Quantcast
Channel: ዘ-ሐበሻ – Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 8745 articles
Browse latest View live

ከአማራ ዴሞክራሲያዊ ሃይል ንቅናቄ የተሰጠ መግለጫ

$
0
0

ታኀሳስ 23/04/2007 ዓ ም

የአማራ ዴሞክራሲያዊ ሃይል ንቅናቄ ታጋዮች ከወልቃይት ጠገዴና አርማጭሆ ህዝብ ጎን በመሰለፍ በዘረኛውን ናዚ ወያኔ መከላከያና ከትግራይ ተስፋፊ ታጣቂዎች ጋር ከባድ ውጊያ አያካሄደ ይገኛል።አዴሃን ከኤርትራ/ሻቢያ/ ምድር ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለውጤት የሚያበቃውን የአደረጃጀት ስልት በመንደፍ /በመቀየስ/ ወደ ተጨባጭ ስራ መግባቱን ይፋ ማድረጋችን ይታወሳል።

አዴሃን በሁሉም የአገራችን አካባቢዎች የሚያደርገው እንቅስቃሴ እንደተጠበቀ ሆኖ በተለይም የወያኔ ስርአት አረመኔያዊ አገዛዝ ግፊት ቀማሽ ለሆነው ከወልቃይት ጠገዴና አርማጭሆ አካባቢ ልዩ ትኩረት በመስጠት እየተንቀሳቀሰን እንገኛለን። ከዚህ ቀደም ህውሃት በወረራ የያዛቸውን የወልቃይት ጠገዴና የአርማጭሆ ሰፋፊ ለም መሬቶችን አስተማማኝ ለማድረግ እና አዳዲስ መሬቶችን ለመያዝ የነደፈውን እስትራቴጂ ተግባራዊ ሊያደርግ እየተዘጋጀ መሆኑንና ታላቋን ትግራይ ለማስፋት ባለው ህልም መሰረት ከፍተኛ ዝግጅት እያደረገ መሆኑን August 19 – 2014 ” ህወሃት በወልቃይትና ጠገዴ ህዝብ ላይ ተጨማሪ የዘር /ማጽዳት/ፍጅት ለማካሄድ እየተዘጋጀ ነው።” በሚል ርዕስ መረጃዎችን ይፋ አድርገን ነበር።

በሌላ በኩልም November 19- 2014” የጠገዴ ወረዳ ህዝብ አማራ እንጂ ትግሬ አይደለንም በማለት እራሱን ለመከላከል እየተዘጋጀ ነው።” በሚል ርዕስ ለህዝብ የተበተነውን የትግል ጥሪ ፓምፕሌት ጨምረን ይፋ አድርገን እነደነበር ይታወሳል። በመሆኑም ወያኔ የትግራይን የመስፋፋትና አማራውን የማጥፋት አባዜውን እውን ለማድረግ፦ ህዝቡም እራሱን ለመከላከልና ማንነቱን ለማስከበር በጀግንነት ዱር ቤቴ ብሎ የራሱን የጎበዝ አለቃ መርጦ በከባድ መሳርያ የሚታገዘውን የወያኔ ሰራዊት በከፍተኛ ደረጃ እየመከተ ይገኛል። በመሆኑም መላው የኢትዮጵያ ህዝብ በተለይም በቅርብ የሚገኘው አማራውና እንዲሁም በተለያየ መንገድ ወያኔን ለማሰወገድ በትግል ላይ ያሉ ድርጅቶች ከህዝብ ትግል ጎን እንዲቆሙ አሳስበንም ነበር። ይኸው ዛሬ የወያኔ የጸጥታ መከላከያና፡ የትግራይ ታጣቂዎች እንዲሁም ስውር ነብስ ገዳይ ደህንነቶች በማን አለብኝነት በሰላማዊ ህዝብ ላይ ከታህሳስ 17- 2007 ጀምሮ ግልጽ ጦርነት ከፍተዋል። ህዝቡም እራሱን ለመከላከል ሲል በሚቻለው ሁሉ ራሱንና ሀገሩን ከባዳዎች ስብስብ ለመከላከል ዘረኛውን አባገነን ስርአት እየተፋለመው ይገኛል።

የአማራ ዴሞክራሲያዊ ሃይል ንቅናቄ ታጋዮችም ሁኔታውን በቅርብ እየተከታተልን ከህዝቡ ጎን በመሰለፍ ታረካዊ ግዳጃችንን እየተወጣን እንገኛለን። በአሁኑ ጊዜ አረመኔው የወያኔ ስርአት በርካታ የመከላከያ ሃይሉን ከትግራይ ግንባሮችና ከመሃል ሀገር ሳይቀር ወደ ስፍራው በማንቀሳቀስ የሚያካሄደውን የማንነት ትግል በሃይል ለመጨፍለቅ እርብርብ እያደረገ ይገኛል ። በተለይ የናዚው ወያኔ የግፍ አገዛዝ ሰለባ ላለመሆን እራሳቸውን መከላከል የማይችሉትን ህጻናት፣ ሽማግሌዎችንና ሴቶች ላይ አረመኔያዊ የሆነ ጥቃት እየፈጸመ ይገኛል።አሁን ባለንበት ሰአት የወልቃየት ጸገዴና አርማጭሆ ህዝብ በከፍተኛ ወኔ እየተጠራራ እየተደራጀ የጀመረውን የነጻነት ትግል ለማጠናከር ዱር ቤተ ብሎ ከያለበት የእከተተ ይገኛል ።

የአማራ ዴሞክራሲያዊ ሃይል ንቅናቄም የቻለውን ሁሉ በማድረግ ከህዝቡ ጎን ተሰልፎ የራሱን ታሪካዊ አስተዋፆ በማበርከት ህዝቡን የድል ባለቤት ለማድረግ ተግቶ በሰራት ላይነው ። ሁኔታው የሚመለከታችሁና የሚያሳስባችሁ ወገኖች ሁሉ የተቀጣጠለውን ካለው ህዝባዊ ትግል ጎን እንድትሰለፉ አዴሃን ወቅታዊ ጥሪ ያቀርባል።በሁሉም መስክ ትግሉን ለማጠናከር በየቀኑ ሁኔታውን በመከታተል፣ እንድትሳተፉ በድጋሜ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

፠ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ፠

ሞት ለወያኔ

የአማራ ዴሞክራሲያዊ ሃይል ንቅናቄ ስ\አስፈፃሚ

 

10897830_1530702910533439_7009177353300305907_n


በአፋር ከ40 በላይ የሚሆኑ ወጣቶች የትጥቅ ትግሉን ለመቀላቀል ጫካ ገቡ

$
0
0

አኩ ኢብን ከአፋር ለዘ-ሐበሻ እንደዘገበው:-

በሰሜናዊው የአፋር ክልል ከባራሕሌ ወረዳ ቁጥራቸው ከ 40 በላይ የሚሆኑ ወጣቶች በወረዳውና በመላው አፋር ክልል ላይ የወያኔ ተወካዮች በህዝብ ላይ newsእያደረሱ ያሉትን በደል በመቃወም ወደ ትጥቅ ትግል ከአፋር ኡጉጉሞ ጋር ለመቀላቀል ወደ ጫካ መግባታቸው ተረጋገጠ።

በአፋር ክልል እየተባባሰ የመጣውን የሰብዓዊ መብት ጥሰትና የወያኔ እና አገልጋዮቹ አብዴፓ ፈላጭ ቆራጭነትን ማስወገድ የሚቻለው በህዝብ አንድነትና ቁርጠኝነት መሆኑን አምነው ብዙ ወጣቶች ለአገራቸው መስዋዕት ለመሆን የተዘጋጁ እንዳሉ እሙን ነው።

በዚህ ዜና ላይ ተጨማሪ መረጃ ይዤ እቀርባለሁ።

ዛሬ የወያኔው ፖሊስ ስለለቀቀው የአንዳርጋቸው ጽጌ አዲስ ቪድዮ ዙሪያ የተሰጡ አስተያየቶች

$
0
0

የሕወሓት አስተዳደር ፖሊስ ዛሬ ስለአንዳርጋቸው አዲስ ቪድዮ ለቋል:: በየሶሻል ሚዲያዎችም መነጋገሪያ ሆኗል:: በዚህ ዙሪያ ከሶሻል ሚዲያዎች የተለያዩ አስተያየቶችን ስለቪድዮው ሰብስበናል ያንብቧቸው:-
andargacew Tsige
የጆሜክስ ካሳዬ አስተያየት:-

ሌባና ፖሊስ የሚባለው የገዢው አገልጋይ የሆነው የፌዴራል ፖሊስ ፕሮግራም የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ቪዲዮ በማሳየት አሜሪካን የሚያስንቅ የምርመራ ሥልት አለን እንደ ሌባ ሻይ ሳንገርፋቸው ይናዘዛሉ በማለት የድፍረቱን (የድድብናውን) ልክ ሊያሳየን ሞክሯል፣ ይህ መራር ቀልድ በአስቀያሚ የማዕከላዊ ምርመራ ሂደት ውስጥ ያለፉትንና ቶርቸርን ያስተናገዱት ጓደኞቼን ሳስብ ድፍረቱ አሳምሞኛል ፤ጓደኞቼም በማዕከላዊ ቆይታቸው የታዘቡት ጥፍራቸው የተነቀለባቸውን ተማሪዎች ሳስብ እነዚህን መርማሪዎች እና ጋዜጠኞች በፍትህ አደባባይ አገኛቸው ዘንድ ዘወትር እናፍቃለሁ፤

ፕሮግራሙ አሜሪካን ሊያብጠለጥል የፈለገበት እና የጠቀሰወው ሰሞነኛው የቶርች ሪፖርት ኢትዮጵያም ተሳታፊ መሆኗን እንዳጋለጠ ዘንግተውት ይሆን ብዬ አልጠይቅም አንዴ ምንም አያመጡም አያውቁም ተብለን ተንቀናልና (ሕዝብን ከመናቅ ካለሆነ ከምን ይመነጫል?)፡፡

በዚህ እጅ እግር የሌለው ከመቆራረጡ የተነሳ አሁንም የመግረፍ እንጂ የካሜራ እውቀት የሌላቸው ብቻ የቀረጹት እንደሆነ በሚያሳብቀው ቀረጻ አልሞተም ለማለት ካልሆነ በቀር እርግጠኛ ነኝ እነሱም አልገባቸውም፡፡

አንድ ሰው ለአንድ ቃለ መጠይቅ 10 ደቂቃ ለሚፈጅ ልብስ ለምን ይቀያይራል?

የሚናገረውን እውነት ነው ብለን እንድናምን በተያየ ቀናት የተቀረጸ ነው ብለን ብንቀበል እንኳ ራሳቸውን የሚያሳጣ እንጂ ምንም የተላለፈ መልዕክት የለም፡፡
ምርመራችሁን ጨርሳችሁ ፈርዳችሁበት እያለ ስለሚበላው ሳይሆን ስለምታደርጉበት እናውቅ ዘንድ እስከዛሬ በፍርድ ቤት ራሱን እንዲከላከል እድል በተሰጠው ነበር፤ እኛም ባመናችሁ ነበር፡፡

ከጠበቆች ከእምነት አባቶች እና ቤተሰብ (ወይም ከኤምባሲው ተወካይ) እንዲያገኘው እድል በተሰጠው ነበር፡፡
ዜጎች በሕግ እስካልተወሰነባቸው ድረስ እንደጥፋተኛ ያለመቆጠር መብት (ሕገ-መንግስቱን መጥቀሴ በራሳቸው ሜዳ ለማሳጣት እንጂ ያከብሩታል በሚል የዋህነት አይደለም) በሕገ-መንግስቱ አንቀጽ 20.3 ዛሬም በፖሊስ ተጥሶ የሙስሊም አመራሮች እና ጋዜጠኞች ሽብርተኛ ተብለው ምስላቸው በአጃቢነት ቀርቧል፤ ግልጽ ባልሆነው ይቅርታ የተለቀቀው አርቲስት ደበበ እሸቱ (ሳይፈረድበት) የአሸባሪነት ማጀቢያ በመሆን ስሙ በድጋሚ እንዲጠፋ ሆኗል፡፡
የሚንቀውን ሕዝብ የሚያስተዳድረው ሕወኃት (ኢሕአዴግ) ልሳን የሆነው ኢብኮ (ኢቲቪ) እና የሌባና ፖሊስ ፕሮግራም የኢትዮጵያ ሕዝብ ደንቆሮ ነው ብሎ ያስባሉ፡፡
እኛስ የእነሱን ግምት በዝምታችን እያረጋገጥን እስከመቼ እንቆይ ይሆን?
————————————————————
የጋዜጠኛ ዳዊት ሰለሞን አስተያየት:-

አንዳርጋቸው ጓደኞቹን ሰላም አላቸው
ፍርድ ቤት የመቅረብ፣ ጠበቃ የማቆም፣ በቤተሰቦቹ ፣በወዳጆቹ የመጎብኘትና ሐኪም የማናገር መብቶቹን የተነፈገ ሰው በአፋኞቹ በተዘጋጀለት ቀረጻ (መቀረጹንም ካወቀ) የተናገረው ነገር በምን አግባብ በምርመራ ጥበብ የተገኘ ሊባል ይችላል?
እውነቱን ለመናገር አንዳርጋቸው ጽጌ በዛሬው ቪዲዩ በስም እየጠራ የጠቀሳቸውን ሰዎች እኔ የምቆጥረው የከበረ ሰላምታ እንደላከላቸውና ትግሉን የምር እንዲገፉበት እንዳበረታታቸው ነው፡፡

ፖሊስ በእሰረኞች አያያዝና በምርመራ ወቅት ይጠቀማቸዋል ስለሚባሉ ኢ ሰብዓዊነት የጎደላቸው ቴክኒኮች ውሸትነት ህዝቡን ማሳመን ከፈለገ
—ማዕከላዊ የወንጀል ምርመራን ለህዝብ ክፍት ያድርግ እያንዳንዱ የምርመራ ክፍል ምን አይነት የምርመራ መሳሪያዎች እንዳሉት ጭምር ህዝብ ይመልከታቸው

–በአሁኑ ወቅት በማዕከላዊ የሚገኙና ከዚህ በፊት በወንጀል ምርመራው ያለፉ ዜጎች ገለልተኛ በሆነ አካል ምን እንደተፈጸመባቸውና እነማን እንደፈጸሙባቸው እንዲናገሩ ያድርግ

መቼም የሙስሊም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት የሆኑት እነአቡበከር በፍርድ ቤት የተናገሯቸው ለጆሮ የሚሰቀጥጡ የጭካኔ የምርመራ አይነቶች የፖሊስ ፕሮግራሙ አቅራቢ እንደተናገረው የተፈጸሙባቸው በአይ ኤስ አይ ኤስ ወይም በአሜሪካን ወታደሮች አይደለም ፡፡እነአቡበከር ይህን ግፍ በሰውነታቸው ያሳለፉት በማዕከላዊ የወንጀል ምርመራ ነው፡፡
—————————————–
የጋዜጠኛ መሳይ መኮንን አስተያየት:-

ህወሀቶች አቶ አንዳርጋቸውን ዛሬ አሳዩን። አሜሪካን ሚስጢር የምታስወጣው በማሰቃየት ነው እኛ ግን በፍቅርና በእንክብካቤ ነው የሚለውን እንድናምንላቸው የሄዱበት ዙሪያ ጥምጥም በራሱ ያደክማል። ለማንኛው አንዲን በማየቴ በግሌ ደስ ብሎኛል፡፡ በተቃዋሚዎች ዙሪያ ህወሀቶች እንዲናገርላቸው ያደረጉት የሚመስለው ግን ያው ቀድመን የገመትነው ነው። ገና ከዚህ የባሰውንም ሊያሳዩን ይችላሉ።
—————————————–
የጋዜጠኛ ደረጀ ሃብተወልድ አስተያየት:-
ምዕራባውያን ሀገሮች- በሰላማዊና በትጥቅ ትግል ከሚንቀሳቀሱ አንዳንድ ተቃዋሚዎች ጋር እንዲያደራድሩት ጥያቄ እንዳቀረበ በኢሳት በመነገሩ የተበሳጬው የኢህአዴግ መንግስት፤ በዛሬውፖሊስ ፕሮግራም መቶ ቦታ የተቆራረጠ የአቶ አንዳርጋቸውን ንግግርና ምስል በማቅረብ ምላሽ ለመስጠት ሞክሯል። ወይ ጭንቀት!!!
አንዳርጋቸው፤ሁሌም ጀግና ነህ!!!
——————————
ሳም ቮድ ሶን አንዳርጋቸው የተባሉ ግለሰብ የሰጡት አስተያየት:-
ወያኔ አሁንም እንደለመደው ቆርጦ እና ቀጥሎ በ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ላይ ይሄንን ቪድዮ ለቋል እውነታው ግን እስካሁን ድረስ የ ኢንግሊዟ አምባሳደር ባለፈው ለጉብኝት በሄዱበት ወቅት የት ቦታ እንደወሰዷቸው አና አካባቢውን የት ቦታ እንኳ እንደታሰረ እንደማያውቁ ባለፈው ገልፀዋል እናም ወያኔ ለፕሮፖጋንዳው እንዲመቸው አድርጎ ቆርጦ እና ቀጥሎ ይሄንን ቪድዮ ለቀቀ እውነት አንዳርጋቸው ምን ተጠይቆ ነው የተናገረው ለምን የጠያቂው ድምፅ እና ጥያቄው ምን እንደሆነ አያሰሙንም ደሞ ይህ ቪደዮ አሁን የተቀረፅ ለመሆኑ ምንም አይንአይንተ ማስረጃ የለም::
———————————–
የሁኔ አቢሲኒያ አስተያየት:-

በዛሬው እለት በፖሊስ ፕሮግራም የተለቀቀው የጋሽ አንዳርጋቸው ጽጌ ቪዲዮ ጋሽ አንዳርጋቸው ከፍተኛ ድብደባ እንደደረሰበት ያስታውቃል።
ከሞቀ ኑሮው መካከል ስለህዝቡ ሲል እንዲህ ይሰቃይ? እስከመቼ ጀግኖቻችንን ለጅብ ሰጥተን ልንተኛ ይሆን ኢትዮጵያ ውስጥ ምርመራ የምናደርገው ሰብአዊ በሆነ መልኩ ነው እያለን ነው – የወያኔ ፖሊስ::

የወያኔ ፍሬ መራገፊያው ደርሷል !!!

$
0
0

ከ-ከተማ ዋቅጅራ

rtወያኔ ማለት፡- ወይ ያኔ የሚለውን ፍቺ ይሰጠናል። ወይ ያኔ ደግሞ የቁጭት ቃል ነው። ይሄ የቁጭት ቃል ምስረታቸው ጋር ይወስደናል።ጥቂት ሆነው ወደ መሰረቱት ጋር ያኔ ነበር ስሩን ማድረቅ ያኔ ነበር በአንድ ቦንብ እህ ማለት የሚለውን የቁጭት ቃል ይነግረናል። ወያኔ (ወይ ያኔ) ያኔ ተመሰረቱ ለነሱ አላማ፣ ለነሱ ድብቅ እቅድ፣ ለነሱ የደም ማፍሰ እርካታ፣ ተመሰረቱ። ታዲያ ያንን ድብቅ አላማቸውን ለማሳካት የራሳቸው የቅርብ ሰው የሚባሉትን በአላማቸው ያልሄዱትን የፈጁ እና ያስፈጁ የማፊያ ግሩፕ ናቸው። ምስኪኑን የትግራይ ህዝብ በማያውቀ ለድብቅ አላማቸው ያለምንም ርህራሄ ዳር ቆመው ድብቅ ሴራቸው ለማስፈጸም ወገኑን በማያውቀው እንደ ቅጠል እንዲረግፉ ሲያደርጉ ልባቸው የደስታ እንጂ የሃዘን ስሜት አልነበራቸውም።

 
ወያኔ መሰረቱ ውሸት፣ ምሶሶው ውሸት፣ ግድግዳው ውሸት፣ ጣራውም ውሸት የሆነ የውሸተኞችና የማፊያ ግሩፕ ነው። አንድ ያነበብኩት ጽሁፍ ትዝ አለኝ፡ <<በኢሕአዲግ ዘምን የሚመረቁ ባለስልጣን እና ካድሬዎች ከአንድ ወፍጮ ቤት ተፈጭተው የወጡ እና እቤት ቁጭ ብለው ሁሉን ነገር በትእዛዝ የሚቀበሉ የወፍጮ ውጤቶች ምሩቆች ናቸው>> የሚለው ።በትክክል ይህ ሃሳብ ይገልጻቸዋል። ባለስልጣኑም ሆነ ካድሬው ወደ ወያኔ (ወይ ያኔ) ወፍጮ ቤት ይገባሉ 1ኛ ድግሪ 2ተኛ ድግሪ ማስተር ዶክተር ፕሮፌሰር እያለ የወፍጮ ውጤቶች የትምህርት ደረጃ ይሰጣቸዋል።ያልሆኑትን መሆን ያልሰሩትን ሰራን ማለት ተንኮል እና ውሸት ከመሰረቱ አይደለ። እናም ገና አፋቸውን ሲከፍቱ ማን ምን እንደሆነ ይታወቃል ወሬአቸው በሙሉ ዱቄት ዱቄት ይላል ምክንያቱም የአንድ ወፍጮ ፍጭት ውጤት ስለሆኑ ነዋ ! ምድረ ዱቄታም ሁሉ። አሁንማ ዱቄት ዱቄት የሚለውን ንግግራቸውን መስማት ህዝቡ ምን ያህል እንደሰለቸውና እንዳንገሸገሸው ቢያውቁት ዱቄት አፋቸውን በየመድረኩ በተገኘው አጋጣሚ አያቦኑብንም ነበረ።

 
ኢሕአዲግ ለህዝቦች እኩልነት የቆመ ድርጅት ነው ይሉናል ዋናዎቹ ካድሬዎች የወያኔ የወፍጮ ውጤቶች። እንዴት በምን አይነት መስፈርት በየትኛው ልኬት ነው ብለህ ስትጠይቃቸው በዱቄት አፋቸው ሳያፍሩ በዝርዝር ያቦኑታል እዚህ ዝርዝር ውስጥ አልገባም እኔም ዱቄት ማቡነን እንዳይሆንብኝ። ግን በትንሹ የህዝቡን ቁጥርና የስራ ድርሻቸውን እንቃኛለን። ለህዝቦች እኩልነት የቆመ ድርጅት ነው ስለሚሉ የቱ ጋር ነው እኩልነቱ ያለው የሚለውን ለማየት…. ኦሮሞ 34.5% አማራ 26.9% ሶማሌ 6.2% ትግሬ6.1% ሲዳማ 4.1% ጉራጌ 2.8% ወላይታ 2.3% ሃድያ 1.7% አፋር 1.7% ይሄንን የቁጥር አሃዝ ያገኘሁት ከgoogle wikipedia ላይ ነው። ታዲያ አሁን ወደ እውነታው ስንመጣ መከላከያ ሚኒስቴር በሃላፊነት ቦታ ያሉት 94% ወያኔ ነው ደህንነት ምንስቴር፣ የውጪ ጉዳይ ሚንስቴር፣ ጉምሩክ፣ ኢምግሬሽን፣ አየር መንገድ፣ አየር ሃይል፣ ቴሌኮሙንኬሽን፣ መብራት ኃይል ሌሎችም በሙሉ እድርና እቁብ እራሱ ሳይቀር በወያኔ ካድሬ ነው የተያዘው። ይሄንን ደግሞ አገር ቤትም ሆነ በውጪ ባለው ህዝብ የታወቀ ነው።

 
በዱቄት አፋቸው ኢሕአዲግ ለብሔር ብሔሮች ነጻነት አመጣ ብለው ዱቄታቸውን ያቦኑብናል።የቱጋር ነው የብሔር ብሔረሰቦች መብት የተከበረው ከታች እስከላይ ሃገሪቷን የተቆጣጠራችሁት እናንተ ያውም ያለ መስፈርት ምንም እውቀትና ችሎታ ሳይኖራቸው ሌላው ግን ችሎታ ኖሮት እውቀት ኖሮት አቅም ኖሮት በነጻነት መስራት ያልቻለ ስንት ዜጋ አለ ብለህ በምትናገርበት ግዜ በየቦታው የተቀጠሩት ካድሬዎች የወፍጮ ቤት ወሬአቸውን ይጀምራሉ አድጋለች ተመንድጋለች ይሄ ገባ ይሄ ወጣ ይሄ ሆነ…. ወዘተ ይሉናል መቼስ የወፍጮ ቤታቸውን ወሬአቸውን እንድደግምላችሁ እንደማትፈልጉ አውቃለው የወያኔን ባህሪ የማያውቀው ሰው የለም ያልተረዳቸውም ዜጋ የለም ስለዚህ ዱቄቱን በማቡነን ውድ ህዝቤን አላሰለቸውም።

 
አሁን ግዜው የሰፊው ህዝብ ነው የወያኔ የግፍ ጽዋ ሞልቷል ግፍ የሰሩና የሚሰሩ በአገራችን ምድር የሚነግሱበት ግዜ መቋጫው ደርሷል የሕወሓት ዋና ዋና የማፊያው መሪዎች እርስ በእርስ እየተባሉ ነው አውሬ አውሬን እንደሚበላው። የመከላከያው ሰራዊት ደግሞ ወታደሩ ከነ ሙሉ ትጥቁ እየካደው ነው። ህዝቡ ደግሞ ወያኔን ለመደምሰስ አጋጣሚውን እየጠበቀ ነው። ይሄ ነው ድል ከአሁን በኃላ የወይ ያኔ (ወያኔ) ድምጽ የሚሰማ የለም በፊት እንደ ፈለጉ ሲንሸራሸሩበት የነበረ አገር አሁን እንደፈለጉት መንሸራሸር ቀረ በፊት በውጪ ተዝናንተው ይኖሩ የነበረ አሁን ግን በውጪ የሚኖረው ዜጋ መፈናፈኛ አሳጥቶአቸዋል። በፊት እያሳደዱን እየደበደቡን እያሰሩን እያሰቃዩን እያንገላቱን እየገደሉን ይኖሩ የነበረ። አሁን ግን ነገሮች ሁሉ ተቀይሮ ግጥሚያው ፊት ለፊት ሆኗል። ህዝብን ያሸነፈ ማንም የለም ህዝብ ሁሌም አሸናፊ ነው። ከውስጥ እስከ ውጭ ከመሃል እስከ ዳር ከደቡብ እስከ ሰሜን ከምዕራብ እስከ ምስራቅ በአንድነት ተነሰተናል ወያኔ ከገባበት ቃሪያ ውስጥ ሰንጥቀን ፍሬአቸውን ለማራገፍ በቆራጥነት ተነስተናል። ወያኔ ሆይ ከአሁን በኋላ ገድሎ መፎከር የለም አቃጥሮ መኖርም የለም አሰቃይቶ መክረምም የለም ጥቂቶችን የሆኑ ወያኔዎች ከነ ወፍጮ በታቸው ለማጥፋት ቆርጠን ተነስተናል። ኦሮሞው ጋር ሂድ ቆርጦ ተነስቷል አማራው ጋር ሂድ ቆርጦ ተነስቷል ሱማሌው ጋር ሂድ ቆርጦ ተነስቷል ደቡቡ ጋር ሂድ ቆርጦ ተነስቷል አፋሩ ጋር ሂድ ቆርጦ ተነስቷል።

 
ወይ ያኔ (ወያኔ) ሆይ አርቀህ የቆፈርከውን የግፍ እና የመከራ ጉድጓድ ከነጭፍሮችህ በመቅበር ለድል ለነጻነት ለዲሞክራሲ ለእኩልነት ለእድገት የምንዘምርበት ግዜ ደርሷል። ህዝቤ ሆይ ወይ ያኔን(ወያኔ) እንደ ቃሪያ ፍሬ አራግፈን እናስወግደው::ነጻነት ፈላጊ ነጻነት ያመጣል።

 
ከ-ከተማ ዋቅጅራ
Email-waqjirak@yahoo.com

የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ሰላማዊ እንቅስቃሴ ደጋፊዎች ህብረት የአቋም መግለጫ

$
0
0

UCMየኢትዮጵያ ሙስሊሞች ሰላማዊ ና ህጋዊ የመብት ማስረከብ ትግል ከጀመረ እነሆ ሶስት አመት አስቆጠረ ለዚህ ሰላማዊ የመብት ትግል መነሻ የሆነው ሙስሊሙ ህብረተሰብ ሶስት ህጋዊ የመብት ጥያቄዎችን ለመንግስት በማቅረብ ምላሽ እንዲሰጣቸው በወከላቸው የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አማካኝነት ከመንግስት ጋር ውይይት ከጀመሩ ቦኋላ መንግስት ከሙስሊሙ ህብረተ ሰብ ለቀረበለት ጥያቄ መልስ ከመስጠት ይልቅ የህዝበ ሙስሊሙን ጥያቄ ይዘው የቀረቡትን ህዝቡ መርጦ የወከላቸው መሪዎቹን አስሮ ጥያቄዎቻቸውን በማዳፈን መልስ ለመስጠት ፈቃደኛ ባለመሆኑ ነበር። --[ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]=—–

ፍትሕ አያረጅም! የኢትዮጵያና የአርሚኒያ ትግል -ኪዳኔ ዓለማየሁ

$
0
0

መግቢያ፤

Justiceኢትዮጵያንና አርሚኒያን ከሚያመሳስሏቸው ጉዳዮች አንደኛው የአንድ ዓይነት የኦርቶዶክስ ሃይማኖት የእምነት መሠረት (ዶግማ) ተከታዮች ያሉባቸው ሐገሮች መሆናቸው ነው። በዚህ ጽሑፍ የማተኩርበት ተመሳሳይነት ግን ሁለቱም ሐገሮች በከባድ የጦር ወንጀሎች ተጠቅተው እያንዳንዳቸው ቢያንስ አንድ ሚሊዮን ሕዝብ የተጨፈጨፈባቸው መሆኑ ነው። ሌላም እጅግ አስጸያፊ ግፍ የተፈጸመባቸው ሐገሮች ናቸው። በተጨማሪም፤ ሁለቱን ሐገሮች ያቀራረባቸው ሌላው ጉዳይ በኦቶማን ዘመነ መንግሥት፤ ከቱርኮች ግፍ በመሸሽ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ መንግሥት መልካም ፈቃድ ወደ ኢትዮጵያ የተሰደዱት 40 አርመኖች ኑሯቸውን በሐገራችን መቀጠላቸው ነው። እነዚህ አርመኖችና ተወላጆቻቸው በኢትዮጵያ ተመቻችተው የኖሩና ብዙዎቹም አማርኛውን ያቀላጥፉ እንደ ነበር የታወቀ ነው። በዚህ አጋጣሚ፤ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አማካኝነት ዱባይ በምሠራበት ጊዜ እዚያ ይኖር የነበረውን፤ ወዳጄን፤አቶ የርቫንትን እያስታወስኩ፤ አርመኖች ያቋቋሟትን ሻርጃ (Sharjah) የምትገኝ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ለኢትዮጵያውያን ምእመናን በማጋራታቸው፤ ውለታቸውን አልረሳውም።

በአርመኖችና በኢትዮጵያውያን ላይ የተፈጸሙት እልቂቶችና የጦር ወንጀሎች፤

በአርመኖች ላይ የተፈጸመው የጦር ወንጀል እ.አ.አ በ1915-23 በኦቶማን (Ottoman) (በኋላ ቱርክ) ዘመነ መንግሥት መገባደጃ ጊዜ ነበር። እንደሚታወቀው፤ በኢትዮጵያ ላይ የተፈጸመው እልቂት እ.አ.አ በ1935-41 በኢጣልያ ፋሺሽቶችና በቫቲካን ያልተቆጠበ ድጋፍ የተከናወነ ነበር። ከላይ እንደ ተገለጸው፤ ሁለቱም ሐገሮች ቢያንስ አንድ አንድ ሚሊዮን ሕዝብ ተጨፍጭፎባቸዋል። በተጨማሪም እጅግ ብዙ አርመኖች ከሐገራቸው እንዲሰደዱ ተገድደው ለከባድ ችግር ተጋልጠዋል። በኢትዮጵያ ላይ የተፈጸመው ግፍ በብዙ የኢጣልያ አውሮፕላኖች በተነሰነሰው የመርዝ ጋዝ እንዲሁም በሌሎች ልዩ ልዩ መሣሪያዎች የተጨፈጨፈው ሕዝብ፤ (በሶስት ቀኖች አዲስ አበባ የተገደሉት 30 000 ኢትዮጵያውያን ጭምር) ብቻ ሳይሆን የወደሙትን 2 000 ቤተ ክርስቲያኖች፤ 525 000 ቤቶችና 14 ሚሊዮን ያህል እንስሶች ያካትታል። በተጨማሪም እጅግ ብዙ ዝርፊያ የተከናወነ መሆኑ የታወቀ ነው።

የአርመኖች ትግል ለፍትሕ፤

በአርመኖች በኩል፤ ከ100 ዓመት በፊት በቱርኮች ለተፈጸመባቸው ወንጀል ተገቢውን ፍትሕ ለማስገኘት ያላሰለሰ ትግላቸውን እየቀጠሉ ነው። መሠረታዊ ዓላማቸውም ያ ከባድ ጥቃት የዘር ማጥፋት ወንጀል (genocide) መሆኑ በዓለም አቀፍ ደረጃ እንዲታወቅላቸው ለማድረግ ነው። በዚህ በፈረንጆች የዘመን አቆጣጠር በ2015 የእልቂቱ መቶኛ ዓመት የሚደፍን በመሆኑ በሰፊው ለመዘከር እቅድ አላቸው። በዚህ ተግባር ከተሰማሩት ውስጥ፤ የአርመን መንግሥት እንዲሁም በአሜሪካ የሚገኙ፤ (ሀ) የአርመን ብሔራዊ ኮሚቲ በአሜሪካ (Armenian National Committee of America) (www.anca.org) እና (ለ) የአሜሪካ አርመናዊ ሸንጎ (Armenian Assembly of America) (www.aaainc.org) ይገኙበታል።

ሰሞኑን በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መማከሪያ (Foreign Affairs Council) በተሰኘው ድርጅት አማካኝነት ታትሞ በወጣው ፎሪን አፌርስ (Foreign Affairs) መጽሔት (January/February 2015)፤ ቶማስ ደ ዋል (Thomas de Waal) የተባለ ዘጋቢ፤(“The G-Word; The Armenian Massacre and the Politics of Genocide”) (ትርጉም፤ የጂ-ቃል፤ ስለ አርመኖች እልቂትና የዘር ማጥፋት ፖለቲካ) በሚል አርእስት የሚከተሉትን ቁም-ነገሮች አቅርቧል፤

(ሀ) እ.አ.አ. በ1918 የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ቲዮዶር ሩዝቬልት (Theodore Roosevelt) በአርመኖች ላይ ስለ ተፈጸመው ስደትና እልቂት አሜሪካ በኦቶማን መንግሥት ላይ ጦርነት ማወጅ አለባት በማለት ሐሳባቸውን በደብዳቤ ገልጸው ነበር።

(ለ) የአርመኖች የፍትሕ ትግል በአሜሪካ መንግሥት መርሆ ላይ ከፍተኛ አጽንኦት አስክትሏል። እ.አ.አ. በ1951 የአሜሪካ መንግሥት ጠበቆች ቱርኮች በአርመኖች ላይ የፈጸሙት እልቂት እንደ የሰው ዘር ማጥፋት ወንጀል (genocide) እንዲታይ ሔግ (The Hague) ለሚገኘው ዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት (International Criminal Court) አመልክተው ነበር። ነገር ግን የተባበሩት መንግሥታት የዘር ማጥፋት ወንጀል ስምምነት (United Nations Genocide Convention) የታወጀው እ.አ.አ. በ1948 ከአርመኖች እልቂት በኋላ በመሆኑ እስካሁን ጉዳዩን ለፍርድ የማቅረቡ ሒደት አልተሳካም።

(ሐ) እ.አ.አ. በ1975 የአሜሪካ ተወካዮች ምክር ቤት (House of Representatives) መሪ፤ ቲፕ ኦኒል (Tip O’Neill) እ.አ.አ. ሚያዚያ 24ን (April 24) የሰውን ልጅ የርስ በርስ ኢሰብአዊነት ብሔራዊ የመዘከሪያ ቀን (National Day of Remembrance of Man’s Inhumanity to Man” ተብሎ እንዲሰየምና በዘር ማጥፋት ወንጀል የተጠቁትን በሙሉ፤ በተለይም እ.አ.አ. በ1915 ለተሰዉት አርመኖች መታሰቢያ እንዲሰየም ሥልጣኑን ለአሜሪካ ፕሬዚዳንት የሰጠበት የውሳኔ መግለጫ አውጥቶ ነበር። ነገር ግን በሌላው የአሜሪካ ምክር ቤት፤ በሴኔት (Senate) የአርመኖችን እልቂት እንደ የዘር ማጥፋት ወንጀል የመቁጠር ጉዳይ ተቀባይነት ሳያገኝ ቀርቷል።

(መ) ፕሬዚዳንት ሬጋንም (President Reagan) በመጀመሪያ በ እ.አ.አ. በ 1981 ለአርመኖች የዘር እልቂት (genocide) እውቅና በመስጠት ገለጻ አድርገው ነበር። ነገር ግን እ.አ.አ. በ1982 ሁለት አርመናዊ ወጣቶች በሎዛንጀለስ ከተማ የቱርክ ቆንስል መሪ የነበረውን ከማል አሪካንን (Kemal Arikan) በመግደላቸው የፕሬዚዳንት ሬጋን አቋም ተለወጠ።

(ረ) የቱርክ መንግሥት ለአሜሪካ ጠንካራ ድጋፍ ከሚያበረክቱት መንግሥቶች አንዱ በመሆኑ በተለይም የሰሜን አትላንቲክ ሐገሮች ድርጅት (NATO) አባል በመሆኑ በአርመኖች ላይ ስለ ተፈጸመው የኦቶማኖች የጦር ወንጀል አሜሪካ ያላት አቋም ተለዋዋጭ ሆነ።

(ሠ) የአሜሪካና የቱርክ መንግሥቶች ባላቸው የጥቅም ቅድሚያ ለአርመኖች የሚገባውን ፍትሕ ለጊዜው ያመከኑት ቢመስልም የአርመን ታጋይ ድርጅቶች የመቶ ዓመት ጥረታቸውን አጠንክረው እየቀጠሉ ነው። ለዚህም በምርጫ መብታቸው እየተጠቀሙ በአሜሪካ የኮንግሬስ አባሎችና በሐገሩ ፕሬዚዳንት ላይ የማያቋርጥ አጽንኦት እንዲከሰት ለማድረግ እየጣሩ ነው። የዚህም ጥረት ውጤት አንደኛው ምሳሌ፤ እ.አ.አ. በሚያዚያ 24 ቀን 2010፤ ፕሬዚዳንት ኦባማ (President Obama) የሚከተለውን ገለጻ ማድረጋቸው በቶማስ ደ ዋል ጽሑፍ ተዘግቧል፤

“1.5 million Armenians were massacred or marched to their death in the final days of the

Ottoman Empire……..The Meds Yeghern (“Great Catastrophe”) is a devastating chapter in the

History of the Armenian people, and we must keep its memory alive in honor of those who

were murdered and so that we do not repeat the grave mistakes of the past.”

(ትርጉም፤ በኦቶማን መንግሥት የመጨረሻዎቹ ቀናት 1.5 ሚሊዮን አርመኖች ተጨፍጭፈዋል ወይም ለሞት

ወደሚዳርጋቸው እንዲጓዙ ተደርገዋል። ታላቁ ሰቆቃ (መቅሠፍት) በአርመኖች ታሪክ እጅግ አሰቃቂ ምእራፍ

ነበር። ያለፈውን ስሕተት እንዳንደግመው ለተገደሉት ሰዎች ክብር የዚያን ዘመን ትዝታ ሕያው አድርገን

 

 

ልናስታውሰው ይገባናል።)

ከዚህ በላይ ከተዘረዘረው መገንዘብ የሚቻለው፤ ምንም እንኳ አርመኖች የሚፈልጉት፤ ማለትም በቱርኮች የተፈጸመባቸው ጭፍጨፋ እንደ የዘር እልቂት ወንጀል (genocide) የማሳወቅ ዓላማ እስካሁን ባይሳካላቸውም ጥረታቸው በከፍተኛ ደረጃ እየቀጠለ የአሜሪካ መሪዎች ጭምር ተስፋ አላስቆረጧቸውም። “የአርመን ብሔራዊ ኮሚቲ በአሜሪካ” ድርጅት የሕዝብ ግንኙነት ዲሬክተር የሆነችውን ወ/ሮ ኤሊዛቤት ሹልድጂያንን (Elizabeth Schouldjian) ሰሞኑን በስልክ አነጋግሬያት አርመኖችና የአርመን መንግሥት ትግላቸውን የሚቀጥሉ መሆኑንና በዓለም አቀፍ ደረጃ በሚያከናውኑት እንቅስቃሴ ከአውሮፓ የሰብአዊ መብት ፍርድ ቤት ጋር ጭምር ጉዳዩን እንደሚገፉበት ገልጻልኛለች።

የኢትዮጵያስ ትግል?

ኢትዮጵያ ለተፈጸመባት እጅግ አሰቃቂ ግፍ ተገቢውን ፍትሕ አላገኘችም። ካሣ ተብሎ ለቆቃ ግድብ መሥሪያ የዋለው $25 ሚሊዮን እና ወደ ሐገሩ የተመለሰው የአክሱም ሐውልት በምንም መስፈርት ብቁ ነው ሊባል አይችልም። ኢጣልያ ለሊቢያ $5 ቢሊዮን፤ ለዩጎዝላቪያ $125 ሚሊዮን፤ ለግሪክ ሐገር $105 ሚሊዮን፤ ለሶቪየት ዩኒየን $100 ሚሊዮን፤ ወዘተ ከተስማማችው ጋር ሲመዛዘንና በተለይም በኢትዮጵያ ላይ ከፈጸመችው ክፍተኛ የጦር ወንጀል ጋር ሲነፃፀር በግልፅ የሚታየው የተዛባ ፍትሕ የሚያስቆጭ ነው። “በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ” እንደሚባለው፤ ኢጣልያ የፈጸመችው ወንጀል አልበቃ ብሏት፤ በቅርቡ፤ የቫቲካን ተወካይ በተገኙበት፤ አፊሌ በምትባል የኢጣልያ ከተማ፤ “የኢትዮጵያ ጨፍጫፊ” በመባል ለሚታወቀው፤ ለሮዶልፎ ግራዚያኒ አንድ መታሰቢያና መናፈሻ ተመርቆለታል። እንደ ኬንያና ኢንዶኒዚያ ያሉ ሐገሮች ከቀድሞ አጥቂዎቻቸው ከእንግሊዝና ከኔዘርላንድስ ተገቢውን ይቅርታ ተጠይቀው ካሣ ጭምር ሲከፈላቸው ኢትዮጵያ የተሟላ ፍትሕ ሊነፈጋት አይገባም። ስለዚህ፤ ዓለም አቀፍ ሕብረት ለፍትሕ – የኢትዮጵያ ጉዳይ (Global Alliance for Justice – The Ethiopian Cause) የተሰኘው ድርጅት ከዚህ በታች ለተዘረዘሩት ዓላማዎች እየታገለ ይገኛል፤

(ሀ) የኢጣልያ መንግሥት ለኢትዮጵያ ሕዝብ ተገቢውን ካሣ እንዲከፍል፤

(ለ) ቫቲካን የኢትዮጵያን ሕዝብ ይቅርታ እንድትጠይቅ፤

(ሐ) የኢጣልያ መንግሥትና ቫቲካን የተዘረፉትን ንብረቶች ለኢትዮጵያ ሕዝብ እንዲመልሱ፤

(መ) የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ፋሺሽት ኢጣልያ በኢትዮጵያ ላይ የፈጸመችውን የጦር ወንጀል

እንዲመዘግብ፤ እና

(ሠ) በቅርቡ ለፋሺሽቱ “የኢትዮጵያ ጨፍጫፊ” ለሮዶልፎ ግራዚያኒ ኢጣልያ ውስጥ በአፊሌ ከተማ፤  የተሠራው

መታሰቢያ እንዲወገድ።

አቤቱታውንም ለሚመለክታቸው ሁሉ፤ ለኢጣልያ መንግሥትና ለቫቲካን፤ ለአውሮፓ ምክር ቤት፤ ለአፍሪካ አንድነት ድርጅት፤ ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት፤ ለፕሬዚዳንት ኦባማና ለሌሎች አንዳንድ የዓለም መንግሥታት መሪዎች፤ እንዲሁም በፍትሕ ለሚያምኑ ሰዎች በሙሉ አቅርቧል። በዚህ አጋጣሚ በየዓመቱ የካቲት 12ን ለመዘከር በ30 ከተሞች በዓለም አቀፍ ደረጃ ለሐገር ፍትሕና ክብር ለሚንቀሳቀሱ ሁሉ ልባዊ ምሥጋና ይድረሳቸው። የኢትዮጵያ አርበኞች ማሕበርም የሚያከናውነው ጥረት ሊጠቀስ ይገባል።

በተጨማሪም፤ በድርጅቱ ድረ-ገጽ (www.globalallianceforethiopia.org) የሚገኝ፤ ቫቲካን የኢትዮጵያን ሕዝብ ይቅርታ እንድትጠይቅ እየተፈረመ ያለ ዓለም አቀፍ አቤቱታ ይገኛል። እስካሁን ክ4200 ሰዎች በላይ ፈርመውታል። ይህንን ጽሑፍ የሚመለከቱ ሁሉ አቤቱታውን እንዲፈርሙት ተጋብዘዋል።

 

 

 

4

ለውድ ሐገራችን ለኢትዮጵያ ስለሚያስፈልገው ፍትሕና ክብር እስካሁን የተከናወነው ጥረት የሚያበረታታ ቢሆንም በውጤት ደረጃ አመርቂ ደረጃ አልደረሰም። በተለይም አርመኖች ለክብራቸውና ለሐገራቸው ፍትሕ ከሚያከናውኑት ትግል ጋር ሲነፃፀር በኛ በኩል ጥረታቻችንን ማጎልበት እንደሚገባን ግልጽ ነው። ስለዚህ ለሐገርና ለፍትሕ የሚቆጭ ሁሉ በትግሉ እንዲሳተፍና እንዲደግፍ ያስፈልጋል። የአገር ወዳዶች የተባበረ ጥረት የትግሉን ውጤት የተሳካና የተፋጠነ ለማድረግ አስተዋፅኦ ይኖረዋል።

ቸሩ የኢትዮጵያ አምላክ ለሐገራችን የሚገባው ክብርና ፍትሕ እንዲገኝ የጀመርነውን ጥረት፤ በሁሉም አገር ወዳድ ተሳትፎ፤ አጠናክረን እንድንቀጥል ብርታቱን ይስጠን። አሜን!

 

 

Hiber Radio: “አንዳርጋቸው በምን ዓይነት ሁኔታ ውስጥ ይህን እንደተናገረ ይታወቃል”–ኤፍሬም ማዴቦ የግንቦት 7 ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ (እና ሌሎችም ዘገባዎች)

$
0
0

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ


የህብር ሬዲዮ ታህሳስ 26 ቀን 2007 ፕሮግራም

ለክርስትና ዕምነት ተከታዮች እንኳን ለብርሃነ ልደቱ አደረሳችሁ !

< ...በአንዳርጋቸው ላይ የተለያዩ የፕሮፖጋንዳ ቪዲዮዎች እንደሚያሳዩ አስቀድመን አውቀናል ።በምን አይነት ሁኔታ ውስጥ እንደተናገረ ይታወቃል። ይሄኛው ቪዲዮ ከዚህ ቀደም አገዛዙ ካሳያቸው ሁሉ መናኛ ነው አስገድደው እንደሚያናግሩት የታወቀ ነው።ይሄ ስርዓት በሰቆቃ የተገነባ ነው...የኢትዮጵያ ሕዝብ ከግንቦት ሰባት እና አብረውት ከሚሰሩት ሁሉ የሚጠብቀው ነገር አለ። የትግላችን የመጨረሻ እርምጃ ላይ ደርሷል...ለጠላታችን ግን መጣንልህ ...>>

አቶ ኤፍሬም ማዴቦ የግንቦት ሰባት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ንቅናቄ የ ዝብ ግንኙነት ሀላፊ የህወሓት አገዛዝ ትላንት በአቶ አንዳርጋቸው ላይ ያሰራጨውን ፊልም ጉዳይ በተመለከተ ከህብር ሬዲዮ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ጠቅሰዋል (ሙሉውን ያዳምጡ)

<... ምርጫው ውስጥ ለመግባት ወይም ላለመግባት አልወሰንም ለምርጫው ግን መስራት ያለብንን እየሰራን እንቆያለን...ያነሳናቸው ጥያቄዎች ባልተመለሱበት ሁኔታ በእኛ በኩል ምርጫ መግባት አለመግባት የሚታሰብ አይደለም። ያነሳነውን ጥአቄ ለማስመለስ የሚከፈለውን መስዋዕትነት ለመክፈል እኛ ቆርጠናል እነሱም....>>

አቶ ግርማ በቀለ የዘጠኙ የፖለቲካ ፓርቲዎች ትብብር ዋና ጸሐፊ የትብብሩን ሁለተኛ ዙር የትግል መርሐ ግብር መተመለከተ ለህብር ከሰጡት ቃለ ምልልስ የተወሰደ(ሙሉውን ያዳምጡት)

<<..የቤቴ ዋጋ ጨምሯል በሚል ተጨማሪ ብድር መውሰድ ብዙ ጊዜ ከጥቅሙ ጉዳቱ ያመዝናል...በዕዳ ብዛት የሚሄዱበትን አጥተው በአጣብቂኝ ራሳቸውን ያጠፉ ኢትዮጵያውያን እኮ አሉ መጠንቀቅ ያስፈልጋል ...>>

አቶ ተካ ከለለ በአትላንታ የቲኬ ሾው አዘጋጅ የቤት ዋጋ ጨምሯል በሚል ስለሚወሰድ ተጨማሪ ብድር የሚያስከትለውን ጥቅምና ጉዳት አብራርተዋል(ሙሉውን ያዳምጡት)

ሌሎችም

ዜናዎቻችን

በአቶ አንዳርጋቸው ላይ የተሰራ የአገዛዙ የፕሮፓጋንዳ ፊልም በራሱ የሰብአዊ ጥሰትን ያሳያል

የጅቡቲ ሰራዊት የኢትዮጵያን ግዛት ዘልቆ መግባቱ የአፋር ተወላጆችን አስቆጣ

አፋሮች የክልሉን ፕሬዝዳንት ለፍርድ ለማቅረብ ዝተዋል

የኤርትራው ፕ/ት ኢሳያስ አፈወርቂ በአገራችን ላይ ጦርነት ታውጆብናል ጠላቶቻችንን እናሸማቅቃለን ሲሉ ዛቱ

ከኢትዮጵያ ስለኮበለሉት ፓይለቶች ዛሬም ዝምታን መርጠዋል

ሕጋዊው ቅዱስ ሲኖዶስ በስሜ የተሰራጨው ህገደንብ የተሳሳተ ነው ሲል አስታወቀ

ኢትዮጵያዊ ደም ያለው ጌዲዮን ዘላለም ለአሜሪካ ብሔራዊ ቡድን በመጫወት የመጀመሪያ ሊሆን ነው ተባለ

በአቶ አንዳርጋቸው ላይ አገዛዙ ይፋ ያደረገው ፊልም የስርዓቱን ኢሰብዓዊ አያያዝ ሊያስተባብል መሞከሩ እንደማይሳካ ተገለፀ

ፊልሙን ተከትሎ ከአገር ውስጥና ከውጭ በማህበራዊ ሚዲያው በስርዓቱ ላይ ተቃውሞው ቀጥሏል

ሌሎችም ዜናዎች አሉ

ዞን ዘጠኝ ጦማርያን እና ጋዜጠኞች ለአስራ አምስተኛ ጊዜ ተቀጠሩ

$
0
0

zone 9

በዛሬው እለት በካንጋሮ ፍርድ ቤት የቀረቡት የዛኦን ዘጠኝ ጦማርያን እና ጋዜጠኞች ከዚህ ሁሉ ኢ-ፍትሃዊ እስር በኋላም ቢሆን ከፊታቸው ላይ ሳቅና ፈገግታን ሊነጠቁ ያልቻሉ መሆኑ በግልጽ ለአምባገነኖች እና አሽከሮቻቸው አሳይተዋል:: በሙሉ ራስ መተማመን ስሜት እና በታላው ብሩህ መንፈሳቸውን ተላብሰው ካንጋሮ ፍርድ ቤት ይደረሱት ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን የአሸናፊነት ስሜት በፊታቸው ይነበባል::ፖሊስ ጉዳዩን የሚከታተሉ እና በፍርድ ቤቱ የተገኙትን ስልካቸውን እንዲያጠፉ ያደረገ ሲሆን በችሎት ክተሰየሙት ዳኛ አንዱ መቀየራቸውም ታውቋል:;እንዲሁም ፖሊስ ያሰራቸውን ጦማርያን እና ጉዳዩን ሊክታተሉ የመጡትን በአይን እንኳን እንዳይነጋገሩ ሲያዋክብ ታይቷል::

በኢሕአዴግ አቃቢ ህግ የተፈበረኩ የሃሰት ክሶች ላይ ቡድን ድርጅት የተባሉት፣የተከሳሾች የሥራ ድርሻ እንዲሁም የ48ሺህ ብር ጉዳይ አልተሻሻሉም ከተባሉት ክሶች ውስጥ ተካተዋል።በተጨማራም የተለያዩ ስልጠናዎችን ወስደዋል የተባለው በዝርዝር እንዲቀርብ አዟል። ከዚህ ውጪ ያሉ የክስ ማሻሻያዎች ተቀባይነት አግኝተዋል። ፍርድ ቤቱ አልተሻሻሉም ብሎ የጠቀሳቸው አራት ነጥቦች በድጋሚ ተሻሽሎ እንዲቀርብ ለጥር 6 ቀጠሮ ሰጥቷል። (ምኒልክ ሳልሳዊ እንደዘገበው)


የግንቦት 7 ሕዝብ ግንኙነት አቶ ኤፍሬም ማዴቦ ስለ አዲሱ የአንዳርጋቸው ቪዲዮ ተናገሩ (ያድምጡ)

$
0
0

የግንቦት 7 ለፍትህና ለዲሞክራሲ ንቅናቄ የ ዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ ኤፍሬም ማዴቦ የህወሓት አገዛዝ በአቶ አንዳርጋቸው ላይ ያሰራጨውን ፊልም ጉዳይ በተመለከተ ከህብር ሬዲዮ ጋር ቃለ ምልልስ አድርገዋል:: ያዳምጡት::

< ...በአንዳርጋቸው ላይ የተለያዩ የፕሮፖጋንዳ ቪዲዮዎች እንደሚያሳዩ አስቀድመን አውቀናል ።በምን አይነት ሁኔታ ውስጥ እንደተናገረ ይታወቃል። ይሄኛው ቪዲዮ ከዚህ ቀደም አገዛዙ ካሳያቸው ሁሉ መናኛ ነው አስገድደው እንደሚያናግሩት የታወቀ ነው።ይሄ ስርዓት በሰቆቃ የተገነባ ነው...የኢትዮጵያ ሕዝብ ከግንቦት ሰባት እና አብረውት ከሚሰሩት ሁሉ የሚጠብቀው ነገር አለ። የትግላችን የመጨረሻ እርምጃ ላይ ደርሷል...ለጠላታችን ግን መጣንልህ ...>>
የግንቦት 7 ሕዝብ ግንኙነት አቶ ኤፍሬም ማዴቦ ስለ አዲሱ የአንዳርጋቸው ቪዲዮ ተናገሩ (ያድምጡ)

የወልቃይትን መሬት በተመለከተ በብአዴን አመራሮች መካከል አለመግባባት ተፈጥሯል

$
0
0

ሁኔ አቢሲኒያ

Photo File

Photo File

ከ1983 ዓ.ም ጀምሮ የአማራ ህዝብ መሬት በግፍ እየተቀማ ለትግራይ ነዋሪዎች ከትግራይ ህዝብም ለህወሀት ደጋፊዎች መከፋፈሉ ይታወሳል ይህንን ተከትሎ ላለፉት በርካታ አመታት የራያ፣ የሁመራ እና የወልቃይት ህዝብ ለስደት እና ለጥፋት የተዳረገ ሲሆን ከሰሞኑም የትግራይ ክልልን ለማስፋፋት በተደረገው ጥረት ተቃውሞ ያሰሙ የክልሉ ነዋሪዎች ለድብደባ እና ለእስር መዳረጋቸውን ተከትሎ የአካባቢውን ህዝብ ለማነጋገር ወደስፍራው አቅንተው የነበሩት አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ከፍተኛ ተቃውሞ ድርሶባቸው ወደባህርዳር መመለሳቸውን ተከትሎ በዛሬው እለት ከፍተኛ የብአዴን አመራሮች እና የክልሉ ባለስልጣናት በጉዳዩ ላይ ለመወያየት ከቀኑ 4 ሰዓት ጀምሮ ባህር ዳር የክልሉ መስተዳደር የስብሰባ አዳራሽ ተገኝተው የነበረ ቢሆንም ስብሰባው ባለመስማማት እስከ 6፡30 ከተካሄደ በኋላ ተሰብሳቢው የተባለው መሬት የአማራ መሬት ነው የሚል አዝማሚያ በማሳየቱ ከፍተኛ ብስጭት ውስጥ የገቡት አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ከምሳ በኋላ ስብሰባው ሲጀመር ከፌዴራል መንግስት መመሪያ መምጣቱን ተናግረው የሚቀጥለው ቅዳሜ ጥር 2 በአቶ አዲሱ ለገሰ እና በአቶ በረከት ስምኦን ሰብሳቢነት ስብሰባው ከእንደገና እንደሚካሄድ ተናግረው ስብሰባውን በትነውታል።

ይህንን ዜና ከባህር ዳር ያደረሰኝ ግለሰብ እንዳረጋገጠልኝ ከሆነ የወልቃይት መሬት ጉዳይ የክልሉን ካድሬ ቁጭት ውስጥ እንደከተተው የታወቀ ሲሆን ቅዳሜ የሚፈጠረውን ጉዳይ ለመገመት አስቸጋሪ መሆኑን ጨምሮ ገልጿል።

ሰው በላውን ወያኔን እናጠፋዋለን!!! -ከ-አዲስ ብርሃኑ

$
0
0

 ከ-አዲስ ብርሃኑ

andargacew Tsigeአንዳርጋቸውን ሳስበው ውስጤ ያለው የኢትዮጵያዊነት ወኔ ይቀጣጠልብኛል። ብርሃን ካለ  ጨለማ  የለም ብርሃን ከሌለ ግን ጨለማ አለ። አንዳርጋቸው ማለት ለኢትዮጵያዊያን በሙሉ ብርሃን ማለት ነው። የለኮሰው ብርሃን በኢትዮጵያ በሙሉ የሚበራ ብርሃን ነው። አንድአርጋቸው በኢትዮጵያ የለኮሰው ብርሃን የሰላም ብርሃን ነው፣ የፍቅር ብርሃን ነው፣ የቆራጥነት ብርሃን ነው፣ የጀግንነት ብርሃን ነው፣ የአንድነት ብርሃን ነው፣ የትግል ብርሃን ነው። በዚህ ብርሃን ውስጥ የማይጓዝ ማንም ኢትዮጵያዊ የለም። አንድአርጋቸው የኢትዮጵያ ብርሃን!!!የእውነት ብርሃን ጥቅም ያለወጠህ ብርሃን የለኮስከው የነጻነት የትግል ሻማ አንተ ሻማ ሆነህ እየቀለጥክ ብርሃንነትን የለበስክ የኢትዮጵያ ብርሃናዊ ጀግና  አንተ  ነህ።

ወያኔ የፈራው ስራህን ብቻ ሳይሆን ስምህንም ጭምር ነው። አንድነት ለወያኔ አይመቸውም አንድነትን ይፈራል ህብረትን ይጠላል ለያይቶ እና ከፋፍሎ መግዛትን ነው የሚፈልገው። ስለዚህ አንድአርጋቸው ሲባል ያባንነዋል።ወያኔ ለዘረፋው አንድነት አይመቸውም ለተንኮል ስራው አይመቸውም ስለዚህ እንኳን ስራህን ስምህንም አይወዱትም። በኢትዮጵያዊያን ግን ስምህም ተግባርህም ይወደዳል። እዚህ ጋር ነው ቁም ነገሩ በህዝብ መወደድ እና መከበር። የኢትዮጵያ  ህዝብ የሰላም ብርሃን የለኮሱትን እና ወደ ብርሃን የሚወስዱትን ብርቅዬ ታጋይ በማይጠፋው በኢትዮጵያዊ መዝገብ ውስጥ ጽፈው ያስቀምጧቸዋል ። ወያኔ እና ከነግብርአበሮቹ ግን ከነስራቸው ይጠፋሉ።

ስለ አንዳርጋቸው ጽጌ የተለቀቀውን ቪዲዮ አይቼ በጣም ነውያፈርኩት በቪዲዮ መግቢያው ላይ ምዕራባዊያን የእስር አያያዝ ላይ ትችት ሲያቀርቡ ኢትዮጵያ  ውስጥ ግን የእስረኛ  አያያዝ በሰላም እንደሆነ እጅ እጅ ያለውን ወሬአቸውን በተለመደ የውሸት ቋንቋቸው ዛሬም ሲደግሙት አይናቸውን በጨው አጥበው በመቅረብ አንዳርጋቸው የሚናገረው ንግግር እራሱ ፈልጎ እንደሆነ አድርጋችሁ አቀረባችሁ። ቪዲዮው ስንመለከት ግን 14 ደቂቃ ባልሞላች ንግግር ውስጥ የአንድአርጋቸው የለበሰው ልብስ በየደቂቃው የቀያየራል ቪዲዮው በየደቂቃው ይቆራረጣል ይበጣጠሳል በዛ ላይ የተላለፈው መልእክት ምን እንደሆነ የማይገባ። ይህንን ቪዲዮ እንደ ኢትዮጵያዊ ሆኜ ሳስበው  በጣም አሳፋሪ ነው እንደ  ወያኔ አውሬነት ሳየው ደግሞ የምጠብቀው ስለሆነ አይደንቅም የሚገርመው  የካድሬዎች ጫጫታ ነው ተንጫጩ እኮ ወይ መንጫጫት በዚህ ዘምን የሚታለል ወይም የወያኔን ስራ የማያውቅ ማንም ኢትዮጵያዊ የለም ኢትዮጵያ  ውስጥ የመንግስት አቸባሪ ነው ያስቸገረው። አንዳርጋቸው የለኮሰው የትግል ብርሃን ወያኔን ጥሎ  ካልሆነ  በስተቀር መቆሚያ  የለውም።

ወያኔ የአንድአርጋቸውን  ጽጌ ቪዲዮ የለቀቀው ግራ  ገብቶት ነው ወያኔ ሲጨንቀው ሲጨንቀው ማስተንፈሻ ይፈልጋል ሰሞኑን 3ት የአየር ሃይል አብራሪዎች ከነ ሄልኮፕተር ወደ ኤርትራ መግባታቸው ወያኔን መካዳቸው ያስደነገጠው በተጨማሪም 4ት የአየር ሃይል የተዋጊ አብራሪዎች ወደ ኬኒያ መግባታቸው እና የመከላከያ ሰራዊት ከነ ትጥቁ እየከዳቸው ስለሆነ የመውደቂያው ዋዜማ  ላይ መሆኑን ስላወቀው ስለደነገጠ ማስተንፈሻ ስለፈለገ የህዝቡን ሃሳብ ለመበተን በጣም አሳፋሪ እና የተቆራረጠ በዛ ላይ ሃሳቡ ግልጽ ያልሆነ  ቪዲዮ ለመልቀቅ ተገደዋል። አሁን ወያኔ  በሚደሰኩረው ዲስኩር ዲስኩር ተታሎ ግዜ ሰጥቶ የሚያወራ ቢኖር ወያኔ እና ካድሬዎች ብቻ ናቸው። እኛ ግን አንዳርጋቸው በለኮሰው የብርሃን የትግል ጉዞ ተጉዘን ወያኔን ለመደምሰስ ቆርጠን ተነስተናል። ወያኔ ሆይ አሁን የዘራኽውን ማጨጃህ ሰዓት ላይ ነህ። የኢትዮጵያ ህዝብ የተገደለበት የቆሰለበት የተደበደበበት የተሰደደበት የተረገጠበት የተናቀበት ግዜ አብቅቶ ኢትዮጵያዊው ቁጭቱን ለከፍል ቆርጦ ተነስቷል። ህዝብ ያቸንፋል ወያኔ እና ካድሬዎች ለአንደ እና ለመጨረሻ ግዜ ይጠፋሉ።

ድል ለኢትዮጵያዊያን!!!

ከ-አዲስ ብርያኑ

የማለዳ ወግ … ሰሚ እስኪገኝ እያነባን እንጮሃለን ! – ነቢዩ ሲራክ

$
0
0
የማለዳ ወግ … አፈ ጉባኤ አባ ዱላ …ግን ለምን አልሰሙንም ?

* የኮንትራት ሰራተኛዋ አይነ ብርሃኗን ማጣትና የስም የለሿ ሟች እህት መጨረሻ   !
*  ሰሚ እስኪገኝ እንጮሃለን  !

saudiwታህሳስ 27 ቀን 2007 ዓም ሰኞ በማለዳው ያገኘኋቸው ሁለት መረጃዎች የወጡት በሁለቱ አንጋፋ የሳውዲ ጋዜጦች በአረብ ኒውስ Arab News  እና በሳውዲ ጋዜት Saudi Gazette  ነው ። በአንዱን አይቸ ቢከፋኝ ፣  መፍትሔ ላይገኝ ይህን መርዶ ከንፈር ለማመስመጠጥ  ብቻ መረጃ ብየ ልለጥፍ ይሆን ?  እያልኩ ከራሴ ጋር ሙግት ገጥሜ ነፍሴን ሳስጨንቀት በሌላኛው ጋዜጣ የወጣውን ሌላ መረጃ አንድ ወዳጀ በጓዳው የመልዕክት መሰረጫ እንደኔው ማልዶ ያጋጠመውን የወገን መከራ አደረሰኝ ። ሁለቱንም አሳዛኝ መረጃዎች ተመለከትኳቸው ፣ ያማል ብቻ ተብሎ የሚታለፍ አይደለም  !

     sau-wo-300x213መዲና የተባለች እህት በጽዳት ላይ እያለች አይኗ ላይ ተፈናጥሮ የገባው መርዝ የአይን ብርሃኗን አሳጥቷት በከፋ አደጋ ላይ ወድቃለች  ፣ ሴት አሰሪዋ መዲናን ለማሳከም ደፋ ቀና ቢሉም ለህክምና የተጠየቀው ወጭ ለአቅማ ቸው በላይ በመሆኑ ነገሮች የተወሳሰቡ መሆኑ ተጠቁሟል መረጃው የሳውዲ ጋዜጥ ነው  …. !  መረጃውን በፊስ ቡክ ካሰራጨሁት በኋላ ለማጣራት ሞክሬ እንደተረዳሁት ስትታመም ስትጎዳ ሊያሳክሙ ፣ በአሰሪና ሰራተኛ ህግ ከለላ በጅዳ ቆንስል የመጣችው እህት ጉዳዩዋን የሚከታተልላት ቀርቶ የመዲናን ለዚህ አደጋ መጋለጥ የሚያውቅ የመንግስት ተወካይ የለም  !
    ሌላዋ እህት የሆነችውን አረብ ኒውስ በአንዲት የጋዜጣው ጠርዝ ካይ እንዲህ ሲል በአጭር አረፍተ ነገር አስፍሮታል ” ኢትዮጵያዊ የቤት ሰራተኛ አል ጀውፍ በተባለ የሃገሪቱ ግዛት በአሰሪዋ ቤት ራሷን በመስቀል ራሷን በራሷ ገድላለች “ይላል  …መረጃው የአረብ ኒውስ ነው  …. !   ስለዚህች እህትም ቢሆን በአቅራቢያው ያለው የሪያድ ኢንባሲ መረጃ የለውም  ፣ መረጃውን ቀድመው ይወቁት አልልም ፣ ቢያንስ ከእኛ እኩል በየጋዜጣው የሚወጣውን እንኳ አለማወቃቸውን እኩለ ቀን ላይ ወደ ሪያድ ኢንባሲ ደውየ ለማወቅ ችያለሁ  ! ሁሉም ያማል  !
ከሳምንት በፊት እኔ ከምኖርበት ጅዳ ከተማ ልጆችን ወደ ት/ቤት በማድረስ ላይ እያለች በተፈጠረ መኪና ግጭት የያዘቻቸውን ህጻናት አትርጋ እሷ መስዋዕትነት የከፈለችን ትጉህ እህት ያዩ አረቦች ተገርመው በምትሰራበት ቢተ ሲጫወቱ የሰማች እህት ታሩኩን በደፈናው ብትነግረኝም ዝርዝር መረጃ አለነበረውምና በዝምታ አልፊው ነበር።  ዛሬ እኩለቀን ላይ ከላይ የጻፍኩትን የሁለቱን ጋዜጦች መረጃ የተመለከተ ወንድም አንዲህ የሚል መልዕክት ደረሰኝ ይህን “ሄሎ ነብዩ ሰላም ነህ ነብዩ በአንድ ጉዳይ ፈልጌህ ነበር
ስልክህን  ልትልክልኝ በትህትና እጠይቃለህ በጣም የማከብሪህ  እና ማደንቅህ …” ይላል ፣ አመስግኘ ስልኬን ሰጠሁት ፣ ምሽቱን ደውሎልኝ ከባድ የመኪና አደጋ ደርሶባት ራሷን የማታውቀውን እህት ጉዳይ አንስቶ በዝርዝር አጫወተኝ ፣ ይህች እህት ያን ሰሞን የአሰሪዎቿን ልጆች አትርፋ መኪናው የዳጣት ለመሆኗ ብዙ መሄድ አላስፈለገኝ። ከወዳጀ ጋር ይህችን ምንዱብ የአልጋ ቁራኛ ለማየት ቀጠሮ ብንይዝም አልስቻለኝምና ወደ ተባለው ሆስፒታል ሄጀ የማትሰማ የማትናገረውን እህት አይቻት ሰላሜን በገዛ እጀ አጥቸ ተመለስኩ  !
    ማለዳ በሰማሁት ባነበብኩት ምሽት  ላይ ባየሁት ውስጤን  ጥሩ ስሜት አልተሰማው ምና ከንዴት በሽታ ውጭ ምንም ላላመጣ በስጨት አልኩ  ፣ ዝም ማለት ግን አልለመደ ብኝምና እናገረዋለሁ  !  … ደግሞ ብስጭቴን ስጽፈው ይቀለኛልና መቸክቸክ ያዝኩ …
ሰሚ ያጣ ጩኸት …
    መረጃ ማቀበሉ በህግ አስፈጻሚ አካላት በኩል ውጤት አለማምጣቱን አሰላስየው የአፈ ጉባኤ አባ ዱላን ሰሞነኛ የሳውዲ ጉብኝትና መፍትሔ እንደማያመጡ እያወቀ እንደኔው ባለመተንፈሱ የተበሳጨውን የጅዳና የሪያድ ነዋሪ አስታወስኩ ! ከምንሰማ ከምናየው የዜጎች አበሳ ጋር ሰሚና ሁነኛ የመብት አስከባሪ የበላይና የበታች ሹማምንት አጥተን በስቃይ ላይ ለመሆናችን ምስክሮች የምናቀርባቸው መረጃዎች ናቸው ። በሳውዲ 350 ሽህ የኮንትራት ሰራተኛ እንዳለ በመንግስት ተረጋግጦ እየተነገረን ፣ የተበተኑት መብት ሳይጠበቅ አዳዲስ መከረኞችን አምጥተን ልንደፋ  ዝግጅቱ የተጠናቀቀ ይመስላል ።  እኛ ይህ ነገር በተቀናጀ ጥናት፣ በበቂ ዝግጅት ፣ በበሳል አመራር  ካልተመራ ሌላ አደጋ አለው እያልን ነው ።  መከራ ብሶቱን ፣ አሰከፊ ምስሉን እያሳየን ” አረ ያገር ያለህ !”  እያልን እጮህን ነው  ! ሰሚ ህግ አውጭና ህግ አስፈጻሚ ግን የለም  ! ሰሚ ያጣው ጩኸታችን ሰሚ እስኪገኝ ግን ዝም አንልም ፣ እንጮሃለን  !
ግን ለምን አልሰሙንም ?

የተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ በሳውዲ አረቢያ ጉብኝት አድርገዋል። የሰራተኛ ሚኒስትር አድል ፈቂን ጨምሮ በርካታ የመንግስ ሃላፊዎች አግኝተው እኔና መሰሎቸ ሌት ተቀን ስለምንናገረው በቂ ዝግጅት ሳይደረግ ስለተላኩ የእኛ ዜጎች ለአባ ዱላ ነግረውልናል ።  አፈ ጉባኤ አባ ዱላ በኮንትራት ሰራተኞች ጉዳይ ከሳውዲዎችና መብታችን ካላስጠበቁልን የሪያድ ኢንባሲና የጅዳ ቆንስል ሃላፊዎች ፣ በሃላፊዎች  ከተመረጡ  የሪያድ የጅዳ “የተከበሩ ምርጥ” ዜጎች ፣  ከኢህአዴግ የድርጅትና ከተለያዩ ጥሪ ከተደረገላቸው የ ማህበር አባላት ጋር  መክረዋል።

አፈ ጉባኤውና ልዑካኑ በአንጻሩ በማህበራዊ ኑሮው ፣ በመብት ጥበቃው ፣ በኮንትራት ሰራተ ኞች የለት ተለት የመረረ እውነት ተመልካችና ገፋች የሆነውን ነዋሪ ጠርተው ቀርቶ ሊያይ ሊያነጋገራቸው ሄዶ በሆድ አደር አጋፋሪዎች ተከልክሏል። ነዋሪ ዜጋው እንዲህ ተገፍቶ  የሃገሪቱ የበላይ ህግ አውጭ የሆነው የተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ሳያዩትና ሳያነጋግሩት ሔደዋል ። የአፈ ጉባኤ አባ ዱላን ማግኘትና ብሶቱን ማሰማት የፈለገው ነዋሪ ጉጉት ምን ይሆን ? ብየ ጠያይቄም ነበር ። ያገኘሁት የምላሽ እውነታ ነዋሪው ማቆሚያ ስለጠፋው የኮንትራት ሰራተኞች አበሳ ለመናገር መተንፈስ እንጅ መጓጓቱ መፍትሔ ከባለስልጣኑ ይገኛል ብሎ አለመሆኑን ተረድቻለሁ።  እውነት ነው አባቶች  ” ድሃ በህልሙ ቅቤ ባይጠጣ… ” እንደሚሉት ሆነና  ነዋሪው ሆየ ብሶቱን ማሰማቱ ህመሙን ያቀልለት መስሎታል  ! ፕሬዚደንትና ጠቅላይ ሚኒስትሩን ጨምሮ እስካሁን ሳውዲ ለመጡት ከፍተኛ ባለስልጣኖች የአለ የሌለ የተባለውን ጥያቄ አቅርቦ ምልስ እንዳልተገኘ አሳምሮ የሚያውቀው ነዋሪ በዚህና በዚያ ተስፋ  ቆርጧል… ግን ተስፋ ቆርጦም መናገር መተንፈስ ይፈልጋል !

የአስፈሪው ቀን መቅረብ  ምልክቶች …

በሳውዲ መንግስት የተዘጋው የኮንትራት ሰራተኞች ይጀመራል ተብሎ በዋና ዋና ደላሎች ወሬው ከተነዛ ወዲህ በመንግስት በኩል የረቂቅ ደንቡ መውጣቱን ሰምተናል ። ጸድቆ ጉዞው ሊጀመር ተቃረበ ሲሉን ደግሞ አፈ ጉባኤ አባ ዱላ ገመዳ ከሳውዲ ባለስልጣነናት ጋር ስለአዲሱ ረቂቅ ህግ መምከራቸውን ሰምተናል ! ከሳውዲዎች ጋር   ስለመከሩ ስለዘከሩበት ህግ በሳውዲ ነዋሪ ከሆነው ኢትዮጵያዊ ጋር አለመምከራቸው ግን ታላቅ ታሪካዊ ስህተት ነው ባይ ብዙ ነን  !  ነዋሪው ብሶቱን ለመናገርም ሆነ ከመምከር መወያየቱ የሚገኝ ፋይዳ አለ ብሎ ሳይሆን እንደ ተወካዮች ምክር ቤት ከፍተኛ ባለ ስልጣን ለምን ዜጎችን እኩል አይተው አላነጋገሩንም ? ሃሳባችን ለምን አያደምጡትም? ለምን አልሰሙንም ?  ለምን የታመቀ ችግራችን ቢያንስ አላዳመጡንም  ? በኦሮሞ ልማት የተመረጡ አባላት ሰብስበው ለቴሌቶን ብር ከመሰብሰብ በስደት ስላለው ስለከፋው ዜጋ መምከር ለምን አለቀደመም?   አፈ ጉባኤ አባ ዱላ  እንደ ኢትዮጵያ የተወካዮች ምክር ቤት ሳውዲን እየጎበኙ ለምን ወደ ዘውግ አድልተው ወርደው ጊዜን ማባከብ አስፈለጋቸው? በጉብኝታቸው ሁሉንም ባንድ የኢትዮጵያ ባንዴራ ማሰተባሰበርና ማመካከር ሲገባ ቅድሚያ ለኦሮሞ ማህበር ከዚያን የኢህአዴግ አደረጃጀት እያሉ ስደተኛውን ከመበታተንና በማዕከላዊነት ያልተማከለ ፣በዘውግ አስተዳደር የከረረ  አካሄድን እንድናይ ለምን አደረጉ?   አፈ ጉባኤ አባ ዱላ ከምንም በላይ በሁለት ሃገራት የሰራተኛ ውል ማዕቀፍ ውጭ ወደ ሳውዲ የመጡና  እንደ ጨው የተበተኑትን የኦሮሞ ፣የአማራ፣ የትግራይ ፣ የጉራጌ እና የቀሩትን ብሔረሰቦች የአብራክ ክፋዮች ሁኔታ ለመረዳት የጉዳዩ ባለቤትና መከራውን ገፋች ነዋሪውን አላነጋገሩትም።  መፍትሔው  መብታችን ማስከበር ቀርቶ ዜጎች ያለንበትን ሁኔታ መሸፋፈን ከሚቀናቸው ከቆንስልና ከኢንባሲ ተወካዮች እስከ ድርጅትና ማህበራት ያሉትን”ምርጥ ” የተባሉ ነዋሪዎች ማነጋገር መፍትሔ ነውን ?  አፈ ጉባኤ አባ ዱላ ነዋሪውን በነቂስ ጠርተው በመሰብሰብ ለምን ስለመጡበት ጉዳይ ማብራሪያም ሆነ የነዋሪውን ሃሳብ አልወሰዱም ?  የሚሉ በርካታ ውሃ የሚያነሱ እውነት ያላቸው ጥያቄዎችን ነዋሪው ሲያሰማ አድምጫለሁ ! እኔም ሆንኩ ነዋሪው በእስካሁኑ ሂደት ያየነው ለውጥ ኑሮ ባያስደስተንም ባለስልጣን በመጣ በሄደ ቁጥር ድመጻችን ይሰማ ዘንድ እንሻለን ፣   የለውጥ ተስፋ ባይታየንም የወገናችን አበሳ ግን መናገር አናቆምም  ! አዎ  ! ሰሚ እስክናገኝ እንጮሃለን  !

እስኪ ቸር ያሰማን  !

ነቢዩ ሲራክ
ታህሳስ 27 ቀን 2007 ዓም

ያለፈው ሥርዓት “አስማተኛ” ሳይሆን አይቀርም!

$
0
0

tplfእኔ የምላችሁ ግን … ኢህአዴግ ሥልጣን ከያዘ ስንት ዓመቱ ነው? ይሄንን ቀላል ጥያቄ የምጠይቃችሁ ወድጄ እንዳይመስላችሁ፡፡ ግራ ቢገባኝ ነው፡፡ ሌላም ጥያቄ አለኝ – ያለፈው ሥርዓት ከተገረሰሰ ምን ያህል ጊዜ ሆነው? (ውዥንብሩ መጥራት አለበት!) አንዳንዴ ያለፈው ሥርዓት “አስማተኛ” ይመስለኛል፡፡ ለምን መሰላችሁ? አንዳንድ ሰዎች አሁንም ከ24 ዓመት በኋላ እንኳን ስለሱ ማውራት አልተዉም፡፡ ለሁሉ ነገር ያለፈውን ሥርዓት ካልጠሩ አይሆንላቸውም – በተለይ የኢህአዴግ ካድሬዎች፡፡ (ፍሬሾቹን ማለቴ ነው!)

ሰሞኑን EBC ባቀረበው የዜና ዘገባ ላይ “…የሴቶች ጥቃት ያለፈው ሥርዓት ችግር ስለሆነ እንታገለዋለን…” (really?!) የሚል ነገር የሰማሁ መሰለኝ፡፡ እውነቱን ልንገራችሁ አይደል … ራሱ ኢህአዴግም እንኳን የሴቶች ጥቃት “ያለፈው ሥርዓት” ችግር ነው አይልም፡፡ እንዲያ ካለማ— ያለፈው ሥርዓት አልተገረሰሰም ማለት ነው፡፡ ወይም ደግሞ እንዳልኩት “አስተማኛ” ነው፡፡ (መቃብር እየፈነቀለ የሚወጣ!)
ይሄውላችሁ — በሴቶች ላይ የሚፈፀሙ ጥቃቶች ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በዓይነትም በመጠንም እየጨመሩ ለመምጣታቸው ከፖሊስ ፕሮግራም የበለጠ ማስረጃ የለም፡፡ (የሴቶች መብት ተሟጋቾችም ምስክር ናቸው!) አስገድዶ መድፈር፣ አሲድ መድፋት፣ ከባድ ድብደባና የአካል ማጉደል እንዲሁም አሰቃቂ ግድያዎች…በእጅጉ በርክተዋል፡፡ (ሰብዓዊ ልማት ተዘንግቷል!)

እናም— የሰሞኑ የEBC ዘገባ blame shifting (“የእምዬን ወደ አብዬ”) እንጂ ሌላ ሊሆን አይችልም፡፡ ሃቁን እንነጋገር ከተባለ — የሴቶች ጥቃት “ያለፈው ሥርዓት” ችግር ሳይሆን የእኛው የራሳችን ችግር ነው፡፡ (የኋላ ቀርነት፣ የትምህርት አለመስፋፋት፣ የግንዛቤ ማነስ፣ የአመለካከት ችግር ወዘተ…) ነገርዬው እምብዛም ከስርዓት ጋር የሚያያዝ አልመሰለኝም (ፖለቲካ እኮ አይደለም!) የግድ የሥርዓት ችግር ነው ከተባለም ባለቤቱ የአሁኑ ሥርዓት ነው፡፡ እናሳ? … እናማ በሴቶች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን ወዳለፈው ሥርዓት ለማሻገር ከመታተር ይልቅ እውነታውን ተቀብሎ ለመፍትሄ መትጋት ይሻላል፡፡ (ያለፈው ሥርዓት ከበቂ በላይ የራሱ ኃጢያቶች እንዳሉት አንዘንጋ!!)

ይሄውላችሁ —– እንኳንስ በቅርብ ዓመታት እየተባባሰ የመጣው “የሴቶች ጥቃት” ይቅርና በእርግጥም ካለፈው ሥርዓት የተወረሱ ናቸው የሚባሉት (እነ ድህነት፣ ሙስና፣ የስልጣን ጥመኝነት፣ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት፣ የነፃነት አፈና፣ የፍትህ መጓደል ወዘተ…) ቢሆኑም እንኳ — 20 ዓመት ስላለፋቸው ውርስነታቸው አብቅቷል፡፡ (ከአባት የተወረሰ ንብረትም እኮ ለዘላለም በውርስነት አይጠራም!) ከምሬ እኮ ነው… ከአሁን በኋላ ችግሮችን ባለፈው ሥርዓት ማሳበብ ራስን ለትዝብት ማጋለጥ ነው፡፡

በመጨረሻ አንድ ሃሳብ ላቅርብ፡ ከፆታዊ ጥቃቶች አንዱ የሆነው አስገድዶ መድፈር፣ ለምን በፀረ ሽብር ህጉ ውስጥ አይካተትም? ይሄ እኮ… ሥርዓቱን ወይም ህገመንግስቱን በኃይል ለመናድ ከመሞከር ፈፅሞ አይተናነስም፡፡ ሴቶች ላይ ጥቃት መፈጸም – ቤተሰብን — ህዝብን — መንግስትን —- አገርን — ማሸበር ነው!!

Politica Befegegta

ተመስገን ደሳለኝን ጨምሮ ዝዋይ የታሰሩ 16 የፖለቲካ እስረኞች ጠያቂና ምግብ እንዳይገባላቸው ተከለከሉ

$
0
0

ነገረ ኢትዮጵያ

• የሰማያዊ ወጣቶችና የነገረ ኢትዮጵያ ባልደረባ እንዳይጠይቁ ተከልክለዋል

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝን ጨምሮ በዝዋይ የፌደራል ማረሚያ ቤት ታስረው የሚገኙ 16 የፖለቲካ እስረኞች ባልታወቀ ምክንያት ጠያቂና ምግብ እንዳይገባላቸው ተከለከሉ፡፡

temesgen1ዛሬ ታህሳስ 28/2007 ዓ.ም የሰማያዊ ፓርቲ ወጣቶችና የነገረ ኢትዮጵያ ም/ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ በላይ ማናዬ የገናን ዋዜማ ዝዋይ ከሚገኙ እስረኞቹ ጋር ለማሳለፍ ከአዲስ አበባ ተነስተው ወደ ዝዋይ አቅንተው የነበር ቢሆንም ሊጠይቋቸው ያስጠሯቸው የፖለቲካ እስረኞች ‹‹በማንኛውም አይነት ሰው መጠየቅ አይችሉም፡፡ ምግብም አይገባላቸውም፡፡›› ተብለው ሳይጠይቁ ለመመለስ ተገደዋል፡፡

ጠያቂዎቹ ‹‹የመጠየቅ መብት አለን›› በሚል ወደ ውስጥ ለመግባት ግፊት በማድረጋቸው ፖሊሶች ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፣ ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ፣ አበበ ቀስቶ፣ ናትናኤል መኮንን፣ በቀለ ገርባ፣ ጄኔራል አሳምነው ጽጌና ጀኔራል ተፈራ ማሞን ጨምሮ ጠያቂና ምግብ እንዳይገባላቸው የተከለከሉትን የ16 የፖለቲካ እስረኞችን ስም ዝርዝር አሳይተዋቸዋል፡፡

የሰማያዊ ፓርቲ ወጣቶችና የነገረ ኢትዮጵያ ባልደረባ ለእስረኞቹ ምግብና ጠያቂ እንዳይገባ የተከለከለበትን ምክንያት ለማጣራት ቢሞክሩም ፖሊሶች ‹‹የሚጣራ ነገር ስላለ ነው፡፡ እሱ እየተጣራ ነው፡፡›› ከማለት ውጭ ምክንያቱን በግልጽ ሊነግሯቸው አልቻሉም፡፡

ክልከላው እስከመቼ እንደሚቆይ በውል የታወቀ ነገር የሌለ ሲሆን ከአዲስ አበባ ተነስቶ የገናን በዓል ዋዜማ ከእስረኞቹ ጋር ለማሳለፍ ወደ ዝዋይ ካቀናው የሰማያዊ ፓርቲ ልዑክ በተጨማሪ የእስረኞቹ ቤተሰቦችም በክልከላው ምክንያት ሳይጠይቁና ምግብ ሳያስገቡ ተመልሰዋለል፡፡

የአንደርጋቸው ፅጌ አስገራሚ መልዕክት ከማይታወቀው እስር ቤት

$
0
0

ከእያስፔድ ተስፋዬ

ትናንትና በኢትዮጲያ ቴሌቪዥን በፖሊስ ፕሮግራም ላይ ተቆርጦ ተቀጥሎ የተላለፈው የአንዳርጋቸው ፅጌ ድንቅ የትግል ጥሪ መልዕክት ለሊቱን ሙሉ ሲደንቀኝ ነው ያደረው፡፡ ኢቲቪ በነካካ እጇ ያልተቆራረጠውን ሙሉ ቪዲዮ ደግሞ ብትለቅልን እንዴት ሸጋ ነበር፡፡ 

አንዳርጋቸው ፅጌ በተቆራረጠው ቪዲዮም ውስጥ እንኳን ያስተላለፋቸው 3 መልዕክቶች ድንቅ ናቸው፡፡ ሙሉውን ንግግሩን ፅፌ እለጥፈዋለሁ፡፡ እስከዛው ግን መልዕክቶቹ እነኚህ ናቸው፡- 

1ኛ፡- ለወጣቱ የተላለፈ የትግል ጥሪ፡- ወጣቱ የሴት ጓደኛውን ቀጥሮ ሸሚዙን ሲያስተካክል መዋል ሆኗል ስራው፡፡ እንዴት አድርጎ ከኢትዮጲያ እንደሚወጣ እና ደቡብ አፍሪካ ወይም አሜሪካ እንደሚገባ ብቻ ነው የሚያስበው፡፡ ወደ ፖለቲካው የሚመጣው ወጣት ቁጥር እጅግ አናሳ ነው፡፡ ተፒለፍ እና ኢህአፓ ጊዜ የነበረው ፖለቲካ በትምህርታቸው ጎበዝ የነበሩ ተማሪዎችን ሳይቀር ነበር የሚስበው፡፡ አሁን ግን የፊልም አክተር እና ዘፋኞች የሚኖሩበትን ቤት በፊልም እያየ በምኞት ብቻ የሚኖር ወይም እንዲህ አይነት ቤቶች ወዳሉበት አካባቢ ለመሰደድ የሚፈልግ ወጣት ነው ያለው፡፡ በሚል አንዳርጋቸው ወጣቱ ካረፈበት የእንቅልፍ አዚም እንዲላቀቅ እና ለትግል እና ለመደራጀት እንዲዘጋጅ ያስተላለፈው መልዕክት ነው፡፡


2ኛ፡- የተባበረ ትግል ጥሪ፡- አንዳርጋቸው ይህንን ጥሪ ያስተላለፈው ለሶስት አካላቶች ነው፡፡ አንደኛ የኦሮሞ የአማራ እና የደቡብ ኤሊቶች ልዩነታቸውን አጥብበው በህብረት እንዲሰሩ የጠየቀበት፡፡ ሁለተኛ በውጭ ያሉ የፖለቲካ ድርጅቶች 5 እና 20 እየሆኑ ለየብቻቸው የሚያደርጉትንና እንደ አንዳርጋቸው አገላለፅ ‹‹ዩኒቲ ኦፍ ፐርፐዝ›› የሌለበትን ትግል እንዲተው የተናገረበት እና ሶስተኛ ደግሞ በሀገር ውስጥ የሚገኙ ዘጠና ፓርቲዎች 1500 ፊርማ ብቻ እያሰባሰቡ እዚህ እና እዚያ የፈሉበትን ሁናቴ የተቃወመበት ነው፡፡
3ኛ፡- ምርጫ ቀልድ መሆኑን ያጋለጠበት መልዕክት፡- መንግስት ግልፅነት ያለው አሰራር ሳይከተል ተቃዋሚዎች እንዴት ብለው ነው የምርጫ ማኒፌስቷቸውን ማዘጋጀት የሚችሉት የሚል ጥያቄ በቪዲዮው ላይ ሲጠይቅ የሚሰማው አንዳርጋቸው ፅጌ ቃል በቃል ‹‹ምርጫው ቀልድ ነው›› ሲልም ይደመጣል፡፡ 

andargacew Tsige
ሌላው በዚህ ቪዲዮ ላይ ያስተዋልኩት ነገር ከ 6 ደቂቃ ከ 55 ሰከንድ እስከ 7ኛው ደቂቃ ከ 4 ሰከንድ ድረስ እጅግ በጣም ሳግ በተናነቀው እና በተጎዳ ድምፅ ‹‹ከዚህ በኋላ ያለው ነገር የበለጠ ቀውስ እና የበለጠ ኪሳራ በሀገሪቷ እና በህዝቧ ላይ የሚያደርስ ነገር ነው የሚል ዕምነት ነው ያለን›› የሚለው ንግግሩ ነው፡፡ ምኑ ነው የበለጠ ቀውስ እና ኪሳራ ያመጣል ያለው ነገር; ምናልባት ኢቲቪ ትጥቅ ትግሉ የበለጠ ኪሳራ ያመጣል እያለ ነው የሚል ምስል በተመልካች ዘንድ ለመፍጠር አሳባ ነው; ያም ቢሆን ደግሞ ትጥቅ ትግሉ የበለጠ ቀውስ እና ኪሳራ ያመጣል ሲል ማሰማት ነበረባት፡፡ እኔ ግን ሲመስለኝ የበለጠ ቀውስ እና ኪሳራ የሚያመጣ ያለው ምርጫውን እና አሁን ያለውን ስርአት ነው፡፡ ይህን ያልኩበት ምክንያትም በንግግሩ መጨረሻ ላይ የበለጠ ቀውስ እና ኪሳራ የሚያደርስ ነው የሚል እምነት ነው ‹‹ያለኝ›› ሳይሆን የሚለው ‹‹ያለን›› ነው የሚለው፡፡ ይህ ማለት የአንድን ቡድን አቋም እየገለፀ እንዳለ ግልፅ ነው፡፡ በቡድን ደረጃ ያውም አንዳርጋቸው ‹‹እኛ›› እያለ የሚያወራለት ቡድን ደግሞ ስለ ትጥቅ ትግሉ እንዲህ አይነት አቋም እንደሌለው ግልፅ ነው፡፡


በመጨረሻም ቪዲዮውን ደግሜ ደጋግሜ ካየሁት በኋላ የገባኝ ነገር ቢኖር አንዳርጋቸው ባገኛት ትንሽ ቀዳዳም ቢሆን መልዕክቱን ማስተላለፉን እና ምናልባትም ይህ መልዕክት በቴሌቪዥን እንዲሰራጭ ያደረጉት ሰዎች የውስጥ አርበኛ ሊሆኑ እንደሚችሉ ነው፡፡


የአውስትራልያ እና የኢየሩሳሌም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አባ መቃርዮስ የልደትን በዓል በማስመልከት ያስተላለፉት መልዕክት

$
0
0

አባ መቃርዮስ ሊቀ ጳጳስ ዘኢየሩሳሌም ወአውስትራልያ ወዘኵሎን አድያሚሃ
ABBA MEKARIOS ARCHBISHOP OF THE DIOCESE OF JERUSALEM AND AUSTRALIA

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
ክብር ለእግዚአብሔር በአርያም ሰላምም በምድር ይሁን ሉቃስ 2፤14

Abune Mekariosለተወደዳችሁ በአውስትራልያና በመላው ዓለም ለምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ካህናትና ምዕመናን! እንኳን ለጌታችን ለአምላካችንንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት በሰላም አደረሳችሁ።

የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት ሰውና እግዚአብሔር የተገናኙበት፤ ትንቢተ ነቢያት የተፈጸመበት፤ እርቅና ሰላም የተሰበከበት ምድራውያንና ሰማያውያን ፍጥረታት በአንድ ላይ እግዚአብሔርን ያመሰገኑበት፤ በዓል ነው።

በዚህ ቀን የሩቅ ምሥራቅ ነገሥታት በኮከብ እየተመሩ በመምጣት ለተወለደው ንጉሥ ወርቅ ዕጣን ከርቤ እጅ መንሻ አቅርበዋል። ወርቅ ለመንግሥቱ፤ ዕጣን ለክህነቱ፤ ከርቤ ማኅየዊ ለሆነ ሞቱ ምሳሌ እንደሆነ ሊቃውንት ይተረጉማሉ::

Read Full Story in PDF

የግልና የ«ብሄር» ነፃነት በኣቶ ገብሩ ኣስራት እይታ

$
0
0

ኣምሃ ኣስፋው

«ሉኣላዊነትትና ዴሞክራሲ በኢትዮጵያ» የተሰኘው የኣቶ ገብሩ መፅሃፍ ከፍተኛ ተቀባይነትና ኣድናቆት እንዳተረፈ በየድረ ገፁ ተወስቷል። መፅሃፉ በኣማርኛው ጥራትም ሆነ በይዘቱ ጥልቀት ሊደነቅ የሚገባው ይመስለኛል። እርግጥ ብዙ የፊደል ግድፈቶች ኣሉበት። ይህ ግን፣ የኣርታኢዎች ስህተት ብቻ ሳይሆን፣ መቀምሮች (Computers) ማንም ሳያዛቸው በራሳቸው ፊደሎችን የመቀያየር ጠባይ ስላላቸውም ጭምር ነው። ይህ መፅሃፍ የደረሰን ከወያኔ/ህወሃት ኣባል እይታ ቢሆንም የዘመኑን ታሪክ ለማወቅ እጅግ ጠቃሚ ይመስለኛል። ሁኔታው ሲፈቅድ፣ ኢትዮጵያዊያን ልጆች ከሚማሩባቸው መፃህፍት ኣንዱ ቢሆን ከተለያዩ ኣቅጣጫዎች በሚመጡ ሃሳቦች የታነፁ ዜጎችን ለማፍራት ይጠቅማል የሚል እምነት ኣለኝ።
የኣቶ ገብሩን መፅሃፍ በኣማርኛው ጥራትና በይዘቱ ጥልቀት ባደንቀውም፣ የኣንድምታውን ትክክለኛነትም ሆነ የጭብጡን እውንነት እቀበላለሁ ማለቴ ኣይደለም። የዛሬው ፅሁፌም ምክንያት ከማይስማሙኝ ኣስተሳሰባቸው ኣንዱን ለመተቸት ነው፤ በንግግር ነፃነት ስለሚያምኑ ትችቴ ቅር እንደማያሰኛቸው በማመን።
Gebru Asrat
ኣቶ ገብሩ ባለማለት፣ የማለትን ጥበብ የተካኑ ፖለቲከኛ ይመስላሉ። የኣፄ ቴዎድሮስን የጀግንነት ኣሟሟት ሲተርኩ፣ ጠላቶቻቸውን፣ እንግሊዞችን፣ እየመሩ ያመጡት ኣፄ ዮሃንስ መሆናቸውን ይዘሉታል። የኣፄ ምኒልክንና የጣሊያኖችን ውል ደጋግመው ሲያትቱ፣ ጣሊያኖች ኤርትራን በኣፄ ዮሃንስ ዘመን ያልያዟት ለማስመሰል ይሞክራሉ። በሻብያና በኢትዮጵያ ህዝብ መሃከል በተደረገው የመጨረሻ ጦርነት፣ ከምእራብ እስከምስራቅ፣ ከሰሜን እስከደቡብ ያለውን ህዝብ ጀግንነት ሲያሞግሱ፣ ሸዋን እንዳልነበረ ሁሉ ይዘሉታል። በምርጫ 97 የቅንጅትን ኣባል ማህበሮች እንቅስቃሴ ሲገልፁ፣ የመኢኣድ ኣስተዋፅኦ እንዳልነበር፣ እነ ኣቶ ሃይሉ ሻውል ደግሞ እንዳልተፈጠሩ ለማድረግ ሞክረዋል። በደፈናው «ነባር ፖለቲከኞች» ይሏቸዋል። ኣድሃሪ፣ ፊውዳል፣ ነፍጠኛ፣ ትምክህተኛ፣ ምናልባትም እንደ ቀስተ ደመና የምሁራን ሳይሆን የደንቆሮዎች ስብስብ ከሚል ኣስተሳሰብ ብዙም የራቁ ኣይመስለኝም።

እነዚህ የቀድሞ ባለስልጣኖች ስልጣናቸውን ሲነጠቁና ጥቅማቸውን ሲነፈጉ የሚያሰሙት የ«ተሳስተን ነበር» ጩኸት ይገርመኛል። እንዲያውም የጥላሁንን ዘፈን ያስታውሰኛል።

የልብን ሰርቶ ይቅር በሉኝ፣
ምንስ ኣጠፋሁ ምን በደልኩኝ፣

የሚለውን። በስልጣን ላይ እያሉ የኢትዮጵያ ህዝብ ስቃይ ካልታያቸው፣ ስልጣኑን እንደገና ቢያገኙ የህዝቡ በደል ተመልሶ እንደማይሰወርባቸው ምን ዋስትና ኣለን? ኣሁንም ቢሆን፣ የኣቶ ገብሩ ኩራታቸው፣ ጭንቀታቸውም ሆነ ተስፋቸው ለትግሬና ለኤርትራ ህዝብ ብቻ ነው። ይህንን ለመረዳት በመፅሃፉ ሽፋን ላይ ያለውን ካርታ መመልከቱ ብቻ ይበቃል። የመፅሃፉ እኩሌታ የሚነግረን የትግሬን ህዝብ ታላቅነትና ጀግንነት ነው። ካንድ ቦታ፣ ኣንዱን የደርግ መኮንን «ሻብያን ማሸነፍ ለኛ ቀላል ነበር። ሞራላችንን የሰበራችሁትና፣ ድል ያደረጋችሁን እናንተ(ወያኔዎች) ናችሁ።» ብሎ እንዲናገር ያደርጉታል። ከእውነተኛ ሰው ይልቅ የመድረክ ገፀ ባህሪ ነው የመሰለኝ። የትረካቸውን እውነትነት በቦታው ለነበሩና ለታሪክ ኣዋቂዎች ትቼ ወደ ተነሳሁበት ኣላማ ልመለስ። በመፅሃፋቸው ማጠቃለያ ላይ፣ ስለብሄር ነፃነት፣ ስለግል ነፃነትና ስለኢትዮጵያዊነት ያትታሉ።

በመጀመርያ ሌሎችም እንዲያስቡበት ኣንድ ኣንድ ጥያቄዎችን እና የኣቶ ገብሩን ሃሳቦች ላቅርብ።

1. ብሄር ማለት ምን ማለት ነው? ኣቶ ገብሩ ይህንን ጥያቄ ኣይነኩትም፤ ብቻ ትርጉሙ ኣከራካሪ እንዳልሆነ ሁሉ «የብሄር ነፃነት» የሚለውን ሃሳብ እንደልብ ይጠቀሙበታል። መዝገበ ቃላቱ፣ መንደር፣ ኣውራጃ፣ ምድር፣ ኣለም፣ ኩል (Universe) ፣ ባንድ ቋንቋ የሚናገሩ፣ ወገን፣ ነገድ፣ ህዝብ፣ ኣገር፣ ባንድ መንግስት ስር የሚተዳደሩ፣ ባንድ መድበል ስር የተጠቃለሉ ሙሉ መፅሃፎች እያሉ እጅግ ሰፊ የሆነ ትርጉም ይሰጡታል። ሆኖም ኣቶ ገብሩ መፅሃፋቸውን የፃፉት በኣማርኛ ስለሆነ የብሄር ትርጉም ኣማርኛ የተቀበለው ብቻ መሆን ይገባው ነበር። ትርጉሙን በመቀየር ኣዲስ የኣማርኛ ቃል መፍጠራቸው ከሆነም፣ ከመጠቀማቸው በፊት ቃሉን መደንገግ(Define) ነበረባቸው። ዘመናዊ ኣማርኛ የተቀበለው የብሄር ትርጉም «በኣንድ መንግስት ስር የሚተዳደር ህዝብ» የሚለውን ነው። ለዚህም ነው «የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን፣ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ» እንጂ «የትግሬ ብሄራዊ ቡድን፣ የኣማራ ብሄራዊ ባንክ» የማንለው። ኣቶ ገብሩ ጎሳ የሚለውን ቃል ኣይወዱትም እንጂ የሚፈልጉትን ሃሳብ «ጎሳ» ወይም «ነገድ» የሚሉት ቃሎች የተሻለ ይገልፁላቸው ነበር። ግን፣ ወያኔዎች ሁሌም ድብቅ ኣላማ ስላላቸው «ብሄር» ሲሉ «ኣስፈላጊ በሆነ ጊዜ ነፃነቱን የሚያውጅ የህዝብ ስብስብ» ማለታቸው ይሆናል። ለዛሬው ግን የብሄር ትርጉም ልፅፈው የፈለግሁት ጉዳይ ላይ የሚያመጣው ለውጥ ስለሌ፣ ባላምንበትም የኣማራ ብሄር፣ የትግሬ ብሄር፣ የኦሮሞ ብሄር፣ የደቡብ ብሄር … እየተባሉ የሚጠሩ ህዝቦች ኣሉ፣ የሚለውን ሃሳብ ተቀብየ ልቀጥል።

2. «ፍፁማዊ የግል ነፃነት» በሚል ሃረግ የግል ነፃነት ደጋፊዎችን ለማጣጣል ይሞክራሉ። ፍፁማዊ የሚባል ነገር ኣለ? እንኳንስ በህብረተሰባዊ ስይንስ ይቅርና በሂሳብና በፊዚካ ኣለምም ፍፁማዊነት እንደሌለ ሳያውቁት ቀርተው ኣይመስለኝም። ሆኖም ፍፁማዊነት የለም ተብሎ ኣላስፈላጊ የሆኑ ኣምባገነናዊ ስርኣቶች በህዝብ ላይ ኣይጫኑም።

3. የብሄር ነፃነት ማለት መዝፈንና መጨፈር ብቻ ኣይደለም ብለው ይነግሩናል። የብሄር ነፃነት የሚሰጠን፣ ግን የግል ነፃነት ሊያሟላው የማይችል ምሳሌ ሊሰጡን ይችላሉ? ብየ ጥያቄየን ሳልጨርስ መልሱን ይሰጡናል። የብሄር ነፃነት ልጆችህን በራስህ ቋንቋ ማስተማር፣ ቋንቋህን ማሳደግና ማበልፀግን ያካትታል ብለው።

ሶስተኛዋን ጥያቄ ልውሰድና ሃሳቤን ላጠቃል።
ቋንቋ ሊያድግ የሚችልባቸው መንገዶች ሁለት ናቸው።
1. ሀ. ልጆችን በሚፈልጉት ቋንቋ ማስተማር። ለ. በሚፈልጉት ቋንቋ መፃፍ። መ. በሚፈልጉት ቋንቋ ላይ ምርምር ማካሄድ። ሰ. የሚፈልጉትን ቋንቋ በመገናኛ ብዙሃን ማሰራጨት።

2. ሌሎች ቋንቋዎች እንዳያድጉ በመከልከል የሚፈልጉት ቋንቋ ብቸኛ ተጠቃሚ እንዲሆን ማድረግ። ኣማርኛ ኣድርጓል ተብሎ እንደሚታማው ማለት ነው።
እውነተኛ ዴሞክራሲ ካለ… ግን፣ እውነተኛ ዴሞክራሲ ማለት ምን ማለት ነው? ለኔ ዴሞክራሲ ማለት የግለ ሰብን መብት የሚያከብር እንጂ የኣብዛኝውን ህዝብ ፍላጎት የሚያስፈፅም ስርኣት ኣይደለም። ኣብዛኛው የኣሜሪካ ህዝብ ባርነትን ይደግፍ ነበር። የባሮቹን የግል መብት ይፃረራልና እንድያ ኣይነቱ ስርኣት እውነተኛ ዴሞክራሲ ሊሆን ኣይችልም።
እውነተኛ ዴሞክራሲ ካለ፡
geberu asrat new book
ማንኛውም ሰው በሚወደው ወይም ያተርፈኛል በሚለው ቋንቋ የሚያስተምር ትምህርት ቤት መክፈት ይችላል። ማንኛውም ሰው ልጁን የፈለገው ትምህርት ቤት ሰዶ ማስተማር ይችላል። የዚህም ምንጩ የግለሰብ ነፃነት እንጂ የብሄር «ነፃነት» ኣይደለም። የራዲዮና የቴሌቪዥን ጣቢያ ማቋቋም፣ ጋዜጣና መፃህፍትን ኣትሞ ማሰራጨትም የግል እንጂ የብሄር «ነፃነት» ኣይደለም። እርግጥ ሰዎች ተሰብስበው ከላይ
የተገለፁትን ሁሉ በቡድን ማድረግ ይችላሉ። ይህም ቢሆን ግለሰቦች መብታቸውን ሰብስበው የፈጠሩት ቡድን እንጂ፣ ቡድኑ የቸራቸው ነፃነት ኣይደለም። እነዚህ ተቋሞች በመንግስት ደረጃም ሊመሰረቱ ይችላሉ። ኣሁንም ቢሆን ግለሰቦች ነፃነታቸውን በምርጫ ላቆሙት መንግስት ኣካፍለውት እንጂ መንግስት ለግለሰቦች የሚታደል ነፃነት የለውም።

ታድያ የብሄር ወይም የቡድን «ነፃነት» ጥቅሙ ምን ላይ ነው? ትሉኝ ይሆናል። በመጀመርያ የብሄር ወይም የቡድን ነፃነት የሚሉት ነገር የለም፣ የብሄር ኣምባገነንነት እንጂ። ኮሚኒስቶች እውነቱን ግልፅ ኣድርገው ሲናገሩ «የላብ ኣደሩ ኣምባገነንነት» እንደሚሉት ማለት ነው። የቡድን ወይም የብሄር «ነፃነት» በቁጥር ሁለት የተገለፀውን ኣይነት፣ የሌሎችን የግል ነፃነት መግፈፊያ መሳሪያ ነው። ከኢትዮጵያዊነት ጋርም ጨርሶ ኣይጣጣምም።
ምሳሌ ልስጥ፡፡ የብሄር «ነፃነት» የሚፈጥራቸው ህጎች የሚከተሉትን ይመስላሉ።

• ትግሬ ውስጥ ትግሬ ላልሆነ ሰው የንግድ ፈቃድ ኣይሰጥም።
• ኦሮሞ ክልል ውስጥ ጉራጌኛ መናገርም ሆን መፃፍ ክልክል ነው።
• ሃረር ውስጥ ኣማራ መምረጥም ሆነ መመረጥ ኣይችልም።
የብሄር «ነፃነት» (ትክክለኛው ስሙ ግን የብሄር ኣምባገነንነት ሊሆን ይገባዋል) ጥቅሙ ኢትዮጵያዊነትን መወሰን ብቻ ነው። ስለዚህ ከኢትዮጵያዊነት ጋር ሊታረቅ የሚችል ባህርይ የለውም።

በስደት ከሚገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክ የልደትን በዓል በማስመልከት የተላለፈ ቃለ ቡራኬ

“እነርሱ ከደደቢት መጥተው የለ፣ እኛም ሸሚዛችንን እንሸጠለንን” የአንድነት አመራር –ኖአሚን በጋሻው

$
0
0

የምርጫ ቦርድ ታህሳስ 28 ቀን  ባደረገው ስብሰባ፣ የሕወሃት አባል ናቸው የሚባሉት የቦርዱ ምክትል ሊቀመንበር አቶ አዲሱ ከአንድ ቀን በፊት በፋና ራዲዮ የተናገርሩትን በማጽደቅ፣ አንድነት ፓርቲ በምርጫው እንዳይወዳደር የምርጫ ምልክት አልሰጥም የሚል ኢሕገ መንግስታዊ የፖለቲካ ዉሳኔ አስተላልፏል። የአንድነት ፓርቲ በሁለት ወራት ጊዜ ዉስጥ ለሁለተኛ ጊዜ ጠቅላላ ጉባኤ አድርጎ አመራሩን ካልመረጠ በምርጫዉ መወዳደር እንደማይችልም ምርጫ ቦርድ ገልጿል።

የአንድነት ፓርቲ ያለፈው ታህሳስ  ወር 2006 ዓ.ም ጠቅላላ ጉባኤ አድርጎ ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራውን መምረጡ፣  ኢንጂነሩም ከዘጠኝ ወር አገልግሎት በኋላ፣  ከአባላትና ከደጋፊዎች በተነሳ ግፊት፣ የመሰረቱትን የሥራ አስፈጻሚ በትነው ፣ በመስከረም ወር 2006 ዓ.ም ከሃላፊነታቸው በፍቃዳቸው መልቀቃቸው ይታወቃል።

tigstuበድርጅቱ ደንብ መሰረት ብሄራዊ ምክር ቤቱ፣ ከመካከሉ ሶስት አመራር አባላትን አወዳድሮ፣ አቶ በላይ ፍቃደን የድርጅቱ ሊቀመንበር አድርጎ መርጧል። ከአቶ በላይ ጋር አሁን የአዲስ አበባ ምክር ቤት ሃላፊ አቶ ነገሰ ተፋረደኝ፣ አቶ ትእግስቱ አወሉ እና አቶ ደረጀ ለእጩነት ራሳቸውን አቅርበው የነበረ ሲሆን፣ አቶ ነገሰ «እኔን ልትመርጡ ያሰባችሁ፣ አቶ ደረጄን ምረጡ” በሚል ከዉድድሩ ራሳቸዉን በማውጣታቸው ምርጫው በተቀሩት ሶስት እጩዎች መካከል ተከናዉኗል። አቶ በላይ ፍቃደ አብላጫ ድምጽ ሲያገኙ፣ አቶ ደረጄ በሁለተኛ በመሆን ብዙ ድምጽ ያገኛሉ። አቶ ትእግስቱ አወል የርሳቸውን አንድ ድምጽ ብቻ አግኘተው ሶስተኛ ሆኑ። ሁለተኛ የሆኑት አቶ ደረጀ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል ሆነው እየሰሩ ነው።

አቶ በላይ በደንቡ መሰረት አዲስ የሥራ አስፈጻሚ አዋቅረዉ፣ በምክር ቤቱ ያጸድቃሉ። የምክር ቤቱ ዉሳኔ፣  ሕጉ እንደሚጠይቀው፣ ለምርጫ ቦርድ ይላካል። ምርጫ ቦርድ ለአዲሱ አመራር እውቅና አልሰጥም የሚል ደብዳቤ ይጽፋል። የደብዳቤ ምልልሶች ይጧጧፋሉ። በዚህ ወቅት ብቻ ቢያንስ ወደ ዘጠኝ ደብዳቤዎችን አንድነት ከምርጫ ቦርድ ጋር ተጻጽፏል። አንድነት ምንም አይነት የደንብም ሆነ የህግ ጥሰት እንዳላደረገ ለማስረዳት ተሞከረ። የአመራር አባላቱ ምርጫ ቦርድ ድረስ በመሄድ ሁኔታዉን ለማስረዳት ሞከሩ።  አዉቆ የተኛን ቢቀሰቅሱት አይሰማም” እንደሚባል ምርጫ ቦርድ በፍትሃዊነት ሁሉንም ድርጅቶች የሚያገለግል ሳይሆን ከሕወሃት መመሪያ ተሰጥቶች ጠንካራ የተባሉ ድርጅቶች ለመኮርከም የተዘጋጀ በመሆኑ፣ ለመስማት ፍቃደኛ አልሆኑም። የአንድነትን ትእግስት፣ የምርጫ ቦርድን አደርባይነት እንግዲህ ተመልከቱ።

የአንድነት ፓርቲ የሰለጠነ ፖለቲካ የሚያራምድ ፓርቲ እንደመሆኑ,  የሚሰራዉን ደባ ታግሶ፣ በመንገዱ ላይ የሚቀመጠዉን መሰናክል ድንጋይ እያለፈ ሕዝቡን ማደራጀቱን እየቀጠለ፣ አላስፈላጊ ጭቅጭቅ ዉስጥ መግባት አያስፈልግም በሚል ምርጫ ቦርድ የጠየቀዉን ለማሟላት ወሰነ። ምርጫ ቦርድ በድርጅቱ ደንብ ላይ የጠቅላላ ጉባኤ የኮረም ቁጥር መጠቀስ አለበት የሚል ጥያቄ በማቅረቡ፣ ምንም እንኳን የኮረም ቁጥር መግባት አለበት የሚል ሕግ ስለሌለ ያንን  የመጠየቅ መብት ምርጫ ቦርድ ባይኖረውም፣ ለአባላቱም ስልጠና ለመስጠት አስቦ ስለነበረ፣ አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ ይጠራል። በጠቅላላ ጉባኤው ምርጫ ቦርዱ  የጠየቀው የደንብ መሻሻል ያደርጋል። የብሄራዊ ምክር ቤት ፕሬዘዳንት ሲመርጥ አንድ ድምጽ ብቻ ያገኙት አቶ ትእግስቱ አወል፣  በአቶ በላይ ፍቃደ አመራር ላይ ጥያቄ ያነሳሉ። አቶ በላይ ስልጣኑ የጠቅላላ ጉባኤ እንደመሆኑ፣  የተመረጡት በድርጅቱ ደንብ መሰረት በምክር ቤት እንደሆነ ገልጸው፣ ጠቅላላ ጉባኤው ግን በማናቸውም ጊዜ የምክር ቤቱን ዉሳኔ የመቀልበስ መብት እንዳለው በማስረዳት፣ እንደገና ምርጫ ማድረግ እንደሚቻል ያሳወቃሉ። የድርጅቱ የበላይ አካል የሆነው ከአራት መቶ በላይ ተወካዮች ያሉበት  ጠቅላላ ጉባኤው ፣ የብሄራዊ ምክር ቤቱ በፍቃዳቸው ከሃላፊነታቸው በለቀቁት በኢንጂነር ግዛቸው ምትክ ፣ አዲስ አመራር ማስመረጡ ትክክልና ደንቡን ያልጣሰ መሆኑን ያረጋግጣል። አዲሱን አመራር በድጋሚ ያጸድቃል። አቶ ትእግስቱ አወልን እና አቶ የማነን የተባሉ ግለሰብን ጨምሮ ከአምስት የማይበልጡ ይቃወማሉ። (ቀደምም ብሎ ብዙ ድምጽ ሲያሰሙ የነበሩት አቶ  ዘለቀ ረዲ በጠቅላላ ጉባዔው ወቅትም አልተገኙም ነበር)

አንድ መረሳት የሌለበት፣  የጠቅላላ ጉባኤ በሚደረግበት ጊዜ የምርጫ ቦርድ ተወካይ በስፋራው የተገኙ ሲሆን፣ የጠቅላላ ጉባኤውን ስሜትና የተወካዮችንም አንድነት  በሚገባ ተገንዝበው ሄደዋል።

የጠቅላላ ጉባኤው ቃለ ጉባኤ ፣ የተሻሻለዉን ደንብ በጊዜው ለምርጫ ቦርድ ይላካል። ሆኖም አሁንም ምርጫ ቦርድ አንድነት የምርጫ ዘመቻዉን እንዳያጧጡፍና አባላትን እና ደጋፊዎች ለማዳከምና ለማዘናገት ሲል፣  ሰበብ እየፈጠረ ፣ በኢቲቪም አንድነት ችግር እንዳለበት እየለፈፈ፣ ጸረ-ዴሞክራሲያዊና ጸረ-ሕዝብ ተግባሩን ይቀጥልበታል።

ሕወሃት፣ በጠቅላላ ጉባኤ ያልተገኙት አቶ ዘለቀ ረዲ፣ ለሊቀመነበርነት ተወዳድረው አንድ ድምጽ ብቻ (የራሳቸዉን ድምጽ)  ያገኙት አቶ ትእግስቱ አወሉ ( ሁለቱም አንድነትን በዉህደት ከተቀላቀለው ከብርሃን ለዲሞክራሲ ፓርቲ የመጡ ናቸው)፣ አቶ የማነ የመሳሰሉት በጣት የሚቆጠሩ ሰዎችን በማሰባሰብ፣ ትልቅ የኢቲቪ ሜዲያ ሽፋን በመስጠት፣ የስብሰባ አዳራሾችን በመፍቀድ፣ በገንዘብም በመደገፍ ፣  የአየለ ጫሚሶን አይነት ድራማ ለመስራት መንቀሳቀስ የጀመሩ ይመስላል። እነ ኢንጂነር ዘለቀና ትእግስቱ አወል ከአራት መቶ በላይ የጠቅላላ ጉባኤ አባላት 10 እንኳን የደገፋቸው ሳይኖር፣ ሕወሃት እነርሱን እያደራጀ ፣ የኢሕአዴግ ካድሬዎችም እንዲቀላቀሏቸው እያደረገ ፣ ስለ እነርሱ እያወራለን ይገኛል።

ሕወሃት “አንድነት እንደገና ጠቅላላ ጉባኤ ጠርቶ አመራሩን ማስመረጥ አለበት። አለበለዚያ በምርጫው አይወዳደርም” የሚል ዉሳኔ ነው በመጨረሻ ሲሰጥ አላማ ምን እንደሆነ በግልጽ አሳይቷል። አንደኛ የአንድነት ደጋፊዎችና አባላት እንዲደናገጡን ተስፋ እንዲቆርጡ ነው። ሁለተኛ አንድነት እንደገና ጠቅላላ ጉባኤ በመጥራት ጊዜዉን እንዲያጠፋ ነው። ሶስተኛ ጠቅላላ ጉባኤው ወጭ የሚጠይቅ እንደመሆኑ አንድነትን በገንዘብ ማዳከም ነው። ቢቻላቸውም ደግሞ አራተኛ በአቶ ዘለቀረ ረዲ ወይም ትእግስቱ አወል የሚመራ የአየለ ጫሚሶ አይነት “አንድነት” ተመስርቶ የአንድነትን ሕጋዊ ሰርተፊኬት ለነርሱ በመስጠት አንድነት ከምርጫው ዉጭ እንዲሆን ማድረግ ነው።

ቅንጅትን  ለአየለ ጫሚሶ ሲሰጡ፣ ያኔ የቅንጅት መሪዎች ከእስር ቤት መዉጣታቸው ነበር። በመካከላቸውም ብዙ አለመስማማቶች ነበር። አሁን ያሉት የአንድነት አመራር አባላት በሥራ አስፈጻሚ ውስጥ ሆነ በምክር ቤቱ፣  የጠነከረ አንድነት ያላቸው ናቸው። ይሄንንም በስራቸው እያሳዩ ነው። በአንድነት ታሪክ አሁን ያለበት አይነት ጥንካሬ አንድነት ኖሮት አያውቅም።

አባላትና እና ደጋፊዎች ተስፋ ለማስቆረጥ ከሆነ ደግሞ፣ ከምርጫ ቦርድ በሚሰዘነዘረው ዱላ እንደዉም አባላት የበለጠ ይጠናከራሉ እንጂ አይዳከሙም። አቶ አዲሱ፣  በፋና ራዲዮ የተናገሩት እንደተሰማ፣ በአገሪቷ ሁሉ ያሉ አባላት ፣ “ይሄ ያህል በራዲዮ ኛ ላይ ዘመቻ ከተጀመረ ጥሩ ሰርተናል ማለት ነው” እያሉ የበለጠ ለመስራት መሯሯጥ ጀምረዋል። አላወቁትም እንጂ ሕወሃት ለአንድነት ትልቅ ማስታወቂያ እየሰራለት ነው። እንኳን የነ አቶ አዲሱና አቶ መርጋ ተራ ደብዳቤ ይቀርና፣  ሞት  ወይም እሥር የማይፈሩ ጀግኖች የበዙበት ፓርቲ ነው የአንድነት ፓርቲ።

አንድነትን በገንዘብ ለማዳከም የታሰበዉን ካየን ደግሞ፣ አንድ የአንድነት አመራር አባል እንደተናገሩት  “እነርሱ ከደደቢት መጥተው የለም እንዴ። ሸሚዛችንን ሽጠን የሚያስፈልገውን እንሸፍናለን” እንዳሉት ፣ ለትግሉ የሚያስፈለገው ወጭ ይሸፈናል። አንድ ጊዜ ሕዝቡ ከጎኑ የሆነ ድርጅት አይወድቅም። የጠቅላላ ጉባኤ ተጠርቶ እንደገና አቶ በላይ ሆነ ሌላ ጠንካራ አመራር የአንድነት ጠቅላላ ጉባኤ ይመርጣል። ሕወህትቶች ደስ ካልተተሰኙ ጸጉራቸውን ይንጩ እንጂ፣ መሪያችንን  እኛ እንጂ  እነርሱ አይመርጡልንም።

እንግዲህ ዉድ ኢትዮጵያዉያን ይሄ ሁሉ ትግል ነው። ሕወሃት የሚፈልገው ምርጫዉን ከትርኪምርኪ ድርጅቶች ጋር አድርጎ አሸነፍኩ ብሎ ማወጅ ነው። አላማቸው አንድነት ምርጫዉን ቦይኮት እንዲያደረግ ነበር። አንድነት ቦይኮት ማድረጉ ጉዳት እንጂ ጥቅም እንደሌለው በመግልጽ በዉጭም ሆነ በአገር ዉስጥ ያሉት በማሳመን የምርጫ ዘመቻዉን ሲያጋግለው፣ ኦፌሴላዊ የምርጫ ዘመቻ ገና  ሳይጀመር፣ ገና ከወዲሁ ለክልልና ሆነ ለፌደራል ተወዳዳሪዎች አዘጋጅቶ እንደጨረሰ ሲገልጽ፣ በየከተሞችን በሚሊዮኖች ድምጽ ለፍትሃዊ ምርጫ በሚል ሰልፎችን እና ሕዝባዊ ሰብሰባዎች ሲጠራ፣ ሕውሃት ደነገጠ። ያንን ለማስቆም ብሎ ከህዝብ ካዝና የተገኝ ገንዘብን እየበተነ ነው።

እንግዲህ የአገራችን ፖለቲካ ግለቱ ጨምሯል።  ከዳር የቆምን፣ ተስፋ ቆርጠን የተቀመጥን ትግሉን እንቀላቀል። ከሚሊዮኖች አንዱ እንሁን። አንድነትን እንደገፍ። የለዉጥና የነጻንትን ችቦ እናቀጣጥል። እኛ ከተባበረን የሃባትሙ አያሌውን አባባል ልዋስን እመኑኝ ደርግም ወድቋል፤ ወያኔም ትወድቃለች።

 

ጎበዝ ጠንከር ነው –ግርማ ሰይፉ የአንድነት ም/ሊቀመነበር

$
0
0

Girma  Seifuምርጫ ቦርድ ማንም ይዘዘው ማንም ወይም በግል ተነሳሽነት እያደረገ ያለው ነገር የኢትዮጵያን የመድበለ ፓርቲ ስርዓት ከምን ጊዜውም በለይ ወደኋላ ለመመለስ እንደሆነ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ሊረዳው ይገባል፡፡ ምርጫ ቦርድ ምርጫ እንዲያሰተዳድር በተሰጠው ኃላፊነት የፓርቲዎች አስተዳደሪ ለመሆን እየቃጣው ያለ ተቋም ነው፡፡ ስናከብረው ለመከበር ፈቃደኛ አልሆነም፡፡ ለዚህ ተቋም መጠናክር የበኩላችንን መወጣት አለብን ብለን የተነሳን ፓርቲዎችን ጭምር እየገፉ አለቆቹን ለማስደሰት ደም ተግቶ እየሰራ ይገኛል፡፡ ይህን የሚያደርጉትን ሰዎች ደግሞ በህዝብ ፊት ለብይን እንዲቀርቡ በግልፅ ማጋለጥ ይኖርብናል፡፡
ትላንትና ዶ/ር አዲሱ በሚዲያ ቀርቦ የተናገረው በምንም መልኩ አንድነትን አይመጥንም፡፡ የተቀሩት የቦርድ አባላትም ይመጥነናል ካሉ ትዝብት ላይ ይወድቃሉ፡፡ የምርጫ ቦርድ አባላት ሳያገባቸው እንፈትፍት ሲሉ መፈተፍቱን ለእኛ ተዉልን ነው ያልናቸው፡፡ ዶ/ር አዲሱ በሚዲያ የቦረድ ውሳኔ ሊሆን ይችላል ብሎ ካቀረበ በኋላ ዛሬ ታህሳስ 28 2007 ቦርድ ተሰብስቦ ውሳኔ ሰጥቶዋል፡፡ ይህን ውሳኔ እንገራችሁ ብለው በስልክ ከጠሩን በኋላ የአንድነት ፓርቲ የወረዳ አባላት የሆኑትንም በተመሳሳይ መልክ ጠርተው ነበር፡፡ ለነገሩ ይህ አካሄድ አንድነትን ስለማይመጥን በፅሁፍ እንዲገልፁልን ነግረናቸው ተመልሰናል፡፡ ለማንኛውም ዶ/ር አዲሱ የሰጠው መግለጫ ይህ መግለጫ እንዲሰጥ የወሰኑትን ጨምሮ ለተቀሩት የቦርድ አባላት ያላቸውን ንቀት የሚያሳይ ነው፡፡ ቦርዱ ተሰብሰቦ ምንም ዓይነት ውሳኔ ከመወሰኑ በፊት ውሳኔውን ሚዛን የሚያሳጣ መግለጫ ለመስጠት ምን እንዳጣደፋቸው መገመት ቀላል ነው፡፡ በልባቸው የሚደግፉትን ፓርቲ ለማንገስ ያላቸውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው፡፡
ልክ የዛሬ አምስት ዓመት አንድነት ላይ ተመሳሳይ ግብ ግብ ተፈጥሮ ነበር፡፡ የዚህ ተልዕኮ ፈፃሚዎች ዛሬ ላይ ሆነው ምን እንደተጠቀሙ ሲያሰላስሉ ምን እንደሚሰማቸው ባላውቅም ዛሬ በዚህ ተግባር ላይ የተሰለፉት አባላት ደግሞ ምን እንደሚያደርጉ መጠበቅ ነው፡፡ ለመማር ያልተፈጠረን ሁሉ ምንም ማድረግ ይቻላል? ማንም ተላላኪና ላኪ ሆኖ ቢያገለግልም ዛሬ የተሰማኝ ነገር አንድነት በምርጫ ለመሳተፍ ሲወስን እንደዚህ ዓይነት ተቋማት በምን ያህል ደረጃ ለመዋረድ ዝግጁ እንደሆኑ ለመረዳት የሚያስችል ነው፡፡ አሁንም ትግሉ መራራ፣ የሚያስከፍለው መስዋህትነትም ውድ ሊሆን እንኳን ቢችል የአንድነት አባላት በድል እንደሚወጡት ምንም ጥርጥር የለኝም፡፡ እሩቅ እንደሆነ አውቀን ለጀመርነው ትግል አቋራጭ እንደማንፈልግ መግለፅ ይኖርብናል፡፡
ውድ የአንድነት አባላት ለቀጣይ አንድነት ከምርጫ ቦርድ አሻጥር ለማላቀቅ ለምናደርገው ትግል ቀበቶ ጠበቅ ነው፡፡ ከሰማይ በታች አንድነት ለመፍታት የማይችለው ፈታኝ ነገር ምርጫ ቦርድም ሆነ በውሰጥችን ያሉት ዙንቢዎች ሊያቀርቡ አይችሉም፡፡ ጎበዝ ጠንከር ነው፡፡

 

ታሪክ ለመስራት እንዘጋጅ – አቶ ተክሌ በቀለ የአንድነት ተቀዳሚ ም/ሊቀመንበር
አንድነት ፓርቲ የኢህኣዴግን ምንነት ላላመኑ ወገኖች ለማጋለጥ በትጋትና በስሌት ሲሰራ ቆይቷል፡፡እየሰራም ነዉ፤እዚህ ደርሷል፡፡ “የሆደ ሰፊዉን ምርጫ ቦርድ” ሆድ በገሃድ አጋልጧል፡፡በነአሞራዉና ወዲ ቐሺ(በተጋሩ ሁሉ) ትግልና ሞት የሚቀልዱትን በህዝብ ፊት ወጥተዉ ዛሬም እንዲዋሹና ለኢትዮጵያችን የፖለቲካ ታሪክ እነማን ምን እንደሆኑ አንድነት ፓርቲ የበኩሉን ሚና ተጫዉቷል፡፡ ለኔ ከባድመ ዉሳኔና ልህዝቡ በወቅቱ ከተነገረዉ ጋር ይመሳሰላል፤ይጠጋጋል፡፡ኢህኣዴግ ምርጫዉን እንደማይፈልገዉ፤ከፈለገዉም ለተለመደዉ ቀልዱ ከነማን ጋርና በምን ሁኔታ እንደሚፈልገዉ ፓርቲያችን ሶስተኛዉን (የአዉሮፓና አሜሪካ ታዛቢዎች የሌሉበት ምርጫ መሆኑን፤የህዝብ ታዛቢዎች የተበላሸ የምርጫ ሂደትና ፓርቲዎችን የማፈራረስ/የማዳከም ስራዎች) ነጥብ አስመዝግቧል፡፡
በዚህ ሂደት ላይ ሰፊ እዉነታ ለህዝብ ይቀርባል የሚል እምነት አለኝ፡፡ከምርጫዉ ቦርድ መጋረጃ ካሉት ወገኖች ጋር በሃሳብ እየተሸነፈ ግን ተሳትፎዉ ያለተቋረጠ አንድ ከፍተኛ አመራር እንዳለ እናዉቃለን፡፡ሁሉን ነገር በደንብና በመርህ የምንሰራዉ ለኢህኣዲግ/ምርጫ ቦርድ ካለን ፍርሃት ሳይሆን ለወደፊቱ ለምናስተዳድረዉ ህዝባችንና ለኢትዮጵያችን ፖለቲካ ክብር ስንል ነዉ፡፡እናም ከደንብ ወጥተን የሰራነዉ ክዋኔም በግፍ የገፋነዉ አመራርም፤አባልም የለም፡፡በመቻቻል መንፈስ ዲሰፒሊን ተጥሶም እንዲጓተት ተደርጓል፡፡ይህንንም የኢህኣዴግ ተባባሪነት ለታሪክ አስቀምጠነዋል፡፡
ምርጫ ቅንጦት ሆኖብን፤የተከበሩ እየተባሉ ለመጠራት ሳይሆን እፊታችን ላይ ያለ እድልና ስልትም ስለሆነ አንድነት ፓርቲ መጪዉን ምርጫ የምር እንዲሆን ወስኗል፡፡ ኢህኣዴግ ደግሞ ማበላሸቱን ተያያይዞትል፡፡ምርጫ በአምባገነን ቡድኖች ለሚገዙ አገራት ለለዉጥ እንዱ ስልት እንጂ ብቸኛዉ አለመሆኑ ይታመናል፡፡ፓርቲያችን ለለዉጥ ተደራጅም ይላል፡፡እዉነተኛ ፓርቲዎች ከምርጫዉ ባሻገር ላለዉ ግብ እንዲዋሃዱና እንዲተባበሩም ጥሪ አቅርቧል፤ስልቶችን ለማቀራረብም እየጣረም ነዉ፡፡የአንድነት ኣባላት በያለንበት ድርብ ሃላፊነት አለብን፡፡ለአንድነት ሃይሎች ስልቶቻችን ሁሉ በማቀራረብ የተጀመረዉ የስልጣን ሃይሎችን እያራገፉ ትግሉን በሰለጠነና አንድነቱን በጠበቀ መልኩ የማስቀጠልና ልዩነቶችን በማቻቻል ሰፊ መሰረት የማንበር ሃለፊነት አለብን፡፡ ታሪክ ለመስራት እንዘጋጅ፤ፊታችንን ወደ ዋናዉ ግብ እናድርግ፤ከሃዲዱ አንወርድም!

 

አሁን አንድነት ግልፅ ጦርነት የታወጀበት ይመስላል  – አቶ ኪዳኔ አመነ – የመድረክ ወጣት አመራር
አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ በተመለከተ ብዙ እየሰማን ነው፡፡ ፓርቲው ራሱን የማፅዳት ሃላፊነት ከተወጣ በኋላ ገዢው ፓርቲ ጥርሱን የነከሰበት ይመስላል፡፡ ብዙ ፈተና እየገጠመው ነው፡፡ በምርጫ ቦርድ ጥያቄ መሰረት ጠቅላላ ጉባኤ በድጋሚ እስከማድረግም ደርሰዋል፡፡በኔ እምነት አንድነት ፓርቲ በበኩሉ ብዙ ርቀት የሄደ ይመስለኛል፡፡ ትእግስታቸው አደንቃለሁ፡፡ ፓርቲው በውስጡ ከጥቂቶች በቀር በዙዎቹ ቁምነገር የሚያስቡ የምናከብራቸውና የምንወዳቸው ጥሩ ሰዎች አሉት፡፡ ትርጉም ያለው የፖለቲካ እንቅስቃሴ ከሚያደርጉ ጥቂት ፓርቲዎች አንድነት አንዱ ነው፡፡ እናም በኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ና እውነተኛ ፍትህ ለማምጣት የአንድነት መኖር ከፍተኛ ትርጉም አለው፡፡ ፓርቲው የአንድነት ፓርቲ አባላትና የኢትዮጵያ ህዝብ ብቻ ሣይሆን የራሳችን አቋምና መስመር ይዘን በሌላ ፓርቲ ያለን ሰዎች እንኳ አንድነት እንዲኖር አጥብቀን እንፈልጋለን፡፡ ወደፊት አንድነትም እኛም ቤታችን እያፅዳን መንገድ ላይ መገናኘት አለብን፡፡

 

ያኔ ብቻ ነው ኢትዮጵያን የምናድናት፡፡ እንዳንራመድ ቀይዶ የያዘን ገመድ እየበጣጠስን፤ ፀረ-ለውጥና አድሃሪ አቋምን እየመከትንና እያፀዳን የዴሞክራሲ እና የሉዓላዊነት ፍለጋው ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል፡፡
አሁን አንድነት ግልፅ ጦርነት የታወጀበት ይመስላል ፡፡ አንድነቶች አሁን ነው የፖለቲካ ፅናታቸው በጥበብ ማሳየት ያለባቸው፡፡ ወንድሞቻችን በርቱ!!!

 

Viewing all 8745 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>