነኛዎቹ ሲሆኑ፣ እጅግ ብዙዎቹ ክልከላዎች በሀገሪቱ በነበረው ህዝባዊ እንቅስቃሴ ወቅት ገዢዎችን አንጀት ያሳረሩ ድርጊቶቸን ዝርዝር ለማወቅ ከመጥቀማቸው ውጭ ፋያዳቸው አይታየኝም፡፡

በአዋጁ ውስጥ አስደናቂ ሊባሉ የሚችሉት ግን ማየት መስማት የሚከለክሉት የመጀመሪያዎቹ አንቀፅ ላይ የሰፈሩት ክልከላዎች ናቸው፡፡ መለኮታዊ ንጉስ አውርዶ እንዴት ሰልፍ ተከለከልን ያሉ ታጋዮች ለዚህ ነው ዓይናችን የጠፋው አካላችን የጎደለው ያሉ ሁሉ በተገኙበት ስብሰባ ይህን ማድረግ አስገራሚ ሆኖ በታሪክ ይመዘገባል፡፡

አዋጁን ተከትሎ በሚዲያ የሚተላለፉት ነገሮች ደግሞ የበለጠ አስደማሚ ናቸው፡፡ አንድ አንድ ነዋሪዎች በመባል የሚታወቁ አስተያየት ሰጪዎች አዋጁ ዘገየ፣ ለልማታችን ያስፈልገናል፣ ወዘተ የሚሉ አሰተያየቶች ሰጥተዋል፡፡ ማለት የፈለጉት ለእኛ ብቻ ሳይሆን ለአስተያየት ሰጪዎችም ሆነ አስተያየት ሰብሳቢዎች ግልፅ አይመሰለኝም፡፡ ሕገ መንግሰታዊ ስርዓት ይከበር እያልን፣ በአስቸኳይ አዋጅ መብታችን ተገድቦ ይኑር ማለት ትርጉሙ አይገባም፡፡ ግራ ገብቷቸው ግራ የሚያጋቡ የዚህ ዓይነት አስተያየት ሰጪዎችና ሰብሳቢዎች ያሉበት ሀገር ውስጠ ነው የምንገኘው፡፡

ተንታኞች ተብዬዎቹ ደግሞ አዋጁ ምንም አያስገርምም ሁሉም ሀገሮች የሚያደርጉት ነው በሚል ፈረንሳይን፣ ቱርክን፣ አሜሪካን የመሳሰሉ ሀገሮችን በመጥቀስ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ብርቅ ነው እንዴ!! እያሉን ይገኛሉ፡፡ ይህን አዋጅ ልዩ የሚያደርገው ደግሞ አዋጁ ሲዘጋጅ ልምድ የተወሰደበት ሀገር አለመጠቀሱ ነው፡፡ ይህን እኛም እንዳንጠረጥር አዋጁን ያዘጋጀው ማንም ይሁን ማን ደረጃውን ያልጠበቀ ዝርክርክ መሆኑን ግን አለመግለፅ ትዝብት ላይ ይጥላል፡፡ ይህን አዋጅ ሰመለከት ይህ ካቢኔ ተብዬው ሀገሪቱን የሚገዛው ቡድን ያለውን አቅም ለመረዳት ችያለሁ፡፡ በምንም ሁኔታ በአስቸኳይ ደረጃውን የጠበቀ መግለጫ ማውጣት እንደማይችል፤ ይህን ዓይነት የባለሞያ ስራ ሊያግዝ የሚችል የባለሞያ ስብስብ እንደሌለው ጭምር ተረድቻለሁ፡፡ አዋጁን መታወጁን ጠቅላይ ሚኒስትሩ የገለፁ ዕለት ዝርዝሩን እንደደረስን እናቀርባለን የሚለው የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የተደጋገመ ማስታወቂያ የሰለቸው ልጄ ስብሰባውን በእንግሊዘኛ ነው እንዴ ያደረጉት? ብሎኛል:: ይህ በሙሉ የሚያሳየው አሰቸኳይ ጊዜ አዋጁ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ ፕሮግራም እየተባለ የሚወጡት በሙሉ ደረጃቸውን ያልጠበቁ መሆናቸው ነው፡፡ “ነበር” በሚል መፅኃፍ ውስጥ ደርጎች መግለጫ እንዴት ያወጡ እንደነበር የተፃፈውን ስመለከት በዚያ ቀውጢ ወቅት ከዚህም ከዚያ የተሰባሰቡ ወታደሮች የሰሩትን መስራት የማይችል ሃያ አምሰት ዓመት በስልጣን ላይ የቆየ መንግሰት እንዴት አሳዛኝ እንደሆነ አንባቢ ሊፈርድ ይችላል፡፡

በነገራችን ላይ ከቅዳሜ ጀምሮ የሚፀና አዋጅ እሁድ ለምን ታወጀ? ሰኞ ምክር ቤቱ ሰለሚከፈት በዝርዝር አዘጋጅተው ለምን ምክር ቤቱ ሲከፈት አላቀረቡትም? የሚሉና የመሳሰሉትን ጥያቄዎች ማንሳት ይቻላል፡፡ በእኔ እምነት ከቅዳሜ ጀምሮ የፀና ይሆናል የሚል ህገወጥ አካሄድ የመረጡት ምክር ቤት በሌለበት የታወጀ በማሰመሰል፣ በአርባ ስምንት ሰዓት ውስጥ ለምክር ቤት አቅርቡ የሚለውን ህገ መንግሰታዊ ድንጋጌ ለመጣስ እንደሆነ ግልፅ ነው፡፡ ይህን በማድረግ በሁለተኛው አማራጭ አሰራ አምስት ቀን ማግኘት የቻሉ ሲሆን ባገኙት አስራ አምስት ቀን የዝግጅት ጊዜ ውስጥም የሚሰሩትን ሰራ ጥራት ለማስጠበቅ አልቻሉም፡፡

አዋጁ ዋና ዓላማው አስፈራርቶ መግዛት ስለሆነ ከሞላ ጎደል ሊሳካለት ይችላል የሚባለው ለመፍራት በተዘጋጁት ላይ ብቻ ነው፡፡ ነፃነት ወይም ሞት ብሎ ለተነሳ ግን ይህ አዋጅ ምን ይቀንሰበታል? ብዬ ጠይቄ መልሱ ምንም የሚል ነው የሆነብኝ፡፡ ለማነኛውም ይህ አሰቸኳይ ጊዜ አዋጅ ህወሃት/ኢህአዴግ በውስጡ እፈጥራለሁ ላለው “ጥልቅ ተሃድሶ”  ይሁን “ፈርሶ መሰራት” በአባላቱ መካከል ሊፈጠር ለሚችል ቀውስ መቆጣጠሪያ ለማድረግ ነው በሚል በተሰፋ ለመሞላት ለሚፈልጉት ተሰፋ ከሰጣቸውም ተሳስቼም ቢሆን ይህ ተሰፋ ዕውን ቢሆን ደስ ይለኛል፡፡

መልካም የአስቸኳይ ጊዜ ይሁንልን!!!!

የአሰቸኳይ ጊዜ አዋጅ ብርቅ ነው!!! –ግርማ ሠይፉ ማሩ

$
0
0

girmaseifu32@yahoo.com, www.girmaseifu.blogspot.com

girma seifu

ግርማ ሠይፉ ማሩ

የአስቸኳይ ጊዜው ሴክፌታሪያት አዋጁ ግቡን መቷል ብለው መግለጫ መስጠታቸውን ሰምተናል፡፡ ይህ አዋጅ በአጭሩ ዝም ጭጭ አድርጎ ለመግዛት የተቀየሰ ዘዴ ነው ለምንል ሰዎች ዜጎች ዝም ጭጭ እንዲሉ ተደርጓል ማለት ነው፡፡ አሰገራሚው ነገር መስከረም 1967 “መለኮታዊ ንጉስ” የሚባሉትን አውርዶ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ደርግ ለምን አወጀ ብለው የሚከሱ፣ ሲከፋም በዚሁ ምክንያት ነው ጫካ የገባነው ብለው የሚፎክሮ የዲሞክራሲ አርበኞች በህይወት እያሉ አሁን “ዲሞክራሲያዊ” የተባለ የአስቸኳይ ጊዚ አዋጅ አውጀውልናል፡፡ ይህ አዋጅ በቴሌቪዥን ሲነበብ አደመጥኩት ክልከላዎቹ በሙሉ ድሮም በህግ የተፈቀዱ በተግባር ግን የማይቻሉ የነበሩ ናቸው፡፡ ለማረጋገጥ በጋዜጣ የወጣውን በጥሞና ደግሜ ደግሜ አነበብኩት ብዙዎች መመሪያው “ክልክል” ያላቸው ድሮም ወደፊትም ክልክል ናቸው፡፡ ለምሣሌ ንብረት ማውደም፣ ሰው መግደል፣ ያልተፈቀደ የሠራዊት ዩኒፎርም መልበስ፣ ህገወጥ ቅስቀሳዎች፣ ወዘተ በሙሉ መቼም ያልተፈቀዱ ወደፊትም የማይፈቀዱ ክልከላዎች ናቸው፡፡ ተፈቅደው ነገር ግን በተግባር ያልነበሩት የአደባባይ ሠልፍ እና ስብሰባ ዋነኛዎቹ ሲሆኑ፣ እጅግ ብዙዎቹ ክልከላዎች በሀገሪቱ በነበረው ህዝባዊ እንቅስቃሴ ወቅት ገዢዎችን አንጀት ያሳረሩ ድርጊቶቸን ዝርዝር ለማወቅ ከመጥቀማቸው ውጭ ፋያዳቸው አይታየኝም፡፡

በአዋጁ ውስጥ አስደናቂ ሊባሉ የሚችሉት ግን ማየት መስማት የሚከለክሉት የመጀመሪያዎቹ አንቀፅ ላይ የሰፈሩት ክልከላዎች ናቸው፡፡ መለኮታዊ ንጉስ አውርዶ እንዴት ሰልፍ ተከለከልን ያሉ ታጋዮች ለዚህ ነው ዓይናችን የጠፋው አካላችን የጎደለው ያሉ ሁሉ በተገኙበት ስብሰባ ይህን ማድረግ አስገራሚ ሆኖ በታሪክ ይመዘገባል፡፡

አዋጁን ተከትሎ በሚዲያ የሚተላለፉት ነገሮች ደግሞ የበለጠ አስደማሚ ናቸው፡፡ አንድ አንድ ነዋሪዎች በመባል የሚታወቁ አስተያየት ሰጪዎች አዋጁ ዘገየ፣ ለልማታችን ያስፈልገናል፣ ወዘተ የሚሉ አሰተያየቶች ሰጥተዋል፡፡ ማለት የፈለጉት ለእኛ ብቻ ሳይሆን ለአስተያየት ሰጪዎችም ሆነ አስተያየት ሰብሳቢዎች ግልፅ አይመሰለኝም፡፡ ሕገ መንግሰታዊ ስርዓት ይከበር እያልን፣ በአስቸኳይ አዋጅ መብታችን ተገድቦ ይኑር ማለት ትርጉሙ አይገባም፡፡ ግራ ገብቷቸው ግራ የሚያጋቡ የዚህ ዓይነት አስተያየት ሰጪዎችና ሰብሳቢዎች ያሉበት ሀገር ውስጠ ነው የምንገኘው፡፡

ተንታኞች ተብዬዎቹ ደግሞ አዋጁ ምንም አያስገርምም ሁሉም ሀገሮች የሚያደርጉት ነው በሚል ፈረንሳይን፣ ቱርክን፣ አሜሪካን የመሳሰሉ ሀገሮችን በመጥቀስ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ብርቅ ነው እንዴ!! እያሉን ይገኛሉ፡፡ ይህን አዋጅ ልዩ የሚያደርገው ደግሞ አዋጁ ሲዘጋጅ ልምድ የተወሰደበት ሀገር አለመጠቀሱ ነው፡፡ ይህን እኛም እንዳንጠረጥር አዋጁን ያዘጋጀው ማንም ይሁን ማን ደረጃውን ያልጠበቀ ዝርክርክ መሆኑን ግን አለመግለፅ ትዝብት ላይ ይጥላል፡፡ ይህን አዋጅ ሰመለከት ይህ ካቢኔ ተብዬው ሀገሪቱን የሚገዛው ቡድን ያለውን አቅም ለመረዳት ችያለሁ፡፡ በምንም ሁኔታ በአስቸኳይ ደረጃውን የጠበቀ መግለጫ ማውጣት እንደማይችል፤ ይህን ዓይነት የባለሞያ ስራ ሊያግዝ የሚችል የባለሞያ ስብስብ እንደሌለው ጭምር ተረድቻለሁ፡፡ አዋጁን መታወጁን ጠቅላይ ሚኒስትሩ የገለፁ ዕለት ዝርዝሩን እንደደረስን እናቀርባለን የሚለው የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የተደጋገመ ማስታወቂያ የሰለቸው ልጄ ስብሰባውን በእንግሊዘኛ ነው እንዴ ያደረጉት? ብሎኛል:: ይህ በሙሉ የሚያሳየው አሰቸኳይ ጊዜ አዋጁ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ ፕሮግራም እየተባለ የሚወጡት በሙሉ ደረጃቸውን ያልጠበቁ መሆናቸው ነው፡፡ “ነበር” በሚል መፅኃፍ ውስጥ ደርጎች መግለጫ እንዴት ያወጡ እንደነበር የተፃፈውን ስመለከት በዚያ ቀውጢ ወቅት ከዚህም ከዚያ የተሰባሰቡ ወታደሮች የሰሩትን መስራት የማይችል ሃያ አምሰት ዓመት በስልጣን ላይ የቆየ መንግሰት እንዴት አሳዛኝ እንደሆነ አንባቢ ሊፈርድ ይችላል፡፡

በነገራችን ላይ ከቅዳሜ ጀምሮ የሚፀና አዋጅ እሁድ ለምን ታወጀ? ሰኞ ምክር ቤቱ ሰለሚከፈት በዝርዝር አዘጋጅተው ለምን ምክር ቤቱ ሲከፈት አላቀረቡትም? የሚሉና የመሳሰሉትን ጥያቄዎች ማንሳት ይቻላል፡፡ በእኔ እምነት ከቅዳሜ ጀምሮ የፀና ይሆናል የሚል ህገወጥ አካሄድ የመረጡት ምክር ቤት በሌለበት የታወጀ በማሰመሰል፣ በአርባ ስምንት ሰዓት ውስጥ ለምክር ቤት አቅርቡ የሚለውን ህገ መንግሰታዊ ድንጋጌ ለመጣስ እንደሆነ ግልፅ ነው፡፡ ይህን በማድረግ በሁለተኛው አማራጭ አሰራ አምስት ቀን ማግኘት የቻሉ ሲሆን ባገኙት አስራ አምስት ቀን የዝግጅት ጊዜ ውስጥም የሚሰሩትን ሰራ ጥራት ለማስጠበቅ አልቻሉም፡፡

አዋጁ ዋና ዓላማው አስፈራርቶ መግዛት ስለሆነ ከሞላ ጎደል ሊሳካለት ይችላል የሚባለው ለመፍራት በተዘጋጁት ላይ ብቻ ነው፡፡ ነፃነት ወይም ሞት ብሎ ለተነሳ ግን ይህ አዋጅ ምን ይቀንሰበታል? ብዬ ጠይቄ መልሱ ምንም የሚል ነው የሆነብኝ፡፡ ለማነኛውም ይህ አሰቸኳይ ጊዜ አዋጅ ህወሃት/ኢህአዴግ በውስጡ እፈጥራለሁ ላለው “ጥልቅ ተሃድሶ”  ይሁን “ፈርሶ መሰራት” በአባላቱ መካከል ሊፈጠር ለሚችል ቀውስ መቆጣጠሪያ ለማድረግ ነው በሚል በተሰፋ ለመሞላት ለሚፈልጉት ተሰፋ ከሰጣቸውም ተሳስቼም ቢሆን ይህ ተሰፋ ዕውን ቢሆን ደስ ይለኛል፡፡

መልካም የአስቸኳይ ጊዜ ይሁንልን!!!!

Viewing all 8745 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>