Quantcast
Channel: ዘ-ሐበሻ – Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 8745 articles
Browse latest View live

በህገ-ወጥ ርምጃ ሕጋዊው ሰላማዊ ሰልፋችን አይቀለበስም!!! ሲሉ አንድነትና በ33ቱ ፓርቲዎች በጋራ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጡ

$
0
0

በአንድነትና በ33ቱ ፓርቲዎች በጋራ የተሠጠ ጋዜጣዊ መግለጫ

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ላለፉት ሦስት ወራት ‹‹የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት›› በሚል መሪ ቃል በመላ ኢትዮጵያ ህዝባዊ ንቅናቄ ሲያደርግ መቆየቱ የሚታወቅ ነው፡፡ በዚህም መሰረት በጎንደር፣ በደሴ፣ በባህርዳር፣ በአርባ ምንጭ፣ በጅንካ፣ በፍቼና አዳማ ከተሞች ሕዝቡን ያሳተፉ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፎች ያጋጠሙ የገዥው ፓርቲ እንቅፋቶችን እየተራመደ በተሳካ ሁኔታ ያደረገ ሲሆን በተለያዩ ከተሞች ሕዝባዊ ስብሰባዎችንም አከናውኗል፡፡

ፓርቲያችን የመጀመሪያውን ሕዝባዊ ንቅናቄ ለማጠናቀቅም በአዲስ አበባ ከተማ መስከረም 5 ቀን 2006 ዓ.ም የሚካሄደውን የመጀመሪያው ምዕራፍ የማጠቃለያ የተቃውሞ ሰልፍ ከ33ቱ ፓርቲዎች ጋር ለማካሄድ ወስኖ ይህንንም ውሳኔ ለኢትዮጵያ ህዝብ በማሳወቅ ሰፊ እንቅስቃሴ ውስጥ ገብቷል፡፡ በዚህ ሂደትም አመራሩና የፓቲው አባላት በከፈሉት መስዋዕትነትና ግፊት ህዝቡን ያሳተፉ የተቃውሞ ሰልፎች እንደጅምር አበረታች ናቸው ብለን ብናምንም የህዝቦች መብት ሳይሸራረፍ እስከሚከበር ድረስ፣ ነፃነታችን እስከሚረጋገጥ ድረስ የሚቀጥል እንደሆነ ለማረጋገጥ እንወዳለን፡፡

በአዲስ አበባ የምናካሂደውን የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ ለማከናወን ከማሳወቅ ጀምሮ የገጠመን ውጣ ውረድና ማደናቀፍ ትልቋ ከተማችን ሃላፊነት በማይሰማቸው አስተዳዳሪዎች የምትመራ መሆኑንም ያረጋገጥንበት አጋጣሚም ነው፡፡

ሰላማዊ ሰልፍና ሕዝባዊ ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍል ደብዳቤ ላለመቀበል ከማስቸገርም በላይ የቢሮ ሓላፊዎችና ሌሎች በቀጥታ ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት ስልጠና፣ ስብሰባ፣ እንግዳ ለመቀበልና ሌሎችን ተልካሻ ምክንያቶች በመደርደር ለማደናቀፍ ጥረት አድርገዋል፡፡ ደብዳቤ ፈርሞ መቀበል የማይችል አካል ሃላፊነት የማይሰማው ነው ከማለትም ባለፈ በህግ የሚያስጠይቅ ሀላፊነትን ባግባቡ አለመወጣትን የሚያመለክት ድርጊት ነው፡፡

ከንቲባውና የከንቲባው ፅ/ቤትም በአግባቡ ካለማስተናገድም በላይ የአንድነትን ከፍተኛ አመራሮች (ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳና አቶ አስራ ጣሴን) ሀላፊነት በጎደለው ሁኔታ ስለሰላማዊ ሰልፉ እንደራደር በማለት አመላልሰዋል፡፡ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ማሳወቅ በቂ ቢሆንም ከከንቲባው ጋር መነጋገር ያስፈለገበት ዋና ምክንያት ለፖሊስ በሚሰጥ የውስጥ መመሪያ እየተካሄደ ያለው ማደናቀፍ እንዲቆም፣ መስተዳድሩ መመሪያ ብሎ ያወጣውና ለወረቀት ብተና፣ ፖስተር ልጠፋ፣ የመኪና ላይ ቅስቀሳና ፔቲሽን ለማስፈረም ልዩ ፈቃድ እንደሚያስፈልግ የሚያዝ፤ ይህ ካሆነ ፖሊስ ርምጃ እንዲወስድ የሚያደርገውን ሕገ-መንግስት የሚጥስ መመሪያ በተመለከተ ነበር፡፡

ምንግዜም ህጋዊ መስመር ተከትሎ ከማስተዳደር ይልቅ በህገ-ወጥ መንገድ ማፈንና ማደናቀፍ የሚመርጠው ገዥ ፓርቲ ለህጋዊ የሰላማዊ ሰልፍ ጥያቄያችን የመረጠው መንገድ ህገ-ወጥነትን ነው፡፡ ይህ ህገወጥነትም መንግስትን ዋጋ ያስከፍለዋል፡፡ ስለዚህ፡-

1ኛ. ሰላማዊ ሰልፋችንን ለማድረግ ከነሐሴ 21 ቀን 2005 ዓ.ም ጀምሮ ያሳወቅን በመሆኑ በታቀደው ቀን መስከረም 5 ቀን 2006 ዓ.ም ከጠኋቱ 3፡00 ሰዓት ጀምሮ በመስቀል አደባባይ ይደረጋል፡፡

2ኛ. ለሰላማዊ ሰልፉ ቅስቀሳና ሂደት ላይ ለሚከሰቱ ማናቸውም ጉዳቶች ተጠያቂው መስተዳድሩና መንግስት ነው፡፡

3ኛ. ሕገ-መንግስቱን የማስከበር ተልዕኮ ያለው ፖሊስ በህገ ወጥ መመሪያ አባሎቻችንን ከማሰርና ማዋከብ እንዲቆጠብ እንዲሁም ህጋዊ መሰረት ያለውን ሰላማዊ ሰልፋችንን ፀጥታ የማስከበር ሃላፊነት እንዳለበት እያሳሰብን ቅስቀሳ በሚደረግበት ወቅት ተገቢውን ጥበቃ በማድረግ ሃላፊነቱን እንዲወጣና የህግ የበላይነትን እንዲያስጠብቅ ከአደራ ጋር እናሳስባለን፡፡ ህዝቡም መስከረም 5 ቀን 2006 ዓ.ም ወደ አደባባይ በመውጣት የተቃውሞ ድምፁን በሰላማዊ መንገድ እንዲያሰማ ሃገራዊ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡

 

             ዘላለማዊ ክብር ለኢትዮጵያ!!!

የአንድነት ፓርቲና የ33ቱ ፓርቲዎች

መስከረም 1 ቀን 2006

አዲስ አበባ

MILLIONS OF VOICE FOR FREEDOM !


የሙስና ነገር (ክፍል ሁለት) በዳዊት ከበደ ወየሳ

$
0
0

የሙስና ነገር (ክፍል ሁለት)
በዳዊት ከበደ ወየሳ

እውነት የማይመስሉ ግን እውነት የሆኑ የሙስና ታሪኮች – በኢትዮጵያ።

አሁን በኢትዮጵያ አቆጣጠር ወደ 2006 ተሻግረናል። ከአመት ወደ አመት ስንሸጋገር ደግሞ ያለፈውን አመት የሙስና ነገር በገደምዳሜ ዳሰስ አድርገን ብናልፍ ክፋት የለውም። በመሆኑም የስራ ባልደረባዬ ክንፉ አሰፋ “ክፍል አንድ” ብሎ በጀመረው የሙስና ጉዳይ… “ክፍል ሁለት” ብዬ እኔ ቀጠልኩበት፤ አንብቡት።

የጉምሩክ ከፍተኛ ሃላፊዎች ሲታሰሩ፤ በየፊናው የነበሩ ጉምቱ ባለስልጣናት መደንገጣቸው አልቀረም። “እገሌስ መቼ ነው የሚታሰረው ወይም የምትታሰረው?” የሚለው ሹክሹክታም ከቢሮ አልፎ በአደባባይ የህዝቡ መነጋገሪያ ሆኖ ሰንብቷል። በዚያኑ ሰሞን ከኢትዮጵያ የመጣ አንድ ዘመዴ ጋር ቁጭ ብለውን ስናወራ፤ “ገብረዋህድ የሚባለውንስ እንኳንም አሰሩት።” አለኝ።

“ምነው?” አልኩት።

“በጣም መጥፎ ሰው ነው” ብሎ ጀመረልኝ – ፊቱን አጨፍግጎ። “መጥፎ ሰው ነው። አንዳንዴ እንደተራ ሰው ሻይ ቤት እና ቡና ቤት ገብቶ፤ የሆነ ነገር አዝዞ ይቀመጣል። ከዚያም አንዱ ተስተናጋጅ፤ ሂሳቡን ከፍሎ ሲወጣ፤ ድንገት ደረሰኝ ይዞ ካልወጣ…  ከመቀመጫው ተነስቶ፤ ‘ሌቦች አጭበርባሪዎች’ ብሎ ይሳደብና ፖሊስ ወዲያው ጠርቶ የንግድ ቤቱን ያሳሽጋል።” (ደረሰኝ ለደንበኛ አለመስጠት ሙስና መሆኑን እዚህ ላይ ጠቅሰን እንለፍ)… እናም ይህ የጉምሩኩ ምክትል ሰውዬ ያላስለቀሰው ነጋዴ የለም።

ደግሞም በነጋዴዎቹ ቢበቃው ጥሩ ነበር። የመስሪያ ቤቱን ሰራተኞች በሙስና እየወነጀለ ያላሳሰረው ሰራተኛ እንዳልነበር፤ የቅርብ ሰዎች ያወራሉ። እዚህ ላይ አንድ አስቂኝ ነገር አለ። ይሄ ለሰማይና ለመሬት ከብዶ ህዝቡን ሲያስለቅስ የነበረ ሰውዬ በመጨረሻ የሱም ቀን ደረሰና ሊታሰር ሆነ። እናም በቁጥጥር ስር በዋለበት ቀን፤ ሁለት የፌዴራል ፖሊስ አባላት ወደ ቢሮው ገብተው በቁጥጥር ስር ሊያውሉት ሲሉ ይደነፋል።

“ማን እንደሆንኩ ታውቃለህ?” ይላል።

“አዎ እናውቃለን!” አሉት። አንድ ሁለት ቃል ከተለዋወጡ በኋላ፤ ልክ እንደ ነጋ ገብረእግዚአብሄር – አንቱ ወደተባሉ ከፍተኛ የህወሃት አባላት ስልክ መደወል ይጀምራል። ከባለስልጣናቱ የሚሰማው ነገር ያልጠበቀው ነበር። በመሃል ፌዴራል ፖሊሶቹ ከቢሮው እንዲወጡ ያደርግና ከውስጥ በኩል የቢሮውን በር ይቆልፈዋል። ፖሊሶቹ ቢያንኳኩ – ቢያንኳኩ የሚከፍት ሰው ጠፋ። የጉምሩክ መስሪያ ቤት ተጨነቀ። በቢሮ አካባቢ ያሉት “በቃ ይሄ ሰውዬ እንደ አጼ ቴዎድሮስ የራሱን ህይወት ሊያጠፋ ነው” ብለው በመስጋት፤ ከአሁን አሁን የተኩስ ድምጽ በጉጉት ይጠባበቃሉ። ሌሎች የግቢው ጥበቃ ሰራተኞች ደግሞ፤ ‘ከፎቅ ላይ ራሱን ወርውሮ ይገድላል’ በሚል ስጋት አንገታቸውን ወደ ፎቁ አንጋጠው፤ ድንገት ከፎቅ ላይ ሲወድቅ ሮጠው እንደኳስ ሊቀልቡት ተዘጋጅተዋል። ይሄ ሁሉ ሲሆን፤ ሰውየው ቢሮውን ቆልፎ ከህወሃት ባለስልጣናት እስከ ጠቅላይ ሚንስትሩ ቢሮ ድረስ ስልክ እየደወለ ነበር።

የደወለላቸው ባለስልጣናት በሙሉ ለራሳቸው በመስጋት የተለያየ ምክንያት እየሰጡ ስልኩን ጆሮው ላይ ዘጉበት። በዚህች ቀውጢ ወቅት በመከላከያ ውስጥ የኮሎኔል ማዕረግ የተሰጣት፤ እጩ ጄነራል ሚስቱም ልታድነው አልቻለችም። ፌዴራሎቹ ጉዳዩን አስመልክተው ወደ አለቆቻቸው ደወሉ። “ሰውየው እራሱን እንዳያጠፋ ስለሰጋን ነው” አሉ።

ከአለቆቻቸው የተሰጣቸው መልስ አጭር ነበር። “እራሱን አያጠፋም። ተጨማሪ ትዕዛዝ እስከሚሰጥ ድረስ እዚያው ቆዩ”።

“ሰራተኛ ሲወጣ፤ እሱ ከቢሮ ካልወጣ ሰብራችሁ ትገባላችሁ” ተባሉ። ፖሊሶቹም ሰራተኛው ከስራ እስኪወጣ መጠባበቅ ጀመሩ። ሰራተኛው ከወጣ በኋላ፤ ፌዴራሎቹ በር የሚሰብሩበትን መሳሪያ እያፈላለጉ ሳለ ገብረዋህድ ከተደበቀበት ቢሮ ሹክክ ብሎ ወጣ።

“ምነው ብዙ የምታስጠብቀን?” ብለው ጠየቁት ፌዴራሎቹ።

“በሰራተኛው ፊት ታስሬ መሄድ ስላልፈለኩ ነው” አላቸው።

ገብረዋህድ በማግስቱ የፈራው ደረሰበት።  ለፖሊስ ቃሉን ከሰጠ በኋላ፤ በሚቀጥለው ቀን የመንግስት ንብረት እንዲያስረክብ ወደ ጉምሩክ ሲወሰድ፤ በሰራተኞቹ ፊት ሁለት እጁን ተጠንጎና በፌዴራል ፖሊሶች እየተጎነተለ መጣ። “ከዚህ በላይ ውርደት?” ብለን ቃሉን አለመጨረሹ ይሻለናል።

ሌላም የሚገርም ነገር አለ። ይሄ ሰው ከመታሰሩ አንድ ወር በፊት በመላው አገሪቱ የሚገኙ የጉምሩክ ባለስልጣናትን በኮንፈረንስ ስብሰባ አድርጎ ነበር። የፈረደበትን የሟቹን ጠቅላይ ሚንስትር ፎቶ በመለጠፍም “በሙስና ለምትጨማለቁት እንደደርግ ጥይት አናጎርሳችሁም፤ እናስራችኋለን።” እያለ ስለመለስ ራዕይ ሲያወራ ነበር። በንግግሩም መጨረሻ፤ (ያን ሰሞን የመለስ ሚስት የምኒልክን ቤተ መንግስት ለቅቃ ነበርና…) “በአሁኗ ደቂቃ የመለስ ዜናዊ ልጆች መኖሪያ ቤት እንኳን የላቸውም። ሜዳ ላይ ነው የቀሩት።” ሲል የዋሆቹ ሲያለቅሱ፤ ነገሩን የሚያውቁ ግን ስቅስቅ ብለው ይስቁ ነበር።

ገብረዋህድ ከታሰረ በኋላ በስሙ የአርሲን ቆዳ ስፋት የሚያህሉ የቤት ካርታዎች ሲገኙ፤ “ምናለበት አንዱን ቤት ሜዳ ላይ ለወደቁት ለመለስ ዜናዊ ልጆች ቢሰጣቸው ኖሮ?” መባሉ አልቀረም።

ወደ አዲስ አበባ ከተማ ሲገቡ፤ ቦሌ መንገድ ላይ ያሉትን ህንጻዎች ከተመለከቱ፤ ህዝቡ ራሱ እንደጎበዝ አስጎብኚ ይነግርዎታል። “ይሄ ህንጻ የጄነራል ጻድቃን ነው። ይሄኛው የጄነራል እገሌ ነው እያሉ፤ መድሃኔአለም ቤተ ክርስቲያን ፊት ለፊት ከሚገኘው ኤድናሞል ህንጻ ጋ ሲደርሱ ደግሞ “ከጎኑ ያለው የሚያምር ህንጻ የጄነራል አባ ዱላ ነበር።” ይሏችኋል።

“አሁንስ የማነው?” ካሉ አስጎብኚዎ የሙስናን ነገር እያጣቀሰ ወሬውን ሊቀጥል ይችላል። እኛም እንንገርዎ – የነ አባ ዱላን ነገር። አባ ዱላ ገመዳ አሁን የፓርላማው አፈ ጉባዔ ነው። ከዚያ በፊት የኦሮሚያ ፕሬዘዳንት፡ ከዚያም በፊት የመከላከያ ሚንስትር፡ ከዚያ በፊት በሻዕቢያ የተማረከ የደርግ ወታደር ነበር… መቼም አንድ ወታደር ለሻዕቢያ እጅ ሰጥቶ ከተማረከ ከዚያ በፊት ምን ነበር? ተብሎ አይጠየቅም። እናም አባዱላ እና በሙስና ስለተሰራው ትልቅ ቤተ መንግስት የመሰለ ቤታቸው ከማውራታችን በፊት፤ ሰውየው ሌሎቹን ጄነራሎች ጭምር እንዴት በሙስና እንዳነካኩ ላጫውታችሁ።

በአንድ ወቅት ለጄነራሎቹ (ያው ከአባ ዱላ በቀር ብዙዎቹ ህወሃቶች ናቸው) አዲስ አበባ ውስጥ መኖሪያ እንዲሰሩ መሬት ተሰጣቸው። የሲሚንቶ እና የሌላ ሌላው ነገር ዋጋ መጨመርን ተከትሎ የብዙዎቹ አቅም የሚችለው አልሆነም። እናም የኦሮሚያ ፕሬዘዳንት የነበሩት አባ ዱላ ገመዳ ከሌሎቹ ጄነራሎች ጋር በመመሳጠር በኦሮሚያ የሚገኙ መሬቶች፤ እየተሸነሸኑ ለጄነራሎቹ በስጦታ መልክ እንዲሰጣቸው አደረጉ። ይህ የተደረገው ያለ ምክንያት አይደለም። በኋላ ላይ ጄነራሎቹ በኦሮሚያ ባለስልጣናት የተሰጣቸውን መሬት እየሸጡ፤ አዲስ አበባ ላይ በተሰጣቸው መሬት ላይ ህንጻ

ከቢሾፍቱ እስከ አዳማ፤ አልፎም እስከ ሻሸመኔ ድረስ ያሉ መሬቶች በዚህ አይነት የሙስና ቅብብሎሽ ለጄነራሎቹ ታደሉ። አባ ዱላ ገመዳ ይሄንን ሁሉ ሲያደርግ፤ ለሱም ትንሽ ጉርሻ ይሰጠው ነበር። ያቺ በጉቦም በ እጅ መንሻም ያገኛትን ገንዘብ ሰብስቦ ቦሌ መድሃኔአለም ፊት ለፊት የተንጣለለ ህንጻ መገንባት ጀመረ።

እንግዲህ ልብ በሉ። በቦሌ መንገድ እርስዎ ብቻ አይደሉም የሚሄዱት- ሟቹ ጠቅላይ ሚንትርም በዚያ መንገድ ብዙ ጊዜ ተመላልሰው ነበር – ያውም መንገድ እየተዘጋ። እናም አስጎብኚው ለርስዎ እንደሚነግርዎ ለመለስ ዜናዊም፤ “ይሄ የእገሌ ነው። ይሄኛው የጓደኛችን እገሌ ነው።” መባሉ አልቀረም። ነገር ግን ሟቹ ጠቅላይ ሚንስትርም ቢሆኑ፤ የስርአቱ ዋነኛ መገለጫ የሆነውን የሙስና አደጋ በዝምታ ሲያልፉት ነበር። የኢህአዴግ ሰዎች ሙስናን እንደጥፋት የሚያዩት ከዚያ ሰውዬ ጋር እስከሚጣሉ ድረስ ነው። እናም ከአባ ዱላ ጋር እስከሚጣሉና የጄነራልነት ማዕረጉን እስከሚገፈፍ ድረስ ምንም አላሉም። በኋላ ላይ ግን… አባ ዱላ ከህወሃት ሰዎች ጋር ሳይሆን ከራሱ ሰዎች ጋር መጋጨት ጀመረ። በተለይም በኦህዴድ ውስጥ ካለው ከነ ግርማ ብሩ ቡድን ጋር ክፉኛ ተጋጨ – የቁርጡ ቀን ሲመጣም በመታሰር፣ ክብርን በማጣት እና ንብረቱን በመስጠት መካከል ዋዠቀ።

በመጨረሻ አባ ዱላ ገመዳ ያሰራውን እና ሊኖርበት የነበረው በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ የወጣበት ባለ ትልቅ ግቢ ቪላ ጥያቄ ውስጥ ገባ። ጸቡ እየከረረ ሲመጣ፤ በመጀመሪያ ደረጃ ያሰራው ትልቅ ህንጻ በሙስና መሆኑን ነገሩት። መጀመሪያ ሊከራከር ፈለገ። በኋላ ላይ ግን ደሞዙና የወጣው ወጪ እንደማይመጣጠን ሂሳቡን ሰርተው ሲያሳዩት፤ “አይ እኔ እንኳን Surprise ላደርጋችሁ ብዬ ነው” አለ።

ኦህዴዶቹም በመገረም፤ “ምንድነው Surprise የምታደርገን?” ሲሉ ጠየቁት።

“ይሄንን ቤተመንግስት የመሰለ ቪላ የሰራሁት ለኔ ሳይሆን፤ ለድርጅታችን ነው።” ብሎ የቤቱን ቁልፍ ሲያስረክብ፤ አጨብጭበው ዝም አሉት። አሁን በቦሌ በኩል ስታልፉ፤ “ይሄኛው የጄነራል አባ ዱላ ነበር” ይሏችኋል። ከርክክቡ በኋላ ግን የኦህዴድ ዋና ጽህፈት ቤት ሆኗል – እውነት የማይመስል የአገራችንን ታሪክ ነው እያወጋናችሁ ያለነው።

ባለስልጣናቱ “Surprise” ከመባላቸው በፊት፤ እዚያው ቤት ምሳም እራት ተጋብዘው በልተዋል። የቤት ምርቃቱ ጊዜ፤ ስጦታ ይዘው መጥተዋል። ጸቡ ሲመጣ ዝምድናው ወደ ሙስና ተቀይሮ፤ አባ ዱላ ገመዳ ቪላ ቤቱን ከነ ሙሉ እቃው የኦሮሚያ ቤተ መንግስት እንዲሆን ሰጥቶ ከመታሰር አመለጠ። የጄነራልነት ማዕረጉን ከመቀማት ግን አልዳነም። ከመከላከያ ሚንስትርነትም ሆነ ከኦሮሚያ ፕሬዘዳንትነት በጥፋት ተወንጅሎ ከተነሳ በኋላ ይህንን ታማኝ ሰው ሙስና የሌለበት ቦታ ሊመድቡት ፈልገው ክፍት የስራ ቦታ ፓርላማ ውስጥ ተገኘ። እናም የፓርላማው አፈ ጉባኤ በመሆን፤ ኢህአዴግን በማገልገል ላይ ይገኛል – አባ ዱላ (ምናሴ ገብረማርያም )።

እንግዲህ ይህ ሙስና የምንለው ነገር… ዋናዎቹን ሰዎች እስካላስከፋ ድረስ፤ በኢህአዴጎች ዘንድ እንደባህል የሚቆጠር ነውር ያልሆነ ተግባር ነው። የሙስና ነገር አውርተን… የኢህአዴግ ሙስና እመቤት ስለሆነችው ወ/ሮ አዜብ መስፍን ሳንጨዋወት ብንቀር እሳቸውም ቅር ይላቸዋልና ስለ ወይዘሮዋ ትንሽ እንዙር።

በአንድ ወቅት ለጄነራሎቹ መሬት ሲታደል ወይዘሮዋ ቦታ አምልጧቸው ኖሮ ተናደዋል። ወደ አዳማም ሆነ ቢሾፍቱ ደውለው ቢጠይቁ፤ “መሬት ተወዲ’ዩ” አሏቸው። ቆይተው ግን በኦሮሚያ ሰበታ ከተማ መሬት መሰጠት መጀመሩን ሰምተው፤ እንዲሰጣቸው ጠየቁና ተሰጣቸው። ከዚያም የሚያውቋቸውን ሰዎች እየላኩ መሬት ያሳድሉ ጀመር። በኋላ ላይ… የሰበታ ከተማ አስተዳዳሪዎች ሁኔታው ሲበዛባቸው፤ በወ/ሮ አዜብ አማካኝነት የሚላኩትን ሰዎች መሬት ከለከሏቸው። በዚህን ጊዜ ወ/ሮ አዜብ መስፍን እሳት ለብሰው፣ እሳት ጎርሰው ለከተማው አስተዳዳሪ ደወሉና ከፍ ዝቅ አድርገው ተናገሩት። በመጨረሻ የሆነው ነገር ነው የሚገርመው… ወይዘሮዋ ዛቻ ቢጤ አሰሙ። እንዲህ ሲሉ።

“እንዲያውም በሰበታ አካባቢ ሙስና አብዝታችኋል ማለት ነው! ሙስና ስላበዛችሁ ግምገማ መደረግ አለበት።”

ወ/ሮ አዜብ እንዳሉትም በህወሃት ሰዎች ታጅበው ሰበታ ከተማ በመገኘት የመንግስት ሃላፊዎችን ከላይ እስከታች አተረማመሷቸው። ለሳቸው መሬት የሰጧቸው ሰዎች ሳይቀር፤ በሙስና ተወንጅለው እየተለቀሙ ታሰሩ። መሃንዲሱ እና መሬት ፈቃጆቹ ሁሉ ተቀፈደዱ። ከዚያም የራሳቸውን ታማኞች ሹመው ሰበታ ከተማን ለቀው ተመለሱ። ባለፈው አመት ኢቲቪ ስመለከት እነዚያ በሰበታ ከተማ “ሙስና ውስጥ አላችሁበት” የተባሉ ሰዎች እያንዳንዳቸው ከአስር አመት በላይ እንደተፈረደባቸው ሰማሁ። በርግጥ ሰዎቹ ሙስና ውስጥ ነበሩበት። ቢሆንም ግን ለወ/ሮ አዜብ መስፍን እና ለሌሎች መሬት ሲሰጡ፤ ሙስና አልተባለም… የአዜብን “ትዕዛዝ አንቀበልም” ሲሉ ግን የጨዋታው ህግ ተቀይሮ፤ ሰዎቹ በሙስና ወንጀል እየተለቀሙ ወህኒ ወረዱ።

መቼም የወ/ሮ አዜብ መስፍን ታሪክ ማለቂያ የለውም። ባለፈው ሰሞን ደሞ፤ አቶ አያሌው የተባሉ ትልቅ ባለሃብት ፍርድ ቤት ቀርበው ሲናገሩ፤ “ክቡር ፍርድ ቤት እኔ ምንም ጥፋት እንደሌለብኝ አቃቤ ህጉም ያውቀዋል። የኔ ጥፋት ከወ/ሮ አዜብ መስፍን ጋር በሽርካነት እንድሰራ ተጠይቄ እምቢ ማለቴ ነው።” ብለው ነበር። አቶ አያሌው በተከበሩበት አገር አስራ ስድስት አመት ተፈርዶባቸው ወደ እስር ቤት መወርወራቸውን ከጥቂት ወራት በፊት ስንሰማ ማዘናችን አልቀረም። እንግዲህ አቶ አያሌው በደርግ የሶሻሊዝም ዘመን ሳይቀር በንግድ ሙያ ውስጥ የቆዩ ናቸው። የደርግ ዘመን አልፎ በዘመነ – ነጻ ገበያ ሲታሰሩ ያልገረመው ሰው የለም።

እዚህ ላይ የምናወራው ላይ ላዩን የምናውቀውን… እውነት የማይመስል፤ ነገር ግን እውነት የሆኑ የሙስና ታሪኮችን ነው። ውስጥ ውስጡን የማናውቀው ብዙ ነገር ሊኖር እንደሚችል ምንም አያጠያይቅም። ሌላ ነገር ትውስ አለኝ። የዛሬ 12 አመት ወ/ሮ አዜብ መስፍን ወደ አሜሪካ ሲመላለሱ፤ ብዙም አይን የሚገቡ ሰው አልነበሩም። ሃብታቸውም ሰማይ አልደረሰም ነበርና ብዙዎች ትኩረት አንሰጣቸውም ኖሯል። ሆኖም እዚሁ አሜሪካ ኮሎምበስ ኦሃዮ ለምትገኘው እህታቸው፤ 250 ሺህ ዶላር ካሽ ከፍለው ቪላ ቤት ሲገዙ ብዙዎቻችን ማመን አቃተን። እናም ‘አዜብ ሙስና ውስጥ የለችበትም’ እያለ ለሚጨቀጭቀኝ ዘመዷ ስልክ ደወልኩና ጠየኩት።

“የምንሰማው እውነት ነወይ?” አልኩት።

“ምኑ?” አለኝ።

“ዘመድህ ካሽ ከፍላ ለእህቷ ቪላ ቤት የመግዛቷ ነገር…” ብዬ ሳልጨርስ፤ የነገሩን እውነተኛነት አረጋግጦ በትህትና ሊያስረዳኝ ሞከረ።

“እሷም ሆኑ ልጆቿ ሲመጡ የሚያርፉበት ቤት ያስፈልጋቸዋል። … ታዲያ ይህን ማድረጓ ምን ያስደንቃል?” የሚል አይነት ምላሽ ሰጠኝ። ለነገሩ ከደጃዝማች ጎላ የሚወለዱ፤ የነአዜብ መስፍን የቅርብ ዘመዶች ብዙ ናቸው። ድርጊቷን የሚደግፉ እንዳሉ ሁሉ፤ በግልጽ የሚቃወሟትም አሉ። ለገንዘብ ሳይሆን ለህሊናቸው ላደሩ ዘመዶቿ አክብሮት እንዳለኝ በዚህ አጋጣሚ ጠቅሼ የውጪ ሃብት ግዢውን ነገር እዚህ ላይ ገታ ላድርገው።

          የ”ደቡብ ክልል” ፕሬዚዳንት የነበሩት የአቶ አባተ ኪሾ ጉዳይም አለ። አባተ ኪሾ  ከወያኔ ሳይጣሉ ከደቡብ በጀት ተመላሽ የሆነ ሰባ ሚሊዮን ብር (70.000.000) ለመንግስት ተመላሽ ሊያደርጉ ሲሉወዲህ በል! የምን መንግስት ነው?” በማለት ወ/ሮ አዜብ ተቀብለው ወስደዋል።  ብሩ ወደ አዜብ ካዝና ይግባ እንጂ የፖለቲካ ቂም የተቋጠረባቸው አቶ አባተ ወደ ወህኒ ከመወርወር አልዳኑም። አቶ አባተ ኪሾ ይህንን ጉዳይ /ቤትም ጭምር ምስክር ሰጥተውበት ነበር።

 

የወ/ሮ አዜብን ጉዳይ ጨርሼ ወደሌሎቹ መሄድ ብፈልግም። ብዙ እውነት የማይመስሉ፤ ነገር ግን እውነት የሆኑ አስገራሚ ነገሮች ታወሱኝ። ስለሁሉም ነገር ምንም ማለት ስለማልችል ጥቂት ነገር ብዬ የሴትዮዋን ነገር ልቋጭ። በኢትዮጵያ የፀረ ሙስና ኮሚሽን ሲቋቋም በዋናነት እንዲሰራ ከታዘዙት ነገሮች አንዱ፤ የመንግስት ባለስልጣናት ሃብታቸውን እንዲያስመዘግቡ ማስደረግ ነው። ይህ ስራ እንደተጀመረ… “አሻፈረኝ አላስመዘግብም” ካሉት ውስጥ ወ/ሮ አዜብ እና የህወሃት ጄነራሎች መሆናቸውን ከዚህ በፊት በሌላ ጉዳይ ላይ ጠቅሼው ነበር። አሁንም ልድገመው። እናም የወ/ሮ አዜብ መስፍን የሃብት መጠንም ሆነ ምንጭ እስካሁን ድረስ በመንግስት ደረጃ አልተመዘገበም። አሁንማ ሴትዮዋ ጥቁር ሲለብሱ፤ ጥቁር ለብሰው የሚያጅቧቸው፤ ሲያስነጥሳቸው መሀረብ የሚያቀብሉ አሽከሮች አላቸው። ሴትዮዋ ከመለስ ዜናዊ ሞት በኋላ እንደጎማ ተንፈስ ብለዋል። ሜጋ ሚሊዮን ዶላር ከሚያንቀሳቅሰው የህወሃት ኤፈርት ሊቀመንበርነት ተነስተው፤ የመለስ ዜናዊ ፋውንዴሽን ዛፍ አስተካይ ከመሆን ያለፈ ስልጣን እንደሌላቸው እየስማን ነው።

 

በሌሎች ላይ የሚደረገውን የሙስና ክስ አመሰራረት እያየን… “የሙስና እመቤቷ ወ/ሮ አዜብ እና ሌሎች የኢህአዴግ ሰዎችስ ተራ መቼ ይሆን?” ማለታችን አልቀረም። ደግሞም “የጉምሩክ ባለስልጣናት ሲታሰሩ ዋነኛውን ሃላፊ አቶ መላኩ ፈንታን ወንጀል አግኝተውበት ይመስላችኋል?” አይደለም። ነገሩ የህወሃቱን ገብረዋህድ ብቻውን ቢያስሩት በህወሃት አካባቢ ከፍተኛ ጫጫታ መምጣቱ አይቀርም። ስለዚህ ከብአዴንም “የአማራ ድርጅት አባል አስረናል” በማለት ነገሩን ለማብረድ የተጠቀሙበት ነው የሚመስለው።

 

ባለፈው አመት ብቻ ምን ያህል ሙስና እንደተፈጸመ እናውጋ እና እንለያይ። ባለፈው አመት (እ.ኢ.አ 2005) ከ1 ሺህ 500 በላይ ጥቆማዎች ለፀረ ሙስና ኮሚሽን ደርሰው በ200 ያህሉ ላይ ክትትል አድርጓል። የሚገርመው ግን ከሁለት ሺህ በላይ ጥቆማዎች ደግሞ፤ ከስልጣኔ በላይ ነው በማለት ባሉበት ትቷቸዋል። (ይህንን መረጃ ያገኘነው ከራሱ ከፀረ ሙስና መስሪያ ቤት ነው።) እነዚህ ከፀረ ሙስና ኮሚሽን አቅም በላይ የሆኑት እንግዲህ፤ የጄነራሎቹ፣ የነአዜብ እና የህወሃት ከፍተኛ ንብረት እና የመከላከያ ጉዳይ መሆኑ ነው።

ለመሆኑ መከላከያ ሚንስቴር መስሪያ ቤቱ በሙስና ተወዳዳሪ ያልተገኘለት፤ ከፌዴራል መንግስት ውጪ የራሱ ባለ አምስት ሆቴል እና ሌሎች የንግድ ስራዎችና ገቢዎች እንዳለው ያውቃሉ? የምናወራው እውነት ስለማይመስሎት፤ የሙስና ታሪካችን ስለሆነ አብረውን ይቆዩ።

 

ፀረ ሙስና ኮሚሽኑ ከስልጣኑ ውጪ ያሉትን ሙስናዎች አይከታተልም። እናም ከዚህ በታች ያሉት ኮሚሽኑ እርምጃ ስለወሰደባቸው ጉዳዮች ነው።

 

ባለፉት ሁለት አመታት ከአንድ ሺህ በላይ የሙስና ክሶች ተከፍተው፤ ጉዳያቸው በፍርድ ቤት ታይቷል ወይም እየታየ ነው። እውነት ከማይመስሉ መካከል አንዳንዶቹን እንጥቀስ። በየሰፈሩ ወጣቶችን ሳያደራጁ፤ ያደራጁ አስመስለው መሬት የወሰዱ የኢህአዴግ  አባላት ብዙ ናቸው። የሃሰት የማህበራት ማደራጃ ሰነድ በማዘጋጀት ግምቱ 25 ሚሊዮን ብር የሆነ መሬት በነዚህ ሰዎች እንደአባት ውርስ ። ከሰላሳ ሚሊዮን ግምት በላይ ያለው 4ሺህ ካሬ መሬትም በ’ነዚህ የኢህአዴግ ሰዎች ያለአግባብ ወደ ግል ይዞታነት ተቀይረዋል ወይም ካርታ ወጥቶባቸዋል፤ አልፎ ተርፎም የገንዘብ ብድር ተወስዶባቸዋል። ግምቱ 842 ሚሊዮን ብር የሆነ መሬትም ያለአግባብ በግለሰቦች እጅ ገብቶ፤ የፀረ ሙስና ኮሚሽኑ የሚያደርገው ጠፍቶት፤ ግራ እንደተጋባ 2006 ዓ.ም. ገብቷል።

 

የኢህአዴግ አባላትና ሹመኞች በመሬት ቅርምት ብቻ አያበቁም። ጉምሩክ መስሪያ ቤት ዋነኛ የገቢ ምንጫቸው ነበር። በኮንትርባንድ የተያዘን ለዋስትና የተያዘን ቦንድ ሰነድ በማጥፋት ገንዘቡን ቅርጥፍ አድርገው ይበሉታል። የኢህአዴግ ወዳጆች ወይም ጉቦ የሚሰጡትን አነስተኛ የታክስ መጠን በማስከፈል ከመቶ ሚሊዮን ብር በላይ ወደ ግለሰቦች ኪስ ገቢ ሆኗል።

 

በመንግስት መስሪያ ቤቶች ትላልቅ ግዥና ሽያጭ ሲደረግ ያለው ማጭበርበር ደግሞ አይን ያወጣ ነው። የአፋር መስተዳድር ቻይናዎች መንገድ እንዲሰሩ ከተዋዋሉ በኋላ የፌዴራሉ መንግስት የሰጣቸውን 10.7 ሚሊዮን ብር እጃቸው አስገብተው ከመብላታቸው በፊት ተይዘዋል። እንዲህ አይነት ብዙ ታሪክ  መዘርዘር ይቻላል። ባለፈው አመት ብቻ ልዩ ልዩ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ባወጧቸው ጨረታዎች እና የሃራጅ ሽያጮች 3 መቶ ሚሊዮን ብር ተጨበርብሮ የተያዙም የተፈቱም ሰዎች አሉ።

 

ከፊንጫ ስኳር ፋብሪካ 75 ሚሊዮን ብር መሰረቁን እንንገርዎና በየመስሪያ ቤቱ እንዲህ ያለው ማጭበርበር ምን ያህል ሊሆን እንደሚችል እርስዎ ይገምቱ።

 

“በኢትዮጵያ አየር መንገድ በኩል የሚመጡ ተጓዦች ንብረት መጥፋቱንስ ሰምተው ይሆን?” አዎ ባለፈው አመት ብቻ፤ ከሰባት ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያላቸው ንብረቶች እና ሻንጣዎች ጠፍተዋል።

 

“ጉድ ሳይሰማ መስከረም አይጠባም” ነው የሚባለው… እንዲህ እንዲህ እያልን፤ የዳኛውንም፣ የጉቦኛውንም ታሪክ እያወራን ከቀጠልን ጊዜና ምሽቱ ላይበቃን ነው። ስለዚህ የሰማነውን በልቦናችን ያሳድርልን በማለት ልንለያቹህ ነው። ጊዜ አግኝተን እንደገና ከተጨዋወትን ከአጼ ምኒልክ ቤተመንግስት ስለተሰረቁት የወርቅ ሹካ እና ማንኪያዎች ጭምር እናወጋለን። እንደገና ከተገናኘን የአጼ ኃይለስላሴ የወርቅ ቀለበት ስርቆት እንጨዋወታለን። አረ ሌላም አለ። የአጼ ምኒልክን ሽጉጥ ሰርቆ፤ መጠጥ ቤት ሲፎልል የነበረን አንድ የኢህአዴግ ኮሎኔል ኢትዮጵያ ውስጥ በሚታተመው ጋዜጣዬ ላይ አጋልጠነው ነበር። በአገራችን የሚፈጸመው እውነት የማይመስለን የኢህአዴግ ሙስና ማብቂያ ያለው አይመስልም። በዚሁ እንሰነባበት… መልካም አዲስ አመት።

 

Pen

በበዓል የረሃብ አድማ!! –ርዕዮት ምን ልትነግረን ነው?

$
0
0

ከዳዊት ሰለሞን (ጋዜጠኛ)

በብሄራዊ በዓላት ቀን በአብዛኛው ከወደ እስር ቤት የሚሰማው ዜና አስደሳች ነበር፡፡ይህንን አጼዎቹ ፣ሰው በላው የደርግ ስርዓትና ብሶት ወለደኝ ያለን ኢህአዴግ ሲያደርጉት ቆይተዋል፡፡በዘንድሮው አዲስ አመትም የመንግስትን ይቅርታ በማግኘት ከወዳጅ ዘመዶቻቸው የተቀላቀሉ ስለመኖራቸው ተሰምቷል፡፡በአዲሱ ዓመት ይቅርታ ከተቸራቸው እስረኞች መካከል ታዋቂ ፖለቲከኞች፣አክቲቪስቶችና ጋዜጠኞች አለመኖራቸው ተፈቺዎቹ በደረቅ ወንጀል ታስረው የነበሩ መሆናቸውን ለመናገር ብዙ መድከም አይጠይቅም፡፡
መንገስት ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ፣ሂሩት ክፍሌና ዘሪሁን ገ/እግዚአብሄር አቅርበውት ለነበረ የይቅርታ አቤቱታ የእምቢታ ምላሽ መስጠቱም ይቅርታ የሚገባውና የማይገባው በመንግስት ማውጫ ውስጥ ስለ መኖሩ ማሳያ ነው፡፡የይቅርታው ጉዳይ ለጊዜው ይዘግይልንና በጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙ ላይ በበዓል ቀን ስለ ተፈጸመ ግፍ ላካፍላችሁ፡፡

 ጋዜጠኛ ርዕዮት ዓለሙ

ጋዜጠኛ ርዕዮት ዓለሙ


ጋዜጠኛዋን በበዓሉ ዋዜማ ለመጠየቅ ወደ ቃሊቲ አምርተን ነበር፡፡በመጠየቂያ ሰዓት መድረስ የቻልን ቢሆንም ጥበቃዎቹ ‹‹ርዕዮት የምትጠየቀው በዋናው በር ሆኗል፡፡ስለዚህ ወደ ዋናው በር ሂዱ›› አሉን፡፡ዋናው በር ፈጣን ተራማጅ በ10 ደቂቃ የሚደርስበት በመሆኑ ሰዓቱ እንዳይረፍድና እንዳንከለከል በማለት መሮጥ ጀመርን፡፡
ዋናው በር ግብረ ገብነት አልያም ፖሊሳዊ ስነ ምግባር በዞረበት ለሰላምታ እንኳ አግኝቷቸው የማያውቁ የሚመስሉ ጠባቂዎች ‹‹በዚህ በኩል እስረኛ አይጠየቅም ሂዱ ››አሉን፡፡ግትር ብለን በዚህ በኩል ግቡ ተብለናል አልን፡፡ሰዓቱ እየሄደ ፖሊሶቹም በአቋማችን የበለጠ በመበሳጨት እየዛቱ ነው ፡፡በመካከሉ የርዕዮት ታናሽ እህት እስከዳር አለሙና እጮኛዋ ስለሺ ሀጎስ ከግቢው ውስጥ እየተጣደፉ ወጡ፡፡
ስለሺ አንገቱን አቀርቅሮ እጆቹን እያወናጨፈ ብቻውን ያወራል፣እስከዳርን በሙሉ አይን ማየት ያስፈራል፡፡ ፊቷ በርበሬ መስሎ በእንባ ጎርፍ እየታጠበች ነው፡፡አብሮኝ የነበረው ሰውና እኔ ለመግባት እናደርግ የነበረውን ትንቅንቅ በመተው ሁለቱን ለማጽናናት እና ምን እንደተፈጠረ ለማወቅ መወትወቱን ተያያዝነው፡፡
ርዕዮት ቤተሰቦቿን እንዳገኘች‹‹ያለሁበት ሁኔታ አስቸጋሪ ነው፣ችግር ውስጥ ነኝ››ትላቸዋለች፡፡በዚህ ወቅት በዙሪያዋ የነበሩ ሴት ፖሊሶች ጋዜጠኛዋ ላይ በመጮህ ‹‹ስለ ራስሽ ብቻ አውሪ››ይሏታል፡፡
‹‹የነገረችን እኮ ስለ ራሷ ነው››የእስከዳር ምላሽ ነበር፡፡በዚህ መሃል በጊዜያዊነት የሴቶች ዞን ሃላፊ የሆነች ፖሊስ ‹‹እናንተ አቅማችሁ ጋዜጣ ላይ ነው ከፈለጋችሁ ሂዱና እንዳንጠይቃት ተከለከልን በሉ፡፡››በማለት በዚህ ቦታ ለመጥቀስ ኢትዮጵያዊ ጨዋነት የሚያቅበንን የስድብ መዓት በስለሺ ፣በርዕዮትና በእህቷ ላይ ታወርዳለች፡፡

ርዕዮት ሁኔታውን መቋቋም ተስኗት ሃላፊዋን ለምን እንዲህ አይነት በደል እንደምትፈጽምባት ለመጠየቅ ስትሞክር እየገፈታተሩ ወደ ውስጥ እንድትገባ በማድረግ እነ ስለሺን ግቢውን እንዲለቁ ያደርጋሉ፡፡
በንጋታው መስከረም 1/2006 ነው፡፡የመንግስት ሃላፊዎችና የሃይማኖት አባቶች የቴሌቭዥኑን መስኮት በአዲስ አመት ቀና መልዕክት አጨናንቀውታል፡፡አዲስ ቀን አዲስ ገጠመኝ እንደሚፈጥር ተስፋ ያደረጉት የርዕዮት ቤተሰቦች ከቃሊቲ አልቀሩም፡፡ነገር ግን የሰሙት ነገር በቀኑ እንጂ በአስተዳደሩ መካከል ለውጥ ወይም ዕድሳት አለመኖሩን ነው፡፡ለካ የአዲስ አመት በጎ መልእክት የሚያስተላልፉልን መሪዎቻችን ያሉት‹‹በድሮው ቀን ነው፡፡››
ርዕዮትን እንዲጠይቁ የተፈቀደላቸው ‹‹እናቷ፣አባቷና የነፍስ አባቷ ብቻ ናቸው››እነ ስለሺ ከቃሊቲ ሃላፊዎች ዛሬ ያደመጡት መንፈስ ሰባሪ ቃል ነው፡፡የህግ ባለሞያው አቶ አለሙ ጌቤቦ ድርጊቱ ህገ መንግስታዊ ጥሰት እንደሆነ በመግለጽ ቃሊቲ ደርሰው ልጃቸውን ሳይጠይቁ ተመልሰዋል፡፡ወላጅ እናቷ ያመጡትን ምግብ ለማስገባት ቢሞክሩም ርዕዮት በቃሊቲ የሴቶች ዞን ጊዜያዊ ሃላፊ እየደረሰባት የሚገኘውን ህገ ወጥ ድርጊት ለመቃወም የርሃብ አድማ በመጀመሯ እናት ያመጡትን ምግብ የሚቀበላቸው አላገኙም፡፡
ወዳጄ ስንቶቻችን ነን አዲሱ ዓመት በጾም ቀን ዋለ ብለን የተከፋን?ይህው እንግዲህ በዓሉን ርዕዮት በርሃብ አሳልፋዋለች፡፡
የርዕዮት የርሃብ አድማ መልእክቱ ግልጽ ነው፡፡አቅም ያላት በራሷ ላይ በመሆኑ ራሷን በመቅጣት ህገ ወጦችን እምቢ አለቻቸው በዚህ ሰላማዊውን ታጋይ ማህተመ ጋንዲን መሰለችው፡፡ሰዎቹ እየበሉ በርሷ ላይ የሚፈጽሙት በደል እየተራበች በምታስተላልፈው መልእክት የህሊና ርሃብተኞች መሆናቸውን ይነግራቸዋል፡፡
ከቃሊቲ ውጪ ያለንም ምግብ ወደ አፋችን ባስጠጋን ቁጥር ርዕዮት የቃሊቲ አጥር ሳይበግራት ትመጣብናለች፡፡በምግብ ብቻ በማይኖርባት አለም በምግብ ብቻ ለመኖር ለምናደርገው ከንቱ ሩጫም ርሃቧ ትልቅ ደወል ይሆንብናል፡፡

ገድሎ ለቅሶ የሚደርሰው ስርዐት ሞቶ ቀብር የምንወጣለት አዲስ አመት ይሁልን

$
0
0

Melak addis  ametመቸም የዘመን ዑደት ማለት አሮጌው አልፎ አዲሱ የሚተካበት፣ ዘር አፈር ቅሞ ወሀ ጠጥቶ በቅሎና አብቦ የሚያሸትበት መስከረም ማለትም አይደል? አዎ አዲስ ዘመናችን ምድሪቱ ጭጋግን ለብሳ፣ አራዊቱ ያጠራቀሙትን ስብ እያቀለጡ የሚኖሩበት፣ አእዋፍ ስደት የሚጀምሩበትና የሰው ልጅ አንደ በቆሎ በልብስ የሚጠቀለልበት የበረዶ ወቅት ባለመሆኑ እርግጥም አዲስ አመት ነው። በምንም መስፈርት በማንም መለኪያ ዘመን አቆጣጠራችን ለኛ ተገቢም ትክክልም ነው። አዲስ አመት ማለት ለኛ ለኢትዮጵያውያን ተስፋ ማለትም ነው።

ታድያ ተስፋ ላይ ለቅሶና ቀብር እንዴት ርዕስ ሆነ ማለታችሁ አይቀርም። አዎ ሸፍጥ ሞቶ ሀቅ ቀብር ቢወጣና ለእውነት ኖረን ስለ ዕውነት ብናልፍ፤ በዚህ የአመታት ቅብብሎሽም እንደ አደይ አበባ ሁሉ የተስፋ ብስራት ቢያሸትልን ምን ይለናል? የሚል መንደርደርያ ነው የዚህን አይነት ርዕስ ያስመረጠኝ። አዎ እነዚህ አዲሶቹ ገድሎ ቀብር ወጪዎች ‘ተረትና ማቅራራት’ የአማራ ነው እንዳለው አስተኳሻቸው ገድለው አያቅራሩም። በፊት በረሃ እያሉ እርግጥ ነው በአንድ ጥይት 10 ሰው መደዳውን እንደሚገድሉ ተራራው እንደሚንቀጠቀጥላቸው ነግረውን ነበር። ‘ፍሬንድሊ ፋየር’ የምትለውን ብልጥ ቃል መጠቀም የጀመሩት ግን ያኔ ‘ፍሬንዶቻቸውን’ እያጋደሙ ሲያርዱ ነበር። እድሜ ለገብረመድህን አርአያ አስገድሎ አሸርጦ ማልቀስን በሜጋ የፊልም ቅንብር ሀውዜን ላይ መተወናቸውን ነግሮናል። አተረፉበት ነው የሚባለው! ከበሩበት እንጂ ሸገር ይዞአቸው የገባው ሞት የሀውዜኑም አይደል? ከዚያ በሁዋላ ያፈነገጠውን ሁሉ እርድ ያደርጉና ጉድ ተሰራን? ገዳዩን ለማግኘት የማንፈነቅለው ድንጋይ የለም ብለው አደባባይ ይምላሉ።

በሁዋላ ግን የፈነቀሉትን ድንጋይ መቃብሩ ላይ ቆልለው ወሬውንም ያጠፉታል። አይንአውጣ ስለሆኑ ለቅሶ ሁሉ ይደርሳሉ። ስፍስፍ ብሎ የሚያለቅስና ሁዋላ አደጋ የሚያመጣ የሚመስላቸውን መንጥረው ለማባረር የሚጠቀሙበትም ይመስላል። ይህ ወንጀላቸው ወደ ህግ ባይመጣም እንኳ ሕሊናን መበጥበጡና ነገም ለኔ አይመለሱም የሚለው ፍርሀት መኖሩን ከሰዎቹ ፊት ማንበብ ይቻላል። ይህ ጥርጣሬና ፍርሃት ፊታቸውን አበላሽቶታል።

የሆነ እርኩስ መንፈስ የተጠናወተው የሚመስል ቅብዝብዝ ዐይኖች አላቸው። የተሸበረ ፊ የሌለው ባለስልጣን እኮ የለም። አዎ የሰው ደም ያቅበዘብዛል። እነዚህ በጎደለ የተተኩ ከበረሀኞቹ በላይ በረሀኛ የሚመስሉትም ቶሎ የደለበ ግን መታረጃውን ያየ ሰንጋ መስለዋል የሚሉም አሉ። አሁን በቀደም ሼክ ኑሩን መስዋዕት ሲያደርጓቸው ገድሎ አልቃሾቹ መስጊድ እንደጧፍ ሲነድ ቤተክርስትያን እንደ ደመራ ቦግ ሲል ሕዝቡ ሲተራረድና እነሱ ገላጋይ ሆነው ሲወጡ የሚያሳይ ባለቀለም ሕልም አይተው ነበር። ሕዝቡ ግን አረ ቀልዳችሁን አቁሙ ብለው ‘የሞኝ ለቅሶ መልሶ መላልሶ’ የሚል የአማራ ተረት ተረተባቸው ሲባልም ሰምተናል። አዎና አርባ አመት ሙሉ ገድሎ ማልቀስ እንዴት ይቻላል? ማነው ስሙ አንድ አስለቃሽ ጋዜጠኛ ወደ ወሎ ሄዶ የ’አይዶል ሾው’ ቢሆን “ለዛሬው አልተሳካልህም” የሚያስብል ሳይጀመር ያለቀ ዘገባ አቅርቦ ነበር። ከዚህ የበለጠ ጭካኔ መቸም የለም።

ለቅሶ ላይ መፈክር ሲያሰሙ እንዲውሉ አደረጋቸው። ውሸታቸው ወንዝ የመሻገር አቅም ስለሌለው ውሸቱን በውሸት ለመሸፈን አሁን መዘዙ ለሼኩም ልጅ አልቀረለት መታሰርና መጋዝ ውስጥ ወስጡን ሌላ ሞት መደገስ ሆነ። የሰለቸንም ይኸው ነው! ዘዴውም ጃጀ እንደ ተሰነጣጠቀ ሽክላ በድምጽ ሲፈርስም አየነው። አሁን አስተኳሹ ብቻ ሳይሆን ስርዐቱም ሞቱን በጸጋ ሊቀበል ይገባዋል። ብዙ የለቅሶን ወሬ ወደ የመልካም ምኞት መግለጫ እንቀይረውና በሚቀጥለው አመት ገድሎን ለቅሶ የሚወጣው ጎጠኛና ወሮበላ ስርዐት ሞቶ ቀብር የምንወጣለት ይሁን ብለን እንመራረቅ። እንዲህ እያልን ምክርም እንምከር “ከነሱ ጋር በልቶ በሰላም ተኝቶ ማደር የለምና በቁልቋል የተመሰልክ ተላላ ሆይ ይህንን አጋም ተጠግተህ እድሜ ልክህን አታልቅስ።” ብለን። የፍቅር አደይ አበባ የተነጠፈባት፣ የተስፋ ቀስተ ደመና የተዘረጋባት፤ ፍትህ፣ ነፃነትና እኩልነት መለያዋ የሆነች ውብ ኢትዮጵያ የመልካም አዲስ አመት ምኞታችን ትሁንልን እውነትም እናድርጋት።
ዳኛቸው ቢያድግልኝ
biyadegelgne@hotmail.com

የአርቲስት ሻምበል በላይነህ አገራዊ ስራዎች አርአያነት –“ወጣቱ አንበሳ ላገርህ ተነሳ…” (ከሉሉ ከበደ)

$
0
0

shambel belayeneh
ሉሉ ከበደ (ጋዜጠኛ)

ውድ ኢትዮጵያን ወገኖቼ እንኳን ለአዲሱ አመት አደረሳችሁ። እዲሱ አመት ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ታላቅ ብስራት ይዞ የሚመጣ ይሁን። ያለምንም ደም መፋሰስ ይህ ዘረኛ የወያኔ ገዢ ቡድን መቃብር ገብቶ፤ ዘረኝነት፤ ጎጠኝነትና በታኝነት ከምድራችን ጠፍቶ፤ የኢትዮጵያ ህዝብ ተፋቅሮ ተከባብሮ፤ ሲያጠፉ የሚቀጣቸውን የሚሽራቸውን፤ ሲያለሙ የሚሾማችውን የሚሸልማቸውን መሪዎች በድምጹ መርጦ፤ የሚኖርበት፤ ኢትዮጵያዊ ሁሉ ከዘር ማንነቱ በፊት በኢትዮጵያ ሲምል ሲገዘት የምናይበት፤ ዜጎች ሁሉ ለሀገሬ፤….. ለወገኔ.. እያሉ ሲተጉ፤ ለጋራ እድገትና ብልጽግና ሲጓጉ….አንተ ትብስ አንቺ ትብሽ እያሉ አንዳቸው ላንዳቸው ሲሞቱ የምናይበት የተአምር ዘመን ይሁንልን,….ዘረኞች ለአንዴና ለመጨረሻ የሚጠፉበት ዘመን ይሁንልን….2006. አሜን!
አርቲስቶች የተሰጥኦና የህዝብ ሁለንተናዊ ባህልና ወግ፤ እናም የህዝብ ድጋፍና አድናቆት ውጤቶች እንደ መሆናቸው፤ ስራዎቻቸው ሁሉ የህብረተሰብ ህይወት ነጸብራቆች የመሆን ተፈጥሮአዊ ግዴታ አለባቸው። ሰላምና ጦርነት፤ ድልና ሽትንፈት፤ ደስታና ሀዘን፤ ፍቅርና ጥላቻ ምን ጊዜም ከሰው ልጅ ጋር የሚኖሩ ክስተቶች በመሆናቸው፤ ሰውም በጥብበ ስራዎቹ ውስጥ እነዚህን ባህሪያት እያንጸባረቀ፤ ይማማርባቸዋል። ይዝናናባቸዋል። ያስተላልፋቸዋል። ለሚከታተል ትውልድ የታሪክ መንገሪያም ያደርጋቸዋል ።
ጥበብ የአንድ ህብረተሰብ የስልጣኔ፤ የባህል፤ የሳይንስ፤ የፖለቲካ፤ የሁለንተናዊ እድገት ነጸብራቅና ማሳያም ነው። ጭቆናን ለመታገል፤ ፍትህ ርትእ እንዲሰፍን ህዝብን መቀስቀሻና ማስተማሪያ መሳርያም ነው። ትያትር፤ ስነጽሁፍ፤ ሙዚቃ፤ወዘተ…የህዝብን ንቃተ ህሊናና ታሪካዊ ሁለንተናዊ እውቀት እንደሚያጎለብቱ የሚያጠያይቅ ነገር የለውም።
በሀገራችን የወኔ ስራት ከሰፈነ ያልፉት ሀያ ሁለት አመታት ወዲህ ኢትዮጵያውያን አርቲስቶች አድሎን፤ ዘረኛነትን፤ የመብት ረገጣን በመታገል ረገድ ማን ምን አስተዋጾ አበረከተ ብለን የመረመርን እንደሆን፤ የተወሰኑ ጠንካራ አርቲስቶች እንዳሉን ብናውቅም፤ አሰሩትም ፤አንገላቱትም፤ ሰደቡትም አዋረዱት፤ ስለመከረኛው የኢትዮጵያ ህዝብ አለቀሰ አንጎራጎረ፤ መከረ አስተማረ፤ አጽናና እንጂ ለወያኔ ስራት አድሮ የወያኔ ፕሮፓጋንዳ ማይክራፎን አልሆነም። የሚወዳት ሀገሩንም ጥሎ አልሄደም….ማን?… ሀዋርያውን ብላቴና ቴዲ አፍሮን ዙፋኑ ላይ እናስቀምጠዋልን።
አርቲሥቶች ህዝባዊ ሀላፊነት አለባቸው። ይህም ማለት በጥበብ ስራዎቻቸው የሚያገለግሉትን ህብረተሰብ የሞያ ስነምግባርን በጠበቀ መልኩ፤ ማህበራዊ፤ ባህላዊ፤ ኢኮኖሚያዊ፤ ከባቢያዊ ብሎም ፖለቲካዊና አስተዳደራዊ ህጸጾችን እያፈነፈኑ፤ ነቅሰው እያወጡ፤ በብሩሽ በዜማ በግጥም እያዋዙ ማዝናናት፤ ህብረተሰብን ማስተማር፤ ማንቃት፤ የሞራልና የዜግነት ግዴታ ሊሆንባቸውም ይገባል።

አርቲስት በአድናቂዎቹ ልብ ውስጥ የዘራው ፍሬ በአንድ ወይ በሌላ መልኩ ውጤት ማፍራቱ አይቀርም። የህውሀት ካድሬዎች ፖለቲካ አስተምረው፤ አንቅተው፤ ካሸፈቱት የትግራይ ወጣት፤ በዘፈን በጭፈራና በቀረርቶ የሸፈተው ሳይበለጥ አይቀርም።
ተወዳጅ አርቲስቶች ከአንድ ጠንካራ ፖለቲከኛ የበለጠ ድምጣቸው በአድናዊዎቻቸው ዘንድ ይሰማል።
ክቡር ለሆነው የሰው ልጅ ሰባዊ መብትና ነጻነት ጥብቅና የቆሙ የጥበብ ሰዎች እንደ ነጻ አውጭ አርበኛ ሲሞገሱ፤ ሲወደሱና ሲመለኩ ይኖራሉ።
በሌላ መልኩ አድርባይ ፤ እበላባይ አርቲስቶችን፤ አንባ ገነኖች፤ ህዝብን በዜማና በጥበብ እንዲያደነዝዙላቸው ማበረታታት ማስገደድም የተለመደ ነው። እንዲመለኩ እንዲዘመርላቸው፤ መልካቸው አምሮ እንዲሳልላቸው፤ የሚገዟት አገር በምስላቸው እንድትሸፈን ያስደርጋሉ። የተለመደ ነው። የመለስ ዜናዊ ፎቶ ከዚያች ቅዱስ ምድራችን ተለቅሞ ይልቆ ይሆን?
ወያኔ ወደ ስልጣን የመጣ የመጀመሪያዎቹ አመታት እንደነጻ ፕሬስ ጋዜጠኞች በርካታ አርቲስቶች ማለት ይቻላል፤ የአንድነትን ጥቅም፤ በዘር የመከፋፈልን ጉዳት፤ በዜማዎቻቸው ለማስገንዘብ ሞክረዋል። ከፊሎቹ ከልባቸው በራሳቸው ሰብእና ውስጥ ካላቸው ኢትዮጵያዊ ስሜት ተነስተው እንደቴዲ አፍሮ አይነቶቹ በሀገራቸውና በህዝባቸው ጉዳይ ላይ የማይናወጥ ጠንካራ ወገንተኝነት እንደያዙ ዘልቀዋል።
አንዳንዶች ደግሞ በወቅታዊ የህዝብ ብሶት ላይ ያተኮረ ስራ ማቅረብ ገበያ ያስገኛል ብለው በማመንም ሊሆን ይችላል፤ የህዝቡን ብሶት የሚኮረኩሩ ስራዎችን አቅርበው የተቸራቸው ድጋፍና ጭብጭባ ሳያባራ፤ ሶስት መቶ ሰላሳ ዲግሪ ተሽከርክረው፤ በአንዲት ቀን ጀንበር ወደ ካድሬነት የተለወጡ አሉ። ሰለሞን ተካልኝ ተገፋን ሲል በዘመረበት አፉ ነው ስለመለስ ዜናዊ ቅንድብ ማማር ማላዘን የጀመረው።
ገናናዋ የደቡብ አፍሪካ ተወላጅ ማሪያ ማኬባ እንደ አውሮፓውያኑ ዘመን አቆጣጠር 1963 ዓ ም ለተባበሩት መንግታት ድርጅት የደቡብ አፍሪካው የነጮች መንግስት ያሰፈነው የአፓርታይድ ስራት፤ በሀገሬው ተወላጅ ላይ እያደረሰ የነበረውን ስቃይ በመመስክሯ ነበር የገዛ አገሯን የዜግነት መብት ገፏት፤ ካገሯ እንድትሰደድ ያደረጋት አፓርታይድ። ማሪያ ለስርአቱ ያጎበደደችበት ጊዜ አልነበረም። በዜማዎቿ ህዝቡ ለነጻነቱ እንዲታገል ታበረታታ ትቀሰቅስ ነበር።
ከዚያ በኋላ ለሰላሳ አመታት በኖረችበት የስደት ዓለም፤ በዜማዎቿ ፤ በንግግሮቿ፤ አፓርታይድ ምን አይነት ስራት እንደሆነ፤ በደቡብ አፍሪካ ህዝብ ላይ ምን አይነት ግፍ እንደሚፈጸም ስትነግር፤ የደቡብ አፍሪካውያንን ባህሎችና ልምዶች ስታስተዋውቅ ኖረች።
ቁጥራቸው በቀላል የማይገመት ኢትዮጵያን አርቲስቶች ሀገራቸውን ጥለው በውጭው ዓለም ለመኖር ሲወስኑ ጥቂቱ፤ የስራቱን እኩይ ተግባራት እየኮነኑ የህዝባቸውን መከራና ስቃይ በማስተጋባታቸው የዘረኛው ህውሀት ቡድን ሰለባ በመሆናቸው ለስደት ተዳርዋል። ከነዚህም ታማኝ በየነ በዋናነት ይጠቀሳል። ሌሎችም የተሻለ ህይወትና ኑሮ ፍለጋ ያተርፈናል ወዳሉት አህጉር ተሰደዋል። ይሁንና እነዚህ አርቲስቶች ሀሳብን እንደልብ መግለጽ በሚቻልበት ሀገር ውስጥ የመኖራቸውን ያህል ኢትዮጵያ ውስጥ እየደረሰ ያለውን ሁለንተናዊ ጥፋትና የሰብአዊ መብት ረገጣ፤ በጥበብ ስራዎቻቸው በመዋጋት ረገድ የዜግነት ግዴታቸውን እየተወጡ ነው ወይ?
ከቅርብ አመታት ወዲህ ሀገር ቤት ያሉ አርቲስቶች እጅግ በሚያሳፍርና ለማመን በሚያዳግት መልኩ፤ የኢትዮጵያን ህዝብ ክደው፤ የወያኔ የፕሮጋንዳ እቃና አጫፋሪ ሆነው፤ የገዛ ሀገሩን ባንዲራውንና ወገኑን ክዶ፤ ስለ ዲሞክራሲ የተናገረውን፤ ስለመብት የተናገረውን፤ የጻፈውን ሁሉ በመጨፍጨፍና ወህኒ በማጋዝ አለም አቀፍ ዝና ላተረፈው መለስ ዜናዊ ፤ የወርቅ ብእር ሽልማት መስጠት ፤ የኢትዮጵያን መፍረስና የአንድን ዘር የበላይነት ተቀብሎ፤ በሎሌነት ለማደር ከመዘጋጀት ውጭ ምንም አይነት መልእክት ያለው ተግባር አልነበረም። ስመጥሩና እጅግ ተወዳጅ የነበሩ አርቲስቶች ዛሬ ወደ ነፈሰበት አዘንብለው፤ ስለወያኔ ስራት ና መሪዎች መልካምነት የምስክርነት ቃላቸውን ሲሰጡ መስማት ጥበብ በኢትዮጵያ ውስጥ መዝቀጧንና ተጠባቢውም በአድርባይነትና እበላባይነት ሰብእና ውስጥ መስጠሙን ያመለክታል።
በራሱ ሩጫና ጥረት የሚተዳደር አዝማሪ የህዝብ ግጥም እየተቀበለ ዜጎችን ማዝናናት ያልቻለበት ደረጃ ላይ መደረሱ፤ ያስደነግጣል። ልማታዊ ግጥም እንጂ መቀበል አለመቻሉ፤ ወያኔ የኢትዮጵያን ህዝብ ምን ያህል አካሉንም ህሊናውንም እንደገዛው አመላካች ነው። ይህ ቡድን እምን ድረስ ዝቅ ብሎ የኢትዮጵያን ህዝብ ለመቆጣጠረ እየሞከረ እንዳለ የሚያስገነዝብ ሁኔታ ነው።
ሀተታውን እዚሁ ላይ ላቁመውና ዋናው የርእሴ ጉዳይ ወደ ሆነው እንደ ማሪያ ማኬባ በተሰደደበት የባእድ አገር ፤ በሚያውቅበትና በሚችለው ሙያው እናት ሀገር ኢትዮጵያን የወረራት ህውሀት ዘረኛ አስተዳደር በሀገርና በህዝብ ላይ እያደረሰ ያለውን አደጋና ጥፋት በዜማው እየነገረ፤ እየመከረ፤ የሚበጀውን እያመለከተ ትግሎን ስለተያያዘው አርቲስት ሻንበል በላይነህ ስራዎች ላወሳ እሻለሁ።
ውድ አንባቢያን አርቲስቱ ባልፉት አመታት የተጫወታቸውን በርካታ ቀስቃሽ ዜማዎች ሁሉ በዚህ አጭር ጽሁፍ ውስጥ አካቶ ለማመላከት አይቻለኝም ። ለዛሬ በቅርቡ ካወጣቸው ሲዲዎች “ በቁም እንዋደድ እናም ሀይለስላሴ” የሚል መጠሪያ ከሰጣቸው ሁለት አልበሞቹ ውስጥ በሀገራችን ባለው ወቅታዊ እውነታ ላይ ያጠነጠኑ ቀስቃሽ ግጥሞቹን፤ ከየዘፈኑ የተወሰኑ ስንኞች እያወጣሁ ያሰውን ሁኔታ እንዴት ቁልጭ አድርጎ እንዳስቀመጠው ለማመላከት እሞክራለሁ፤ ሌሎች አርቲስቶቻችንም ወቅታዊውን ሁለገብ ትግል ለማገዝ በዜማዎቻቸው ህዝቡን ለነጻነት ማነሳሳት እንዲጀምሩ ጥሪ ለማቅረብ እሻለሁ። ከንግዲህ ኢትዮጵያውያን በሚችሉት ሁሉ ወደ ትግሉ በመቀላቀል የወያኔን ስርአት እስትንፋስ ማሳጠር ግድ ይላል።
ይሰማ ድምጻችን…. ግጥም አይገልጥም፤ ዜማ..ሻንበል በላይነህ
….እኛ አንበተንም፤ እኛ አንበተንም፤ ሙስሊም ክርስቲያኑ ልዩነት የለንም።
ዛሬም ቢሆን እንደበፊታችን፤ ተጠናክሮ ይህ አንድነታችን፤
ሙስሊም ክርስቲያኑ በለቅሶም በሰርጉም፤ አብረን እንኖራለ በክፉም በደጉም። …..
አዎ!.. “..ተነሱ ውጡና እስላም ወንድሞቻችሁን ስደቡ፤ እርገሙ፤ መንግስት ሊሆኑባችሁና ሊያጠፏችሁ ነው “ እያለ የኢትዮጵያን ክርስቲያኖች እያስፈራራና እየዛተ አደባባይ የሚያወጣ፤ በመንግስት ቅርጽ መደራጀት የቻለ የወንጀለኞች ቡድን፤ ምናልባትም በዛሬዪቱ አለማችን በአይነቱ የተለየ የሆነ፤ መንግስት የሚመስል የወንጀለኞች ቡድን ፤ ሀገር በተቆጣጠረበት፤ ሻንበል በላይነህ በምርዋ ድምጹ በጣፋጭ ዜማው ያንቆረቆረልን መልእክት ህዝባዊ እንጉርጉሮ መሆን ያለበትና ሁሉም ኢትዮዝፕያዊ ሊያንጉራጉረው የሚገባ የሙስሊም ክርስቲያኑን መተላለቅ ለሚናፍቀው ወያኔ ጠንካራ ምላሽ ነው።

ህዝበክርስቲያን፡ መስሊሙ፤
ሁሌም በውኑ፡ በህልሙ፤
ያስባል ስለሰላሙ ….
ችግሩ የኢትዮጵያን ህዝብ ከማሸበር ተግባሩ ያልታቀበው የወያኔ ቡድን ነው እንጂ፤ ህዝቡ ስለሰላሙ ያስባል። በአስራ አምስተኛው ክፍለ ዘመን ግራኝ አህመድ ሙስሊሙን ይዞ ያን ያክል ጥፋት ሲያደርስ፤ ሙስሊሙን የድጋፍና የሀይል ምንጭ አድርጎት ለራሱ የመንግስትነትን ስልጣን ለመቀዳጅት ተዋጋ እንጂ፤ ነብዩ ሙሀመድ ያላዘዙትን፤ እስልምናን በሰይፍ በኢትዮጵያ ውስጥ ሊያስፋፋ አልነበረም ጦርነቱ ፤ “አህባሽ የሚባለውን እስልምና ፤ እኔ ያመጣሁልህን ተቀበል ፤ ለሺዎች ዘመናት ይዘህ የተጓዝከውን እምነትህን ጣል” እያለ በኢትዮጵያዊው ሙስሊም ላይ ከጂሀድ ያልተናነስ ስራ እየሰራ ያለው ወያኔ ነው። ማሰር መግደል። ኢትዮጵያዊው ሙስሊም ክርስቲያን ወንድሞቹን ያሸ በረበት ዘመን የለም። አርቲስቶቻችን እንደሻንበል በላይነህ በዜማቸው ደግመው ደጋግመው ሊናገሩት የሚገባ እውነታ ነው።
አማራ… ግጥም፤ አይገልጽም። ዜማ፤ የህዝብ…
……ምነው ምን በደለ ደጉ ያገሬ ሰው፤ አረ የሰው ያለህ ፡አረሰው፡ አረ ሰው። እሳት ቢያንቀላፋ ገለባ ጎበኘው፤ ዘመን አረጀና ይሄ ቀን አገኘው። ከባህር ይሰፋል አማራ ማለት፤ ያንድነት ሀረግ ነው ኢትዮጵያዊነት ……
በፋሸሽት ወረራ ዘመን ተፈጸመ ያልተባለ ግፍ፤ አማሮች እስከወዲያኛው እንዲጠፉ፤ በሽታ ገብቷል ብለው የወያኔ ጤና ጥበቃ ሀላፊዎች ወጣት የአማራ ታዳጊዎችን በክትባት ዘመቻ እንዳይወልዱ ያመከነ አውሬ ቡድን የጁን ማግኘት አለበት። ይህ በጥይት ተጨፍጭፎ አላልቅ ያለ ህዝብ፤ እንደሌሎቹ ኢትዮጵያውያን እንደኦሮሞው፤ እንደትግሬው፤ እንደአፋሩ እንደ ደቡቡ እንደ ሁሉም….. ደሙን እያፈሰሰ ፤ ኢትዮጵያን ሲያቀና ዳር ድንበር ሲያስከብር ኖረ እንጂ፤ ወያኔ ሻእቢአና መሰሎቻቸው እንደሚያወሩት ተረት፤ ሌሎቹን ሲገዛና ሲጨቁን አልኖረም። ይልቁን ከማንም በክፋ መልኩ ሲረገጥ ነው የምናየው። የጎጃምን ድሀ አርሶ አደር፤ ከትግራይ ደሀ አርሶ አደር፤ የትግራይን ድሀ አርሶ አደር፤ ከሀረርጌ ድሀ አርሶ አደር ባጠቃላይ የኢትዮጵያን ድሀ ህዝብ አንዱን ካንዱ የተለየ የሚያደርገው የትኛው ኑሮው ነውና ነው አማራው ተለይቶ እንዲጠፋ የተፈረደበት? የህውሀት በሽተኞች አማራውን የበቀል ኢላማ ያደረጉበት ምክንያት እንደሎሎቹ ሁሉ ለኢትዮጵያ ቀናኢ በመሆኑ ነው። ወያኔ አማራን በማጥፋት ኢትዮጵያን የሚያጠፋ ሊመስለው ይችል ይሆናል፤ ግና ለኢትዮጵያ ደሙን ያፈሰሰላት ከሰሜን ምጽዋ ጫፍ እስከ ደቡብ ዶሎ፤ ከምስራቅ ፌርፌር ጫፍ እስከ ምእራብ ኢሎባቡር ጫፍ ያለ ህዝብ ሁሉ ነው። አሁንም ከወያኔ የማጥፋት ዘመቻ ያድናታል። ኢትዮጵያን ይታደጋታል።

ዘንድሮ… ግጥም፤ ተስፋዬ ለማ። ዜማ፤ ተስፋዬ ለማ
……ህጻናት ሲሸጡ ወተው በማደጎ፤ ያለቅሳል ባመቱ ወላጅ አደግድጎ…. ሻንበል በላይነህ በዜማው የነገረን የምናየው ነገር ነው። በማደጎ ስም ህጻናቶቻችንን እየቸበቸበ ያለው ወያኔ ህጻናቱ ካገር ከወጡ በሗላ የት ወደቁ ያለበት ጊዜ የለውም። በስርቆትና በዘረፋ ስለተጠመደ ስለዜጎች የሚያስብበት ገዜ የለውም። ሽያጩ ግን በስፋት እንደቀጠለ ነው። በየ አለሙ ያሉት ኢምባሲዎቹም ድለላውናንና ዶላር ማቀባበሉን እንጂ ስለኢትዮጵያውያን መብትም ሆነ ህይወት የሚያገባቸው ነገር የለም። ዓለም ደቻሳ ቤይሩት ወያኔ ኢንባሲ ፊት ለፊት ነበር ኡ ኡ እያለች በባእድ ጫማ ስትረገጥ መሬት ለመሬት ስትጎተት በዚያው የራሷን ህይወት ያጠፋችው። የኢትዮጵያ ኢምባሲ ተብሎ ወያኔዎች እዚያው ነበር አድፍጠው በዚያች ኢትዮጵያዊ ድሀ ላይ ይደርስ የነበረውን የሚመለከቱት። እነዚህን ነው ሀያ ሁለት አመት ተሸክመን የተቀመጥነው።
…..ጥያቄ ባነሳ መብቱን ያስከበረ፤ ጸረ ሰላም ሲሉት በህግ ሽብር፤ እውነቱን አውጥቶ ስለተናገረ፤ ስንቱ ጋዜጠኛ እስር ቤት ታጎረ… ዘንድሮ
ፍርሀት አሽነፈን…. ግጥም፤ ተስፋዬ ለማ። ዜማ፤ ተስፋዬ ለማ
….ፍራት አሽመድምዶን ጥሎን ባደባባይ፤ ክፉንም ደጉንም ሁነናል ተቀባይ፤ የቆረቆረንን ምቹ ስናስመስል፤ ስንጨስ እንኖራልን ስንጠቁር ስንከስል……
አዎ .. ኢትዮጵያውያን በባህላችንም በተፈጥሮአችንም፤ ለህግ የመገዛት፤ የማክበር፤ በይሉኝታ መገዛት መፍራት፤ ስለሚያጠቃን፤ አንዳንድ ጌዜ ስንገፋና መብታችን ሲገፈፍ፤ ይህ ተፈጥሮ ከልክ ያለፈ ትግስት እንዲኖረን ያደረገ ይመስላል። ለዚህ ስርአት ያሳየነው ከልክ ያለፈ ትግስት ፍርሀት ነው የሚመስለው። አርቲስት ሻንበል በበላይነህ ምናልባትም ይህንኑ ታዝቦ ሳይሆን አልቀረም በዜማው እየነገረን ያለው። ሆድ ይፍጀው ወይም የባሰ አታምጣ እያልን ይኸው ሀያ ሁለት አመታት ጉዳት ተሸካሚዎች ሆነን በዚያው ጉዞ ቀጥሏል።
….. በጥቅም ሲፈረድ፤ በወገን ሲሰራ፤ አይተን እያለፍን ስንጠብቅ ወር ተራ፤ ፍርሀት እንደውሀ ወኔያችን አፍሶት፤ ይዘን ኖራለን የማይወጣ ብሶት…
መለስ ስብሀት ሰራሹ የወያኔ ገዢ ቡድን ወደስልጣን ከመጣበት ጊዜ ጀምሮ በመንግስቱም ሆነ በግላ ተቋማት፤ ያሻውን ሲሰራ ስንቱን ሺህ ሰራተኛ በገፍና በግፍ እያባረረ የወደደውን የራሱን ምልምል እስከ አሁን ድረስ ሲሰገስግ፤ ሁሉም ተራው ሲደርስ ሜዳ ላይ እየተጣለ ከማልቀስ በቀር ዛሬ በወገኔ ላይ የደረሰ ነገ በኔ ነው ብሎ አምርሮ ስራቱን ለመዋጋት የተነሳ እስካሁን የለም።
የቀድሞው ሰራዊት….. ግጥም ይልማ ገብረአብ። ዜማ ሻምበል በላይነህ ….ጊዜ ተለውጦ ቀን እስከሚከዳው፤ አንጠፍጥፎ ቀምሶ ውሀውን ከኮዳው፤ ያገር መሰረቱ ህብረቱ እንዳይናድ፤ ኑሮውን አድርጎ በቀበሮ ጉርጓድ፤ ታግሎ ወድቆልናል ስላንድነታችን፤ ውለታው ይዘከር የሰራዊታችን። ሳያጓድል ያባት አደራ፤ ያስጠበቀ ያገር ባንዲራ፤ እንዳናጣ የባህር በር፤ ነፍሱን ከፍሏል ለኛ ክብር……
የወደቀ ዛፍ ምሳር ይበዛበታ እንደሚባለው ; የኢትዮጵያ ብሄራዊ ጦርሰራዊት መበተኑ ሳያንሰው ፤ ለወያኔ የፕሮፓጋንዳ ሰለባ እንደሆነ እስካሁን በመቆየቱ እድሜ ልኩን ሲዘመርለትና ሲሞገስ ሊኖር የሚገባው ጀግና ሰራዊት፤ ባልፉት ሀያ ሁለት አመታት እንደዋዛ ተዘንግቶ ቆይቶ ነበር። ሻንበል በላይነህ ምስጋና ይድረሰውና ዛሬም እንደትናንቱ የዚያን ክቡር ሰራዊት ገድል አንስቷል። ይበል የሚያሰኝ ነው። የኢትዮጵያን ሰራዊት ሀያል ክንድ አጣጥመው የሚያውቁት ገንጣይና አስገንጣይ እንዳላሸነፉት ልቦናቸው ያውቀዋል። ሰራዊቱን በአካልና በሞራል ከውስጥ ይገልላቸው የነበረው መንግስቱ ሀይለማርያም ባለውለታቸው ነው። በዚያ በውሸት ፕሮፓጋንዳቸው እውነት ለዲሞክራሲና ለእኩልነት የሚዋጉ መስሎት በገፍ እየሄድ ሲቀላቀላቸው፤ ያልተቀላቀለውም መሳሪያውን አውርዶ ባዶ እጁን የቆመ ወታደር በመትረየስ እያጨዱ ነበር ተሯሩጠው ድፍን ኢትዮጵያን እንደ ወባ ትንኝ የወረሯት። መልካሙ ነገር ኢትዮጵያውያን ጀግኖቻችንን መሸለም መጀምራቸው ነው። ያየር ሀይል፤ የምድር ጦር የባህር ሀይል ጀግኖቻችን አሁንም ሊዘፈንላቸው ሊሸለሙና ሊወደሱ ይገባል።

ታሪክ ይፍረደን፤ ግጥም፤ ተስፋዬ ለማ። ዜማ፤ ተስፋዬ ለማ
…የነበረው ቀርቶ ያልነበረው ሆነ፤ የሰራነው ሁሉ እንደቀልድ ባከነ….. ……… .የራሳችን ቋንቋ የራሳችን ፊደል፤ የራሳችን እምነት የራሳችን ባህል፤ የነሉሲ ሀገር፤ የሰው ልጅ መገኛ፤ በራሱ የተሟላ ማን ነበር እንደኛ……
እርግጥ ነው። በራሱ የተሟላ እንደኛ ማንም አልነበረም:: ምን ያደርጋል፤ በመካከላችን የበቀሉ፤ በዚችው ምድር ላይ የተፈለፈሉ፤ ለራሳቸው ታሪክ ባእድ ሆነው፤ አባቶቻቸው የባእድ ጠላት አሽከሮችና ባንዳዎች፤ ያ ጠላት በወላጆቻቸው እአምሮ ውስጥ ባሰረጸው እኩይ አስተሳሰብ ተኮትኩተው ያደጉ፤ ጊዜ ለነሱ አድልታ ኢትዮጵያ እጃቸው ላይ ወደቀች። በማግስቱም … የአድዋው ታሪክ ለአማራው፤ ለደቡቡ ምኑ ነው፤ የኢትዮጵያ ባንዲራ ጨርቅ ነው፤ እንኳን ከትግራይ ተወለድኩ፤ የሚል ሰው መሪ ተብሎ ባደባባይ የሚናገር፤ ሚኒሊክ ቤተ መንግስት መኖር የቻለ አጥፊ አየን። መልካሙ ነገር እግዚአብሄር ባጭር አስቀረው። የጀግኖቻችን ሀውልቶች ፈረሱ። በባንዳ ልጆች ስም ተተኩ። በዘመናት አብሮ መኖር የተገነባ የደምና የስጋ ውህደት እንዲለያይ የዘር አጥር ግርግዳ የሚገነቡ፤ በስጋ ፤ ኢትዮጵያውያን፤ በመንፈስና በገቢር ባእዳን የሆኑ ገዢዎችን ለማስተናገድ በቃን። የሻምበል በላይነህ ዜማ ይህንን ነው ልብ ብሎ ለሰማ የሚነግረው።
ኢትዮጵያ…. ግጥም፤ ይልማ ገብረአብ። ዜማ፤ ይልማ ገብረአብ
…….ኢትዮጵያ ህይወታችን፤ ኢትይጵያ ኩራታችን፤ ኢትዮጵያ እምነታችን፤ ያገር ፍቅር ጽናት የምንማርብሽ፤ በፈጠርሽው ትውልድ ይመርብሽ፤ ዛሬም ትላንትም የምልሽ ህይወቴ፤ ውዳሴ ነሽ ለኔ የዘላለም ሀብቴ…. ከዳሽ በሞትሽ ለማትረፍ፤ በሚኒሊክ ጅራፍ ልገረፍ….
ውድ አንባቢያን እነዚህ ሁሉ መልክቶች ሻንበል በላይነህ በቁም እንዋደድ በሚለው አልበሙ ውስጥ ያካተታቸው ስራዎቹ ናቸው። ሀይለስላሴ የሚል ርእስ የተሰጠው ሲዲም ብዙ ታሪካዊና ወቅታዊ መል እክቶች አሉት፤ በተለይም በከፍጠኛ ሁኔታ ወጣቶችን ለትግል የሚያነቃቃ መልእክቶችም አሉ። እራሱን ማዳመጡ የተሻለ ነው። የሻንበል በላይነህ ስራዎች ለአርቲስቶቻችን በአርአያነት የሚጠቀሱ ናቸው። ተመሳሳይ ስራዎች ከየአቅጣጫው ብቅብቅ ቢሉ የህዝባችንን ንቃት እጥፍ ድርብ ያሳድጉታል። ሻንበልም የነጻነት ቀን እስከሚመጣ በያዘው መንግድ እንደሚጓዝና ሌሎችንም እንደሚያስከትል ተስፋ አደርጋለሁ።
ኢትዮጵያ ለዘለአለም ትኑር
lkebede10@gmail.com

የደርብ ከፈለኝ አስተያየት በእኔ እይታ –መሠረት ከቴክሳስ

$
0
0

‘አህያውን ፈርቶ ዳውላውን’ በሚል ርእስ በተክለሚካኤል ላይ የስድብ ውርጅብኝ ያወረዱት ደርብ ከፈለኝን ሳስብ በእኛ በኢትዮጵያውያን ውስጥ በብዙ ሰዎች ዘንድ የማየው በሽታ ታወሰኝ። ይኸውም ታዋቂን፣ሀብታምን፣ባለስልጣንን እንደው ብቻ በማናቸውም መልኩ በማህበረሰቡ አይን ውስጥ የገባን ሰው ማሞካሽት፤ ቢሳሳት እንኳን ስህተቱን ስህተት ነው ብሎ ደፍሮ ከማረም ግለሰቡ ከተናገረው ይዘት ጋር በማይገናኝ ሁኔታ አቃንቶ እንዲህ ለማለት ፈልጎ እኮ ነው ብለው የሚሉ ብዙ ሰዎችን አውቃለሁ። እንዲህ አይነት ሰዎች ከባለ ጉዳዩ በላይ ተቆርቋሪ ሆነው ከስህተቱ እንዳይማር መንገድ የሚዘጉ፣እንደዚያ አይነት ሰው ስህተት ቢፈጽም እንኳን ይቅርታ መጠየቅ የማይገባው መሆኑን እስከመግለጽ ይደርሳሉ።

             ይህን መሰል አንድ እውነተኛ ታሪክ ላጫውታችሁ። በአሜሪካን አገር ውስጥ አንድ የአበሻው ብዛት ከሁለት ሺህ አይበልጥባትም በምትባል ከተማ ውስጥ አበሾች ተሰባስበው ቤተክርስቲያን ይተክላሉ። ቤተክርስቲያኗም የምትተዳደረው አቡነ ይስሐቅ በሚባሉት ጳጳስ ስር ነበር። አቡነ ይስሐቅ ነፍሳቸውን እግዚአብሔር በገነት ያኑርልንና በዘመናቸው የኢትዮጵያን ቋንቋ የማይናገሩ ህዝቦችን አስተምረው የእኛን ኦርቶዶከስ እምነት አለማቀፋዊ ይዘት ያላበሱ ትልቅ አባት ነበሩ። እሳቸው ከሞቱ በሁዋላ ቤተክርስቲያኗ ከአገር ውስጥም ከውጨውም ሲኖዶስ ሳትሆን ከምእመናን በተውጣጡ የቦርድ አባላት እየተመራች ባለችበት ሁኔታ ውስጥ የቤተክርስቲያኗ ካህን ምእመኑን ለመከፋፈል እራሳቸውን አንዴ የወሎ ሰው ነኝ ብለው ወሎዬውን ሲሰብኩ ሌላኛውን ጎጃሜነኝ ሲሉ ሌላውንም ሌላ እያሉ ምእመኑን እየፈተሹ ባሉበት ሂደት ውስጥ አንድ ቀን ያልታሰበ ዱብዳ ተፈጠረ ። ይኸውም ካህኑ ከአራት አባት ምአመናን ጋር የቆመችውን ሴት የተናገሩትን ለመድገም በሚያሸማቅቅ ቃላት ዘለፉዋት። መንፈሳዊው አባት ሲሳደቡ ምእመን አባቶች ቆመው ታዘቡ። በትዝብት ማለፉ አስተማሪነት የለውም በሚል በአደባባይ በደፈናው ስህተት መፈጸማቸውን አምነው ይህቺን ሴት በቤተመቅደስ ቆመው ይቅርታ እንዲጠይቁ ከ4ምእመናን ሶስቱ ጠየቁ። አራተኛው ግን ይህ ነገር በእኛው መሀል ይቅር፣ ሴትየዋን እኛ ይቅርታ ጠይቀን ለሌላም ሰው እንዳትናገር እናግባባት በሚል አቋም ይይዛሉ። የተቀሩት ሶስቱ ግን ይህ በተአምር አይደረግም ብለው ጉዳዩን ምእመኑ ፊት ይዘውት ቀረቡ። ብዙዉ ምእመን ካህን ቢያጠፋ እግዜር ይጠይቀው እንጂ ሰው ምን አገባው ባይ ሆነና ለካህኑ የቆመው ሰው ጉልበት አገኘ። እነኝህኞቹ እውነትን ይዘው ካህኑን ሞገቱዋቸው። ካህኑም ስለ እውነት ስንት ነገር እያስተማሩ ፊትለፊታቸው እውነት ሲያፈጥባቸው አልቻሉምና ልክናችሁ ልጆቼ ብለው ለይቅርታ ንስሀቸውን መናዘዝ ሲጀምሩ ከአራቱ አንዱ የሆነው ሰው ‘ልጅ እንጂ አባት ይቅርታ እንዴት ይጠይቃል’ በማለት ሌላውን ምአመን ምን ዝም ትላላችሁ በማለት ሲያነሳሳ ካህኑም ወዲያው ሀሳባቸውን ገልብጠው ጥፋተኛ አይደለሁም በማለት ጉባኤው በብጥብጥ ተበተነ። ይህቺ አጋጣሚ ለካህኑ የትልቌ እድል በር ከፈተችና ለእውነት ሲሙዋገቱ የነበሩት ምእመናንና ተከታዮቻቸው ሲቀሩ የተቀሩትን ይዘው ቤተክርስቲያኗን ለአባ ጳውሎሱ ሲኖዶስ የእጅ መንሻ አድርገው በማቅረብ እሳቸውም የጳጳስነት ሹመታቸውን በማግኘት ሂደቱ ተጠናቀቀ።

መቼም ይሄ ጥፋት ህሊና ለአለው ሁሌም ሲያሳፍር የሚኖር ነው። ዛሬ በዚያ አካባቢ ለአንድ ቤተክርስቲያን የማይበቃ ህዝብ በአለበት፣ ሁለት ቤተክርስቲያን ተሰርቶ ሰዉም ቂም ቋጠሮ ያንን ክፉ ቀን በሁለቱም ወገን የማይረሱት ታሪክ ሆኖ ተቀምጧል። የያኔው ቄስ የዛሬው ጳጳስ እድሜ ሰጥቷቸው ይህን ማስተዋል ከቻሉ የህሊና ቁስል እንደሚሆንባቸው አልጠራጠርም። የእሳቸው ተቆርቋሪ ነኝ ብሎ ትልቅ ስህተት ውስጥ የጨመራቸውን ሰው ግን ያ ሰይጣን ባያሳስተኝ ኖሮ እኮ እንደሚሉ አሁንም በድጋሚ አልጠራጠርም። ሰውየው ካህን ተሳስቷል ከሚለው ሃሳብ ተሻግሮ ይቅርተቀ ይጠይቅ  የሚለው ሃሳብ  አሳፋሪ አድርጎ በውስጡ በማመኑና እምነቱን ከእራሱ አልፎ ለሌሎችና ባለጉዳዩንም የሃሳቡ ተጋሪ በማድረጉ  እራሱ መሳሳቱ ሳይበቃው ካህኑንና ሌሎችንም ከእውነት ጋር አጣልቱዋቸው ለብዙዎች የተረፈ የታሪክ ጠባሳ ጥሎ አልፉዋል። ደርብ ከፈለኝ በጽሁፎት ላይ ማጋነን ባይሆንብኝ ከ90 በመቶ በላይ ትችቱ ተክለሚካኤልን መዝለፍ  ነው። አንባቢም ሆነ ተተቺ እንዲሁም ተቺ እርሶ ትችቱን ስር በያዘና በጥሩ ምክንያቶች የእራስዎትን እይታ ቢሰጡ መልካም ነበር። መቼም ዶ/ር ብርሃኑ እንደቄሱ ደጋፊ ከአገኘሁ ብሎ ሽምጥጥ አድርጎ የእርስዎ ደጋፊ ሊሆን እንደማይችል እገምታለሁ። የእኔ ጽሁፍ አላማ በተክሌ ጽሁፍ አስተያየት ለመስጠት ባይሆንም ዶ/ር ብርሃኑ ግን የተክሌ ሀሳብ የእሱ ብቻ አለመሆኑን ሊገነዘበው እንደሚገባ አሳስባለሁ። ባለራዕዩ፣  ምሁሩ ፣ የምርጫ 97 ሞተሩ፣የእስርቤቱ ታሪክ ጸሐፊው እንዲሁም የግንቦት 7 ፈጣሪው ብርሃኑ እንደ ሰው ለፍጹምነት ሲሮጥ ያልፋል እንጂ ፍጹም አይደለም። እንደ ሰው የሚጎለውን ፊትለፈት ነግረነው አድመጭ መሪያችን እንዲሆን ማድረግ ይኖርብናል።  መተቸትን ዛሬ በቅርብ ሆኖ ካላስለመድነው ነገ ስልጣን የመያዝ አጋጣሚው ቢፈጠርና  አውሬ ሆኖ ቢበላን ጥፋቱ የእኛ እንጂ የእሱ አይሆንም። ለማንኛውም ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ እባክህን አስተያትህን ስጠን። ካልሆነ ግን ኢሳት ላይ ጠይቁት ከተባለ ይህቺ ጥያቄ የእኔ ናት።

መሠረት ከቴክሳስ

 

Pen

 

ሕዝብን የሚያሸብር ሥርዓትና የህዝቡ መከራ -አበራ ሽፈራው /ከጀርመን/

$
0
0

አበራ ሽፈራው /ከጀርመን/

ዛሬ አለማችን በከፍተኛ ስልጣኔ ላይ ትገኛለች። በዚህም ስልጣኔ ውስጥ በኢንተርኔትና ተያያዥ የመገናኛ ዘዴዎች ተጠቅሞ የሰው ልጅ የሚፈልገውን መረጃ መፈልግ፣ማግኘት፣መለዋወጥና ማሳወቅም ሆነ ማወቅ የሚችልበት ጊዜ ላይ ደርሰናል።

ጊዜው ለውሸታሞች ፣ ለአታላዬች፣ ለግፈኞች እና ለበዝባዦች የሚመች አይደልም፤ ዓለም መድረስ ወደሚፈልግበት እየሔደ  ነው፤ጊዜው ወደፊት መሄድን እንጂ እንደኃለኛው ዘመን ማሰብን አይፈቅድም፤ ስለዚሀ ከጊዜው ጋር አብሮ መሄድ ካልሆነም ውሸታሞች ውሸታቸውን ሊድብቁ የሚችሉብትን አዳዲስ መሳሪያዎችን መፈብረክ ይጠይቃል።አለመታደል ሆነና ህወሓቶች  ስለእነሱና ስለተግባራቸው ማንም የሚያውቅ አይመስላቸውም። ትልቁ የሚያውቁትም ቃታን እየሳቡ ሰውን መግደል ብቻ መሆኑን ድርጊታቸው እያሳየን ነው፤ በዚህም ድርጊታቸው እንደ ትልቅ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ባለሙያዎች እራሳቸውን ከመሪዎቻቸው ጀምሮ ሲያጋንኑ፣ ከበሮ ሲያስደልቁ ኖርዋል አሁንም በሰብዓዊ ፍጥረት ላይ ግድያን መፈጸም፣መስረቅ፣መንጠቅ፣ማሸማቀቅ፣እያሰሩ ማሰቃየት፣በአጠቃላይ ግፍን መፈጸምና ማሸበር እንደትልቅ ሙያና ተግባር ተያይዘውታል።

ህወሃት /TPLF/ እ.ኤ.አ ከ1976-1991 በሰው ልጆች ላይ በፈጸማችው የሽብር ወንጀሎችና ጥቃቶች በአሸባሪነት ተመዝግቦ የነበረ ቡድንም ነበር። ህወሓት ሽብርን ለመፈጸም ለ39 ዓመታት ያካበተው ልምድ ቢኖረውም ከዚህ በላይ መሽበር ግን የህዝቡ ግዴታ ሊሆን አይግባም።

ህወሓት ዛሬ ሰላማዊ የፖለቲካ ትግልን ሽብር፣የሃይማኖት ነጻነት ጥያቄን ሽብር፣ጋዜጠኝነትን ሽብር፣መደራጀትን ሽብር ፣ሃሳብን በነጻነት መግልጽን ሽብር በማለት ህዝብን ሲያሸብር ሲታይ ህወሓት ስሙንና ተግባሩን ለሌላ ለመስጠት የፈለገ ይመስላል።

በየጊዜዉ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥንና ሬድዮ ድርጅት አማካኝንት የሚነዙትን ፕሮፓጋንዳ ላየና ለሰማ ሁሉ ሽብርተኝነት ህወሃትን ያስመረረው ይመስላል። ይልቁንም የኢትዮጵያ ህዝብ በህወሃት መሸበሩንና መማረሩን፤ የሽብርተኝንት ታሪክም የህወሓት የራሱ የ39 ዓመታት ታሪክ እንጂ የኢትዮጵያ ህዝብ ታሪክ እንደልሆነ ለህወሓት ለራሱ ሊነገረው ይገባል።

  1. 1.    ህወሓት መንግስት ከመሆኑ በፊት የፈጸማቸው የሽብር ተግባራት ምን ነበሩ ?

ሀ. ህወሓት አሸባሪ ድርጅት የነበረና የተመዘገበም መሆኑ፡-

በዩ.ኤስ.ኤ አሜሪካ በአገር ውስጥ ደህንነት መስሪያ ቤት አማካኝንት በሜሪላንድ ዩንቨርስቲ በአለም አቀፍ ደረጃ የአሸባሪዎችን እንቅስቃሴና ድርጊታቸውን የሚመዘግበውና የሚተነትነው የመረጃ ማዕከል ማለትም The National Consortium for the study of Terrorism and Responses to Terrorism/START/ ለመረጃ መሰብሰቢያ ባዘጋጀው ዳታ ቤዝ  ወይም  GTD/Global Terrorism Data Base/ ክፍት በሆነው የመረጃ ፍልሰቱ ውስጥ እ.ኤ.አ ከ1976-1991 ድረስ አሥር/10/ ልዩ ልዩ የሽብር ጥቃቶች በህወሓት/TPLF/ መፈጸማቸውን መዝግባል፤ በነዚህ የሽብር ድርጊቶቹ ህወሓት አሸባሪ ድርጅት ተደርጎ ተመዝግባል። ይህ የመረጃ ማዕከል ህወሓት የፈጸማቸውን የሽብር ድርጊቶች የዘረዘረ ሲሆን በዚህ መረጃ ላይ ድርጊቱ የተፈጸመበት ቀን፣ ቦታ፣የአደጋው ብዛት፣ የአደጋው አይነት፣የተጠቀማቸውን የመሳሪያ ዓይነት ለመመዝገብ ሞክሯል፤በዚህ መረጃ መሰረት በራያ ቆቦ፣በትግራይ ቦታዎች፣በላሊበላ፣በጅሬ፣በኮረም፣በወርቅ አምባ፣በአክሱምና በሌሎች ቦታዎችም የሽብር ድርጊቱ የተፈጸመ መሆኑን ጽፋል፤በነዚህም ጥቃቶች የሃይማኖት ተቃማትና መሪዎች፣በግለሰብ ህይወት እና ንብረት ላይ፣ በመንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች ላይ፣በንግድ ተቃማት ላይ ፣በጋዜጠኞች እና ሚዲያዎች ላይ ሽብሩ መፈጸሙን ዘርዝሯል። ስለዚህ ህወሓት አሸባሪ ድርጅት እንደነበረና ተግባሩም ሽብር እንደነበረ ለማወቅ ይቻላል። ለበለጠ መረጃ http://www.start.umd.edu/start/  ይመልከቱ።

 

ለ. ህወሓት ልዩ ልዩ ሽብሮችን ሲፈጽም እንደነበረ አባሎቹ የነበሩ መመስከራቸው፡-

የህወሃትን እኩይ ተግባር በማጋለጥ የሚታወቁት አቶ ገብረመድህን አርአያ ስለ ህወሓት ያለፈው ታሪክ ላይ በጻፋቸው ጽሁፎች ላይ ህወሓት ግልጽ አሸባሪ መሆኑን በተደጋጋሚ ከመግለጻቸውም በላይ አሁንም ካዩትና ከሰሙት እዉነታዎች ተነስተዉ ይህንን አሽባሪ ድርጅት እያጋለጡም ይገኛሉ።

ህወሓት ከምስረታው ጀምሮ የተነሳው የራሱን የህወሓትንና የኢትዮጵያን ህዝብ ጥቅም ለማስጠብቅ ሳይሆን ጥቂቶች በስውር ይዘዉት የተነሱትን ስውር የዘረኝነት፣የብዝበዛና የጭቆና ዕቅዶቻቸውን ከግብ ለማድረስ እንደህነ ተግባራቸው ያሳየና፤ ይህንንም ግባቸውን ለመፈጸም የትኛውንም ሽብር ከመፈጸማቸው ጋር ተያይዞ ህወሓቶች በዓለም ከሚታወቁ የሽብርተኛ ቡድን ተርታ ተሰልፈው የነበረ ቢሆንም ከቀዝቃዛው ጦርነት ማብቃት ጋርና ከደርግ መንግስት መንኮታኮት ጋር ተያይዞ አገራችን በአሸባሪዎች እጅ ወደቀች፤ ደርግና ባለማሎቹም እንዲሁም ዋና ዋናዎቹም የዓለም መንግስታትም ህዝቡንና አገራችንን አሳልፈው ለሽብርተኞች  ሰጡ ። ይለወጣል ብለው ብዙዎች ቢጠብቁትም ተግባሩ ያለቀቀው ህወሓት/ኢህአዴግ መንግስት ከሆነም በኃላ ከቡድናዊ ሽብርተኝንት ወደ መንግስታዊ ሽብርተኝነት ተሸጋገረ።

  1. 2.   የህወሓት/ኢህአዴግ  የመንግስት ስልጣን ከያዘ በኃላ ወደ መንግስታዊ ሽብርተኝነት መቀየር /State Terrorisim/

ሀ . ለመሆኑ የመንግስት ሽብርተኝንት/ State Terrorisim/ ምንድ ነው? 

ጸሃፊዎች የሽብርተኝነት መሰረታዊ ዓላማ ሽብርተኞቹ የሚፈልጉትን ፖለቲካዊ፣ኢኮኖሚያዊና ሃይማኖታዊ ግቦችን ተግባራዊ ለማድረግ ልዩ ልዩ መንገዶችን ተጠቅመው በህዝቦች ላይ ከሚገባው በላይ ፍርሃትን በመፍጠርና በማስገደድ ዓላማቸውን ከግብ ማድረስ እንደሆነ ይገልጻሉ።

በ acadamia.org ላይ የመንግስት ሽብርተኝነትን እንደዚህ ጽፎታል፡- State terror refers to the use or threat of violence by the state or its agent or supporters,particularly against civilian individuals and population,as a means of poletical intimidation and control.

የፖለቲካ የበላይነትን ለመያዝና ጫናን ለመፍጠር በተለይም በሰላማዊ ግለሰቦችና ህዝቦች ላይ ተገቢ ያልሆነን ጥቃትን በራሱ በመንግስት፣በተወካዮቹና በደጋፊዎቹ  ሲፈጸም ይህንን ጥቃት መንግስታዊ ሽብር ብሎታል።

እንግዲህ ህወሓት/ኢህአዴግ  ምንም እንካን የመንግስትን ሥልጣን የያዘ ቢሆንም ሌሎች አሸባሪ ድርጅቶች የሚፈጽማቸውን ተግባራት በግልጽና በአደባባይ ይፈጽማል። ከነዚህም ውስጥ ፍንዳታን ይፈጽማል ፣ያፍናል፣ህጋዊ ያልሆኑ እስራትን ይፈጽማል፣በሰብዓዊ ፍጥረት ላይ የማይፈጸሙ ድብደባዎችን፣ በወንዶችም ሆነ በሴቶች የመራቢያ ብልቶች ላይ አደጋን ማድረስ፣አካለ ስንኩል ማድረግ፣ ቤተሰቦች እንዲለያዩ ማድረግ፣ ስውርና የአደባባይ ላይ ግድያዎችንና ሌሎችም ተግባሮችን ይፈጽማል።ከዚህም ድርጊቱ አንጽር ህወሓት/ኢህአዴግ  ከአሸባሪነት መገለጫዎች የዘለሉ ተግባሮችን የሚፈጽም ቡድን መሆኑን ያሳያል።

ህወሓት/ኢህአዴግ  በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ የሚፈጽመውን የሽብር ጥቃቶችን ኢትዮጵያውያን በግልጽ የሚያውቁት ጉዳይ መሆኑ ፣የልዩ ልዩ ሃገራት መንግስታትና በኢትዮጵያ የሚኖሩ የልዩ ልዩ ሃገራት አምባሳደሮችም ሳይቅሩ በግልጽ የሚያውቁት መሆኑና ይህንንም የሚያግዙ የተለያዩ መረጃዎች እየወጡ መሆናቸው፤በተለይም የዩ.ኤስ.ኤ አሜሪካንና ሌሎችንም መረጃዎችን በመሰብሰብ እና በማጋለጥ የሚታወቀው ዊኪሊክስ ይፋ ባደረጋቸው መረጃዎች መሰረት እነዚህ እውነታዎች ግልጽ እየሆኑ መምጣታቸውና በተለይም ህወሓት የራሱን የሽብርን ጥቃት ለመፈጸም እንዲያግዘው ኢትዮጵያ ውስጥ የሽብር ጥቃት እንዳለ ለማስመሰል ሲጠቀምባቸው የነበሩትን የማታለያ እንቅስቃሴዎች ማለትም የሽብር መሳሪያዎችን በራሱ ወታደሮችና የደህንነት ሰዎች በልዩ ልዩ ቦታዎች በማስቀመጥ መልሶ በራሱ የደህንነት ሰዎች እንደተገኙ በማስመሰል ያደርገዉ የነበረውን ተግባር አጋልጧል፤ እነዚህም ድርጊቶቹ  አስቀድሞም ብዙዎች  የነበራቸውን ጥርጣሬም አጠናክሮታል።

 

ለ. ህወሓትኢህአዴግ የፈጸማቸው የሽብር ጥቃቶችስ ምንድ ናቸው?

ህወሓት/ኢህአዴግ የመንግስትን ሥልጣን ከያዘ በኃላ መጠነ ሰፊ የሽብር ጥቃቶችን በህዝቡ ላይ በተለያዩ ጊዜያትና ቦታ የፈጸመ ሲሆን ዋና ዋናዎቹን በጥቂቱ እንመልከት፡-

  1. በወልቃሪት ጠገዴ ህዝቦች ላይ የተፈጸሙት የዘር ማጥፋት ዘመቻና የዚህንም ህዝብ ህልዉና በማጥፋት የራሱን መስፋፋት ከግብ ለማድረስ በህዝቡና በትውልዱ ላይ የተወሰደዉ የዘር ማጥፋት ተግባር እጅግ ዘግናኝ ተግባር የሆነና ጉዳዩ ገና መፍትሄ ያልተገኘለት ይልቁንም ገና ብዙ ቀውስን ሊፈጥር የሚችል ተግባር መሆኑም እራሱም ህወሃትም ያልተረዳው ግፍ ነዉ።ለበለጠ መረጃ http://ethio-wolqait.blogspot.de/. እና ሌሎችንም ተያያዥ ጽሁፎችን ይመልከቱ::
  1. በጋምቤላ በአኟኮች ላይ እ.ኤ.አ በዲሴምበር 13/2003 በጋምቤላ ከተማ የተደረገው የጅምላ ግድያ/Gonocide/ 424 ስዎችን በጅምላ በመግደል ታሪክ የማይረሳው የመንግስት ሽብር የተፈጸመ ሲሆን ብዙዎችም አገራቸውን ጥለው እንዲሰደዱ ተደርገዋል፣የአኟክ ሴቶች በወታደሮች ተደፍረዋል፣በመቶዎች የሚቆጠሩ ቤቶች ወድመዋል፣የሚመገቡአቸው ምግቦችና የቤት እንሥሣቶችም እንዲወድሙ ተደርጓል።ይህ ሽብር  ህወሓት በዚህ ክልል ውስጥ ለመስፋፋት ብሎ በህዝብ ላይ የተፈጸመ ግልጽ ሽብር ነው።ለዚሀም ድምዳሜ ላይ ያደረሰኝ ጉዳይ አብዛኛው የጋምቤላ ሰፋፊ መሬቶች በህወሃቶችና የጥቅም ተጋሪዎቻቸው ቁጥጥር ውስጥ መሆኑና እየተበዘበዘ መሆኑ ነው። በዚሁ ክልል  ስለተፈጸመው ጅምላ ግድያና ህወሓት  በዚሁ ክልል ስለሚፈጽማቸው የሃብት ብዝበዛ ለማውቅ ከፈለጉ የአኟክ የፍትህ ካውንስልን ዌብ ሳይት “http://www.anuakjustice.org/”  ይመልከቱ።
  1. የሲዳማ ህዝቦች ሰላማዊ ጥያቄዎች በማንሳታቸው እና ህገ-መንግስታዊ መብቶቻቸውን ተግባራዊ ለማድረግ በመነሳታቸው ብቻ ከ 11 ዓመታት በፊት እ.ኤ.አ ሜይ 24/ 2002 በአዋሳና አካባቢው ከ100 በላይ የሲዳማ ተወላጆችን በጅምላ በመግደልና ከ250-300 የሚሆኑትን በማቁሰል የተፈጸመው ዘግናኝ ሽብር ለታሪክ የማይረሳና የህወሓትን ግልጽ ሽብርተኝነት የሚያሳይ ሌላው ሀቅ ነው። ለበለጠ መረጃ http://sidamaliberation-front.org/ ይመልከቱ።
  1. በኢትዮጵያ አቆጣጥር ከ1997 ዓ.ም ምርጫ በኃላ በህዝብ ምርጫ የተሸነፈው ህወሓት/ኢህአዴግ ከህጻናት እስከ አዋቂ በጠራራ ጸሃይ በመቶዎች የሚቆጠሩትን ንጹሃን ግንባር ግንባራቸውን ብሎ በመግደል፣ በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩትን አካለ ስንኩል በማድረግ፣በሽዎች የሚቆጠሩትን ደግሞ በእሥር ቤቶች ውስጥ በማሰርና በማሰቃየት በኢትዮጵያ ህዝብና በዓለም ማህበረሰብ ፊት ግልጽ ሽብር የፈጸመ ቡድን መሆኑ የቅርብ ግዜ እውነታዎች ናቸው።
  1. በአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ውስጥ በተወሰኑ በኦሮሞና በትግራይ ተማሪዎች መካከል በተደረግ ግጭት ግልጽ በሆነ መድሎና በማን አለብኝነት በኦሮሞ ተማሪዎች ላይ ከትምህርት ገበታቸው እንዲባረሩ ተወስኖ የነበረውን ውሳኔ ሰንመለከት እጅግ የሚያሳዝን ተግባር መሆኑና ድርጊቱ በአዲሱ ትውልድም ላይ የተቃጣ ሽብር ከመሆኑም በላይ ኢትዮጵያውያን በአገራችን በግልጽ መድሎ ውስጥ መሆናችንን ያሳያል።
  1. በኦሮሞ ህዝቦች ውስጥ የሚደረጉትን ትግሎች በሙሉ ከኦነግ ጋር በማያያዝ የኦሮሞ ህዝቦች በእስር ቤቶች ውስጥ እንዲማቅቁ መደረጉና አብዛኛው የአገሪቷ እስር ቤቶች ኦሮሚኛ የሚነገርባቸው እስከ መሆን መድረሳቸውን ከፖለቲከኞች አፍ መስማታችን እጅግ ከባድ ችግሮች በህዝቡ ላይ መኖራቸውንና በኦሮሞ ህዝብ ላይ ሽብር እየተፈጸመ መሆኑን ያሳየናል።
  1. ህወሓት/ኢህአዴግ ሊፈጽመው የሚፈልገውን ሽብር በሽብር ህግ ድጋፍ እንዲደረግለት በህዝቡ ሳይሆን ለህወሓት የብዝበዛና የጭቆና መሳሪያነት በሚያገለግለው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አማካኝነት አጽድቆ የሽብር ጥቃቱን እየፈጸመ ሲሆን በዚህ ጥቃትም ልዩ ልዩ አካላት የህወሓት የሽብር ጥቃት ስለባዎች ሆነዋል። በዚህም ውስጥ ጋዜጠኞች፣የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችና አባላት፣ የነጻነት ተማጋቾችና ልዩ ልዩ ግለሰቦች በሙሉ በዚሁ ጥቃት ውስጥ ወድቀዋል።

ከጋዜጠኞች መካከልም፡- ርዮት አለሙ፣ውብሸት ታዮ፣እስክንድር ነጋ፣ በተለያዩ ጊዜያት በፍርድ ቤት የሚመላለሰው ተመስገን ደሳልኝ እና ሌሎችም ከሃገር ውስጥ ፣ የስውዲን ጋዜጠኞች ጀሃን ፕርሰን/Johan person/ እና ማርቲን ሽብዮ/Martin Schibbye/ ከውጭ ይገኙባቸዋል።

ከፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችና አባላትም ውስጥ አንዱዓለም አራጌ ፣በቀለ ገርባ፣ኦርባና ሌሊሳና ሌሎች በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ በእሥር ቤቶች የሚማቅቁ ይጠቀሳሉ።

በተለይም ተዋቂ ጋዜጠኞችን በሽብርተኝነት ሰበብ አስሮ ሌሎች በአገራቸው በሚደረገው የነጻነት እንቅስቃሴ ላይ ምንም እንዳይናገሩ በማድረግ በነጻው ሚድያ ላይ ግልጽ የመንግስት ሽብር እንዳለ ሁሉም የሚያውቀውና እ. ኤ. አ ከ2007-2012 ድረስ ብቻ 49 የሚሆኑ ጋዜጠኞች በዚህ የህወሓት የሽብርተኝነትን ድርጊት በመፍራትና በግዳጅ ከሃገር መሰደዳቸውን ለጋዜጠኞች መብት የሚከራከረው ሲፒጄ/Commitee to Prtect Jornalists / በተለያዩ ጊዜያት ገልጸዋል፤በዚህም ምክንያት አገራችን ለጋዜጠኞች ህይወት አደገኛ አገር መሆናንና ከሱማሊያና ከኢራቅ ቀጥላ  ለጋዜጠኞች የስደት ምክንያት በመሆን ታዋቂ ሆናለች ።

  1. በተለያዩ ጊዜያት በአፋር፣በሶማሊያና በጋምቤላ ክልሎች የህወሓት የመሬት መስፋፋትን ተግባራዊ ለማድረግ በሚደረገው እንቅስቃሴ ውስጥ የእነዚህን ህዝቦች የመሬት ሃብት ተጠቃሚነትን በመንጠቅ የህወሓት የብዝበዛ ቡድን አባላትና ጀሌዎቻቸው በህዝቦች ህይወት ላይ ተደጋጋሚ አደጋ በመፍጠርና በማፈናቀል አስከፊ ተግባር እየተፈጸመ ያለው በዚሁ ተስፋፊ  የህወሓት/ኢህአዴግ ቡድን አሸባሪነት መሆኑም ሊሰመርበት ይገባል።
  1. በአማራ ተወላጆች ላይ ከደቡብ ከጉራፈርዳ፣ከቤንሻንጉል ጉምዝና ከሌሎችም ክልሎች በማፈናቀል፣መሬት በመንጠቅና በማሳደድ የዘር ማጽዳትን ተግባርን የሚያቅደው እራሱ ህወሓት መሆኑንና ከትግሉ ጀምሮ ይዞት የመጣው በማኔፌስቶውም ላይ በግልጽ ያስቀመጠውና እየተገበረ ያለው ተግባር ነዉ፤በዚህም ብዙ ጭቁን አማሮች የሚከላከልላቸው አጥተው የዚሁ የሽብር ጥቃት ሰለባ ሆነው ተቀምጠዋል።
  1. ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ በተለይም ከአንድ ዓመት ወዲህ በሙስሊም ወንድሞቻችንና እህቶቻችን ላይ የሚፈጸመው የአደባባይ ላይ ድብድባ፣እስራትና ግድያዎች የህወሓት/ኢህአዴግ ሌላው ህዝብን የማሽበር ተግባሩ አካል እንደሆነ ብዙዎች ይስማሙበታል።
  1.  በሃገር ውስጥ ባሉ ሰላማዊ ትግልን አማራጭ ትግል በማድረግና ህግን ተከትለው የሚታገሉትን የተቀዋሚ ፓርቲዎች አመራርና አባላት ላይም እየደረሰ ያለው ወከባና እንግልት ሰላማዊ ትግሉን እጅግ መራራ አድርጎታል፤ለዚህም ማስረጃ ይሆን ዘንድ በቅርቡ በሰማያዊ ፓርቲ ላይና በአንድነት ፓርቲዎች አመራሮችና አባላት ላይ እየደረሰ ያለው ግፍ ህወሓት/ኢህአዴግ በፍጹም ማን አለብኝነት መቀጠሉንና ሰላማዊ ትግሎችንም ጭምር ለማጥፋት መቀጠሉ ይህ ሥርዓት በግልጽ በመንግስታዊ ሽብርተኝነት መቀጠሉን ግልጽ አድርጎልናል።
  1. 3.   ህወሓት/ኢህአዴግ የሽብር ጥቃትን ለምን ይፈጽማል ?

ወሓት/ኢህአዴግ በየትኛውም የታሪክ አጋጣሚ ኢትዮጵያዊነትን የተላበሰና ለእውነተኛ ዲሞክራሲና ፍትህ የቆመ ቡድን ሳይሆን በጥቂቶች ጠባብና ዘረኞች የተዋቀረ የማፍያ ቡድን መሆኑን ሁሉም ኢትዮጵያዊ ያውቃል። የህወሓት ዓላማና ግብ በእርግጥም የነጻነትና የዲሞክራሲ ሳይሆን ጥቂቶች የአገሪቷን ወታደራዊ፣ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ መዋቅሮችን በሙሉ ተቆጣጥረው ለዓመታት የተመኙትን የኢኮኖሚና የመሬት መስፋፋትን ዕውን ለማድረግ የሚያደርጉት እንቅስቃሴ አካልና፤በኢትዮጵያ ህዝብ ደምና ሀብት ለመክበር በሚቋምጡና በሚተገብሩ የህወሓት መሪዎችና ጀሌዎቻቸው አማካኝነት ይህንን ስውር ተግባር ለማስፈጸም የሚፈጸም የሽብር ተግባር ነው።

የዚህን እውነታዎች ለማወቅ ለሚፈልጉ ሁሉ አሁን በተጨባጭ የሚታየውን እውነታን ማየት ይቻላል።አጠቃላይ የኢኮኖሚው ክፍል በሙሉ ማለት ይቻላል በህወሓት ቁጥጥር ስር መውደቁና፤ የወሓት የንግድ ድርጅቶች ሙሉውን የአገሪቷን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴዎችን በሙሉ ለመቆጣጠር ሩጫ ላይ መሆናቸውና፤ እነዚህን ሁኔታዎችን የሚያመቻቹ የመንግስት መዋቅሮች በእነዚሁ በህወሓት ሰዎች እጅ ቁጥጥር ስር መዉደቁ ግልጽ ማስረጃ ሆኖ ይገኛል፤ለምሳሌ ኢፈርት በሁሉም የአገሪቷ የንግድ ሴክተሮች ተጽዕኖን እንዲፈጥርና ሌሎችን ከገበያ ውጭ እንዲሆኑ የሚያደርገው እንቅስቃሴና በብሄራዊ ባንክ፣በግሙሩክ፣በአየር መንገድ፣በአገር ዉስጥ ገቢ መስሪያ ቤቶች፣በወታደራዊ ተቋማት፣በፖሊስና ደህንነት መስሪያ ቤቶች ተሰግስገው አገሪቷን ለመበዝበዝ የሚያስችሉአቸውን ሁኔታዎች በቁጥጥር ውስጥ ያስገቡ በመሆኑ፤ ይህንን ብዝበዛ የሚቃወምም ሆነ የሚነካ ሃይል በሙሉ የጥቅሞቹ ተቀናቃኝ አድርጎ በመቁጠሩና፤ ይህንን የህወሓትን ቡድን ስውር ዓላማን ለማስፈጸመ መንግስታዊ ሽብርን አንዱ አማራጭ አድርገው የያዙት መሆኑ፤ ህወሓትን የሚያሳስበው የፍትህና የዲሞክራሲ ጉዳይ ሳይሆን ይህንን የብዝበዛ መዋቅራቸውን የሚነካ ሃይል ሁሉ በአሸባሪነት በመፈረጅ የብዝበዛ ተግባራቸውን ከግብ ለማድረስ የመንግስት ሽብርተኝነትን  እያቀጣጠሉ መሆኑ ነው።

  1. የህወሓት/ ኢህአዴግ የሽብር ተግባራት በህዝቡ ላይ የፈጠራቸው ችግሮች ምንድን ናቸው ?

 

የህወሓት/ኢህአዴግ ቡድን በሚፈጥራቸው የሽብር ተግባራት የተነሱ በህዝቡና በአገሪቷ ላይ የፈጠሩት ተጽዕኖዎች የሚከተሉትን ያካትታሉ፡-

  1. በህዝቡ ላይ ፍርሃት መንገሱና በብዙዎች ላይ የስለልቦናም  ችግር ያስከተለ መሆኑ፤
  2. ስደትና በስደትም የተነሳ ወጣቶች በጎረቤት አገራትና በየበረሃው ለሞት መዳረጋቸው፤
  3. እስራትና ሞት፤
  4. ግልጽ የህወሓትንና የጥቅም ተጋሪዎቻቸውን ልዩ ልዩ ብዝበዛዎችን ከፍርሃት የተነሳ በዝምታ ማየት፤
  5. በህዝቡ ላይ ሰብዓዊ ጥሰቶች በብዛት እየተፈሰሙ መምጣታቸው፤
  6. የመሬትና የተፈጥሮ ሃብቶች ብዝበዛ መቀጠሉ፤
  7. የሃገሪቷ ሃብቶች በጥቂቶች እጅ እየወደቁ መምጣታቸው፤
  8. ህዝቡ መብቶቹን እንዳይጠይቅ መገደዱ፤
  9. የስራና የትምህርት እድሎች መድሎዎች መፈጠራቸው ይህንንም መድሎ በዝምታ ለመቀበል መገደድ፤
  10. የስራና የመኖሪያ ቦታዎች ችግር መፈጠሩ፤
  11. የሙስና መስፋፋት መባባሱ፤
  12. የህግ የበላይነት ቀርቶ የህግ  መድሎ መፈጠሩ፤
  13. ግልጽ የንግድና የስራ ቦታዎች መድሎ መኖሩ፤
  14. ህዝቡ ከተቀዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር እንዳይቀላቀልና መብቶቹን እንዳያስከብር መሆኑ፤
  15. በንሮ ውድነት መማቀቅ፤
  16. ህዝቡ በሃገሩ ላይ የበይ ተመልካች መሆኑ፤
  17. የንብረት መነጠቅ ችግሮች መደራረብና ሌሎችም:-

 

  1. 5.   ከፖለቲካ ፓርቲዎች ፣ከስቪክ ማህበራትና ከኢትዮጵያ ህዝብ አጠቃላይ ምን ይጠበቃል ?

ህወሓት/ኢህአዴግና የጥቅም ተጋሪዎቹ ይዘው የተነሱትን የኢኮኖሚ፣የንግድና የመሬት መስፋፋት ከግብ ለማድረስ በሚያደርጉት የብዝበዛና የዝርፊያ እንቅስያሴ ዉስጥ ማናቸውንም ሰላማዊና ህጋዊ ትግሎች ሳይቀሩ በሽብርተኝነት ሰበብ መግደል፣ማሰር፣ማሳደድ፣ማሸማቀቅና ማስፈራራት የህወሓት የየዕለት ተግባር ሆኗል። ይሁንና ይህንን ሁኔታ ለመለወጥ እራሳችን ለመታገል ካልቆረጥንና መሰዋዕትነትን ለመክፈል ካልተነሳን ችግሩ ማብቂያ እንደማይኖረው ሊሰመርበት ይገባል።

በሃገራችን ታሪክ ህዝብንና አገርን በማሽበር በኢትዮጵያውያን ብቻ ሳይሆን በዓለም የሽብርተኝነት መዛግብት ውስጥ የተመዘገበውን ይህንን ሽብርተኛን የህወሓትን ቡድን ከድርጊታቸው እንዲያቆሙ ማድረግ ወይም እራስን የመከላከል ተፈጥሮአዊና ህጋዊ መብቶችን ተጠቅሞ ወደ መከላከል መግባት፣ የህወሓት ፍጹም አምባገነንነት እንዲያበቃና የአገራችንና የህዝቦቻ ነጻነት እንዲረጋግጥ ማድረግ ለነገ የሚባል ጉዳይ አይደለም።

በእርግጥም ህዝብን በማሸበር ህወሓት ለዓመታት በህዝቦች መብቶችና ህይወት ላይ የሚፈጽማቸው የሽብር ጥቃቶች እንዲያበቁ አስፈላጊዉ ሁሉ ባለመደረጉ ዛሬ ህዝባችን በመከራ ውስጥ መሆኑ ለሁሉም የተሰወረ አይደለም።ትግሉ አሁን የመንግስት ስልጣን ይዘው በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ግፍን ከሚፈጽሙ የመንግስት ሽብርተኞች ጋር እንጂ ከህገ መንግስት ጋር አይደለም፤ህግ በትክክል እየተጣሰ ያለው በእነዚህ እኩይ ተግባርን በሚፈጽሙ የህወሓት/ኢህአዴግ በዝባዥ ሥርዓትና የሥርዓቱ መሪዎች ነው፤ ይህንን አስከፊ ሥርዓት ለማስወገድ መነሳት፣ መታገልና አስፈላጊውን መስዋዕትነት ከፍሎ በድል ማጠናቅቀ ጊዜ የሚሰጠው ጉዳይ አይደለም።

 

በሃገራችን የበይ ተመልካች ሆነን መቀጠል ያብቃ፤ጥቂቶች ብዙሃኑን የሚዘርፉበትና የሚጨቁንበት ሊያበቃ ይገባል፤የተወለድንባቸውና ያደግንባቸው ቦታዎች የራሳችን እስር ቤቶች ሊሆኑ አይገባም፤ወታደሩ፣ፖሊሱና የደህንነት ሀይሉ ኢትዮጵያውያንን የሚወክል መሆን ይኖርበታል እንጂ ለጥቂት ዘረኞች ቅጥረኛ ሆኖ የሚያገለገለበት ጊዜ ሊያበቃ ይገባል።

 

ህወሓት/ኢህአዴግን መታገልና ማስወገድ የተቀዋሚ ፓርቲዎች፣የስቪክ ማህበራት፣ የሰብዓዊ መብት ተከራካሪዎችና ለእውነት የቆሙ ጋዜጠኞች ብቻ ሳይሆን የሁሉም ኢትዮጵያዊ በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ ያሉ ሁሉ  ትግል ሊሆን  ይገባል።

 

 

ለዚህም ይረዳ ዘንድ የሚከተሉት ሁኔታዎችን ማየት ይኖርብናል ብዮ አስባለሁ፡-

 

 

  1. ነጻነቱን የተነጠቀዉ ሁሉም መሆኑና ነጻነቱን ማስመለስ የሁሉም መሆኑ፤ ስለሆነም ትግሉም የሁሉንም ተሳትፎና መስዋዕትነትን የሚጠይቅ በመሆኑ ሁሉም በመረጠዉ የትግል መንገድ ወደ ትግሉ መቀላቀል ይጠበቅበታል።ድልን የሚጠብቅ ሁሉ የትግሉም አካል ሊሆን ይገባል፤
  2. የህዝቦች መቀራረብና በጋራ ጠላት ላይ የጋራ ትግልን ማፋጠን ለነገ የማይባል መሆኑ፤
  3. የተማሩና የህዝባቸው ሮሮ የሚሰማቸው ሁሉ ዛሬ ህዝቡ የሚፈልጋቸው በመሆኑ ያስተማራቸውን ህዝብ ለማገልግል የሚቆርጡበት ጊዜ መሆኑ፤
  4. የፖለቲካ ፓርቲዎች ልዩነቶችን በማጥበብና ለትዉልዱ በማሰብ በጋራ ጠላት ላይ በጋራ መነሳት መቻልና ለህዝቡ የትግል ፍላጎት መዳረሻ ሊሆኑና ሊያታግሉ ይገባል፤
  5. የስቪክ ማህበራትም ያላቸዉን ትስስር በማጠናከር ትግሉን ማገዝ ይኖርባቸዋል፤
  6. አዲሱ ትውልድም ለራሱ ሲል ወደ ትግሉ መቀላቀል ይኖርብታል፤
  7. በውጭ የሚገኙም የዚህን ዘረኛና አሸባሪ መንግስታዊ ቡድን ተግባር በማጋለጥና በዲፕሎማሲው ዘርፍ አስፈላጊውን እንቅስቃሴ በማድረግ ዕርቃኑን ማስቀረትና አገራትና መሪዎቻቸው ከተጨቆነው ህዝብ ጋር እንዲወግኑ ጥረት ማድረግ፤
  8. በፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል፣ በስቪክ  ማህበራት መካከል፣ በሰብዓዊ ድርጅቶች መካከል በሃገር ውስጥም ሆነ በውጭ ያሉት የእርስ በእርስ ግንኙነቱን በአህጉራት መካከልና በዓለም አቀፍ ደረጃ በማጠናከር የህወሓትን የመከፋፈል አቅምን መስበር መቻል፤
  9.  በውጭ ያሉ ምሁራንም የተለያዩ ሙያዊ ድጋፍ እንዲያደርጉ ማበረታታትና ተነሳሽነት መፍጠር፤
  10. የህወሓት የንግድ ድርጅቶች ምርቶችን ባለመግዛትና የንግድ አገልግሎቶቹን ባለመጠቀም ጭምር የህወሓትን የብዝበዛ መስመሮች መዝጋትና
  11. ልዩ ልዩ ትግሎችን  በሃገር ውስጥና በውጭ ማቀጣጠልና ተግባራዊ ማድረግ ግድ ይላል።

 

እነዚህንና ሌሎች ተግባራትን በመፈጸም ይህንን ሽብርተኛ ቡድን ከሃገራችንና ከህዝባችን ላይ ማንሳት ይጠበቅብናል።

 

 

  1. 6.  ማጠቃለያ

 

ከላይ ከተዘረዘሩትም ሆኑ ሌሎች በዚህ ጽሑፍ ካልተጠቀሱ የህወሓት/ኢህአዴግ ተግባራት ስንነሳ ግዜው መሰባሰባችንን ይጠይቃል። ከራሳችን ይልቅ ለደሃው ህዝባችን ልናስብና የመከራውን ግዜ ልናሳጥር የሚገባን ሰዓት ላይ ነው ያለነው፤ ስልሆነም አስፈላጊውን ሁሉ ማድረግ ይጠበቅበናል።

 

ህወሓት/ኢህአዴግ በሰላማዊ ትግል ላይ ባሉ የሰላማዊ ትግል አራማጅ ፓርቲዎች ላይም  ሳይቀር መንግስታዊ ሽብርን ቀጥል። ይህንን የፓርቲዎችን ትግል ማገዝና ችግራቸውን መጋራት ለነገ የሚባል ሳይሆን ዛሬ የሚተገበር ተግባር ነዉ። በሩቁ ሆኖ ፓርቲዎቹ ብቻቸውን እንዲታገሉ  መፈልግ ትግሉን ይጎዳዋል እንጂ አይጠቅመዉም፤ ስለሆነም ትግሎችን መደገፍና ከውጤት ላይ ማድረስ የሁሉም ተጠቂ ሁሉ ሃላፊነት ነው ።

 

በመጨረሻም አንድ ነገርን ሳልል አላልፍም ይኽውም ትግሎቻቸን ግቦቻቸውን እውን የሚያደርጉ ግለሰቦችን፣ ቡድኖችንና አስተሳሰቦችንና ፖሊሲዎቻቸውን ማየት ይኖርባቸዋል ፤ እነዚህም ቢሆኑ የብዙሃኑን ተሳትፎ ይጠይቃሉ ። ይኽንን ያልኩባቸው ምክንያቶችለመመልከት ያህል በዓለማችን እንደሚታየው አብዛኞች ትግሎች ግባቸውን እንዲስቱ የሚደረጉበት አጋጣሚዎች ተፈጥረዋል፤ ትግሎች በልዩ ልዩ ምክንያት በድሎቹ ዋዜማና አስቀድሞ የራሳቸው ስውር ግብ ባላቸው ግለሰቦችና ቡድኖች እጅ በመውደቃቸው ብዙ መስዋዕትነት የተከፈለባቸው ትግሎች ግቦቻቸውን እየሳቱ ሌሎች ትግሎችን የሚጠይቁበት ሁኔታዎች ታይተዋል።ለምሳሌም በሃገራችን የተደረጉት የተማሪዎች ትግል በደርግ እጅ መውደቅና የኢህአዴግ ትግል በጥቂቶች የህወሓቶች እጅ መውደቁ፣አሁን በአረቡ ዓለም የሚደረጉ ትግሎችንም ስንመለከት ደግሞ እንዲሁ ብዙ መስዋዕትነት ከተከፈለባቸው በኃላ ባልታሰቡና ወይም ያልተጠበቀ ግብ ባላቸው እጅ እየወደቁ ሌላ ተጨማሪ መከራን ሲፈጥሩ ተስተውላል፤ስልሆነም ትግሎች ግቦቻቸውን የሚተገብሩ ሰዎችንና ቡድኖችን ማንነት ማወቅ ይኖርባቸዋል ለዚህም የብዙሃኑ ተሳትፎዎች ወሳኝነት ይኖረቸዋል

 

 

እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ።

 

 

 Pen-4

aberashiferaw.wordpress.com

ኤርትራን በአቋራጭ (ከኤፍሬም እሸቴ)

$
0
0

በሰሜን ምዕራቧ የአሜሪካ ከተማ በሲያትል ኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን የሚርመሰመሱበት አንድ ሰፈር አለ። ንግድ ቤቶቹ፣ ጋራዦቹ፣ ሬስቶራንቶቹ እና እዚያ አካባቢ የሚቆሙት መኪናዎች አብዛኛው የኛ ሰዎች ንብረት ናቸው። ከመንገዱ አንዱ ኮርነር ላይ “ስታርባክስ” ቡናመጠጫ ደረቱን ሰጥቶ መንገዱን ቁልቁል ይመለከታል። ወደ ውስጥ ሲገባ አንዱ ጥግ “የኢትዮጵያውያን ጥግ” ነው፤ ሌላው ደግሞ “የኤርትራውያን ጥግ”።

 

አንድ ኢትዮጵያዊ ሲገባ እግሩ የሚመራው ወደራሱ አገር ጥግ ነው። መቀመጫ ባይኖርና በኤርትራው ጥግ በኩል ባዶ ቦታ ቢገኝ፣ ወደዚያ ለመሔድ አይሞክርም። ድንበር አይሻገርም። አንድ ኤርትራዊም እንዲሁ ወንበር ቢሞላበት ወደ ኢትዮጵያው ጥግ ለመሔድ አይሞክርም። ይህንን የሚነግረኝ ወዳጄ እየሳቀ ነው። ስታርባክሱ የባድመ ግንባር (ጦርነት የሌለበት፣ ነገር ግን ወታደሮቹ የተፋጠጡበት) አሊያም የአሰብ ቡሬ ግንባር መሰለኝ። ለመግባት አልፈለግኹም።

 

ኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን በየሄዱበት ድንበርተኛ ሆነው መኖር ይፈልጋሉ ልበል? የተለያየን አገሮች ነን ብለው እንደሚለፍፉት ሳይሆን ተለያይተውና ተቆራርጠው ለመኖር አይፈልጉም።  ሆድ ሲያውቅ ዶሮ ማታ። የሚገርመው ግን ድንበርተኛ መሆን ሲፈልጉ ባድመ ግንባርንም አብረው እየገነቡ ነው። ጦራቸውን ሰድረው። የአበባ መስክ ያለበት ድንበር አይመቻቸውም – ሁለቱም። “አብረው ለመኖር የማይችሉ፣ ተለያይተው ለመኖርም የማይችሉ” የተባለው ለእነርሱ ሳይሆን አይቀርም። ይህንን የሚያፈርስ ገጠኤርትራን በአቋራጭ

መኝ ያገኘኹት ደግሞ ከሰሞኑ ወደ ሰሜን ካሊፎርኒያ ጠቅላይ ግዛት ሳን-ሖዜ ከተማ በሔድኩበት ወቅት ነውና ገጠመኙን በደስታ (ከልቤ ደስስስስ እያለኝ) ላጫውታችሁ።

 

በሰሜን አሜሪካ የተለያዩ ስብብሰቦች አሉ። ከሰፈር ልጅና ዕድር ጉባኤ እስከ ሃይማኖትና ፖለቲካ፣ ከብሔረሰብ ስብስብ እስከ ስፖርት ቡድኖች ድረስ። ከነዚህ ውስጥ በአሜሪካ የሚገኙ ወጣቶች ያቋቋሙትና ባለፈው ሳምንት 13ኛ ዓመቱን ያከበረው “የሰሜን አሜሪካ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጉባኤ” አንዱ ነው። ከመላው አገሪቱ የሚሰባሰቡ ወጣቶች የሚካፈሉበት የሦስት ቀናት ኮንፈረንስ አካሂዷል።

 

ዝግጅቱን ያዘጋጁት በሳንሆዜ እና በአካባቢው የሚገኙ ወጣቶች እና እነርሱ የሚያገለግሉባቸው አብያተ ክርስቲያናት ናቸው። ኋላ ግን እንደሰማኹት ዝግጅቱን አብረው ያከናወኑት ከሳንሆዜ ወጣ ብለው ከሚገኙት ከተሞች (ለምሳሌ ከኦክላንድ) የመጡ ኤርትራውያን ወጣቶች ጭምር መሆናቸውን ተረዳኹ። ለካስ አለማወቄ ነው እንጂ እዚያው አብረውኝ ከሚውሉት መካከል አንዳንዶቹ ኤርትራውያን ነበሩ። አንዱ ወጣት መልከ መልካም ልጅ ራሱን አስተዋውቆ እስኪነግረኝ ድረስ አላወቅኹም ነበር።

 

አማርኛው ለክፉ አይሰጥም። በእጁ የያዘው መጽሐፍ የአማርኛ ነው።

“የት ለመድክ አማርኛ” አልኩት።

“እዚሁ ነው የለመድኩ”።

“ስንት ጊዜ ፈጀብህ?”

“አንድ ስድስቲ ምናምን ወር ይሆናል”።

 

ዲያቆን ነው። የቤተ ክርስቲያን ትምህርት ይማር ነበረው ከአንድ ኢትዮጵያዊ መሪጌታ ኖሯል። እሳቸውን ሁል ጊዜ “ደህና ነሽ” ይላቸው እንደነበር “ነሽ ለሴት፣ ነህ ለወንድ” እያሉ እንደሚያርሙት እየሳቀ ነገረኝ። ገና ለጋ ወጣት። 19 ዓመቱ ነው። በዚህ ዓመት የመጀመሪያ ዓመት ትምህርቱን ተከታትሏል። ወደ ሁለተኛው ተሸጋግሯል። በዕድሜ እኩያ ከሚሆኑት ኢትዮጵያውያኑ ጋር ቶሎ ተላምዷል። ወጣት አይደል?

 

ሌላው ወጣት ወደ ሃያዎቹ አጋማሽ ነው። እዚሁ አሜሪካ ያደገ ሳይሆን የስደትን መከራ ቀምሶ የመጣ ስክን ያለ ልጅ ነው። እንደ ሌሎቹ ስደተኛ ወገኖቹ በሱዳንና የመን አልተጓዘም። በከባዱ የኢትዮ-ኤርትራ ድንበር አልፎ ኢትዮጵያ በሰላም ለመግባት የቻለ “ዕድለኛ ልጅ”። ቃሉን ተውሼ እንጂ “ዕድለኛ ልጅ” ያለው ራሱ ነው። አማርኛ ጥሩ አድርጎ ይናገራል። “መጻፍ ነው ችግሬ”  ብሎኛል። ታሪኩ ደግሞ ልብ ይነካል።

 

ወጣቱ ብሔራዊ ውትድርናውን ጨርሷል። ከአንዱ የጦር ግንባር ወደ ሌላው ጦር ግንባር ሲዟዟር አሳልፏል። ጦርነት ባይኖርም። “ዓይንህን ለአፍታ እንኳን ከምሽጉ እንድትነቅል አይፈቀድም” ብሎኛል። “አንድ ቦታ አያስቆዩንም። መቀያየር ነው። አንዴ ቡሬ፣ አንድ ባድመ፣ አንዴ ….”። ከዚያ ሲመርረው አገሩን ጥሎ ለመሰደድ ወሰነ።

 

“አገሩ ውስጥ ወጣት የሚባል የለም’ኮ። አንድ ልጅ 16፤ 17፣ 18 ዓመት ከሆነ የሚያስበው መጥፋት ነው። አባት ከሆንክ ግን የት ትሔዳለህ። መማረር ብቻ። ሰዉ አይናገርም። ዝ…..ም ብቻ”። (‘ም’ን ላላ አድርጎ እየጠራት።)

 

ወደ ኢትዮጵያ ሲገባ ሽሬ አካባቢ ወደሚገኝ የስደተኞች ካምፕ እንዲገባ ተደረገ። እርሱ ብቻ ሳይሆን ከሌሎች ብዙ የአገሩ ሰዎች ጋር። ለአራት ዓመታት ኖረ።

 

“ምን ታደርግ ነበር?” ጠየቁት።

“ለእኔ ስኮላርሺፕ ማለት ነበር። አማርኛ ተማርኩ። መጻሕፍት ማንበብ ቻልኩ። የሚገርምህ ወደ አሜሪካ ስመጣ ሻንጣዬ 50ኪሎ ይመዝናል። 48ቱ ኪሎ መጽሐፍ ነው።”

“ሌሎቹስ ጓደኞችህ ምን ይሠሩ ነበር?”

“ሌሎቹም ዝም ብለው አልተቀመጡም። ቅኔ፣ ዜማ፣ መጻሕፍት ለመማር ወደ ጎጃም፣ ወደ ጎንደር፣ ወደ ሸዋ ሄዱ።”

“ኢትዮጵያ መጥተህ አታውቅም አይደል ከዚያ በፊት?”

“አላውቅም። ናጽነት ከመጣ በኋላ ደግሞ ችግር ሆነ። ኢትዮጵያ ማለት ሰይጣን ማለት ነበር የሚመስለኝ።”

ገታ አደረገና አንገቱን ነቀነቀ። እኔም “ለምን እንደዛ አሰብክ ምናምን” ወደሚል ጥያቄ ውስጥ መግባት አልፈለግኹም። ከሚናገረው ይልቅ በአካላዊ እንቅስቃሴው የሚያሳየው ብዙ ይናገር ነበር።

 

ወጋችንን ሳናጠናቅቅ የራት ሰዓት ደረሰና ወደ ማዕዱ ታደምን። ቀስ በቀስ ጠረጴዛችን ሞላች። ሁሉም ኤርትራውያን ናቸው። ወንዶችም ሴቶችም። ገና ወጣቶች። ሁሉም አማርኛ ይሰማሉ፣ ይናገራሉ። የተማሩት ግን በቅርብ ነው። አንዲቱ ልጅ ብቻ ገና አማርኛ አልተማረችም። አንዱ ኢትዮጵያዊ እየሳቀ “ጆሮሽን ቢቆርጡሽ አትሰሚም ማለት ነው?” አላት። ሌሎቹ የአገሯ ልጆች ሳቁ። ትርጉሙ ሲነገራት እሷም ሳቀች። የዛሬ ዓመት እሷም አማርኛ የምትችል ይመስለኛል።

 

“አማርኛ መማር ይሄን ያህል ቀላል ነው ማለት ነው?” አልኳቸው። አዎንታዊ መልስ አገኘኹ። በውስጤ “ለምን ትግርኛ አልተማርኩም ነበር? የመማር ዕድል ነበረኝ? ልማረው የምችለው ሌላ የአገራችን ቋንቋ  ነበር?” እያልኩ አሰላሰልኩ።

 

“አስመራ፤ ቤት ሙዚቃ ውስጥ አማርኛ ዘፈን እኮ መክፈት አይቻልም” አለኝ ቅድም ታሪኩን ያጫወተኝ ልጅ። ለካስ ክልከላው ጠንከር ያለ ኖሯል። ግን አልሰራም። ወጣቶቹ የፖለቲካ ድንበርን በፍቅር እየተሻገሩት ነው። ለብዙ ዘመናት ሲዘራ የነበረው የጥላቻ ዘር በጥቂት ግንኙነቶች ሲመክን ማየት እጅግ ያስደስታል። ወጣቱ በትግራይ ስላጋጠመው መልካም ነገር ሁሉ ተናግሮ አይበቃውም።

 

“አዲስ አበባ የቆየኹት አንድ ሳምንት ብቻ ነው። አሜሪካ ልመጣ ስል።” . . . ትንሽ ቆየት ብሎ ቢያየው ተመኘኹ። አዲስ አበባ የብሔረሰቦች ሁሉ መናኸሪያ፣ የኢትዮጵያዊነት ናሙና ማሳያ። ክትፎውን ቢበላ፣ ጠጁን ቢጠጣ፣ ከወያላው ጋር ቢላከፍ፣ ቆጮውን ቢሞክር፣ ቡላውን፣ ጨጨብሳውን፣ ዶሮ ወጡን …። “አብሮ የበላን ቅዱስ ዮሐንስ አይሽረውም” ይሉ የለ አባቶቻችን?

 

የሄድንበት ኮንፍረንስ እሑድ ማታ ሲጠናቀቅ ከሲያትል በመጡ ወጣቶች እና በሳንሆዜ አካባቢ በሚገኙበት መካከል ትልቅ የጨረታ ፉክክር ተጀምሮ ነበር። የሳንሆዜዎቹ ቁጥራቸው አነስተኛ በመሆኑ ውድድሩ ሲከብዳቸው ኤርትራውያኑ ወጣቶች ያግዟቸው ጀመር። በዚያ ውስጥ የምመለከተው የተለያዩና ለጦርነት የሚፈላለጉ ድንበርተኛ አገሮች ሳይሆን ወጣትነትና ፍቅር ያስተሳሰራቸው ፍጡራንን ነበር። ጠቢቡ ሰሎሞን እንዳለው ሆነ፤ “የጐመን ወጥ በፍቅር መብላት የሰባ ፍሪዳን ጥል ባለበት ዘንድ ከመብላት ይሻላል።” (መጽሐፈ ምሳሌ 15፥17)

Moving-picture-Ethiopia-flag-flapping-on-pole-with-name-animated-gif

ይቆየን – ያቆየን


Hiber Radio: “በኢትዮጵያ ስም እንማማላለን እንጂ አንተባበርም”–ዶ/ር መረራ ጉዲና (ቃለ ምልልስ Audio)

$
0
0

merara gudinaህብር ሬዲዮ ከዶ/ር መረራ ጊዲና የመድረክ እና የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንፈረንስ የወቅቱ ሊቀመንበር ጋር የተደረገ ወቅታዊ ቃለ መጠይቅ

ዶ/ር መረራ ጊዲና ስለ ተቃዋሚዎች የትብብር ጥያቄ፣ በወቅቱ የሰላማዊ ሰልፍ እንቅስቃሴ የት ድረስ መሄድ እንደሚቻል፣ በገዢው ፓርቲ የኮንደሚኒየም ተመዝገቡ ዘመቻ፣ በውጭ ያለው በአገሩ ለውጥ እንዲመጣ የሚደግፈው ሀይል እውን ተገቢውን ድጋፍ ያደርጋል? ተቃዋሚዎችስ የሚገባቸውን ያህል እየተንቀሳቀሱ ነው? ስለ አዲሱ <<የኢትዮጵያ ፖለቲካ ምስቅልቅል ጉዞና የሕይወቴ ትዝታዎች>> መጽሐፋቸው ምን ይላሉ? ለምድነው የኦሮሞ ተወላጅ ኢትዮጵያውያን በውጭ አገር ከሌሎች ወገኖቻቸው ጋር ተሰልፈው የማይታገሉት? የሙስሊሙን ሰላማዊ እንቅስቃሴን አስመልክቶና በሌሎችም ጥያቄዎች ላይ አወያይተናቸዋል። ለአጭር ጊዜ ቆይታ በመጡበት አግኝተን ለአቀረብንላቸው ጥያቄ በመቀበል ፈቃደኛ በመሆናቸው በህብር ሬዲዮ አድማጮች ስም እናመሰግናለን:-

ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ እና አንዳርጋቸው ጽጌ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከሕዝብ ጋር ሊወያዩ ነው

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) የግንቦት 7 ንቅናቄ አመራር የሆኑት ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ እና አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ እሁድ ሴፕቴምበር 22 ቀን 2003 በዋሽንግተን ዲሲ/ ቨርጂኒያ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ለሕብረተሰቡ ገለጻ ለማድረግ ሕዝባዊ ስብሰባ መጥራታቸውን የመርሃ ግብሩ አዘጋጆች ለዘ-ሐበሻ በላኩት በራሪ ወረቀት አስታወቁ። “የወቅቱ የኢትዮጵያ ተጨባጭ ሁኔታና ለነፃነትና ለዴሞክራሲ የሚደረገው ትግል ላት ገለጻ ይደረጋል” በሚል በአርሊንግተን ቨርጂኒያ ከቀኑ 2 ሰዓት ጀምሮ የተጠራው ይኸው ሕዝባዊ የውይይት መድረክ ሰፊ የጥያቄና መልስ ክፍል ስለሚኖረው ማንኛውም ኢትዮጵያዊና ኢትዮጵያን ወዳጅ በመገኘት እንዲሳተፍ አዘጋጆቹ ጥሪያቸውን አቅርበዋል። ለዚህ ሕዝባዊ ውይይት መድረክ የመጥሪያ በራሪ ወረቀት የሚከተለው ነው።

Dr berehanu nega

የኢትዮጵያውያን ባህልና የጋብቻ ቅድስና – (ተፈራ ድንበሩ)

$
0
0

ኢትዮጵያ ቅድስት መሆኗን የሚያሳዩ ማስረጃዎች፤
ኢትዮጵያ የሚለው ያገራችን መጠሪያ የተገኘው በካም ወገን ሴማዊ ከሆነውና ከነሙሴና አሮን በፊት ካህን ከነበረው መልከጼዴቅ ከሚባል ኢየሩሳሌምን ከመሠረተው ንጉሥ በተወለደውና ኢትዮጵ ከሚባል በኋላ ኢትዮጲስ ተብሎ የኢትዮጵያ ንጉሠነገሥት ከነበረ ሰው የመጣ ስያሜ መሆኑን የቤተክርስትያን መረጃዎች ያመለክታሉ (ፍቅሬ ቶሎሳ 1-10)። ኢትዮጵያውያን ከሁለቱ የኖህ ልጆች ካም (በኩሽ በኩል) እና ሴም (በአብርሃም በኩል ከእሥራኤላውያን ወገን) የተገኙና ተደባልቀው የተባዙ ዘሮች ሲሆኑ ለምሳሌም አፋር (ከ Ophir) የሴም ወገን ከሆነው ነገደ ዮቅጣን የመጣና በአፍሪካ ቀንድ ከጥንት ጀምሮ የነበረ ሕዝብ ሲሆን የአህጉሩ መጠሪያም ከዚሁ ቃል እንደተገኘ ይነገራል። በአርኪዎሎጂና አንትሮፖሎጂ ጥናት ከመረጋገጡ በፊት ሔሬዶተስና ዲዎዶረስ የተባሉ የጥንት የታሪከ ፀሐፊዎች የመጀመሪያው ሰው የኖረው በኢትዮጵያ እንደነበረ ጽፈዋል (Gates 68)። ኢትዮጵያውያን ዛሬ በቋንቋ ተለያይተው ይታዩ እንጅ፣ የካም፣ የሴም፤ የኦሞቲክና የኒሎቲክ ነገዶች ውሁድ የሆነ አንድነት አላቸው። በባህል ብቻ ሳይሆን በዘርም ተቀላቅለዋል። አሁን ባገራችን ከሚነገሩት ከ፹ በላይ ቋንቋዎቻችን ውስጥም ብዙዎቹ ከጥንቱ ግዕዝ፣ ከሳባ (ሱባ)፣ እብራይስጥ፣ ግሪክና ከሌሎች የሴምና የኩሽ እንዲሁም በአባይ ወንዝና ኦሞ ሐይቅ የተሰየሙ (ኒሎቲክ እና ኦሞቲክ ) አፍሪካዊ ቋንቋዎች ተገኝተውና ተቀያይጠው ትውልዶች እየበዙ ሲሄዱ በተጓዳኝ የተባዙ ናቸው።

መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚያመለክተን ኢትዮጵያ በእግዚአብሄር ዘንድ ከፍተኛ የቅድስና ደረጃ አላት (መዝሙር ፷፰፤፴፩፣ ትንቢተ አሞጽ ፱፡፯)። አገራችን መንፈሳዊነት የሰፈነበት ባህል ያላት ስለሆነች ልዩነቶችን አቻችሎ አብሮ መኖርን፣ ለጋስነትን፣ መረዳዳትንና እንግዳ ተቀባይነትን አዋህዳ ለቤተሰብም ከፍተኛ ክብር በመስጠት የኖረች የጥንት አገር ነች። ሆኖም ትውልድ እየበዛ ሲሄድ ይህች ምድራዊ ገነት የሆነች አገር በየቦታው የተሟላ የተፈጥሮ ሀብትና የአየር ንብረት ስላላት ብዙዎች ሕዝቦቿ በተለያዩ አካባቢዎች በወንዝ፣ ተራራ፣ ወዘተ ተካለውና ራሳቸውን ችለው ለረጅም ዘመናት ሲኖሩ በቋንቋዎቻቸውም እንደዚሁ ተለያይተው ዛሬ የሚታየውን የብሔር-ብሔረሰብ ሰያሜዎች ዝርዝር ሊያስከትል ችሏል (ተፈራ ድንበሩ 59-60) ።
eth church cry
በመዝሙር ፷፰፡፴፩ ላይ “ኢትዮጵያ ታበፅሕ እደዊኃ ሀበ እግዚአብሔር” የተባለችበትም ያለምክንያት አይደለም፤ ከእግዚአብሔር በሲና ተራራ ሕገ-ኦሪትን የተቀበለው ሙሴ የተመላለሰባት፣ ክርስቶስ ከእናቱ ከቅድስት ድንግል ማርያም ጋር በሕፃንነቱ ተሰዶ የሄደባት አገር በመሆኗ ኢትየጵያ ለቅድስት ድንግል ማርያም አሥራት እንደተሰጠችና በሷ አማላጅነት የመዳን ተስፋ እንደተሰጠን ቅዱሳት መጻሕፍት ይናገራሉ። በ፬ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በቅዱስ ፍሬምናጦስ/አባሰላማ/ አማካይነት ክርስትና በመንግሥት ደረጃ ቢታወጅም ከዚያ በፊት ሐዋርያው ቅዱስ ማቴዎስ ወንጌልን ያስተማረበት አገር ነበረች፤ ቅዱስ ፊልጶስ ያጠመቀው የቤተመንግሥት ሹም ወደ ኢየሩሳሌም ለአምልኮት መሄድ ቀደም ሲል ኢትዮጵያውያን ከኢየሩሳሌም ጋር የነበራቸውን ሃይማኖታዊ ትሥሥር ያመለክታል (የሐዋርያት ሥራ ፰፡፳፮)። ክርስትና ቀድሞ ከገባባቸው አገሮች አንዷ ኢትየጵያ ስለሆነች ኦሪትንና ሐዲስን አጣምራ የቆየች ብቸኛ አገር ነች። እንዲሁም ፳፻/ ሁለት ሺ/ ዓመታት ከክርስቶስ ልደት በፊት በሥነጽሐፍ ዕድሜው ተወዳዳሪ ያልተገኘለት የግዕዝ ቋንቋችን በጽሐፍ ላይ የነበረ የመንግሥት መገልገያ ቋንቋ ሲሆን መጽሐፍ ቅዱስ መጀመሪያ ከተጻፈባቸው በጣት ከሚቆጠሩ — እብራይስጥ፤ አርማይክ፣ ፅርእ/ግሪክ/፣ ሲራይክ፣ ኮፕቲክ እና ከላቲን ቋንቋ በፊት የነበረ የአገራችን ትልቅ ሰነድ መሆኑ ሊያኮራን ይገባል። በቀደምት ሥነጥበብ ሙያ የሚታወቁት እነሼክስፔር፣ ሚካኤል አንጀሎና ላዎናርድ ዳቪንሲ ከመፈጠራቸው ከ፩ ሺ ዓመት በፊት ዓለም በጭለማ ውስጥ በነበረበት በ፮ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ታላቁ የቤተክርስትያናችን የዜማ አባት ቅዱስ ያሬድ ድጓ፣ ጾመድጓ፣ ምእራፍ፣ ዝማሬና መዋሴትን ደርሶ የግዕዝ፣ እዝልና አራራይን ቅኝት ለዓለም አበርክቷል።
አገራችን የብዙ ጻድቃንና ሰማዕታት አገር ነች፤ ለምሳሌ በ፲፭ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የነበረችው ክርስቶስ ሰምራ የኃጢአት ምንጭ የሆነው ሰይጣን ከአምላካችን ይቅርታ ተደርጎለት የሰው ልጅ ሁሉ ሥርየት እንዲያገኝ ቀንና ሌሊት በመፀለይ የቅድስና ሥራ የሠራችና ሌሎች እንደ አቡነ ገብረመንፈስቅዱስ፣ አቡነ ተክለሃይማኖት፣ አቡነ አረጋዊ፣ አባ ሣሙኤል ዘዋልድባ፣… ወዘተ ያሉ የቅድስና ገድሎቻቸው በቤተክርስትያን የሚታወቅላቸው ታላላቅ መንፈሳውያን አገር ነች። እንዲሁም ኢየሱስ ክርስቶስ በቤተልሔም እንደሚወለድ አወቀው ለክብሩ የሚገባውን ስጦታዎች ይዘው በኮከብ እየተመሩ ወደ ኢየሩሳሌም ከሔዱት ሰባሰገል ከሚባሉ አዋቂ ሰዎች መካከል ኢትዮጵያውያን ነበሩበት። ኢትዮጵያ ኦሪትን ከሐዲስ ኪዳን ጋር አስማምታ ፈሪሀ እግዚአብሄር ያደረበትንና የሰውን ልጅ አክብሮ፣ መብቶቹን ጠብቆ ማኅበራዊ አኗኗርን አዋህዶ የተሟላ ባህል ካላቸው ቀደምት አገሮች ውስጥ የሚተካከላት እንደሌለ ያሁኑ ልጆቿ ጠንቅቀው ያውቃሉ?

የሮማው መሪ ጁሊየስ ቄሣርና የአይሁድ መሪ ሄሮድስ ሥልጣናቸውን ለማቆየት የተወለደ ሕፃን ሁሉ ሲገድሉ ኢትዮጵያ ሰብአዊነትን በሚከተሉ የጥበብ ሰዎች ትመራ ነበር (ፍቅሬ ቶሎሳ 29-30)። እንደ ፈረንሳይ፣ ጀርመን፣ እንግሊዝ የመሳሰሉ የአውሮጳ አገሮች ማንበብ መጻፍ በማያውቁባቸውና ያልሠለጠኑ (barbarians) በነበሩባቸው ዘመናት አገራችን በራሷ ፊደል በተጻፈ ሕግና በመንግሥት ትመራ ነበር። በአውሮፓ ሰዎች በባህር ላይ ዘረፋ (piracy) ሲተዳደሩ በነበሩ ጊዜ ኢትዮጵያ ሕግና ሥርዓት የሰፈነባት አገር ነበረች። ሰብአዊ መብት በሌላው ዓለም እየተጣሰ ሰላማዊ ሕዝቦች ሲበደሉ ያገራችን መሪዎች ታድገዋቸዋል። የአይሁድ አክራሪዎች በአረቢያ ናግራን፣ በግብፅ የእስልምና አክራሪዎች በክርስትያኖች ላይ የፈጸሙትን የሰብአዊ መብት ጥሰት ተከላክለዋል፤ ሆኖም በዓለም ላይ በተፈጸመው የሃይማኖት ጦርነት ውስጥ ኢትዮጵያ አልተሳተፈችም። የአገራችን መሪዎች ከ፪፻ በላይ የእስልምና እምነት ተከታዮችን በእምነታቸው ምክንያት ለሕይወታቸው ሲሸሹ በስደት እኤአ በ፮፻፲፫ እና ፮፻፲፭ ዓም ተቀብለው አስተናግደዋቸዋል። ስደተኞቹን እንዲመልሱ የአረቢያው መሪ አቡ ሱፊያን በኃይል ለመጠቀም ቢዝትም የኢትዮጵያ ንጉስ አርማህ (አል አስማሃ ወይም ነጋሽም ይባሉ ነበር) የሚመጣውን ኃይል በኃይል መክቶ ለመመለስ በመወሰን የስደተኞቹን መብት በማስከበር በዓለም የመጀመሪያው መሪ ነበሩ። በዚህ የተነሣ ንጉሡን ነጃሽ በማለት በስማቸው መስጊድ አሠርተው አክብረዋቸዋል፤ ሆኖም አንዳንድ የአሁኑ እስልምና ሃይማኖት ፀሐፊዎች ለክብራቸው የተሠራላቸውን መስጊድ እንደማስረጃ በመውሰድ ንጉሥ አርማህን እስላምናን ተቀብለዋል እስከማለት ደርሰዋል።

ኢትዮጵያ በተለያዩ ጊዜያት በእንግድነት ወይም በጥገኝነት መጥተው በሰላም የሚኖሩ የማናቸውንም የሕዝብ ወገኖች ተቀብላ በማስተናገድ የታወቀች ነች። ማናቸውንም ሃይማኖት የሚከተሉ ኢትዮጵያውያን ሰው በመግደል ጽድቅ አለ ብለው ሳይሆን በመፈቃቀር የሚያምኑ ሲሆን፤ የእስልምና፣ የአይሁድና የክርስትና እምነት ተከታዮች ተከባብረው በሰላም የሚኖሩባት አገር ነች። ኢትዮጵያዊ ስደተኞችን መንገድ በመምራት የምትታወቅ ሲሆን፣ ዛሬ እንደ ሲናይ ባሉ የአረብ በረሀዎች ስደተኞች በእንግድነታቸው መንገድ ሲጠይቁ በአጻፋው በአንድ በኩል ሃይማኖት አለን ብለው በሚመጻደቁ በሌላ በኩል ደግሞ ነፍሰገዳይ በሆኑ ሰዎች ንብረታቸው ተዘርፎ የሚሰጡት ሲያጡ የሰውነት ሕዋሳቶቻቸው ተቆራርጦ የሚሸጥበት ዓይነት ክስተት በኦጋዴን፣ አውሳ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ ትግራይ፣ አፋር… ወዘተ በማናቸውም የኢትዮጵያ ክፍለ ሀገር ባላገር ዘንድ እንዲህ ያለ ድርጊት አስነዋሪ ነው።
ኢትዮጵያ ዲፕሎማሲን በማስተማር ቀደምት ከሆኑ አገሮች አንዷ ስትሆን ንግሥት ሳባ ለንጉሥ ሰሎሞን ባበረከተችው ስጦታ በእሥራኤልና ኢትዮጵያ መካከል አንድነት አንዲፈጠር ከማድረጉም በላይ ከንጉሥ ሰሎሞን በተወለደውና በኋላም በኢትዮጵያ በነገሠው ቀዳማዊ ምንሊክ አማካይነት የመጀመሪያው ጽላት ወደ አገራችን ገብቶ ይገኛል። ክርስቶስ የተሰቀለበት ግማደ-መስቀልም እንደዚሁ በአገራችን በግሸን ገዳም የሚገኝ ሲሆን በአገራችን የተፈጸሙ አያሌ መንፈሳዊ ገድሎችን ከቤተክርስትያን መረጃዎች ማግኘት ይቻላል።

ኢትዮጵያ በሕዝቦቿ የተባበረ ኃይል ወራሪዎችን እየመከተች የቆየች እንጂ በቅኝ ያልተያዘች አገር ከመሆኗም በላይ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅትን ቻርተር ካረቀቁት አገሮች አንዷ ነች። በቅኝ ግዛት የተያዙ የአፍሪካ አገሮችን ነፃ እንዲወጡ እንደነ ኔልሰን ማንዴላ ያሉትን በቅርቡም የናሚቢያን የነፃነት ታጋዮችን በማሠልጠንና ሌሎች በቅኝ አገዛዝ ሥር ለነበሩ አገሮች የቁሳቁስና የዲፕሎማሲ እርዳታ በማድረግ በአፍሪካ የፀረ-ቅኝ አገዛዝ ትግል ከፍተኛ ሚና ተጫውታለች። በ፲፱፻፶፭ ዓም የተመሠረተው የአፍሪካ ኅብረት በኢትዮጵያ መሪዎች የተገኘ ውጤት ነው ። እነዚህ አገራችንና ሕዝቦቻችንን ከሚያኮሩ ብዙዎች ነገሮች ጥቂቶች ብቻ ናቸው።

ኢትዮጵያዊ ሥነምግባር እጅግ የሚየኮራ — ሌብነት፣ ቅጥፈት፣ ሰውን በግፍ መግደል በየትኛውም እምነት የተወገዘ (taboo) ነው፤ እንኳንስ በሰው ላይ በእንሰሳት ላይ አንኳ ግፍ መፈጸም ከጥንት ጀምሮ በኢትዮጵያ ውጉዝ ነው። ዛሬ በአገራችን ከአሥራአምሰት እስከ ሃያ ሚሊዮን ሕዝብ ሥራ የሌለውና በአጠቃላይ 80% የሚሆነው ሕዝባችን ከድህነት መሥመር /poverty line/ በታች የሚኖር እንደሆነ የሚታወቅ ሲሆን አንደችግሩ መጠን ቢሆን ኖሮ በሌሎች አገሮች የሚፈጸሙ ወንጀሎች መናኸሪያ በሆነ ነበር፤ ሆኖም በዚህ የኑሮ ደረጃ ላይ ካለው ሕዝባችን ውስጥ እናቶች መቀነታቸውን እየፈቱ ያላቸውን ሲለግሱ ማየት የተለመደ ሲሆን፣ በየትኛውም አካባቢ ያለ ሕዝባችን ያለውን አካፍሎ የመኖር ባህል አለው። በበለፀጉ አገሮች በመንፈስ ጭንቀት ራስን ማጥፋት የተለመደ ሲሆን፣ የአገራችን ደሀ እንኳ በቅድስናው ስለሚያምን በተስፋ የተሞላ ስለሆነ መሬት ራሷ አፏን ከፍታ ካልዋጠችው በስተቀር እጁን ለሞት አይሰጥም።
ኢትዮጵያዊ ባህል በእድር፣ በእቁብ፣ ደቦና ሌሎች ማኅበራዊ ተቋሞች ተባብሮ ተጋግዞ መኖር ነው። ከመልካም ባህሎቿ መገለጫዎች ውስጥ ጋብቻ የተከበረ ተቋም ነው።

ቅዱስ ጋብቻ፤
ጋብቻ በሌላ አገላለጽ ትዳር ይባላል። ትዳር መተዳደር ከሚለው ቃል የተገኘና ኑሮን መሥርቶ በኃላፊነት ባለቤት ሆኖ ቤተሰብ ማስተዳደር ማለት ነው። ስለሆነም አንድ ሰው ትዳር ይዟል ሲባል በመሸበት አዳሪ ከመሆን ወይም ከነጠላነት/ላጤነት/ ወደሰከነና የተከበረ የኅብረተሰብ ሚና ተሸገጋግሮ ቋሚ/ሙሉ/ መተደዳሪያ ይዞ መኖርን ያመለክታል። በጋብቻ ተሳሥሮ ወልዶ ከብዶ መኖር የተቀደሰ ባህላችን ሲሆን በቤተሰብ አባላት መካከል ያለው መደጋገፍና መተሳሰብ በዓለም ላይ ተወዳዳሪ የሌለው ነው፤ ወላጆችን መጦር ወንድምና እህትን ብቻ ሳይሆን ዘመድ አዝማድን ወይም ረዳት የሌለውን የቤተሰብ አካል አድርጎ በሞግዚትነት ማሳደግ፣ ማስተማር ወይም ትዳር ማስያዝ ኢትዮጵያዊ ወግ ነው። ባል (ወንድ) እና ሚስት (ሴት) ተጋብተው ልጆችን በማፍራት የትውልድ ሐረግ የሚፈጠርበት ዓይነተኛ ሥርዓታችን ቤተሰብ ነው።

ጋብቻ ከባህላችን መገለጫዎች ውስጥ መሠረታዊ ሥርዓት ሲሆን በየብሔረሰቡ ያሉትን ዝርዝር የጋብቻ ሥርዓቶች በስፋት ለመግለጽ ጊዜና እቅም የሚጠይቅ ስለሆነ በዚህ ጽሑፍ ትኩረት ለማድረግ የተሞከረው በጋራ ባህሎቿና የኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነትን በሚከተሉት ወገኖች ያለውን ልማድ (tradition) ነው።

ስለጋብቻ መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል፤ “ እግዚአብሔርም ሰውን በመልኩ ፈጠረው፤ በእግዚአብሔር መልክ ፈጠረው፤ ወንድና ሴት አድርጎ ፈጠራቸው፤ እግዚአብሔርም ፣ ባረካቸውም፣ እንዲህም አላቸው፤ ብዙ ተባዙ ምድርንም ሙሉአት ግዟትም፤ የባህርን ዓሣዎች የሰማይን ወፎች በምድር ላይ የሚንቀሳቃሱትንም ሁሉ ግዟቸው” (ኦሪት ዘፍጥረት ፩፡ ፳፯-፳፰)። “እግዚአብሄር አምላክም በአዳም ከባድ እንቀልፍን ጣለበት፤ አንቀላፋም፤ ከጎኑም አንዲት አጥንትን ወስዶ ስፍራውን በሥጋ ዘጋው፤ እግዚአብሔር አምላክም ከአዳም የወሰዳትን አጥንት ሴት አድርጎ ሠራት፤ ወደ አዳምም አመጣት። አደምም አለ፤ ይህች አጥንት ከአጥንቴ ናት፤ ሥጋም ከሥጋዬ ናት፤ እርስዋም ከወንድ ተገኝታለችና ሴት ትባል። ስለዚህ ሰው አባቱንና እናቱን ይተዋል፤ በሚስቱም ይጣበቃል፤ ሁለቱም አንድ ሥጋ ይሆናሉ” ኦሪት ዘፍጥረት ፪፡ ፳፩-፳፬። እንዲሁም በማቴዎስ ወንጌል ፲፱፡ ፬-፮፣ ኦሪት ዘፍጥረት ፪፡ ፳፪-፳፬፣ የሐዋርያው ጳውሎስ መልእክት ወደ ኤፌሶን ሰዎች ም ፭ ቁ ፴፩-፴፪ ሁሉ እንደተገለጸው የእግዚአብሔር ቃል “ሰው አባቱንና እናቱን ይተዋል ከሚስቱም ጋር ይተባበራል፤ ሁለቱም አንድ ይሆናሉ” ይላል።
ዝሙትም ፈጽሞ የተከለከለና ኃጢአት ነው። “አመጸኞች የእግዚአብሔርን መንግሥት እንዳይወርሱ አታውቁምን? አትሳቱ ሴሰኞች ቢሆኑ ወይም ጣኦትን የሚያመልኩ ወይም አመንዝሮች ወይም ቀላጮች ወይም ከወንድ ጋር ዝሙት የሚሠሩ ወይም ሌቦች ወይም ገንዘብን የሚመኙ ወይም ሰካሮች ወይም ተሳዳቢዎች ወይም ነጣቂዎች የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም። (፩ኛ ቆሮንጦስ ፮፡ ፲-፲፩) “ሥጋችሁ የክርስቶስ ብልቶች እንደሆነ አታውቅምን? እንግዲህ የክርስቶስን ብልቶች ወስጄ የጋለሞታ ብልቶች ላደርጋቸውን? አይገባም። ወይስ ከጋለሞታ ጋር የሚተባበር አንድ ሥጋ እንዲሆን አታውቁምን? ሁለቱ አንድ ሥጋ ይሆናል ተብሏልና። ከጌታ ጋር የሚተባበር ግን አንድ መንፈስ ነው። ከዝሙትም ሽሹ። ሰው የሚያደርገው ኃጢአት ሁሉ ከሥጋ ውጪ ነው፤ ዝሙትን የሚሠራ ግን በገዛ ሥጋው ላይ ኃጢአትን ይሠራል (፩ኛ ቆሮንጦስ ፮፡ ፲፭-፲፰)። እንዲሁም በማቴዎስ ወንጌል ፲፱፡ ፲፰-፳ ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰዎች በሰጠው ሕግ “አትግደል፤ አታመንዝር፣ አትሥረቅ፣ በሐሰት አትመስክር፣ አባትህንና እናትህን አክብር፤ ባልንጃራችህን እንደራስህ ወደድ” ብሏል። ፩ኛ ቆሮንጦስ ፯፡ ፪-፮ ላይ፣ “ስለዝሙት ጠንቅ ለእያንዳንዱ ለራሱ ሚስት ትኑረው፣ ለእያንድንዲቱ ደግሞ ለራስዋ ባል ይኑራት። ባል ለሚስቱ የሚገባትን ያድርግላት፤ እንደዚሁም ደግሞ ሚስቲቱ ለባልዋ። ሚስት በገዛ ሥጋዋ ላይ ሥልጣን የላትም፤ ሥልጣን ለባልዋ ነው እንጂ፤ እንዲሁም ደግሞ ባል በገዛ ሥጋው ላይ ሥልጣን የለውም ሥልጣን ለሚስቱ ነው እንጂ።…እርስበርሳችሁ አትከላከሉ፤ ራሳችሁን ስለ አለመግዛት ሰይጣን እንዳይፈታተናችሁ ደግሞ አብራችሁ ሁኑ” ይላል።
እግዚአብሔር ጋብቻን የመሠረተው ሰው ብቻውን ከሚሆን ይልቅ ከሚስቱ ጋር እንዲረዳዱ፣ በመንሳዊ አንድነት በፍቅር ተባብረው አንዲኖሩና ዘር እንዲተኩ ነው። ስለሆነም ከዚህ ውጭ የሚደረግ ግንኙነት ሁሉ ሕገወጥና ኃጢአት ነው። ኦሪት ዘሌዋውያን ም ፲፰፡ ፳፫-፳፫ ላይ፣ “ከሴትም ጋር እንደምትተኛ ከወንድ ጋር አትተኛ ጸያፍ ነገር ነውና፤ እንዳትረክስበትም…” ይላል። ኦሪት ዘሌዋውያን ፳፡ ፲-፲፮ እንደተገለጸው የሚያመነዝር ወይም ግብረሰዶም የሚፈጽም ወይም ከእንሳሳ ጋር የሚገናኝ በሞት እንዲቀጣ ያዛል።

ልጅ በወላጆቹና ዘመዶች ታፍሮና ተከብሮ የሚኖርበት ኢትዮጵያዊና ማኅበራዊ ትልቅ እሴት ሲወርድ ሲዋረድ የቆየው ቤተሰብ ሲሆን፣ የመንፈሳዊ መሠረቱ ጥንካሬ በክርስትያኑ ሕዝባችን ብቻ ሳይሆን በሌሎች እምነት ተከታዮች ጭምር ጋብቻ በአገራችን ክቡርና የተቀደሰ ሆኖ ቆይቷል።

ቀደም ሲል ልጅህን ለልጄ እየተባለ ቤተሰቦች የልጆችን ጋብቻ ይወስኑ የነበረው ባህል ዛሬ ኋላ-ቀር ሆኖ ቢታይም በወቅቱ በነበረው ሁኔታ ለቤተሰብ መጠናከር ከፍተኛ አስተዋጽዖ ያደረገና ተቀባይነት የነበረው ባህል ነበር። ለአቅመ አዳምና ሔዋን ያልደረሱ ሕፃናት በቤተሰቦቻቸው ውሳኔ ተጫጭተው አንድ ላይ እንዲያድጉ ከተደረገ በኃላ ዕድሜአቸው ደርሶ በአካል መገናኘት ሲጀምሩ ጋብቻው እውን እየሆነ ይሄድ ነበረ። ሁለቱም ሌላ የሚያውቁት ጓደኛና የፆታ ግነኙነት ስለማይኖራቸው ጋብቻውን ከማክበርና ትዳራቸው እንዲሳካ እንደ አንድ አካል ለአንድ ዓላማ በመቆም ጠንካራ ቤተሰብ ከመገንባት በስተቀር ሌላ ምርጫ አልነበራቸውም፤ ሆኖም ይህ የቆየ ልምድ መሥመሩን ስቶ በተለይ ሴቶች ልጆች ሰብአዊ መብታቸው እየተገፈፈ ቅጥ ያጣ የወንድ ጭቆና እየከፋ ስለሄደ በሕግ የቀረ ሲሆን ሴቷም የመምረጥ ዕድል ልትቀዳጅ ችላለች።

ሆኖም ጋብቻን በነፃ ምርጫ የመፈጸሙ መብት የማያወላዳ ሲሆን ነፃነቱም በአግባቡ ትግባራዊ ካልሆነ የራሱ መዘዝ ሳይኖረው አልቀረም። ዛሬ በሃይማኖት ሥርዓት ካልተገዙ በስተቀር ወንዱም ሆነ ሴቷ ብዙ ጋደኞችን ሲፈትሹ ከቆዩ በኋላ ይጋባሉ፤ በራሳቸው ምርጫ መጋባታቸው በጉልህ የሚታይ የመብት መሻሻል ሲሆን ለወጣቶቹ መሳሳብ ቀጥታና ተዘዋዋሪ ምክንያት (ውበት፣ ሀብት፣ ፀባይ፣ ማህበራዊ ሚና፣ ወዘተ) እንደሚኖር የታወቀ ነው። ሆኖም ሲፈላለጉ የተሳሳቡበት/ የተማረኩበት ነገር ሲለወጥ ወይም ወረቱ ሲያልቅ መውደድ ሚዛኑን ያጣና በሰበብ አስባቡ አለመግባባትና የፍቅር መሻከር ይከተላል። ሲተጫጩ ሊማረኩበት የቻሉበት ነገር የፍቅር መነሻ መሆኑ ባይከፋም በመንፈሳዊ ኃይል ካልተጠናከረ መጀመሪያ ያሳሳባቸው ነገር ቢለወጥ፣ መንፈሳዊ እምነትና የቤተሰብ ጫና በበጎ መልኩ መፍትሔ ሊሰጥ የሚችልበት ኃይል ስለማይኖር የጋብቻው ኅልውና አደጋ ላይ ሊወድቅ ይችላል። ቤተሰብም የመበተን ዕድል ሊያጋጥመው ይችላል። እንዲየውም ሠልጥኗል በሚባለው ዓለም ውስጥ የግለሰብ መብት በከፍተኛ ደረጃ ስሚከበርና ይህም ለማኅበራዊ ፍላጎት ሳይሆን ለግለኝነት የሚያመቻች ስለሆነ በቅዱስነቱ ልጆችን ወልዶ በጋራ በአንድ መንፈስ በማሳደግ ፋንታ ጋብቻ እንደማንኛውም ኮንትራት እየታየ ጥቅሞችን እንደመስጠትና መቀበል ያሉ ቁሳዊ ልውውጥ ተራ ባህርይ ውስጥ ስለሚገባ ማኅበራዊ እሴትነቱና ለዛው ጠፍቶ በሕግ ሽፋን ውስጥ ብቻ እርቃኑን ስለሚቀር ፍቅር አልባ ይሆናል፤ ዓላማውን ለመፈጸም ብቃት ከማጣቱም በላይ ሕልውናውም አስተማማኝ አይሆንም።
በሌላ መልኩ ዛሬ በመብት ስም በተለይም ሠለጠኑ በሚባሉት አገሮች እየተከሠተና አልፎ አልፎም በመንግሥት ደረጃም ዕውቅናን ያገኘው እጅግ አሳፋሪ የሆነው የተመሣሣይ ፆታ ጋብቻ /same sex marriage/ ጉዳይ ሲሆን ኅብረተሰባችን ውስጥ ያልገባ ቢሆንም በተለይ በመደበኛ ትምህርት ቤት በሥነፍጥረት /biological science/ ትምህርት የሰዎች የግል ምርጫ መሆኑን እንዲያይ ተደርጎ የሚማረው ወጣት በማኅበራዊ ኑሮ ላይ የሚያስከትለውን አደገኛነት ጠንቅቆ እንዲያውቀው ማድረግ ያስፈልጋል።

ስለተመሣሣይ ፆታ ግንኙነት ወይም ጋብቻ እግዚአብሔር በሰዶምና ገሞራ ሕዝቦች ላይ ቅጣት በመፈጸም ለዓለም ሕዝብ ትምህርት ሰጥቷል። ይህም በኦሪት ዘፍጥርት ም ፲፰ እና ፲፱ ላይ ተገልጿል። ሰዶምና ገሞራ በሚባሉ በዮርዳኖስ ወንዝ ዳርቻ በሚገኙ ሁለት የጥንት ከተሞች ውስጥ እግዚአብሔር ከፈቀደው የተፈጥሮ የፆታ ግንኙነት ውጭ ወንድ ከወንድ እየተገናኘ ኃጢአት ስለበዛ እግዚአብሔር ከተማውን ከነሕዝቡ ሊያጠፋ እንዳሰበ ለአብርሃም ነገረው። አብርሃምም ጥቂት ንጹሐን ሰዎች ቢገኙ እንዲምርለት ለምኖት ፲ እንኳን ንጹሐን ሰዎች ቢገኙ በነዚያ ምክንያት ሁሉንም እንደሚምርለት እግዚአብሔር ቃል ገባለት። በመሸ ጊዜ ሁለት ሰዎች ወደሰዶም ገቡ፤ ሎጥም በሰዶም በር ተቀምጦ ነበር፤ ሎጥም በእንግድነት ተቀብሎ ያሳድራቸው ዘንድ ለመናቸው፤ በቤቱም አስተናገዳቸው፤ ሆኖም የሰዶም ሰዎች ተሰብስበው እንደተለመደው ሁለቱን ሰዎች በግበረሥጋ ሊደፍሯቸው የቤቱን በር ሰብረው ሊገቡ ሎጥን በታገሉት ጊዜ በሰዎች ተመስለው የመጡት ሁለት እንግዶች መላእክት ስለነበሩ ሕገወጦቹን ሰዎች አሳወሯቸው፤ ሎጥንም አሉት፣ ቤተሰብህን ይዘህ ከዚህ ከተማ ውጣ፤ እኛም ይህን ከተማ እናጠፋዋለን አሉት፤ በዘገየ ጊዜም አዝነውለት እጁን ይዘው አወጡት፤ ወደኋላም እንዳያይ ነገሩት፤ ከነቤተሰቡም ከሰዶም ወጥቶ ከመቅሰፍቱ ሲድን ሰዶምና ገሞራ ከነሕዝቡ ተቃጠሉ፤ ሆኖም የሎጥ ሚስት ወደኋላ ስለተመለከተች የጨው ሀውልት ሆና ቀረች። ከዚህ በኋላ ሕገወጥ የፆታ ግንኙነት ግብረሰዶም ተባለ።

ዛሬ ያለው ችግር በአንዳንድ ማህበረሰቦች ዘንድ እንዲህ ያለ የፆታ ሥርዓት እንደ የግለሰብ ነፃነት ወይም የፆታ ግንኙነት ምርጫ መታየቱ ሲሆን ሊሰመርበት የሚገባው ጉዳዩ በግለሰብ ላይ ብቻ ሳይቆም ቤተሰብን፣ ብዙሓን ሕዝቦችን፣ እንዲሁም አገርን የሚበክል ነገር መሆኑ ነው።
The liberal choice for sexual orientation does not stop on an individual. Homogeneous marriage distorts the basic fabric of the social network reflected in a natural family of parent-offspring relationship by obliterating this human relationship and throwing it into the abyss of mere sexualized instinct.

ባሁኑ ጊዜ በአንዳንድ መንግሥታት የተመሣሣይ ፆታ ጋብቻ መፈቀድ በጥንቃቄ ሊታይ የሚገባው ጉዳይ ነው። ሰዎች በዚያ ባሕርይ በመነደፋቸው ምክንያት ኅብረተሰቡ እየተጸየፋቸው ስላገለላቸው ራሳቸውንም እስከማጥፋት የደረሱ ስላሉ በአብዛኛው መንፈስ መድልዎ /discrimination/ ሳይፈጸምባቸው እንደሌሎች ዜጎች በሰላም የመኖር ነፃነት እንዲኖራቸው ተብሎ አገርን ከማስተዳደር አንፃር እየተወሰደ ያለ እርምጃ ነው አንጂ ትክክል ሆኖ አይደለም ። ለምሳሌ ሲጋራ አጫሾች ሰብአዊ መብት ተጠብቆላቸው በተከለለ ቦታ ማጨሳቸው ምርጫቸው ተቀባይነት አለው ማለት አይለም፤ ሲጋራንም የጤንነት ጠንቅ ከመሆን አያስቀረውም። ከሰብአዊነትና ደህንነት አንፃር የግለሰቦችን ነፃነት ለመጠበቅ የሚወሰደው ሕጋዊ አቋም ወይም አስተዳደራዊ እርምጃ የግለሰቦቹን ጥፋትና ስህተት ትክክለኛ አያደርገውም፣ መቻቻልን /tolerance/ እንጂ። በመንፈሳዊ መንገድም ብናየው እግዚአብሔር ሕግን የሰጠን በፈቃዳችን አንድንፈጽም ሲሆን ሕጉን ባለመከተል ኃጢአት ብንሠራ የምናጣውን ሁሉ ገልጾልናል (፩ኛ ጴጥሮስ ፪፡ ፲፮፣ ገላትያ ፭፡ ፩ የዮሐንስ ወንጌል ፰፡ ፴፩-፴፮)፤ ለመዳን ፈቃደኞች ካልሆንን እና የመዳኛውን ሕግ ትተን የመሞቻውን ነፃነት የምንመርጥ ከሆነ እንጎዳበታለን። ስለሆነም የእግዚአብሔርን ሕግ ከመከተል በስተቅር ሌላ የሚጠቅም አማራጭ እንደሌለ ማውቅ ብልህነት ነው።

የተፈጥሮ ቤተሰብና ሚናው፣
ሰው ሊወለድ የሚችለው ከተፈጥሮ እናትና አባት ብቻ ነው። ሆኖም በማደጎ እጅ ላይ የወደቀ ልጅ የማደጎ ወላጆቹ ምንም ያህል ደጋግ ቢሆኑ የማንነት ጥያቄ ማንሳቱ አይቀርም፤ ይህ ደግሞ የሥነልቡና ችግር ይኖረዋል። ወላጆቻቸው የሞቱባቸው ልጆች እንኳ ከማደጎ ወላጆች ጋር የሚኖራቸው ግንኙነት እስከሞት ድረስ ያደረሰ ቀውስ ማስከተሉ በየጊዜው በዜና ማሠራጫዎች ይሰማል። በአሜሪካን አገር ብቻ ከ፲፱፻፹፱ እስከ ፳፻፲፫ ዓም በማደጎ ከውጭ አገር ከመጡ ሕፃናት ውስጥ ፪፻፺፫ ሞትና ሌላ ከባድ ጉዳት እንደደረሰባቸው ኒጌል ባርበር የተባለ ሳይኮሎጅስት ካቀረበው ስታትስቲከስ ታውቋል።

የተመሣሣይ ፆታ ጋብቻ ብለው ግብረሰዶማውያን የሚጠሩት እውነተኛ ጋብቻ ሳይሆን ሕገወጥ እና በወሲብ ላይ ያተኮረ ግንኙነትና ዝሙት ነው። በአሁኑ ጊዜ ዓለምን እየበከለ ያለው የተመሣሣይ ፆታ ጋብቻ ዓላማው ፍትወተሥጋ (ወሲብ) ብቻ ሲሆን ብዙ ተባዙ ምድርንም ሙሉአት የሚለውን አምላካዊ ቃል የሚፃረር ስለሆነ ልጆች ከወላጆቻቸው ውጭ በእንጀራ እናት ወይም እንጀራ አባት ሥር ስለሚያድጉ የእናት-አባት የወንድም-እህት ወዘተ ቤተሰባዊ ፍቅርና ጣእም ከቶውንም ያጣሉ። ምክንያቱም ከተቃራኒ ፆታዎች (ባልና ሚስት) ውጭ የሚጋቡ ሰዎች ልጅ ለማግኘት በማደጎ ማምጣት አለበለዚያም አመንዝራ የመፈጸም ምርጫ ውስጥ ይገባሉ። እግዚአብሔር ለሰዎች የፈቀደውን የወላጅ-ተወላጅ የተፈጥሮ ሕግ ተከትሎ በቤተሰባዊ ግንኙነት ማኅበራዊ ኑሮ በመኖር ፋንታ እንደ እንሰሳ በዘፈቀደ የመገናኘትና አንደከብት የአባቱን ማንነት ጥያቄ ውስጥ የሚጥል ተወላጅን (offspring) ያስከትላል። በዚህ መልክ ልጆች የተባሉ ተወላጆች ሁሉ እውነተኛ አባትና እናት ሳይሆን በማደጎ ወላጆች ሥር ስለሚያድጉ ይህ የትውልድ ሐረግን ስለሚያጠፋ ሰዎችን በዝምድና ማየት ሳይሆን በአካል ብቻ የመቁጠር ዕድል ስለሚያስከትል ፍቅር፣ ኃላፊነት፣ ሞራል፣ የማንነት ጉዳይ…ወዘተ እየደበዘዙ ሰብአዊነት በእንሰሳዊ ባሕርይ ይዋጣል።

ቤተሰብ ከእግዚአብሔር የተሰጠን በረከትና ልጆች በማኅበራዊ ፍጡርነት ከእግዚአብሔር በተሰጣቸው ፀጋ ፍቅርን የሚያዩበት፣ የሚገልጹበት ትንሹ የኅብረተሰብ ሕዋስ ነው። “ዞሮ ዞሮ ከቤት ኖሮ ኖሮ ከመሬት…” እንደሚባለው ቤተሰብ ተወዳዳሪ በሌለው መስዋዕትነት የተፈጥሮ ፍቅር የሚተገበርበትና ልጅ በወላጁ፣ ወላጅ በልጁ..ወዘተ ፍጹም ተስፋ የሚጥልበትና የሚመካበት የአለኝታነት መገለጫ ነው፤ ቤተሰብ የሰዎች ሰብአዊ ክብርና የትውልድ ሐረግን ተከትሎ የሚመጣ ወግና የማንነት መግለጫ ነው፤ ቤተሰብ በተፈጥሮ የሚተማመኑበት የአንድነትና የባለቤትነት መገለጫ አካል ነው፤ ቤተሰብ የራሴ ከሚሉት አካል ጋር በእውነት ስለ እውነት ከምንም ጋር በማይተካከል ነፃነት የሚገናኙበት በእግዚአብሔር ፀጋ የተገኘ ሕዋስና ርህራሄን፣ ምህረትን፣ ይቅርታንና ልግሰናን የሚያገኙበት ትንሹ መንግሥት ነው፤ ቤተሰብ ተወዳዳሪ በሌለው ቅንነት ኃላፊነት የሚፈጸምበት የኅብረተሰብ አካል ነው። ቤተሰብ ይህን ሁሉ ማኅበራዊ እሴት ተሸክሞ የሚቆም የኅብረተሰብ ምሰሶ ነው። ነገር ግን ከላይ እንደተገለጸው የተመሣሣይ ፆታ ግንኙነት ሕገወጥ ከመሆኑም በላይ ቤተሰብን መሠረት ያሳጣዋል።

መልካም ባህላችንን ጠብቀን ለሌላው ዓለም ማስተማር፣
ምሰሶ ከተዛባ ቤት እንደሚናጋ ሁሉ ቤተሰብም ከእግዚአብሔር የተሰጡትን ማኅበራዊ እሴቶች መሠረት ካጣ ኅብረተሰብ ይናጋል፤ የሰው ልጅም መንፈሳዊ ኃይሉን ስለሚያጣና ለእንሰሳዊ /instinct/ ሥጋዊ ፍላጎት በመገዛት ሙሉ ሰብአዊነቱን ስለሚያጣ የራሱን ክብር ዝቅ ያደርጋል። በዚህ የተነሣ መንፈሳዊ ሙሉነት አይሰማውም። ሰብአዊ ክብሩን የማይጠብቅ ሰው ጥሩ ማኀበራዊ ባህል ሊኖረው አይችልም። ፍቅር፣ ኃላፊነት፣ ይሉኝታ፣ ሞራል በተሞላበት ማኅበራዊ ባህል ያልተገነባ ቤተሰብ ደግሞ ለቁሳቁስና ግብረሥጋ ግንኙነት የሚተባበር ልቅ የሰዎች ስብስብ ስለሚሆን ለማናቸውም ሕገወጥ ተግባሮች የተጋለጠ ነው፤ ምክንያቱም ሥጋዊ ፍላጎቱን ሊገዛ ካልቻለ እንኳንስ ለመንፈሳዊ ሕይወት ቀርቶ ሰው-ሠራሽ ለሆነውም የመንግሥት ሕግ መገዛት አይችልም። ስለዚህም ነው የአመንዝራ ትውልድ እየበዛ የአንድ ወላጅ ልጆች የሚበዙበትና ስብእናቸው ያልተሟላ ስለሚሆን ቁሳዊ ችግር እንኳ ሳያግጥማቸው ሰዎች በመንፈስ ጭንቀት ሐሳርና መቅስፍት የሚደርስባቸው።

ሰው ራሱን መግዛት አቅቶት በሥጋዊ ፍላጎቱ ከተሸነፈ ለእንስሳዊ ባህርይ ስለሚገዛ የራሱን ሰብአዊ ክብር ከማጣቱም በላይ የቤተሰቡን /ዘመዶቹን/ የተፈጥሮ ግንኙነት በጣጥሶ ህልውናቸውን ያጠፋል። ቤተሰብ ጠንካራ ማኅበራዊ መሠረት ከሌለው ደግሞ አንድነት የሌለው በደመነፍስ ፍላጎት የተሞላ የግለሰቦች ጥርቅም ስለሚሆን አጥንት እንደሌለው ሥጋ የመፈራረስ ዕድል ውስጥ ይወድቃል። የቤተሰብ መዳከም ደግሞ የኅብረተሰብን ድርና ማግ ይበጣጥሰዋል፤ ይህም መልካም ሰብእናን የሚያሳሳ ስለሚሆን የአገርን ማኅበራዊ እሴቶች በማጥፋት ዜጎችን ከኅብረተሰቡ ጋር ትሥሥር ሳይኖራቸው የግል ፍላጎታቸውንና ጥቅማቸውን ለማሟላት ብቻ የሚፈልጉ በዘፈቀደ ስሜት የሚመሩ የግለሰቦች ክምችት በማድረግ ሰብአዊነትን ስለሚያጠፋ ለመልካም አስተዳደር መጓደል ከፍተኛ አስተዋፅዖ ሊያደርግ ይችላል።
“እንሰሳ ሰው ሆነ ሰውም እንሰሳ ሆነ” እንደተባለው ከኅብረተሰባችን ውጭ ያሉትም ቢሆኑ በአርዓያሥላሴ የተፈጠሩ ስለሆኑ በዚህ መነሻውም ሆነ መድረሻው ወሲብ ብቻ በሆነ ባህርይ እየተለከፉ ከሄዱ ይህ ልምድ ለሥጋቸውም ሆነ ለነፍሳቸው የዘለቄታ ጥቅም ስለሌለውና በመጨረሻም ትውልዳቸውን ጭምር እያበላሸ ተጨማሪ ማህበረሰቦችንም ሊበክል ስለሚችል ከዚህ ልምድ እግዚአብሔር እንዲያወጣቸው ልንፀልይላቸው ይገባል። ሆኖም በእነዚህ ርካሽ በሆኑና በእንሰሳዊ ደመ-ነፍስ (instinct) ባህርይ በተበረዙ ልማዶች የራሳችንን መልካም ባህል ማዳከም የለብንም፤ የአገራችንን የጋብቻ ሥርዓት በአጠቃላይም በመልካም ባህላችን ውስጥ ያሉ ማኅበራዊ እሴቶቻችንን እያዳበርን ልንጠብቃቸው እና ሌሎችን ኅብረተሰቦች ልናስተምራቸው ይገባናል እንጂ።
ይህ ክስተት ወደ ባህላችን ዘልቆ ስላልገባ አሳሳቢ የማይመስላቸው የዋህ ወገኖች አሉ። ይኽም ራሷን አሸዋ ውስጥ ደብቃ የሚሆነውን ሁሉ አላይም ብላ የቀረውን አካሏን ለአደጋ እንደተወችው እንሰሳ እንደመሆን ነው። ሆኖም ዛሬ ዓለም እየተቀራረበች ባለችበት ዘመን በተለይ ወጣቱን ትውልድ በቅድሚያ በማስተማር በአገሩ ባህል ሙሉ እምነት አድሮበት ከዚህ መጥፎ ባህል ራሱን እንዲጠብቅ በወቅቱ ማስገንዘብ ይመረጣል።

አዲስ ፕሬዚደንት በአዲስ ዓመት –በተክሉ አባተ

$
0
0

ይድረስ ለአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ፡

unknown_personጤና ይስጥልን አቶ አንዳርጋቸው እንደምን አሉ ፤ በኢሳት መስኮት እንዳየሁዎ ጤናዎ በመልካም ሁኔታ ላይ ይገኛል ብየ እገምታለሁ ። እንደባህላችን ከብቶቹስ እንዴት ናቸው እንዳልልዎ ኤርትራ ከብት ለማርባት እንዳልሄዱ አውቃለሁና ምንም እንዲሉኝ አልጠብቅም ። ልጆቹስ እንዳልል መንታዎቹ ልጆችዎ በ single  mother ለንደን በእንክብካቤ እያደጉ መሆኑን ስለሰማሁ በጥያቄ አላስቸግርዎትም ። ትግሉ ብል ይሻላል እንዴት ነው እየሰመረ ነው ? በረሃውን እየለመዱት ነው ? በቃ የግንቦት ሰባት ህዝባዊ ህይል በየጦር ሜዳው ወያኔን እያርበደበደው ነው አይደል ? እንግዲህ አራት አመት ሞላዎ እኮ ! ዘመኑ እንዴት ይሮጣል ጃል ።  ቀጣዩን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ፣ የአንድነት ለዴሞክራሲ እና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ሊቀ መንበር አንዱአለም አራጌ የአመቱ ሰው ተብሎ በመሰየሙ የተሰማቸውን ደስታ ገለጹ

$
0
0

ትርጉም  በግርማ ሞገስ

 

ዶር ነጋሶ ጊዳዳ፣ የአንድነት ለዴሞክራሲ እና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ሊቀ መንበር አንዱአለም አራጌ የአመቱ ሰው ተብሎ በመሰየሙ የተሰማቸው ደስታ ለመግለጽ በእንግሊዘኛ የፃፉት መልዕክት በጥያቂያቸው መሰረት ከሞላ ጎደል እንደሚከተለው ቀርቧል።

 

ቅዳሜ መስከረም 4 ቀን 2006 ዓ.ም. 
Saturday, September 14, 2013

 

አንዱአለም አራጌና ቤተሰቦቹ

አንዱአለም አራጌና ቤተሰቦቹ

“ዘሐበሻን እና ሌሎች ሚዲያዎችን የመድረስ አቅም ያላቸው እህቶቻችን እና ወንድሞቻችን አንዷለም አራጌን የአመቱ ሰው አድርገው መምረጣቸውን መስማቴ ታላቅ ደስታ ሰጥቶኛል። አንዷለም ለህዝቡ እና ለአገሩ ብዙ ያበረከተ እና የተጠየቀውን መስዋዕት ሁሉ ካለ ምንም ስስት የከፈለ እና በመክፈል ላይ የሚገኝ ድንቅ ግለሰብ በመሆኑ ለአንዷለም ይኽን እውቅና በመለገሳችሁ ላመሰግናችሁ እወዳለሁ።

እንደ ኢትዮጵያ አቆጣጠር በ1998 ዓ.ም. ከእስር ቤት ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ በተለይ ደግሞ መድረክን ወደ ህብረት ከፍ ለማድረግ የፖለቲካ ፕሮግራም እና መተዳደሪያ ደንብ አብረን መቅረጽ ከጀመርንበት ጊዜ ጀምሮ አንዷለምን አውቀዋለሁ። ብዙ ፍሪያማ አሳቦችን ለግሷል። መድረክ ወደ ግንባር ደረጃ እንዲደርስ ለማድረግም ካለምንም መታከት ሰርቷል። አንዷለም አንድነት ፓርቲን ወክሎ በመድረክ ስራ አስኪያጅ ኮሚቴ ወስጥ በነበረበት ጊዜ ለመድረክ ፕሮጀክት መሳካት ብዙ ከጣሩት የአንድነት ሰዎች ውስጥ አንዱ ነበር። ለወቅቱ የመድረክ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ አክብሮት ነበረው። እጅግ ቀና የሆነ የስራ ግንኙነት ነበራቸው። ያኔ እንደማውቀው እና ዛሬም እንደሚመስለኝ አንዷለም መድረክን በሚመለከት ከአንድነት ከሚሰሙ አሉታዊ ድምጾች ጋር አይስማማም። ቀደም ሲልም በዚህ ጉዳይ ላይ ጽኑ ክርክሮች አድርጓል።

 

አንዷለም ከመኢአድ እና ያኔ ከአንድነት ተነጥለው ከሄዱት ወገኖች (ዛሬ ሰማያዊ ፓርቲ) ጋር ውህደት እንዲደረግ ይፈልግ ነበር። በዚህ አቅጣጫ አንዷለም የአንድነት ፓርቲን ስራ አስኪያጅ ኮሚቴ አግባብቶ ወይዘሮ ላቀች ደገፉ እና አቶ ተመስጌን ዘውዴ ያሉበትን የድርድር ኮሚቴ ፓርቲው እንዲመሰርት አድርጎ ነበር። ሁለተኛ እስር እስከተበየነበት ጊዜ ድረስ ለዚህ ጉዳይ መሳካት በመስራት ላይ ነበር አንዷለም።

 

አንዷለም ቁርጠኛ የሰላማዊ ትግል ተዋጊ ነበር። የማህተማ ጋንዲ እና የማርቲን ሉተር ተከታይ። የፖለቲካ እንቅስቃሴዎቹ የሚመሩት በእነዚህ ሁለተ ሰዎች ትምህርቶች ነበር። አንዷለምን ሽብርተኛ ነው ወይንም ከሽብርተኞች ጋር ግንኙነት ነበረው ብለው የሚያስቡ ሰዎች ካሉ አዕምሮዋቸውን የሳቱ እና እራሳቸው ሽብርተኞች ናቸው።

 

አንዷለም የአንድነት ጸሐፊ እና የአንድነት ህዝብ ግንኙነት ኮሚቴ ሊቀመንበር በነበረበት ጊዜ ለድርጅቱ ስኬት ለሊት እና ቀን ሰርቷል።

ባለቤቱን እና ሁለት ልጆቹን ይወድ ነበር። ቀኑን እና ምሽቱን ለአንድነት ሲሰራ ውሎ ምሽት ላይ ወደ ቤተሰቡ ነበር የሚሄደው። ወደ መዝናኛ ቦታዎች ከመሄድ ፈንታ።

 

ዶር ነጋሶ ጊዳዳ፣ የአንድነት ለዴሞክራሲ እና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ሊቀ መንበር

ዶር ነጋሶ ጊዳዳ፣ የአንድነት ለዴሞክራሲ እና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ሊቀ መንበር

የግል ህይወቱን በሚመለከት፣ አንዷለም የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርቶችን በንጹሕ ልቦና የሚከተል መንፈሳዊ ሰው ነው። አንዷለም “ ግራ ፊትህን በጥፊ ለመታህ ሰው ቀኝ ፊትህን ስጠው። ሌሎች በአንተ ላይ እንዲፈጽሙብህ ያማትፈልገውን አንተም በሌሎች ላይ አትፈጽም።” የሚሉት የእየሱስ ክርስቶስ ትምህርቶች ተከታይ ሰው ነው። ሰው አስቀይሞ ወይንም ተሳድቦ አያውቅም። ሲሰደብም መልሶ አይሳደብም። አይበቀለም አንዷለም። ምክርን እና ማጽናናትን ለሚሹ ሁሉ አንዷለም ጊዜ ነበረው።

 

አንዷለም አዕምሮ-ክፍት እና ግልጽ ሰው ነው። የማዳመጥ ልዩ ችሎታ አለው።

 

አንዷለምን “የአመቱ ሰው” ብላችሁ መምረጣችሁ ትክክለኛ ውሳኔ ነው። ይገባዋል። ለሁላችሁም ምስጋናዬ ይድረሳችሁ።

 

ዶር ነጋሶ ጊዳዳ፣

 

የአንድነት ሊቀመንበር”

 

 

 

የፖለቲካ ኃይል ምንጮች ክፍል አንድ/2፡ የዝንጀሮዎቹ ጌታ ሞተ –ለምን እና እንዴት? ከግርማ ሞገስ

$
0
0

ግርማ ሞገስ (girmamoges1@gmail.com)
ሰኞ መስከረም 6 ቀን 2006 ዓ.ም. (September 16, 2013)

Girma Moges

አቶ ግርማ ሞገስ

የዝንጀሮዎቹ ጌታ አጭር ታሪክ የተወሰደው ቻይናዊው ሊዩ ጂ/ Liu-Ji (1311-1375) ከጻፈው የሞራል ማስተማሪያ መጽሐፍ ነው። ይኽ አጭር ታሪክ የአምባገነን ገዢዎች የፖለቲካ ኃይል ከየት እንደሚፈስላቸው (ምንጩ ምን እንደሆነ) እና እንዴት ምንጩን በመቆጣጠር የአምባገነኖችን አቅም መቆጣጠር አልፎም ምንጩን በማድረቅ አምባገነኖችን ማስራብ እንደሚቻል በምሳሌ አድርጎ ግልጽ ያደርጋል። ሰለዚኽ የሰላማዊ ትግል ተመራማሪው እና ዘመናዊ የፖለቲካ ሳይንስ ጠበብቱ ሲድኒ ታይ (Sidney Tai) ከቻይንኛ ወደ እንግሊዘኛ ቋንቋ ተረጎመው። የእንግሊዘኛ ትርጉሙን “በማጭበርበር መግዛት” (“Rule by Tricks”) የሚል ርዕስ ሰጠው እና ሰላማዊ ቅጣቶች (Nonviolent Sanctions) በሚል ርዕስ የአልበርት አነስታይን ሰላማዊ ትግል ምርምር ተቋም በሚያትማት ጋዜጣ ላይ አሳተመው ሲድኒ ታይ (Sidney Tai)። የዝንጀሮዎቹ ቅጣት ሰላማዊ ቅጣት እንደነበር እና የዝንጀሮዎቹ ጌታ ቅጣት ግን የኃይል ቅጣት (Violent Sanction) እንደነበር ወደፊት ከቦታው ስንደርስ እናስተውላለን። በቅርብ ደግሞ ጂን ሻርፕ (Gene Sharp) የተባለው ሌላው የዘመናችን የሰላማዊ ትግል ተመራማሪ እና በካምብሪጅ ዩንቨርስቲ መምህር ይኽን አጭር ታሪክ ከአምባገነን ወደ ዲሞክራሲ በሚለው መጽሐፉ ገጽ 17-18 ላይ ሰላማዊ ትብብር የመንፈግ ትግል (Nonviolent Non-cooperation Struggle) የሚለውን የሰላማዊ ትግል ጽንሰ አሳብ ለማብራራት ተጠቅሞበታል። የዚህ ጽሑፍ ግብ በዚህ አጭር ታሪክ አንባቢዎች እየተዝናኑ እንዲመራመሩ ማድረግ ነው። ይኽ ምርምር በቅርብ ለንባብ ለማቀርበው ጽሑፍ መሰረት ይጥላል የሚል እምነት አለኝ።   ቀጣዩን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ  

 

የምስራች ለኢህአዴግ የምጡቅ ጭንቅላት ባለቤትነት ምልክቶች በአንድ ካድሬ ተገኘ

$
0
0

ከዳዊት ሰለሞን (ጋዜጠኛ)

ኢህአዴግ መለስን በተፈጥሮ ሞት እንደተነጠቀ የድርጅቱ አመራሮች የሙሉ ጊዜ አገልግሎቱን ለለቅሶው ባበረከተው ቴሌቪዥን በመቅረብ ሟቹ መለስ የምጡቅ ጭንቅላት ባለቤት እንደነበሩ ይናገሩ ነበር፡፡የኢህአዴግን አቅጣጫ የሚቀይሱ፣የትግራይን ስትራቴጂክ እቅድ የሚነድፉ፣የድርጅቱን የንድፈ ሃሳብ መጽሄት በዋና አዘጋጅነት የሚያገለግሉ፣የአገሪቱን የጦር ሃይል በ1997 ጠቅልለው ወደ ራሳቸው ዕዝ ያስገቡ፣ዶክተሩን፣መምህሩን፣ተማሪውን፣አርቲስቱን፣ወጣቱን፣በንግራቸው የሚያማልሉ፣የአፍሪካ አዲስ ተስፋ ተሰኝተው በእነ ቶኒ ብሌር የተመረጡ፣የአገር ውስጡን ተቃዋሚ ጣት እቆርጣለሁ በማለት የሚያስፈራሩ፣እነዚህና ሌሎች ስንክሳሮች ተመዝዘው መለስ‹‹የምጡቅ ጭንቅላት ባለቤት ናቸው ››ተባሉ፡፡ከመለስ በኋላ ይህን ጭንቅላት ስለ ማግኘቱ የተነገረለት ወይም አለኝ ያለ እስከ ዛሬ ማለዳ አላጋጠመኝም ነበር፡፡
በመለስ እግር የገቡት አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ የመለስ ጫማ እንዳልበቃቸው በመታመኑ በክላስተሮች የተከፋፈሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሮች ተመደቡላቸው ወይም ተመደቡባቸው፡፡(ሂደቱን አንዳንዶች በጠቅላይ ሚኒስትሮች ብዛት አገራችን እመርታ አስመዘገበች በማለት መቀለዳቸውን አስታውሳለሁ)ነገር ግን ለእኔ ሹመቱ የእመርታ ጉዳይ ሳይሆን ያን ምጡቅ ጭንቅላት በአንድ ሰው መተካት አለመቻሉን ኢህአዴግ ማመኗን የሚያሳብቅ ነው፡፡

(የፎቶ ምንጭ አዲስ ፎርቹን ጋዜጣ)

(የፎቶ ምንጭ አዲስ ፎርቹን ጋዜጣ)


ኢህአዴግ አንዱን መለስ በብዙ ለመተካት እየወሰደ ከሚገኘው እርምጃ በተቃርኖ ዳንኤል ብርሃነ የሚባል ግለሰብ የምጡቅ ጭንቅላት ባለቤት ነኝ››በማለት ራሱን አስተዋውቋል፡፡ይህ ምጡቅ ጭንቅላት በመፈለግ ከመለስ ሞት በኋላ በቀን ብርሃን ባትሪ እያበራ ሲፈልግ ለከረመው ኢህአዴግ ትልቅ የምስራች ነው፡፡
ወዳጄ እርስዎ ‹‹ምጡቅ ጭንቅላት››የሚል ቃል ሲያደምጡ ወደ አይነ ህሊናዎ የሚመጡት እነ አልበርት አነስታይን፣ሊዮ ቶሎስቶይ፣አጼ ምኒልክ፣ማዘር ቴሬዛ፣ኔልሰን ማንዴላና ሌሎች ይሆናሉ ፡፡በኢህአዴግ ማውጫ የምጡቅ ጭንቅላት ባለቤትነት ሁሉን በጠላትነት አይን ማየት፣ዘረኝነት፣ፍረጃ፣አማራጭ የሚባል ሃሳብ ጠረጴዛው ላይ እንዳይቀርብ የተለየ ሃሳብ አመንጪን መምታት ነው፡፡በዚህ ረገድ የፌስ ቡኩ ዳንኤል ብርሃነ ‹‹የምጡቅ ጭንቅላት ባለቤት ስለ መሆኑ መከራከር ጉንጭን ማልፋት ነው፡፡የህግ ባለ ሞያና የምጡቅ ጭንቅላት ባለቤት ነኝ የሚለን ግለሰቡ በቅርቡ ፖስት ያደረጋቸውን ወይም አስተያየት የሰጠባቸውን አንዳንድ ጹሁፎች በመመልከት ምጡቅ ጭንቅላት እኛ በምናውቀውና እነርሱ በሚሉት መካከል የሰማይና የምድር ያህል ልዮነት እንዳለው እንገነዘባለን፡፡
Wossi Zebdewos:- ”There was a defection news/ Rumor at the first place??”

Daniel Berhane:- ”Yes, there is such a news from the enemies of Tigrai.”
ዘብዴዎስ የተሰኙ የፌስ ቡክ ተጠቃሚ ለዳንኤል እነ አርከበን በተመለከተ የኩብለላ የጭምጭምታ ዜና ከመነሻው ስለ መኖሩ ይጠይቁታል፡፡ዳኒ በመልሱ ‹‹አዎን ከትግራይ ጠላቶች እንዲህ አይነት ወሬ ነበር››ብሎ ቁጭ፡፡በቃ በእርሱ ምጡቅ ጭንቅላት ውስጥ እነ አርከበ ኮበለሉ ማለት የትግራይ ጠላት መሆን ነው፡፡ የባለስልጣኑን ኩብለላ ከትግራይ ጠላትነት ጋር ሊያቆራኝ የሚችል የዳንኤል ምጡቅ ጭንቅላት ካልሆነ በቀር እንዲህ አይነት ጭንቅላት ማግኘት ያስቸግራል፡፡እንቀጥል
Daniel Berhane:- #Ethiopia: History repeats itself. Now Arena-Tigray is the enemy with-in.
አረና በቀድሞ የህወሃት ከፍተኛ አመራሮች የተመሰረተ ፓርቲ ነው፡፡ዳንኤል ይህንን ፓርቲ እንዴት እንደሚመለከተው ሲጠቅስ በውስጥ ያለ ጠላት ብሎታል፡፡በቃ ለዚህ ምጡቅ ጭንቅላት ህወሃትን መቃወም ጠላትነት ነው፡፡አረና በትግራይ ምድር ሆኖ ህወሃትን መቃወሙን ደግሞ በውስጥ ያለ ጠላት በማለት እንዲፈርጅ አድርጎታል፡፡ምን ይደረግ የምጡቅ ጭንቅላት ባለቤት ነዋ፡፡አሁንም ከዳንኤል ይቅርታ ከምጡቅ ጭንቅላት ጋር ነን፡፡
Daniel Berhane:- በትግራዮች እና በኢሕአዴግ አባላት ላይ ማህበራዊ መገለልን ያወጃቹሁ ሰዎች(ጨዋው የኢትዮጲያ ሕዝብ አሳፈራችሁ እንጂ)፣ በተግባርም የትግራዮች ቤት ሲቃጠል እና ‹‹የሚቃጠል›› ተብሎ ሲፃፍበት ግድ ያልሰጣችሁ ሰዎች፣ የበድሩ አደምን ዘረኛ መፈክር ከማውገዝ ይልቅ የቃላት ጨዋታ የመረጣችሁ ሰዎች፣ በእናንተ አመራርና ቅስቀሳ ስለተደበደቡና ስለተገደሉ ትግራዮች ከመቆጨት ይልቅ መከራከር የመረጣችሁ ሰዎች፣ እንኳን በፈቃዳችሁ መራብ ቀርቶ ምግብ አጥታችሁ ብትራቡ ግድ የሚሰጠው የሚኖር ይመስላችላኋል
ደረጄ ሀብተወልድ የጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙን የርሃብ አድማ በማስመልከት የዳንኤል ወንድሞች የሰጡት ምላሽ አበሳጭቶት እነርሱ እኮ ለቅንጅት አመራሮች የርሃብ አድማ የሰጡት መልስ ተመሳሳይ ነበር እናም ርዕዮት የርሃብ አድማ በመጀመሯ ያዝናሉ ብለን መጠበቅ አይገባም፡፡ይላል ዳኒ ለደረጀ መልስ በመጻፍ‹‹እንኳን በፈቃዳችሁ መራብ ቀርቶ ምግብ አጥታችሁ ብትራቡ ግድ የሚሰጠው የሚኖር ይመስላችላኋል››ምጡቅነቱን አሳየን፡፡አዎን በዳንኤል ዙሪያ ግድ የሚለው ላይኖር ይችላል፡፡እናንተ ግድ እንዲላችሁ ነፍስ መበላለጥ አለበት፡፡ደግሞስ ይህን ዘረኛ ከፋፋይ የፖለቲካ እሳት እንዲዛመት ያደረጋችሁት እናንተው መሆናችሁን መዘንጋት አይኖርብህም፡፡በጣም ግራ ያጋባኝ ነገር ድሬዳዋ ያደገ ሰው በድሬ የተማረ ከየት ነው ይህንን ዘረኛ አመለካከት የያዘው?
Daniel Berhane:- It is boring to see such a long collection of stupid comments. If you don’t like the info, go hang yourselves.
ዳንኤል ለለጠፈው ጽሁፍ በዛ ያሉ ሰዎች ተቃራኒ አስተያየት መሰንዘር በመጀመራቸው ባለ ምጡቅ ጭንቅላቱ ‹‹እኔ የሰጠሁት መረጃ ያልተመቸው ራሱን ማጥፋት ይችላል ብሎ አረፈው፡፡ጠላትነት፣ራስን ማጥፋት፣ማንም ስለ እናንተ ግድ የለውም፣የትግራይ ጠላቶች ››የሚሉ ቃላትን በዳኒ እያንዳንዱ ጽሁፍ ውስጥ ተሰግስገው ያገኛሉ፡፡እነዚህን ቃላትም መለስ በህይወት ዘመናቸው የተካኑባቸው እንደነበሩ ካስታወሱ ቃላቶቹ ምጡቅ በመሆን የሚገኙ ወይም የምጡቅነት መለኪያ መሆናቸውን ይረዳሉ፡፡

Daniel Berhane:- ርዐዮት ሐኪም ተከለከለች በለኝ – ምንም ማድረግ ባልችል አብሬ እታመማለሁ፡፡
ፍቅረኛዋን በዚህ ቅዳሜና/እሁድ ሳታገኝ ቀረች በለች አዝናለሁ፡፡
ሌላው የሚዲያ ሰርከስ አይመለከተኝም፡፡
ወዳጄ ስላቁን ተመልከቱ፡፡የርእዮትን የርሃብ አድማ ፍቅረኛዋን ከማግኘት ጋር በማቆራኘት እቃቃ ሊያደርገው ይሞክራል፡፡አስረኛዋ በማንም የመጎብኘት ፍቅረኛዋን ጨምሮ መብት አላት፣ህክምና ማግኘትም የታሳሪ መብት ነው፡፡ወደ ጡት ካንሰርነት ሊያደግ የሚችል እጢ እንዳለባት የተነገራት ሴት የህመሙን እድገት ለመቀነስ የተመረጠ ምግብ መብላት፣ጭንቀት ከሚፈጥር ሁኔታ መራቅ ይገባታል፡፡የጀመረችው የርሃብ አድማ ደግሞ በተቃራኒው ለህመሙ መፋጠን የራሱን አስተዋእጾ ያበረክታል፡፡ምጡቅ ሆይ ሰብዓዊነት ግድ ሊለን አይገባም ይሉን ይሆን?አብረው የሚታመሙ ከሆነ ምነው አብረዋት ባይራቡ የመራቧን መንስኤ ባያወላግዱት?ረስቼው ምጡቅነት ለካ ለሰብዓዊነት ቦታ የለውም፡፡


ቀነኒሳ በቀለ ሞ ፋራህን በግማሽ ማራቶን ቀጣው፤ መሠረት እና ጥሩነሽ 2ኛና 3ኛ ወጡ

$
0
0

kenenisa 1(ዘ-ሐበሻ) ዛሬ በሰሜን እንግሊዝ ታላቁ የግማሽ ማራቶን ሩጫ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የተሳካ ውጤት አስመዘገቡ። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ለኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ራስ ምታት ሆኖ የነበረውና በ5 ሺህ እና በ10 ሺህ ሜትር የወርቅ ሜዳሊያዎችን ሲጠቀልል የነበረው እንግሊዛዊው አትሌት ሞ ፋራህ ዛሬ በሃገሩ ላይ በቀነኒሳ በቀለ ተቀጥቷል።

ቀነኒሳ በቀለ በዛሬው ውድድር ሞ ፋራህን ያሸነፈው ውድድሩን በአንድ ሰዓት ከ08 ደቂቃ በማጠናቀቅ ሲሆን ትውልደ ሶማሊያዊ እንግሊዛዊው ሞ ፋራህ በአንድ ሰዓት ከ09 ደቂቃ ሁለተኛ በመውጣት ውድድሩን ሲያጠናቅቅቅ አትሌት ኃይሌ ገብረ ሥላሴ ደግሞ ሶስተኛ በመሆን ውድድሩን አጠናቋል፡፡ እንደ ስፖርት ተንታኞች ከሆነ ኃይሌ ለቀነኒሳ ማሸነፍ ትልቁን ሚና ተጫውቷል። የቀነኒሳ ማሸነፍም ኢትዮጵያ ወደፊት በማራቶን ተተኪ አትሌቶችን እያገኘች መሆኑን የሚያሳይ መሆኑን አስተያየት ሰጪዎች ይናገራሉ።

በተመሳሳይ ዛሬ መስከረም 5 /2005 (ሴፕቴምበር 15 ቀን 2013) ዓ/ም የተካሄደው የሰሜን እንግሊዝ ታላቁ ግማሽ ማራቶን ሩጫ መሠረት ደፋርና ጥሩነሽ ዲባባ ሁለተኛና ሶስተኛ በመውጣት አሸንፈዋል። በዚህ የሴቶች ግማሽ ማራቶን ውድድር ኬንያዊቷ አትሌት ጀፕቶ አንደኛ ስትወጣ አትሌቷ ጅፕቶ ከአስር ዓመት በፊት በፓዉላ ራድክሊፍ የተያዘ የ1፡05፡40 ሰዓት የቦታው ሪከርድ ለመስበር 9 ሰከንድ ብቻ እንደቀራት ከሥፍራው የተገኘው መረጃ ያመለክታል። የዚህ ውድድር ያለፈው ዓመት አሸናፊ ኢትዮጵያዊቷ ጥሩነሽ ዲባባ ነበረች። በ5 ሺህ እና በ10 ሺ ሜትር በድል ያስጨፈሩን መሰረት እና ጥሩነሽ በዚህ የግማሽ ማራቶን ያገኙት ውጤት የሚያኮራ ነው።

እንኳን ደስ ያለን!!

ቀነኒሳ በቀለ ያሸነፈበት ቪድዮ – Video

ኃይሌ ሩትስ በሚኒያፖሊስ ቀለበት አሠረ

$
0
0

hailie roots

(ዘ-ሐበሻ) በሬጌ የሙዚቃ ስልት የሚታወቀው ድምጻዊ ኃይሌ ሩትስ በሚኒሶታ ትናንት ሴፕቴምበር 15 ቀን 2013 ዓ.ም ቀለበት አሰረ። ድምፃዊ ኃይለሚካኤል ጌትነት (ኃይሌ ሩትስ) ቀለበት ያሠረው ነዋሪነቷ ሚኒሶታ ውስጥ ከሆነችው ከወይዘሪት ነዋል ስምዖን ጋር መሆኑን ጨምሮ የደረሰን መረጃ ያመለከታል።
በዳውንታውን ሚኒያፖሊስ በተለምዶ “SEVEN Steakhouse” እየተባለ በሚጠራው ቦታ ቀለበቱን ያሠረው ድምፃዊ ሃይሌ ሩትስ ሠርጉን ኢትዮጵያ እንደሚያደርግ ይጠበቃል።

በዚህ የሠርግ ሥነ- ሥርዓት ላይ የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች ለመገኘት ሄደው የነበረ ቢሆንም ከበሩ ጀምሮ ፎቶ ግራፍ ማንሳት ክልክል ነው የሚሉ ፖስተሮች በመለጠፋቸው አንዳችም ፎቶ ግራፍ ለማንሳስት አልቻልንም። በተጨማሪም በቀለበቱ ላይ የታደሙት ወገኖችም በስልካቸው ጭምር ፎቶ ግራፍ ማንሳት እንዳልቻሉም ለማወቅ ተችሏል። “ቺጌ” በሚል አልበሙ ታዋቂነትን ያተረፈው ኃይሌ ሩትስ በአንድ ወቅት በዘ-ሐበሻ ላይ በታተመው ቃለ ምልልሱ ላይ “እኔ ብዙ ግርግር አልፈልግም፤ ብዙ መታየትም አልወድም” ሲል መናገሩን ያስታወሱት ወገኖች ምናልባትም የቀለበቱ ፎቶ ግራፍ እንዳይነሳ የከለከለው በሚዲያዎች በኩል ስሙ እንዳይነሳ ይሆናል የሚሉ አስተየት ይሰጣሉ።

ሃይሌ ሩትስ በዘ-ሐበሻ ላይ በታተመው ቃለ ምልልሱ ላይ፡ “ጥያቄ፡- የቤተሰቦችህ ሁኔታ ምን ይመስላል? የት ተወለድክ? የት አደግክ? የት ተማርክ? ከቤተሰብ ያንተን ፈለግ የተከተለ አለ?” የሚል ጥያቄ ቀርቦለት “ዘጠኝ ወንድማማቾች ነን፡፡ ሁለት እህቶች አሉኝ፡፡ ከመጨረሻ ሁለተኛ ልጅ ነኝ፡፡ እናቴ በህይወት የለችም፡፡ አባቴ አለ፡፡ አባታችን ነው ያሳደገን፡፡ ያደግሁት እንግሊዝ ኤምባሲ አካባቢ ነው፡፡ አንደኛ ደረጃን ስላሴ ካቴድራል፤ ሁለተኛ ደረጃን ደግሞ ዳግማዊ ምኒልክ ነው የተማርኩት፡፡ ከዚያ በኋላ ትምህርት አልሆነኝም (ሳቅ)፡፡ እግርኳስ ተጨዋች ነበርኩ፤ እግርኳስ በጣም ነበር የምጫወተው፤ ከዚያ እርሱን ተውኩና ወደ ሙዚቃው ገባሁ፡፡
ሙዚቀኛ በዘሬም የለም፤ እኔ ብቻ ነኝ በድፍረት የወጣሁት፡፡ ለዚያ ነው በወቅቱ ሙዚቃ ስጀምር ተቸግሬ የነበረው፡፡ መግባባት አልነበረም፤ ቤተሰብ የሚፈልገው የሃይማኖት እና ሌላ ሌላውን ሙያ ስለነበር ይህን አይደግፉትም ነበር፡፡ እና በወቅቱ ችግር ነበር፡፡” ሲል መመለሱ ይታወሳል።

ከዚህ ቀደም በዘ-ሐበሻ ድረ ገጽ ላይ የታተመውን ቃለ ምልልስ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

በአዲስ አበባ ግብረሰዶም በአስደንጋጭ ፍጥነት እየተስፋፋ ነው!

$
0
0

መታሰቢያ ካሣዬ

*ግብረሰዶማዊያን በኢትዮጵያ ውስጥ “ሬንቦ” የተባለ ማህበር አቋቁመዋል
*በግብረሰዶማውያን ዙርያ የተካሄዱ ጥናቶች አዳዲስ መረጃዎችን ይፋ አድርገዋል 
*ከ14 ዓመት በታች የሆኑ ህፃናትና የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች የጥቃት ሰለባ ሆነዋል 
*ኢትዮጵያውያን ከተመሳሳይ ፆታ ጋር ወሲብ ሲፈፅሙ የሚያሳዩ ፊልሞች ለገበያ ቀርበዋል

ca338e3c9262ffb7fda1ab099ab32cf1_M ከወራት በፊት እዚህ አዲስ አበባ ከተማችን ውስጥ የተፈፀመ ታሪክ ነው፡፡ ድርጊቱ የተፈፀመው በአንድ ስመ-ጥር የወንዶች ልብስ መሸጫ ቡቲክ ውስጥ ነው፡፡ ወጣቱ በቡቲኩ ውስጥ ተቀጥሮ መስራት ከጀመረ ቆየት ብሏል፡፡ በአለባበሱ ሽቅርቅርና ዘመናዊ ነው፡፡ ወደ ቡቲኩ የሚመጡትን ደንበኞች በፈገግታና በትህትና እየተቀበለ ያስተናግዳል፡፡ ደንበኞች የፈለጉትን ልብስ አስወርደው ለመለካት ወደ መልበሻ ክፍል ሲገቡ በዓይኑ ይከተላቸዋል፡፡ በገቡበት የመልበሻ ክፍል መጋረጃ ላይ አይኖቹን ተክሎ ለደቂቃዎች እንደሚቆይ የቡቲኩ ባለቤት ብዙ ጊዜ ታዝቦታል፡፡ ሆኖም ደንበኞቹ አዲሱን ልብስ ለብሰው ሲወጡ ለማየት ከመጓጓት የተነሳ እየመሰለው በዝምታ ያልፈዋል፡፡ “ለምን እንዲህ ታያለህ?” ብሎ ጠይቆት አያውቅም፡፡

አብዛኛዎቹ የቡቲኩ ደንበኞች ወንዶች ናቸው፡፡ እጅግ ጥቂት ሴቶች፤ ለፍቅረኞቻቸው፣ ለባሎቻቸውና ለወንድሞቻቸው ልብስ ለመግዛት አሊያም ለማጋዛት ካልመጡ በቀር የሴት ዘር ወደ ስፍራው ዝር አይልም፡፡
የቡቲኩ ባለቤት አብዛኛውን ጊዜ ከቡቲኩ አይጠፋም፡፡ አልፎ አልፎ ከውጪ የመጡ ዕቃዎችን ለመረከብ፣ ክፍያ ለመፈፀምና መሰል ለሆኑ ጉዳዮች ወጣ ማለቱ ግን አይቀርም፡፡ የቡቲኩ ባለቤት ከወራት በፊት ተመሳሳይ ጉዳይ ገጥሞት ነው ቡቲኩን ለሰራተኛው ትቶለት የሄደው፡፡ ባለቤቱ ከሄደ በኋላ ዕድሜው በሃያዎቹ መጀመሪያ ላይ የሚገመት አንድ ወጣት ልብስ ለመግዛት ወደ ቡቲኩ ገባ፡፡ የቡቲኩ ሰራተኛ አይኑን ወጣቱ ላይ ተከለ፡፡ ወጣቱ ረዘም፣ ቀጠን ያለና ያለ ዕድሜው የተንቀዋለለ አይነት ነው፡፡ የሚፈልገውን ጅንስ መረጠና ወደ መለኪያ ክፍሉ ገባ፡፡ የቡቲኩ ሰራተኛ ጊዜ አላጠፋም፡፡ የቡቲኩን በር ከውስጥ ቆልፎ ወደ መለኪያው ስፍራ ሄደና መጋረጃውን ገለጠው፡፡ ወጣቱ ከለበሰው የውስጥ ሱሪ በስተቀር ከወገቡ በታች እርቃኑን ነበር፡፡ ሊለካው በያዘው ጅንስ ሱሪ አፉን አፈነው፡፡ ያላሰበው ነገር የገጠመው ወጣት፤ ለመጮህ፣ ለመታገልም ሆነ ለማምለጥና ለመከላከል አቅም አልነበረውም፡፡ እንደ ብረት ጠንክሮ ከያዘው እጅ ለማምለጥ በሞት ሽረት ትግል ቢፍጨረጨርም አልሆነለትም፡፡ እዛው የልብስ መለኪያ ክፍል ውስጥ አስገድዶ ደፈረው፡፡
የቡቲኩ ባለቤት ከጉዳዩ ተመልሶ ሱቁ ሲደርስ ቡቲኩ ያለወትሮው ተዘግቷል፡፡ ሁኔታው ያልተለመደ በመሆኑ ቡቲኩን በራሱ ቁልፍ ከመክፈቱ በፊት ጉዳዩን ለፖሊስ አመለከተ፡፡ ፖሊሶች በስፍራው ደርሰው በሩ ሲከፈት ተገድዶ የተደፈረው ወጣት፤ እዛችው የልብስ መለኪያ ክፍል ውስጥ በትውከትና በሰገራ ተጨማልቆ ወድቋል፡፡ ሌላ በቡቲኩ ውስጥ የተገኘ ሰው ግን አልነበረም፡፡ ባለቤቱ በሁኔታው እጅግ ደነገጠ፡፡ ፖሊሶች እሱን በቀጥጥር ስር አዋሉና ወጣቱን ወደ ህክምና ሥፍራ ላኩ፡፡ የቡቲኩ ባለቤት የሠራተኛውን ባህሪና ለደንበኞቹ የነበረውን አቀባበልና ስሜት ቀስ እያለ ማስታወስ ጀመረ፡፡ እንዴት ይህንን ነገር ሳልጠረጥር ቀረሁ ሲልም ተቆጨ፡፡ ግን ሁሉም ነገር ጅብ ከሄደ—- ሆኖበታል፡፡ ለቀናት በፖሊስ ጣቢያ ቆይቶ፣ በዋስ ተለቀቀ፡፡ ወንጀል ፈፃሚው ግለሰብ ግን ዛሬም ድረስ ዱካው አልተገኘም፡፡
እንዲህ ያሉ ታሪኮች ዛሬ በአገራችን በተለይም በመዲናችን የተለመዱ ተግባራት ሆነዋል፡፡ ድርጊቱ ከዕለት ወደ እለት እጅግ በሚዘገንንና በሚያስደነግጥ ሁኔታ እየተስፋፋ ነው፡፡ ህፃናት ልጆች በትምህርት ቤታቸው ውስጥ በሚያስተምሯቸው መምህራን እየተደፈሩ ነው፡፡
ለዚህ ደግሞ በፌደራሉ የመጀመሪያ ፍርድ ቤት ሰባተኛ ወንጀል ችሎት እየታየ ያለውና በ“ካራክተር ሆልማርክ አካዳሚ” መምህራን ተፈፀመ የተባለው የግብረሰዶም አስገድዶ የመድፈር ወንጀል የቅርብ ጊዜ አብነት ነው፡፡ ስድስት መምህራን የአስርና የአስራ አንድ አመት ዕድሜ ባላቸው ሁለት ህፃናት ላይ በተደጋጋሚ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ፈፅመዋል የሚል ክስ ቀርቦባቸው፣ ጉዳዩ በክስ ሂደት ላይ ይገኛል፡፡
በአሁኑ ወቅት ድርጊቱ እጅግ እየተስፋፋ ሲሆን በማህበረሰቡም ላይ የስነ ልቦናና የማህበራዊ ግንኙነት እንዲሁም፣ የትምህርት ማቋረጥና የጤና ችግር እያስከተለ እንደሆነ በአዲስ አበባ ከተማ ሴቶችና ወጣቶች ቢሮ በቅርቡ የተደረገ ጥናት ይጠቁማል፡፡ ጥናቱ በአሁኑ ወቅት ተመሳሳይ ፆታን ለወሲብ ማሰብ እጅግ እየተለመደ መምጣቱንና ከተመሳሳይ ፆታ ጋር ወሲብ በመፈፀም ሥራ የሚተዳደሩ ሰዎች መበራከታቸውን ይፋ አድርጓል፡፡ የዚህ ችግር ሰለባዎች በአብዛኛው ዕድሜያቸው ከ15 ዓመት በታች የሆኑ ህፃናት፣ የአንደኛና የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች እንዲሁም የከፍተኛ ተቋማት ተማሪዎች፣ በወሲብ ንግድ ሥራ ላይ የተሰማሩ ሰዎችና በማረሚያ ቤቶች ውስጥ የሚገኙ የህግ ታራሚዎች መሆናቸውንም ጥናቱ አረጋግጧል፡፡
የግብረሰዶማዊነት ችግር የምዕራባውያንና የሰለጠኑት አገራት ችግር ብቻ እንደሆነ መቁጠር፣ ህብረተሰቡን ለአስከፊ ጉዳት እንደዳረገው የጥናት ሪፖርቱ ይጠቁማል፡፡ ይሄ ዓይነቱ አዝማሚያ መዘነጋት በመፍጠር ወላጆች ስለ ልጆቻቸው አዋዋል፣ የባህርይ ለውጥና አለባበስ እንዳያስተውሉና ወቅታዊ እርምጃዎች እንዳይወስዱ ያደረገ ሲሆን ልጆችንም እጅግ ለከፋ ጉዳት እያጋለጠ ነው፡፡ ትናንት በሩቁ ስንሰማው የነበረው ግብረሰዶማዊነት፤ ዛሬ የእያንዳንዳችንን ቤት የሚያንኳኳ የሁላችንም ሥጋት ሆኗል፡፡ ከጥቂት ዓመታት በፊት በ“ሴቭ ዘ ቺልድረን ካናዳ” እና በ“ብራይት ፎር ቺልድረንስ ቮለንተር አሶሴሽን” ትብብር የተካሄደ ጥናት እንዳመለከተው፤ በከተማችን አዲስ አበባ ከሚፈፀሙ የአስገድዶ መድፈር ወንጀሎች መካከል 22 በመቶ የሚደርሱት የተፈፀሙት በወንዶች ላይ ነው፡፡ እነዚህ ወንዶች የተደፈሩትም ተመሳሳይ ፆታ ባላቸው ሰዎች ነው፡፡ ጥቃቱ ከተፈፀመባቸው አብዛኛዎቹም ዕድሜያቸው ከ14 ዓመት በታች የሆኑ ህፃናት ናቸው፡፡ ከጥቃቱ ፈፃሚዎቹ መካከል 43.7 በመቶ ያህሉ የጥቃቱ ሰለባዎች የቅርብ ሰዎች እንደሆኑ ጥናቱ አመልክቷል፡፡
የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወጣቶች ማህበር ከክፍለ ከተማው ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመተባበር የግብረ ሰዶማዊነት መስፋፋትን ለማውገዝ ሰሞኑን አንድ ትልቅ ጉባዔ አዘጋጅቶ ነበር፡፡ በገነት ሆቴል በተዘጋጀውና በሺዎች የሚቆጠሩ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ ታዋቂ የኪነጥበብ ባለሙያዎችና የክፍለ ከተማው ነዋሪዎች በተገኙበት በዚህ ጉባዔ ላይ “ዩናይትድ ፎር ላይፍ ኢትዮጵያ” በተባለ አገር በቀል መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት የተዘጋጀ ጥናታዊ ፅሁፍ ቀርቧል፡፡ የድርጅቱ መሥራችና ዳይሬክተር ዶ/ር ሥዩም አንቶኒዮስ በዚሁ ጥናታቸው ላይ እንደገለፁት፣ ግብረሰዶማዊነት በአገሪቱ እጅግ በጣም በሚያስደነግጥ ሁኔታ እየተስፋፋ ነው፡፡
የመጀመሪያና የከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የግብረሰዶማውያን መፈልፈያ ቦታዎች እየሆኑ ነው፡፡ በአንድ መንግስታዊ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ውስጥ በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ፣ በሴቶች የመኝታ ክፍሎች (ዶርም) ውስጥ ከ130 በላይ የተለያዩ አርቴፊሻል የወሲብ መሣሪያዎች ተገኝተዋል፡፡ እዚሁ አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ በሚገኝ አንድ የኮንዶሚኒየም ህንፃ ውስጥ አንድ የአስራ ሰባት አመት ወጣት በርካታ ወንድ ህፃናትን እያባባለና እያስገደደ ደፍሯል፡፡ በከተማውም ሆነ በአገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የግብረሰዶም ተግባር እጅግ በሚያስደነግጥ ፍጥነት እየተስፋፋ መሆኑን የጠቆሙት ዶ/ር ሥዩም፣ ከአዲስ አበባ ከተማ ውጪ በተለያዩ ጊዜያት በወንዶች ፊንጢጣ ውስጥ ገብተው የቀሩ የለስላሳ ጠርሙስና ሌሎች ባዕድ ነገሮች በቀዶ ጥገና ወጥተዋል ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያውያን ወንዶች ከወንድ ጋር፣ ሴቶች ደግሞ ከሴቶች ጋር ወሲብ ሲፈፅሙ የሚያሳዩ ፊልሞች ተሠርተው ገበያ ላይ መዋላቸውንም ጠቁመዋል፡፡
በአገሪቱ የግብረሰዶማዊነት ተግባር እጅግ መስፋፋቱን አመላካች ከሆኑት ተግባራት መካከል ግብረሰዶማውያኑ “ሬይንቦ” የተባለ ማህበር በግልፅ አቋቁመው፣ አባላት ለመመልመልና ድርጊቱን ለማስፋፋት እየተንቀሳቀሱ መሆኑን ዶ/ር ሥዩም ተናግረዋል፡፡ ድርጊቱ በአገሪቱ እንዲበራከትና እንዲስፋፋ ካደረጉት ምክንያቶች መካከል በSex tourism አማካኝነት ወደ አገራችን የሚገቡ የውጪ ዜጐች፣ ከኢትዮጵያ ውጪ ኖረው የሚመጡ ኢትዮጵያውያን፣ ወደተለያዩ አገራት ለንግድና ለሌሎች ሥራዎች የሚንቀሳቀሱ ሰዎች እና የልቅ ወሲብ ፊልሞች መበራከት እንደሆኑ ተጠቁሟል፡፡
አሁን በአገሪቱ ውስጥ ባለው ሁኔታ የሴት ግብረሰዶማዊያን (ሴት ለሴት ግንኙነት የሚፈፅሙ) በቁጥር አነስተኛ መሆናቸውን የገለፁት ዶ/ር ሥዩም፣ የወንድ ግብረሰዶማውያን ቁጥር ከጊዜ ወደጊዜ እየጨመረ ነው ብለዋል፡፡ በሆነ አጋጣሚ ወይም በመደፈር ወደ ግብረሰዶማዊነት ህይወት የሚገቡ ወጣቶች ወይም ህፃናት ድርጊቱን እንዳያቆሙና ከችግራቸው እንዳይላቀቁ ግብረሰዶማውያኑ ያስፈራሯቸዋል – “አንድ ጊዜ በፊንጢጣ ግንኙነት ማድረግ ከጀመርክ ፊንጢጣ ውስጥ የሚፈጠር እጭ ይኖራል፡፡ እጩ ደግሞ በየጊዜው ስፐርም ማግኘት ይኖርበታል፣ ያለዚያ ግን አንጀትህን ይቦድሰውና ለከባድ የጤና ችግር ትጋለጣለህ” እያሉ፡፡ በዚህ ምክንያትም አንድ ጊዜ የችግሩ ሰለባ የሆኑ ሰዎች ከድርጊቱ ለመላቀቅና ወደ ትክክለኛው ህይወት ለመመለስ አይፈልጉም፡፡ ይህ አባባል ግን ፈፅሞ ከእውነት የራቀና ግብረሰዶማውያኑ የአባላት ቁጥራቸውን ለማበራከት የሚጠቀሙበት ዘዴ ነው ብለዋል፡፡ ህብረተሰቡ ይህንን እጅግ አደገኛ በሆነ ፍጥነት እየተስፋፋ ያለውን የግብረሰዶማዊነት ተግባር ለመግታት ከፍተኛ ንቅናቄ ማድረግ እንደሚገባውና እያንዳንዱ ሰው በቤቱ ውስጥ በልጆቹ ላይ የሚታዩ ለውጦችን ትኩረት ሰጥቶ በመከታተል፣ ልጆቹ ወደማይመለሱበት ጥፋት ውስጥ ከመግባታቸው በፊት ሊታደጋቸው ይገባል ሲሉ ዶ/ር ሥዩም ተናግረዋል፡፡
ግብረሰዶማውያን በከተማዋ የተለያዩ ቦታዎች የራሳቸው መገናኛ ሆቴሎች፣ መቀጣጠሪያ ካፌዎች፣ የተመሳሳይ ፆታ ወሲብ መፈፀሚያዎች፣ መዝናኛና ማሣጅ ቤቶች እንዳሏቸው ለማወቅ ተችሏል፡፡ ከተመሳሳይ ፆታ ጋር ወሲብ በመፈፀም ሥራ የሚተዳደሩ ግብረሰዶማውያን (ቆሚታዎች ነው የሚባሉት) በአብዛኛው በቦሌ አካባቢ የሚገኙ ሲሆን በተለይ ደግሞ ፍሬንድሺፕ ህንፃ፣ ቦሌ ድልድዩ አጠገብና፣ ቦሌ ሸዋ ዳቦ አካባቢዎች ይጠቀሳሉ፡፡ ፒያሣ የሚገኙ ጥንታዊ ሆቴሎችና ረዘም ያለ ዕድሜን ያስቆጠረ አንድ ካፌም የግብረሰዶማውያን መገናኛ፣ መቀጣጠሪያና መተዋወቂያ ሥፍራዎች ናቸው፡፡ ከጥናቱ ለመረዳት እንደተቻለው፣ ግብረሰዶማውያኑ አብዛኛውን ጊዜ ከተለመዱት የወንዶች አለባበስና ስታይል ለየት ያሉና በቀላሉ አይን የሚስቡ ነገሮችን ማድረግ የሚያዘወትሩ ሲሆኑ አብዛኛዎቹ በግራ ጆሮአቸው ላይ ሎቲ ያደርጋሉ፡፡ ጠበብ ያሉ (ታይት) ሱሪዎችን፣ ሰውነትን በተለይም ደረትና ክንድን የሚያጋልጡ ልብሶችን መልበስና ሱሪያቸውን ዝቅ በማድረግ ፓንታቸውን እያሣዩ መሄድንም ያዘወትራሉ፡፡ ቅንድባቸውን ለመቀንደብ፣ ጥፍራቸውን ለመሞረድና የእግር ተረከዞቻቸውን ለመሠራት አብዛኛዎቹ ግብረሰዶማውያን የሴቶች የውበት ሳሎኖችን ያጣብባሉ፡፡ ብዙውን ጊዜም ነጣ ያሉ (ድፍን ነጭ) ካልሲዎችን በክፍት ጫማ ማድረግን ያዘወትራሉ፡፡ ሁልጊዜም ንፁህና መልካም ጠረን እንዲኖራቸው ይተጋሉ፡፡ በአዲስ አበባ የሚገኙ በርካታ ፔኒሲዮኖች ለግብረሰዶማውያን አገልግሎት በመስጠት ተግባር ላይ እንደሚሳተፉም ለማወቅ ተችሏል፡፡
ለግብረሰዶማውያንነት በአብዛኛው ተጋላጭ የሚሆኑት በወላጆቻቸው የተረሱ ህፃናት፣ ከአንድ ወላጅ ጋር ብቻ የሚኖሩ፣ የጐዳና ተዳዳሪዎች፣ ስደተኞች፣ የአዕምሮ ውሱንነት ችግር ያለባቸው ሰዎች፣ የአካል ጉዳተኞችና በህፃናት ማሳደጊያ ውስጥና በማረሚያ ቤቶች ውስጥ ያሉ ሰዎች መሆናቸው በጥናቱ ተጠቁሟል፡፡ የግብረሰዶማዊነት ችግር ለኤችአይቪ፣ ለወሲባዊ ግንኙነት ፍላጐት ለማጣት፣ ራስን ለመጥላት፣ ከሰዎች ለመገለልና ለብቸኝነት፣ ለጭንቀትና ፍርሃት እንዲሁም ከአስራ አራት በላይ ለሚሆኑ የጤና ችግሮች እንደሚያጋልጥ ተገልጿል፡፡ ይህ ወቅታዊ ጥሪ ለወላጆች፣ ለመንግስትና ለህብረተሰቡ እንዲሁም ጉዳዩ ለሚመለከታቸው አካላት ሁሉ የቀረበ ሲሆን ጉዳዩ አፋጣኝ የመፍትሔ እርምጃ ካላገኘ እጅግ አደገኛ ለሆነ የማህበረሰባዊ ቀውስ ይዳርጋል፡፡

addisadmassnews.com

የቤተመንግስት ደህንነት ሃላፊ ተነሱ (ከኢየሩሳሌም አርአያ)

$
0
0
tplf
የቤተ-መንግስት የደህንነት ጥበቃ ዋና ሃላፊ ሆነው ሲያገለግሉ የቆዩት የሕወሐት አባል አቶ ጌታቸው ተፈሪ ከስልጣናቸው መነሳታቸውን ምንጮች አስታወቁ። አቶ ጌታቸው ቀደም ሲል በክልል 14 ፖሊስ ኮሚሽን የደሕንነት ልዩ ተወርዋሪ ሃይል ሃላፊ ተደርገው ሲያገለግሉ መቆየታቸውን የጠቆሙት ምንጮች፣ ከዚያም ወደ ቤተ መንግስት ተዛውረው መመደባቸውንና በተጨማሪ የአገር ውስጥ ደህንነት ምክትል ሃላፊ በመሆን ከአቶ ወ/ስላሴ ወ/ሚካኤል ጋር ሲሰሩ መቆየታቸውን አስረድተዋል። የአቶ መለስና ወ/ሮ አዜብ የቅርብ ሰው የሆኑት አቶ ጌታቸው ተፈሪ በነበራቸው ታማኝነት የቤተመንግስት የደህንነት ሃላፊ ተደርገው በአቶ መለስ ተመርጠው እንደተሾሙ ያስታወሱት ምንጮች፣ በማያያዝም እስከ 1994ዓ.ም የቤተመንግስት የደህንነት ጥበቃ በሃላፊነት ሲመሩ የቆዩት አቶ ዘርኡ መለስ በወቅቱ ከአቶ መለስ ጋር በፈጠሩት የፖለቲካ ልይነት ምክንያት ካዛንቺስ አካባቢ በሚገኘው የቀድሞ “ኮከብ ሬስቶራንት” የአሁኑ “ሚልክ ሃውስ” መኖሪያ ሕንፃ አንደኛ ፎቅ ቤታቸው ውስጥ አንገታቸው በስለት ታርዶና በድናቸው ተበላሽቶ መገኘቱን አመልክተዋል። ይህን አሰቃቂ ግድያ ያከናወነው አሁን በእስር ቤት የሚገኘው የቀድሞ አገር ውስጥ ደህንነት ሃላፊና የአቶ መለስ ቀኝ እጅ ወ/ስላሴ ወ/ሚካኤል መሆኑን ምንጮቹ አጋልጠዋል።
አቶ ጌታቸው ተፈሪ ከስልጣን እንዲነሱ የተደረገው በደህንነት ዋና ሹም አቶ ጌታቸው አሰፋ ትእዛዝ መሆኑን ያመለከቱት ምንጮች፣ በአሁኑ ወቅት በምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ እንደማይታወቅ ጠቁመዋል። አቶ ጌታቸው ተፈሪ የወ/ስላሴ መታሰር ቅር ሳያሰኛቸው እንዳልቀረና በተጨማሪም የነአዜብ ቡድን ደጋፊ መሆናቸውን ምንጮቹ አመልክተዋል።

 

Viewing all 8745 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>