Quantcast
Channel: ዘ-ሐበሻ – Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 8745 articles
Browse latest View live

Health: ያልተመለሱ ወሲብ ነክ ጥያቄዎቻችሁ እና አዳዲስ የሕክምናው ሳይንስ ምላሾች

$
0
0


የ‹‹ጂስፖት›› አገር ከወዴት ነው?
ወሲብ በብርሃን ወይስ በጨለማ?

sex-good-for-healthበሴቶች በኩል የሚደፈር ርዕሰ ጉዳይ አይሁን እንጂ በርካታ ወንዶች በጋራ ሲሰበሰቡም ሆነ አንድ ለአንድ ሲያወሩ ወሲብ ነክ ጉዳዮችን አንዴ ወይም ሌላ ጊዜ ማንሳታቸው አይቀርም፡፡ በሴቶቹ ክብ ውስጥ ተገኝቼ ውይይታቸውን ባላዳምጥም እነርሱም ቢሆኑ ከጓደኞቻቸው ጋር ይህን ስሱ ርዕስ ሲያነሱና ሲጥሉ እንደሚቆዩ እገምታለሁ፡፡ በኛ አገር በወሲብ ነክ ጤና ጉዳዮች ላይ የህክምናው ሳይንስ ሰዎችም ይሁኑ ሚዲያው በግልፅ የመነጋገር እና ችግሮችን የማቅለል ልምዱ አነስተኛ በመሆኑ ወደ ጤና ተቋማት ለመሄድ እና የባለሞያን ሀሳብ ለማግኘት ተነሳሽነቱ ባይኖር ብዙ አይገርምም፡፡ ‹‹ቄሱም ዝም፣ መፅሐፉም ዝም›› በሆነበት የወሲብ ጤና ጉዳይ በውጪው ዓለም ለቁጥር የሚያታክቱ አማካሪ ባለሞያዎችና የፃፏቸው መፅሐፍት ለሰዎች የእለት ተዕለት ጭንቀቶች መፍትሄን ቢሰጡም እኛ አገር ገና ብዙ የሚቀረን እርምጃ አለ፡፡ ይህንን መነሻ አድርገን የተለያዩ ሴክስ ኤክስፐርቶች የፃፏቸውን መፅሐፍትና መጣጥፎች በማጣቀሻነት በመጠቀም በተለያየ ጊዜ የሚገጥመው ወሲብ ነክ ችግሮች እና ያልተመለሱ ጥያቄዎችን በመመለስ ግንዛቤን የሚያሲዝ አጭር ምልከታ ልናደርግ ወደናል፡፡

ምን ያህል ወሲብ? በየስንት ጊዜው?
በዚህ ለኑሮ መሮጥ የሁሉም ሰው ዕለታዊ የቤት ስራ በሆነበት ጊዜ በፍቅርም ይሁን ትዳር ውስጥ ያሉ ጥንዶች እርስ በእርሳቸው ፍቅራቸውን ለመግለፅ እና ወሲብ ለመፈፀም በቂ ጊዜ ላያገኙ ይችላሉ፡፡ ወሲብ መፈፀም አካላዊ ግንኙነት ብቻ ባለመሆኑ ሁለቱም ተጣማጆች አእምሮአቸው አሪፍ እና ዘና ብሎ ቅርርቡንም ፈልጎ ወደ ወሲብ ሲያመራ በእርካታ የሚያጥለቀልቅ እና አዝናኝ ጥምረትን ይፈጥራሉ፡፡ አንዳንድ ጥንዶች ግንኙነት ከፈፀሙ ረጅም ጊዜ ሆኗቸው ሊሆን ይችላል፡፡ ሌሎች ጥንዶች በሳምንት አሊያም በወር ምን ያህል ጊዜ ይሆን ወሲብ የሚፈፅሙት? ሲሉ በውስጣቸውም ይጠይቃሉ፡፡ በሳምንት፣ በወር ይህን ያህል ጊዜ ወሲብ ሊፈፅም ይገባል የሚል ምትሃታዊ ቁጥር የለም፡፡ የህክምና ሳይንስ ባለሞያዎችም ቁርጥ ያለ መልስ አይሰጡም፡፡ ‹‹ይህ በግንኙነቱ ጤናማነት ደረጃ እና በጥንዶች ቅርርቦሽ የሚወሰን ነው›› ባይ ናቸው፡፡
ሆኖም ግን ጤናማ ግንኙነት ውስጥ ያሉ ጥንዶች ወሳኝ ጉዳዮች መካከል ፍቅር መስራት ዋነኛው እንደመሆኑ በግንኙነት ቆይተው ለበርካታ ወራት ወሲብ ካልፈፀሙ ጥያቄ ማንሳቱ ጤናማ ነው፡፡ ለምን ያህል ድግግሞሽ እና መቼ የሚለውን ለማጥናት ሙከራ ያደረጉ ተመራማሪዎች ያሳተሙት ውጤት መነሻ ሀሳብን ሊሰጥ ይችላል፡፡ ዱሬክስ ኩባንያ 2006 ላይ ያወጣው ዓለም አቀፍ ሴክስ ሰርቬይ ላይ ዝቅተኛ ወሲብ ይፈፅማሉ የተባሉት የሲንጋፖር ሰዎች ሲሆኑ በወር 6 ጊዜ ነው ወሲብ የሚፈፅሙት፡፡ ባለሞያዎች በመጨረሻ የሚያጠቃልሉት ወሲብ የሚፈፀምበት ድግግሞሽ በሁለቱ ጥንዶች ስምምነት ያለው ከሆነ በፍቅር ግንኙነቱ አለዚያም ትዳሩ ላይ የሚፈጠር ችግር የለም፡፡ ይሁንና ከሁለቱ አንዱ ወሲብ እየፈለጉ ሌላኛው ወገን የሚያዘገየው ከሆነ በጉዳዩ ላይ በግልፅ ተወያይተው ሁለቱንም የሚያስማማ የጊዜ ርቀት እንዲያስቀምጡ እና ስሜታቸውን ተረድተው ቢዝናኑበት መልካም ነው ይላሉ፡፡

በወሲብ ስንት ደቂቃ ይቆያሉ? ቀድሞ የመጨረስ ጣጣ
በርካታ ወንዶች ወሲብ እየፈፀሙ በርካታ ደቂቃዎችን መቆየትን በፍቅር እና ትዳር አጋራቸው ዘንድ ነጥብ ያስቆጥርልናል ብለው ያስባሉ፡፡ አሳዛኙ ነገር ግን በዚህ መነሻነት በሚፈጠር መጨናነቅና የስነ ልቦና ውጥረት ገና እንደደረሱ ጨርሰው ለማቆም የሚገደዱት ናቸው የሚበረክቱት፡፡
በወሲብ የመቆየት ጊዜ ምን ያህል መሆን አለበት ለሚለው የተለያዩ የህክምና ሳይንቲስቶችና መፃህፍት የተለያዩ ምላሾችን ይሰጣሉ፡፡ በህክምናው ቋንቋ Intravaginal Ejaculatiry Latency Time (IELT) የሚባለው የቆይታ ጊዜ የሚቆጠረው ወንዱ በሴቷ ብልት ውስጥ ብልቱን ከከተተበት ደቂቃ ረጭቶ እስከሚወጣበት ድረስ ያለው ነው፡፡ ‹‹ይህ ጊዜ ልክ አንድ ደቂቃም ይሁን አንድ ሰዓት ወሳኝ ሊሆን የሚገባው በዚህ ጊዜ ሁለቱም ተጣማጆች እኩል እርካታን ከወሲብ ተጎናፅፈዋል ወይ የሚለው ነው›› ይላሉ ዶ/ር ሄለን ኦኮኔል የተባሉት የኒውሮሎጂ ባለሞያና የወሲብ ጉዳዮች አማካሪ፡፡ በደቂቃ ልኬን ማወቅ አለብኝ ለሚሉ ወንዶች መልስ ቢሆን ብለው በአማካይ አንድ ወንድ በወሲብ መቆየት ያለበትን የደቂቃ ርዝመት ያጠኑ ባለሞያዎች እ.ኤ.አ 2005 ላይ ጆርናል ኦፍ ሴክሹዋል ሜዲስን በተሰኘ የምርምር መፅሔት እንደፃፉት በአማካይ አንድ ወንድ ወሲብ እያደረገ ሊቆይ የሚችለው ለአምስት ደቂቃ ከ30 ሰከንድ ያህል ነው፡፡ ይህ ቆይታ ታዲያ ቅድመ ዝግጅቱን መተሻሸቱን እና መሳሳሙን አይጨምርም፡፡ ብልቱ ከሴቷ ብልት ገብቶ ስፐርሙን እስካፈሰሰበት ቅፅበት ያለውን ብቻ ይመለከታል፡፡ የጥናቱ አድራጊዎች ገና እንደገቡ የሚያፈሱ ሰዎችን አስመልክተው ሲፅፉ ‹‹ወሲብ መዝናኛ ነው፣ ዘና ብለው ከሴቷ ብልት መቆየታቸውን እንደ ደስታ እያሰቡ ሳይጣደፉ የሴቷ ደግሞ ስሜት እያደመጣ ወሲብ ማድረግን ይልመዱ›› ሲሉ መክረዋል፡፡ ከፍርሃት፣ ከጭንቀት እና መጠራጠር የፀዳ ንፁህ ግንኙነት ውስጥ ያሉ ጥንዶች የሚቆዩበትን ጊዜ እንዳሻቸው ሊለጥጡት ይችላሉ፡፡ ‹‹ወሳኙ የስነ ልቦናዊ ጥምረታቸው ልክ ነው›› ይላሉ የጥናቱ መሪ አያን ኬርነር፡፡ አካላዊ እና ከብልት ጡንቻዎች ጋር የተያያዘ ችግር ካለ ይህን በህክምና ማስታገስ እንደሚቻልም ያክላሉ፡፡

በወር አበባ ጊዜ ሴክስ ይፈቀዳል?
ሴቶች የወር አበባ ላይ በሚሆኑበት ወቅት አንዳንድ ጊዜ ተጣማጆቻቸውን ሴክስ ይከለክላሉ፡፡ ‹‹አሞኛል›› ይላሉ፡፡ እውን በወር አበባ ጊዜ ወሲብ መፈፀም ህመም ይሆናል? የጎንዮሽ ጉዳትስ ይኖረው ይሆን? የሚል ጥያቄ የሚያነሱ ወንዶችም ሴቶችም መልስ እንዲሆን ታዋቂዋ የሴክስ ኤክስፐርት እና የጉድቫይብስ መፅሔት ፀሐፊ ካሎል ኩዊን ያቀረቡት ፅሑፍ የሚለውን እንመልከት፡፡ ኤክስፐርቷ እንደሚሉት በወር አበባ ጊዜ ወሲብ መፈፀም ችግር የለውም፡፡ ይሁንና በአንዳንድ ሀይማኖታዊ ምክንያቶች የተነሳ ብዙ ሴቶች ከወሲብ ሲታቀቡ እንዳስተዋሉ ተናግረዋል፡፡ በሳይንሱ ግን አይከለከልም፡፡ እንዲያውም በወር አበባ ወቅት ከሚከሰተው ህመም የሚገላግልና የመዝናናት ስሜትን የሚፈጥሩት ኢንደርፊን የተባሉት ሆርሞኖች ሴክስ በሚፈፅሙ ወቅት በሰውነታቸው ስለሚለቀቅ ራስ ምታት፣ ድብርት እና ቀርጠት የመሳሰሉት የወር አበባ ህመሞችን ማስታገስ እንደሚችሉ ባለሞያዋ ያብራራሉ፡፡ ይሁንና የወር አበባ ወቅት የማህፀን ጫፍ ደሙን ለማስወጣት ከፈት የሚልበት በመሆኑ እንዲሁም የብልታቸው አካባቢ ከወትሮው በተለየ አሲዳማነቱ የሚቀንስ በመሆኑ ለተለያዩ ኢንፌክሽኖች እና አባላዘር በሽታዎች የሚጋለጡበትም ወቅት ስለሚሆን ሁልጊዜም ኮንዶም መጠቀምን አይርሱ ሲሉ ሀሳባቸውን ያጠቃልላሉ፡፡

ወሲብ በጠዋት የጤና ነው?
የባለቤቷ የወሲብ ፍላጎት ጉዳይ ያሳሰባት ሴት ባቀረበችው ጥያቄ እርሱ ወደ ቤት ማታ ሲመጣ ደካክሞ ይመጣና ይተኛል፡፡ ጠዋት ላይ ግን አፈፍ ያደርገኝና ወሲብ መፈፀም እንጀምራለን፡፡ ይሄ የሌሎች ወንዶች ተፈጥሮ ይሆን ወይ? የጤናስ ነው? ስትል ትጠይቃለች፡፡ ለእርሷና ሌሎች ተመሳሳይ ጥያቄ ለሚኖራቸው ሰዎች ኤክስፐርቶቹ የሚሉት አላቸው፡፡ በእርግጥም የወንዶች ተፈጥሯዊ የሆርሞን ስርዓት የሚፈጥረው ፍላጎት አለ፡፡ የወንዶች የወንዴ ሆርሞን ቴስቴስትሮን መጠን በቀን ውስጥ ከፍ እና ዝቅታ ይገጥመዋል፡፡ በተለይ ከጠዋቱ 12 ሰዓት እስከ 4 ሰዓት መጠኑ ከፍ ብሎ የሚገኝበት በመሆኑ ወሲብ ቢጠይቅ አትፍረጂበት ይላሉ ዩሮሎጂስት ሐኪሟ፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ያደረ ሽንት በሽንት ከረጢት ስለሚጠራቀም ግፊቱ ደም ወደ ብልቱ በብዛት እንዲደርስና ብልቱ እንዲወጠር ያደርጋል፡፡ እነዚህ የሆርሞኖችና በደም ፍሰቱ የብልት መወጠር ምክንያቶች በጠዋት ለወሲብ መነቃቃቱ ተፈጥሯዊ ነው፡፡ የጠዋት ጉልበትና ብርታቱም ሳይነዘጋ፡፡

የ‹‹ጂስፖት›› አገር ከወዴት ነው?
ሴቶችን የማርካት ፈተና
ሴቶች በወሲብ መርካታቸው ጉዳይ እንደ ሁለተኛ ነገር ሲወሰድ የነበረበት ዘመን አብቅቶ ዛሬ ዛሬ አብዛኛዋ ሴት ከፍቅር እና ትዳር ግንኙነቷ ከወንድ እኩል የወሲብ እርካታን ትፈልጋለች፡፡ የሴክስ ኤክስፐርቶች ይህን የእርሷን እርካታ ለማረጋገጥ የሚሻ ወንድ ሰውነቷን፣ ስሜቷ የሚቀሰቀስበትና ከእርካታም የሚያደርሷትን ቦታዎች ልቅም አድርጎ ማወቅ ይገባዋል ይላሉ፡፡ ሴቷን ብልት ቁልፍ የእርካታ ስፍራ ‹‹ጂስፖት› ማወቅ የሁሉም ወንድ የቤት ስራ መሆን አለበትም ይላሉ፡፡ ትክክለኛ ቦታውን በመጠቆም በኩል እንዲሁም ከነጭራሹ ስለመኖሩ የሚጠራጠሩ ባለሞያዎች ቢኖሩም በአመዛኙ ግን ጂ ስፖት ቁልፍ የሴቷ የእርካታ ማዕከል ተደርጎ ይወሰዳል፡፡ ይህ ስፍራ ጥንት በህንድና ቻይና ፅሑፎች በግምት ሲገለፅ የኖረ ቢሆንም በዘመናዊ የህክምና ሳይንስ የታወቀው በጀርመናዊው የማህፀን ስፔሻሊስት ዶ/ር ኸርነስት ግራፊንበርግ እንደነበር መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ በእርሱ በመታወቁም ይህ የሴቶች የእርካታ ማዕከል በአባቱ ስም የእንግሊዝኛ ፊደል ‹ጂ› በመውሰድ ‹ጂ ስፖት› ተባለ፡፡ እርሱ እንደሚገልፀው ጂስፖት የሚገኘው በሴት ብልት ፊት ግድግዳ በብልቷ የላይኛው ጫፍ እና በብልቷ ስንጥቅ መካከል ነው፡፡ ይህ ስፍራ በጣትም ሆነ በወንድ ብልት በሚነካካበት ወቅት በሚፈጠር የነርቮች መነቃቃት ወደ እርካታ ጫፍ ትስፈነጠራለች፡፡ የወንዱ ብልት ሲገባና ሲወጣም ይህን ስፍራ እንዲነካካ ካልሆነለትም በጣቱ ጭምር እንዲያነቃቃው የሴክስ ኤክስፐርቶቹ ይመክራሉ፡፡

ወሲብ በብርሃን ወይስ በጨለማ?
በርካቶች ወሲብ ሲፈፅሙ መብራት ያጠፋሉ፡፡ ከፊሎች ደግሞ መብራት በርቶ እርስ በእርስ እየተያዩ ሁለ ነገራቸውን እያደነቁ መፈፀሙ የተሻለ እርካታ ይሰጣቸዋል፡፡ በወሲብ ጉዳዮች የሜንስ ሄልዝ መፅሔትን የሚያማክሩት ክሊኒካል ሳይኮሎጂስት እንደሚሉት በብርሃን ወይም በመብራት ወሲብ መፈፀም ዝግጁ የሆኑ ጥንዶች በግንኙነታቸው ጥልቀትና ግልፅነት የሚተማመኑ፣ ተጣማጃቸውን የሚያፈቅሩ፣ የወሲብ አካላቶቻቸውን ብቻ ሳይሆን መላ አካላትና መንፈሳቸውም ጥምረት እንዲፈጠር የሚፈልጉና የሚፈቅዱ በመሆናቸው ሊደሰቱ ይገባል፡፡ ግን ደግሞ ጭለማው እና መብራቱ መጥፋቱም በመጥፎ ምልክትነት ሊወሰድ አይገባም፡፡ አንዳንድ ተፈጥሮ ይህን አይፈቅድም፡፡ ሁለታችሁ ብቻ ባላችሁበት ክፍል ሁልጊዜ መብራት እንዲጠፋ የምትፈልጉ ከሆነ ግን እስቲ አብርታችሁ ሞክሩት፡፡ ስለግንኙነታችሁ አንዳንድ ነገር ሊገልጥላችሁ ይችላል፤ ሌሎች በርካታ ጉዳዮችን ከወሲብ ህይወት ጋር ተያይዘው ሊነሱ እንደሚገባቸውና ምላሽ እንደሚፈልጉ እንረዳለን፡፡ በሌላ ጊዜ ርዕሰ ጉዳዩን ልናነሳው ቀጠሮ ይዘን የዛሬን እናብቃ፣ ሰላም!


ህወሃቶች በደደቢት ለአርቲስቶቹ የነገሯቸው እና ያልነገሯቸው ታሪኮች ሁሉ የሚያሳዩት አሁንም ህወሓት ስለመንደሩ እንጂ ለኢትዮጵያ አለመቆሙን ነው

$
0
0

Agazi+Victim-1
ፎቶ -በ1997 ዓም በአዲስ አበባ በአጋዚ ጦር የተገደሉ ኢትዮጵያውያን

መንደርደርያ

ኢትዮጵያ በታሪክ የእርስ በርስ ጦርነትን እንደ ትልቅ ታሪክ የምትዘክር ሀገር ሆና አታውቅም።እንደዚያ ቢሆን ኖሮማ ዘመነ መሳፍንት የብዙ የእርስ በርስ ጦርነቶች ባለ ታሪክ ነበር።ሆኖም ግን የወቅቱ የሀገራችን መሪ ግዜያዊ ድል ሲያገኝ የእኔን ማሸነፍ የኢትዮጵያ ታሪክ አድርጉልኝ ሲል አልተሰማም።ጉዳዩ የእርስ በርስ ጦርነት ነዋ! በተቃራኒው ግን ኢትዮጵያ ለነፃነቷ እና ለአንድነቷ የሞቱላትን ከህወሓት በፊት የነበሩት የኢትዮጵያ መሪዎች ትልቅ ቦታ ሰጥተውት ኖረዋል።እነኝህ መሪዎች ከጣልያን ጋር የነበረውን ትንቅንቅ ዘከሩ እንጂ ለስልጣን የተደረጉ ውግያዎችን የኢትዮጵያ ትልቁ ታሪክ ነው ብለው አልተሟገቱም።ህወሓት ግን ያለፉትን ለኢትዮጵያ የሞቱትን እየነቀፈ እና እየወቀሰ ሲመቸው ደግሞ ለማደብዘዝ የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ እየከፈተ ኢትዮጵያ የተፈጠረችው ደደቢት ላይ ነው መሰል ንግግር ሊያሰማን ይዳዳዋል።
ፖለቲከኞችን ማሳመን ያልቻለው ህወሓት ለአርቲስቶች ምን ነገራቸው?

ሰሞኑን አርቲስቶችን አሳፍሮ ደደቢት ላይ የከረመው የወያኔ አመራር ቡድን 150 ሚልዮን ብር ወጪ(ለፀጥታ ጥበቃ፣ትራንስፖርት፣ለሁሉም አርቲስቶች የቀን አበል፣የምሽት እራት እና ዳንስ ወዘተ) መውጣቱን የውስጥ አዋቂ ዘገባዎች ዘግበዋል።አርቲስቶቹም ድራማ ሲሰሩ ከርመዋል።ሰው ለሰው ድራማ በዋና አክተሩ ተወክሏል፣የህወሓት የዛሬ የአዲስ አበባ እና መቀሌ ህንፃ ባለቤቶች ሲደንሱ ታይተዋል።ለአርቲስቶቹ በእርስ በርስ ጦርነት ወቅት እንዴት ድልድይ እንደፈረሰ፣የቱ ጋር ትግራይን ለመገንጠል እንደተዶለተ፣የቱ ድንጋይ ላይ ተቀምጠው ለሻብያ የምፅዋ ጦርነት የትግራይ ልጆች እንዲላኩ እንደተወሰነ፣የቱ ጋር ስለ ብሔር ብሔር በሚል ሽፋን የኢትዮጵያ ጉድ የሆኑትን ጉድ የብሔር ድርጅቶች ለመፈልፈል ህወሓት እንደዶለተች ተነገረ።

ለአርቲስቶቹ ከተናገሩት ውስጥ አቶ ስዩም መስፍን፣አቦይ ስብሐት እና ሳሞራ የኑስ እንዴት ኢህአፓን እና ኢድዮን እንዴት ከትግራይ እንዳስወጡ ተተረከ።አቦይ ስብሃትም በመሃል የሚያስቆማቸውን ሳል እየሳሉ ሲቀጥሉ እንዲህ አሉ ”የቀድሞዎቹ ተቃዋሚዎች ሁሉም የተሰገሰጉት የቀደመውን ስርዓት ለመመለስ የሚፈልጉ ነበሩ” ካሉ በኃላ የኢትዮጵያን የፖለቲካ ችግር የብሔር ችግር ነው ካሉ በኃላ የብሔር ችግርን ”የማይታረቅ ቅራኔ” ሲሉ ስደመጡ ተሰብሳቢውን አስደንግጧል።

ቀጥሎ ከተናገሩት ውስጥ አቶ በረከት ነበሩ።አቶ በረከት አቦይን የወረፉበት ንግግር አቦይን ”ድራማቲክ” አቀራረብ ያለው ሲሉ ተደምጠዋል። አቶ በረከት የገለጡበት መንገድ እንዲህ ይነበባል -”የአቦይ ስብሐት አይነት ድራማቲክ አቀራረቦች ስንሰማ ልንዋጥ እንችላለን።በታሪክም ልንጠፋ እንችላለን” በማለት ነበር።የሁሉም ንግግሮች ያጠነጠኑት ትግራይ በሌላው ኢትዮጵያ ላይ የበላይ እንደሆነ ማብራራት ነበር።ደደቢት ላይ ህወሓት ባይመሰረት ኖሮ ኢትዮጵያ ትጠፋ እንደነበር ለመግለፅ መድከም ሌላው ለማስተላለፍ የታሰበው መልዕክት ነበር።

ህወሓት የፖለቲካ ማሳመኛው ፍልስፍናው ሁሉ ተሟጦ የቀረው የደርግ ዘመንን ደጋግሞ ማንሳት ብቻ ሆኗል።አሁን ኢህአዴግን ፖሊሲህ ዘመን ያለፈበት በቂም፣በዘር እና በበቀል የታሸ ነው የሚለው ደግሞ ኢህአዲግ አዲስ አበባ ሲገባ ገና በእግራቸው መቆም ያልቻሉ ሕፃናት የነበሩ ወይንም ገና ያልተወለዱ ናቸው።ህወሓት የኢትዮጵያን ሕዝብ ዲሞክራሲ የነጠቀ፣በጠራራ ፀሐይ ድምፄ ተሰረቀ ያሉ ወጣቶችን በጥይት የቆላ፣ብሔር ከብሄር በማጋጨት ከእራሱ የወጡ አባሎቹ የመሰከሩበት፣አባላቱ በሙስና በሰበሰቡት ገንዘብ መሃል አዲስ አበባ እና መቀሌ ላይ ባለ ሰባት ፎቅ ሲገነቡ እፍረት የማይሰማቸው አባላት ያሉት ወንጀለኛ ድርጅት መሆኑን የሚሞግቱት አሁንም ወያኔ አራት ኪሎ ቤተ መንግስትን ሲቆጣጠር በእናታቸው እቅፍ ሆነው ጡት የሚጠቡቱ ናቸው። በመሆኑም ተከራክሮ የማያሳምነውን ትውልድ ሸሽቶ ስለፖለቲካ ቢናገሩ እናንተን አይመለከትም ለማለት የሚቀሉትን አርቲስቶችን መማፀኑ ካለተከራካሪ የእኔን ብቻ ስሙኝ ስልት መሆኑ ነው።

ህወሓት ለአርቲስቶች ያልነገራቸው

የህወሓት መሪዎች አርቲስቶቹን ፈረንጆቹ ”ዱላ እና ካሮት” በሚሉት አስተያየት እያዩ እና አንዳንዴ ፈገግ መልሰው ኮስተር እያሉ በማሳቀቅ የተረኩት ሁሉ ዛሬ ላለችው ኢትዮጵያ እና ዓለማቀፋዊ ሁኔታ ፋይዳው ምንድነው? ብሎ መጠየቅ ተገቢ ነው። የስብሰባው ዋና ዓላማ ህወሓት የተንጠለጠለበት የጎሳ ፖለቲካ እንዳይበጠስ በመስጋት የጎሳውን ታላቅነት የሰበከ መስሎ ብዙዎች አይናቸውን ተክለውባቸዋል ባለው አርቲስቶች በኩል ህዝብን ማስፈራራት፣ተስፋ ማስቆረጥ እና ”መጪውም ገዢዎችህ እኛ ነን።” የሚል መልእክት ለሕዝቡ ማስተላለፍ ነው።”መጪው ምርጫንም ክደደቢት አንፃር ተመልከቱ እና እንዴት ነው በካርድ ስልጣን እንድለቅ የምታስቡት?” የሚልም ቃና አለበት።

እዚህ ላይ ግን አምባገነኖች የራሳቸውን ታሪክ እራሳቸው ከሚተርኩት በዘለለ ነፃ የታሪክ ምሁራን የራሳቸውን ምርምር አድርገው ታሪክ እንዲፅፉ አይፈልጉም እና ተራክዎችም ሆነ ሰሚዎች እራሳቸው እንደሆኑ የመቃብር ጉዞ ይጀምራሉ።እዚህ ላይ ህወሃቶች ለአርቲስቶቹ ያልነገሯቸውን ማንሳት ተገቢ ነው።
አቦይ ስብሐት፣አቶ ስዩም እና አቶ በረከት ቢቢሲ ስላረጋገጠው ህወሓት ለትግራይ ሕዝብ በ 1977 ዓም እረሃብ የመጣውን የዕርዳታ እህል ሱዳን እየተወሰደ ይሸጥ እንደነበር እና የጦር መሳርያ ይገዛበት እንደነበር አልነገሩትም።
በደርግ ዘመን በአሶሳ የአማራ ተወላጅ ናችሁ ተብለው በአንድ ቤት ተከተው በእሳት ስለተቃተሉት ምንም አላሉም።
ኤርትራ ከኢትዮጵያ ትለይ ብለው እስከ ምፅዋ እና ከረን ድረስ የትግራይ ተወላጆች ደም እንዲገብሩ መላካቸውን አላነሱትም።
ህወሓት እስካሁን ድረስ በአሜሪካ የሽብር መዝገብ ላይ እንደሰፈረ መሆኑን ትንፍሽ አላሉም።
በህወሓት የተሳሳተ ፖሊሲ ሳብያ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሴት እህቶቻችንን ለአረብ ሀገር መከራ መዳረጋቸውን ያነሳ የለም።
በህወሓት ውሳኔ በሺህ የሚቆጠሩ ሕፃናት ለጉድፈቻነት መዳረጋቸው እና በለውጡ ህወሓት ብዙ ሚልዮን ዶላር ማትረፉን ትንፍሽ ያለ የለም።
ህወሓት ከተሞች በጎዳና ተዳዳሪዎች፣ወጣቶች ለጫት እና ለሽሻ፣የዩንቨርስቲ ምሩቃን የኮብል ስቶን ሥራ ሰራተኛ እንዲሆኑ የተደረጉት በዘመነ ህወሓት መሆኑን ለመናገር የደፈረ የለም።
በከተሞች የሚኖሩ ብዙ ሺዎች የገዛ ቤታቸው በግሬደር ሲፈርስ እና የጎዳና ተዳዳሪ የሆኑት በህወሓት ዘመን መሆኑን ህወሀቶች አላነሱትም።
ገበሬው ለዘመናት ከኖረበት ቦታ በጎሳ እና በቋንቋ እየለዩ ለዘመናት ከኖረበት ቦታ የተፈናቀለው በዘመነ ህወሓት መሆኑን ያወሳ የለም።
አስራሶስት የህወሓት አመራሮች በስዊድን ዓለም አቀፍ የጦር ፍርድ ቤት በዓለም አቀፍ ወንጀለኛነት ከተከሰሱ ገና ቀናት እየተቆጠሩ መሆናቸውን ሊያስታውሱ አልፈለጉም።
ከሁሉም የሚገርመው ህወሃቶች ከአርትስቶቹም ሆነ ከትግራይ ሕዝብ የደበቁት ትልቅ ጉዳይም አለ።የሀውዜን እልቂትን ጉዳይ።ይህንን እልቂት አቦይ ስብሐት አዲስ የማስቀየሻ ያሉትን ሃሳብ ይዘው ቀርበዋል።”በጉዳዩ ላይ የእስራኤል እጅ አለበት” ነበር አቦይ ያሉት።መቸው ህወሃቶች ከገደሉ ወይም ከተኮሱ አልያም ከተናገሩ በኃላ ነው ማሰብ የሚጀምሩት።ለእዚህም ነው ነገሩን ከመካከለኛው ምስራቅ ሃገራት ጋር በማያይዝ ከአረብ ሃገራት ያተረፉ የመሰላቸውን የተናገሩት። ከህወሓት የለቀቁት የቀድሞ ከፍተኛ ባለስልጣናቱ ግን በሃውዜን እልቂት ላይ የህወሓት ቁልፍ ባለስልጣናት እጅ ሆን ተብሎ የተቀናበረ መሆኑን ያብራራል።አቶ ገብረ መድህን አርአያ፣አቶ ግደይ እና አቶ አብርሃም ያየህ በተለያየ ጊዜ በጉዳዩ ላይ ማብራርያ ሰጥተዋል።ከእዚህ በታች የአቶ ገብረ መድህን የቀድሞው የህወሓት መስራች እና የፋይናንስ ኃላፊ በሃውዜን እልቂት ህወሓት አቀናባሪ እንደነበር እና ምክንያቱንም ጭምር እንዲህ ያብራራሉ።

”“ወይ፡ ሀውዜንም የወያኔ ድራማ ነው።” በዚያን ጊዜ ሕወሀት በምትሰራው ስራ ምክንያት እጅግ በጣም ተጠልታ ነበር። ሰው አጣች። ምልምል ጠፋ። እናስ? ተንኮል አሰቡ። የዚያን ግዜ የትግራይ አስተዳዳሪ ለገሰ አስፋው ነው። ከዚያ ወያኔ ሀውዜን አንድ ክ/ጦር እያስገባች እያስወጣች ወያኔ ሀውዜን ስብሰባ ልታደርግ ነው የሚል ወሬ ለደርግ ደህንነት እንዲደርሰው አደረገች። ሀይሉ ሳንቲም (ሳነቲም ቅጽል ስሙ ነው) የሚባል የወያኔ የጦር ደህንነት፡ የወያኔ ጦር ሀውዜን ሊሰበሰብ ነው የሚለውን መረጃ ለለገሰ አደረሰ። እውነት እንዲመስልም፡ በገበያው ቀን የተወሰኑ ታጋዮች ባካባቢው ውር ውር ሲሉ እንዲታዩ ተደረገ። የሀውዜን ገበያ መቼም እጅግ የታወቀ ነበርና ከብዙ ቦታ ብዙ ሰዎች ለንግድ ይመጣሉ። በእለቱ ስድስተ የደርግ ሚጎች እየተመላለሱ በመስቀልያ ቅርጽ፡ ገበአውን ደበደቡት። ይሄ ሁሉ ሲደረግ ቪዲዮ ይነሳ ነበር። ነገሩ ለረጅም ግዜ የተቀነባበረ መሆኑ የሚታወቅባቸው ምክንያቶች የሚከተሉት ናቸው። ወደ አስራ ሁለት ፎቶ አንሺዎች ሱዳን ውስጥ ሄደው እንዲሰለጥኑ ተደርጓል። ገብሬ የዚያን ግዜ ቪዲዮ ካሜራ አያውቅም ነበር። እነ ተክለወይን አስፍሀ፡ እነ ሱራፌል ምህረተአብ፤ እነ እያሱ በርሄ ካሜራ ቀራጭነት ሱዳን ውስጥ ተምረው መጡ። ያ ሁሉ ድብደባ ሲደረግ ተራራ ላይ ቆመው እያንዳንዱን ሚግ ከሁሉም አቅያጫ ቪዲዮ ያነሱ ነበር። ይቀርጹ ነበር። በነጋታው ይሁን ማታውኑ ያ ሁሉ ፊልም ሱዳን ውስጥ በቲቪ ታየ። ገበያ ላይ የሞተው ሰው እንሰሳ፡ ህዝብ፡ ሽማግሌ ሕጻናት በቲቪ በደንብ ተቀርጿል።

የምንስ ለቅሶ መልሶ መልሶ

ባጠቃላይ ህወሓት በኢትዮጵያ ታሪክ ላይ ምንም አይነት አሻራ የለውም የሚል የለም።ሆኖም ግን መታሰብ ያለበት ጉዳይ ዛሬ ላይ በሞቱት አጥንት ላይ ተቀምጠው በሙስና በስብሰው፣ዲሞክራሲን በእግራቸው እረግጠው እና በርካታ ግድያ ፈፅመው የሞቱትን እያነሱ መመፃደቅ አሁንም በሞቱት ላይ መሳለቅም አያጣውም።ለሕወሃቶች የምመክራቸው ሴኮቱሬ ከደደቢት ያስተላልፍ የነበረውን ፕሮፓጋንዳ ዛሬ ላይ ደግመው ማንበብ ቢችሉ የሚል ነው።”ትግላችን የኢትዮጵያ ሕዝብ ካለምንም ገደብ የመፃፍ፣የመናገር እና ሃሳብን በነፃት የመግለፅ ነፃነትን ለማረጋገጥ ነው።ትግላችን ህዝቦች ካለ አንዳች ፍርሃት ሰላማዊ ሰልፍ የሚያደርጉበትን በፈለጉት የሀገሪቱ ቦታዎች የመኖር መብታቸው እንዲረጋገጥ ነው” ይል ነበር። ለእዚህ ነዋ ”ህገ መንግስቱ ይከበር” ያሉትን ንፁሃን ወጣቶች እስር ቤት የምታማምቁት? ለእዚህ ነዋ ! ”ነፃነት ለፍትሃዊ ምርጫ” ብለው የተሰለፉትን የሰማያዊ ፓርቲ እና የዘጠኙን ፓርቲዎች ጥሪ በድብደባ መባረራቸው እና መታሰራቸውን ምን እንበለው። በደደቢት ህወሃቶች ለአርቲስቶቹ የነገሯቸው እና ያልነገሯቸው ታሪኮች ሁሉ የሚያሳዩት አሁንም ህወሓት ስለመንደሩ እንጂ ለኢትዮጵያ አለመቆሙን ነው።

ጉዳያችን ታህሳስ 23/2007 ዓም (ጃንዋሪ 1/2015)

ምክር እስከመቃብር(ካልፎሂያጁ ማስታወሻ የተቀነጨበ)- ክፍል ሁለት –በእውቀቱ ሥዩም

$
0
0

እንደምነሽ ሸገር
የከሰመው ወንዝሽ
የከሰመው ወዝሽ
የሚታየው ነጥፎ
እንደምነው ጣፎ
እንዴት ነው ቀበና
እስቲ ድንጋይ ላጥምድ መረብ ልጣልና፡፡
Beweketu Seyoun joke about African leaders summit [Very Funny]
በነገራችን ላይ በኣዲስ ኣበባ የሚገኙ ካፌዎችና ምግብ ቤቶች“ ኒውዮርክ”“ ዴምቨር” “ወዘተረፈ ተብለው የሚጠሩትን ያክል ባውሮፓና በኣሜሪካ ያሉ ሬስቶራንቶች ደግሞ ”ዱከም“ ፤ ኣራትኪሎ ፤ ፒያሳ በሚል ተሰይመዋል፡፡ የዚህ ምክንያቱ ምንድር ነው ፡፡ ኣዲስ ኣበባ ስትኖር ውጩን ይናፍቅሃል፡፡ ውጭ ስትኖር ደሞ ኣገር ቤት ይናፍቅሃል፡፡ መኖር ማለት የማይበርድ ናፍቆት ማለት ይሆን? መልመድ ይቅደም! ናፍቆት ይውደም!! ያለምንም ደም!!!


ፌንተን መንገድ ዳር ከሚገኙ ያበሻ ሬስቶራንቶች ባንዱ ተኬ ከተባለው የቀድሞው የብሄራዊ ቡድናችን በረኛ ጋር ኣመሸሁ፡፡
ሊጋብዘኝ ዝግጁ እንደሆነ ሲነግረኝ “ኣንድ ሽሮና ኣንድ ያሣ ዱለት ቢመጣልኝ ደስ ይለኛል!“ኣልሁ ራሴን እያከክሁ፡፡
“ይሄ ሁሉ ምግብ ምን ይሰራልሃል? ገና ለገና ኣገርቤት የምግብ እጥረት ስላለ ለወር የሚበቃህን ያህል በልተህ ልትሄድ ነው?“
ምግቡ ሲመጣ ተኬ ከኣሣ ዱለቴ ኣንድ ጉርሻ ጎረሰና ኣላምጦ ግንባሩን ከሰከሰ፡፡
” እንዴት ነው?“ ስል ጠየኩት፡፡


“ምምምም ያባቴን ኣውራጣት፤ ያባቴን ኣውራ ጣት ይላል” ኣለ፡፡
“ጉደኛ ነህ! ያባትህን ኣውራጣት በልተህ ታውቃለህ?”
“ምን መሰለህ!በልጅ እያለሁ ማታማታ የኣባቴን እግር ማጠብ ነበረብኝ፡፡ ትዝ ይለኛል፤ያባቴ እግር በጣም ቀጭን ተመሆኑ በላይ ሲበዛ ጸጉራም ነው፡፡ እግሬን እጠብልኝ ከሚለኝ ይልቅ እግሬን ኣበጥርልኝ ቢለኝ ይሻል ነበር፡፡ ወንድ ልጅ ሲወለድ ከነቃጭሉ ዱብ ኣለ ይባል የለ፡፡ፋዘር ደሞ ከነገምባሌው ነው ዱብ ያለው፡፡እና እግሩን ኣጥቤ ስጨርስ ኣውራጣቱን ያስመኝ ነበር፡፡ያውራ ጣቱ ጣእም እስታሁን ምላሴ ላይ ኣልጠፋም፡፡ኣውራ ጣቱ ይህን ዱለት ይህን ዱለት ይላል፡፡ኣሁን ሳስበው ኣባቴ ምናባቱ ቆርጦት እንደዛ እንደሚያረግ ኣይገባኝም፡፡እግር የሚስም ባርያ የመግዛት ኣቅም ስላልነበረው እኛን ልጆቹን እንዲህ ያስመን ነበር፡ ፡ ኣየህ ልጅ ማለት እግዜር ለወላጅ የፈነገለው ባርያ ማለት ነው፡፡”


በልተን ስንጨርስ ሊመክረኝ ተዘጋጀ፡፡
“ወደ ኢትዮጵያ የሚያስመልስህ ነገር ምንድነው?”
“ያገር ፍቅር!”
“ትያትር ቤቱን ነው ?”
“እረ ስሜቱ!”
ተኬ በመልሴ በጣም ሳቀ፡፡
“ምን ኣሳቀህ?፡፡ ኣገሬ ገብቼ ከልማቱም ከግማቱም ብሳተፍ ኣይሻልም?“ኣልኩት በቁርጠኝነት፡፡
“እንደ ወንድም ልምከርህ፡፡ እዚህ ብትቀር ይሻልሃል፡፡ ደመወዝ ይመስል ውሃ በወር ኣንዴ የሚመጣበት ኣገር ምኑ ይፈቀራል?መብራቱስ የታል? እዚህ ኣሜሪካ በየቤቱ ደጅ ላይ የሚቆመው ክሪስማስ ትሪ ከኣዲስ ኣበባ የተሻለ ያበራል፡፡ ኢትይጵያ ውስጥ ካምፖል ይልቅ ብርሌ ብዙ ስራ ይሰራል፡፡የሰለጠነው ዓለም ጨረቃ ላይ ከተማ ለመገንባት ሲራኮት እኛ በጨረቃ ብርሃን ራት እንበላለን፡፡ በዝያ ላይ የለማኝና የጎዳና ተዳዳሪው ብዛት ኣይዘገንንም?”
“እዚህም እኮ ለማኝ ኣለ” ኣልሁ፡፡


“ያገራችንን መናጢ ለማኝ ካሜሪካ ለማኝ ጋር ስታወዳድረው ሼም ኣይሰማህም? የዚህ ኣገር ለማኝ እንደምታየው ኣለቅጥ ወፍራም ሲሆን የሚለምነውም ለጂም ነው፡ ፡ ባለፈው ቬጋስ ሄጄ ያያየሁት ለማኝ ምን እያለ እንደሚለምን ታውቃለህ?”
“ምን ኣለ?”


‘ወንድሞቼ ለዛሬ ሌሊት ሸሌ የምገዛበት ፍራንክ ስለቸገረኝ ጣልጣል ኣርጉልኝ’
ስስቅለት ጊዜ ቀጠለ፡፡
”በዛ ላይ ኣገሩ ውጥረት ነግሷል፡፡ ኣዲስ ኣበባ ውስጥ የሚታየው መፈክር ይዞ የሚሮጥ ወጣትና ቆመጥ ይዞ የሚያባርር ፖሊስ ብቻ ነው፡፡ኣንተም ገና ኤርፖርት እንደደረስህ ነው መሮጥ የምትጀምረው፡፡ከምርጫ ጋር በተያያዘ ብዙ ጣጣ ይኖራል፡፡ኣደራ ገዥውን ፓርቲም ሆነ ጎምዥውን ፓርቲ እንዳትመርጥ ፡፡ዝምብለህ በኤፍ ኤም ደውለህ ለፍቅረኛህ ዘፈን ምረጥ፡፡ፌር የሆነ ምርጫ ያለው እዛ ይመስለኛል፡፡ I hope የጥላሁንን ገሰሰን ዘፈን ስትመርጥ የጥላሁን ጉግሳን የሚጋብዙ ዲጄዎች እንዳልተቀጠሩ ተስፋ ኣለኝ፡፡“
በፈገግታ ማዳመጥ ቀጠልኩ፡፡


”ያገራችን ብቸኛ ጸጋዋ ኣየሯ ነበረ ፤ ኣሁን እሱም እየተበላሸ ነው ኣሉ፡፡በኛ ጊዜ ጸሃይ ኣመለ ልስልስ ነበረች፡፡ ኣሁን ሙቀቱ ኣይጣል ነው!ጸሃይ በጣም ከማቃጠሏ የተነሳ ያዲሳባ ሴቶች እንጀራ የሚጋግሩት ጃንጥላቸው ላይ ነው ሲባል ሰምቻለሁ ፡፡ እንድያውም ኣንዳንዴ ሳስበው የሰማይ ኮርኔስ የተቀደደው በኢትዮጵያ ኣቅጣጫ ሳይሆን ኣይቀርም፡፡ድሮ ሽማግሌ ኣያትህ እንዲመርቅህ ከፈለግህ የማለዳ ጸሃይ ስር ወስደህ ታሰጣዋለህ፡፡ ዛሬ የማለዳ ጸሃይ ስር ብታሰጣው ይረግምሃል፡፡ምነው ምነው ልጄ ኣልሞት ኣልኩህ? እንዲህ እንደ እንፋሎት ዳቦ በገዛ ላቤ ከምትጥብሰኝ በግልጥ እንደ ደመራ ለምን ባደባባይ ኣታነደኝም?ኣይ ኣይይይ!ርጉም ሁን ፡፡ዘርህ ይማረክ፡፡ቤትህን ቡልዶዘር ያፍርሰው፡፡ርስትህን ህንድ ይረሰው፡፡ሎተሪን ኣንተ ቁረጠው እጣውን ግን ለጠላትህ ይድረሰው ብሎ ይረግምሃል፡፡

‹‹እንደ ኢህአዴግ ያለ አሸባሪ የለም›› አብርሃ ደስታ (ከቂሊንጦ እስር ቤት)

$
0
0

መልዕክት ከቂሊንጦ እስር ቤት!

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

‹‹እንደ ኢህአዴግ ያለ አሸባሪ የለም›› አብርሃ ደስታ (ከቂሊንጦ እስር ቤት)

Abrha Desta“እዚህ እስር ቤት ውስጥ በሽብር ስም የገባ ሰው በፈጠራ ወንጀል እንደገባ ነው የሚታመነው፡፡ ስለዚህ የሽበር ክስ ተመስርቶባቸው የታሰሩትን ሰዎች ማንም ወንጀለኛ አድርጎ አይመለከታቸውም፡፡ በእርግጥም አሸባሪ የለም፤ የፈጠራ ክስ ነው ያሳሰራቸው፡፡ አሸባሪ አለ ከተባለም እንደ ኢህአዴግ ያለ አሸባሪ የለም፡፡
ነጻ መውጣት ያለበት ቡድን አለ፣ እሱም ኢህአዴግ ራሱ ነው፡፡ እኔ አልታሰርኩም፡፡ የታሰሩት ኢህአዴጎች ናቸው፡፡ እስር የአዕምሮ ነው፡፡ እኔ አዕምሮየ አልታሰረም፡፡ ነጻ ሰው ነኝ፤ ውስጤ በጣም ነጻነት አለው፡፡ የታሰሩት ኢህአዴጎች ናቸው፡፡

እኔ እስር ቤት እንድገኝ ያደረገኝ ወንጀል አይደለም፡፡ መቃወሜና ይህን ተቃውሞየን በጽፍም በፊት ለፊትም መግለጼ ነው፡፡ ይህን ደግሞ ብዙ ኢትዮጵያውያን ያውቁልኛል፡፡ ሌላው ቢቀር ጥቂት የህወሓት ሰዎችም ያለ መረጃ እንደታሰርኩኝ በማመን እስሩን እየተቃወሙ ይመስለኛል፡፡ አንድ ቀን ወደ ህሊናቸው ከተመለሱ ስህተታቸው በህዝብ ፊት ያዋርዳቸዋል፡፡”

‹‹በሐሰት ፕሮፖጋንዳ ሰው ማሳበድ ይፈልጋሉ›› ኦኬሎ አኳይ፣ የቀድሞው የጋምቤላ ክልል ፕሬዚዳንት

“የሆነ ያልሆነውን የሚያወራው በዙሪያዬ ቢሰበሰብም እኔ በጣም ሰላም ይሰማኛል፡፡ ካድሬዎች አብረውን እስር ቤት አሉ፡፡ ወሬ ነው የሚለቃቅሙት፡፡ ይህን ወሬ ሲለቃቅሙ ይቆዩና የሆነ ያልሆነውን እያወሩ፣ የሐሰት ፕሮፖጋንዳ እየነዙ ሊያሳብዱህ ይሞክራሉ፡፡ እስር ቤትም ችግር ፈጣሪዎች ራሳቸው ኢህአዴጎች ናቸው፡፡ እኔማ ሰላማዊ ሰው ነኝ፡፡ ጉዳዩንም ፍርድ ቤት ይጨርሰው፡፡ ፍትህ አገኛለሁ ብዬ ባላስብም ፍርድ ቤት የሚወስነውን እጠብቃለሁ፡፡
እየመጡ የሚጠይቁኝ ዘመዶች አሉኝ፡፡ ቤተሰቦቼ ደህና መሆናቸውን መረጃ አገኛለሁ፡፡ ስለዚህ ምንም የምረበሽበት ነገር የለም፡፡ በህግ የምከራከርባቸው ብዙ ነጥቦች አሉ፡፡ ቢሆንም ከውሳኔ በፊት ምንም ባልናገር ጥሩ ነው፡፡ እዚህ ድረስ እየመጡ ለሚጠይቁኝ ሁሉ ክብር አለኝ፡፡”

የአርቲስቶቻችን ክፍያ እና ግነቱ –እውን የአርቲስቶቻችን ክፍያ እንደሚባለው ነው? ነው ወይስ ያጋንኑታል?

$
0
0

የቁምነገር መጽሄት ትንታኔ

መነሻ

በሀገራችን የኪነ ጥበብ ሙያ ውስጥ በሙያው አንቱ የተባለ አንድ አርቲስት ከዓመታት በፊት በአንድ ፊልም ላይ እንዲተውን ጥያቄ ይቀርብለታል፡፡ ጥያቄውን ተቀብሎ በክፍያውም ተስማምቶ ፊልም ይሰራል፡ ፡ የፊልሙ ምረቃ እየተዘጋጀ ባለበት ወቅት ከፊልሙ ፕሮውዲውሰሮች መሀከል አንዱ ወደ እዚህ አንጋፋ አርቲስት መጥቶ ስለፊልሙ ምረቃ ሥነሥርዓት ዝግጅት ያጫውተዋል፡፡

ስለ ፊልሙ ምረቃ ዝግጅት ካብራራለት በኋላ ከፊልሙ የምረቃ ቀን ቀደም ብሎ በመገናኛ ብዙሃን ላይ ስለሚደረገው የማስታወቂያና ገበያ መጥሪያ እቅድ በመንገር የእሱም ትብብር በዚህ ረገድ እንደሚያስፈልግ ይነግረዋል፡ ፡ አንጋፋው አርቲስት ስለ እቅዱ ሁኔታ በጥሞና ሲያዳምጥ ከቆየ በኋላ ‹ታዲያ እኔ በዚህ በኩል ምን አስተዋፅኦ ላደርግ እችላለሁ?› የሚል ጥያቄ ያቀርብለታል፡፡

ፕሮውዲውሰሩ ፊልሙ የተሰራው በአነስተኛ በጀት ቢሆንም ከፍተኛ ወጪ እንደወጣበትና የፊልሙ ተዋንያንም ከፍተኛ ተከፋይ እንደሆኑ የሚገልፅ ማስታወቂያ በየሬዲዮና ጋዜጣ ላይ ለማስነገር አስበናል› ይለዋል፡፡ ‹እናስ?› የአንጋፋው አርቲስት ጥያቄ ነበር፡፡ ‹እናማ አንተም የፊልማችን ዋና መሪ ተዋናይ በመሆንህ የእስከ ዛሬውን የፊልም ክፍያ ሪከርድ እንደሰበርክና ከፍተኛ ክፍያ እንደተከፈለህ አስመስለን ለማስነገር ስላሰብን በዚህ በኩል እንድትተባበረን ነው› አንጋፋው አርቲስት ሁኔታው አልገባውም፡፡ ‹ስለሁኔታው ምናልባት ጋዜጠኞች ደውለው ቢጠይቁህ ግር እንዳይልህ ብዬ ነው› በማለት ሁኔታውን ቀለል አድርጎ ነግሮት ይለየዋል፡፡ ከቀናት በኋላ እሱም ባልሰማው ሁኔታ ‹የሀገራችን የፊልም ክፍያ ሪከርድ ተሰበረ› በሚል ርዕስ በአንድ የኤፍ ኤም ጣቢያ ላይ ስሙ ተጠቅሶ ፊልሙን ከሰራበት ክፍያ በሶስት እጥፍ ከፍ ያለ ገንዘብ እንደተከፈለው ተጠቅሶ ለህዝብ ይተላለፋል፡፡ ይህንን የሬዲዮ ወሬ የሰማችው የአርቲስቱ ባለቤት በማግስቱ ባለቤቷን ታኮርፈዋለች፡፡ ‹ምነው?› ሲላት ‹ለምንድነው በየፊልሞቹ ላይ ስትሰራ የሚከፈልህን ክፍያ ዋጋ የምትደብቀኝ?› ትለዋለች፡፡ አርቲስቱ ውሸት ያደገበት ነገር ባለመሆኑ ‹እንዴት ነው አንቺን የምዋሽሽ?› በማለት ጥያቄውን በጥያቄ ይመልሳል፡፡

በሬዲዮ የሰማችውን የሪከርድ ክፍያ ዜና ዋቢ አድርጋ ስትነግረው የሰራው ስህተት ቁልጭ ብሎ ታየው ፡፡ ለማስታወቂያና ለገበያ መሳቢያ በሚል በቃል ቀለል ተደርጎ የተነገረው ነገር ውሎ ሳያድር ትዳር ለማፍረስ የሚበቃ ወሬ መሆኑ ታወቀው፡፡‹እኔስ ለባለቤቴ እውነቱን በመናገርና በማስረዳት ችግሩን ተወጣሁት፤ በሬዲዮ አማካይነት የተዋሸው የኢትዮጵያ ህዝብንስ እንዴት ብዬ ነው የማሳውቀው?› የአንጋፋው አርቲስት አቤቱታ ነበር፡፡

የአርቲስቶች ክፍያ እንደተባለው ነውን?

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የአንድ የጥበብ ስራን ጥበባዊ ዋጋ ከክፍያ ጋር የተያያዘ መሆኑን ለማሳየት በመገናኛ ብዙሃን ዘንድ አንደ አንድ ማሳያ ተደርጎ የሚወሰደው ለሥራው የወጣውን ወጪ ከፍ አድርጎ በማቅረብ እየሆነ ነው፡፡ከፍተኛ ወጪ የወጣበት ሥራ ከፍተኛ ተመልካች አልያም አድማጭ ያገኛል በሚል ስሌት የሚቀርበው የክፍያ አሃዝ ግነት ጥበቡን ከመጥቀም ይልቅ እየጎዳው እንደውም ‹ይሄ ነው እንዴ ይህንን ያህል ወጪ ወጣለበት የተባለው ፊልም/ሙዚቃ?› እስከመባልና ለኪሳራ በር ሲከፍት ይታያል፡፡ ከፍተኛ በጀት ተመድቦላቸው የሚሰሩ ፊልሞችና የሙዚቃ ሥራዎች በሰለጠኑት ሀገራት ከፍተኛ ተቀባይነትና ገቢ ሲያገኙ ይስተዋላል፡፡ የወጣው ከፍተኛ ወጪም የስራውን ደረጃ ለመጠበቅ ስለመዋሉ ሌላ ተናጋሪ ሳይሆን ፊልሙ ወይም የሙዚቃ ሥራው አፍ አውጥቶ ሲናገር ይታያል፡፡ በኛ ሀገር ያለው እውነታ ግን ከዚህ በተገላቢጦሽ ያለ ይመስላል፡፡ ከፍተኛ ወጪ ወጣባቸው የሚባሉትና የሚነገርላቸው ፊልሞች እና ሙዚቃዎች ተገቢ የሆነ የተመልካችና የአድማጭ አትኩሮት ሲነፈጋቸው በአነስተኛ በጀት ብቻ ሳይሆን በጀማሪና ወጣት ተዋንያን የሚሰሩት ሥራዎች ገበያውን ሲቆጣጠሩት ይታያል፡፡

የማስታወቂያ ሥራ አንድን የጥበብ ስራ በሚፈለገው ደረጃ ወደ አድማጭና ተመልካች እንዲደርስ ለማድረግ የራሱ የሆነ አስተዋፅኦ ያለው ቢሆንም ሥራን በአግባቡ ሳይሰሩ በማስታወቂያ ሥራ ላይ ብቻ የማተኮሩ ሁኔታ ከፈረሱ ጋሪው እንዲቀድመው ምክንያት እየሆነ ነው፡፡ የተጋነኑ አልፎ አልፎም ሀሰተኛ የክፍያ ዜናዎች በይፋ በመገናኛ ብዙሃን ማስነገር ከጥቂት ዓመታት ወዲህ ጠቀሜታ እንደነበረው የሚናገሩ የፊልምና የሙዚቃ ፕሮውዲውሰሮች አሉ፡፡ በዚህ መንገድም ገና እያቆጠቆጠ ከነበረው የሀገራችን ፊልም ኢንዱስትሪ ላይ ጠቀም ያለ ገቢ የሰበሰቡ ፕሮውዲውሰሮች ስለመኖራቸው ይነገራል፡፡ ቁም ነገሩ ግን በዚህ መንገድ አንዱ ተጉዞ ተጠቃሚ ስለሆነ ብቻ ሁሉም ይህንን ጎዳና መከተል አለባቸው ወይ ? የሚለው ነው፡፡ ከዓመታት በፊት ከመቶ አስከ አምስት መቶ ሺህ ብር ወጪ እንደወጣበት ይገለፅ የነበረው የፊልም ስራ በአጭር ጊዜ ከአንድ ሚሊዮን እስከ ሃያ ሚሊዮን ብር ‹ወጣበት› ሲባል በየመገናኛ ብዙሃኑ ለህዝብ ሲተላለፍ እያደመጥን ነው፡፡ በሙዚቃው ዘርፍም እስከ አራት ሚሊዮን ብር ‹ተከፈለ› የሚሉ ዜናዎች ይነገራሉ፡፡ እውነታውስ?

ጉዳዩ በፊልምና ሙዚቃ ሙያዎች ውስጥ ጎልቶ ይታይ እንጂ በስፖርቱ ዘርፍም ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ‹እከሌ የተባለው ተጫዋች በዚህ ያህል ክፍያ ወደ እዚህ ክለብ ተዛወረ › የሚሉ ዜናዎችን በመገናኛ ብዙሃን ዘንድ ማድመጥ የተለመደ ሆኗል፡፡ ከተጫዋቾች ዝውውር ጋር ተያይዞ ያለውን ጉዳይ አሳሳቢነት መነሻ በማድረግም መፅሔታችን የሽፋን ርዕሰ ጉዳይ አድርጋው ነበር፡፡ በቁም ነገር መፅሔት 13ኛ ዓመት ቅፅ 13 ቁጥር 185 ላይ እንደገለፅነው እስካሁን ይፋ በተደረጉት መረጃዎች መሠረት በዚህ ዓመት ክለቦቹ በአጠቃላይ ለተጫዋቾቹ ወጭ ያደረጉት የገንዘብ መጠን 28 ሚሊዮን ብር ገደማ ነው፡፡ ይህ ቁጥር ቅዱስ ጊዮርጊስ፣ ኢትዮጵያ ቡናና ደደቢት ይፋ ያላደረጉትን የዝውውር ወጭ ያላካተተ ነው፡፡ የነዚህ ክለቦች ወጭ ሲደመር ከ40 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሚደርስ ይገመታል፡፡ ይሁንና ከዚህ ገንዘብ ውስጥ ሀገሪቱ የምታገኘው ምንም ጥቅም የለም፡፡፡ የዝውውር (የፊርማ) ወጭ በከፍተኛ ሁኔታ (ካላቸው አቅም አንጻር) የሚያወጡት ክለቦችም ሆኑ ወሳኝ ተጫዋቾቻቸውን የሚያጡት ክለቦች ከጥቅማቸው የባሰ ኪሳራን ያስተናግዳሉ፡፡
መንግስት በተጫዋቾቹ ላይ የሚቆርጠው ግብር እንደማንኛውም የመንግስት ሠራተኛ በደሞዛቸው ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ በአሳዛኝ ሁኔታ በኛ ሀገር ለአንድ ተጫዋች የሚከፈለው ደሞዝ ከፍተኛው በወር 3ሺ 500 ብር ነው፡፡ በ2 ዓመታት ውል ከ1 ሚሊዮን ብር በላይ ከንግድ ባንክ እግር ኳስ ክለብ የተከፈለው ፊሊፕ ዳውዝ የወር ደሞዙ ተብሎ ፔሮል ላይ የተቀመጠው ብር 2800 ብቻ ነው፡፡ መንግስት ግብር የሚቆርጠውም ከ1 ሚሊዮን ብር ላይ ሳይሆን ከወርሃዊ ደሞዙ ላይ ነው፡፡ የሌሎቹም ተጫዋቾች ተመሳሳይ ነው፡፡ ደመወዛቸውና ለፊርማ ተብሎ የሚሰጣቸው ክፍያ የማይገናኝ ነው፡፡ በዚህ ሂደት ሀገሪቱ ከእግር ኳስ ተጫዋቾች ዝውውር ማግኘት የሚገባትን ገንዘብ እያገኘች አይደለም፡፡ ለውጭ ሃገር ተጫዋቾች የሚከፈለው ገንዘብ ደግሞ ወደ ዶላር ተመንዝሮ ከሀገር የሚወጣ ብር መሆኑ ሲታሰብ ነገሩን የባሰ ያደርገዋል፡፡

የተሻለ ገቢን ለማግኘት ሲባል በማስታወቂያ ሰበብ የተሳሳተና ሀሰተኛ መረጃን ለህዝብ ማስተላለፍ ብቻ ሳይሆን የግለሰቦችን ዝና አላግባብ መገንባትም ከሙያ ስነ ምግባር አንፃር እንዴት እንደሚታይ ግልፅ አይደለም፡፡ በተለይም ግለሰቦች ባገኙት ልክ ግብር መክፈላቸው ተዘንግቶ ያላገኙትን ገቢ እንዳገኙ አስመስሎ ማስነገር ከህግ አንፃር እንዴት እንደሚታይ ያነጋግራል/ከኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን የስራ ኃላፊ ጋር የተደረገውን ቃለ ምልልስ በገፅ 8 ላይ ይመልከቱ /፡፡
የቁም ነገር መፅሔት የጋዜጠኞች ቡድን ባለፉት ዓመታት በመገናኛ ብዙሃን ስም ተጠቅሰው የተላለፉ የአርቲስቶች ክፍያ ዋጋዎችን ለመመርመርና እውነተኛነቱን ለማረጋገጥ ሙከራ አድርጓል፡፡ ሙከራው ራሳቸው አርቲስቶቹ በመገናኛ ብዙሃን ላይ ቀርበው የተናገሩትና በይፋ ያረጋገጡትን ይጨምራል፡፡
bedlu
አርቲስት ሔለን በድሉ
ይህቺ ወጣት ተዋናይት በተለያዩ ፊልሞች ላይ ስትሰራ ትታወቃለች፤ በቅርቡም በተጠናቀቀው ሰው ለሰው ድራማ ላይ ስትተውን የነበረችው ሔለን በቅርቡ ይወጣል ያለችው አዲስ ፊልም ላይ እንድትተውን 80ሺህ ብር እንደተከፈላት መፈራረሟን በጥር ወር 2006 ከታተመው ላይፍ መፅሔት ጋር ያደረገችው ቃለ ምልልስ ላይ ተናግራለች፡፡

አርቲስት መሐመድ ሚፍታ

መሐመድ ቀደም ሲል በሞዴሊንግ ሙያ ላይ የተሰማራና በተለያዩ መድረኮች ላይ የሚታይ ወጣት ነው፡፡ የዛሬ ሶስት ዓመት የተጠናቀቀው ገመና የቲቪ ድራማ ላይ በመተወን ወደ ፊልሙ ዓለም የተቀላለቀለው መሐመድ ወደ እውቅና ማማ ላይ የወጣው ወዲያውኑ ነው፡፡ መሐመድ ከፊልም ስራው በተጨማሪም የተለያዩ ድርጅቶችን ምርት ለማስተዋወቅ የማስታወቂያ ሞዴል ሆኖ የሚሰራ ሲሆን የዛሬ ዓመት ገደማ ‹ስማድል› ለተባለው ሞባይል ለሁለት ዓመት የማስታወቂያ ሞዴል ለመሆን 400 ሺህ ብር እንደተከፈለው በመጋቢት ወር በተላለፈ የታዲያስ አዲስ የሬዲዮ ፕሮግራም ላይ ቀርቦ ተናግሯል፡፡

ባለፈው ዓመት አጋማሽ ላይ ደግሞ ተቀማጭነቱ ሳውዲ አረቢያ የሆነ አንድ የንግድ ተቋም መሀመድን በ30 ሺህ ዶላር /600ሺህ ብር/ የማስታወቂያ ሞዴል ሆኖ እንዲሰራ መፈራረሙ በኢትዮፒካ ሊንክ ፕሮግራም ላይ ለህዝብ ተላልፏል፡፡
daniel
አርቲስት ሚኪያስ መሐመድ

ባለ ታክሲው በተሰኘው የመጀመሪያ ፊልሙ ተቀባይነትን ያገኘው ወጣቱ ተዋናይ ሚኪያስ መሐመድ በቅርቡ ተመርቆ ለእይታ በበቃው የመቅደስ በቀለ ማክዳ ‹ሊነጋ ሲል› ፊልም ላይ በመሪ ተዋናይነት ይሰራል፡፡ ከዚሁ ፊልም ምረቃ ጋር ተያይዞ በታዲያስ አዲስ የሬዲዮ ፕሮግራም ላይ የተላለፈው ዘገባ እንደሚያመለክተው ከሆነ ሚኪያስ መሐመድ በዚህ ፊልም ላይ ለመስራት ብር 400 ሺህ ተከፍሎታል፡፡ ይህንን ክፍያ ስለማግኘቱም ሚኪያስ በፕሮግራሙ ላይ ቀርቦ አረጋግጧል፡፡
helen berehe
ድምፃዊት ሔለን በርሄ
ወጣቷ አቀንቃኝ ሔለን በርሄ የመጀመሪያ አልበሟን ተከትሎ የተለያዩ ፊልሞችን የማጀቢያ ሙዚቃ እንድትሰራ ጥያቄ የቀረበላት አርቲስት ነች፡፡ በ2003 ዓ.ም ተመርቆ ለእይታ የበቃውን ‹ፔንዱለም› ፊልም ማጀቢያ ሙዚቃ የሰራችው ሔለን ለዚህ ነጠላ ዜማዋ ብር 100 ሺህ ከፕሮዲውሰሩ ቶም ፊልም ፕሮዳክሽን እንደተከፈላት በኢትዮፒካ ሊንክ ፕሮግራም ላይ ተናግራለች፡፡
የአርቲስቶቻችን ክፍያ እና ግነቱ – እውን የአርቲስቶቻችን ክፍያ እንደሚባለው ነው? ነው ወይስ ያጋንኑታል?
ዝናህ ብዙ ፀጋዬ

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በልዩ ልዩ ፊልሞች እና የቴሌቪዥን ድራማ ላይ በመስራት የሚታወቀው አርቲስት ዝናህብዙ በሙያው የፊልም ባለሙያ ባይሆንም በየተሳተፈባቸው ፊልሞች ላይ ብቃቱን እያሳየ ያለ አርቲስት ነው፡፡ ዝናህብዙ በፊልም ሥራ ላይ ብቻ ሳይሆን በማስታወቂያ ሥራዎች ላይም ከፍተኛ ተከፋይ ስለመሆኑ ይነገራል፡፡ በቅርቡም
መስከረም 10 ቀን 2007 ዓ.ም በኢትዮፒካ ሊንክ ፕሮግራም ላይ በቀጥታ ስልክ ላይ ቀርቦ ዘሚሊ ለተባለው ፋብሪካ ለአንድ ዓመት ማስታወቂያ ለመስራት አንድ መቶ ሺህ ብር፤ ለካንጋሮ ጫማ ፋብሪካ ማስታወቂያ ደግሞ ለሁለት ዓመት ኮንትራት 200 ሺህ ብር እንደተከፈለው ተናግሯል፡፡
jossy gebre
ድምፃዊ ዮሴፍ ገብሬ/ ጆሲ/

ዮሴፍ ገብሬ ጆሲ ኢን ዘ ሀውስ/ዮሴፍ በቤት ውስጥ/ የተሰኘ ፕሮግራም በኢቢኤስ ቲቪ ላይ የሚያቀርብ አርቲስት ሲሆን በቅርቡ ‹መቼ ነው› የተሰኘውን ሁለተኛ አልበሙን ለአድማጭ አቅርቧል፡ ፡ ጆሲ ይህንን አልበሙን ሰርቶ ለአድማጭ ለማቅረብ ከፍተኛ ወጪ ማውጣቱንና ከአልበሙ ሽያጭ ላይም 193ኛ ዕትም የተወሰነ ገቢውን የበጎ አድራጎት ስራ ለሚሰራ ድርጅት ለመስጠት መወሰኑን በገዛ ፕሮግራሙ ላይ በሰጠው ቃለ ምልልስ ላይ ተናግሯል፡፡ መስከረም 24 ቀን 2007 ዓ.ም በተላለፈው በታዲያስ አዲስ የሬዲዮ ፕሮግራም ላይ እንግዳ ሆኖ ቀርቦም ‹ዳሽን ቢራ› አልበሙን ሁለት ሚሊዮን ብር ስፖንሰር እንዳደረገውና እንደከፈለው ተናግሯል፡፡

አርቲስት /ሞዴል ሳያት ደምሴ

Sayat-Demissie-press-conferenceሳያት ደምሴ ወደ ኪነጥበቡ ዓለም ከመግባቷ በፊት የምትታወቀው በቁንጅና ውድድር
ላይ ተሳትፋ ‹ሚስ ኢትዮጵያ› የተሰኘውን ውድድር በማሸነፏ ነው፡፡ ሳያት ከቁንጅና ውድድሩ በኋላ መጀመሪያ ፊልም ከዚያም ወደ ሙዚቃው ዓለም ገብታ የመጀመሪያ አልበሟን ከሶስት ዓመት በፊት ለአድማጭ አቅርባለች፡፡ ህዳር 13 ቀን 2007 ዓ.ም የወጣው አዲስ አድማስ ጋዜጣ በፊት ለፊት ገፁ ላይ የሳያት ደምሴን ፎቶግራፍ በማድረግ ከአንድ የጀርመን ኩባንያ ጋር እጅግ ከፍተኛ በሆነ ክፍያ ፊልም ልትሰራ መሆኑን ይገልፃል፡፡ ሳያት (የጋዜጣው ዘገባ እውነት ከሆነ) በዚህ ፊልም ላይ በመስራቷ በሀገራችን ታሪክ ከፍተኛዋ የፊልም ተከፋይ ትሆናለች ይላል ጋዜጣው፡፡ ነገር ግን ሳያት በፊልሙ ላይ በመስራቷ ከፍተኛ ክፍያ ታገኛለች ተባለ እንጂ ምን ያህል ክፍያ እንደምታገኘ ጋዜጣው አልጠቀሰም፡፡ ክፍያውን የተመለከተ ህጋዊ የውል ስምምነት ከፊልሙ ፕሮውዲውሰሮች ጋር ስለማድረጓም የተባለ ነገር የለም፡፡

ጉዳዩን በተመለከተ አርቲስት ሳያት ደምሴን አግኝተን የተባለው ነገር እውነት ስለመሆኑና ስለ ውል ስምምነቷ ለመጠየቅ ያደረግነው ሙከራ/ ስልኳ ከአገልግሎት ውጪ ነው ስለሚል/ ለጊዜው አልተሳካልንም፡፡ ሳያት በማንኛውም ጊዜ የዜናውን ትክክለኛነት ሊያረጋግጥ የሚችል ህጋዊ መረጃ ካላት ለአንባቢያን ለማቅረብ የምንችል መሆኑን እንገልፃለን፡፡

የአርቲስቶቹ ምላሽ ምንድነው?

በጉዳዩ ዙሪያ ስማቸው የተጠቀሱ አርቲስቶችን በተመለከተ አግኝተን ለማነጋገር ሙከራ ያደረግን ሲሆን የአንዳንዶቹ ስልክ ዝግ ሲሆን የሌሎቹ ስልክ ምላሽ አይሰጥም ወይም አያነሱትም፡ ፡ ካገኘናቸው አርቲስቶች መሀከል የአንዳንዶቹ ምላሽ የሚከተለውን ይመስላል፡፡

አርቲስት ዝናህብዙህ ፀጋዬ ከሁለቱ ድርጅቶች ጋር የተደረገው ስምምነት ትክክል እንደሆነና የውሎቹ ማለቂያ ቀን ጊዜ በቅርቡ የሚጠናቀቅ በመሆኑ በስራውም ለውጥ እየታየበት በመሆኑ ከዚህ የተሻለ ክፍያ ለማድረግ እየተነጋገረ እንደሆነ ለቁም ነገር መፅሔት ተናግሯል፡፡ ያልተከፈለን ክፍያ አጋኖ ማቅረብ ህዝብን መዋሸት እንደሆነ የገለፀው ዝናህብዙ ከድርጅቶቹ ጋር የተደረገውን የውል ስምምነት ለማሳየት እንደሚችልና ከአንድ ሳምንት በኋላ ለመገናኘት ቀጠሮ ጠይቋል፡፡

አርቲስት መሀመድ ሚፍታ ከሁለቱ ድርጅቶች ማለትም ከስማድልና ከሳውዲው ኩባንያ ጋር የማስታወቂያ ስራ እንደሚሰራ አረጋግጦ ዝርዝር ምላሽ ለመስጠት ግን የፊልም ቀረፃ ላይ በመሆኑ መልሶ እንደሚደውል ገልፆ ስልኩ ተዘግቷል፡፡

የመገናኛ ብዙኃን ኃላፊነት

መገናኛ ብዙኃን በእውነት ላይ የተመሰረተ መረጃ ለህዝብ ማቅረብ ዋና ስራቸው እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ከዚህ አንፃር በጋዜጠኞች አማካይነት ለህብረተሰቡ የሚቀርቡ ዘገባዎች በመረጃ ላይ የተመሰረተና ተአማኒነት ያለው መሆን እንዳለበት መንገር ለቀባሪው ማርዳት ነው የሚሆነው፡፡ በጓደኝነትም ሆነ በትውውቅ በመገናኛ ብዙኃን ላይ የሚቀርቡ ተመሳሳይ መረጃዎች እውነት ሆነው ካልተገኙ የተአማኒነት ችግር እንደሚፈጥሩ ግልፅ ነው፡፡ በመሆኑም ትክክለኛና ህጋዊ አሰራሮች በተግባር መመልከት የማንኛውም ዜጋ ኃላፊነት መሆኑ ሳይዘነጋ ገንዘብንም ሆነ ሌሎች የግል ዝናን የሚያገዝፉ ዘገባዎች ለህዝብ ሲተላለፉ በማስረጃ ላይ የተመሰረቱ ሊሆኑ ይገባል፡፡
ህብረተሰቡ በመገናኛ ብዙኃን የሚቀርብለትን ዘገባ አምኖ የሚቀበለው ጋዜጠኞች ሁኔታውን ‹አረጋግጠው ነው› በሚል እምነት በመሆኑ ከክፍያ ጋር የተያያዙ ዘገባዎች በውሎች የታሰሩ መሆኑን ማረጋገጥ የጋዜጠኞች ሃላፊነት ነው፡፡ አለበለዚያ ለማስታወቂያና ለግል ዝና መገንቢያ በሚል ‹እከሌ ይህን ያልህ ተከፈለው› የሚለው ዜና የተአማኒነት ዋጋ ማስከፈሉ አይቀርምና ጋዜጠኞች ለሙያቸው ክብር ሊሰጡ ይገባል፡፡

በነገራችን ላይ እስከ ዛሬ ድረስ በመገናኛ ብዙኃን ላይ ከክፍያ ጋር ተያይዞ ስማቸው የተጠቀሱ አርቲስቶች የተባለው ነገር እውነት መሆኑን በማስረጃ ለማቅረብ ፍላጎቱ ካላቸው ዝግጅት ክፍላችን አሁንም በሩ ክፍት እንደሆነ ለመግለፅ እንወዳለን፡፡

የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ይግባኝ ለታህሳስ 30 ተቀጠረ * ዝዋይ እስር ቤት ሆኖ በፕላዝማ ችሎቱን ተከታትሏል

$
0
0

Temesgen Desalegn behindbar
(ዘ-ሐበሻ) ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ችሎት ያስገባው የይግባኝ ጥያቄን ለመስመት ስድስት ኪሎ የሚገኘው ፍርድ ቤት ተሰይሞ የነበረ ሲሆን ጉዳዩን ተመስገን እስር ቤት ሆኖ በፕላዝማ ተከታትሏል::

ከ’ፍሪ ተመስገን ደሳለኝ” የፌስቡክ ገጽ የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው ዛሬ ታህሳስ 23/2007 ጠቅላይ ፍረድቤት በዋለው ችሎት የጋዜጠኝ ተመስገን ደሳለኝን ይግባኝ ከሰማ በኋላ ጉዳዩ ለይግባኝ ያስቀርባል አያስቀርብም የሚለውን ለመወሰን ለታህሳስ 30/2007 ዓ.ም ቀጥሮ ሰቷል፡፡

ጋዜጠኛ ተመስገን ችሎቱን የተከታተለው ዝዋይ እስር ቤት ሆኖ በፕላዝማ ነው::

ከህወሓት ጉያ ስለ እናት ኢትዮጵያ –ህወሓቶች ስለ ህወሃት ሲናገሩ ––የጋዜጠኛ ሳዲቅ አህመድ የድምጽ ልዩ ዘገባ

$
0
0

(ክፍል አንድ) ህወሓት ለአማራ ህዝብ ስር የሰደደ ጥላቻ አለዉ፣ኦሮሞዎችን ነጥሎ የዘር ማጥፋት ዘመቻ ከፍቷል ይላሉ ህወሓቱ። ሳዲቅ አህመድ ልዩ ፕሮግራም አዘጋጅቷል።

(ሳዲቅ አህመድ)

(ሳዲቅ አህመድ)

ግርማ ሞገስ እና አዳነች ፍስሃዬ በምርጫ 2007 ዙሪያ –ቪ.ኦ.ኤ –ክፍል 1

$
0
0

ግርማ ሞገስ እና አዳነች ፍስሃዬ በምርጫ 2007 ዙሪያ – ቪ.ኦ.ኤ – ክፍል 1

Girma Moges


“ለኢትዮጵያ አንድነት በጽናት እንቆማለን” –ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም

$
0
0

(የፀሐፊው ማስታወሻ — ይህን ፅሁፍ በነጻነት ለሀገሬ ስም ለአማርኛ አንባቢዎቼ አቀርባለሁ። የነፃነት ለሀገሬ ትርጉሞች የረቀቁና የተጣሩ ናቸው። የነፃነት ለሀገሬን ድጋፍ በማግኘቴ ታላቅ ደስታና ክብር ይሰማኛል። ነፃነት ለሀገሬ ያልተዘመረለት/ያልተዘመረላቸው የኢትዮጵያ ጀግና/ጀግኖች ናቸው። ከፍተኛ ክብርና አድናቆቴን ለነፃነት ለሀገሬ አቀርባለሁ/አቀርብላቸዋለሁ !!! ትግሉ ይቀጥላል ለነፃነት ለሀገሬ!!!)

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም

ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ

የአፍሪካ አሜሪካዊ ደራሲ፣ ገጣሚ፣ የዳንስ ተወዛዋዥ፣ ተዋናይ እንዲሁም የሙዚቃ አቀንቃኝ የሆነችው ማያ አንጌሉ እንዲህ በማለት አውጃ ነበር፣ “የእኛን ጀግኖች እና ጀግኒቶች ማስታወስ እና መዘከር እንዴት ያለ ጠቃሚ ነገር ነው!“እኛም እነዚህንም የሀገር ጀግኖች እና ጀግኒቶች ተራ በተራ እያነሳን እናክብራቸው፣ እናወድሳቸው ምክንያቱም በአሁኑ ጊዜ ሀገሪቱ ከገባችበት ማጥ ውስጥ እንድትወጣ ለማድረግ እና ነጻነት እና ዴሞክራሲ በሀገራችን እንዲሰፍን እራሳቸውን ለመስዋዕትነት ያቀረቡ የሀገር ዕንቁዎች ናቸውና፡፡
Eskinder-Nega
1ኛ) እስክንድር ነጋ፡ የሀገሪቱ መናገሻ ከተማ ከሆነችው ከመሀል አዲስ አበባ በስተደቡብ በኩል ወጣ ብሎ በጥቂት ኪሎ ሜትሮች ርቀት ላይ ከሚገኘው በአስከፊናቱ ከሚታወቀው ከመለስ ዜናዊ የቃሊቲ የማጎሪያ እስር ቤት ታስሮ በመሰቃየት ላይ ከሚገኘው ከታዋቂው እና የኢትዮጵያ የፕሬስ ነጻነት ቀንዲል ከሆነው ከእስክንድር ነጋ እጅ በድብቅ በወጣ ደብዳቤው “በጽናት እቆማለሁ” በማለት ጽፏል፡፡

እስክንድር “በጽናት እቆማለሁ!” ሲል ዝም ብሎ ስለእራሱ ለመጻፍ ፈልጎ አይደለም፡፡ ሆኖም ግን በማጎሪያው እስር ቤት በመሰቃየት ላይ ስላሉት የስራ ባልደረባ ጋዜጠኛ ጓደኞቹ፣ ጦማሪያን፣ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች እና ስለሌሎች የፖለቲካ እስረኞች ዓላማም ጭምር ነው፡፡ ከዚህም በላይ አንድ የህሊና እስረኛ ወይም ደግሞ አንድ የፖለቲካ እስረኛ ብቻውን በጽናት ሊቆም አይችልም፡፡ ብቻውንም በጽናት ቆሞ ብቻውን ውጤት ሊያመጣ እይችልም፡፡ እንደዚሁም ደግሞ ኢትዮጵያ እራሱን ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ (ህወሀት) እያለ ከሚጠራው የአምባገነን ወሮበላ ስብስብ መዳፍ ስር ወድቃ በመማቀቅ ላይ እያለች ለዚህ እኩይ ምግባር አራማጅ ዘረኛ ድርጅት የአደባባይ እስረኛ ምርኮኛ ሆኖ በጸጥታ ስለሚገኘው ከ90 ሚሊዮን በላይ ለሆነው ኢትዮጵያዊ/ያት ወገኑ ሁሉ መልዕክት ለማስተላለፍ አስቦ የጻፈው መሆኑን በድፍረት መናገር እችላለሁ፡፡ ኢትዮጵያ ከወያኔ አምባገነን የወሮበላ ስብስብ ነጻ ለመውጣት እና እውነተኛ የመድብለ ፓርቲ ዴሞክራሲ ለመገንባት በጽናት ትቆማለች፣ እናም ታሸንፋለች!

እ.ኤ.አ በ2014 የተጠናቀቀውን አሮጌ ዓመት ምክንያት በማድረግ የእኔን ጀግና እስክንድር ነጋን እና የእኔን ጀግኒት ርዕዮት ዓለሙን እንደዚሁም በእነርሱም ስም ሁሉንም የፕሬስ ነጻነት የህሊና እስረኛ ጀግኖች እና ጀግኒቶች ኢትዮጵያውያን/ት የህሊና እና የፖለቲካ እስረኞች፣ ለምንም ለማንም ለድርድር ለማይቀርበው ነጻነት ምርኮኛ ለሆኑ ህዝቦች፣ ለነጻ እና ፍትሀዊ ምርጫ ለሚታገሉ፣ ለመልካም አስተዳደር እና ለሰብአዊ መብት መከበር ለሚታገሉ ወገኖች ሁሉ ደወል በመደወል ድምጼን ከፍ አድርጌ በመናገር አወድሳቸዋለሁ፡፡ እነርሱን በማወደስ በኩራት እንዲህ እላለሁ፣ “እንደ ፖለቲካ እስረኛነታችሁ በጽናት ቆማችኋል! እኛም በጽናት ቆመናል! ኢትዮጵያ በአምላክ ቸርነት እንደ አንድ ሀገር ብሄር በጽናት ቆማለች፡፡ የእኛን ነጻነት በመግፈፍ በባርነት እና በሁለተኛ ዜጋነት በማስቀመጥ ሲበዘብዙን እና ሲመዘብሩን ለመቆየት ዕቅድ አውጥተው የቆሙት ሆድ አምላኩ ፍጡሮች ጽናት እስከሚሟሽሽ እና ደብዛው እስከሚጠፋ ድረስ በጽናት እንቆማለን፡፡ ድል አድራጊነት ለእውነት በጽናት ለቆሙት ብቻ የተሰጠ ጸጋ ነው!“

ሸክስፒር እንዲህ በማለት ጽፈው ነበር፣ “ጥቂቶች ታላቅ ሆነው ተወልደዋል፣ ጥቂቶች ታላቅነትን በሂደት ይጎናጸፋሉ፣ ጥቂቶች ደግሞ ሁኔታዎችና ፈተና ታላቅነትን ያጎናፅፋቸዋል፡፡“ እንደዚሁም በተመሳሳይ መልኩ በእኛ ጀግኖች እና ጀግኒቶች ላይ እምነትን መጣል ይቻላል የሚል እምነት አለኝ፡፡ እንደ እስክንድር እና ርዕዮት ያሉ ዜጎች (ሁሉንም በኢትዮጵያ በማጎሪያው እስር ቤት በመማቀቅ ላይ የሚገኙትን ሌሎችን የህሊና እስረኞች ይወክላሉ) ጀግኖች እና ጀግኒቶች ናቸው ምክንያቱም በሀገሪቱ ላይ ፈታኝ የሆነ አደገኛ ሁኔታ በተፈጠረበት ጊዜ ጀግንነት በእነርሱ ላይ እምነቱን ጥሏልና፡፡ የእነርሱን የህይወት ዕጣ ፈንታ ፈልገው ባገኙበት ጊዜ እንደ አብዛኞቻችን ፊት ለፊት መጋፈጥን እርም ብለው አላስወገዱም ወይም ደግሞ እንደ ግመል ሽንት ወደኋላ አልተስፈነጠሩም፣ እንደዚሁም እንደ ተልባ ስፍር አልተንሸራተቱም፡፡ እነዚህ የጀግንነት ተምሳሌቶች የአሽከርነት ወይም የለማኝነት ባህሪን አልተላበሱም፡፡ እነዚህ የጀግንነት ቀንዲሎች ሌሎች ለከርስ ብቻ የቆሙት ሆዳሞች እንደሚያደርጉት ሁሉ ስብዕናቸውን በቤሳ ሳንቲም አልለወጡም፣ እንደሌሎች ቆርጦ ቀጥሎች አይደሉም፣ በጽናት ከቆሙለት ዓላማ አንዲት ጋት ወደኋላ አላፈገፈጉም፡፡ ላመኑበት ዓላማ በጽናት ቆመዋል፣ ይቆማሉም፡፡ በወሮበላ የጫካ አገዛዝ ነጻነት በሌለው አጥር የሌለው አስርቤት ውስጥ እየሰገዱ እና እየተንገዳወሉ ከመኖር ይልቅ ያመኑበትን ዓላማ በማራመድ ነጻነትን ይዞ በእስር ቤት መኖርን መርጠዋል፡፡

እስክንድር እና ርዕዮት በጉልበታቸው የሚንበረከኩ ቢሆን ኖሮ፣ ራሳቸውን ዝቅ አድርገው በማጎንበስ ቢለምኑ ኖሮ፣ ወንጀለኛ ተብለው የተፈበረኩባቸውን የሸፍጥ መሰሪ የውንጀላ ክሶች አምነው ይቅርታ ቢጠይቁ ኖሮ፣ የአሳሪዎቻቸውን እግር ቢልሱ እና ይቅርታ እንዲደረግላቸው ቢለምኑ ኖሮ ከማጎሪያው እስር ቤት ይወጡ ነበር፡፡ ከእነዚህ የዓላማ ጽናት ተምሳሌቶች ቀደም ብሎ አሁን በህይወት በሌሉት መለስ ዜናዊ እና ደቀመዝሙሮቻቸው አማካይነት ይቅርታ እየተደረገላቸው እንደወጡት በርካታ ወገኖች ሁሉ ያለምንም ችግር ከማጎሪያው እስር ቤት ይወጡ ነበር፡፡ በሸፍጥ የፍብረካ ወንጀል ክስ አሸባሪ በሚል የገዥው ወሮበላ ስብስብ የማደናገሪያ ታፔላ ተለጥፎባቸው በዝንጀሮው የይስሙላ ፍርድ ቤት 11 ዓመታት በእስራት እንዲቀጡ ተበይኖባቸው የነበሩት ጆሀን ፔርሰን እና ማርቲን ሽብዬ በተመሳሳይ መልኩ ይቅርታ ጠይቀው እንዲወጡ ነበር የተፈለገው፡፡

መለስ በጥቃት ሰለባዎቻቸው ላይ የውሸት የፍብረካ ውንጀላ የጥፋተኝነት ክስ እንዲመሰረት ካደረገ በኋላ በህዝብ ፊት በአደባባይ አምነው ይቅርታ ጠይቀው እንዲወጡ ማድረግ የመጨረሻው የውርደት መቅጫ ወይም ማሸማቀቂያ መሳሪያው ነበር፡፡ ይህንን እኩይ ድርጊት እ.ኤ.አ በ2005 የተካሄደውን ሀገር አቀፍ ምርጫ ተከትሎ ተከስቶ በነበረው ውዝግብ ምክንያት ሰብስበው በማጎሪያው እስር ቤት አጉረዋቸው በነበሩት በደርዘን በሚቆጠሩ የተቃዋሚ የፖለቲካ መሪዎች ላይ ተግብረውታል፡፡ በኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪያ በሆነችው ሴት የፖለቲካ ፓርቲ መሪ በነበረችው በብርቱካን ሚደቅሳ ላይ ሁለት ጊዜ ተግብረውታል፡፡ አቶ መለስ በማጎሪያው እስር ቤቱ እየተንገዳወሉ እና እየተልፈሰፈሱ ምንም ዓይነት ወንጀል ያልሰሩትን ንጹሀን ኢትዮጵያውያን/ት እንደ ሀቀኛ ሰው ለምነው በማታለል እያግባቡ እና እያሳመኑ ለአቶ መለስ እብሪተኛ ዓላማ ይቅርታን እንዲጠይቁ እና ከማጎሪያው እስር ቤት በይቅርታ እንዲወጡ የሚያደርጉ ካድሬዎች ነበረው፡፡ አቶ መለስ የራሱን ብልሹ አመራር እና ፖሊሲን የሚቃወሙትን ንጹሀን ዜጎችን ሁሉ በህዝብ ፊት በአደባባይ ማዋረድ ትልቅ እርካታን ይሰጠው ነበር፣ በንጹሀን ዜጎች ላይ የሚፈጽሙት ይህ እኩይ ድርጊት የእርሳቸውን በሰዎች ስቃይ እና ውርደት ላይ ጮቤ የሚረግጠውን የክፋት ነብሱን በደስታ ባህር ውስጥ እንዲዋኝ ያደርገዋል፡፡ ይቅርታ ጠይቀው የውርደት ካባን ተከናንበው እንዲወጡ የሚያደርገው የገዥው አካል ዲያብሎሳዊ ባህሪ አሁንም ቢሆን ለእስክንድር እና ለርዕዮት ክፍት ሆኖ እየጠበቀ ነው፡፡ ሆኖም ግን እነዚህ የጽናት ተምሳሌቶች ይጸየፉታል እንጅ አይፈልጉትም፡፡ እነዚህ የጽናት ባለሟሎች ባልሰሩት ጥፋት ላይ የሚቀርብላቸውን የይቅርታ ጥያቄ መሰረተ ቢስ በማለት እንዲህ የሚል መልዕከትን ያስተላልፋሉ፣ “ለአንድ ነጻ ለሆነ ወንድ ወይም ሴት ይቅርታ ልትሰጡ አትችሉም፣ የሞራል ስብዕናውም በፍጹም የላችሁም…የእናንተን ይቅርታ ተሸክማችሁ የትም መሄድ ትችላላችሁ፣ የእናንተ በቅጥፈት እና በሸፍጥ የተሞላ ተራ እና የወረደ የወሮበሎች ይቅርታ በአፍንጫው ይውጣ…!“

በአደጋ ምክንያት አካላቸውን ማንቀሳቀስ የማይችሉት እና ሽባ የሆኑት የሆሊውድ ፊልም ዋና አዘጋጅ የነበሩት ክርስቶፈር ሪቭ በአንድ ወቅት እንዲህ ብለው ነበር፣ “ጀግና በርካታ ውጥንቅጥ መሰናክሎች በበዙበት ወቅት እራሱን ፈልጎ የሚያገኝ እና ለፍትሀዊ ዓላማው በጽናት የሚቆም እና ለተግባራዊነቱ ያለማሰለስ የሚታገል ተራ ግለሰብ ነው፡፡“ እስክንድር፣ ርዕዮት እና ሌሎችም ዜጎች መሰናክሎች እና ችግሮች በበዙበት ወቅት እራሳቸውን ፈልገው ያገኙ እና ለፍትሀዊ ዓላማ በጽናት በመቆም ለስኬታማነታቸው በቆራጥነት ያለማወላወል የሚታገሉ ተራ ዜጎች ናቸው፡፡ ለዚህም ነው እስክንድር፣ ርዕዮት እና ሌሎች የኢትዮጵያ የፖለቲካ እና የህሊና እስረኞች ሁሉ ለእኔ ጀግኖች እና ጀግኒቶች የሆኑት፡፡ ሁሉም ለዓላማቸው እና ለዓላማዎቻቸው ስኬታማነት ብቻ በጽናት የሚታገሉ ናቸው፡፡

ድፍረት ጀግናነት እና ጀግኒነት የተዋቀሩበት የሞራል ብቃት ውጤት ነው፡፡ ይህንን ጉዳይ በማስመልከት ሮበርት ኤፍ ኬኔዲ በአንድ ወቅት እንዲህ ብለው ነበር፣ “የሞራል ድፍረት… በጣም ስቃይ የበዛባትን ወደ መልካም ነገር ለመለወጥ በለውጥ ፈላጊ ሰዎች አማካይነት የሚደረግ አንድ አስፈላጊ እና ዋና የጥራት መለኪያ ነገር ነው፡፡“ በእያንዳንዱ ጊዜ አንድ ሰው ለዓላማ ሲቆም፣ ወይም የሌሎችን ህይወት ለማሻሻል በጽናት ሲታገል ወይም ደግሞ ኢፍትሀዊነትን ሲዋጋ በተለያዩ በሚሊዮኖች በሚቆጠሩ ኃይል እና ድፍረት ማዕከል በመሆን የጭቆና እና የብዝበዛ ስርዓትን መንግሎ በመጣል ለተስፋ መለምለም የመሰረት ድንጋይ የሚሆን ማዕበላዊ መልዕክት ሊያስተላልፍ/ልታስተላልፍ ይችላል/ትችላለች፡፡

እስክንድር ነጋ፣ ርዕዮት ዓለሙ እና ሌሎችም ጀግኖች እና ጀግኒቶች የፖለቲካ እስረኞች እውነተኛ የሞራል ድፍረት አላቸው፡፡ እነዚህ የጽናት ቀንዲሎች ለፕሬስ ነጻነት እና ሀሳብን በነጻ የመግለጽ መብት፣ ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ እና ለሰብአዊ መበቶች መከበር በጽናት ቆመዋል፡፡ ለህግ የበላይነት መርሆዎች መከበር በጽናት ቆመዋል፡፡ ከህወሀት የወሮበላ ስብስብ ቡድን በተቃራኒው ቆመዋል፡፡ እነዚህ የነጻነት ቀንዲሎች 90 ሚሊዮን ለሚሆኑት ኢትዮጵያውያን/ት ወገኖቻቸው ተስፋን የሚያለመልም ሂደትን በመተግበር በጽናት ቆመዋል፡፡

አሮጌውን ዓመት 2014ን ደወል በመደወል ስንሸኝ እና አዲሱን ዓመት 2015ን እየተቀበልን ባለንበት በአሁኑ ወቅት ሁሉም አንባቢዎቼ እስክንድር ነጋን፣ ርዕዮት ዓለሙን፣ ወብሸት ታዬን፣ አንዷለም አራጌን፣ በቀለ ገርባን፣ አቡባከር አህመድን፣ የዞን 9 ጦማሪያንን ማለትም አጥናፍ ብርሀኔን፣ ዘላለም ክብረትን፣ በፈቃዱ ኃይሉን፣ አቤል ዋቤላን፣ ማህሌት ፋንታሁንን፣ ናትናኤል ፈለቀን፣ አስማማው ኃይለጊዮርጊስን፣ ተስፋለም ወልደየስን እና ኤዶም ካሳዬን ጨምሮ በማክበር እና በማመስገኑ እረገድ ለጀግንነታቸው እውቅና እንድንሰጥ እና እንድንዘክራቸው እንድትቀላቀሉኝ በትህትና እጠይቃለሁ፡፡ እነዚህ ጀግኖች እና ጀግኒቶች በአስር ሺዎች ለሚቆጠሩ ስም የለሾች፣ የማይታወቁ ትንታጎች፣ ያልተዘመረላቸው እና ያልተሰገደላቸው ጀግኖች እና ጀግኒቶች ለእኩልነት፣ ለፍትህ እና ለክብር ሲባል በዓለም ፍጹም አስቀያሚ በሆኑት በኢትዮጵያ የማጎሪያ እስር ቤቶች በመሰቃዬት ላይ ለሚገኙት ህዝቦች ጥቂት ምሳሌዎች ብቻ ናቸው፡፡ በአስከፊነቱ በሚታወቀው እና ቃሊቲ በመባል በሚጠራው እና በሌሎች በመለስ ዜናዊ የእስረኞች የማጎሪያ ቅርንጫፍ እስር ቤቶች በመላ ኢትዮጵያ በመማቀቅ ላይ ለሚገኙ ጀግኖች እና ጀግኒቶች በሙሉ ታላቅ ክብር እሰጣቸዋለሁ፡፡ ክብር እና ሞገስ ለእነርሱ ይሁኑ!

2ኛ) ርዕዮት ዓለሙ፡ አሁን በህይወት በሌሉት በመለስ ዜናዊ የሸፍጥ ወንጀል ፍብረካ የ14 ዓመታት እስራት የተፈረደባት እና የኢትዮጵያ የፕሬስ ነጻነት ቀንዲል ለሆነችው የ36 ዓመቷ ወጣት ጀግኒት ጋዜጠኛ ርዕዮት ዓለሙ ታላቅ ክብር አለኝ፡፡ ርዕዮት “የኢትዮጵያ እውነት ተናጋሪዋ እስረኛ” በመባል በዓለም አቀፍ ደረጃ ዕውቅናን አግኝታለች፡፡ ዓለም አቀፍ የጋዜጠኞች ተከራካሪ ኮሚቴ/Committee to Protect Journalists ባቀረበው ዘገባ መሰረት ርዕዮት የታሰረችው የህዳሴው ግድብ እየተባለ ለሚጠራው የግድብ ግንባታ ገንዘብ ለማሰባሰብ እያደረገ ባለው የተሳሳተ አካሄድ በገዥው የፖለቲካ ፓርቲ ላይ ጠንካራ ትችትን በመሰንዘሯ እና በወቅቱ የሊቢያ መሪ የነበሩት ኮሎኔል ሙአማር ጋዳፊ እና መለስ ዜናዊ አንድ ዓይነት ተመሳስሎ ያላቸው ከአንድ ባህር የተቀዱ አምባገነን መሪዎች ናቸው ብላ እውነትን አፍርጣ በመናገሯ ነበር ብሏል፡፡

3ኛ) ውብሸት ታዬ፡ የህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይን አጠቃላይ በሙስና መዘፈቅ አስመልክቶ በሚያዘጋጀው ጋዜጣ ትችት በማቅረቡ እና የጋዜጠኝነት የተመልካችነት ሙያውን በመስራቱ ብቻ በአምባገነኑ የወሮበላ ስብስብ ገዥ አካል የፍብረካ ወንጀል ክስ ተመስርቶበት የ14 ዓመታት እስራት ተፈርዶበት በማጎሪያው እስር ቤት እየተሰቃዬ ያለውን ጀግና ጋዜጠኛ እና አርታኢ ውብሸት ታዬን ከልብ አከብረዋለሁ፡፡ የውብሸት ታዬ የ5 ዓመት ልጅ የፍትህ እንዲህ የሚሉት ጨዋነት የተሞላባቸው ቃላት በአዕምሮዬ ላይ ሁልጊዜ ያቃጭላሉ፣ “በማድግበት ጊዜ እንደ አባቴ ሁሉ እኔም ወደ እስር ቤት ነው የምሄደው ማለት ነው?“

4ኛ) አንዷለም አራጌ፡ ወደ ማሪያው እስር ቤት ከመጋዙ በፊት የተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲ ኮከብ የአመራር አባል የነበረውን አንዷለም አራጌን አከብረዋለሁ፡፡ አንዷለም አራጌ ከአዲሱ የኢትዮጵያ የፖለቲካ መሪዎች፣ ጋዜጠኞች እና የሲቪል ማህበረሰብ ወጣት ዝርያ መካከል የሚመደብ ሲሆን በህዝቡ ዘንድ በስፋት የሚከበር እና ተቀባይነት ያለው የጽናት ተምሳሌት ወጣት የፖለቲካ ፓርቲ የአመራር አባል ነው፡፡ እ.ኤ.አ እስከ ሜይ 2010 መለስ ዜናዊ 99.6 በመቶ የህዝብ ድምጽ በማግኘት ምርጫውን በድል አድራጊነት አሸንፊያለሁ በማለት ባዶ ዲስኩር እስካሰሙበት የይስሙላ ሀገር አቀፍ ምርጫ ድረስ አንዷለም አራጌ ለዴሞክራሲ መገንባት እና ለህግ የበላይነት መከበር በጽናት በመቆም ሲታገል የቆየ ትንታግ ወጣት ነው፡፡ ግልጽ በሆነ ሀሳብ በመሞላት፣ ፍጹም የሆነ ምሁራዊ አንደበትን በመላበስ፣ ሊታመን ቀርቶ ሊታሰብ በማይችል ድፍረት የተሞላበት አካሄድ፣ በአስደማሚ አንደበተ ርትዑ ንግግር፣ እንደጦር በሚወጋ አመክኗዊ አቀራረቡ፣ ጉብዝና የተመላበት አቀራረብ፣ እውነታዎችን ፈልፍሎ በማውጣት እና ለእውነት በጽናት በመቆም የመለስ ዜናዊን የቴሌቪዥን የቅድመ ምርጫ ክርክር ተሰላፊ አሽከሮች በሚያቀርባቸው በእውነት ላይ የተመሰረቱ አመክኗዊ የክርክር ጭብጦች ባዶ መሆናቸውን ያጋለጠ እና መቅኖ ያሳጣ ጀግና የፖለቲካ ሰው መሆኑን በተግባር ያረጋገጠ ወጣት ነው፡፡ በእርግጠኝነት ይኸ ዓይነት ጽናትን የተላበሰ የትግል መስመር በቀጣይነትም ሊያዝ የሚገባው ጉዳይ ነው!

5ኛ) አብርሃ ደስታ፡ ወጣቱን፣ ፍርኃት የለሹን እና ልዩ ተሰጥኦ ያለውን ኢትዮጵያዊ ጦማሪ አብርሀም ደስታን ከልብ አከብራለሁ፡፡ አሁን በቅርቡ እ.ኤ.አ ጁላይ 7/2014 ወደ ማጎሪያው እስር ቤት ከመጋዙ በፊት በእራሱ ማህበራዊ ድረገጽ በለቀቀው ጽሁፍ አብርሃ ህወሀት እራሱ ሀሳብን በነጻ የመግለጽ መብት እንዲኖረው ጠንካራ የሆነ የክርክር ጭብጥ ሲያካሂድ ነበር፡፡ “የህወሀትን ካድሬዎች ጠላት ያለማድረግ ወይም ደግሞ በእኔ ድረገጽ እንዳይጠቀሙ ክልከላ የማላደርግበት ምክንያት የህወሀትን ምሁራዊ ክልከላ እና ኪሳራ ማወቅ ጠቃሚ እንደደሆነ ስለማምንበት ነው“ ብሎ ነበር፡፡ ሰዎች ምን ማለት እንደፈለጉ በማዳመጥ የአንድን ሰው የማሰብ እና ምክንያታዊነት ችሎታ መገምገም እንችላለን፡፡ የሚጽፉትን በማንበብ ማወቅ ይቻላል፡፡ ስለሆነም ካድሬዎቹ እንዲጽፉ እንፍቀድ፡፡ እራሳቸው ማን እና ምን እንደሆኑ እራሳቸውን እንዲገልጹ እንፍቀድ፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ምን ለማለት እደፈለጉ የሚጽፉትን እናንብብላቸው፡፡ እነርሱንም በሚገባ እንወቃቸው፡፡ እነርሱን ድል ለማድረግ በመጀመሪያ እነርሱን ደህና አድርገን ማወቅ ያስፈልጋል፡፡ የእራስህን ጠላት ማወቅ ጠቃሚነቱ የጎላ ነው፡፡ ለዚህም ነው ይህንን ድርጊት ማድረግ ያለብን!”

6ኛ) የዞን 9 ጦማሪያን፡ የዞን 9 ወጣት ጀግኖች እና ጀግኒቶች ጦማሪያንን አከብራቸዋለሁ፣ አወድሳቸዋለሁ፡፡ እነዚህ ወጣት ኢትዮጵያውያን እና ኢትዮጵያውያት በኮምፒውተር የመክፈቻ ቁልፎች በመጠቀም እና ለነጻነት ያላቸውን ቀናኢነት በግልጽ በማንጸባረቃቸው እራሱን ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ (ህወሀት) እያለ በሚጠራው የአሸባሪ የጨለማ ቡድን ስብስብ ልብ ውስጥ ሽብር ለቀቁበት፡፡ ይህንን ጉዳይ በማስመልከት ሂዩማን ራይትስ ዎች የተባለው ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት ወጣት ጦማሪያኑ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በአስቸኳ ከእስር እንዲለቀቁ በማሳሰብ እንዲህ የሚል ዘገባ አውጥቷል፣ “ስራቸውን በአግባቡ የሚሰሩትን ጦማሪያን እና ጋዜጠኞችን ለማጥቃት በሚል እኩይ ምግባር የጸረ ሽብር ህግ የሚባል የማደናገሪያ ህግ አዋጅ አድርጎ በማውጣት እና እራሳቸውን በዚያ ውስጥ በመወሸቅ በንጹሀን ዜጎች ላይ እያደረሱት ባለው ጥቃት በህገ መንግስቱ እና ሀሳብን በነጻ የመግለጽ ዓለም አቀፋዊ መብት ላይ የተደረገ ዘለፋ ነው፡፡ “አጥናፍ ብርሀኔን፣ ዘላለም ክብረትን፣ በፈቃዱ ኃይሉን፣ አቤል ዋቤላን፣ ማህሌት ፋንታሁንን፣ ናትናኤል ፈለቀን፣ አስማማው ኃይለጊዮርጊስን፣ ተስፋዓለም ወልደየስን እና ኤዶም ካሳዬን ምርጥ የኢትዮጵያ ወጣት የነጻነት ታጋይ ቀንዲሎች በመሆናቸው አከብራቸዋለሁ፣ አወድሳቸዋለሁ፡፡

7ኛ) በቀለ ገርባ፣ አቡባከር አህመድ እና ሌሎች የነጻነት ታጋዮች፡ ስለእምነት ነጻነት፣ በሰላማዊ መንገድ ስለመሰብሰብ መደራጀት እንዲሁም ሀሳብን በነጻ ስለመግለጽ መብት በመናገራቸው እና በመጠየቃቸው ብቻ ወንጀል እንደሰሩ ተደርጎ እራሱን ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ (ህወሀት) እያለ በሚጠራው አምባገነን የወሮበላ ስብስብ የጭቃ ጅራፍ እየተገረፉ እና እየተለበለቡ በመሰቃዬት ላይ የሚገኙትን በቀለ ገርባ፣ አቡባከር አህመድን እና ሌሎችንም ለነጻነት የሚታገሉ ትንታግ ኢትዮጵያውያን/ት ጀግኖች እና ጀግኒቶች ሁሉ ከልብ አከብራቸዋለሁ፣ አወድሳቸዋለሁ፡፡

በቀለ ገርባ የኦሮሞ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲ ንቅናቄ/Oromo Federalist Democratic Movement እየተባለ የሚጠራው የፖለቲካ ድርጅት ምክትል ሊቀመንበር እና በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የእንግሊዝኛ ቋንቋ መምህር የነበረ ነው፡፡ ለአሸባሪ ድርጅት ጽሁፍ አቅርቧል በሚል በቁጥጥር ስር እንዲውል ከተደረገ በኋላ የሸፍጥ ክስ ተመስርቶበት በዝንጀሮው የይስሙላ ፍርድ ቤት የ8 ዓመታት እስራት ተፈርዶበት በአሁኑ ጊዜ በማጎሪያው እስር ቤት በመማቀቅ ላይ የሚገኝ የነጻነት ታጋይ ነው፡፡ በቀለ ወያኔን ወደኋላ የሚንሸራተት እና ለማስተዳደርም አቅም ሳይኖረው በኃይል ለመግዛት ብቻ የተቀመጠ አስከፊ ድርጅት ነው የሚል ትችት ማቅረቡ የሚታወስ ነው፡፡ በህወሀት የጭቆና አገዛዝ አራት ዓይነት የዜግነት መደቦች አሉ በሚል የክርክር ጭብጡን እንዲህ አቅርቧል፣ “የመጀመሪያው የዜግነት መደብ በስልጣን ላይ ያሉትን እና መሬትን እንደ ጉልት ሽንኩርት በመቸብቸብ ላይ የሚገኙትን ያጠቃልላል፡፡ የሁለተኛው የዜግነት ምድብ ደግሞ መሬት የሚወስዱትን እና የሚቀበሉትን ያካትታል፡፡ ሶስተኛው የዜጎች ምድብ ደግሞ እነዚህ ህገወጥ ድርጊቶች ሲፈጸሙ በመታዘብ የተመልካችንትን ሚና የሚጫወተው የህብረተሰብ ክፍል ነው ይላል፡፡ የመጨረሻው እና አራተኛው የዜግነት ምድብ ደግሞ ዜጎች በዜግነታቸው ይዘውት የነበረውን አንጡራ ይዞታቸው የሆነውን መሬታቸውን እና ቤቶቻቸውን ኃይልን በመጠቀም የሚወሰዱባቸው ፍትህ ያጡ እና የነጡ ዜጎችን ያካተተ ነው፡፡“ በቀለ ገርባ በቁጥጥር ስር ውሎ ወደማጎሪያው እስር ቤት ከመጋዙ አንድ ቀን በፊት ህወሀት የሸፍጥ የአሸባሪነት ክስ በመመስረት እርሱን ለማጥቃት የጥቃት ዱለታ እያደረገ እንደሆነ ለአምነስቲ ኢንተርናሽናል ተወካይ ግልጽ አድርጎ ነበር፡፡

አቡባከር አህመድ ጠንካራ የሆነ የእምነት ነጻነት መከበር ተሟጋች ታጋይ ነው፡፡ አቡባከር ጥያቄዎቹን በተቀነባበረ መልክ አዘጋጅቶ የህግ የበላይነት አክባሪ እና አቀንቀቃኛ መሆኑን እንዲህ በማለት ገልጾ ነበር፣ “ማንኛውንም አመራር አልተቃወምንም፡፡ እኛ ጥያቄ አድርገን ያቀረብነው ህገመንግስቱ ይከበር የሚል ብቻ ነው፡፡ ሁላችንም በአንድ ድምጽ እያልን ያለነው ህገመንግስቱን ማክበር አለባቸው የሚሉን አካሎች እራሳቸው በእርግጠኝነት ህገመንግስቱን ማክበር አለባቸው የሚል ነው፡፡“

ከሁሉም በላይ ስም ለሌላቸው፣ እውቅናን ላላገኙት፣ በግልጽ ላልታወቁት እና ላልተዘመረላቸው በአስር ሺዎች ለሚቆጠሩት በኢትዮጵያ ለነጻነት ልዕልና፣ ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ እና ለሰብአዊ መብቶች መከበር በጽናት በመቆም ለሚታገሉት ጀግኖች እና ጀግኒቶች ኢትዮጵያውያን/ት የፖለቲካ እስረኞች ታላቅ ክብር እሰጣለሁ፣ አወድሳቸዋለሁ፡፡ ለተቀደሰው ዓላማቸው በጽናት በመቆም ጋሬጣውን ሁሉ ችለው በድል አድራጊነት ነጻነትን ያቀዳጃሉ!

እስክንድር ነጋ ድፍረትን በተቀላቀለበት ሁኔታ “በጽናት እቆማለሁ” በማለት አውጇል፣

እ.ኤ.አ ሜይ 2013 ወንድሜ እና የተከበረው ጓደኛዬ እስክንድር ነጋ እንዲህ የሚል ደብዳቤ ጽፎ ነበር፣ “በጽናት እቆማለሁ!“ ያ ደብዳቤ በአስከፊነቱ ከሚታወቀው ከመለስ ዜናዊ የቃሊቲ የማጎሪያ እስር ቤት በድብቅ ወጥቶ ነበር፡፡

“በጽናት እቆማለሁ!“ የሚለው ደብዳቤ 7 ቀላል አንቀጾችን/paragraphs አካትቶ የያዘ ብቻ ነበር፡፡ ሆኖም ግን በውስጡ ይዞት የነበረው መልዕክት ለሰባት እንዲያውም ለሰባት ሰባ ዓመታት የሚያቆይ መልዕክትን አጠቃሎ የያዘ ነበር፡፡ “በጽናት እቆማለሁ!“ የሚለው ደብዳቤ ለፍትህ አልባው አገዛዝ አልታዘዝም፣ አላጎበድድም፣ አልሰግድም፣ ጸጥ ብዬ አልገዛም የሚል ደፋርነትን የተላበሰ ደብዳቤ ነበር፡፡ ይህ ደብዳቤ በተስፋ የተሞላ ነው፡፡ ይህ ደብዳቤ ስሜትን የሚኮረኩር እና የነጻነት ትግሉን ሆ ብለን እንድንቀላቀል የሚገፋፋ ነው፡፡ ይህ ደብዳቤ ነብያዊ መንፈስን የተላበሰ ነው፡፡ ይህ ደብዳቤ ከልብ ውስጥ እጅግ በጣም ዘልቆ የተጻፈ ነው፡፡ ይህ ደብዳቤ በስሜታዊነት ሳይሆን ጥልቀት ባለው ሁኔታ የስነ ልቦናዊ የአስተሳሰብ ሂደቶችን ባካተተ እና ምክንያታዊነትን አጉልቶ በማሳየት የተዘጋጀ የምሁራዊ አንደበት መግለጫ ነው፡፡ ይህ ደብዳቤ ለቤተሰቡ፣ ለባለቤቱ እና ለልጁ በቀጥታ እንዲደርስ ሆኖ የተዘጋጀ ደብዳቤ ነው፡፡ ይህ ደብዳቤ ለኢትዮጵያ ህዝብ ሁሉ እንዲደርስ ተብሎ የተጻፋ ነው፡፡ ይህ ደብዳቤ ለኢትዮጵያ ዲያስፖራ ሁሉ እንዲደርስ ተብሎ የተጻፈ ነው፡፡ ይህ ደብዳቤ ለመጭዎቹ የኢትዮጵያ ትውልዶች በታሪክ የሚቀመጥ ተብሎ የተጻፈ ነው፡፡ ይህ ደብዳቤ ለነጻነት እና ለሰው ልጆች ክብር ሲባል የተጻፈ ነው፡፡ ይህ ደብዳቤ የአንድን ሰው የነጻነት ጥያቄ ጩኸት፣ አንድ ሰው የወለደውን ልጅ ማሳደግ እንዲችል ነጻ የመሆን መብት እንዲኖረው እንዲሁም አንድ ሰው ከባለቤቱ እና ከቤተሰቡ ጋር ነጻ ሆኖ የመኖር መብት እንዳለው ለማሳወቅ የተጻፈ ነው፡፡ ይህ ድብዳቤ ስለእያንዳንዱ ዜጋ መብት እና እያንዳንዱም ዜጋ በመረጠው ሙያ ሀገሩን የማገልገል መብት እንዳለው ለማሳወቅ የተጻፈ ነው፡፡ በመጨረሻም “በጽናት እቆማለሁ!“ አንድ ነገርን በውል ያመላክታል፡ እውነትን፡፡ በጽናት መቆም ማለት ስለእውነት እና ስለእውነት ብቻ በመቆም አንድን ሰው ነጻ ያወጣል ማለት ነው፡፡

ለጥቂት ጊዜ ፍቀዱልኝ እና የሚሰማኝን የእራሴን እምነት ልግለጽ፡፡ “በጽናት እቆማለሁ!“ የሚለውን ደብዳቤ ደጋግሜ ብዙ ጊዜ አንብቤዋለሁ፡፡ በአዕምሮዬ ላይ ያጫረውን ጥርጣሬ ለማስወገድ እንዲቻል በማለት ይህንን ደብዳቤ አንብቤዋለሁ፡፡ ከዚያ በኋላ ጥርጣሬዎቼ ሁሉ ሙጥጥ ጥርግ ብለው ጠፉ፡፡ ከዚያም በጽናት ቆምኩ፡፡ ወደ ነጻነት የሚወስደው መንገድ ረዥም፣ ብዙ ውጣ ውረድ ያለበት እና እጅግ በጣም አድካሚ እንደሆነ በተሰበረ ልብ ባለሁበት ወቅት ነበር ደብዳቤውን ያነበብኩት፡፡ በእኔ ፍጹም የሆነ እምነት የቱንም ያህል ለነጻነት የሚደረግ ጉዞ ረዥም አይደለም፡፡ ለሰኞ ትችቴ “ርዕስ የሚሆን ቃላትን ባጣሁበት ወቅት“ ነበር የእስክንድርን ደብዳቤ ያነበብኩት

ምንም የምለው ነገር የለም፡፡ ወዲያውኑ ሲኒየ እስከሚሞላ ድረስ በአዲስ ሀሳብ ተጥለቀለቅሁ፡፡ በየጊዜው ስለሁኔታው ባሰብኩ ቁጥር የእስክንድርን ደብዳቤ አነባለሁ እናም ስለሁኔታው አስባለሁ፡፡ የእስክንድር ድምጽ ጆሮ እያላቸው ለመስማት ለማይፈልጉት ወገኖች የጸጥታ ድምጽ ሊሆን ይችላል፡፡ ለእኔ የእርሱ ጸጥታ የሰፈነበት “በጽናት እቆማለሁ!“ የሚለው ድምጽ በየዕለቱ “በጽናት እቆማለሁ!“ “በጽናት እቆማለሁ!“ እያለ ደጋግሞ በህሊናዬ ያቃጭልብኛል፡፡

ለመሆኑ እስክንድር “በጽናት እቆማለሁ!“ ሲል ምን ማለቱ ነው? በቀላል አነጋገር በመለስ ዜናዊ የቃሊቲ የማጎሪያ እስር ቤት ቀን በቀን በእስር ላይ ሆኘ እገኛለሁ ለማለት ፈልጎ ነውን? እንደ እስክንድር፣ ርዕዮት እና ሌሎችም የነጻነት ታጋዮች የመሳሰሉ ሰዎች “በጽናት እቆማለሁ!“ ሲሉ በእርግጠኝነት ምን ለማለት ፈልገው ነው?

“በጽናት እቆማለሁ!“ በማለት እስክንድር ሲጽፍ ምን ለማለት እንደፈለገ ከእርሱ ጋር ለመነጋገር ወይም ጠይቆ ለመገንዘብ አስፈላጊ ነው ብዬ አላምንም፡፡ የእርሱ ቃላት ለእኔ ከምንም በላይ ጎላ ብለው የተጻፉ እና ግልጽ መልዕክት ማስተላለፍ የሚችሉ ናቸው፡፡ እስክንድር ማለት የፈለገው ዶ/ር ማርቲን ሉተር ኪንግ በአንድ ወቅት “ጽናት” በሚል ርዕስ እንደጻፉት ለማለት ፈልጎ ነው፡፡ ከግማሽ ምዕተ ዓመት በላይ ሰዎች ዶ/ር ማርቲን ሉተር ኪንግን ለምን ያህል ጊዜ ነው በጽናት የምንቆመው? ነጻነታችንን ለመቀዳጀት ምን ያህል ጊዜ መቆየት አለብን?” በማለት ይጠይቁ ነበር፡፡ (በእርግጥ ህዝቦች ከዚያ የበለጠ እንዲህ የሚል ትርጉም ያለው ጥያቄ መጠየቅ ይችሉ ነበር፣ “እንደዚህ ዓይነቱን ዋጋቢስ የሆነ ስርዓት የምንታገሰው እስከ ምን ያህል ጊዜ ነው?”) ዶ/ር ማርቲን ሉተር “ሩቅ አይሆንም” በማለት ነግረዋቸው ነበር፡፡ ለሌሎችም ጥያቄዎች አጭር እና ተገቢውን መልስ እንዲህ በማለት ሲሰጡ ነበር፡

በአሁኑ ጊዜ “ምን ያህል ጊዜ ይወስዳል?” የሚል ጥያቄ እንደምትጠይቁ በሚገባ እገነዘባለሁ…

በዛሬው ዕለት ከሰዓት በኋላ ልላችሁ እችላለሁ አጋጣሚው ምን ያህል አስቸጋሪ ቢሆንም፣ ሰዓቱ ተስፋ አስቆራጭ ቢሆንም ጊዜው በጣም ረዥም አይሆንም ምክንያቱም እውነት መሬት ከነካች በኋላ እንደገና ትነሳለችና፡፡

ምን ያህል ጊዜ? ረዥም ጊዜ አይሆንም ምክንያቱም የቱንም ዓይነት ውሸት እና ቅጥፈት ለዘላለም ሊኖር አይችልምና፡፡

እኮ ለምን ያህል ጊዜ? ረዥም ጊዜ አይሆንም ምክንያቱም የዘራኸውን ታጭዳለህና…

እኮ ለምን ያህል ጊዜ እኮ ነው የምንለው? ረዥም ጊዜ አይሆንም ምክንያቱም የሞራል ስብዕና ጠርዙ ረዥም ነውና፣ ሆኖም ግን ወደ ፍትህ ዘንበል ይላል፡፡

እስክንድር፣ ርዕዮት እና ሌሎች የነጻነት ታጋዮች ለምን ያህል ጊዜ ነው በጽናት የሚቆሙት? ኢትዮጵያ ለምን ያህል ጊዜ በጽናት መቆም አለባት? ረዥም ጊዜ አይሆንም፣ ሆኖም ግን ተስፋየለሽ ሰዓት ቢሆንም ቅሉ ረዥም አይሆንም ምክንያቱም ህወሀት የዘራውን ያጭዳልና፡፡ ድልአድራጊነት ጽናቱ ላላቸው ሰዎች ሁሉ የተረጋገጠ ነው፡፡

እስክንድር በደብዳቤው እንዲህ በማለት ጽፎ ነበር፣ “ግለሰቦች ሊቀጡ ይችላሉ፣ ሊሰቃዩ ይችላሉ (ኦ ልጀን እንዴት እዳጣሁት እና እንደናፈቀኝ) ከዚህም በላይ ሊገደሉ ይችላሉ፡፡ ሆኖም ግን ዴሞክራሲ ሊወገድ የማይችል የሰብአዊነት ዕጣፈንታ ነው፡፡ ዴሞክራሲን ማዘግየት ይቻል ይሆናል ሆኖም ግን ማሸነፍ አይቻልም፡፡“

ፍትህን ማዘግዬት ይቻላል፣ ሆኖም ግን በፍጹም ማሸነፍ አይቻልም፡፡ በሰብአዊ መብት ላይ ወንጀልን የፈጸሙ ወንጀለኞች በእመቤት በፍህ ላይ ያላግጣሉ፣ አፍንጫቸውን ይነፋሉ፣ አመልካች ጣታቸውንም ይቀስራሉ፣ ሆኖም ግን እመቤት ፍትህ በእጇ ላይ ምን እንዳለ እንጅ ምን ይዛ እንዳለች ማወቅ ይኖርባቸዋል፡፡ የሰው ልጅ ታሪክ የመጨረሻ መቆሚያ ጠርዙ የሰው ልጆች የሰብአዊ መብት ዕድል የሚከበርበት፣ የነጻነት እና ዴሞክራሲ መኖር፣ ከጭቆና ነጻ የመሆን፣ ከደናቁርት ወሮበላ ዘራፊ አምባገነኖች መላቀቅ፣ አንድ ሰው ከአምላኩ የተሰጡትን ተፈጥሯዊ የማሰብ፣ የመፍጠር እና ነጻ የሆኖ ሰብአዊ መብቶች ማከበር ነው፡፡

እስክንድር ለልጁ ያለውን ሀሳብ እንዲህ በማለት ገልጿል፣ “ኦ ልጀን እዴት እዳጣሁት እና እንደናፈቀኝ“ በማለት የተሰማውን ስቃይ አሳውቋል፡፡ የልጁ ስም ናፍቆት የሚባል ሲሆን ትርጉሙም “አንድን ሰው በመለየት ማጣት” የሚል ነው፡፡ ምን ዓይነት የሚገርም እና ነብያዊ የስም አወጣጥ ዘዴ ነው! ናፍቆት እ.ኤ.አ በ2005 ወላጆቹ በእስር ቤት ያለምንም ወንጀል 16 ወራት ታስረው ክሳቸው እንዲቋረጥ ተደርጎ ከተፈቱበት በመለስ ዜናዊ የቃሊቲ እስር ቤት ነው የተወለደው፡፡ አረመኔው እና ጨካኙ መለስ ዜናዊ ናፍቆት ገና ያልዳበረ ህጻን በነበረበት ጊዜ የህክምና እገዛ እንዳያገኝ በራሱ ትዕዛዝ እገዳ ጥለው ነበር፡፡ የመለስን ጣልቃገብነት በተመለከተ ያለው ማስረጃ አወዛጋቢ አይደለም፡፡ መለስ እስክንድርን እና ሰርክዓለምን ለመበቀል ሲል የቀናት እድሜ ብቻ የነበረውን ህጻን ልጃቸውን ለመግደል በጽናት ወስኖ ነበር፡፡ መለስ አስክንድርን እና ሰርክዓለምን ህጻን ልጃቸው በእስር ቤት ውስጥ እንዲሞት በማድረግ በሀዘን እንዲገረፉ ለማድረግ ፈልጎ ነበር፡፡ መለስ ጠላቶቸ ናቸው የሚለዉን ሰዎች በአደባባይ በህዝብ ፊት እንዲዋረዱ ማድረግ ብቻ ደስ የሚያሰኘው ሰው ነበር። ሆኖም ግን ከህዝብ እይታ ውጭም ቢሆን ጠላቴ የሚለዉን ንጹሀን ዜጎች ሲሰቃዩ እና መከራ ሲደርስባቸው ማየት ከምንም በላይ ደስ ያሰኘው ነበር ፡፡ እሱን በቅርብ የሚያውቁት ሰዎች ለዚህ ምስክርነት ይሰጣሉ፡፡ እስክንድር እና ሰርክዓለም በመጨረሻ በጻፉት ደብዳቤ ህጻን ልጃቸው በእግዚአብሄር ታምር ከሞት እንደተረፈ ይፋ አድርገዋል፡፡

አሁን በህይወት የሌሉት መለስ ዜናዊ እ.ኤ.አ ሴፕቴምበር 2010 በኒዮርክ ከተማ በኮሎምቢያ ዩኒቨርስቲ በመገኘት ንግግር እንዲያደርጉ ፕሮግራም ተይዞላቸው በነበረበት ወቅት እስክንድር እና ባለቤቱ ሰርክዓለም (በእራሷ መብት እና በምታሳየው ደፋር የጋዜጠኝነት ባህሪ እ.ኤ.አ በ2012 ከሴቶች የግንኙነት ተቋም/Women’s Media Foundation የጋዜጠኝነት ሽልማት አሸናፊ የሆነች) ሰውዬው በዩነቨርስቲው ተገኝቶ ንግግር እንዳያደርግ የሚቃወም ደብዳቤ ለዩኒቨርስቲው ፕሬዚዳንት ጽፈው ነበር፡፡ የተቃውሟቸውን መሰረትም እንዲህ በማለት ግልጽ አድርገው ነበር፣

ህጻኑ በሚወለድበት ጊዜ ከሚጠበቀው የክብደት መጠን በእጅጉ የቀነሰ መሆኑ ይኸውም ሊሆን የቻለበት ምክንያት ሰርካለም በአፍሪካ በአስከፊነታቸው ከሚታወቁት እስር ቤቶች መካከል ታስራ በመቆየቷ ምክንያት በአካል እና በስነልቦና የተጎዳች በመሆኑ የህጻኑን ህይወት ለማዳን ህይወት አድን የህጻናት ማቆያ የሚሆን ኢንኩቤተር በመጠቀም ኃላፊነት በጎደላቸው እና ምንም ዓይነት ደንታ በማይሰማቸው የበቀል መሪዎች ለሞት ተፈርዶበት የነበረው ህጻን በእስር ቤት ዶክተሮች ጥረት አዲስ የተወለደው ህጻን በእግዚአብሄር ታምር ሊድን ችሏል፡፡ (ክብር ምስጋና ለእግዚአብሄር ይሁን)፡፡

ሸክስፒር እንዲህ በማለት ጽፈዋል፣ “ሰዎች በህይወት ዘመናቸው ይኖሯቸው የነበሩት ጭራቃዊነቶች በህይወት ካለፉ በኋላም ይኖራሉ…“መለስ ከሰራቸው በርካታ ጭራቃዊነት ድርጊቶች መካከል አንዱ በአሁኑ ወቅት መለስ ከሞተ ከሁለት ዓመታት በኋላም በእስክንድር፣ ሰርክዓለም እና በናፍቆት መብት ድፍጠጣ ላይ የሰሯቸው ግፎች አሁንም እንዳሉ ናቸው፡፡ መለስ በሞተ ጊዜ የሱ ጭራቃዊ ድርጊታቸው የመጥፎዎች ሁሉ ተምሳሌት ሆኖ ጣላቴ ናቸው ብለው የሚያስቧቸውን ወገኖች ለማጥፋት እና የበቀል እርምጃ ለመውሰድ ከእባብ በበለጠ መልኩ በመተጣጠፍ አደገኛ ሁኔታን የሚፈጥር ሆኖ ቀጥሏል፡፡

እስክንድር እና ቤተሰቡ በእግዚአብሄር ኃይል ጽናቱን ሰጥቷቸዋል፡፡ መለስ የአምላክን ቁጣ ሊያመልጡ በፍጹም ሊያመልጡ አልቻሉም፡፡ እርግጠኛ ነኝ እስክንድር እንዲህ ይላል፣ “እራስህ ለመበቀል አታስብ፣ ሁሉንም ነገር ለአምላክ ቁጣ ብቻ ተወው ተብሎ እንደተጻፈው እራሱ ይበቀልልሀል፣ በቀል የእኔ ነው፣ ጌታ የሀጢያት ደመወዝን እኔ እከፍላለሁ ብሏልና፡፡“ የአምላክ ቁጣ በመለስ የበሰበሰው እና እየተፍረከረከ ባለው ስርዓት ላይ ጉብኝት እያደረገ ነው፡፡ እስክንድር አምላክ ሲፈቅድ ቤተሰቡን ሰብስቦ በሰላም እንደሚኖር ጥርጥር የለኝም፡፡

እስክንድር በደብዳቤው ላይ እንዲህ የሚል ጽሁፍ አስፍሮ ይገኛል፣ “የዳኝነት ሂደት ስርዓት በሌለበት፣ መከራ በተንሰራፋበት ዴሞክራሲ ባህሪ እና ጠቃሚነቱን ያጣ ነብስ የሌለው ባዶ ነገር ነው፡፡ እጣፈንታዬን እቀበላለሁ፣ እንዲያውም መልካም ዕድልን እንዳገኘ ሰው እታቀፈዋለሁ፡፡ በቅማሎች መሀከል ቢሆንም በእስር ቤት በሰላም እንቅልፌን እተኛለሁ፡፡ የእኔ አሳሪዎች ግን በሞቀ አልጋ ላይ ሚስቶቻቸውን አቅፈው በቤታቸው የሚተኙ ቢሆንም እንደ እኔ ሰላማቸው የተረጋጋ ይሆናል የሚል እምነት የለኝም፡፡“

በዚህ ዓይነት ሁኔታ ነው እግንዲህ ኔልሰን ማንዴላ ዕጣ ፈንታቸውን ተቀብለው በአፓርታይድ የዘረኝነት ስርዓት ለ27 ዓመታት በጽናት ታስረው በጽናት ለድል የበቁት፡፡ እንደማንዴላ እስክንድርም በማጎሪያው እስር ቤት ነጻነት ይሰማዋል፣ እናም ሰላሙ የተረጋጋ ነው፡፡ እስክንድር እንደ ማንዴላ የማይበገር ነብስ ያለው መሆኑን አሳይቷል፡፡ እንደ ማንዴላ የእስክንድር እራስ ደምቷል ሆኖም ግን አላጎነበሰም፡፡ እስክንድር በምንም ዓይነት ሁኔታ አልፈራም፡፡ እስክንድር የእራሱ ዕጣፈንታ ጌታ ነው፡፡ እስክንድር ማንዴላ እንዳደረጉት ሁሉ እንዲህ በሚሉት በዊሊያም ኤርነስት ሄንለይ ግጥሞች በመሳሳት አይበገሬነቱን አስመስክሯል፣

እኔን በሚሸፍን በድቅድቅ ጨለማ፣ ጥቁር የተናቀ ወድቆ የገለማ፣

ስብዕናውን ያጣ ከዋልታ እስከ ዋልታ፣ በዘረኛ ወጥመድ ተይዞ እሚፈታ፡፡

ለማይበገረው ደንዳናው ጽናቴ፣ አምላክን ላማስግን ሳለሁ በህይወቴ፡፡

በጭካኔው ማዕበል በአደገኛው ቦታ፣ አልንፈራገጥም አልጮህ በዝምታ፡፡

በእስር ቤት መታጎር ሆኖ ዕጣፈንታዬ፣ ጭንቅላቴ መድማት ቢሆን አበሳዬ፣

ካመንኩበት ጽናት ወይ ፍንክች ወይ ዝንፍ፣ ምድር ቢገለበጥ ሰማይ ቢያወርድ ዶፍ፡፡

ጭካኔ ቢበዛ ስቃይ ቢጠነዛም፣ ከቆምኩበት ጽናት አላጎነብስም፣

እግሮቸም አይርዱ እጀቸም አይዝሉ፣ ዓይኖቸም ፈጠዋል ሳይንቀዋለሉ፣

ጆሮዬም ይሰማል፣ ምላሴም ይቀምሳል፣ አፍንጫዬ ዋናው ነገርን ያሸታል፡፡

ስለዚህ ምን ገዶኝ ከዓላማዬ ጽናት ከቶ ማን አግዶኝ?

ከዚህ ከሰቆቃ ከዋይታ እና ከእንባ፣ ከዚህ ከጭካኔ ከጨለማው አንባ፣

ፍትህ ትፈልቃለች በፍቅር ተውባ፣ ነጻነት ይመጣል ከግፈኞች ጀርባ፣

እናም ለዘመናት የተከማቸው ግፍ፣ እኔን ሳያሸብር ይታየኛል ሲረግፍ፡፡

የማስገቢያው በሩ ይጣመም ይዘርጋ፣

የሸፍጥ ክስ ይምጣ እየተወራጋ፣

ቅጣቱ ይቆለል ይምጣ እየተላጋ፣

ለእኔ ጉዳይ አይደል ከቶ የለው ዋጋ፡፡

እንግዲህ እወቁኝ ከቶም እንዳትንቁኝ፣

ለዓላማዬ ጽናት ነብሴን የሰጠሁ ነኝ፡፡

ለዓላማዬ ጽናት ምንም ሳልረታ፣

ለዕጣ ፈንታ አዛዡ እሆናለሁ ጌታ፣

ከጌታ በመለስ ከፍጥረት ኃያሉ፣

ለነብሴ ዋስትና በምድር ሳር ቅጠሉ፣

አድራጊ ፈጣሪው እኔ ነኝ ሻምበሉ፡፡

ረዥም እድሜ ለእስክንድር፣ ለአይበገሬው አንበሳ!

ቪቫ እስክንድር አይበገሬው!

እስክንድር በደብዳቤው እንዲህ በማለት ጽፏል፣ “መንግስት በሚከተለው የፖለቲካ የሞራል ስብዕና ኪሳራ ምክንያት በተደጋጋሚ እና በማያቋርጥ ሁኔታ ሲዋሽ ቆይቷል፡፡ ሁሉም የታሪክ ታላላቅ ወንጀሎች የምንረሳቸው ካልሆነ በስተቀር በጊዚያቸው በነበረው የሞራል ስብዕና ላይ የተመሰረቱ ናቸው፡፡“

እስክንድር ስለምን እየጻፈ እንደሆነ በሚገባ አውቃለሁ፡፡ እ.ኤ.አ በ2006 “በፖሊስ መንግስት ሸፍጠኞች፣ ዓቃብያነ ህጎች እና ዳኞች የመሰረት ድንጋዮች“ በሚል ርዕስ ለመጀመሪያ ጊዜ ባዘጋጀሁት ባለ32 ገጾች ትንታኔ ትችት በወያኔ የዝንጀሮው የይስሙላ ፍርድ ቤት ላይ ሸንቋጭ ትችት አቅርቤ ነበር፡፡ ያ ትችት እ.ኤ.አ በ2005 የተካሄደውን ሀገር አቀፍ ምርጫ ተከትሎ ተፈጥሮ በነበረው ውዝግብ ቃሊቲ እየተባለ በሚጠራው እስር ቤት ታስረው ሲማቅቁ በነበሩት ወደ 130 ወይም ከዚያ በላይ የሚሆኑ ዋና የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች፣ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች፣ የሲቪል ማህበረሰብ ወትዋቾች፣ ጋዜጠኞች እና ሌሎች ወገኖች ላይ ተመስርቶ በነበረው የክስ ሂደት ላይ ሙያዊ የሆነ ትንታኔ በመስጠት ዓላማ ላይ ያነጣጠረ ነበር፡፡

የወያኔ የታዕይታ የፍርድ ሂደት ዓለም አቀፉን ማህበረሰብ ለማታለል የተደረገ የመድረክ ተውኔት ከመሆን ዕጣፈንታ የዘለለ አልነበረም፡፡ ያ ፍርድ ቤት ግልጽ በሆነ መልኩ የተዋረደ፣ በስብዕና ጥንካሪያቸው ሳይሆን በታዛዥ እና ሎሌነታቸው እየተመረጡ ለታዕይታ የተቋቋመ ችሎት ነበር፡፡ ያ ፍርድ ቤት የሸፍጥ ክስ እንዲመለከት፣ አጭበርባሪ ዓቃብያነ ህጎች የተመደቡለት፣ ምንም ዓይነት የፍትህ ስርዓት ሂደትን ያልተከተለ እና ውጤቱ ምን እንደሚሆን አስቀድሞ የታወቀ ይኸውም አንድ ነገርን ብቻ ለማድረግ ማለትም ፍትህን በግልጽ በአደባባይ ለማጨናገፍ የተቋቋመ የግፈኞች የይስሙላ የፍርድ ቤት ችሎት ነበር፡፡ የህወሀት የዝንጀሮ የይስሙላ ፍርድ ቤት እስከ አሁንም ድረስ አልተቀየረም:: እንግዲህ እስክንድር “መንግስት በፍትህ አደባባይ በህዝብ ፊት እየዋሸ ነው ያለው” ሲል ሌላ ሳይሆን ይህንን ማለቱ ነው …” የመንግስት ውሸት በዝንጀሮው የይስሙላ ፍርድ ቤት ችሎት መድረክ ላይ እውነትን አፈር ድሜ እያስበላ፣ የሰብአዊ መብቶች በመንግስት ስህተቶች እና ቅጥፈቶች እየተደፈጠጡ ያሉበት ሁኔታ ነው ዛሬ በኢትዮጵያ ያለው ቀውስ፡፡ “በአሁኑ ወቅት ያለው ቀውስ” በሚል ርዕስ በጀምስ ሩሴል ሎዌል ግጥሞች ውስጥ እንዲህ የሚሉትን የግጥም ስንኞች እንመልከት፣ “ውሸት ደረቱን ግልብጦ በችሎት ወንበሩ ላይ እና በስህተት እግሩን አንፈራጥጦ በዙፋኑ ላይ ተቀምጧል”:

ለነጻነት ተብሎ ተግባር ሲከናወን፣ በቆራጡ ትግል እውነት እውን ሲሆን፣

ነቢያዊ ደስታ ስናገኝ ሀሴትን፣ በምስራቅ በምዕራብ ስንል ዘብነን ዘብነን፣

ጽናትን ሰንቀን ከመከራው ጽዋ ከግፉ ተላቀን፣ ድል አድራጊ ሆነን በሲቃ ተውጠን፡፡

ደንታቢስ ቢመስለው ታላቁ ተበቃይ፣

ታሪክ ይዘግባል በምድር በሰማይ፣

በጽናት መቆም ነው ለወሳኙ ትግል፣

በበከተው ስርዓት ለመጎናጸፍ ድል

እውነት ለዘላለም በመስቀያ መድረክ፤

ውሸት ለዘላለም በዙፋኑ መድረክ፣

ሆነው አይቀጥሉም አያብልም ታሪክ፡፡

እናም ያ መስቀያ ይጠፋል ይበናል፣

ከጀርባው ባዘለው ጨለማ ማዕበል፡፡

በስውር ከሚያየው ከአምላክ ተነጥሎ፣

ደባን የሚፈጽም እውነት አስመስሎ፣

የአምላክ ሰይፍ ሲመዘዝ ሊሆን አከንባሎ፣

የት ይገባ ይሆን ያ ግም ዘባትሎ?

ወሮበላ ዘራፊዎች ለዘላለም በዙፋን ተኮፍሰው ሊኖሩ ይችላሉን? በፍጹም!

እስክንድር በደብዳቤው እንዲህ በማለት ጽፏል፣ “አሰልችው እና የተለመደው የሸፍጥ የፍርድ ሂደት ምንም ዓይነት ፋይዳ ያለው ለውጥ አያመጣም፡፡ ሆኖም ግን በአንድ ወቅት ክርስቶፎር ሂቸንስ እንደገለጹት የሚያስከትለው ‘የኢምክንያታዊነት ስብስብ እና የንቀት ደረጃን ከማሳየት ያለፈ እርባና የለውም‘“ ለማለት የተፈለገው ይህ ጉዳይ ያለጥፋቱ በግፍ ታስሮ እንደነበረው ንጹህ ፈረንሳያዊ ሻምበል እንደ ድሬይፈስ ያለ የኢትዮጵያዊ ጉዳይ ነው፡፡ በዚህ ፈታኘኝ ወቅት ብቻ ነው የበከተ እና የበሰበሰውን አምባገነናዊ ስርዓት ገርስሶ መጣል የሚያስፈልገው እንጅ ጥቃቅን ነገሮችን በማከናወን ታጋሽነትን የማራዘም ጨዋታን በመጫወት ከቶውንም ሊሆን አይችልም፡፡

እስክንድር የፈረንሳይ ጦር አዛዥ እንደነበሩት እንደ ሻምበል አልፍሬድ ድሬይፈስ በሀሰት ክስ ተመስርቶባቸው እ.ኤ.አ በ1894 በሚስጥራዊ የጦር ፍርድ ቤት በሀገር ክህደት ወንጀል በሚል የጥፋተኝነት ውሳኔ ተላልፎባቸው እንደነበሩት ንጹህ ዜጋ ማለት ነው፡፡ የፈረንሳይ ዕውቅ ደራሲ የነበሩት ኢሚሌ ዞላ ታዋቂ ደብዳቢያቸውን በብዕራቸው በመጻፍ እንዲህ ብለው ነበር፣ “አይሁዶችን ለማግለል ሲባል እና በሀሰት ወንጅሎ ጥቃት ለመሰንዘር በመገፋፋት በድሬይፈስ ላይ የሀሰት ክስ በመመስረቱ ምክንያት የፈረንሳይን ፕሬዚዳንት እና የፈረንሳይን መንግስት ከስሻለሁ፡፡“ ድሬይፈስ ምንም ሳያቅማሙ እና ሳይሸበሩ በጽናት ቆመው በመከራከራቸው በመጨረሻ ከሀሰት ውንጀላው ሙሉ በሙሉ ነጻ ሆነው ተሰናብተዋል፡፡

በጊዜ ሂደት እስክንድርም እንደ ሻምበል ድሬይፈስ ነጻ ሆኖ ይወጣል፡፡ እራሱ በሰራቸው በሰው ልጆች ላይ የተፈጸሙ ወንጀሎች ጉሮሮውን ታንቆ ባለው አምባገነን እስክንድር በሀሰት የፍብረካ ወንጀል በሀገር መክዳት በሚል የሸፍጥ ውንጀላ ታስሮ በማጎሪያው እስር ቤት ውስጥ በመማቀቅ ላይ ይገኛል፡፡

እስክንድር የጽናት ተምሳሌት! በግፈኞች ቢከሰስም በጽናት የቆመ ጀግና!

እስክንድር በደብዳቤው እንዲህ በማለት ጽፎ ነበር፣ “…እ.ኤ.አ በ1930ዎቹ ስታሊኒኒያዊ አምባገነኖች ሚስጥር እንድታወጣ ለማስገደድ አልነበረም የሚገርፉህ እና የሚያሰቃዩህ፣ ሆኖም ግን የሀሰት መግለጫ ለማውጣት እንዲመቻቸው በሚስጥር ህገወጥ ነገር ለመስራት ተባባሪ እንድትሆን ነበር ለማግባባት የሚሞክሩት፡፡ ለዚህም ነው እንግዲህ በኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት ቀውስ ዋና መሰረት ሆኖ የሚታየው፡፡ እንደዚሁም 30 ዓይነት ተደጋጋሚ ድፍረት የተሞላባቸው የፍርድ ሂደቶች ቢካሄዱም ፍትህን ከማዛባት ባለፈ ነጻነትን ሊያጎናጽፍ እንደማይችል ባለስልጣኖች አልተረዱትም፣ በዚህም መሰረት ግፈኞች ከታሪክ ትምህርትን አልቀሰሙም፣ እንዲያውም በታሪክ ተጽፍ ከተያዘው ስሀተት በበለጠ መልኩ ወንጀልን በመስራት በሰብአዊ መብት ድፍጠጣ ወንጀል ባህር ውስጥ እስከ አንገታቸው ድረስ ሰምጠው በመዋኘት ላይ ይገኛሉ፡፡“

ስታሊን በአንድ ወቅት የአንድ ሰው መሞት አሰቃቂ ነው፣ የሚሊዮኖች ሞት ግን የቁጥር ጉዳይ ነው ብለው ነበር፡፡ ሆኖም ግን ስታሊን በሚሊዮን የሚቆጠሩ ህዝቦቻቸውን እራሳቸው አልገደሉም፡፡ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ህዝቦች ጆሮ ዳባ ልበስ ብለው ጻጥ ካላሉ እና የሀሰት ውንጀላን ለመፈብረክ በሚስጥር የሚተባበሩ ሰዎች እስከሌሉ ድረስ ጭራቃዊነት ድርጊት በንጹሀን ዜጎች ላይ በፍጹም አይፈጸምም፡፡ ጭራቃዊነት ድርጊት ሲፈጸም እየተመለከቱ እና ይኸ ለእኔ ጉዳዬ አይደለም እያሉ በወገኖቻቸው ስቃይ ላይ የሚሳለቁ ህሊናየለሽ ወገኖች ሁሉ ለሸፍጥ ተግባር በሚስጥር ለሚሰሩ መሰሪ ጭራቃዊ ተግባሮች ሁሉ ተባባሪዎች መሆናቸውን መገንዘብ አለባቸው፡፡ እንደዚሁም ደግሞ ቢዝነስ እና የፖለቲካ ተግባራት መጣመር የለባቸውም የሚሉ ወገኖች ሁሉ በሚስጥር ለሚተገበሩ የጭራቃዊነት ተግባራት ተባባሪዎች ናቸው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ጭራቃዊነት ድርጊት ሲፈጸም እየተመለከቱ አላየሁም ብሎ መካድ ከጭራቃነት ጋር በሚስጥር የሸፍጥ ዱለታ ተባባሪ እንደሆኑ ሊገነዘቡ ይገባል፡፡

እንደዚሁም ደግሞ ጭራቃዊ ድርጊትን ከማውገዝ እና ከመታገል አልፎ ይቅርታ መጠየቅ እና ጭራቃዊነትን ለተፈጻሚነቱ ትክክለኛነት ለመስበክ መሞከር ከጭራቃዊነት ጋር በሚስጥር ተባብሮ በንጹሀን ዜጎች ላይ ደባን የመስራት ተባባሪነት መሆኑን በውል ሊገነዘቡ ይገባል፡፡ እንደዚሁም ሆን ብለው ያላወቁ መስለው ከጭራቃዊነት ድርጊት ሲፈጸም ዝም ብለው የሚመለከቱ ሁሉ በሚስጥር ጭራቃዊ ድርጊትን ለመፈጸም ተባባሪዎች ሆነው እንደቀረቡ ሊያውቁ ይገባል፡፡ ከዚህም በላይ “ምንም ዓይነት ጭራቃዊነት አላየሁም፣ ምንም ዓይነት ጭራቃዊነት አልሰማሁም፣ ምንም ዓይነት ጭራቃዊነት አልተናገርኩም” የሚሉ መርሆዎችን እያራመዱ ሰው ሳይሆኑ እውነተኛ ሰው መስለው የሚኖሩ አስመሳዮች ሁሉ በሚስጥር ጭራቃዊነት ድርጊትን እየፈጸሙ እንዳሉ በውል ሊገነዘቡ ይገባል፡፡

እስከንድር በደብዳቤው ላይ እንዲህ በማለት ጽፏል፡ “ ለምንድን ነው የቀረው ዓለም ህዝብ ጉዳዩ የሚሆነው? ይህንን ጉዳይ በማስመልከት ሆራስ በተሻለ መልክ እንዲህ በማለት ገልጸውት ነበር፣ ‘ስሙን ብቻ ቀይር፣ እናም ይህ ታሪክ የአንተም ታሪክ ይሆናል‘ ምን ጊዜም ፍትህ ሲጓደል የእኛ የሰብአዊ ፍጡርነት ስብዕናም አብሮ ይጎድላል፡፡“

እስክንድር ከሮማን ታላላቅ ገጣሚዎች አንዱ የሆኑትን እና በተስፋ በተሞሉ ቃላታቸው ታዋቂ የሆኑትን የሆራስን አባባል ወስዶ ተጠቅሞበታል፡፡ እስክንድር የናዚን ወደ ስልጣን መምጣት ተከትሎ የጀርመን ምሁራን ዝምታን መምረጣቸውን አስመልክቶ ፓስተር ማርቲን ኒሞለር ፍርሀታቸውን የገለጹበትን በመጥቀስ ጩኸቱን አሰምቷል፡፡ ለምንድን ነው ማንም በሌላው ጉዳይ ላይ የሚያገባው? ምክንያቱም ነገ አንተም ተረኛ ነህ! ባለወር ባላሳምንት ነው ነገሩ፡፡

በመጀመሪያ በኮሙኒስቶች መጡባቸው፣ እናም ዝም አልኩ ምክንያቱም ኮሙኒስት አልነበርኩምና፡፡ በቀጣይነትም በሶሻሊስቶች ላይ መጡባቸው፣ አሁንም ምንም ሳልናገር ዝም አልኩ ምክንያቱም ሶሻሊስት አልነበርኩምና፡፡ ከዚያም በሰራተኛ ማሀበራት ላይ መጡባቸው፣ አሁንም ምንም ሳልተነፍስ ዝም አልኩ ምክንያቱም የሰራተኛ ማህበራት አባል አልነበርኩምና፡፡ በመጨረሻም በእኔ በእራሴ ላይ መጡብኝ፣ ሆኖም ግን ለእኔ የሚጮህልኝ ማንም አልነበረም፡፡

እስክንድር እንዲህ በማለት ጥያቄ ያቀርባል፣ “ሌላው ዓለም ለምንድን ነው የሚያገባው?“ እኔ ደግሞ እንዲህ በማለት እጠይቃለሁ፣ “ኢትዮጵያውያን/ት ስለእስክንድር፣ ስለርዕዮት እና ስለሌሎች የፖለቲካ እስረኞች ጉዳይ የሚያገባቸው ለምንድን ነው?“ በመለስ ዜናዊ ውስብስብ እስር ቤት ታጉረው በመሰቃየት ላያ ስላሉት ለእስክንድር፣ ለርዕዮት እና ለሌሎች የፖለቲካ እስረኞች የሚናገርላቸው እና የሚጮህላቸው ሰው አለን?

የወያኔ ወሮበላ ስርዓት ወገኖቻችንን አሳር እና ፍዳ እያሳየ ነጻነታቸውን ገፍፎ ሲገዛ እያዩ ዝም በማለታቸው እና ጥቂቶች ሆዳሞች ደግሞ በርካሽ ጥቅመኝነት ህሊናቸውን ለገንዘብ ሸጠው ወሮበላው የወያኔ ስብስብ ወደ ስልጣን እንዲመጣ በመተባበር እና አሁንም በዚሁ አምባገነንነቱ እንዲቀጥል በሚስጥር እየረዱ በመሆናቸው በኢትዮጵያ ምሁራን ላይ ጣቴን ቀስሬባቸዋለሁ፡፡ ከስሻቸዋለሁም!

የጀግኖች እና የጀግኒቶች ረዥም ጉዞ ለነጻነት፣

እስክንድር በደብዳቤው ላይ እንዲህ የሚል ጽሁፍ አስፍሯል፣ “ ከዋሻው ጭፍ ብርሀን ይታየኛል፡፡ ከዚያ ለመድረስ ብዙ ጊዜ ሊወስድም ላይወስድም ይችላል፡፡ በየትኛውም ዓይነት መንገድ ነገሮች ቢፈጸሙ እኔ በጽናት እቆማለሁ!“

“የድብቁ ኃይል/The Power of Myth” እና የሌሎች ወጥ የሆኑ ስራዎች ታዋቂ የሆኑት ደራሲ ፕሮፌሰር ጆሴፍ ካምፕቤል የጀግናን ጉዞ ከብርሀን ወደ ጨለማ ከዚያም ተመልሶ ከጨለማ ወደ ብርሀን የሚያደርገውን ጉዞ ገልጸዋል፡፡ ጉዞው ጽናትን እና እልህ አስጨራሽ የሆነ ታጋሽነትን የሚጠይቅ አድካሚ ጉዞ ነው፡፡ ጀግና ፈታኝ የሆነ ነገር መምጣቱን ምልክት እስከሚያገኝ ድረስ እና በዚህች ብቸኛ እና በውል ባልታወቀች ዓለም ላይ ድብቅ ኃይሎች እና ድርጊቶች እስከሚከሰቱ ድረስ እንደማንኛውም ተራ ሰው ነው የሚኖረው፡፡ ጀግናው ጥሪውን የሚቀበል ከሆነ ሙከራዎችን እና መከራዎችን በድብቁ ዓለም ላይ ብቻውን ወይም ደግሞ ከሌሎች ጋር ሊጋፈጥ ይችላ፡፡ የእርሱን ውስጣዊ ባህሪ ሊፈትኑ የሚችሉ ከፍተኛ የሆኑ ተግዳሮቶች ሊገጥሙት ይችላሉ፡፡ ጀግናው የገጠመውን ፈተና ሊቋቋም ከቻለ የምሁርነት እና የእራስ እውቀት ታላቅ ስጦታን ይሸለማል፡፡ ጀግና ከዚህ ታላቅ ስጦታ ጋር ወደ ተራው ህዝብ ዘንድ ለመመለስ ወይም ላለመመለስ መወሰን አለበት፡፡ በሚመለስበት መንገድ ላይ በጣም በርካታ የሆኑ ፈተናዎችን ይጋፈጣል፡፡ ጀግናው ስኬታማ የሚሆን ከሆነ ታላቁን ስጦታ በመጠቀም ዓለም ለማሻሻል አጋጣሚውን ሊጠቀምበት ይችላል፡፡ ስለሆነም ካምፕቤል እንዲህ በማለት ጽፈው ነበር፣ “የዓለምን ከጥፋት ለማዳን ጉዞ ላይ አይደለንም፣ ሆኖም ግን የእራሳችንን ከጥፋት ለማዳን ነው፡፡ ይህንንም በማድረግ ዓለምን አናድናለን፡፡ የጠንካራ ሰው ተጽዕኖ ጠንካራ ነገርን ይሰራል፡፡ ”

እንግዲህ እንደዚህ ባለ ጉዞ እና አስገራሚ ሁኔታ ነው እስክንድር፣ ርዕዮት እና ሌሎች አይበገሬ የዓላማ ጽናት ሰዎች በወንጀለኛው የመለስ ዜናዊ እስር ቤት ሆነው እየታገሉ ያሉት፡፡ ያላቸውን ታላቅ የጽናት ስጦታ በመጠቀም እና ለቀሪዎቻችንም በማካፈል በጽናት በመቆም ዓለምን ከጨለማው ወደ ብርሀኑ ይመልሳሉ፡፡ ገና ከመለስ ዜናዊ የጭራቅ እስር ቤት ሆድ ውስጥ ከመድረሳቸው በፊት ከታላቁ ገጸ በረከታቸው አንዱ የሆነውን ጽናትን ልከውልናል፡፡

እስክንድር እንዲህ በማለት አወጀ፣ “ከዋሻው መጨረሻ ያለውን ብርሀን ለማየት እኖራለሁ፡፡“ እስክንድር እና የህሊና የእስር ቤት ጓደኞቹ ረዥሙን እና አድካሚውን ጉዟቸውን ከጨለማው ዓለም ወደ ብርሀኑ ዓለም በማድረግ በስኬት ያጠናቅቃሉ፡፡ እንግዲህ ይህ ነው የሁሉም ጀግኖች እና ጀግኒቶች የተቀደሰ ዕድል እና ዓላማ፡፡

ህወሀት በኢትዮጵያ ጋዜጠኞች እና ጦማሪያን ላይ የከፈተው የጦርነት ዘመቻ እራሱ በእውነት ላይ የተደረገ የጦርነት ዘመቻ ነው፡፡ ላለፉት 23 ዓመታት ህወሀት በሁሉም ጦርነቶች እና አጫጭር ግጭቶች አሸናፊ ሆኖ ቆይቷል፡፡ ሆኖም ግን ጎራዴዎችን እና AK47 ጠብ መንጃዎችን በታጠቁት ወሮበላ አምባገነኖች እና በተማሩ ጋዜጠኞች እና ብዕሮቻቸውን እና የኮምፒውተር መክፈቻ ቆፎቻቸውን ብቻ በሚጠቀሙ ጦማሪያን መካከል የሚደረገው የመጨረሻ እና ወሳኝ ጦርነት ይደረጋል፡፡ ያ ጦርነት በኢትዮጵያ ህዝብ ልብ እና አዕምሮ ውስጥ ነው፣ እንደዚሁም በዚሁ መልኩ ወደፊትም ይቀጥላል፡፡ ምንም ይሁን ምን የዚያ ጦርነት ውጤቱ የተቀደሰ እንደሚሆን ምንም ዓይነት ጥርጥር የለኝም፡፡ በእርግጥ ያ ጦርነት በአሁኑ ወቅት አሸናፊነትን ተቀዳጅቷል፡፡ ኤድዋርድ ቡለዌር ሊቶን በግጥም ስንኞቻቸው በግልጽ እንዳስቀመጡት በጎራዴ ታጣቂዎች እና በብዕር ተኳሾች መካከል በሚደረግ የጦርነት ፍልሚያ የመጨረሻ ድሉ የሚሄደው ወደ ብዕር ተኳሾች ነው ብለዋል፡፡

እውነት መሰረት ነው እንደዚህ ነው የምል፣

ገዥዎች በጉልበት ሁሉን ለመጠቅለል፣

ምለው ተገዝተው ህዝብን ለመበደል፡፡

መሳሪያ ቢያንጋጉ ላውንቸሩን መውዜር፣

በሰማይ ቢበሩ ቢናውዙ በምድር፣

በባህር ቢቀዝፉ ህዝብን ለማሸበር፡፡

ለጊዜው ድንፋታን በጥቅም ላይ ቢያውል፣

መሳሪያ ኃይል ሆኖ አያበቃም ለድል፣

ብዕር ከጎራዴ ያይላል፣ አስተውል፡፡

ጭራቆች ቢስቁ፣

ወሬን ቢሰልቁ፣

ፍትህን ላያውቁ፣

ህዝብን ለመጨረስ

በምኞት አለቁ፡፡

መሰረቱን ሰርቶ ባዶ ጩኸታቸው፣

ህዝብን ለመበደል ሆኖ ዓላማቸው፣

ሌት ከቀን ቢለፉ በነቀዘ አፋቸው፣

ውድቀትን ካልሆነ ድል አይታያቸው፡፡

ስለዚህ ጭቁኖች ታምርን በመስራት፣

ጭራቅ ቄሳሮችን በወኔ በመርታት፣

የእምብተኝነትን አመጽ በማስነሳት፣

ነጻነትን በሉ የህዝቦች አድርጓት፡፡

ስለዚህ ታላቁ፣

የሀሰት ስላቁ፣

ጀብደኝነት ስንቁ፣

ነጻነት እሩቁ፣

ሸፍጠኝነት ወርቁ፣

ከሀዲነት ብርቁ፣

ከርሳምነት እንቁ፡፡

እንደ ጠዋት ጤዛ በኖ እንደሚጠፋ፣

ቀልቀሎ አቁማዳ ባየር የተነፋ፣

ጠበቅ ሲያደርጉት በራሱ ላይ ከፋ፡፡

ስለዚህ ታላቁን የይስሙላ ስሙን፣

በብዕር ምቱ እና ቀሙት ጎራዴውን፣

በዓለም ህዝቦች ሁሉ ሰላም እንዲሰፍን፡፡

ከዚያማ በዓለም ላይ በሰው ልጆች ሁሉ፣

በጎራዴ ማመን ይቀራል በሁሉ፡፡

ብዕር አሸናፊ የሰው ልጆች ማማ፣

ለአምባገነን እሬት ለጭቁኖች አርማ፣

የስልጣኔ አርማ የምሁራን ጫማ፣

ክላሽንኮብ መውዜር ታንክ ሳይሰማራ፣

በጉልበት ሳያምን ብዕርን ከጠራ፣

መንግስት ይጠበቃል ማንንም ሳይፈራ፡፡

ጽናት ለእኔ ምን ማለት እንደሆነ፣

በርካታ ኢትዮጵያውያን ውንድሞቸ እና አትዮጵያውያት እህቶቸ እራሳቸውን እንዲህ በማለት ይጠይቃሉ፣ “የትግላችንን ፍሬ እስከምናይ ድረስ ምን ያህል ጊዜ መታገል አለብን?” እኔ ደግሞ እራሴን እንዲህ በማለት እጠይቃለሁ፣ “ምን ያህል ጊዜ…?“ ሌሎች ደግሞ እንዲህ በማለት ይጠቁኛል፣ “በስልጣን ላይ ላሉት እና ስልጣናቸውን ከህግባብ ውጭ በሚጠቀሙት አምባገነኖች ላይ እውነቱን በመጻፍ እና በመንገር ለምን ያህል ጊዜ ትቆያለህ? እስከ አሁን አልደከመህምን?“

በኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት ላይ ትግል የሚያደርጉ ጥቂት ሰዎች የችግሩን አስቸጋሪነት ከግንዛቤ በማስገባት ሽንፈታቸውን አምነው ተቀብለዋል፡፡ ጎማቸውን እያሽከረከሩ እንደሆነ ይሰማቸዋል፡፡ ሆኖም ግን እንዲህ በማለት እነግራቸዋለሁ፣ “ጠበቅ አድርጋችሁ ያዙ! ለጥቲት ጊዜ ያህል፡፡“ አምባገነኖችን ለማንበርከክ ለነጻነት እና ለዴሞክራሲ የሚደረገው ትግል የ26 ማይል የማራቶን እሩጫ እንጅ የ100 ሜትር የአጭር ርቀት ሩጫ አይደለም በማለት እነግራቸዋለሁ፡፡ እ.ኤ.አ ሜይ 2011 “በኢትዮጵያ ለነጻነት የሚደረግ ታላቁ እሩጫ” በሚል ርዕስ ትችት አቅርቤ ነበር፡፡ በዚያ ትችት ላይ የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች እና ወትዋቾች፣ የተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች እና ሌሎች እልህ አስጨራሽ የሆነውን የማራቶን እሩጫ በጽናት እና በድል አድራጊነት ለማጠናቀቅ ማራቶን ሯጮቻችን በጽናት እና በወኔ መቆም እንዳለባቸው እንዲህ በማለት ተናግሬ ነበር፡፡

…ለነጻነት የሚደረግ የ10 ኪሎ ሜትር ሩጫ ለረዥሙ እና በጣም አስቸጋሪ ለሆነው የማራቶን ሩጫ የመጀመሪያው ክፍያ እንጅ አጠቃላይ ሙሉ ክፍያ አይደለም፡፡ ለዚህም ነው እያንዳንዳችን ልዩ የሆነውን ጽናት የሚለውን የማራቶን ሩጫን ማጎልበት ያለብን፡፡

የማራቶን ሯጯ ገና ሩጫዋን ስትጀምር እስከ ሩጫው ማጠናቀቂያው መስመር ድረስ ያለው ርቀት ታላቅ ጥረትን የሚጠይቅ እና በጣም አድካሚ እንደሆነ ታውቃለች፡፡ ሆኖም ግን ረዥሙን የማራቶን ሩጫ እንዴት አድርጋ ሮጣ ማሸነፍ እንዳለባት ቅድመ ዝግጅት ታደርጋለች፡፡ የማራቶን ሯጭ እንዲህ አይልም፣ ‘እጅግ በጣም ረዥም ነው…በጣም አስቸጋሪ ነው…እኔ በፍጹም ላደርገው አልችልም’ የአሸናፊነት ስነልቦናን ሰንቆ ይገባል እንጅ እሸነፋለሁ በማለት ሞራሉን ገድሎ ወደ ሩጫው አይገባም፡፡ ያለውን እምቅ ኃይል እየመጠነ እና እየለካ እርሱን በአንድ ጊዜ እንዲደክም እና ተስፋ እንዲቆርጥ በሚያደርግ መልኩ ሳይሆን ይልቁንም ከዚያ በተለዬ መልኩ እያበረታ እና በተስፋ እየተሞላ ለአጠቃላይ አሸናፊነት የሚያበቃውን የአሯሯጥ ዘዴ መርጦ በተግባር ይተገብራል፡፡ የማራቶን ሯጭ እያንዳንዱን እርምጃ እንዴት አድርጎ በመወንጨፍ ለድል ሊበቃ እንደሚችል አስቀድሞ ዕቅድ ያወጣል፡፡

የርቀት ሯጯ በቀሪዎቹ የማራቶን ርቀቶች ላይ እራሷን አታስጨንቅም ይልቁንም በቀጣይነት ስለምትራመደው፣ ከፊት ለፊቷ ስለሚጠብቃት ተራራ እና በቀጣይነት ስለምትሮጠው ጠመዝማዛ መንገድ እና ሩጫውን እስከምታጠናቅቅበት ድረስ ላለው ዕቅድ ነው እራሷን የምታዘጋጀው እና ኃይሏን እና ሀሳቧን ሁሉ የምታውለው፡፡ ጥቂቶቻችን የማራቶን ሩጫው 10 ኪሎ ሜትሮች እንዲሆኑ እና በአንድ ጊዜ በፍጥነት ሮጠን ከማጠናቀቂያው መስመር ላይ ለመድረስ እንፈልጋለን፡፡ በረዥም ርቀት ሩጫ ላይ ተስፋ የመቁረጥ እና እራሳችንን ዝቅ አድርገን የማየት ሁኔታን እናንጸባርቃለን፡፡ ገና ስናስበው በጣም የድካም ስሜት ይሰማን እና አንዷንም እርምጃ ሳንሰነዝር በዝረራ ሩጫውን ጥለን እንወጣለን፡፡ ሆኖም ግን ለነጻነት የሚደረግ የማራቶን ሩጫ የማጠናቀቂያ መስመር የለውም፡፡ ማንዴላ “አንድን ታላቅ ተራራ ከወጣን በኋላ ሌሎች በርካታ ተራሮችን መውጣት ይጠበቅብናል” እንዳሉት ማለት ነው፡፡

ማራቶንን መሮጥ እና አንድ ተራራ ብቻ በመውጣት ሌሎች ሊወጡ የሚችሉ በርካታ ተራሮች እንዳሉ አስቀድሞ ማወቅ እና በልበሙሉነት በመሮጥ ከማጠናቀቂያው መስመር መድረስ መቻል ነው እንግዲህ ለእኔ ጽናት ማለት! ሌሎች ተራሮች እስካለቁ ድረስ ተራሮችን መውጣት እና ሌሎች ያልተጠናቀቁ ተራሮች የሌሉን መሆናቸውን ማረጋገጥ ይጠበቅብናል!

ወደኋላ አናፈገፍግም፣ እናም በጽናት እንቆማለን! አይበገሬ እንሆናለን! ድል እናደርጋለን!

በመለስ ዜናዊ የማጎሪያ እስር ቤት በመማቀቅ ላይ ለሚገኙት ጀግኖች እና ጀግኒቶች ልቤ ይሰበራል፣ የደረት ውጋትም ይሆንብኛል፡፡ እስክንድር በግፍ የ18 ዓመታት እስራት ተፈርዶበት በመለስ ዜናዊ እስር ቤት በመማቀቅ ላይ የመገኘቱ ሁኔታ ልቤ እንዲሰበር አድርጎኛል፡፡ ሆኖም ግን እስክንድር ምንም የማይፈራ ደፋር መንፈሰ ጠንካራ የማያጎነብስ በመሆኑ ልቤ በደስታ ይሞላል፡፡ ርዕዮት በመለስ ዜናዊ የማጎሪያ እስር ቤት ሌት እና ቀን በመማቀቅ ላይ መሆኗን ባስታወስኩ ቁጥር ልቤ ይሰበራል፡፡ ሆኖም ግን ክብሯን እና ነጻነቷን ለመግፈፍ ከሚቋምጡት አሳሪዎቿ እኩይ ሀሳብ ከመንበርከክ እና ቅጣቷን ከመቀበል ይልቅ በዓላማ ጽናቷ በመግፋት የምታሳየውን የአይበገሬነት ጽናት ስመለከት ሞራሌ ከፍ ይላል፡፡

በኢትዮጵያ ያሉትን ጅግኖች እና ጀግኒቶች የፖለቲካ እስረኞችን አከብራቸዋለሁ፣ አወድሳቸዋለሁም፡፡ ለወገኖቻቸው ለኢትዮጵያ ህዝብ ሲሉ እየከፈሉት ላለው መስዋዕትነት እና እያሳዩት ላለው የዓላማ ጽናት የሚያነቃቃኝ በመሆኑ እጅግ በጣም ተደስቻለሁ አመሰግናቸዋለሁ፡፡ የዓላማ ጽናቴ የበለጠ እንዲጠነክር አድርገዋል፣ እናም እየከፈሉት ያለውን መስዋዕትነት እንዳስብ እና እንድዘክር የበለጠ የመንፈስ ጥንካሬ እና ስንቅ እንዲሆነኝ አድርገዋል፡፡ የእነርሱን ድፍረት፣ ጠንካራ የሞራል ተስፋ፣ ጽናት፣ የዓላማ ጥንካሬ እና አይበገሬነት ብቻ አደንቃለሁ የእኔ ባህሪም እንዲሆኑ አደርጋለሁ፡፡ የእነርሱን ጽናት ለማግኘት እጓጓለሁ፡፡ እነዚህን ጀግኖች እና ጀግኒቶች ከልብ በመነጨ መልኩ አመሰግናቸዋለሁ፣ አወድሳቸዋለሁ፡፡

እስክንድር ጥልቅ በሆነ ፍልስፍናዊ የአነጋገር አንደበቱ እንዲህ በማለት ጽፎ ነበር፣ “ በጽናት እቆማለሁ!“ ይህንን ፈላስፋዊ አነጋገር ሁልጊዜ በምንግባባበት የተለመደው የዘወትር ቋንቋ ዘርዘር አድርጌ ስመለከተው እስክንድር በቀጥታ ቶም ፔቲ እና “አላፈገፍግም” የሚሉትን ልብ ሰባሪ ግጥሞቹን ሆኖ ነው ያገኘሁት፡፡

እወቅ አንተ ጭራቅ አላፈገፍግም፣

ከገባሁበት ማጥ አንድ ጋት አልርቅም፡፡

ሳላንበረክክህ ከእነርኩስ መንፈስህ፣

ቃል ለምድር ለሰማይ እውነት ነው እምልህ፣

ተመልሸ አልወጣም ከማጎሪያው ቤትህ፡፡

ማፈግፈግ ማፈግፈግ ፍጹም አታስባት፣

አፈር ትበላለህ በእኔ መስዋዕትነት፡፡

እንጦረጦስ ወርደህ ከነጉግ ማንጉግህ፣

የህዝብ ነጻነት ያበራል በቀብርህ፡፡

ከጋነም ከበሩ ማቆም ትችላለህ፣

መግረፍ ማሰቃዬት መግደል ትችላለህ፣

ሆኖም ግን ከግብሬ ከዓላማዬ ቀርቶ፣

መመለስ ይቅር እና ፊቴ አይዞረም ከቶ፣

አንተን ሳያደባይ ካለህበት ገብቶ፡፡

በዓላማ ጸንቼ፣

ሩቅ ተመልክቼ፣

ለፍትህ ጓጉቼ፣

ጽናትን አንግቼ፣

ለነጻነት ሞቼ፣

ሳልገለባበጥ እንደባህር ዓሳ፣

በጽናት ታግዬ እንደ ጫካ አንበሳ፣

ቁርስ መብላት ሳይሆነ አልሜ ለምሳ፣

ሽንፈት ትጋታለህ ብትወድቅ ብትነሳ፡፡

ዓላማዬ አንድ ነው ዓለምን መጠበቅ፣

ከጭራቅ ድሁሮች ከአምባገነን መብረቅ፣

ከግፈኞች ጉያ ተምዘግዝጋ እንዳትወድቅ፡፡

ስለዚህ በጽናት እቆማለሁ ዳግም፣

ላምባገነን ጨካኝ አላጎብስም፣

ጭራቃዊ መንፈስ ከዓለም እስኪወድም፣

ፍትህ በአደባባይ እስከምትለመልም…

ወደኋላ አናፈገፍግም! ለዓላማችን በአይበገሬነት እንቆማለን! በጽናት እንቆማለን! አይበገሬ እንሆናለን! በመራራው ትግላችን በድል አድራጊነት ድልን እንቀዳጃለን!

በመላው ዓለም የምትገኙ አንባቢዎቼ ሁሉ አዲሱ የፈረንጆች ዓመት የደስታ እና የብልጽግና እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ… በ2015 አዲሱ ዓመት ኃይሉ እና ድሉ ሁሉ ከእናንተ ጋር እንዲሆን እመኛለሁ!

ያለው ኃይል ሁሉ ከድል አድራጊዎቹ ከኢትዮጵያ የፖለቲካ እስረኞች ጋር እንዲሆን እመኛለሁ!

ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!

ታህሳስ 24 ቀን 2007 ዓ.ም

የአስገራሚው ክስ አስገራሚ የክስ ቻርጅ (ይመልከቱ)

$
0
0

ከሃገር ቤት የተላከልን የአስገራሚው ክስ አስገራሚ የክስ ቻርጅ የሚከተለው ነው:: በለቅሶ ቤት ውስጥ “መለስ እንኳን ሞተ ብላችሁ ተናግራችኋል…” በሚል ፍርድ ቤት የቀረቡት ግለሰቦች በሃሰተኛ ወሬ በማሰራጨት ወንጀል እንደተከሰሱ ይኸው የክስ ቻርጅ ያሳያል:: ይመልከቱ::
asgeramiw kis

ፍትሕ አያረጅም! የኢትዮጵያና የአርሚኒያ ትግል

$
0
0

ኪዳኔ ዓለማየሁ

መግቢያ፤

Justiceኢትዮጵያንና አርሚኒያን ከሚያመሳስሏቸው ጉዳዮች አንደኛው የአንድ ዓይነት የኦርቶዶክስ ሃይማኖት የእምነት መሠረት (ዶግማ) ተከታዮች ያሉባቸው ሐገሮች መሆናቸው ነው። በዚህ ጽሑፍ የማተኩርበት ተመሳሳይነት ግን ሁለቱም ሐገሮች በከባድ የጦር ወንጀሎች ተጠቅተው እያንዳንዳቸው ቢያንስ አንድ ሚሊዮን ሕዝብ የተጨፈጨፈባቸው መሆኑ ነው። ሌላም እጅግ አስጸያፊ ግፍ የተፈጸመባቸው ሐገሮች ናቸው። በተጨማሪም፤ ሁለቱን ሐገሮች ያቀራረባቸው ሌላው ጉዳይ በኦቶማን ዘመነ መንግሥት፤ ከቱርኮች ግፍ በመሸሽ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ መንግሥት መልካም ፈቃድ ወደ ኢትዮጵያ የተሰደዱት 40 አርመኖች ኑሯቸውን በሐገራችን መቀጠላቸው ነው። እነዚህ አርመኖችና ተወላጆቻቸው በኢትዮጵያ ተመቻችተው የኖሩና ብዙዎቹም አማርኛውን ያቀላጥፉ እንደ ነበር የታወቀ ነው። በዚህ አጋጣሚ፤ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አማካኝነት ዱባይ በምሠራበት ጊዜ እዚያ ይኖር የነበረውን፤ ወዳጄን፤አቶ የርቫንትን እያስታወስኩ፤ አርመኖች ያቋቋሟትን ሻርጃ (Sharjah) የምትገኝ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ለኢትዮጵያውያን ምእመናን በማጋራታቸው፤ ውለታቸውን አልረሳውም።

በአርመኖችና በኢትዮጵያውያን ላይ የተፈጸሙት እልቂቶችና የጦር ወንጀሎች፤

በአርመኖች ላይ የተፈጸመው የጦር ወንጀል እ.አ.አ በ1915-23 በኦቶማን (Ottoman) (በኋላ ቱርክ) ዘመነ መንግሥት መገባደጃ ጊዜ ነበር። እንደሚታወቀው፤ በኢትዮጵያ ላይ የተፈጸመው እልቂት እ.አ.አ በ1935-41 በኢጣልያ ፋሺሽቶችና በቫቲካን ያልተቆጠበ ድጋፍ የተከናወነ ነበር። ከላይ እንደ ተገለጸው፤ ሁለቱም ሐገሮች ቢያንስ አንድ አንድ ሚሊዮን ሕዝብ ተጨፍጭፎባቸዋል። በተጨማሪም እጅግ ብዙ አርመኖች ከሐገራቸው እንዲሰደዱ ተገድደው ለከባድ ችግር ተጋልጠዋል። በኢትዮጵያ ላይ የተፈጸመው ግፍ በብዙ የኢጣልያ አውሮፕላኖች በተነሰነሰው የመርዝ ጋዝ እንዲሁም በሌሎች ልዩ ልዩ መሣሪያዎች የተጨፈጨፈው ሕዝብ፤ (በሶስት ቀኖች አዲስ አበባ የተገደሉት 30 000 ኢትዮጵያውያን ጭምር) ብቻ ሳይሆን የወደሙትን 2 000 ቤተ ክርስቲያኖች፤ 525 000 ቤቶችና 14 ሚሊዮን ያህል እንስሶች ያካትታል። በተጨማሪም እጅግ ብዙ ዝርፊያ የተከናወነ መሆኑ የታወቀ ነው።

የአርመኖች ትግል ለፍትሕ፤

በአርመኖች በኩል፤ ከ100 ዓመት በፊት በቱርኮች ለተፈጸመባቸው ወንጀል ተገቢውን ፍትሕ ለማስገኘት ያላሰለሰ ትግላቸውን እየቀጠሉ ነው። መሠረታዊ ዓላማቸውም ያ ከባድ ጥቃት የዘር ማጥፋት ወንጀል (genocide) መሆኑ በዓለም አቀፍ ደረጃ እንዲታወቅላቸው ለማድረግ ነው። በዚህ በፈረንጆች የዘመን አቆጣጠር በ2015 የእልቂቱ መቶኛ ዓመት የሚደፍን በመሆኑ በሰፊው ለመዘከር እቅድ አላቸው። በዚህ ተግባር ከተሰማሩት ውስጥ፤ የአርመን መንግሥት እንዲሁም በአሜሪካ የሚገኙ፤ (ሀ) የአርመን ብሔራዊ ኮሚቲ በአሜሪካ (Armenian National Committee of America) (www.anca.org) እና (ለ) የአሜሪካ አርመናዊ ሸንጎ (Armenian Assembly of America) (www.aaainc.org) ይገኙበታል።

ሰሞኑን በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መማከሪያ (Foreign Affairs Council) በተሰኘው ድርጅት አማካኝነት ታትሞ በወጣው ፎሪን አፌርስ (Foreign Affairs) መጽሔት (January/February 2015)፤ ቶማስ ደ ዋል (Thomas de Waal) የተባለ ዘጋቢ፤(“The G-Word; The Armenian Massacre and the Politics of Genocide”) (ትርጉም፤ የጂ-ቃል፤ ስለ አርመኖች እልቂትና የዘር ማጥፋት ፖለቲካ) በሚል አርእስት የሚከተሉትን ቁም-ነገሮች አቅርቧል፤

 

(ሀ) እ.አ.አ. በ1918 የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ቲዮዶር ሩዝቬልት (Theodore Roosevelt) በአርመኖች ላይ ስለ ተፈጸመው ስደትና እልቂት አሜሪካ በኦቶማን መንግሥት ላይ ጦርነት ማወጅ አለባት በማለት ሐሳባቸውን በደብዳቤ ገልጸው ነበር።

(ለ) የአርመኖች የፍትሕ ትግል በአሜሪካ መንግሥት መርሆ ላይ ከፍተኛ አጽንኦት አስክትሏል። እ.አ.አ. በ1951 የአሜሪካ መንግሥት ጠበቆች ቱርኮች በአርመኖች ላይ የፈጸሙት እልቂት እንደ የሰው ዘር ማጥፋት ወንጀል (genocide) እንዲታይ ሔግ (The Hague) ለሚገኘው ዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት (International Criminal Court) አመልክተው ነበር። ነገር ግን የተባበሩት መንግሥታት የዘር ማጥፋት ወንጀል ስምምነት (United Nations Genocide Convention) የታወጀው እ.አ.አ. በ1948 ከአርመኖች እልቂት በኋላ በመሆኑ እስካሁን ጉዳዩን ለፍርድ የማቅረቡ ሒደት አልተሳካም።

(ሐ) እ.አ.አ. በ1975 የአሜሪካ ተወካዮች ምክር ቤት (House of Representatives) መሪ፤ ቲፕ ኦኒል (Tip O’Neill) እ.አ.አ. ሚያዚያ 24ን (April 24) የሰውን ልጅ የርስ በርስ ኢሰብአዊነት ብሔራዊ የመዘከሪያ ቀን (National Day of Remembrance of Man’s Inhumanity to Man” ተብሎ እንዲሰየምና በዘር ማጥፋት ወንጀል የተጠቁትን በሙሉ፤ በተለይም እ.አ.አ. በ1915 ለተሰዉት አርመኖች መታሰቢያ እንዲሰየም ሥልጣኑን ለአሜሪካ ፕሬዚዳንት የሰጠበት የውሳኔ መግለጫ አውጥቶ ነበር። ነገር ግን በሌላው የአሜሪካ ምክር ቤት፤ በሴኔት (Senate) የአርመኖችን እልቂት እንደ የዘር ማጥፋት ወንጀል የመቁጠር ጉዳይ ተቀባይነት ሳያገኝ ቀርቷል።

(መ) ፕሬዚዳንት ሬጋንም (President Reagan) በመጀመሪያ በ እ.አ.አ. በ 1981 ለአርመኖች የዘር እልቂት (genocide) እውቅና በመስጠት ገለጻ አድርገው ነበር። ነገር ግን እ.አ.አ. በ1982 ሁለት አርመናዊ ወጣቶች በሎዛንጀለስ ከተማ የቱርክ ቆንስል መሪ የነበረውን ከማል አሪካንን (Kemal Arikan) በመግደላቸው የፕሬዚዳንት ሬጋን አቋም ተለወጠ።

(ረ) የቱርክ መንግሥት ለአሜሪካ ጠንካራ ድጋፍ ከሚያበረክቱት መንግሥቶች አንዱ በመሆኑ በተለይም የሰሜን አትላንቲክ ሐገሮች ድርጅት (NATO) አባል በመሆኑ በአርመኖች ላይ ስለ ተፈጸመው የኦቶማኖች የጦር ወንጀል አሜሪካ ያላት አቋም ተለዋዋጭ ሆነ።

(ሠ) የአሜሪካና የቱርክ መንግሥቶች ባላቸው የጥቅም ቅድሚያ ለአርመኖች የሚገባውን ፍትሕ ለጊዜው ያመከኑት ቢመስልም የአርመን ታጋይ ድርጅቶች የመቶ ዓመት ጥረታቸውን አጠንክረው እየቀጠሉ ነው። ለዚህም በምርጫ መብታቸው እየተጠቀሙ በአሜሪካ የኮንግሬስ አባሎችና በሐገሩ ፕሬዚዳንት ላይ የማያቋርጥ አጽንኦት እንዲከሰት ለማድረግ እየጣሩ ነው። የዚህም ጥረት ውጤት አንደኛው ምሳሌ፤ እ.አ.አ. በሚያዚያ 24 ቀን 2010፤ ፕሬዚዳንት ኦባማ (President Obama) የሚከተለውን ገለጻ ማድረጋቸው በቶማስ ደ ዋል ጽሑፍ ተዘግቧል፤

“1.5 million Armenians were massacred or marched to their death in the final days of the

Ottoman Empire……..The Meds Yeghern (“Great Catastrophe”) is a devastating chapter in the

History of the Armenian people, and we must keep its memory alive in honor of those who

were murdered and so that we do not repeat the grave mistakes of the past.”

(ትርጉም፤ በኦቶማን መንግሥት የመጨረሻዎቹ ቀናት 1.5 ሚሊዮን አርመኖች ተጨፍጭፈዋል ወይም ለሞት

ወደሚዳርጋቸው እንዲጓዙ ተደርገዋል። ታላቁ ሰቆቃ (መቅሠፍት) በአርመኖች ታሪክ እጅግ አሰቃቂ ምእራፍ

ነበር። ያለፈውን ስሕተት እንዳንደግመው ለተገደሉት ሰዎች ክብር የዚያን ዘመን ትዝታ ሕያው አድርገን

 

ልናስታውሰው ይገባናል።)

ከዚህ በላይ ከተዘረዘረው መገንዘብ የሚቻለው፤ ምንም እንኳ አርመኖች የሚፈልጉት፤ ማለትም በቱርኮች የተፈጸመባቸው ጭፍጨፋ እንደ የዘር እልቂት ወንጀል (genocide) የማሳወቅ ዓላማ እስካሁን ባይሳካላቸውም ጥረታቸው በከፍተኛ ደረጃ እየቀጠለ የአሜሪካ መሪዎች ጭምር ተስፋ አላስቆረጧቸውም። “የአርመን ብሔራዊ ኮሚቲ በአሜሪካ” ድርጅት የሕዝብ ግንኙነት ዲሬክተር የሆነችውን ወ/ሮ ኤሊዛቤት ሹልድጂያንን (Elizabeth Schouldjian) ሰሞኑን በስልክ አነጋግሬያት አርመኖችና የአርመን መንግሥት ትግላቸውን የሚቀጥሉ መሆኑንና በዓለም አቀፍ ደረጃ በሚያከናውኑት እንቅስቃሴ ከአውሮፓ የሰብአዊ መብት ፍርድ ቤት ጋር ጭምር ጉዳዩን እንደሚገፉበት ገልጻልኛለች።

የኢትዮጵያስ ትግል?

ኢትዮጵያ ለተፈጸመባት እጅግ አሰቃቂ ግፍ ተገቢውን ፍትሕ አላገኘችም። ካሣ ተብሎ ለቆቃ ግድብ መሥሪያ የዋለው $25 ሚሊዮን እና ወደ ሐገሩ የተመለሰው የአክሱም ሐውልት በምንም መስፈርት ብቁ ነው ሊባል አይችልም። ኢጣልያ ለሊቢያ $5 ቢሊዮን፤ ለዩጎዝላቪያ $125 ሚሊዮን፤ ለግሪክ ሐገር $105 ሚሊዮን፤ ለሶቪየት ዩኒየን $100 ሚሊዮን፤ ወዘተ ከተስማማችው ጋር ሲመዛዘንና በተለይም በኢትዮጵያ ላይ ከፈጸመችው ክፍተኛ የጦር ወንጀል ጋር ሲነፃፀር በግልፅ የሚታየው የተዛባ ፍትሕ የሚያስቆጭ ነው። “በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ” እንደሚባለው፤ ኢጣልያ የፈጸመችው ወንጀል አልበቃ ብሏት፤ በቅርቡ፤ የቫቲካን ተወካይ በተገኙበት፤ አፊሌ በምትባል የኢጣልያ ከተማ፤ “የኢትዮጵያ ጨፍጫፊ” በመባል ለሚታወቀው፤ ለሮዶልፎ ግራዚያኒ አንድ መታሰቢያና መናፈሻ ተመርቆለታል። እንደ ኬንያና ኢንዶኒዚያ ያሉ ሐገሮች ከቀድሞ አጥቂዎቻቸው ከእንግሊዝና ከኔዘርላንድስ ተገቢውን ይቅርታ ተጠይቀው ካሣ ጭምር ሲከፈላቸው ኢትዮጵያ የተሟላ ፍትሕ ሊነፈጋት አይገባም። ስለዚህ፤ ዓለም አቀፍ ሕብረት ለፍትሕ – የኢትዮጵያ ጉዳይ (Global Alliance for Justice – The Ethiopian Cause) የተሰኘው ድርጅት ከዚህ በታች ለተዘረዘሩት ዓላማዎች እየታገለ ይገኛል፤

(ሀ) የኢጣልያ መንግሥት ለኢትዮጵያ ሕዝብ ተገቢውን ካሣ እንዲከፍል፤

(ለ) ቫቲካን የኢትዮጵያን ሕዝብ ይቅርታ እንድትጠይቅ፤

(ሐ) የኢጣልያ መንግሥትና ቫቲካን የተዘረፉትን ንብረቶች ለኢትዮጵያ ሕዝብ እንዲመልሱ፤

(መ) የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ፋሺሽት ኢጣልያ በኢትዮጵያ ላይ የፈጸመችውን የጦር ወንጀል

እንዲመዘግብ፤ እና

(ሠ) በቅርቡ ለፋሺሽቱ “የኢትዮጵያ ጨፍጫፊ” ለሮዶልፎ ግራዚያኒ ኢጣልያ ውስጥ በአፊሌ ከተማ፤  የተሠራው

መታሰቢያ እንዲወገድ።

አቤቱታውንም ለሚመለክታቸው ሁሉ፤ ለኢጣልያ መንግሥትና ለቫቲካን፤ ለአውሮፓ ምክር ቤት፤ ለአፍሪካ አንድነት ድርጅት፤ ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት፤ ለፕሬዚዳንት ኦባማና ለሌሎች አንዳንድ የዓለም መንግሥታት መሪዎች፤ እንዲሁም በፍትሕ ለሚያምኑ ሰዎች በሙሉ አቅርቧል። በዚህ አጋጣሚ በየዓመቱ የካቲት 12ን ለመዘከር በ30 ከተሞች በዓለም አቀፍ ደረጃ ለሐገር ፍትሕና ክብር ለሚንቀሳቀሱ ሁሉ ልባዊ ምሥጋና ይድረሳቸው። የኢትዮጵያ አርበኞች ማሕበርም የሚያከናውነው ጥረት ሊጠቀስ ይገባል።

በተጨማሪም፤ በድርጅቱ ድረ-ገጽ (www.globalallianceforethiopia.org) የሚገኝ፤ ቫቲካን የኢትዮጵያን ሕዝብ ይቅርታ እንድትጠይቅ እየተፈረመ ያለ ዓለም አቀፍ አቤቱታ ይገኛል። እስካሁን ክ4200 ሰዎች በላይ ፈርመውታል። ይህንን ጽሑፍ የሚመለከቱ ሁሉ አቤቱታውን እንዲፈርሙት ተጋብዘዋል።

 

ለውድ ሐገራችን ለኢትዮጵያ ስለሚያስፈልገው ፍትሕና ክብር እስካሁን የተከናወነው ጥረት የሚያበረታታ ቢሆንም በውጤት ደረጃ አመርቂ ደረጃ አልደረሰም። በተለይም አርመኖች ለክብራቸውና ለሐገራቸው ፍትሕ ከሚያከናውኑት ትግል ጋር ሲነፃፀር በኛ በኩል ጥረታቻችንን ማጎልበት እንደሚገባን ግልጽ ነው። ስለዚህ ለሐገርና ለፍትሕ የሚቆጭ ሁሉ በትግሉ እንዲሳተፍና እንዲደግፍ ያስፈልጋል። የአገር ወዳዶች የተባበረ ጥረት የትግሉን ውጤት የተሳካና የተፋጠነ ለማድረግ አስተዋፅኦ ይኖረዋል።

ቸሩ የኢትዮጵያ አምላክ ለሐገራችን የሚገባው ክብርና ፍትሕ እንዲገኝ የጀመርነውን ጥረት፤ በሁሉም አገር ወዳድ ተሳትፎ፤ አጠናክረን እንድንቀጥል ብርታቱን ይስጠን። አሜን!

አንድ ምሽት ከቴዲ አፍሮ ጋር በፍራንክፈርት 

$
0
0

Teddy afro
በልጅግ ዓሊ

የቴዲ አፍሮ ዝግጅት በፋራንክፈርት ሲደረግ በቦታው ተገኝቼ ነበር ። ብዙ ጊዜ ዘፋኝ ሲመጣ አልገኝም ። ዘንድሮ ግን ወያኔ በእሱ ላይ ያደረገውን ተንኮል መቃወም የሚቻለው በዝግጅቱ በመገኘት በመሆኑ ሰብሰብ ብለን ተገኝተን ነበር። ሰልፉ ሳይጠነክር ቀደም ብለን ለመግባት በጊዜ ነበር የደረስነው። ሰዓቱን ጠብቀን ከፍለን ገባንና ጥግ ላይ ወንበር ፈልገን መጠበቅ ጀመርን ። እሱ ወደ መድረክ እስከሚወጣ በልዩ ልዩ ዘፈን እየተዝናናን ቆየን ። ወጣት ይጎርፋል፣ አለባበስ ይታያል፣ ዓመት በዓሉን ዓመት በዓል አስመስለውታል። የአዲስ ዓመት ዋዜማ . . .  ለቀጣዩ የፈረንጆች ዓመት ዝግጅቱ ተጠናቋል። አዳራሹ እኩለ ሌሊት ላይ እየሞላ መጣ።

የሚጠበቀው ቴዲ አፍሮ ወደ መድረክ ሲወጣ ወጣቶች ያብዱ ጀመር። እሱ “ፍቅር ያሸንፋል“ ይላል። ወጣቶቹ ይጮኻሉ። “እወዳችኋለሁ“ ሌላ ጩኸት። አዳራሹ ድብልቅልቅ አለ ! ደስታና ጩኸት ይፈራረቁ ጀመር። ለአንድ ጊዜ  እንኳን ቢሆን ይህንን ዓይነት አቀባበል የኢትዮጵያ ገዥዎች መቼ ይሆን የሚያገኙት ? ብዬ አሰብኩ። በ2015 ይኽንን ብመኝ የተጋነነ ይሆናል?

በተከታታይ አራት ዘፈን ተዘፈነ ። ልዩ ልዩ ዓይነት ጭፈራ ታየ ፣ ውስጥ ሙዚቃ ፣ ደጅ ርችት ፣ መድረኩ ላይ ጭፈራ ቀለጠ ። 2015 በደስታ ተጀመረ ። ለዛሬም ቢሆን ችግራችንን ሁሉ ልንረሳ የተስማማን ይመስላል። ተስፋችንን አንግበን ለፍቅር የተነሳን ሆንን። ፍቅር ያሸንፋል ቴዲ ፣ እኛም ያሸንፋል . . . ። አጠገቤ የነበረው ጓደኛዬ ግን ዘመን መቀየሩን ረስቶት ያሸንፋል እያለ ግራ እጁን ቡጢ ጨብጦ መፈክር ያሰማል። ሌላው አውርድ እጅህን እዚህ ቡጢ አያስፈልግም ይለዋል። የፍቅር ጠላቶችን አደቅበታለሁ ሲል ተሳሳቅን። ወጣቱ መድረኩ አካባቢ እኛ ጥግ ጥጉን ይዘን እስክስታውን ወረድነው።በቴዲ ዘፈን ምንጃርኛም ይሞከራል። ያልተሞከረ አልነበረም። ፍራንክፈርት ቀለጠች . . .  ቤት የቀረም ሰው ያለ አይመስልም . . .  አዳራሹ ምንም ትልቅ ቢሆን ተጨናንቋል። አዲስ ዘመን በአዲስ ተስፋ ተጀመረ።

እንደ ድንገት አንድ ወጣት ከጭፈራው ብዛት ደክሞት አጠገቤ ተቀመጠ።

ደከመህ ? ብዬ ጠየቅሁት ።

ጭንቅላቱን በማወዛወዝ አዎን አለኝ።

ትንሽ ትንፋሽ እሲከያገኝ ጠበቅሁና ቴዲን ትወደዋለህ ? መልሱን በአማርኛ ስጠብቅ በትግርኛ ቀጠለ። በንግግር ልንግባባ አልቻልንም። አማርኛ አይችልም።  ቴዲ አዲስ ዘፈን ሲጀምር ወጣቱ አብሮት ይዘፍናል። ወጣቱ የቴዲን ዘፈን በቃሉ ያወርደዋል። ከቴዲ አፍሮ ጋር በዘፈን ይግባባሉ። ከእኔ ጋር ግን በቋንቋ ልንግባባ አልቻልንም። ለዘመናት የቆየው ጦርነት ምክንያት የወጣቱን ቋንቋ አለመናገራችን ይሆን?? ሃሳብ መጣ ።  አሁን ስለ ወጣቱ የማወቅ ፍላጎቴ ጨመረ ።

ሁሉን ዘፈን ታውቀዋለህ ?

አሁን ገባው መሰለኝ  አዎ ሁ.. ሉ   ን አለኝ በአማርኛ በትግርኛ አነጋገር ። ገና ዘፈኑ ከማለቁ በፊት ልጁ እየሮጠ ወደ ዳንሱ ገባ ። እኔን ጥሎ ከቴዲ ጋር በሙዚቃ ሊግባባ ከነፈ . . . ።

ከጎኔ የነበረው ለጭፈራ የሄደው የጓደኛዬ ትርፍ ቦታ ለወጣቶች መተዋወቂያ ጠቀመኝ ። አንዲት በረጅም ጫማ ላይ የቆመች ወጣት መጣች ።

“መቀመጥ ይቻላል?“ እየተቅለሰለሰች ጠየቀችን ። ባለቤቱ እስከሚመጣ ፈቀድኩ ።

“ይህ ጫማ እግርሽን አያደክመውም?“ ወሬ መጀመሪያዬ ሆነ ።

“ትለምደዋለህ ፤ ከዚያ ብዙም አይሰማህም።“ ስለ ጫማው አስረዳችኝ።

“እዚህ ሃገር ቆይተሻል?“ የሚቀጥለው ጥያቄ ነበር ።

“ ገና አራት ወሬ ነው ?“

“ገና አዲስ ነሻ ? ”

” አዎ ነኝ።”

“የት ነው የተመደብሽ ? ” ከፍራንክፈርት ራቅ ያለ ቦታ ጠራችልኝ ።

“እና ለቴዲ አፍሮ ብለሽ ነው ከዛ ድረስ የመጣሽው ? ”

“ታዲያስ!” አለችኝ በመደነቅ ። አመላለስዋ ለቴዲ ያልተመጣ ለማን ይመጣል? የሚል ጥያቄ ያዘለ  ይመስላል።

ቴዲ አዲስ ዘፈን ጀመረ ። ጥያቄዬን ሳልጨርስ ጥላኝ ነጎደች። ጫማዋን ግን እዛው ጥላው በረረች።

እኔም በተራዬ መድረኩ ጋር ብቃ አልኩ። ከዘፈኖቹ ማህል ቴዲ መፈክሩን ያሰማል። “ ፍቅር ያሰኝፋል“ ወጣቶቹ በሞላ በአንደነት እንደ መፈክር ይደግሙታል ። ሲዘፍን ይከተሉታል ፣ ቴዲ አውቆ ማሕል ላይ ሲያቆም እነርሱ ይሰማሉ ። በዚህ ምሽት ሁሉም ደናሽ ፣ ሁሉም ዘፋኝ ሆኗል ። ጩኸቱ ስለበዛ ለዕረፍት ወደ ውጭ ወጣ አልኩ ። አዳራሹ ውስጥ አንድ ሺህ የሚሆን ሰው አለ ። ደጅ ከ200 -300 የሚሆን ሰው ለመግባት ቆሟል። ይህ ሁሉ ሰው እንዴት ሊሆን ነው ራሴን ጠየቅሁ ። ሕዝብ እንደ ጉድ ይጎርፋል። ይዘፈናል ይጨፈራል፣ ይፈከራል ፣ ቴዲ እውዳቸኋለሁ ይላል፣ ወጣቶቹም በጩኸት ፍቅራቸውን ይገልጹለታል።

ተመልሼ ቦታዬ ተቀመጥኩ ። አሁን ከብዙ ወጣቶች ጋር ተዋወቅሁ። ቦርሳና ጫማ እኔጋ እያስቀመጡ መሄድ ተጀመረ ። ለዚህ የታማኝነት ሥራ በመብቃቴ አልከፋኝም ። ወጣት ሲደሰት ከማየት በላይ ምን የሚያስደስት ነገር አለ ። ኢትዮጵያ ፣ ኤርትራ የሚለው ነገር ቦታ አልነበረውም ። ቴዲም ያውቅበታል፣ ፍቅር ያሸንፋል ! እያለ ፍቅርን ይዘራዋል። ወጣት በቡድን ሆኖ አብሮ ይጨፍራል። የመግባቢያ ቋንቋ የቴዲ ዘፈን ሆኗል። እኔም ለዚህ የተቀደሰ ዓላማ የጫማና የቦርሳ ጥበቃዬን በሰፊው ይዠዋለሁ። ተስማምቶኛል። አይሆንም ብዬ በዘመኑ ቋንቋ አላካብድም ።

ሌላ መጣ ቦታ ጠየቀኝ ። የተለመደው መልስ ተሰጠው ። ኤርትራዊ እንደሆነ ገብቶኛል። ቀስ በቀስ ተግባባን። ለምንድነው ቴዲን የምትወዱት ?

“ቴዲ እንደ ሌሎቹ አያካብድማ ? ኤርትራ ፣ ኢትዮጵያ ገለመሌ ፣ ገለመሌ አይልም ። ይመቻል። ዛሬ እዛ ፍራንክፈርት ሌላም ዘፈን አለ ። “ማህበረኩም“ ያዘጋጀው ነው ።  ከአስመራ የመጡ ታዋቂ ዘፋኞች አሉ። እዛ ማንም አልሄደ ፣ እዚህ ነው የመጣነው።” ብዙ ነገር አስረዳኝ ። እኔም “ማህበረኩም“ ምን እነደሆነ ማጣራት ጀመርኩ ። የሻብያ እጅ ያለበት ድርጅት እንደሆነ ሰማሁ። ገረመኝ ሻዕብያን በዘፈን ማሸነፍ ተቻለ ማለት ነው ?  “ቦለኛ“ የሚተሰኘ የቀድሞ የኤርትራውያን የዘፈን ዝግጅት ታሰበኝ ። ያኔ ወርቅና ጌጥ ሳይቀር የሚሰጥበት ዘመን ነበር ። የዛን ጊዜ ማነው ከቦለኛ የሚቀር።  አሁን ግን ቴዲ በዘፈን አሸነፈ ። የወጣቱን ፍላጎት የወያኔም፣ የሻዕብያም እንዳልሆነ ታዬ . . .  የምን ጦርነት ፣ የምን የሕዝብ እልቂት ፍቅር ያሸንፋል ። ወጣት ተሰብስቦ አንድ ላይ ይጨፍራል ፣ ይፋቀራል፣ ይዝናናል . . .  የጦርነት ጡሩምባ ለዛሬም ቢሆን ቆሟል . . .  የክፍፍል አባዜ ቆሟል ቴዲ የፍቅር ጦሩን ይዞ ዘመቻውን ካለውጊያ ቀጥሏል።

በዚህ ምሽት አንድ ነገር ተመኘሁ በሚቀጥለው ዓመት እነዚህን ወጣቶች የሚያፋቅር ፣ የቴዲ አፍሮን ጥሪ ቀጣይነት ተመኘሁ። ፍቅር የሚያሸንፍበት ቢሆን ብዬ ተመኘሁ። እነዚህ ወጣቶች የሚያፍሩበትን ሳይሆን የሚኮሩበትን ሃገር ተመኘሁ። ቴዲ አፍሮን አሥመራ ንግስት ሳባ ስታዲዩም ውስጥ መድረክ ላይ ሆኖ ፍቅር ያሸንፋል ሲል መስማትን ተመኘሁ። ከሁሉ በላይ ግን ማካበድን የማያውቅ የወጣትነትን ዘመን ተመኘሁ። . . .  በወያኔና በሻብዕያ ትምክህት ሊገዳደሉ የሚችሉ ወጣቶች በአንድነት ሲጨፍሩ ማየትን የመሰለ መልካም ስጦታ ከቴዲ አፍሮ 2015 ተሰጠን። እኛም በደስታ ተቀበልነው ።

ስለ  ሕዝብ ፍቅር የሚዘፍኑ በሰላም ይክረሙ !

beljig.ali@gmail.com

01.01.2015

ፍራንክፈርት

Health: ወደ ጥርስ ሐኪም መሄድ የሚያስፈልግህ ለምንድን ነው?

$
0
0

የጀነራል ሳሞራ የኑስን ፎቶ ግራፍ ለምን ለዚህ የጤና ዘገባ ተጠቀማችሁት እንደማትሉን እርግጠኞች ነን::

የጀነራል ሳሞራ የኑስን ፎቶ ግራፍ ለምን ለዚህ የጤና ዘገባ ተጠቀማችሁት እንደማትሉን እርግጠኞች ነን::


ዘመናዊው የጥርስ ሕክምና ከመጀመሩ በፊት ሰዎች ከወጣትነታቸው ጀምሮ በጥርስ ሕመምና በጥርስ መውለቅ ይቸገሩ ነበር። ብዙ ሰዎች የጥርስ መበለዝ፣ መወላገድ ወይም መውለቅ ውበታቸውን ይቀንስባቸው ነበር። በዕድሜ የገፉ ሰዎች ማኘክ ስለሚቸግራቸው ለተመጣጣነ ምግብ እጥረት ይዳረጋሉ እንዲሁም ያለ ጊዜያቸው ይሞታሉ። በዛሬው ጊዜ በርካታ የጥርስ ሕመምተኞች ከሕመማቸው ነጻ መሆን፣ ዕድሜያቸውን ሙሉ የጥርሳቸውን ጤንነት መጠበቅና ጥርሳቸው ውበቱን እንደያዘ እንዲቆይ ማድረግ ችለዋል። ዘመናዊው የጥርስ ሕክምና እነዚህ ሦስት አስደናቂ ስኬቶች ላይ መድረስ የቻለው እንዴት ነው?

ትምህርት በመስጠትና በየጊዜው ምርምራ በማድረግ ላይ የተመሠረተው በመከላከል ላይ ያተኮረ የጥርስ ሕክምና የጥርስ ሕመምንና የጥርስ መውለቅን ለማስወገድ የሚረዳ ወሳኝ መንገድ ነው። የሆነ ሆኖ ሕክምና የሚያስፈልጋቸው ብዙ ሰዎች ወደ ጥርስ ሐኪም መሄድ አይፈልጉም። አንዳንዶች እንዲህ የሚያደርጉት ሁኔታው ስለማያሳስባቸው ሲሆን ሌሎች ደግሞ የገንዘብ አቅማቸው ስለማይፈቅድላቸው ነው። ከዚህም በላይ መታከም ፈርተው ወደ ጥርስ ሐኪም የማይሄዱ ሰዎች አሉ። አንተ ያለህበት ሁኔታ ምንም ይሁን ምን ራስህን እንዲህ እያልክ መጠየቅህ ተገቢ ነው:- ‘የጥርስ ሐኪሙ ምን ሊረዳኝ ይችላል? ወደ እርሱ መሄዴ ጥቅም ይኖረዋል?’ ለጥርሳችን ቅድመ ጥንቃቄ የማድረጉን አስፈላጊነት ለመገንዘብ የጥርስ ሐኪሞች ለማስወገድ የሚሞክሩት ምንን እንደሆነ ማወቃችን ጠቃሚ ነው።

ጥርስ መጎዳት የሚጀምረው እንዴት ነው?

የጥርስ ሐኪሞች የጥርስ ሕመምና የጥርስ መውለቅ የሚያስከትለውን ሥቃይ ማስቀረት እንድትችል ሊረዱህ ይችላሉ። የአንተ ትብብር ታክሎበት ሐኪሞቹ በጥርስህ ላይ በመጣበቅ ባክቴሪያ የሚፈጥሩ ቆሻሻዎች የሚያደርሱትን ጉዳት ለማስወገድ ይሞክራሉ። ባክቴሪያዎች ጥርስ ውስጥ ተሰግስጎ የሚቀረው ምግብ ስለሚመቻቸው እንደልብ ይራባሉ። እነዚህ ባክቴሪያዎች በምግቦቹ ውስጥ የሚገኘውን ስኳር ወደ አሲድነት የሚለውጡት ሲሆን አሲዱ የጥርስን መስተዋት በመጉዳት ጥቃቅን ቀዳዳዎችን ይፈጥራል። ቀዳዳው ቀስ በቀስ ሰፍቶ ጥርስህ መቦርቦር ደረጃ ላይ ሲደርስ ጥርስህ መበስበስ ይጀምራል። በዚህ ወቅት ምንም ሕመም አይሰማህም፤ ነገር ግን ጥርስህ እየተቦረቦረ ሄዶ የጥርስህ ማዕከላዊ ክፍል ላይ ሲደርስ ኃይለኛ የሕመም ስሜት ይሰማሃል።

በቆሻሻው ምክንያት የሚፈጠረው ባክቴሪያ ሌላም ጉዳት አለው። ቆሻሻው በጥንቃቄ ካልተወገደ በስተቀር ድድን ሊያስቆጣና ከቦታው እንዲሸሽ ሊያደርግ የሚችል ታርታር የተባለ ጠንካራ የቆሻሻ ክምችት ይፈጥራል። ይህ ደግሞ በጥርስህና በድድህ መካከል ክፍተት እንዲኖር በማድረግ ድድህን የሚጎዱ ባክቴሪያዎች እንዲራቡ ምቹ ሁኔታ ይፈጥርላቸዋል። የጥርስ ሐኪምህ ችግሩ እንዲስተካከል ማድረግ ይችላል። ሁኔታውን ችላ ካልከው ግን ጥርስህን አቅፎ በያዘው በድድህ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሊደርስበትና ጥርስህ መውለቅ ሊጀምር ይችላል። በጥርስ መቦርቦር ምክንያት ከሚወልቀው ይልቅ በድድ መጎዳት ሳቢያ የሚወልቀው ጥርስ ይበልጣል።

ባክቴሪያዎች ከሁለት አቅጣጫ የሚሰነዝሩትን ጥቃት በመከላከል ረገድ ምራቅህ የሚጫወተው ሚና አለ። እስክትጠግብ ድረስ በምትበላበትም ሆነ ትንሽ ጣፋጭ በምትቀምስበት ጊዜ ምራቅህ የምግብ ትርፍራፊዎችን አስወግዶ በጥርስህ ቆሻሻ ላይ ያሉትን አሲዶች ለመበረዝ ከ15-45 ደቂቃ ይወስድበታል። ጊዜውን የሚወስነው በጥርስህ ላይ ተጣብቆ የቀረው የስኳር ወይም የምግብ መጠን ነው። ጥርስህ ጉዳት የሚደርስበት በእነዚህ ደቂቃዎች ውስጥ ይመስላል። በመሆኑም በጥርስህ ላይ የሚደርሰው ጉዳት የተመካው በምትበላው የስኳር መጠን ላይ አይደለም ማለት ነው፤ ከዚህ ይልቅ ቶሎ ቶሎ የምትመገብ ከሆነና ስኳርነት ያላቸውን ምግቦች የምታዘወትር ከሆነ ጥርስህ ሊጎዳ ይችላል። በእንቅልፍ ወቅት አፍህ የሚያመነጨው የምራቅ መጠን ስለሚቀንስ ጣፋጭነት ያላቸውን ምግቦች ወይም መጠጦች ከተመገብክና ከጠጣህ በኋላ ጥርስህን ሳትቦርሽ የምትተኛ ከሆነ በጥርስህ ላይ በጣም ከፍተኛ ጉዳት ታስከትላለህ። በሌላ በኩል ደግሞ ከምግብ በኋላ ስኳር አልባ ማስቲካ ማኘክ የምራቅህን መጠን ስለሚጨምር ጥርስህን ከጉዳት ለመከላከል ይረዳሃል።

በመከላከል ላይ ያተኮረ የጥርስ ሕክምና

የጥርስ ሐኪሞች እንደ ጥርስህ ሁኔታ በዓመት አንድ ወይም ሁለት ጊዜ ምርመራ ማድረግ ጥሩ እንደሆነ ይመክራሉ። በምርመራው ወቅት ሐኪምህ ጥርስህን ራጅ ሊያነሳና የጥርስ መበስበስ መኖር አለመኖሩን ለማረጋገጥ ጥንቃቄ የታከለበት ምርመራ ሊያደርግ ይችላል። ሕመም ባለበት ቦታ ላይ ማደንዘዣ በማድረግና በከፍተኛ ፍጥነት የሚንቀሳቀሱ የጥርስ መሰርሰሪያዎችን በመጠቀም የተቦረቦረ ቦታ ካለ ምንም ሳያሳምምህ ይሞላዋል። አንዳንድ ሐኪሞች ይህ ዓይነቱን ሕክምና የሚፈሩ ሰዎችን ለመርዳት ጨረር ወይም ጥርስ ላይ ያለውን ቆሻሻ ለማሟሟት የሚረዳ ቅባት መጠቀም ጀምረዋል፤ ይህ ደግሞ ማደንዘዣንም ሆነ የጥርስ መሰርሰሪያዎችን መጠቀምን ሙሉ በሙሉ አሊያም በከፊል የሚያስቀር ነው። ከልጆች ጋር በተያያዘ ሐኪሞች ይበልጥ ትኩረት የሚያደርጉት አዲስ ለሚበቅሉ የመንጋጋ ጥርሶች ነው፤ ምክንያቱም እነዚህ ጥርሶች ምግብ በሚታኘክበት በኩል ለማጽዳት የሚያስቸግር ስንጥቅ ወይም ጎድጎድ ያለ ቦታ ሊኖራቸው ይችላል። እንዲህ ዓይነት ሁኔታ ካለ ሐኪሞች የላይኛውን የጥርስ ክፍል ለጥ ያለ እንዲሆንና በቀላሉ ለማጽዳት እንዲመች ለማድረግ ሲሉ ቦታው እንዲሞላ ሐሳብ ያቀርባሉ። እንዲህ ያለው እርምጃ ጥርሱ እንዳይበሰብስ ለመከላከል ይረዳል።
አዋቂዎችን በተመለከተ ደግሞ የጥርስ ሐኪሞች ይበልጥ ትኩረት የሚያደርጉት የድድ በሽታ እንዳይከሰት መከላከል በሚችሉበት መንገድ ላይ ነው። በምርመራ ወቅት የተከማቸና ጠጣር የሆነ የጥርስ ቆሻሻ ካገኙ ያጸዱታል። አብዛኞቹ ሰዎች ጥርሳቸውን በሚቦርሹበት ጊዜ አንዳንድ ጥርሶችን ትኩረት ሰጥተው አያጸዷቸውም፤ በመሆኑም ሐኪሞች ጥርስ የማጽዳት ችሎታችንን እንዴት ማሻሻል እንደምንችል ሊጠቁሙን ይችላል። አንዳንድ የጥርስ ሐኪሞች ታካሚዎቻቸው ይህን ጠቃሚ ትምህርት እንዲያገኙ ለማድረግ በጥርስ ንጽሕና አጠባበቅ ወደ ሠለጠኑ ሰዎች ይልኳቸዋል።

የተጎዱ ጥርሶችን ወደቀድሞ ሁኔታቸው መመለስ

የተበላሸ፣ የወለቀ ወይም የተወላገደ ጥርስ ካለህ የጥርስ ሐኪሞች ጥርሶችህን ቀድሞ ወደነበሩበት ሁኔታ ለመመለስ የሚያስችሉ ብዙ አዳዲስ ዘዴዎች እንዳላቸው ማወቅህ ያስደስትህ ይሆናል። ይሁን እንጂ ይህ ዓይነቱ ሕክምና ውድ በመሆኑ ከአቅምህ በላይ እንዳታወጣ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርብሃል። የሆነ ሆኖ ብዙ ሰዎች እንዲህ ላለው ሕክምና ምንም ያህል ገንዘብ ቢወጣ የሚያስቆጭ እንዳልሆነ ይሰማቸዋል። ምናልባት ሐኪሙ በጥርስህ እንደገና ማኘክ እንድትጀምር ሊረዳህ ይችላል። አሊያም ስትስቅ ደስ የሚል ጥርስ እንዲኖርህ ያደርግ ይሆናል፤ ይህ ደግሞ ቀላል አይደለም። ምክንያቱም የተበላሸ ጥርስ በሕይወትህ የምታገኘውን ደስታ ሊቀንስብህ ይችላል።

ሐኪሞች የተሸረፉ ወይም የበለዙ የፊት ጥርሶችን ከተፈጥሯዊው የጥርስ መስተዋት ጋር በሚመሳሰል አንጸባራቂ ንጥረ ነገር መሸፈን ጥሩ እንደሆነ ይናገራሉ። ንጥረ ነገሩ በተጎዳው ጥርስ ላይ ተጣብቆ የጥርሱን ቅርጽና መልክ ይለውጠዋል። ጥርሱ በጣም የተጎዳ ከሆነ ሐኪሞች ብዙውን ጊዜ ክራውን ተብሎ የሚጠራ በጥርስ መልክ የሚሠራ ሽፋን እንዲለብስ ሊያዝዙ ይችላሉ። ይህ ሽፋን ሽራፊውን ሙሉ በሙሉ የሚሸፍነው ከመሆኑም በላይ ጥርሱ የወርቅ ወይም የተፈጥሮ ጥርስ መልክ እንዲኖረው ያደርጋል።

የተወሰኑት ጥርሶችህ ቢረግፉ ሐኪምህ በምን መንገድ ሊረዳህ ይችላል? ሰው ሠራሽ የሆነ ሊወልቅ የሚችል ጥርስ ሊገጥምልህ አሊያም ከወለቀው ቦታ ግራና ቀኝ ባሉት ጥርሶች ላይ ተሰክቶ አንድ ወይም ሁለት ሰው ሠራሽ ጥርሶችን ደግፎ የሚይዝ እንደ ማቀፊያ ያለ ነገር (fixed bridge) በቋሚነት ሊገጥምልህ ይችላል። ሰፊ ተቀባይነት እያገኘ ያለው ሌላው አማራጭ ደግሞ አዲስ ጥርስ ማስተከል ነው። ሐኪሙ ጥርሶችህ በነበሩበት መንጋጋ ውስጥ ከቲታንየም የተሠራ የጥርስ መቀበያ ይቀብርና አጥንትህና ድድህ ሲያገግም ሰው ሠራሽ ጥርሱን አስቀድሞ ድድ ውስጥ በተቀበረው መቀበያ ላይ ያስረዋል። ይህ ዓይነቱ ሰው ሠራሽ ጥርስ እውነተኛውን ጥርስ ይመስላል።
የተወለጋገዱ ጥርሶች የሚያሳፍሩ ከመሆናቸውም በላይ ለማጽዳት ስለሚያስቸግሩ በቀላሉ ለበሽታ ሊጋለጡ ይችላሉ። ከዚህም በላይ ጥርሶች በትክክል ካልተደረደሩ ሕመም ሊያስከትሉና ማኘክ አስቸጋሪ እንዲሆን ሊያደርጉ ይችላሉ። ደስ የሚለው ግን፣ የጥርስ ሐኪሞች የጥርስ ማሰሪያ ሽቦዎችን በመጠቀም ችግሩን ማስተካከል የሚችሉ መሆናቸው ነው። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሽቦዎቹ ንድፍ ላይ በታየው እድገት የተነሳ ዘመናዊዎቹ የጥርስ ማሰሪያዎች ብዙም የማይታዩና ማስተካከያ የማይፈልጉ ሆነዋል።
አንዳንድ የጥርስ ሐኪሞች መጥፎ የአፍ ጠረንን ለማስወገድ ከፍተኛ ጥረት ያደርጋሉ። ብዙ ሰዎች መጥፎ የአፍ ጠረን የሚያስቸግራቸው አልፎ አልፎ ሲሆን አንዳንዶች ግን ዘወትር ያጋጥማቸዋል። መጥፎ የአፍ ጠረን እንዲኖር የሚያደርጉ በርካታ ምክንያቶች አሉ። አንዳንድ የጥርስ ሐኪሞች የችግሩን መንስዔ ለይቶ ለማወቅ የሚያስችሉ መሣሪያዎች አሏቸው። አብዛኛውን ጊዜ ይህ ችግር የሚከሰተው በምላስ የኋለኛ ክፍል አካባቢ በሚፈጠሩ ባክቴሪያዎች አማካኝነት ነው። ስኳር አልባ ማስቲካ በማኘክ የምራቅህን መጠን መጨመርህ ችግሩን ለማስወገድ እንደሚረዳህ ሁሉ ምላስህን መቦረሽህም ለዚህ ትልቅ አስተዋጽኦ ያደርጋል። የወተት ተዋጽኦዎችን፣ ሥጋ ወይም ዓሣ ከተመገብክ በኋላ ጥርስህን ማጽዳትህ በጣም አስፈላጊ ነው።

የሚሰማህን ፍርሃት ማሸነፍ

ወደ ጥርስ ሐኪም መሄድ የሚያስፈራህ ከሆነ ሐኪምህ ይህንን ፍርሃትህን ማሸነፍ እንድትችል ሊረዳህ ይችላል። ስለዚህ ምን እንደሚሰማህ ንገረው። በሕክምናው ወቅት እንዳመመህ ወይም እንደፈራህ ለመጠቆም በእጅህ ምልክት መስጠት ትችል እንደሆነ ጠይቀው። ብዙ ታካሚዎች እንደዚህ ማድረጋቸው ፍርሃታቸውን ለመቋቋም ረድቷቸዋል።

አንዳንድ ጊዜ ደግሞ ሐኪሙ ይቆጣኛል ብለህ ትፈራ ይሆናል። እንዲሁም ለጥርስህ ጥሩ እንክብካቤ አላደረግህም ብሎ ያንቋሽሸኛል ብለህ ትጨነቅ ይሆናል። ነገር ግን ሐኪሞች እንዲህ ማድረጋቸው ገበያቸውን እንደሚዘጋባቸው አውቀው ጥንቃቄ ስለሚያደርጉ መፍራት አይኖርብህም። አብዛኞቹ የጥርስ ሐኪሞች ከታካሚዎቻቸው ጋር በደግነት የመነጋገር ፍላጎት አላቸው።

ብዙ ሰዎች ደግሞ ክፍያውን በመፍራት ወደ ጥርስ ሐኪሞች አይሄዱም። ነገር ግን አሁኑኑ ምርመራ የምታደርግ ከሆነ ከጊዜ በኋላ ለከፋ ችግር ከመጋለጥና ለከፍተኛ ወጪ ከመዳረግ ልትድን ትችላለህ። በየአካባቢው እንደየሰዉ አቅም የጥርስ ሕክምና የሚሰጡ ተቋማት አሉ። በደረጃ ዝቅ ያሉ ናቸው የሚባሉት የጥርስ ሕክምና መስጫ ተቋማት እንኳ ራጅ ማንሻና በከፍተኛ ፍጥነት የሚንቀሳቀሱ የጥርስ መሰርሰሪያ መሣሪያዎች አያጡም። የጥርስ ሐኪሞች አብዛኛውን የሕክምና ሂደት በታካሚዎቻቸው ላይ እምብዛም ሕመም በማያስከትል መንገድ ማካሄድ ይችላሉ። ለማደንዘዣ የሚከፈለው ክፍያም ቢሆን ብዙውን ጊዜ ዝቅተኛ ገቢ ካላቸው ሰዎች አቅም በላይ አይደለም።

የጥርስ ሐኪሞች ተግተው የሚሠሩት በሽታህን ለማስወገድ እንጂ ለማባበስ አይደለም። በዛሬው ጊዜ የሚሰጠው የጥርስ ሕክምና በአያቶችህ ዘመን እንደነበረው ለከፍተኛ ሥቃይ የሚዳርግ መሆኑ አብቅቷል። ጥርስህ ጤናማ መሆኑ፣ ለጠቅላላው ጤንነትህ የሚበጅህ እንዲሁም በሕይወትህ ይበልጥ ደስተኛ እንድትሆን የሚረዳህ ከሆነ ለምን የጥርስ ሐኪም ዘንድ አትሄድም? የሚያስደስት ሁኔታ ያጋጥምህ ይሆናል።

የኢትዮጵያ ወጣቶች ድምጽ ዜናዎች ዘገባዎች እና የተለያዩ ሃገራዊ ጉዳዮችን ያዳምጡ

$
0
0


የኢትዮጵያ ወጣቶች ድምጽ ዜናዎች ዘገባዎች እና የተለያዩ ሃገራዊ ጉዳዮችን ያዳምጡ
የኢትዮጵያ ወጣቶች ድምጽ ዜናዎች ዘገባዎች እና የተለያዩ ሃገራዊ ጉዳዮችን ያዳምጡ

Sport: ባርሴሎና ለሁለት ዓመታት ከተጫዋች ግዥ ታግዷል

$
0
0

የባርሴሎና ፕሬዚዳንት ጆሴፕ ማሪያ በፊፋና ዓለም አቀፉ የስፖርት ፍርድ ቤት ውሳኔ መበሳጨታቸውን በክለቡ ድረገፅ ላይ አስታውቀዋል፣

ዳግም ከበደ

ባርሴሎና የዓለም አቀፉን እግር ኳስ ፌዴሬሽን ህግ ጥሷል በሚል የተጫዋች ዝውውር እንዳይፈፅም ለሁለት ዓመታት የተጣለበትን ማዕቀብ ወደ ዓለም አቀፉ የስፖርት ፍርድ ቤት በማቅረብ ይግባኝ ቢጠይቅም ፍርድ ቤቱ ጥያቄውን ውድቅ አድርጎ የፊፋ ውሳኔ ተግባራዊ እንዲሆን አዟል። ባርሴሎና ከ18 ዓመት በታች ተጫዋቾችን አስፈርሟል በሚል በሁለት የዝውውር መስኮቶች ተጫዋቾችን ወደ ቡድኑ እንዳያስፈርም እገዳ ተጥሎበታል።
suarze barcelona
የዓለም አቀፉ እግር ኳስ ማህበር ፊፋን ውሳኔ ባለመቀበል ይግባኝ ያለው ባርሴሎና አሁንም ውሳኔው እንዲጸና በፍርድ ቤቱ ተወስኗል።ፍርድ ቤቱ ይግባኙን ውድቅ በማድረጉ ቡድኑ እስከ ጎርጎሮሳውያኑ ጥር 2016 ድረስ እገዳው ይጸናበታል። ባርሴሎና ከ18 ዓመት በታች የሆኑ ተጫዋቾችን አስፈርሟል በሚል ለሁለት ዓመታት ተጫዋቾችን እንዳያስፈርም ከመደረጉም በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ተወስኖበታል።
ዓለም አቀፉ የስፖርት ገላጋይ ፍርድ ቤት የወሰነውን ውሳኔ ተከትሎ የባርሴሎና ፕሬዚዳንት ጆሴፕ ማሪያ ባርቱሙ በክለባቸው ላይ የዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ክለብ ፊፋ ለሁለት ዓመታት ተጫዋቾች ግዥ እንዳይፈፅም ማገዱን ተከትሎ ትልቅ የፍትህ በደል ተፈፅሞብናል ሲሉ በክለባቸው ድረ ገፅ ላይ ገልፀዋል።
ባርሴሎና ከ18 ዓመት በታች የሆኑ ህፃናት ልጆችን ከተለያዩ የዓለም ሀገራት ተገቢ ባልሆነ መልኩ በማስፈረሙ ስህተት ፈፅሟል በሚል በፊፋ መወንጀሉ ስሀተት መሆኑንና የተላለፈው ውሳኔም ተገቢ አለመሆኑን ነው ፕሬዚዳንቱ የተናገሩት። ባርሴሎና የላማሲያን አካዳሚ በመባል የሚታወቅ ወጣት ተጫዋቾችን ስልጠና በመስጠትና ወደዋናው ክለብ በማዘዋወር እንደሚጠቀም ይታወቃል። በላማሲያ አካዳሚ ሊዮኔል ሜሲ እና አንድሬ ኢኒየስታን የመሳሰሉ በእግር ኳሱ ውስጥ ተፅእኖ መፍጠር የቻሉ ተጫዋቾችን አፍርቷል።
ክለቡ የተጫዋቾች ግዥ ላይ እንዳይሳተፍ ከታገደ በኋላ ለአውሮፓ ከፍተኛው የእግር ኳስ ፍርድ ቤት ይግባኝ ቢልም ቅሬታው በድጋሚ ውድቅ መሆኑ የክለቡ አመራሮችን አበሳጭቷል። በፍርድ ቤቱ ውሳኔ ክፉኛ የተበሳጩት የክለቡ ፕሬዚዳንት በክለቡ ድረ ገፅ ላይ የተወሰነውን ውሳኔ አብጠልጥለውታል። « ዛሬ ፍትህ ተነፍገናል። ትልቅ ፍትሃዊነት የጎደለው ውሳኔ ዛሬ በክለባችን ላይ ተወስኗል ፣ ውሳኔው ቀጥተኛ ግንኙነት ያላቸው ህፃናትና ቤተሰቦቻቸው፣የክለቡ አባላት፣እንዲሁም መላው እግር ኳስ አፍቃሪ ላይ የተፈፀመ በደል ነው» በማለት ምሬታቸውን በክለባቸው ድረ ገፅ ላይ አስፍረዋል።
አሁን ያለው የተጫዋቾች ስብስብ ክለቡን በእግር ኳስ ደረጃቸው ከፍተኛ ከሚባሉ ክለቦች ተርታ የሚያስመድበው ቢሆንም ውሳኔው ባርሴሎና ላይ ተፅእኖ ይፈጥርበታል። ወደፊት ሊያጋጥም በሚችል የተጫዋቾች ጉዳት ወይም የአቋም መውረድ ክለቡ የተጫዋቾች ግዥ ላይ ለመሳተፍ የሚገደድባቸው ሁኔታዎች ሊፈጠሩ ይችላሉ። በላሊጋው ላይ ያለው የበላይነትና ተፎካካሪነትንም እንዲያሽቆለቁል ሊያደርገው ይችላል።
በፍርድ ቤቱ ውሳኔ የተበሳጩት የክለቡ ፕሬዚዳንት ጆሴፕ ማሪያ በተደጋጋሚ ፊፋ ፍትሃዊነት የጎደላቸው ውሳኔዎችን እንደሚወስን ነው የሚናገሩት።« በተደጋጋሚ ፊፋ የሚወስናቸው ውሳኔዎች ተገቢነት የሌላቸውና የተጋነኑ መሆናቸውን ለማስረዳት ሞክረናል። ሆኖም ግን እራሱ ፊፋና ፕሬዚዳንቱ ህጉን በድጋሚ ቢያጤኑትና እግርኳሱን ከሚረብሽ ድርጊት ቢቆጠቡ ለእግር ኳሱ ወዳጆች መልካም ነው» በማለት በተጫዋቾች ዝውውር ላይ ያለውን ህግ በድጋሚ ማየት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።


ወያኔ የጉራጌ ማህበረሰብ ከሌላው የህብረተሠብ ክፍል ለማጋጨት በወልቂጤ ዩኒቨርሥቲ እየፈጸመው ያለው ደባ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ሊገነዘበው ይገባል

$
0
0

By Seyoum Workneh

ከላይ በርዕሱ ላይ የጉራጌ ማህበረስብ ከሌላው የህብረተሰብ ክፍል ብዬ የተጠቀምኩት ወያኔ/ኢህአዴግ በጉራጌ ዞን በቸሃ ወረዳ ጉብሬ ከተማ ላይ በህዝብ ድጋፍና እርብርቦሽ የተመሠረተችው ወልቂጤ ዩኒቨርሥቲ ውሥጥ በተግባር እያደረገ ያለውን ጉዳይ ነጠል አድርጌ ለማሣየት እንጂ ወያኔ በሁሉም የሐገራችን ክፍል የተሠማራበት እኩይ ተግባር ጠፍቶኝ እንዳልሆነ ልትረዱልኝ እፈልጋለሁ። ባጠቃላይ ወያኔ ኢትዮጵያ ሐገራችን ለማጥፍት ግቡ አድርጎ የሚንቀሳቀሥ የትኛውንም ህዝብ ሊወክል የማይችል በጥቂት ማፍያ ወንበዴዎች የሚመራ የሆዳሞች ድርጅት ነው። የመጨረሻ የሆነውን ሐገር የማፍረሥ አላማቸው እውን እሥኪሆን ድረሥ ሀገሪቷን መምራት ሥለ ሚፈልጉ ህዝቡ አንድ እንዳይሆን የተቻላቸውን ሁሉ ከማድረግ ወደ ኻላ እንደሚያደርጉ ልንገነዘብ ይገባል።

welktie

ከፋፍለህ ግዛ (በዘር) መርህ የሚከተለው ወያኔ ላለፉት 23 ዓመታት ህዝቡን እርሥ ብርሥ እንዳይተማመን፤ እርሥ በርሥ እንዲተላለቅ፤ እርሥ በርሥ እንዲጥላላ አያሌ ሥራዎችን ሠርቷል። ህዝቡን በዘር፣ በሐይማኖት፣ በፖለቲካ አመለካከት፣ በእምነትና በሌሎችም ተመሣሣይ ጉዳዮች ለመከፍፈል በፖሊሢ ደረጃ ተቀርጾ ሢመሩበት የነበረና አሁንም ያለ ህዝብ ፍቃድ የገፉበት ጉዳይና ፖሊሢ ነው። የኢትዮጵያ ሕዝብ ከ3000 አመት በላይ ተከባብሮና ተቻችሎ፣ ያሉትን ልዩነቶች አጥብቦ የኖረባት ሐገር ዛሬ የዘር ፖለቲካን በማራመድ በህዝብ ዘንድ ጥላቻን በማሥፈንና ልዩነቶችን በማሥፍት የኢትዮጵያ ህዝብ ሆድና ጀርባ ለማድረግ ተግተው እየሠሩ ነው። ወያኔ በዚህም ተግባሩ ከልማት መንገድ ይልቅ የጥፍት መንገድ መምረጡን ያመለክታል።

ወያኔ በዚህም መሠሪ ተግባሩ ሙሉ በሙሉ ተሣክቶለታል ማለት ባይቻልም በተወሰነ ደረጃም ቢሆን ግን የዚህ ተግባር እርዝራዦች፣ አደር ባዮች፣ አጎብዳጆችና ሆዳሞች ግን አልጠፉም። አንዳንዶቻችን የወያኔ መሠሪ ተግባርና አላማ ጠንቅቀን የምናውቅ ብንሆንም ከወጥመዱ ማለፍ ያልቻልን ደካሞችም መኖራችን ግን አልቀረም። ወያኔ ሁላችንም ጠባብና ትምክተኛ እንድንሆን እንደሚፈልግ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ጠንቅቆ የሚያውቀው ይመሥለኛል። ይህ ከሆነ ደግሞ ሁላችንም ወጥመዱ ውሥጥ እንዳንደናቀፍ አሥፈላጊ ጥንቃቄ መውሠድ ይጠበቅብናል። ያ ሳይሆን ሲቀር ግን እራሣችን ወያኔ ባዘጋጀው መረብ ውሥጥ ተጠልፈን ትክክለኛ መሥመር እየተከተሉ ያሉትን ማደናቀፋችን ወይም እየተከተሉት ላለው የለውጥ ጎዳና እንቅፍት መሆናችን አይቀሬ ነው። በዚህ ጊዜ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የወያኔ መሣሪያ ሆነናል ማለት ነው።

ወደ ዋናው ጽሁፌ ሥመለሥ ወያኔ በወልቂጤ ዩኒቨርሥቲ እያደረገ ያለውን ነገር አሣሣቢ ደረጃ ላይ በመድረሡ ምክንያት ነው። ይህም ዩኒቨርሥቲው ውሥጥ ወያኔ የራሡን ሠዎች በማዘጋጀት ፍራሽ ከተደረደረበት ክፍል እሥከ የተማሪ ማደሪያ የሆኑትን ዶርሚተሪዎችን በማቃጠል ከሌላ ክልል የመጡት ተማሪዎች ድርጊቱን እንደፈጸሙት በማድረግ የጉራጌ ማህበረሰብ ከሌላ ክልል ለመጡትን ተማሪዎችም ሆነ ሥለ ሌላው ማህበረሰብ የተሳሳተ አመለካከት እንዲኖረው ለማድረግና እርሥ በርሥ ለማጋጨት ነው። በመሠረቱ የጉራጌ ማህበረሠብ በሁሉም የሐገራችን ክፍል በተለያዩ የግልና የመንግሥት መሥሪያ ቤት በተለይ የንግድ ሥራ ላይ ተሠማርቶ የሚሠራ ህዝብ እንደመሆኑ መጠን ከሁሉም የሐገራችን ክፍል የሚመጡ ሠዎች ጋር በደንብ የመገናኘት አጋጣሚ ሥላለው የኢትዮጵያ ህዝብ ምን ያህል ጨዋ እንደሆነ ጠንቅቆ ያውቃል። በዚህም ምክንያት ወያኔ የሚፈጸማቸው ድርጊቴች ወይም የወያኔ ሴራዎች ጠንቅቆ የሚያውቅ ሕዝብ ነው።

ባሳለፍነው ሳምንት ታህሳስ 25, 2014 እኤአ ጠዋት በወልቂጤ ዩኒቨርስቲ ሁለት ተማሪዎች (አንደኛው ከአማራ ክልል የመጣ, ሁለተኛው ከኦሮምያ ክልል) መጣላታቸውን ተከትሎ ከኤሮምያ ክልል የመጡት ተማሪዎች የግቢው ህንጻዎች ላይ በሌሊት አደረሱት የተባለውን ጉዳት ተከትሎ የአካባቢው ማህበረሰብ ላይ የፈጠረው መጥፌ ሥሜት ነው። እዚህ ላይ ሁሉም የጉራጌ ማህበረሰብ ማወቅ ያለበት ነገር ቢኖር የዚህ ሁሉ ተጠያቂው ወያኔ መሆኑን ነው። ምክንያቱም የኦሮሞ ህዝብ ለብዙ አመታት ከጉራጌ ማህበረሰብ አብሮ የኖረና ተጋብቶ የተዋለደ እንደመሆኑ መጠን ምንም አይነት ችግር እንደሌለባቸው ነው። ሥለዚህ የተፈጠረው ድርጊት በማንም ይሁን በማን ወያኔ ህዝቡን ለማጋጨት ሆን ብሎ የፈጸመው እንጂ ከኦሮሞ ምህበረሰብም ሆነ ተማሪዎች ጋር ምንም አይነት ግንኙነት እንደሌለው ነው። ለወደፊትም ቢሆን ጥንቃቄ ልንወስድ ይገባል።

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!

የመስቀሉ ደም –ከሥርጉተ ሥላሴ

$
0
0

bahrdar 7

04.01.2014

ሲዊዘርላንድ – ዙሪክ/

ህማማት – ጸንሶ

ዕንባውን – አፍሶ

መስቀል ረገመ – በደም ተለውሶ

በበላሃሰቦች ኪዳኑ – ተረግጦ።

እህ! – እህህ –ህህህ —ህህህ – ህህህ

ሆይ! አለህን!? – አለህን በቤትህ? – አለህ!?!

እንሆ ——- ዘመን ተገርድሶ

ቀዬውን ተወርሶ – ጢሶ – ጢሶ ——

በትዕቢት – ተጥሶ፤

ፋሽስቱ – ቀስሶ

ዕምነት – ተቆራርሶ

ሽበት – ባት – ተውሶ፤

ቀኑም አለቀሰ – መስቀሉን  – እያዬ

ዘመንም አነባ – ቁም ስቅሉን ስላዬ፤

መርገምትን – አምጦ – እግዚዖታን አዋዬ።

ከልቡ በቅላለች – በላይ እንደ ገና

ዘለቀች ተጣራች መንፈሰ – ገናና

…. ንጥር – ዬአውራ -

ር – ለባንዴራ።

የታሪክ ማህደር – በደም የተቃኘች

ሰንደቁ ናትና ደምቃ –  የታተመች።

አጠናት ከልቡ – የኪዳን ህይወቱን

ይሞቃል ጠረኑ – ድፈረትም ያባቱ፤

የጥንት —– የጥዋቱ

የእናት ሀገር ሃብቱ።

ትናንትን አዳምጦ – በቃኝን አስጊጦ

ነፃነት …. አምጦ – አምጦ – አምጦ -

ዓርነት …… ተጠምቶ – ተጠምቶ – ተጠምቶ -

ተማግዶ – ተማግዶ – ተማግዶ -

ካለ ርህራሄ ተወጋ ——- በዘንዶ፤

ለባዕቱ – ደምቶ – እራሱን ሰጥቶ

ብሩህ ቀን ሰንቆ – ሰላምን ተመኝቶ

እናቱን አላቀ ትውልድ – ታሪክ ሠርቶ።

ሥጦታ – ለቅድስት እናት ለእሙሃይ ይሁንልኝ።

ይህቺ ምልክት አንድ ፊደል „እ“ መዋጧን ታመለክታለች። ከትህትና ጋር፤

እግዚአብሄር ይስጥልኝ።

በተናጥል ሆኖ ፖለቲካውን ማራመድ ጎታች አይደለም –ይልቃል ጌትነት

$
0
0
Hiber Radio Interview with Eng Yilkal Getnet

ይልቃል ጌትነት

የሚሊዮኖች ድምጽ አገር ቤት በአንድነት ፓርቲ ኤዲቶሪያል ቦርድ የምትታተም  ነፃ ጋዜጣ ናት። በሁለተኛ እትሟ የሰማያዊ ሊቀመንበር አቶ ይልቃ ጌትነትን ይዛ ቀርባለች። ሊቀመንበሩ ከሕዝቡ የሚነሱ ፣  አብሮ ከአንድነት ፓርቲ ጋር አብሮ በመስራት ዙሪያ ያጠነጠኑ ጥያቄዎች የቀረበላቸው ሲሆን፣ የአንድነቱ መሪ አቶ በላይ  ፍቃደ በአዲስ ድምጽ ራዲዮ ከሰጡት አስተያየት የተለየ በአብሮ መስራቱ ዙሪያ ተስፋን የሚሰጥ ሳይሆን ተስፋን የሚይጨለም መልሶችን ነበር የመለሱ።

አቶ በላይ ፍቃዱ ፣ አንድነት፣ ሰማያዊ፣ መኢአድ እና ትብብር ተመሳሳይ የፖለቲካ ፕሮግራም ያላቸው እንደመሆኑ በተናጥል መሆናቸው ትርጉም የማይስጥ ነው የሚል ምላሽ በመስጠት ድርጅታቸው የሕዝብ ጥያቄ  በአክበር ዓብሮ ለመስራት መደረግ ያለበትን ሁልሉ እንደሚያደርግ ማሳወቃቸው ይታወቃል። የሰማያዊ መሪ አቶ ይልቃል ጌትነት ግን፣  በተናጥል ሆኖ ፖለቲካውን ማራመድ ጎታች አይደለም የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

ከቃለ ምልልሱ የተወሰነውን እንደሚክከተለው ያንብቡ

ሚሊዮኖች ድምጽ – ትብብሩ ውስጥ ካሉ ፓርቲዎች ውጭ ከእናንተ ጋር ተመሳሳይ አቋም ያለው ፓርቲ አለ ብላችሁ ታስባላችሁ?

አቶ ይልቃል ጌታነት – የሌሎቹ አልጠራም፡፡ ግራ የሚያጋቡና ያልጠራ ነገር አላቸው ብዬ አምናለሁ፡፡ ከዚህ ውጪ ሌሎች ፓርቲዎች ላይ አስተያየት ለመስጠት እቸገራለሁ፡፡ የሀገራችን ፖለቲካ ገና ነው፡፡ በጎንዮሽ ለመተቻቸት ቅንጦት የሆነበት ደረጃ ነው ያለው፡፡ ህዝባችንም በተቃዋሚዎች ላይ ተስፋ በሚያደርግበት ጊዜ መተቻቸት ብዙም ጠቃሚ አይደለም፡፡

ሚሊዮኖች ድምጽ – ‹‹ተመሳሳይ ፕሮግራም እና ዓላማ ያላቸው ተቃዋሚ ፓርቲዎች አንድ ሆነው የማይሰሩበት ምክንያት አሳማኝ አይደለም›› የሚሉ አስተያየት ሰጪዎች አሉ፤ እናንተ ደግሞ ‹‹በውህደት ከመሄድ ይልቅ ብቻችንን ሄደን ዓላማችንን እናሳካለን ነው›› የምትሉት፡፡ በዚህም ብዙ ሰዎች ትችት ይሰነዝሩባችኋል፡፡ መልሳችሁ ምንድን ነው?

አቶ ይልቃል ጌታነት – ተቺዎቻች መጀመሪይአ መብታቸው ነው። ሁለተኛ የአደባባይ ሰዎች ስንሆንና በጋራ ጉዳይ ላይ ስንቆም ተቺዎች ሊያወሩ እንደሚችሉ እናምናለን፡፡ ኢትዮጵያ ሰፊ ሀገር ናት፤ ብዙ ውጥንቅጦች ያሉባት ሀገር ናት፡፡ የሃይማኖት መሪዎች ወይም የሃይማኖት ሰዎች አይደለንም፤ ፖለቲከኞች ነን፡፡ በእኛ አመለካከት፣ በእኛ ሃሳብ የማይስማሙም የሚደግፉም አሉ፡፡ ያ በራሱ ጤናማና እንደመልካም የፖለቲካ እድገት ነው የምናየው፡፡ ከተቺዎቻችን የሚመጣው ሀሳብ ዋጋ ያለው ነገር ሆኖ ስናገኘው ደግሞ እንማራለን፡፡

ሚሊዮኖች ድምጽ – በተናጥል ሆኖ ፖለቲካውን ማራመድ ለለውጡ ጎታች አይደለም?

አቶ ይልቃል ጌታነት  – ጎታች አይደለም፡፡ ቢተባበሩ የበለጠ ጥሩ ነው፡፡ በመርህ ደረጃ ችግር የለም፡፡ በተግባራዊነቱ ላይ ነው እንጂ ችግር ያለው፡፡ ያለችህን ኃይል ሁሉ አጠራቅመህ አንድ ላይ ብታደርጋት የተሻለ ጅረት እንደምትሰራ መገንዘብ የማይችል ሰው ያለ አይመስለኝም፡፡

ሚሊዮኖች ድምጽ – ሰማያዊ እና አንድነት ቢዋሃዱ ሊቀመንበርነቴን ላጣ እችላለሁ የሚል ስጋት አለብህ?

አቶ ይልቃል ጌታነት –  እኔ ስጋት የለኝም፡፡ አንደኛ ስኬትና ውጤት ሊቀመንበር በመሆን ብቻ ነው የሚመጣው ብዬ አላምንም፡፡ ክብርንም፣ ሞገስንም፣ ታሪክንም ሆነ ሰው የሚወዳቸው ነገሮችን በሙሉ ለማግኘት ሊቀመንበር መሆን የግድ አያስፈልግም፡፡ እኔ ሀገሬን ለመጥቀምም ሆነ ራሴ ተከብሬ ለመከበር የሚያስችለኝ ሊቀ-መንበርነቴ ነው ብዬ አላስብም፡፡ 70 ሊቀመንበር ነው እዚህ ሀገር ያለው፡፡ 70ዎቹን ሁሉ እኮ የምታውቀቸው አይመስለኝም፡፡ ምናልባትም አዲስ ጋዜጣ መስርተህ በጋዜጣህ ሁለተኛ ዕትም የመጣኸው እኔ ጋር ነው፡፡ያ የመጣው በተናጥል ሆኖ ፖለቲካውን ማራመድ ለለውጡ ጎታች አይደለም? መብታቸ ው ነው ፡ ፡ ሊቀመንበር በመሆኔ አይደለም፡፡ ስኬትና ውጤት በሥልጣን እርከን አይመጣም፡፡ሌላም አስተያየት አለ፡፡ ‹‹አንድነት እና ሰማያዊ እንዲዋሃዱ የማትፈልገው የመርህ ይከበር አባል ስለነበርክና ከዚያ ጋር በተያያዘ ቂም ነው›› ይባላል፡፡

አቶ ይልቃል ጌታነት –  ይሄ የተሳሳተ መረጃ ነው የሚመስለኝ፡፡ በዛ ደረጃ ከሆነ ከሌሎች ፓርቲ ሰዎች የበለጠ ከአንድነት ሰዎች ጋር ጓደኝነትም ቀረቤታም አለን፡፡ እንዲህ አይነቱ አባባል በመላምት የሚሰጥ አስተያየት ነው፡፡ በጓደኝነት አንድነት ፓርቲ ቤት ካሉ ሰዎች ጋር እንቀራረባለን፡፡ በሥራ አስፈጻሚ ውስጥ ያሉት ሳይቀሩ የቅርብ ጓደኞቼ ናቸው፡፡የምንከባበር ሰዎች ነን፡፡ ቡናም ሻይም አብረን እንጠጣለን፡፡ እዛም ውስጥ እያለን፣ ትግሉ ላይ ባሉ አንዳንድ የመርህ ችግሮች ሳቢያ አብዮት ስናስነሳ ከሰዎቹ ጋር የግል ጠብ እኔ በበኩሌ አልነበረኝም፡፡ ሁሉንም ሰዎች በተለያየ ጊዜ እናገኛቸዋለን፡፡ ከዚያ ከአንድነት ጋር ወደፊት ለመስራትም ሆነ ላለለመስራት የሚወስነን ነገር በሚያራምዳቸው አቋሞች በሚወስዳቸው እርምጃዎችና በያዛቸው የጋራ አስተሳሰቦች መረጃ ነው መታየት ያለበት፡፡ እንደውም ሰማያዊና አንድነት ለመቀራረብ ከሌላው የተለየ ብዙ አጋጣሚዎች ያላቸው ድርጅቶች ናቸው ብዬ አስባለሁ፡፡ ሌላም ሰው ብትጠይቅ እንደዛ የሚል ይመስለኛል፡፡በእኛ ሀገር ባህል ‹‹የተጣላ ሰው ተመልሶ አይገናኝም›› ከሚል የሚነሳ መላምት ካልሆነ በቀር እውነታው እንደሚባለው አይደለም፡፡

ሚሊዮኖች ድምጽ  – ሰማያዊና አንድነት ባንተ የሥልጣን ዘመን አንድ የሚሆኑ ይመስልሃል?

አቶ ይልቃል ጌታነት –  ፖለቲካ ተለዋዋጭ ነገር ነው፡፡ዛሬ አይሆንም ያልከው ነገር በአጭር ጊዜ ሆኖ የሚታይበት ጊዜ አለ፡፡ በተግባር ግን ዝብርቅርቅ ያሉ የአስተሳሰብ ርቀቶችና ልዩነቶች እንዳሉ ይታየኛል፡፡ አብረው ሊያደርጓቸው የሚችሉና ሊያከናውኗቸው የሚችሉ ተግባሮችም እንዳሉ ይሰማኛል፡፡በሂደት ደግሞ በሚያገናኟቸው ነገሮች መቀራረብ ሊፈጥሩ እንደሚችሉ እገምታለሁ፡፡ግን በሐሳብ ደረጃ እኔ ሳየው አሁንም ቢሆን በአንድነት በኩል ያሉት አስተሳሰቦችና ትግሉን የመረዳት ደረጃዎች ከእኔ እይታ ጋር በተወሰኑ ደረጃዎች መራራቆች እንዳሉ ማየት እችላለሁ፡፡ ትግሉን በሚረዱት ደረጃና እንደ ስብስብ በሚወስዷቸው አቋሞች ልዩነት አለ፡፡ አንድነት ከመድረክ ጋር ነበረ፡፡ለምን ከመድረክ ጋር ተለያየ? ወደ መድረክ ሲሄድ ያሻሻላቸው ፕሮግራሞች አሁንስ አሉ ወይ? የሚሉ ጥያቄዎችን ማንሳት ይቻላል፡፡ጥርት ያለ ነገር ካለ አብሮ ለመስራት የሚያስችሉ ሁኔታዎች የሚፈጠሩ ይመስለኛል፡፡

ሚሊዮኖች ድምጽ – በሀገር ውስጥ እና በውጭ ያሉ ለውጥ ፈላጊዎች፣ “ግራ ተጋባን፤ ማንን እንደግፍ? በአንድነት በሰማያዊና በመኢአድ መሀከል እየዋለልን ነው፡፡” ይላሉ፡፡ ለእነዚህ ሰዎች ምን ትላቸዋለህ?

አቶ ይልቃል ጌታነት – መዋለሉ በራሱ አንድ የአስተሳሰብ ደረጃ ስለሆነ በቀና ነው የማየው፡፡ በሂደት ወደ አንዱ ይጠቃለላሉ፡፡ ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ግልጽ ያልሆኑ ሃሳቦች የሚጠሩበት ጊዜ ሩቅ አይመስለኝም፡፡ ያኔ መልስ ያገኛሉ፡፡

ሚሊዮኖች ድምጽ  – የሰማያዊ ፓርቲን የፖለቲካ እንቅስቃሴ በአዎንታዊ ጎኑ የሚያዩት ሰዎች እንዳሉ ሁሉ “ጀብደኝነት የሚወዱ ትንንሽ ልጆች ናቸው፡፡ ፖለቲካውን አያውቁትም፡፡ ዝም ብሎ ከፖሊስ ጋር ከመጋፈጥ የራቀ ዓላማ የላቸውም” ብለው የሚተቿችሁም ሰዎች አሉ፡፡ውዳሴውንና ትችቱን እንዴት ታየዋለህ?

አቶ ይልቃል ጌታነት –  ይሄ ለመተቸት ያህል የሚነገር ነገር ነው፡፡ የጠቀሱት ነገር የለም፡፡ ምን በማድረጋችን ነው የምንተቸው? በወሰድነው አቋም ነው? በፕሮግራማችን ነው? እኔ በተናገርኩት ነገር ነው? ወይስ ምንድን ነው? በያዝነው የፖለቲካ አስተሳሰብም ይሁን በአደባባይ በተናገርናቸው ነገሮች ላይ ማንም ሰው አንድ ሁለት ብሎ ነቀፌታ ሰጥቶ አያውቅም፡፡ እኔ ሶስት ዓመት ያህል በሰፊው ተናግሬያለሁ፡፡ በተለያየ ጊዜ በተለያዩ ሚዲያዎች ላይ ከተናገርኩት ውስጥ ምናልባት “ተቃዋሚዎችን አጣጣለ” ከሚለው አስተያየት ውጪ በፖለቲካዊ አመለካከቴና በፖለቲካዊ ብስለቴ አሳማኝ ትችት ያቀረበ አንድም ሰው የለም፡፡ ለነገሩ አዲስ ፖለቲካ ውስጥ ነው ያለሁት፡፡ በህይወቴ ብዙ የምማረው ነገር አለኝ፡፡ ትላንት የነበረኝ አስተሳሰብና የዛሬው ይለያያል ፡ ፡

http://www.andinet.org/wpcontent/uploads/2015/01/

የጠለምትና የወልቃይት ጠገዴ ጉዳይ የጎንደሬዎች . . .(አንዱዓለም ተፈራ)

$
0
0

አንዱዓለም ተፈራ – የእስከመቼ አዘጋጅ

ታህሣሥ ፳ ፭ ቀን ፳ ፻ ፯ ዓመተ ምህረት ( 01/03/2015 )

welkaiyt

በጠለምት፣ በበየዳ፣ በጃናሞራ፣ በወልቃይት፣ በጠገዴ፣ በአርማጨኾ ነዋሪው እየተባረረ፣ ሀብቱ እየተዘረፈ፣ ያንገራገረው እየተገደለ፤ ሰው በምሬትና በሰቀቀን ኑሮውን መግፋት አቅቶት አጣብቂኝ ላይ ገብቷል። ትናንት ቡያ ነበር ክልሉ። ትናንት በሀከር ነበር ክልሉ። ቀጥሎ ራስ ደጀንን ወደነሱ አካተቱት። ጠገዴን ጠቀለሉት። ገፍተው ስሜን አውራጃን በሙሉ ጠቀለሉ። ወገራ አውራጃን ሽራርፈው ወሰዱና ጎንደር አውራጃን ተጠጉ። አሁን ዘለው የጎንደር ከተማውን ገነት ተራራ፤ የትግራይ መሬት እያሉ ለትግራይ ልጆቻቸው እያሰተማሩ ነው። ጎንደር ከምድረ ገጽ እንድትጠፋ እየተገፋ ነው። ይህ የመኖርና ያለመኖር፤ ውሎ የማደርና በወጡበት የመቅረት፤ ተገፍቶ ተገፍቶ የገደል ጫፍ ላይ የተንጠለጠለ ሕይወት ሕዝቡን ሰቅዞ ይዞታል። ይህ ጉዳይ የጎንደሬዎች ብቻ ጉዳይ አይደለም። አዎ! በዋግም ተመሳሳይ ተግባር እየተፈጸመ ነው። የዋግ ጉዳይ የወሎዬዎች ብቻ ጉዳይ አይደለም። በመተከል ተመሳሳይ ተግባር እየተፈጸመ ነው። ይህ ጉዳይ የጎጃሜዎች ብቻ ጉዳይ አይደለም። በሐረርና በአርሲም ሲጀምር በግልጽ ይህ ጉዳይ ተተግብሯል። በጉራፈርዳና በደቡብ ክልል የተደረገው ኢትዮጵያዊያንን በያለንበት ሰቅጥጦናል። ይህ ጉዳይ የአንድ አካባቢ ወይንም የተወሰኑ ሰዎች ጉዳይ አይደለም። ይህን ካልተገነዘብንና መልስ ካላዘጋጀን፤ ለተከታዩ ሂደት ተጠያቂዎች፤ እኛው ጆሯችንን ደፍነን፣ ዓይኖቻችንን ጨፍነን፣ ዝም ያልነው በሙሉ ነን። የአካባቢው ሰው ብቻ ተቆርቋሪና እርምጃ ወሳጅ ነው የሚል እምነት ካለን፤ ከትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር በምንም መንገድ ያልተለየን ነን። ለምን ይኼን ጉዳይ ክብደት ሠጥቼ የጽሑፌ ማጠንጠኛ እንዳደረግሁት ላስረዳ፤

ጉዳዩ፤ ጠለምት፣ ወልቃይት፣ ጠገዴ፣ አርማጨኾ፣ በየዳ፤ ብራ ዋስያ፣ ሻግኔና ላሄን፣ ድብ ባሕር፣ አብደራፊና ሁመራ፤ከጎንደር ተነጥቀው ለትግራይ ተሠጥተዋል። በጠቅላላው የስሜንና የወገራ አውራጃዎች ወደ ትግራይ ገብተዋል። ይህ በጎንደር ሲሆን፤ በተመሳሳይ መልኩ የወሎው ዋግ ተነጥቆ ለትግራይ ተሠጥቷል።

ጉዳዩ፤  በነዚህ ቦታዎች የነበረው ነዋሪ፤ በደቡብ ኢትዮጵያ የሚኖረው አማራ፤ ሀገርህ አይደለም ተብሎ እንደተፈናቀለው፣ እንደተገደለው፣ ሀብቱ እንደተነጠቀበትና እንደተባረረው ሁሉ፤ እኒህም ለዚሁ ዕጣ ተዳርገዋል። መሬታቸው ብቻ ሳይሆን፤ ሀብታቸው ተዘርፏል። ከብቶቻቸው ተነድተዋል። እህላቸውን ተነጥቀዋል። ያንገራገሩት ተገድለዋል። እሽ ያሉት በወባና በተላላፊ በሽታ እንዲያልቁ ባልሆነ ቦታ ሰፍረዋል።

ጉዳዩ፣  በነዚህ በተነጠቁ ቦታዎች አጎራባች ሆነው የሚገኙት ነዋሪዎች፤ የተነጠቁትን ወገኖቻችንን በማስጠጋት ለወደፊት የባለቤትነት ጥያቄ እንዳያነሱና ሰላም እንዳያገኙ፤ ጎንደሬዎችን እርስ በርስ በማፋጀት ለማጥፋት፤ ሌላ አጀንዳ አውጥቶ፤ በአርማጨኾና በጭልጋ አካባቢ ያሉትን፤ ቅማንትና አማራ በማለት ከፋፍሎ፤ ጥልቅ ግጭት በመፍጠር ለማተላለቅ ቁስቆሳውን እያጧጧፈው ነው።

እንግዲህ ነጥቡ ይህ ጉዳይ ከፍተኛ ትኩረት ሊሠጠው የሚገባው ሀገራዊ አጀንዳ ነው። ያካባቢው ወገናችን ለብቻው ጥቃቱን እስከዛሬ ችለውታል። በዝርዝር ላስቀምጥ፤

  • ከሌሎች የሀገራችን ክፍሎች በባሰ መንገድ በጎንደር በኩል የኢትዮጵያ ደንበር በስፋት ተደፍሯል። መሬቱ ለሱዳን ተሠጥቷል። ከሌሎች የሀገራችን ክፍሎች በባሰ መንገድ የጎንደር ለም መሬት ወደ ትግራይ ተወስዷል።
  • በነዚህ አካባቢዎች ይኖሩ የነበሩት ወገኖቻችን፤ ተለቅመው በመባረር በቦታቸው የትግራይ ሰዋች እንዲሰፍሩ ተደርገዋል። ሕዝቡ ማንነቱን ሳይጠየቅ የተደረገው ነጠቃ፤ ከውጭ የመጣ ወራሪ ከሚያደርገው ግፍና በደል ያልተለየ ነው።
  • በጎንደር ከተማ ውስጥ ሥልጣኑንና ሀብቱን አሟጠው የያዙት የትግራይ ተወላጆች ናቸው። ይህ የከተማውን ወገናችን በጣም ከማማረሩ በላይ፤ የቂም መርዝ እየተከለ ነው።

ይህ ያካባቢውን ወገናችን ወደየት ይገፋዋል?

  • ቀሪው ኢትዮጵያዊ ስላልደረሰልኝ፤ ዝም ብዬ መጠበቄ አያዛልቀኝም። እናም ራሴን ላድን ወደሚል፤
  • የራሴን ዕድል ራሴ ልወስን ወደሚል፤
  • የኔ አጀንዳ የሌሎች አጀንዳ ስላልሆነ፤ የራሴን አጀንዳ ራሴ ብቻ ማንገብ አለብኝ ወደሚል፤

እና ምን መደረግ አለበት?

ሀ)       ታሪኩን መርምረን ማጥናት የያንዳንዳችን ኢትዮጵያዊ ግዴታ ነው። በተለይ በትግሉ ዙሪያ የምንገኝ በሙሉ፤ ይህ ግዴታ፤ ከራሳችን አልፎ ሌሎችን በዚህ ለማጠቃለል ኃላፊነቱ አለብን። ለዚህ በጉዳዩ የጠለቀ እውቀት ያላቸውና አካባቢውን ጠንቅቀው የሚያውቁት ይምሩ።

ለ)       የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር በአሁኑ ሰዓት፤ ትግሬዎችና አማራዎች በቦታ ባለቤትነት ሳቢያ፤ በመካከላቸው የዕልቂት ጦርነት እንዲኖር እያራገበ ነው። አለመታደል ሆኖ መተላለቁ ተጀምሯል። የመለስ የኢንተራሐምዌ ምኞት የሚተገበርበት በር እየተከፈተ ነው። የርሱ ምኞት የራሱን ሥልጣን ለማራዘም ማማካኛ ነበር፤ ሀቅ ሲሆን ደግሞ የራሱን ደጋፊዎችና ወገኖች አደጋ ላይ ሊጥል ነው። እናም ይህ ሁላችንን ሊያሳስበን ይገባል። ክብደት እንሥጠው።

ሐ)      ዋናው መፍትሔ አንድ የትግል ማዕከል ባስቸኳይ መፍጠሩ ነው። በየቦታው የተኮለኮለው የየራስ ድርጅትና የየአካባቢ መሰባሰብ፤ ለኢትዮጵያ መጥፋት ምክንያት ይሆናል። በየድርጅቶቻቸው ተሸጉጠው እኔ እንዲህ፣ እነሱ እንዲያ የሚባለው ፉገራ ያቁም። ለነገዋ ኢትዮጵያ፤ ተወቃሹ የትግሬዎችን ነፃ አውጪ ግንባር ሳይሆን እኛው ራሳችን ነን። የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባርማ የኢትዮጵያ ጠላት ነው። ማን ለኢትዮጵያ አልተውቆረቆርክም ብሎ ያማዋል! ይህ ድርጅት እኮ፤ “እኛ” እና “እነሱ” በማለት፤ የኢትዮጵያን ህዝብ ጠላት ብሎ ፈርጆ፤ ኢትዮጵያን ለማጥፋት የቆመና የራሱን አዲስ ሀገር ለመመሥረት ካልሆነለት ደግሞ ትግራይን ገንጥሎ የራሱ ሀገር ለማድረግ ቆርጦ የተነሳ ጠላት ነው። እናም ሁሉን የየአካባቢ አጀንዳ ባንድነት ያቀፈ የትግል ማዕከል ባስቸኳይ ካልተፈጠረ፤ እንዲህ የባሳቸውንና በመኖርና በመጥፋት መካከል ያሉትን መቆጣጠር አይቻልም። ብሶታቸው ትክክል ነውና የሚወስዱትም እርምጃ ትክክለኛ ይሆናል። በሚያውቁትና በጃቸው ባለ እንጂ በምኞት በኛ አጀንዳ አይታገሉም።

መ)      በተጨማሪ ደግሞ፤ እስላሞች ለብቻቸው፣ በደቡብ የተፈናቀሉት ለብቻቸው፣ መምህራን ለብቻቸው፣ ነጋዴዎች ለብቻቸው፣ ቤት ያጡ ለብቻቸው እየተባለ የሚደረገው ተከላካይነት በተናጠል ለመመታት መዘጋጀት ነው። ለየብቻ እስከቆምን ድረስ ደግሞ፤ በያንዳንዱ ለየብቻ በቆመ ተከላካይ ስብስብ ውስጥ ያሉ ጠንካራ አባላት፤ ወደፊት በመግፋት ብቻቸውን ለማደጋቸው ጥርጣሬ ሊኖረን አይገባም። ደግሞም የቴክኖሎጅው አመቺነትና የወጣቶቻችን ቀልጣፋነት፤ ባጭር ጊዜ ውስጥ ለመሰብሰብና ለማደግ እንደሚያስችል የማይረዳ የለም። ስለዚህ ልንሰጋ ይገባናል። ስለዚህ፤ እያንዳንዳችን የያዝነውን አጀንዳ፤ ከዚህ ሀገራዊ ጉዳይ አንጻር ክብደትና ቅለቱን በማነጻጸር፤ ባስቸኳይ አንድ የትግል ማዕከል መፍጠር አለብን። ለዚህ መፈጠርና አለመፈጠር ተጠያቂዎቹ እኛውና እኛው ብቻ ነን።

የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር በጎንደር የሚያደርገው ተግባር፤ ኢትዮጵያን ለማጥፋት ከሚያደርገው ግስገሳ የተከተለ ነው።  በቀጥታ ሲታይ ለሙን መሬት በቋሚነት ለመውሰድ፤ ግጭቱን ምክንያት ለማድረግና ወታደሮቹን ለማስፈር ያቀደው ሲሆን፤ በተዘዋዋሪ መንገድ ደግሞ፤ ትግራይን ገንጥሎ ለመውሰድ ካለው ዕቅዱ አኳያ፤ የትግራይን የመሬት ይዘት ዓለም አቀፋዊ ድንበር ለማድረግ፤ የአካባቢውን ነዋሪ ለማጥፈት ያዘጋጀው ነው። ቁጭ ብለን ሞት እንዲወስደን እንጠብቅም ያሉት፤ ራሳቸውን መከላከል ጀምረዋል።

ይህ ጉዳይ፤ በሐረር፣ በአርሲ፣ በጉራፈርዳና በሌሎች አካባቢ በአማራው ወገናችን ላይ የደረሰው ቀጣይ እርምጃ ነው። ብዙዎቹ በደረሰባቸው ግፍ ምክንያት፤ ከፍተኛ የንብረትና የሕይወት መስዋዕትነትን እየከፈሉ ናቸው። ጀግንነቱ፣ ቆራጥነቱ፣ ለወገን ያላቸው ፍቅር የማያጠያይቀው የአካባቢው ተወላጆች፤ ዝም ብሎ ማየቱ በቅቷቸዋል። ሌሎች ኢትዮጵያዊ ወገናቸው፤ ጭንቀታችሁ ጭንቀታችን ነው፤ ቁስላችሁ ቁስላችን ነው፤ ብለው አብረዋቸው ካልቆሙ፤ ያናንተ ጉዳይ የኛም ጉዳይ ነው ብለው አብረው ካልተባበሩና የአካባቢው ተወላጆች ብቻውን ከቆሙ፤ የብቻቸውን አጀንዳና የብቻቸውን እርምጃ እንዲወስዱ መንገዱን እየቀደድንላቸው ነው። ይህ የኢትዮጵያ ሕዝብ ጉዳይ ነው። ለብቻቸው መቆም የለባቸውም ብሎ ከሩቅ መደንፋት ይቻላል። ይህ ግን አፍራሽ እንጂ ገንቢ አይደለም። ለብቻቸው እንዳይቆሙ አብሯቸው መሰለፍ ያስፈልጋል።

ለአካባቢው ተወላጆች፤

ላላችሁባቸውና ለምታምኑባቸው ድርጅቶች ንቁ ተሳታፊዎች በመሆን፤ የናንተ ጉዳይ የየድርጅቶቹ ጉዳይ እንዲሆን ጣሩ። በመሠረቱ ደግሞ በአንድነት ታግለን ይሄን የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር መንግሥት ማስወገድ ካልቻልን፤ ወዳልታወቀ የወደፊት እየተጓዝን ነው። እናም ትኩረታችን ይሄን መንግሥት ለማስወገድና በሂደቱ ጉዳያችን ቅድሚያ የሚሠጥበት እንዲሆን መጣር አለብን። አሁንም ዋናው መፍትሔ የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር መውደቅና የኢትዮጵያ ሕዝብ መንግሥት መቋቋም ስለሆነ፤ ይሄን መግፋት አለባችሁ። በሂደቱ ይህ የጎንደር ጉዳይ ሀገራዊ አጀንዳ ሆኖ እንዲቀርብ መጣር የሁላችን ኃላፊነት ነው። ይህ ኢትዮጵያዊነትን መቀበል ማለት ነው። ይህ ጉዳይ የኔ ብሎ መነሳት፤ ከፍተኛ ትኩረት ሊሠጠው ይገባል። eske.meche@yahoo.com

የምርጫ 2007 10ቱ ቃላት -ግርማ ሞገስ

$
0
0

ቅዳሜ ታህሳስ 25/2007 (January 3/2015)

Girma Moges

አቶ ግርማ ሞገስ

የዚህ ጽሑፍ ግብ በምርጫ 2007 ቁም ነገር መስራት የሚፈልግ የምርጫ ፓርቲ ማድረግ ከሚገቡት ሌሎች እጅግ በርካታ ዝግጅቶች በተጨማሪ ከግንዛቤ ሊያስገባቸው የሚገቡ 10 ነጥቦች መዘርዘር ነው። ምርጫው ነፃ እና ፍትሃዊ ካልሆነ ከምርጫ መወጣት (ቦይኮት ማድረግ) ጠቃሚ ነው ለሚሉ ወገኖችም መልስ ይሰጣል ይኽ ጽሑፍ። መልካም ንባብ።

 

  • መንግስት በስልጣን መኖር የሚችለው፥ (ሀ) ህጋዊነት የሚለግሰው ህዝብ ሲኖር፣ (ለ) ህዝብ የሙያ ትብብር ሲለግስ፣ (ሐ) ህዝብ የግብር ክፍያ ትብብር ሲያደርግ፣ (መ) የመንግስትን የአገር ተፈጥሮ ሃብት እና አገራዊ ኢኮኖሚ ባለቤትነት ህዝብ እሺ ሲል ብቻ ነው። እነዚህን የፖለቲካ ኃይል ምንጮች ህዝብ አሳልፎ ለገዢው ቡድን አሳልፎ የሰጠው በፍራቻ ወይንም በፈቃደኛነት ሊሆን ይችላል። ያም ሆነ ይህ የእነዚህ የፖለቲካ ኃይል ምንጮች ባለቤት ህዝብ ነው።፡ ስለዚህ ነው የመንግስት ስልጣን ምንጭ ህዝብ ነው የሚባለው። ህዝብ የመንግስት ስልጣን ባለቤት ነው የሚባለውም ስለዚህ ነው። ስለዚህ የመንግስት ስልጣን ባለቤት የሆነው ህዝብ የመንግስት ስልጣን ለመለገስ የተሳተፈባቸው ምርጫዎች ህገወጥ ሊሆኑ አይችሉም። ተቃዋሚ የምርጫ ፓርቲዎች የመንግስት ስልጣን ባለቤት ባለመሆናቸው እራሳቸውን ከምርጫው በማግለል ምርጫውን ህገወጥ አደረግን ማለት አይችሉም። ህዝብ እስከተሳተፈ ምርጫው ህጋዊ ነው። አብላጫ ድምጽ ያገኘውም ፓርቲ ህጋዊ አሸናፊ ፓርቲ ነው። የተባበሩት መንግስታትም ሆነ የምዕራቡ ዓለም መስፈርት የሚለው ይኽንኑ ነው። (ስድስቱ የፖለቲካ ኃይል ምንጮች ሰላማዊ ትግል 101 በሚል ስያሜ በቅርብ ገበያ ላይ በዋለችው መጽሐፍ ውስጥ በሰፊው ቀርቧል።)
  • በምርጫ በስልጣን ላይ ያለን መንግስት ህጋዊነት ማሳጣት የሚቻለው የመንግስት ስልጣን ባለቤት የሆነው ህዝብ እራሱን ከምርጫ ሲያገል ብቻ ነው። አንድ ህዝብ በምርጫ አልሳተፍም ካለ ምርጫ የለም። አሸናፊ ፓርቲ የሚባልም ነገር የለም። ስለዚህ ህዝብ ከሚሳተፍበት ምርጫ እራሳቸውን ብቻ በማግለል (ቦይኮት በማድረግ) ምርጫውን ወይንም አሸነፈ የሚባለውን ፓርቲ ህጋዊነት እናሳጣዋለን ብለው የሚያስቡ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ካሉ የአስተሳሰብ ዝንፈት ወይንም ጨቅላነት አለባቸው። ህዝብን ሊተኩ ወይንም እራሳቸውን ከህዝብ በላይ አድርገዋል ማለት ነው። አምባገነንነትም በልጅነቱ ይኽንኑ ነው የሚመስለው።
  • ዴሞክራሲ በሰረጸባቸው እንደ አሜሪካ እና እንግሊዝ አይነት አገሮች ውስጥ ምርጫ ህዝብ የመንግስት ስልጣን ባለቤት መሆኑ ማረጋገጫ መንገድ ነው። በእነዚህ አገሮች ምርጫ ቦርዱም ሆነ የህዝብ ታዛቢዎች (የምርጫ አስፈጻሚዎች) ገለለተኛ በመሆናቸው የመራጩ ህዝብ ድምጽ ይሰረቃል የሚል ስጋት የለም። የምርጫ ፓርቲዎች ድምጽ ለማስከበር በሚል የሚያደርጉት ስትራተጂያዊ ዝግጅት አይኖርም።
  • ዴሞክራሲ በሰረጸባቸው እንደ አሜሪካ እና እንግሊዝ አይነት አገሮች ውስጥ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ህዝባቸው እንዲመርጣቸው ስለሚጠይቁ ፓርቲዎቹ የመንግስት ስልጣን ባለቤት አለመሆናቸውንም ማረጋገጫ ነው ምርጫ። ህዝብ የመንግስት ስልጣን ባለቤት በመሆኑ ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ውስጥ የፈለገውን ይቀጥራል (ይመርጣል)። ያልፈለገውን አይመርጥም (አይቀጥርም)። በእነዚህ አገሮች ከሞላ ጎደል ነፃ እና ፍትሃዊ ምርጫ ይደረጋል። ስለዚህ በእነዚህ አገሮች ምርጫ የዴሞክራሲ መገለጫ ነው።
  • ዴሞክራስ ባልሰረጸባቸው እንደ ኢትዮጵያ አይነት አገሮች ውስጥ ምርጫ የህዝብን የመንግስት ስልጣን ባለቤትነት ማምጫ መንገድ ነው። በእነዚህ አገሮች ፥ (ሀ) ሶስቱ የመንግስት ዘርፎች የተነጣጠሉ ባለመሆናቸው፣ (ለ) የኢትዮጵያ ህገ መንግስት እንባ ጠባቂ ብሎ ያሚጠራው ተቋም ነፃ ባለመሆኑ፣ (ሐ) በዘልማድ አራተኛው የመንግስት ዘርፍ ተብሎ የሚጠራው ነፃ ፕሬስ እንደልቡ በነጻነት መንቀሳቀስ ባለመቻሉ፣ (መ) በመንግስት እና በፓርቲ መካከል ሊኖር የሚገባው ቀጭን ቀይ መስመር ባለመኖሩ፣ (ረ) ምርጫ ቦርዱም ሆነ የህዝብ ታዛቢዎች (የምርጫ አስፈጻሚዎች) ገለለተኛ ባለመሆናቸው ነፃ እና ፍትሃዊ ምርጫ የደረጋል ብሎ ማሰብ ላም ባልዋለበት ኩበት መልቀም ይቻላል ብሎ እንደማመን ነው። በእነዚ አገሮች ነፃ እና ፍትሃዊ ምርጫ ይደረግ የሚለው ጥያቄ የሚቀርበው እንደ መታገያ አሳብ መሆኑ ታውቆ የምርጫ ፓርቲዎች ከምርጫ ሳይወጡ ህዝባቸውን የመንግስት ስልጣን ባለቤት ለማድረግ ማለትም ወደ ዴሞክራሲ ለመሸጋገር የጀመሩትን ጉዙ መቀጠል አለባቸው። ስለዚህ ነው በእነዚህ አገሮች በሚደረግ ምርጫ የምርጫ ስትራተጂ ሲቀየት የህዝብ ድምጽ እንዳይሰረቅ ለማድረግ የሚያስችል ዝግጅት በስትራተጂ ውስጥ የሚካተተው።
  • ዴሞክራስ ባልሰረጸባቸው እንደ ኢትዮጵያ አይነት አገሮች ውስጥ በሚደረግ ምርጫ ነፃ እና ፍትሃዊ ምርጫ ካልተደረገ በሚል ምክንያት ከምርጫ መውጣት ለኢህአዴግ (ገዢው ፓርቲ) ጭንቀት መቀነስ ብቻ ሳይሆን ደስታን መለገስ ነው። ባቄላ አለቀ ቢባል ፈስ ቀለለ እንደሚባለው ነው የሚሆንለት ለኢህአዴግ (ገዢው ፓርቲ)። ምክንያቱም የመንግስት ስልጣን ባለቤት የሆነው የኢትዮጵያ ህዝብ በምርጫ እስከተሳተፈ ድረስ ምርጫው ህጋዊ ነው። ያሸነፈውም ፓርቲ ወዲያው አለም አቀፍ እውቅናን ያገኛል። የገንዘብ እና የቁሳቁስ እርዳታም ይቀጥላል። ይኼን ሃቅ ቀደም ብለው በኢትዮጵያ የተደረጉት አራት አገር አቀፍ ምርጫዎች አስተምረውናል።
  • ዴሞክራስ ባልሰረጸባቸው እንደ ኢትዮጵያ አይነት አገሮች ውስጥ በሚደረግ ምርጫ በመሳተፍ የህዝብን ድምጽ ማግኘት ግን ለኢህአዴግ (ገዢው ፓርቲ) መከራ እና ጭንቀትን ይፈጥራል። ይኽን ሃቅ በምርጫ 97 ያስተዋልነው ነው። ሽንፈትን አልቀበልም ካለ ድምጽ ይከበር የሚል እንቅስቃሴ ሊፈጠር ይችላል። ይኽንንም ሃቅ በምርጫ 97 አይተናል። አንዴ ህዝባዊ እንቅስቃሴ ከጀመረ ከዚያ ወዴት እንደሚሄድ መገመት አዳጋች ነው። ስለዚህ የምርጫ ፓርቲዎች ለዚህ አይነት አጋጣሚም ቀደም ብለው መዘጋጀት ይበጃቸዋል። አይመጣምን ትተሽ ይመጣልን ጠብቂ በሚለው መመራት ጠቃሚ ነው።
  • ዴሞክራሲ ባልሰረጸባቸው አገሮች ህዝብ ድምጽ የመሰረቅ እድሉ ከፍተኛ ነው። በሰላማዊ ትግል የህዝብ ነፃ አውጭ እራሱ ህዝቡ መሆኑ ታውቆ የምርጫ ፓርቲዎች እምነታቸው በውጭ አገር ድጋፍ ወይንም በምርጫ ቦርድ ሳይሆን በህዝብ ላይ መሆን አለበት። ስለዚህ የምርጫ ፓርቲዎች ህዝብ ድምጹን እንዳይሰረቅ ማድረግ እንዲችል ማሰልጠን እና ማደራጀት አለባቸው። የምርጫ ፓርቲዎች ማድረግ ከሚገቧቸው ስራዎች ውስጥ ጥቂቱ የሚከተሉትን ያካትታል፥ (ሀ) በህዝብ ታዛቢዎች ላይ ገለልተኛ እንዲሆኑ ጫና በማሳደረ፣ (ለ) ለምርጫ እድሜው የደረሰ በሙሉ ለምርጫ እንዲመዘገብ እና የምርጫ ካርድ እንዲወስድ በማድረግ፣ (ሐ) ህዝቡ የምርጫ ካርዱን የሚቀጥሉት አምስት አመቶች በአገሩ አቅጣጫ ላይ ውስኔ መስጫው መብቱ መተግበሪያ አድርጎ እንዲያምን በማድረግ፣ (መ) በምርጫ እለት የምርጫ ካርድ የወሰደ መራጭ በሙሉ በነቂስ ወጥቶ እንዲመርጥ በማሳመን፣ (ሠ) በምርጫው ዕለት በድስፕሊን የታነጹ እና በምርጫ ህግ የሰለጠኑ የእምነት ጽናት ያላቸው የእጩ ታዛቢዎች በየምርጫ ጣቢያው በማሰማራት ታህሳስ 12/2007 ተመረጡ የተባሉት የህዝብ ታዛቢዎች በእድሜ የገፋውን መራጭ ህዝብ ሳያደናግሩ የምርጫ ካርዶችን እና የምርጫ ኮሮጆዎችን በገለልተኛነት እንዲያስተናግዱ በመከታተል፣ (ረ) እጩዎች ህዝቡ እንዲመርጣቸው የሚያደርጉ መልዕክቶች፣ የትምህርት ደረጃ፣ ማራኪ ባህሪ፣ ተወዳጅነትም እንዲኖራቸው በማድረ (ማሰልጠን ይቻላል)፣ (ሰ) ገዢው ፓርቲ ከሽንፈት ማምለጫ መከራከሪያ እንዳይኖረው እና ሽንፈትን ሳያንገራግር እንዲቀበል ለማድረግ ይቻል ዘንድ በሚሸነፍባቸው የምርጫ ጣቢያዎች እና የምርጫ ክልል ወረዳዎች ሽንፈቱ በከፍተኛ ድምጽ (landslide) እንዲሆን ማድረግ (ሸ) የምርጫ ጣቢያዎች ሲዘጉ ድምጽ ተቆጥሮ አሸናፊ እስኪታወቅ መራጩ ህዝብ ከየምርጫ ጣቢያዎች ርቆ እንዳይሄድ ማድረግ። የህዝብ ድምጽ ከተሰረቀ መራጩ ህዝብ ድምጼን ካላከበርክ እኔም የአንተን ገዢነት አላከብርም የሚል እንቅስቃሴ ሊጀምር ይችላል። ስለዚህ በእነዚህ አገሮች የሚደረግ ምርጫ በአግባቡ ከተያዘ እና ከተመራ የህዝብን የመንግስት ስልጣን ባለቤትነት ማምጫ መንገድ ነው። ዴሞክራሲን ማምጫ ነው።
  • ዴሞክራስ ባልሰረጸባቸው እንደ ኢትዮጵያ አይነት አገሮች ውስጥ የሚደረግ ጠብመንጃ-መር ትግል (ለምሳሌ፥ ትጥቅ ትግል፣ የከተማ ግድያ፣ ሽብር፣ በፕላን ያልተመራ ሰላማዊ አመጽ፣ ወ.ዘ.ተ. ) አምባገነን ማምጫ ነው።
  • ዴሞክራስ ባልሰረጸባቸው እንደ ኢትዮጵያ አይነት አገሮች ውስጥ በሚደረግ ምርጫ የምርጫ ፓርቲዎች በተካሄደው ምርጫ የተገኙ ፖለቲካዊ እና ድርጅታዊ ድሎችን መልቀም የሚያስችሉ ዝግጅቶች ቀደም ብለው ማድረግ አለባቸው። ይኽን ለማድረግ በቅድመ-ምርጫ ዝግጅት፣ በምርጫ እለት እና ከምርጫ ማግስት ሊፈጠሩ የሚችሉ ሁኔታዎችን (Scenarios) ቀደም ብለው መተንተን እና ቀዳዳዎችን መድፈን የሚያስችሉዋቸው ዝግጅቶች ማድረግ አለባቸው። በምርጫ 2007 የተገኙ ድሎች እንደ ምርጫ 1997 መባከን የለባቸውም። ገዢውን ፓርቲ ሊያስበረግጉ እና ሊያስቆጡ ከሚችሉ ድንፋታዎች፣ ዛቻዎች፣ ፉከራዎች፣ ትንኮሳዎች፣ መፈጸም የለባቸውም ተቃዋሚ የምርጫ ፓርቲዎች። ገዢው ፓርቲ ሽንፈት በደረሱበት አካባቢዎች ሽንፈትን የጀግኖች ሽንፈት አድርጎ መቀበል የተሻለ አማራጭ አድርጎ እንዲዎስድ ማበረታታት ያስፈልጋል።

 

 

ከሰላምታ ጋር

ግርማ ሞገስ

 

Viewing all 8745 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>