Quantcast
Channel: ዘ-ሐበሻ – Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 8745 articles
Browse latest View live

አዲስ ጉዳይ ተሰደደች ”ምርጫ መጣ ፕሬስ ውጣ”

$
0
0

10570542_10204024912521089_4618968976545930065_nበአዲሳባ እና በመላው ሀገሪቱ ከፍተኛ ተነባቢነት ካላቸው መጽሄቶች ተርታ የምትመደበው አዲስ ጉዳይ አዘጋጆች መሰደዳቸው ተሰማ። መንግስት አዲስ ጉዳይን ጨምሮ በበርካታ ጋዜጦች እና መጽሄቶች ላይ ክስ ሊመሰርት መሆኑ በተሰማ ማግስት ”ምርጫ መጣ ፕሬስ ውጣ” የሚል ጽሁፍ ያስነበበችን አዲስ ነገር ከመታሰር አለመታስር ይሻላል ብላ መሰደድን መርጣለች።

ደረጄ ሀብተወልድ እንደነገረን የመጽሔቱዋን ባለቤት እንዳልካቸው ተስፋዬን ጨምሮ የመጽሔቱዋ ምክትል ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ኢብራሂም ሻፊ፣ ከፍተኛ አጋዘጅ ጋዜጠኛ እንዳለ ተሽ እና አዘጋጅና አምደኛ ሀብታሙ ስዩም በፕሬሶች ላይ እየተንደረደረ በመምጣት ላይ የሚገኘውን የክስ ናዳ ”ሽል” ብለው አምልጠውታል።

10155812_762741180411560_2062798175_n-150x150በቅርቡም የሰንደቅ ጋዜጣ ከፍተኛ አዘጋጅ የነበረው ዘሪሁን ሙሉጌታ እየደረሰብት ያለውን የደህነነቶች ጭቅጭቅ እና ንትርክ እንዲሁም የእስር እና እንግልት ስጋት ሽሽት ሀገሩን ለአስር አለቆች ትቶ መውጣቱን አለመዘገባችን ይታወቃል። (በቀንፍም እንዲህ እያደራጁ መዘገብ ሳይሻል አይቀርም ብለን በማይቀለደው እንቀልዳለን)

ሰዎቹ ሁሉን አባረው ሲያበቁ የእስር ሱሳቸውን ርስ በርስ በመተሳሰር ይወጡት እንደሁ እናያለን እንግዲህ!


የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ብሔራዊ ምክር ቤት ሁለት ውሳኔዎችን አስተላለፈ

$
0
0

10606470_681304371954500_7184262179990938183_nየአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ብ/ም/ቤት ነሐሴ 04 ቀን 2006 ዓ.ም የጠራው አስቸኳይ ስብሰባ ሁለት ውሳኔዎችን በማስተላለፍ ስብሰባውን በተሳካ ሁኔታ አካሂዷል፡፡
በዚህም መሰረት ጠዋት የተደረገውን ስብሰባ የመሩት አቶ አበበ አካሉ የም/ቤቱ አፈ ጉባኤ ሲሆኑ፣ ምክር ቤቱ የተወያየበት አጀንዳ የመኢአድና የአንድነት የውህደት ሂደትና የተደረሰበትን ውጤት መርምሮ አቅጣጫ ማስያዝ ሲሆን በተደረገውም ሰፊና ጥልቅ ውይይት
- የምርጫ ቦርድ ለመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) በደንቡና በአዋጁ መሰረት እንዲያሟላቸው የጠየቃቸውን ጉዳዮች እስኪያሟላ ድረስ በአንድነት ፓርቲ ደንብና መመሪያ መሰረት ውህደትን በሚመለከትና አዘጋጅ ኮሚቴ መወከል የብሔራዊ ም/ቤት ሥልጣን በመሆኑ ም/ቤቱ የወከለው የጠቅላላ ጉባኤ አዘጋጅ ኮሚቴ ለጊዜው ስራውን እንዲያቆም ውሳኔ በማስተላለፍ ከመኢአድ ጋር የሚደረገው ውህደት በማንኛውም ጊዜ እንደሚቀጥል አስገንዝበዋል፡፡
- በመቀጠልም የአንድነት ፓርቲ መዋቅራዊ አካላት የሥራ እንቅስቃሴ ወደ ነበረበት እንዲመለስና ከብሔራዊ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ጀምሮ እስከ ዝቅተኛው መዋቅር ድረስ የወጡትን የሥራ ዕቅዶች እንዲያከናውኑ ም/ቤቱ መመሪያ ሰጥቷል፡፡
የከሰዓት በኋላ የም/ቤቱን ውሎ የመሩት የም/ቤቱ ም/አፈ ጉባኤ አቶ ደምሴ መንግሥቱ ሲሆኑ የውይይቱ አጀንዳም የፓርቲው የመገናኛ ብዙኃን እንዲመራ ኃላፊነት የተጣለበት ኤዲቶሪያል ቦርድን በተመለከተ ነበር፡፡
- ም/ቤቱ በተደረገው ውይይት ቀደም ሲል የተቋቋመው ቦርድ በአጠቃላይ የፈጸማቸውን የሥራ ክንውን፣ ጠንካራና ደካማ ጎኖች በተመለከተ ሪፖርት እንዲያዘጋጅና በሚቀርበው ሪፖርት መሰረት ተወያይቶ በአዲስ መልክ የኤዲቶሪያል ቦርድ አባላትን ለማቋቋም ለነሐሴ 18 ቀን 2006 ዓ.ም ቀጠሮ በመያዝ ስብሰባው ተጠናቋል ሲሉ አቶ ደምሴ መንግስቱ የብ/ም/ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ለፍኖተ ነፃነት ገልፀዋል፡፡

Millions of voices for freedom – UDJ

ኢንጂነር ግዛቸው የመኢአድ/አንድነት ዉህደት አመቻች ኮሚቴን አፈረሱ

$
0
0

10590397_1465508690367579_46579675110189955_n

ኢንጂነግር ግዛቸው በሕዝብ ዘንድ በጉጉት የሚጠበቀዉን፣ ለአገዛዙ ራስ ምታት የሆነው፣ የመኢአድ እና አንድነት ዉህደት አመቻች ኮሚቴን አፈረሱ። በአባላትና ደጋፊዎች ዘንድም ትልቅ ድንጋጤ ተፈጥሩዋል። በአገዛዙም ዘንድ ደስታው ጨምሩዋል።

– በዉጭ አገር ያሉ የአንድነት ደጋፊዎች በኢንጂነር ገዛቸው ላይ ከፍተኛ ተቃዉሞ እያሰሙ ናቸው።

የመኢአድ የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊ ፣ አቶ ተስፋሁን አለምነህ፣ ለሕብር ራዲዮ ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ፣ የአንድነት እና መኢአድ ዉህደት የሕዝብ ጥያቄ እንደሆነ ገልጾ፣ ገዢው ፓርቲ ምርጫ ቦርድን ተጠቅሞ የሚያስቀምጣቸው መሰናክሎችን አጥብቀው እንደሚያወግዙ ገልጸዋል። ድርጅታቸው አቶ አበባው መሐሪን ጠቅላላ ጉባኤ ጠርቶ ሲመርጥ፣ የምርጫ ቢርድ ሃላፊዎች በተገኙበት የተደረገ እንደሆነ የገለጹት አቶ ተስፋሁን፣ አገዛዙ ዉህድቱ እንዳይሳካና ተቃዋሚዎች ተከፋፍለው እንደለመደው የ2007 ምርጫን አጭበርብሮ ለማሸነፍ ሲል፣ ሆን ብሎ እያደርገ ነው ሲሉም ከሰዋል።


መኢአድ ሰላማዊ ሰልፎችን፣ የሥራና የትምህርት ማቆም አድማዎችን እንደሚጠራ የገለጹት ቶ ተስፋሁን፣ ትግሉ የሚጠይቀው ማናቸዉን መስወአትነት ለመክፈል አመራሩ እንደተዘጋጀም አስረድተዋል።
የመኢአድ እና የምርጫ ቦርድ ፍጥጫ በዚህ ሁኔታ እንዳለ ፣ ከመኢአድ ጎን በመቆም አጋርነት ይገልጻሉ፣ ምርጫ ቦርድ ላይ በጋራ ጫና ለማድረግ ድርጅታቸው ያሰልፋሉ ተብለው የሚጠበቁት፣ ኢንጂነር ግዛቸው፣ ከአንድ ሳምንት በፊት አገር ዉስጥ ላሉ ጋዜጦች የሰጡትን አስተያየት በመቀልበስ፣ የዉህደት አመቻች ኮሚቴዉን ያፈረሱ ሲሆን፣ ለውህደት በሚደረገዉ ከፍተኛ ትንቅን ላይ ቀዝቃዛ ዉሃ ከልብሰዉበታል።


«ኢንጂነር ግዛቸው በአሁኑ ወቅት ከመኢአድ ጋር በመሆን፣ በጋር የሚሊዮኖች ንቅናቄን በማጡዋጣፍ ፣ ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎችን በማድረግ፣ በምርጫ ቦርድና አገዛዙ ላይ ጫና ማሳደር ሲገባቸው፣ የዉህደት አመቻች ኮሚቴውን ማፍረሳቸው ሰላማዊ ታጋዮች አንገት የሚያስደፋ ነው» ያሉት በጉዳዩ ላይ ያነጋገርናቸው የፖለቲካ ተንታኝ የኢንጂነሩን ዉሳኔ የሚረዳዉና የሚጠቅመው አገዛዙን ብቻ እንደሆነም ይናገራሉ።
ከኢንጂነር ገዛቸው አመራር ጋር በተገናኝም በዉጭ አገር የሚኖሩ የአንድነት ደጋፊዎች በኢንጂነር ግዛቸው አመራር ላይ ያላቸውም ከፍተኛ ተቃዉሞ እየገለጹ መሆናቸውን ለመረዳት ችለናል።

Source abugidainfo.com

6 የአንድነት ከፍተኛ አመራሮች ከኢንጂነር ግዛቸው ካቤኔ ራሳቸውን አገለሉ

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) ኢንጂነር ግዛቸው በሕዝብ ዘንድ ከፍተኛ ተስፋ የተጣለበትን የአንድነት እና የመኢአድን ፓርቲዎች ውህደት አመቻች ኮሚቴ ካፈረሱና በርካታ ሕዝብን አሳዝነዋል ከተባለ ወዲህ የርሳቸው ካቢኔ ሆነው በአንድነት ውስጥ እያገለገሉ ከሚገኙት ውስጥ 5ቱ ራሳቸውን ማግለላቸውን ለዘ-ሐበሻ የደረሰው ዜና አመለከተ።
GizachewShiferaw
ራሳቸውን ከኢንጂነር ግዛቸው ካቤኔ ያገለሉትና ለኢንጂነሩም ደብዳቤ ያስገቡት የአንድነት ከፍተኛ አመራር አባላት

  1. ተክሌ በቀለ –ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዘዳንት
  2. በላይ ፈቃዱ —ምክትል ፕሬዘዳንት
  3. ሰለሞን ስዮም —የፖለቲካ ጉዳዮች ሃላፊ
  4. ዳንኤል ተፈራ — የድርጅት ጉዳይ ሃላፊ
  5. ዳዊት አስራደ —የኢኮኖሚ ጉዳዮች ሀላፊ
  6. ፀጋየ አላምረው –የገንዘብ ክፍል ሃላፊ              መሆናቸው ታውቋል።

ከመኢአድ ጋር የሚደረገውን ውህደት እንዲኮላሽ አድርገዋል እየተባሉ የሚተቹት ኢንጂነር ግዛቸው በአስቸኳይ ስልጣናቸውን እንዲለቁ ግፊቱ የጨመረ መሆኑን ያስታወቁት የመረጃ ምንጮቻችን፤ አስተያየት ሰጪዎች በተለይ በሪፖርተር ጋዜጣ ላይ ጃንዋሪ 12 ቀን 2014 የሰጡት ቃለምልልስ ላይ ያሉትን በመጥቀስ “ይህን ካደረግኩ በኋላ ከኢሕአዴግ ጋር ገንቢ ግንኙነት (Constructive Engagement) እንዲኖረን እፈልጋለሁ፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ የጥላቻ ፖለቲካ ማብቃት አለበት፡፡ ኢሕአዴግ ተቃዋሚዎችን የሚያያቸው እንደ ጠላት ከዚያም አልፎ እንደ ሽብርተኛ ነው፡፡ ይኼንን ነገር ለሚያስብ ሰው እኮ በጣም ነው የሚያስደነግጠው፡፡ በእኛም በኩል ኢሕአዴግን የምናየው እንደ አውሬ ነው፡፡ ምናልባት የሠራውን ሥራ ሁሉ ዋጋ (Credit) ያለመስጠት አለ፡፡ አንዳንድ ጊዜ ፖለቲካችን ኢሕአዴግን መቃወም ብቻ ሆኖአል፡፡ ያ መቆም አለበት፡፡ ትልቁ ኳስ ያለው ኢሕአዴግ ዘንድ ነው፡፡ እኔ በበኩሌ ወደፊት በማደርገው እንቅስቃሴ ገንቢ ግንኙነት አድርገን ያለውን የፖለቲካ ምኅዳር ለሁላችንም እኩል ማድረግ አለበት፡፡” የሰውዬው አካሄድ ወዴት ነው እያሉ እንደሚነጋገሩበት አስታውቀዋል።

በትግራይ ክልል አራት መቶ ሺ ህዝብና በሚሊየን የሚቆጠሩ የቤት እንስሳትን የሚቀልብ በለስ ወደመ

$
0
0

ዜና ትንታኔ በአስገደ ገ/ስላሴ ወ/ሚካኤል

ከመቐለ

አቶ አስገደ ገ/ስላሴ

አቶ አስገደ ገ/ስላሴ

በትግራይ ክልል በምስራቃዊ ሰሜን፣በደቡባዊ ምስራቅ በደቡብ ዞኖች የሚኖሩ ከ 1.5 ሚሊየን የሚቀጠሩ እንስሳ ዘቤት የሚቀልብ በለስ የሚባል እፅዋት የህዋሃት መሪዎችና እነሱ የሰርዋቸዉ ደንቆሮ የሳይንስ ተመራማሪ ተብዬዎቹ ሃርና ቀለም ከበለስ አፍርተን ትግራይን ሃብታም እናደርጋታለን በሚል ጥናት የጎደለዉ አውዳሚ ባክቴርያ (ቫይረስ) ሊሆን ይችላል አስገብተዉ በበለስ እፅዋት በማራባታቸዉ ያ የተራባዉ ባክቴርያ ሃር ሳይሆን አመረተዉ ለዚሁ ለተጠቀሰዉ ህዝብ ከ 6ት ወር በላይ 95% የምግብ ፍጆታዉን ይሸፍናል። ሁሉም እንስሳ ዘቤትም አመት ሙሉ ከመመገባቸዉ ህዝሠቡ ለራሱ ለምግብነት ከመጠቀሙ አልፎ ለገበያ እየወረደ በመላዉ የኢትዮጵያ ክልሎች በማሰራጨትበመሸጥ ብዙ ብር ያፍስ ነበር። የነዚህ አካባቢ ህዝብ ከሚያዚያ ወር ግማሽ እስከ ጥቅምት ወር ከላይ እንደጠቀስኩት በሚመገቡት በለስ ነበር።

ስለ በለስ ጥቅም የትግራይ ክልል መሪዎች የነሱ ስሪት ምሁሮች የነሱ ተላላኪዎች የመቐለ ዩኒቨርሲቲ በለስ ተመራማሪዎች ምንም መነሻ የሚሆን የሳይንስ ግኝት በተጨባጭነት የሌላቸዉ ከበለስ ይህን የሚያክል ቶንክ ሃር ቀለም ማርማላት በማምረት በመቶ ሽዎች ለሚቆጠሩ ዜጎች ስራ እንፈጥራለን እያሉከ 13 አመት በላይ በነዛ የፈለጉት ውሸትና ማደናገሪያ ዲስኩራቸዉን የሚያሰራጩባቸዉ ሚድያዎች አድርገዉ ለትግራይ ህዝብ የህልም እንጀራ ያበሉት ነበር።ሌላ ቀርቶ የበለስ ግንድ በመቁረጥ ለምግብነት ለመጠጥ ፣ ለማርማላት ይጠቅማል ተብሎ ለሁሉም ፕሮጀክቶች የሚያስተባብሩ ቢሮ ተመስርቶ ከእርዳታ ሰጪ አገሮች ብዙ ውሸት የውሸት ፕሮጀክቶች እያዘጋጁ እርዳታም ያገኙ ነበር። ውጭ አገር እየሄዱም ስለ በለስ ምርምር ለልመና እንዲመቻቸዉ ብዙ የሃገራችን የውጭ ምንዛሪ በልተውታል ሰብስበውታል የየግላቸዉ ህንፃ ሰርተዋል።

ይህ ሁሉ የደንቆሮ ምርምር አሁን ተጋለጠ

የህወሃት ግብታዊ የሆነ የሳይንስ ግኝት ያሃርና ቀለም ያመርታል ብለዉ ያመጡት ክንችያ የተባለዉ ባክቴርያ በመቶ ሺ አመት የሚቆጠር ህዝቦች ከአመት የምግብ ፍጆታ ከ 60% የሚጠቀሙበት በባክቴርያ ወድሟል እየወደመም ይገኛል። ለዚሁ ለማስረጃነት በትግራይ ክልል ደቡባዊ ምስራቅ በደቡብ በተለይ በራያ መኾኒ ወረዳ በሕንጣሎ በአላጀ እንዲሁም በከፊል እንደርታ ወረዳ አፅቢ ወንበርታ ወረዳዎች ስፋቱ 300 ኪሎ ሜትር ቁመቱ 300 ኪሎ ሜትር ስፋት ( 36000 ስኴር ኪሎ ሜትር መሬት የበቀለ በለስ ሙሉ በሙሉ ወድሟል። ይህ እፅዋት ሞቶ እንደተጣለ እንስሳ በለስም ወደመ።በነዚህ አካባቢ የሚኖሩ ዜጎች ተርበዋል እንስሶችም የሚበሉት አጥተዉ እየሞቱ ይገኛሉ።ለህዝብ የሚበላ ለእንስሳ መኖ የሚሰጥ ወገን የሚሰማቸዉ መሪዎች የሉም። በተለይ ደግሞ ትልቅ አደጋ ደርሶባቸዉ በሞዴልነት ለመጥቀስ በድሮ የዋጅራት ወረዳ ደቡብ 76000 ዜጎች ለመጥቀስ በራያም እንደዚሁ መኾኒ ወረዳና አካባቢዋ ከ 80000 ህዝብ በላይ ረሃብ ላይ ወድቀዋል እንስሳት እየሞቱ ናቸዉ።

የትግራይ ክልል ባለስልጣናት ተመራማሪ ሳይንቲስቶች በህዝባችንና በንብረቱደርሶ ላለዉ የምርምራቸዉ ውድቀት አሳፍሯቸዉ ለሁኔታዉ ተቆርቋሪ ሆነዉ ከመቅረብ ዝምታን መርጠዉ ድምፃቸውን ደብቀዉ ይገኛሉ ።ህዝቡ ግን በተለይ የሕንጣሎ ዋጅራት የመኾኒ ወገኖች እስከ የክልሉ ፕሬዚደንት ኣባይ ወልዱና ኪሮስ ቢተዉ ኣቤት ቢሉም ሰሚ ጆሮ አላገኙም።

የዋጅራት ህዝብ በበለስ መውደም ብቻ አይደለም የከሰረዉ ሰፊ የእርሻዉ ማሳዉ መቐለ ለሚገኘዉ ስሚንቶ ፋብሪካ የሚጠቅም አፈር ስላለዉ ኢፈርት ምንም ግምት ሳይሰጥ መሬቱን ቀምቶት ይግኛል። ከዚህ አፈር የተወሰነ ኮሚሽን እንኳ ቢከፈለዉ ለ 76000 የዋጅራት ህዝብ ይቀበለዉ ነበር ኢፈርት ግን አንድ 2ጃ ደረጃ ት/ቤት ሰርተንላችሁ በማለት እያተላሉዋቸዉ ይገኛሉ። እነዚህ ዜጎች የይገባኛል ጥያቄ ሲያነሱም ብዙ ሰዎች በማሰር ሽብር ፈጥራቹሃል ተብለዉ በእስር ተሰቃይተዋል ለአፍ ጉርስ በማጣ ታቸዉ አዛውንት ሴቶች ህፃናት ለስደት ሲፈልሱ ወጣቶች ወ ደ አረብ አገር ተሰደዉ ሲሰቃዩ ለነዚህ ወገኖች እንደ ማዘን ፈንታ በነዛ እኛ ባልናቸሁ ተንፍሱ ተብለዉ የሚታዘዙ የመንግስትና የፓርቲ ሬድዮ ጣቢያዎች ከኤፍኤም ቴሌቪዢን አድርገዉ እነዚህ ለልመና ለስደት የሚፈልሱ ሰዎች ባቋራጭ ለማደግ የሚፈልጉ ተብለዉ ሰብኣዊ መብታቸዉ ተነክተዋል። በተለይ ደግሞ ሰሓረቲ ሳምረ ወረዳ ነዋሪ የሆኑ ወገኖች እጅጉን ሃብታሞች ነበሩይሁን እንጂ በ 17 አመቱ የትጥቅ ትግል ጊዜ ልጆቻቸዉ ወደ ትግል አክትተዉ የተሰዉባቸዉ ቤታቸዉ ተቃጥሎባቸዉ ሃብታቸዉ በደርግ ተወርሶ የቀረረዉ ሃብታቸዉ ለህዋሃት አስረክበዋል። ብዛት ያላቸዉ ወገኖችም ለህወሃት አመራርና ካድሬዎች ጥያቄ አንስተዉ በመቃወማቸዉ ብዙ ታስረዋል ከባድ ቅጣት ተቀጥተዋል ተሰቃይተዋል ባሁኑ ጊዜ ….. እነዚህ ከጥንት ጀምረዉ እምቢ ለጭቆና አንገዛምብለዉ ያምፁ የነበሩ በመሆናቸዉ ይህ መንግስት የነዚህ ወገኖች ጥንካሬ አይፈልግም ያሰጉታና።
mekelle university
አሁን እነዚህ የበለስ አብቃዮችና ተጠቃሚ ወገኖች የነዛ በለሳቸዉ የወደመባቸዉ ዜጎች በመመልከታቸዉ እያነሱት ያለዉ ጥያቄ የህወሃት ስሪት የዩኒቨርሲቲ ምሁራን እርሻና የተፈጥሮ ሃብት ባለሞያዎች ያላነነሱት ጥያቄ ከቺንያ የሚባል ባክቴርያ ወይም (ቫይረስ) 1ኛ ወደ ሁሉ የበለስ አብቃይ ከባቢዎችከተዘመተ የወደፊት እጣ ፈንታችን ምን ይሆን? 2ኛ ወደ ሌላ እፅዋትና የእርሻ ሰብል ክዘመተ እቺ ኣገር ምድረ በዳ ትሆናለች 3 ይህ በሽታ ሂወት ያለዉ እፅዋት አውዳሚ ከሆነ ከሆነ ሰውና እንስሳም ሂወት ያላቸዉ በመሆናቸዉ ለዜጎች ያለዉ ጠንቅነት ምን ሊሆን ይችላል ። ምክንያቱም ባክቴርያዉ በንፋስ ሃይል እየተዘመተ ስላለ አንድ እርምጃ መውሰድ አለበት ይላሉ። የትግራይ የበለስ ተጠቃሚ ወገኖች 4 ይህ እፅዋት አውዳሚ ኤድስ ወደ አገራችን ያስገቡ የህወሃት ባለስልጣናትና ምሁራን ወደ ፍርድ ይቅረቡልን እያሉም ይገኛሉ 5 የዋጀራት ብቻ የወደመው በለስ በመንግስት ትግራይ የተጠናው በኣንድ አመት 750 ሚሊየን ብር የሚገመት ኪሳራ አጋጥሟል የአላጀ፣ የእንደርታ ራያ ዓዲቐይሕ መኾኒ ቤት ማራ የወደመዉ በለስ ሲገመት በቢሊየን የሚቆጠር ብር ነዉ ይህ የእንስሳትና የሰዉ ሞት ሳይጨምር ነዉ።

6 ይህ በሽታ መንግስት ክልል ትግራይ ስላመጣዉ እሱ ወደ ፍርድ ቤት ቀርቦ የፌደራል መንግስት ይድረስልን እያለ ነዉግን ማን ሰማውና?

7 የሃገራችን ህዝቦች ለምን ችግራችንተረድቶ ችግራችን እንዲፈታለን ለመንግስት ተፅኖ አያሳድርም ?አሁንም ይድረስልን እያለ ነዉ

8 የሃገራችን ብቁ ምሁሮች ተመራማሪዎች በነዚህ የህወሃት ስሪት የልማት ሰራዊት ተብዬዎች የደረሰብን ኣደጋ ተረድታችሁ ዝምታን መምረጣችሁ ስህተት ነዉ ይላል የዋጅራት ህዝብ

9 የሃገራችን ተቃዋሚ ፓርቲዎች ለዜጎችህ ፍትህ ነፃነት የመኖር ፣ የመስራት መበት ለማረጋገጥ እንታገላለን እያላችሁ ከ 400ሺ ህዝብ በላይ በከችንያ ኤድስ ህዝብ ቀለብ ሲወድም ዝምታ መምረጣችሁታዲያ ለማን ነዉ የምትታገሉት ብሎ ይወቅሳል

ከላይ የተዘረዘሩት የህዝብ ጥያቄዎች በኔ እምነት ትክክል ናቸዉ እላለሁ። እኔም ባክቴርያዉ ያለ ጥናት ያስገቡ የመቐለ ዩኒቨርሲቲ የሳይንስ ተመራማሪዎች የትግራይ ክልል ባለስልጣናት በሙሉ የኪቺኒያ ቫይረስ ሲገባ ትግራይ የሃር ክምር በማምረት በቢሊየን የሚቆጠር ዶላር ገቢ ያገኛል ብለዉ የዋሹ የመንግስትና የፓርቲ ሚዲያዎች ወደ ፍርድ ቤትይቅረቡ የወደመዉ በለስ ካሳ ለህዝቡ ይሰጥ ለዘላቂ ጊዜም መቋቋሚያ ይሰጣቸዉ። የቀረዉ በለስ እንዳይወድም በምን እንከላከለዉ ምን እርምጃ ይወሰድ መልስ ማግኘት አለበት።ለወደመውስ እንዴት ወደ ነበረበት ይመለስ የሚል መልስ ማግኘት አለበት። ሃይለማርያም ደሳለኝም ከአንድ ሚሊየን ህዝብ በላይ አሸብሮ ላለዉ የኪንችያ ቫይረስ እንደ ማሸበር ለሰላም ለሚታገሉ ተቃዋሚ ፓርቲ አመራር አባላት እያሸበሩና እያሰሩ ይግኛሉ። በመሆኑ ለኪንቺያ ባክቴርያ አለመጋለጣቸዉ ሃይለማርያም ደሳለኝና አለቆቻቸዉም በደረጃቸዉ መፈረድ አለባቸዉ የህግ የበላይነት አለ ከተባለ የሃገራችን የህዝብ ተወካዮች ፓርላማም ይህ አደጋ እያወቀ ዝምታ መምረጡ እጅጉን ሃላፊነት የጎደለዉ ከመሆኑም በተለይ ከሕንጣሎ ዋጅራት ከአላጀ ከመኾኒ ከእንደርታ ከአፅቢ ወንበርታ ወረዳዎች የተወከሉ የፓርላማ አባላት በወከላቸዉ ህዝብ ደርሶ ያለዉ አደጋ አለማጋለጣቸዉና መፍትሄ ለማግኘት አለመጣራቸዉ ለህዝብ ሳይሆን ውክልናቸዉ ለሆዳቸዉ መሆኑ ውክልናቸዉ ያሳያል። በነገብሩ በቀድሞ የትግራይ ክልል መሪዎች ጊዜ የበለስ አትክልት እንደ የድህነት ማጥፊያ ተቆጥሮ በትግራይ ክልል እንዲስፋፋ ይተከል የነበረዉ ከትግራይ አልፈሎ ወደ መላዉ የሃገራችን ክልሎችም እየተቆረጠ ይሄድ የነበረዉ አሁን እንደዚህ ሆኖ የወደመ ዝም ብለዉ ለሚመለከቱ ባለስልጣናት ሃይለማርያም ደሳለኝ እርምጃ እንዲወስድ ካላደረጉ ራሳቸውም ተባባሪ የበለስ አሸባሪ ሆነዋልማለት ነዉ።

የድረሱልኝ ጥሪ

በሃገራችን የሳይንስ ተመራማሪዎች ይህ የበለስ ቫይረስ በበለስ ላይ እያደረሰ ያለዉ ውድመት በሌሎች እፅዋት እንስሳ ሰዉ አደጋ እንዳይደርስ ከአለም አቀፍ የሳይንስ ምርምር በመተግበር ድርሻችሁንብትወጡ ጥርዬን አቀርባለሁ ይህ በሽታ ነገ ሃገራዊ ሊሆን ይችላል።

በትግራይ ክልል በሰሜን ምእራብ ዞን በታሕታይ ቀራሮ በፃዕዳ የእምባ ቀበሌ ( በቖላቑል) የጀመረዉ መድሃኒት ያልተገኘለት ሰዉ ጨራሽ በሽታ አሁን በወልቃይት በፀለምቲ ባድመ አድያቦ አድዋ ተምቤን ነጋሽ አንዲሁም ወደ አገውና መተማ የተስፋፋዉ ይህ ኪንቺያ የሚባል የበለስ ባክቴርያ ተስፋፍቶ ተፈጥሮ እንዳይጨርስ አሁንም የሳይንስ ምሁራን የዜግነት ግዳጃችሁን ብታውቁ።

በውጭ አገር የምትገኙ ኢትዮጵያወያን ሁሉ በምስራቅ ፣ በደቡብምስራቅ በደቡብ ትግራይ ዞኖች ተፈሮ ያለዉ በበለስ እፅዋት ቫይረስ የአለም የሳይንስ ምሁራን ይምርምር እርዳታዎን እንዲለግሱ ታደርጉ ዘንድ ጥሪዬን አቀርባለሁ::

የሃገራችን የሃይማኖት መሪዎች የእድሜ ባለፀጎች የተቀዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች ምሁራን ተማረሚዎች ወጣቶች ማህበራት ይህ አደጋ ለመከላከል የአቅማችሁን በመስራት ለመንግስት ተፅእኖ በማድረግ የተለመደዉ ልግስናችሁን ትችሩ ዘንድ ጥርዬን አቀርባለሁ።

ባገር ውስጥና በውጭ የምትገኙ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች ለዚህ በበለስ እፅዋትና የበለስ ተጠቃሚዎች የሆኑ ዜጎች የመኖር መብት የመኖር አቤት በቦታዉ መጥታችሁ ምስክርነታችሁን ትሰጡ ዘንድ ጥሪዬን አቀር ባለሁ። እንደዚሁ ያገር ውስጥና የውጭ እርዳታ ለጋሽ የመሆናችሁ ለዚህ ህዝብ ድረሱለት ህዝብ እየተበታተነ ነዉ።

በሃገራችን ያላችሁ የነፃ ፕሬስ ጋዜጠኞች ከያኒዎች ፀሃፊዎች አመደኞች በዚህ በተሸገረዉ ህዘብ በአካል አይታችሁ ለኢትዮጵያ ህዝብና ለአለም አስታውቁት በተጨማሪ የውጭ ብዙሃን መገናኛም ለዚህ አዲስ አ ደጋ ተከታትላችሁ ብትዘግቡት

የሃገራችን የወገን ወዳጅ የሆናችሁ ጠበቆች ለዚህ እፅዋት አውዳሚ ቫይረስ ያስገቡ ህዝቡ ለረሃብ ለስደት የዳረጉ ባለስልጣናትና ተመራማሪ ተብዬዎች ደንቆሮ ዶክተሮች ወ ደ ህግ አቅርባችሁ ታስፈርዱዋቸዉ ዘንድ ደግሜ ጥርዬን አቀርባለሁ በተለይ በቅርብ የምትመለከቱት ያላችሁ በመቐለ የምትገኙ ጠበቆች በቆራጥነት በህግ ድጋፍ ብታደርጉ ለወገን ደራሽ ወገን ነውና::

ከአንድነት ፓርቲ ኢንጂነር ግዛቸው ካቢኔ ስድስቱ አመራሮች ራሳቸውን አገለሉ።

$
0
0

UDJስድስት የአንድነት መራሮች በኣንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር ኢንጂነር ግዛቸው የሚመራ ካቤኔ ውስጥ መቀጠላቸው ትርጉመ ቢስ መሆኑን መረዳታቸውን በመግለጽ ለግዛቸው ደብዳቤ ያስገቡት የአንድነት አመራሮች
ተክሌ በቀለ –ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዘዳንት
በላይ ፈቃዱ —ምክትል ፕሬዘዳንት
ሰለሞን ስዮም —የፖለቲካ ጉዳዮች ሃላፊ
ዳንኤል ተፈራ — የድርጅት ጉዳይ ሃላፊ
ዳዊት አስራደ —የኢኮኖሚ ጉዳዮች
ፀጋየ አላምረው -–የገንዘብ ክፍል ሃላፊ    ሀላፊ : ራሳቸውን ከኢንጅነር ግዛቸው ካቢኔ ማግለላቸው ታውቋል።

ኢንጂነር ግዛቸው በአንድነት እና በመኢአድ መካከል የሚደረገውን ውህደት በማኮላሸት ስራ ላይ ከመሰማራታቸውም ሌላ ሰርጎገቦችን እየሰበሰቡ ፓርቲው የሚያደርጋቸውን እንቅስቃሴዎች እያበላሹ መሆኑን አቤቱታዎች ይሰማሉ፡፤እንዲሁም በጀግናው አንዱአለም አራጌ እና በሃብታሙ መታሰር ጋር እንደሚጠረጠሩ እና የአንድነትን እንቅስቃሴ በዘለቀ ረዲ በኩል ለወያኔ ሪፖርት እንደሚያደርጉ በአባላቶቹ አቤቱታ ይቀርብባቸዋል።

Health: በቀዶ ጥገና ወቅት በሽተኛው ከሰመመን ቢነቃ ምን ሊፈጠር ይችላል?

$
0
0

የቀዶ ጥገና በሚሰራበት ወቅት የማደንዘዣ መድሃኒቶች እንደሚሰጡ አውቃለሁ፡፡ ሆኖም የእነዚህ መድሃኒቶች የአሰራር ምስጢር ምን ይሆን እያልኩ ሁሌ ራሴን እጠይቃለሁ፡፡ ለመሆኑ እንዴት ነው ሰው ሰውነቱ በስለት እየተቆራረጠ ምንም እንዳይሰማው ማድረግ የሚቻለው? በመሀል በሽተኛው ቢነቃስ ምንድነው የሚፈጠረው? እባካችሁን እስቲ በእነዚህ መድሃኒቶች ዙሪያ ማብራሪያ ስጡኝ?
ሜሮን ነኝ

ሜሮን የጠየቅሽን ጥያቄ የብዙ አንባቢዎቻችንም ጥያቄ ይመስለናል፡፡ መድሃኒቶቹ በጤናው ዘርፍ በጣም ትልቅ አስተዋፅኦ ያበረከቱና እያበረከቱም ያሉ ናቸው፡፡ የህክምና አብዮትን የፈጠሩ የእነዚህን ድንቅ የዘመናችን መድሃኒቶችን አሰራር ማወቅ ብዙ ፋይዳ አለው፡፡ እና ስለነዚህ መድሃኒቶች ማወቅ ጠቃሚ በመሆኑ ለአጠቃላይ ግንዛቤ ይረዳ ዘንድ እንደሚከተለው ተዳሷል፡፡
ማደንዘዣ
ብዙ አይነት የሰመመን መድሃኒቶች ሲኖሩ በአጠቃላይ ከአሰራራቸው አንፃር በሁለት ይከፈላሉ፡፡ የመጀመሪያው ለከባድ ቀዶ ህክምና የሚሰጠውና ራስን በማሳት መላ ሰውነትን የሚያደነዝዘው ሲሆን ‹‹ጀነራል አንስቴዥያ›› በመባል ይታወቃል፡፡ ሌላው ለመለስተኛ ቀዶ ህክምና የሚያገለግለው እና ህክምናው የሚሰጥበትን የአካል ክፍል ብቻ የሚያደነዝዘው ሲሆን ‹‹ሎካል አንስቴዥያ›› በመባል ይታወቃል፡፡ ይሄኛው ራስን ሙሉ በሙሉ አያስትም፡፡ የምጥ ህመምን ለመቀነስ ከወገብ በታች የሚያደነዝዘው አይነትም(ስፓይናል አንስቴዥያ) ከዚህኛው አይነት መመደብ ይቻላል፡፡
አሰጣጣቸውም በደም ስር ወይም በጡንቻ ስር በመውጋት አሊያም በጋዝ መልክ በአፍንጫ በመሳብ ሊሆን ይችላል፡፡ ዋነኛው አጠቃላይ ማደንዘዣ በሚሰጥበት ወቅት እንደየሁኔታው መድሃኒቶቹን እርስ በርሳቸው ወይም ከሌላ መድሃኒት ጋር ማጣመር ሊያስፈልግ ይችላል፡፡ በተለይ ጡንቻን ዘና በማድረግ ለህክምናው አጋዥ የሆኑ መድሃኒቶች አብረው ይሰጣሉ፡፡

ሰውነታችን በአጠቃላይ በተለይም የነርቭ ስርዓታችን ያልተለመዱና የማይመቹ ወይም ጎኒ የሆኑ ውጫዊም ሆነ ውስጣዊ ትንኮሳዎች የሚለይበትና ለዚህም አጸፋዊ የመከላከል እርምጃ የሚወስድበት የራሱ የሆነ ድንቅ ጥበብ አለው፡፡ በምሳሌ እንየው፡፡ የጋለ ምድጃን ድንገት ሳናስበው ብንነካው ፈጣኑ የነርቭ ስርዓታችን ይህ ክስተት አደገኛ መሆኑንና ቶሎ ካልተወገደ ከባድ ቃጠሎና ህመም እንደሚያስከትል ተገንዝቦ በድንገት ከቃጠሎው እጃችንን እንድናርቅ ያደርጋል፡፡ ይህ ሁሉ የሚከናወነው ታዲያ በሽርፍራፊ ሰከንዶች መሆኑ ይበልጥ ያስደንቃል፡፡ መልዕክቱ በቅጽበት ቆዳ ላይ ባሉ ህመምን በሚለዩ ህዋሶች ተለይቶ በነርቮች አማካይነት ወደ አንጎል ይደርሳል፡፡ እዚያም ተተርጉሞ ምላሹ ወደ ጡንቻዎችና መገጣጠሚያዎች በሌሎች ነርቮች አማካይነት ተመልሶ ራስን የማዳን አጸፋዊ ተግባር በቅጽበት ያከናውናል፡፡

ውድ ጠያቂያችን ሜሮን የማደንዘዣዎች አሰራርም ይህንን የነርቭ ስርዓት ሂደት መቀነስ፣ መገደብ ወይም ማስወገድ ነው፡፡ ስለሆነም ታካሚው በቀዶ ህክምናው ወቅት ምንም አሳማሚ ስሜቶች ሳይሰማው ዘና እንዲል ያስችለዋል፡፡ ያማ ባይሆን እንኳንስ ‹‹በተቀደሰው ቢላዋ›› መቆረጥ ይቅር እና ጠንከር ያለ ቁንጥጫስ ቢሆን ‹‹ዘራፍ!›› አሰኝቶ ያፈናጥረን የለ፡፡ ዕድሜ ለሰመመኑ እንጂ የህክምና ስታፍ ሁሉ ቡጢና ጡጫ በቀመሰ ነበር- በታካሚው ቅጽበታዊ እርምጃ አማካይነት ማለት ነው፡፡ በዚህ አይነት በጊዜያዊነት ራስን በማሳትና ጡንቻን በማዛል ካልተፈለገ የሰውነት ምላሽ ከመከላከልም በላይ ታካሚውን ካላስፈላጊ ስቃይና ጭንቀት ይታደጋሉ፡፡ ይህ መሰረታዊ የማደንዘዣዎች የአሰራር ሂደት ሲሆን እስካሁንም ብዙ ያልተደረሰባቸው የአሰራር ምስጢሮች እንዳሉት ጥናቶች ይጠቁማሉ፡፡ ተመራማሪዎችም ምስጢሩን የመፈተሽ ተግባራቸውን አላቆሙም፡፡ ሳይንስ ጥበብና ቴክኖሎጂ ምን መቆሚያ አለውና፡፡

ውድ ሜሮን ስለ ሰመመን መድሃኒቶች ሲወሳ መረሳት የሌለበት ሌላው ጉዳይ መድሃኒቶችን ስለሚሰጡት ባለሙያዎች ነው፡፡ ለዚህ ሙያ በቀጥታ የሰለጠኑ ባለሙያዎች (Anaesthetists) ሲባሉ፤ ሐኪም ሆነው በተጨማሪ በሙያው ስፔሻላይዝ ያደረጉ ከሆኑ (Anaesthetologist) ይባላሉ፡፡ በቀዶ ህክምና ቡድኑ ውስጥ በህክምናው ውጤታማነት በተለይም ማደንዘዣው የታሰበለትን ግብ እንዲመታ ከማስቻል አንፃር የእነዚህ ባለሙያዎች አስተዋፅኦ ላቅ ያለ ነው፡፡
ዋነኛ ተግባራቸውም ከዋናው ቀዶ ህክምና በፊት ይጀምራል፡፡ ይኸውም ከታካሚው፣ አሳካሚዎቹና ከሌሎች የጤና ባለሙያዎች ጋር በመተባበር በሽተኛው የሰመመን መድሃኒቱንና ቀዶ ህክምናውን መቋቋም የሚችል ትክክለኛ ዕጩ ስለመሆን አለመሆኑ፤ ይህን አስቸጋሪ የሚያደርጉ ተጓዳኝ በሽታዎች ከፍተኛ ደም ግፊት፣ ስኳር፣ ደም ማነስ… መኖር አለመኖራቸው የመድሃኒቶች ‹‹አለርጂ›› ስለመኖር አለመኖሩ እንዲሁም ቀድሞ መደረግ ስለሚገባቸው ሌሎች ቅድመ ዝግጅቶች ወዘተ በማጣራት አስፈላጊውን ውሳኔና እርምጃ ይወስዳሉ፡፡ በቀዶ ህክምናው ወቅትም መድሃኒቶቹን መጥኖ ከመስጠት ባለፈም የበሽታውን ደም ግፊት፣ የልብ ምት፣ የአንጎልና የነርቮች ሁኔታና ለዚሁ ተግባር በተዘጋጀ መቆጣጠሪያ መሳሪያ አማካኝነት ይከታተላሉ፡፡ ጊዜአዊ የመተንፈሻ ቱቦ ማስገባትና በመጨረሻም ማስወጣትም ሌላው ተግባራቸው ነው፡፡ በመጨረሻም ታካሚው ሙሉ በሙሉ ከማደንዘዣው ተፅዕኖ መላቀቁንና መንቃቱን በማረጋገጥ ተግባራቸውን ያገባድዳሉ፡፡

በነገራችን ላይ የግድ መውሰድ ካለባቸው መድሃኒቶች በስተቀር ከባድ ቀዶ ህክምና የሚደረግለት በሽተኛ ቢያንስ ከህክምናው በፊት ከ6-12 ሰዓታት ምንም አይነት ምግብም ፈሳሽ መጠጥም መውሰድ አይፈቀድለትም፡፡

የማደንዘዣ መድሃኒቶችና አንፃራዊ ጉዳታቸው

የማደንዘዣ መድሃኒቶችም እንደማንኛውም መድሃኒት አንፃራዊ የጎን ጉዳት አላቸው፡፡ ጉዳቶቹም ከቀላል ጀምሮ ህይወትን ሊያሳጣ እስከሚችል ከባድ ጉዳት ይለያያል፡፡ ለምሳሌ ከባድ አለርጂክ ሪያክሽን፡፡ ከበድ ያሉት ችግሮች ያልተለመዱና ከስንት አንዴ የሚከሰቱ ሲሆኑ ብዙዎቹ በቅድመ ጥንቃቄና ክትትል ሊወገዱ ይችላሉ፡፡ ዋነኞቹ የጎን ጉዳቶች የሚከተሉት ናቸው፡፡ ማቅለሽለሽ፣ ማንቀጥቀጥ፣ የጉሮሮ ቁስለትና ህመም፣ የነርቭ መደንዘዝ፣ ቶሎ አለመንቃት… የመሳሰሉት ናቸው፡፡ ለምሳ በምሉ በመድሃኒቶቹ ሳቢያ የሚከሰት ሞት ከ200 ሺ ሰዎች በአንዱ ብቻ ነው፡፡ ሆኖም ግን ደም ግፊት ወይም ልብ ድካም የመሳሰሉ ተጓዳኝ በሽታዎች ባለባቸው ታካሚዎች ላይ የሞት አደጋው ከአንድ እስከ ሁለት በመቶ ከፍ ሊል ይችላል፡፡
ሌላው አልፎ አልፎ ሊከሰት የሚችለው ችግር በሰመመን ውስጥ ሆነውም የህመም ስሜት መሰማቱ ነው፡፡ በዚህ አይነት የተወሰኑ ታካሚዎች ላላስፈላጊ ህመም ሊጋለጡ እንደሚችሉ በቅርቡ ቢቢሲ ያወጣው መረጃ ይጠቁማል፡፡ ፀረ-ህመም መድሃኒቶችን በመጠቀምና በሌሎችም ቅድመ ህክምናዎች (premediatations) እንዲህ አይነቱን ህመም መቀነስ ወይም ማስወገድ ይቻላል፡፡ የመስኩ ተመራማሪዎችም ለእንዲህ አይነቱ ህመም መንስኤና መፍትሄ ፍለጋ በመትጋት ላይ ናቸው፡፡ ምክንያቱም ህክም ከህመምና ከስቃይ የፀዳ መሆን ስላለበት፡፡
ውድ ጠያቂያችን ሌላው ይበልጥ አስገራሚውና አሳሳቢው ጉዳይ በማደንዘዣ ውስጥም ሆኖ ንቁ መሆን (Anesthesia awareness) ነው፡፡ ይህ ያልተለመደ ቢሆንም ሁኔታው አስፈሪና አሳሳቢ ነው፡፡

በዘ-ሐበሻ ጋዜጣ ቁጥር 65 ላይ ታትሞ የወጣ።

(ሰበር ዜና) ፍትህ ሚ/ር የክስ ቻርጆችን ለሃገር ቤት ጋዜጠኞች ማደል ጀመረ (የሎሚ መጽሔትን የክስ ቻርጅ ይዘናል)

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) ቀድሞ በኢትዮጵያ ያሉትን መጽሔቶችን እና ጋዜጦችን እንደሚከስ ያስታወቀው የሕወሓት አስተዳደር ፍትህ ሚ/ር ለጋዜጠኞች የክስ ቻርጆችን ማደል ጀመረ። በዛሬው ዕለት የሎሚ መጽሔት ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ግዛው ታዬ እና ድርጅቱ ዳዲስሞስ ኢንተርቴይመንትና የፕሬስ ሥራዎች ኃ/የተ/የግል ማህበር የክስ ቻርጅ እንደደረሰው ለዘ-ሐበሻ የመጣው መረጃ አመለከተ።

ጋዜጠኛ ግዛው ታዬ

ጋዜጠኛ ግዛው ታዬ


በተመሳሳይ እንደሚከሰሱ የተነገራቸው የአዲስ ጉዳይ ጋዜጠኞች ሃገር ጥለው ለመሰደድ የበቁ መሆኑን ዘ-ሐበሻ በትናንትናው ዕለት መዘገቧ ይታወሳል።

በሎሚ መጽሔት አዘጋጅ ላይ የሕወሓት አስተዳደር ፍትህ ሚ/ር ያቀረበው ክስ “ተከሳሾች በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን ወንጀሉና ወንጀሉ የሚሰጠውን ውጤት በመቀበል መንግስት የሚለወጠው ህገ መንግስታዊ በሆነ መርህ በምርጫ ሆኖ እያለ ኢ-ህገመንግስታዊ በሆነ መንገድ በአመጽ ሥርዓቱን ለመጣል” የሚል ሲሆን ለክስ ያበቁት ጽሁፎችም
1ኛ. በሎሚ መጽሄት ቅጽ 3 ቁጥር 109 “በዓለም በጨቋኝነቷ አቻ የማይገኝላት የሚዲያ ምህዳር በኢትዮጵያ” የሚለው
2ኛ. ሰብ አዊ መብት የሚባል በኢትዮጵያ መንግስት ሙሉ በሙሉ ተረስቷል። የምንገኝበትም ዓለም በመራጮችና የለውጥ ማዕበሎች የሰፈነበት በመሆኑ ኢትዮጵያውያን በቀጣይ ዓመት በሚደረገው የአገራዊ አጠቃላይ ምርጫ በመንተራስ ለበርካታ ዓመታት ከዘለቀ የፍ የጭቆና አገዛዝ ለመላከክ የማይቀረውን የለውጥ ማዕበል ለማምጣት እራሳቸውን ለተጠናከረ ሕዝባዊ ዓመጽ ማደራጀት መጀመራቸው ሊበረታታ የሚገባው ነው” በሚል አረፍተ ነገር፤
3ኛ. በሎሚ ቁጥር 91 ላይ “የአሸባሪነት ፈርጦች” በሚል ር ዕስት ‘ኢህ አዴግም ከማን አንሼ በሚል ስሜት ተቃራኒ ሃሳብ የሚያቀርቡ ጋዜጠኞችን ለስልጣኔ/ወንበሬ) ያስገኛል የሚላቸውን ጠንካራ ተቃዋሚዎችን እያደነ በአሸባሪነት ስም ወህኒ ያወርዳቸው ከጀመረ ሰንብቷል በሚል ጽፏል በሚል
4ኛ.”የኢሕአዴግ የሽብርተኝነት መመዘኛ ምንድን ነው?” “ኢህአዴግ” የሕዝብ ተቀባይነት ያገኘ አይመስለውም ሕዝብ የተቀበለውና አምነዋለው የሚለው ሰው ለኢህ አዴግ ጠላት ነው፤ ሽብርተኛ ተብሎ ይከሰሳል በማለት በሽብር ህግ ተከሰው የተቀጡ ተከሳሾች በህዝብ የሚወደዱና ለገዢ ፓርቲ ተቀናቃኝ በመሆናቸው ብቻ በግፍ የተቀጡ ንጹሃን እንደሆኑ የሚያስመስል ጽሑፍ አቅርቧል በሚል 4 ክሶች ቀርበውበታል።

የክስ ቻርጆቹን ተመልከቷቸው፤ ተጨማሪ መረጃዎች እንደደርሱን እንመለሳለን።
feteh Lomi 1

feteh Lomi 2

feteh Lomi 3


በነኡስታዝ በድሩ ሁሴን ላይ የተፈጸመውን ግፍ ”በአፓርታይድ ጊዜ እንኳን ያልተፈጸመ”በማለት ዳኛው መኮነናቸው ታወቀ ‪

$
0
0

news(ቢቢኤን ራድዮ) የህዝበ ሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎች በዛሬው እለት ፍርድ ቤት የቀረቡ ቢሆንም ዳኞች አልተሟሉም በሚል ያልተካሄደ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን ለሁለቱ ዳኞች ግን እየደረሰባቸው ያለውን ነገር አህመድ ሙስጠፋና ኡስታዝ በድሩ ሁሴን በዝርዝር ማስረዳታቸው ታዉቐል፡፡ ቁልፍ ባለው ሰንሰለት በጨለማ ክፍል እንዳሰሩዋቸው ምግብም እንደከለከሏቸው የገለጹ ሲሆን ዳኛውም ይህን ሲሰሙ እንዴት እንደዚህ ይደረጋል በዚህ ዘመን ቀርቶ በአፓርታይድ ጊዜ እንኳን አይፈጸምም ነበር በማለት መኮነናቸው ታዉቐል፡፡ ዳኛውም አያይዘው እንኳን በ21ኛው ክፍለ ዘመን ቀርቶ አስርቱ ትእዛዛት በሚፈጸሙበት ጊዜ እንኳን እንዲህ አይነት ነገሮች አይደረጉም ነበር ማለታቸው ታዉቋል፡፡
ኮሚቴዎቹም አሰቃቂ ስቃይ በሚፈጸምበት በማእከላዊ እንኳን የምግብ ክልከላ እንደማይፈጸምባቸው ተናግረዋል፡፡ ኡስታዝ በድሩ ሁሴን የታሰረበት ሰንሰለት ረዥም ጥልፍልፍ ሲሆን ዙርያ ጥምም በማሰር ቆልፈውበት እንደነበር ገልጾ ካቴናውም የተፈታለት ፍርድ ቤት ሊመጣ ሲል ከ85 ሰአታት እስር በሁላ እንደሆነ ገልጽዋል፡፡
ጠዋት ወደ ፍርድ ቤት ሊመጡ ሲሉ ኮሚቴዎቹ የበድሩ ሰንሰለት ሳይፈታ ይሂድ ለፍርድ ቤት ማሳየት እንፈልጋለን ብለው የነበረ ቢሆንም የማረሚያ ቤቱ ሃላፊ በግዳጅ ሰንሰለቱን ፈተው ወደ ፍርድ ቤት እንዲሄድ እንዳደረጉ ለመረዳት ተችሏል።

ዐማራው በመስዋዕትነቱ ባቆያት ኢትዮጵያ ለምን ዘሩ ከምድረ-ገፅ ይጥፋ?

$
0
0

moreshየትግሬ-ወያኔ መሪዎች እነ መለሰ ዜናዊ እና ስብሐት ነጋ ወደ ደደቢት በርሃ የገቡበት ዋና ምክንያት በዐማራው ህዝብ ላይ ካላቸው ፍራቻ እና ጥላቻ በመነጨ የበቀል ስሜት ነው። ይህንኑ በፖሊሲ የተነደፈ የበቀል ስሜት ከበረሃ ጀምረው በረቀቀ መንገድ እና በተቀናጀ ሥልት በተከታታይ ተግባራዊ በማድረግ ዐማራን ከኢትዮጵያ ምድር ለማጥፋት ሌት ተቀን ተግተው በመማሰን ላይ ናቸው። ነገር ግን ዐማራው በምን በደሉ እና ኃጢያቱ፣ በደም ዋጋ አንድነቷን ጠብቆ ካኖራት ውድ እናት አገሩ ፈጽሞ ይጥፋ? ለምን?

ለዚህ መነሻ የሚሆነው የትግሬ-ወያኔን መርኅ፣ የአባሎቹንም ማንነት ጠንቅቆ ማወቅ ሲቻል ነው። የትግሬ-ወያኔ ቡድን ጎጠኛ ትግሬዎች የመሠረቱት፣ ናዚያዊ እና ፋሽስታዊ ባሕርይዎች ያሉት ድርጅት ነው። በመሆኑም ኢትዮጵያን ለማፍረስ የኢትዮጵያዊነት መሠረት እና ምንጭ የሆኑ ተቋሞችን ለማጥፋት ይንቀሣቀሣል። የትግሬ-ወያኔ ዐማራውን እና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ኃይማኖትን ከሥር መሠረታቸው መንግሎ ለመጣል ፖሊሲ አውጥቶ ሌት ተቀን የጥፋት ዘመቻውን ያጧጧፈ የዐረመኔዎች እና የሠይጣን አማኞች ድርጅት ነው። የዚህ ቡድን እንቅስቃሴ በባሕርይው ከደቡብ አፍሪቃ የአፓርታይድ ሥርዓት አራማጆች እና ከጀርመኖቹ የናዚ ፓርቲ ጋር ተመሣሣይነት አለው። የጀርመኑ ናዚ ፓርቲ መርኃግብርም ሆነ የመሪዎች ጽኑ ምኞት በዘረኝነት እና በፀረ-አይሁዳዊነት የተሞላ ነበር። በትክክለኛ ቅጅም የትግሬ-ወያኔ ከመሠረቱ ሲታይ ፀረ-ዐማራ እና ፀረ-ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ኃይማኖት እንደሆነ በድርጅቱ ማኒፌስቶ ላይ በግልጽ ተቀምጧል። ስለሆነም በዛሬይቱ ስሟ በካርታ ላይ ብቻ በቀረው ኢትዮጵያ፣ ዐማራው በምን ደረጃ ለፈጽሞ ጥፋት እንደተጋለጠ ለማየት ያስችላል።   ( ሙሉውን ከዚህ ላይ ያንብቡ )

የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ሚድሮክ ያቀረበውን የካርታ መምከን አቤቱታ ተቀበለ

$
0
0

•የአዲስ አበባ አስተዳደር የመከነው ካርታ እንዲመለስ አዘዘ

የአዲስ አበባ አስተዳደር ግንባታ ሳይካሄድባቸው ለዓመታት ታጥረው የተቀመጡ ሁለት ቦታዎች ካርታ ማምከኑን የተቃወመው ሚድሮክ፣ ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ያቀረበው አቤቱታ ተቀባይነት ማግኘቱን ምንጮች ገለጹ፡፡

HMDAMUDIየአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሚድሮክ ልማት ለማካሄድ ከዓመታት በፊት ተረክቦ ግንባታ ሳያካሂድ አጥሮ ያስቀመጣቸው ቦታዎች ያሉበትን ሁኔታ በከፍተኛ ባለሙያዎች አስጠንቶ ነበር፡፡ ባለሙያዎቹ በተለይ በልደታ ክፍለ ከተማ ዋቢ ሸበሌ ሆቴል ጎንና በየካ ክፍለ ከተማ በሻሌ ሆቴል አካባቢ የሚገኙት ቦታዎች ምንም ዓይነት ግንባታ ሳይካሄድባቸው ለዓመታት የተቀመጡ በመሆናቸው፣ ካርታቸው እንዲመክን የውሳኔ ሐሳብ አቅርቦ ነበር፡፡ የሁለቱ ቦታዎች ካርታ እንዲመክን የቀረበው የውሳኔ ሐሳብ ተቀባይነት በማግኘቱ ካርታዎቹ በክፍላተ ከተሞቹ መክነዋል፡፡ 

ነገር ግን ሚድሮክ በተወሰደው ዕርምጃ ደስተኛ ባለመሆኑ ምክንያት ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አቤት ብሏል፡፡ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የቀረቡትን የሚድሮክ መቃወሚያ ሐሳቦች መቀበሉን የሚናገሩት ምንጮች፣ የአዲስ አበባ አስተዳደር ያመከነውን ካርታ በድጋሚ እንዲሰጥ መመርያ ማስተላለፉን አስረድተዋል፡፡

ከፍተኛ ባለሙያዎች ተካተውበት የሚድሮክ 11 ቦታዎችን ያጠናው ኮሚቴ፣ ካርታቸው መክኖ የነበረባቸው ሁለቱ ቦታዎች ምንም ግንባታ እንዳልተካሄደባቸው አመልክቷል፡፡ ከእነዚህ ቦታዎች በተጨማሪ ለሸራተን ማስፋፊያ ከሦስት ዓመት በፊት ነዋሪዎች ተነስተው ነፃ የሆነው መሬትም ግንባታ እንዳልተጀመረበት ኮሚቴው በጥናቱ አመልክቷል፡፡ በተወሰነ ደረጃ ፒያሳ የሚገኘውና ካዛንቺስ አካባቢ የሚገኙት ቦታዎች መሠረት ለማውጣት የተወሰነ ሥራ መሠራቱንም የኮሚቴው ሪፖርት ጠቁሟል፡፡ 

በቀረበው የውሳኔ ሐሳብ ላይ ተመሥርቶ የአስተዳደሩ ካቢኔ የማስተማሪያ ዕርምጃ ይወስዳል ተብሎ ሲጠበቅ፣ ሐሳቡን የሚቀለብስ ሥራ መሠራቱ አስገራሚ እንደሆነባቸው የአስተዳደሩ ሠራተኞች ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ 

ኮሚቴው ከሚድሮክ ቦታዎች በተጨማሪ በአዲስ አበባ ከተማ 109 ቦታዎች ያለግንባታ ታጥረው ለዓመታት መቀመጣቸውንና ከእነዚህ ቦታዎች መካከል 56 ያህሉ ዕርምጃ እንዲወስድባቸው የውሳኔ ሐሳብ አቅርቧል፡፡ የውሳኔ ሐሳቡ ከቀረበ በርካታ ወራትን ቢያስቆጥርም ከብዙ መዘግየት በኋላ፣ የከንቲባ ድሪባ ኩማ ካቢኔ በዚህ ሳምንት በውሳኔ ሐሳቡ ላይ ተመሥርቶ የመጨረሻ መመርያ ለመስጠት ፕሮግራም መያዙ ታውቋል፡፡

Source: Ethiopian Reporter

ፍትህ ሚ/ር በጋዜጠኞች ላይ የጀመረውን ዘመቻ ቀጠለ፤ አፍሮ ታይምስና ጋዜጠኛ ቶማስ አያሌው የክስ ቻርጅ ደረሳቸው (ክሱን ይዘነዋል)

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) ለአዲስ ጉዳይ መጽሔት አዘጋጆች መሰደድ ምክንያት የሆነው የፍትህ ሚ/ር ጋዜጠኞችን ሰዶ የማሳደድ ዘመቻ ቀጥሎ በትናንናው ዕለት ሎሚ መጽሔት እና ጋዜጠኛ ግዛው ታዬ የክስ ቻርጅ የደረሳቸው መሆኑን ዘ-ሐበሻ መዘገቧ አይዘነጋም። ዛሬ በደረሰን መረጃ መሰረት የአፍሮ ታይምስ ጋዜጣ አዘጋጅ ጋዜጠኛ ቶማስ አያሌው ከፍትህ ሚ/ር የክስ ቻርጅ ደርሶታል።

ጋዜጠኛ ቶማስ አያሌው

ጋዜጠኛ ቶማስ አያሌው


የፍትህ ሚ\ር በጋዜጠኛውና በአፍሮ ታይምስ አሳታሚ ድርጅት ላይ የመሰረተው ክስ “የሃሰት ወሬዎችን በማሳተም ሕዝብን ለማነሳሳት በማሰብ ሕዝቡ በህገመንግታዊ ሥርዓቱ ላይ አመኔታ እንዳይኖረው፣ ጥርጣሬ እንዲገባው ለማድረግ በማሰብ” የሚል ነው። ጋዜጠኛ ቶማስ የቀረበበት ክስ በሚያዝያ 21 እና 22 2006 በወጣው አፍሮ ታይምስ ጋዜጣ ላይ “ልዩ ሃይሎችና መከላከያ ሠራዊት ተፋጠዋል” በሚለው ዜና ሥር “ቀደም ባሉት ጊዜያት በጋምቤላ ክልል ሰፍሮ የሚገኘው የመከላከያ ሰራዊት የፈለገውን ሰው ሲያስር፣ ሲገድል፣ ሴቶችን አስገድዶ ሲደፍር ቆይቷል። ይህም የሰራዊቱን ስርዓት አልበኝነትና ሕገወጥ ድርጊት ለማስቆም የሞከረ መንግስታዊ አካል አልነበረም።” በሚል በሰፈረው መረጃ ሲሆን ለዚህም ፍትህ ሚ/ር “አገሩንና ህገመንግስቱን በመጠበቅ እንዲሁም በዓለም አቀፍ ሕብረተሰብና መንግስታት መልካም ስነምግባር እያከናወነ ያለውን የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በሕዝቡ ዘንድ አመኔታ እንዲያጣ ጥርጣሬ እንዲገባው ለማድረግ በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በፈጸሙ ሐሰተኛ ወሬዎችን በመንዛትና ሕዝብን በማነሳሳት ወንጀል ተከሰዋል” ሲል በክስ ቻርጁ ላይ አስፍሯል፡፡

በሃገር ውስጥ የሚታተሙ በርካታ መጽሔቶችን እና ጋዜጦችን እከሳለሁ ሲል የቆየው ፍትህ ሚ/ር ጋዜጠኞችን ለማፈን የሚያደርገውን ተንኮል ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ሲተቹት እንደቆዩ ይታወሳል።

thomas ayalew 1

thomas ayalew 2

ኤርትራ የሩሲያን የጦር ልምምድ ልታስተናግድ ነው

$
0
0

በመላኩ ጸጋው

በቅርቡ በተለያዩ አካባቢዎች ተከታታይ የጋራና የተናጠል የጦር ልምምድ ያደረገችውን ሩሲያን በቀጣይ በኤርትራ በቀይ ባህር አካባቢ ልታስተናግዳት መሆኑን “ጊሲካ አፍሪካ ኦንላይን” በአውሮፓ የሚገኙ የኤርትራ ዲፕሎማቶችን ጠቅሶ ከሰሞኑ ባሰራጨው ዘገባ ገልጿል። የልምምዱ ዋነኛ ዓለማ በአንድ መልኩ የሩሲያን ጦር ዝግጁነት ለማረጋገጥ እንዲሁም በኤርትራ ወደቦች አቅራቢያ ሩሲያ ቋሚ የጦር ሰፈርን (Military base) ለማቋቋም መሆኑን ዘገባው ጨምሮ አመልክቷል። እንደ ዘገባው ከሆነ የሩሲያ የጦር ልምምድ በሶስት ወራት ጊዜ ውስጥ ይጀመራል ተብሎ ይጠበቃል።
news
ኤርትራ ከተወሰኑ ጊዜያት ወዲህ በሩስያ እንደ አንድ ስትራቴጂክ አጋር ሀገር እየታየች መሆኗን ዘገባው አመለክቷል። እንደዘገባው ከሆነ አሜሪካ በጅቡቲ ቋሚ የጦር ሰፈር ያላት ሲሆን በተለያዩ ጊዜያትም ከጅቡቲ ወታደሮች ጋር የአየር ኃይልና የባህር ኃይልን ባቀናጀ መልኩ የጦር ልምምድ ታደርጋች። ጅቡቲ የአሜሪካንን ጦር ከማስተናገድ ባለፈ በዋነኝነትም የፈረንሳይ የጦር ሰፈር በመሆን እያገለገለች ነው። ሱዳን በአንፃሩ ኢራን በቀይ ባህር የሱዳን ምዕራባዊ ግዛት የባህር ኃይል ቤዝ እንድትመሰርት ለማድረግ እንቅስቃሴ የጀመረች መሆኗን ቀደም ያሉ የዩናይት ፕሬስ ኢንተርናሽናል UPI ዘገባዎች ያመለክታሉ። ይህ የሱዳን እንቅስቃሴ ግን በእስራኤል አልተወደደም።

ሩሲያ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በተለያዩ አቅጣጫዎች ተከታታይ የጦር ልምምዶችን በማድረግ ላይ ትገኛለች። እንደ ዘጋርድያን ዘገባ ከቀናት በፊት ከሃያ ያላነሱ የጦር መርከቦችንና በርካታ ተዋጊ አውሮፕላኖችን ባሳተፈ መልኩ በደቡብ ምስራቅ አውሮፓ በሚገኘው ጥቁር ባህር ሰፊ የጦር ልምምድ አድርጋለች። ኢተር ታሰ የዜና ወኪል ባሰራጨው ዘገባም ከዚህም በተጨማሪ ሩስያ በተመሳሳይ መልኩ ከቻይና ጋር በጋራ በመሆን 18 የጦር መርከቦችን ባሳተፈ መልኩ በሻንጋይ አቅራቢያ በያዝነው አመት የጦር ልምምድ አድርጋለች። በሌላ አቅጣጫ ሩስያ ከቀናት በፊት አንድ መቶ ተዋጊ አውሮፕላኖችን ባሳተፈ መልኩ በዩክሬን ድንበር አቅራቢያ ጠንካራ የጦር ልምምድ ያደረገች መሆኑን ዘገባዎች ያመለክታል።

ኤርትራ አልሸባብን በሶማሊያ በማገዝ በሀገሪቱ የውስጥ ጉዳይ በመግባት አካባቢያዊ ሰላምን እያወከች ነው በሚል በተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት በኩል ተከታታይ ማዕቀቦች ጥለውበታል። የቀድሞው የቡሽ አስተዳደርም ሆነ የኦባማ አስተዳደር ኤርትራን ሽብርን በሚደግፉ ሀገራት ዝርዝር ውስጥ እንድትካተት ያደረጓት ሲሆን በቅርቡም በዋሽንግተን በተካሄደው የአሜሪካ አፍሪካ መሪዎች ስብሰባ ከሮበርት ሙጋቤ እና ከአልበሽር ጋር ኢሳያስ አፈወርቂ በስብሰባው ላይ የሚታደሙበት ጥሪ ሳይደርሳቸው ቀርቷል።

ሩሲያ በአንጻሩ ከዩክሬን ጋር በተያያዘ ፖለቲካ ውዝግብ መግባቷን ተከትሎ በምዕራባውያኑ ሀገራት ተከታታይ ማዕቀብ የተጣለበት ሲሆን የሩሲያ መንግስት በአንፃሩ የአውሮፓና የአሜሪካ የግብርና ምርቶች ወደ ሀገሩ እንዳይገቡ እገዳን ጥሏል። የዩክሬኑን ውዝግብ ተከትሎ ሩሲያ ተከታታይ ወታደራዊ ልምምዶችን እያደረገች ሲሆን የቀይ ባህሩም የጦር ልምምድ የዚህ አካል ነው ተብሎ ይገመታል። ዘገባውን ያሰራጨው ጊሲካ አፍሪካ ኦንላይን የመረጃ ስርጭቱን በዋንኛነት በኢትዮጵያ፣ በኤርትራ፣ ሶማሊያ፣ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሶማሌላድ፣ ኬኒያ እና ኡጋንዳ ላይ ትኩረቱን አድርጎ የሚሰራ የሚዲያ ተቋም ነው። በኢጋድ ዙሪያም ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ሰፋ ያሉ ዘገባዎችን ሲያሰራጭ ቆይቷል።

ዜናው የተገኘው ዛሬ በአዲስ አበባ ታትሞ ከወጣው ሰንደቅ ጋዜጣ ነው።

የትንሳኤ ጥሪ ለኢሕአፓ –ቁጥር 2

$
0
0

የትንሣኤ ጥሪ ነሀሴ 2006
ቁጥር 2

‘’we must accept finite disappointment, but never lose Infinite hope.”
MARTIN LUTHER KING JR

“በትግል መሞት ህይወት” ብለው የተነሱት የኢሕአፓ ልጆች አሁንም እንደትናንቱ የሕዝብን መብት፥ የሀገርን ሉአላዊነት እና ክብር ከማንኛዉም ነገር አብልጠው ይታገሉለታል። ይህንንም ሲያደርጉ በድርጂቱ በኢሕአፓ ውስጥ ያገኙትን ልምድ ለሕዝብ በማካፈል ሕዝብን የስልጣን ባለቤት ለማድረግ ነዉ።

በአሁኑ ወቅት ያለብንን ትልቅ ፈተና ለማለፍና ሕዝብን ለድል ለማብቃት በመጀመራያ ሀገርን ከሁሉም በላይ ማስቀደም፤ በውስጣችን ያለዉን መከፋፈል ማጥፋት፡የድርጅትን ህይወት ከግለሰቦች በላይ ማየት፤ ሌት ተቀን ጠንክሮ መስራትን፡ ብሎም ለራስ ጥቅም ተገዢ እለመሆንን ይጠይቃል። የኢሕአፓ መሪወችም ሆነ አባላት እንደማንኛዉም ታጋይ የድርጂታቸዉና የኢትዮዽያ ሕዝብ አገልጋዮች መሆናቸዉን በመገንዘብ ድርጂቱ በኢሕአፓነቱ ሳይሆን፣ ታጋዩ በታጋይነቱ ሳይሆን በመሪዎቹ ሥም ሲጠራና ሲክፋፈል በግዴለሽለት ከአዩት በታሪክ ፊት ይጠየቃሉ።
ውድ ወገኖቻችን በሚያዝያ ወር ትንሳዔ በሚል የመሰባሰቢያ ርእስ አንድ ጽሁፍ አውጥተን መበተናችን ይታወሳል ከዚህም ጽሁፍ ቦኋላ በአንዳንድ የዜና ማሰራጫዎች በመቅረብ የሰብስባችን አላማ ምን እንደሆነ ማብራሪያዎች ለመስጠት ሞክረናል ሆኖም አሁንም የተነሳንለትን ዓላማ እንደገና ማብራራት አስፈላጊ በመሆኑ ትንሳኤ ቁጥር ሁለትን አውጥተናል።
Tensaye
አላማችን አንድና አንድ ነው ይሄውም በኢትዬጵያ ዴሞክራሲያዊና ሰብአዊ መብቶችን የሚያከብር ለህግ የሚገዛ በህዝብ ውክልና ያለው ስርአት እንዲገነባ ጠንካራ ትግል ማካሄድ ነው። ለዚህ ትግል በቆራጥነታቸው የተመሰከረላቸውና ከፍተኛ ልምድ ያላቸውን የኢህአፓ ልጆች እንደገና ማሰባሰብ ከፍተኛ ጥቅም ይኖረዋል ብለን እናምናለን። ቅሬታዎቻችንና እና ልዩነታቸውን አስወግደን ስርዓት በአለው መልክ በዴሞክራሲያዊ አሰራር ድርጅታችን አጠናክረን ብንወጣ ትግሉን ለውጤት ለማብቃት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል።
የትንሳኤ ንቅናቄ ጥረት አንድና ጠንካራ ኢህአፓ እንዲኖር ነው፤ በኢህአፓ ውስጥ የደረሰው መከፋፈል መሰረታዊ በሆኑ የመርህ ልዩነቶች የመጣ ሳይሆን ጓዶች በሰከነ መንፈስ በመግባባትና እንደቀድሞው በመተማመን ባለመወያየታቸው የተፈጠረ ችግር ነው ብለን እናምናለን። ስለዚህ መሰረታዊ ልዩነት በኢህአፓ ታጋዮች ማህል የለም እያልን አስታራቂ ሆነን መቅረብ አንችልም እኛም እራሳችን የሂደቱ አካል ነንና።

ይህ የአንድነት እንቅስቃሴ ሁሉንም የኢህአፓ ልጆች በማሰባሰብ ጠንካራ የሃገርና የህዝብ ሃይል እንዲሆኑ የማድረግ ጥረት በመሆኑ በትግሉ ውስጥ ያለፋችሁ ሃይሎች ሁሉ የኔ ጉዳይ ነው ብላችሁ ልትሳተፉበት ይገባል። ይህ ጥሪ ሀገራችን የገጠማት ችግር እንዲወገድላትና የሰላም፤ የፍትህ፤ የእኩልነትና የብልጽግና ሃገር እንድትሆን ለሚመኙ ወገኖች ሁሉ የሚቀርብ ጥሪ ነው። እንደገና እንዳንሰባሰብ ተጠናክረንም እንዳንወጣ ያልሆነ ቀለም የሚቀቡ ግለሰቦች ካሉ እባካችሁን ወደ ህሊናችሁ ተመለሱ ሁላችንም የምንኮራባቸው የተሰውት ጔዶች አጽም እና ደም ይፋረደናል እንላቸዋለን።
የኢሕአፓ መዳከምና መከፋፈል ለዘረኞችና ለጎጠኞች የልብ ልብ ሰጥቷል። ጠባቡም የወያኔ በድን ኢትዮጲያን እንደዘመነ መሳፍንት በጎሳና በጎጥ ከፋፍሎ ለማጥፋት ታጋዮችን ያስራል፡ይገድላል፡ይደበድባል፡ያሳድዳል፡ሲያስፈልግም ከጎረቤት አገሮች ጋር በመመሳጠር በማንአለብኝነት እስሮ ይወስዳል። ከዚህ በፊት ሱዳን በነበሩ ታጋዮች ላይ ያደረገውን በቅርቡ የመን ላይ በአቶ አንንዳርጋቸዉ ጽጌ ላይ አድርጎታል። የኢሕአፓ ልጆች ከተመክሮ እንደተማርነዉ አንድ ታጋይ መሰዋእትነት ሲከፍል በሺ ታጋዮች እንደሚተካ ስለምናውቅ የብዙሀን ድል ይገኛል በቆራጥ ትገል እያልን ድርጊቱንም በጥብቅ እናወግዛለን። እንዲያዉ ነገርን ነገር ያነሰዋልና በአረመኔዉ የደርግ መንግስት የታጋይ ጓዶቻችን እሬሳ መንገድ ላይ ዘርረዉ የዝንብ መጫወቻ ያደረጉትን ታላቁን ታጋይ ዮወሴፍ አዳነን አይኑን እየሸነቆሩ ቁዋንጃዉን እየቆረጡ የገደሉትን የፋሺስቱን ደርግ አባሎች ህይወት ወያኔ ሲያተርፍ ህይወታቸዉን በሙሉ ለህዝብ ሥልጣን ባለቤትነት እና ለዴሞክራሲ ሲታገሉ ሲወድቁ ሲነሱ የቆዩት ታጋዮች እነፀጋዬ ገ/መድህንን(ደብተራዉ)፡ እነ አበራሺ በርታን፡ እነ ስጦታዉ ሁሴንን ,,,ወዘተ የት እንዳደረሳቸዉ እስከ አሁን እንኩዋን አናዉቅም። ወያኔና የወያኔ መሪወችም ይህን ሚስጥር እንደያዙ አንዳንዶቹ እየሞቱ ቢሆንም ቀሪዎቹ ነገ በህዝብና በህግ ፊት ይጠየቁበታል።

አዎን የኢሕአፓ ጀግኖች ሙሾ ተወርዶላቸዉ፡ ደረት ተመቶላቸዉ፡ የስርዓተ ቀብር ተደርጎላቸዉ ባያዉቅም ያሞራ ቀለብ የዝንብ መጫወቻ ቢሆኑም፡ሰልፋቸዉ ከህዝብ ጋር ነዉና ሕዝብ ሲያሸንፍ ያን ግዜ ያን ቀን ታሪካቸዉ ይዘከራል። አሁንም ቢሆን ቀሪዉና ቀጣዩ ትዉልድ ሰንደቃቸዉን አንስቶ፡ መፈክራቸዉን አንግቦ በመታገል ከዓለሙት እና ከተሰዉለት ግብ ይደርሳል። በሕዝብ ሀይል የሚያምን ሁሉ ይህን አይጠራጠርም።ለዚህ ነዉ ትንሥኤ ኑ በቤታችን እንሰባሰብ ኑ እንታገል የትግላችን ጉዞ እንደ ኩሬ ዉሀ አንድ ቦታ ላይ ተገድቦ መንቀሳቀስ አልቻለምና መፍትሄ እንፈልግለት እያለ ጥሪውን የሚያቀርብ።
መሪነት ታላቅ ሀላፊነት እንደመሆኑ መጠን እንደ ሺልማት የሚሰጥ ገፀ በረከት አይደለም።ታግሎ ማታገልን ቀድሞ መገኛትን ከቂም ነጻ ሆኖ አርቆ አስተዋይነትን ይጠይቃል። “ከሊቀመንበር መንግሥቱ ጋር ወደፌት” ያሉትን ወይም በሙት መለስ “ራዕይ” የሚመሩትን ስናወግዝ ወደ ራሳችንም ዘወር ብለን እራሳችን ልንፈትሽ ይገባል። ከዚህ አንጻር በየትኛውም እርከን የታገላችሁና በመታገል ላይ ያላችሁ ጔዶች ሃላፊነታችሁን በአግባቡ እንድትወጡ አጥብቀን እንጠይቃለን።

ከዚህም ባሻገር የትንሥኤ ቡድን ህልም ኢሕአፓን አጠናክሮ ማውጣት ብቻ ሳይሆን ድርጂቱ እሱን ከመሳሰሉ ጠንካራ ድርጂቶች ጋር በመቀናጀት የጋራ ትግል እንዲያደርግም ይገፋፋል።ወቅቱ በጋራ መሥራትን አጥብቆ ይጠይቃልና።ሕዝቡም “ተባበሩ ወይም ተሰባበሩ” የሚለውን ጥሪ አሁንም እያቀረበ ነው፤ ለሕዝብ የሚሰራ ሁሉ የሕዝብን ድምፅ መስማት አለበት።በህዝብ ያልታቀፈና የሕዝብን ቃል የማያከብር ድርጂት ብቻዉን እነደቆመ ግንድ ነዉ። የሳለ መጥረቢያ በቀላሉ ይቆርጠዋል ለሕዝብ ለመቆም የሕዝብን ድምፅ መስማት፡የሕዝብን ፍላጎት ማወቅ፡ ያንንም ተግባራዊ ማድረግን ይጠይቃል። ያለሕዝብ ድጋፍ ድርጂት ሊኖር አይችልም።ድጋፉን የሚሰጥ ሕዝብ ድምፁን የማሰማት መብት አለዉ የድርጂት መሪወች ይህንን ተገንዝበዉ መተባባር አለባቸዉ እልህ ግትርነትና በድርጅት ውስጥ ለራስ ከፍተኛ ቦታ መስጠት የተከፈለውን መስዋእትነት ያበላሻል። ልዩነትን በነጻ መድረክ ተወያይቶ መፍታት የግድ ባህልና የውዴታ ግዴታ መሆን አለበት። አባላትም መሪዎቻቸውን መከታተል የድርጅታቸውን ፖሊሲ መመርመር ልዩነትን ከማራገብ ይልቅ አንድነትን ማጠናከር ይኖርባቸዋል። በዚህ ዙሪያ ያሉትን ድክመቶቻችን ካስወገድን ኢህአፓን በማጠናከር ተባብሮ በመስራት የሕዝብን ትግል ከግብ ማድስ እንችላለን ብለን እናምናለን።

ለዚህም የተቀደሰ አላማ ኢህአፓ የከፈለውን መስዋእትነት የምናከብር በኢሕአፓ ዙሪያ እንደገና ለመሰባሰብና ኢህአፓን አጠናክሮ እንደቀድሞዉ ቆራጥና የተባበረ ትግል ለማካሄድ ለምትፈልጉ ሁሉ የትንሥኤ ቡድን በድጋሚ ጥሪዉን ያቀርባል። ይህንም እንቅስቃሴ ተካፋይ ለመሆን የምትፈልጉ ሁሉ በነዚህ ኢሜል አድራሻወች ልትገናኙን ትችላላችሁ

TINSAE64@GMAIL.COM
ስለ ሀገር ፍቅራችሁ እና ቅን አመለካከታችሁ አስቀድመን እናመሰግናለን
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር

2007ን ለዴሞክራሲያዊ ለውጥ ሲባል እስከ ምርጫ ወይስ እስከ ዴሞክራሲያዊ መንግስት (ዳንኤል ተፈራ)

$
0
0

ዳንኤል ተፈራ

ዳንኤል ተፈራ — የአንድነት ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ሃላፊ

ዳንኤል ተፈራ — የአንድነት ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ሃላፊ

በጣም በቅርቡ አንድ ስላልነገርኩት ስሙን የማልጠቅሰው ጉምቱ የሚባል ጋዜጠኛ ወዳጄና ሌላ አንድ ጎልማሳ ጋር ኢ-ወጋዊ በሆነ መንገድ ስለተቃዋሚ ጎራው ማውጋት ይዘናል፡፡ የጨዋታችን መነሻ ደግሞ አንድነትና መኢአድ ከብዙ ውጣ ውረድና ድርድር በኋላ ከፍፃሜ ለማድረስ ደፋ ቀና እያሉበት ያለው ውህደት ነው፡፡ የተቃውሞ ፖለቲካውን በቅርበት እንደሚከታተሉ አንዳንድ ግለሰቦች አስተያየት ‹‹ውህደቱ መሳካት አዎንታዊ ጎን ቢኖረውም ዘግይቷል፡፡ በዚህ ጊዜ የውህደቱ ጣጣ አልቆ፣ የሚተባበሩት ተባብረው ወደ ሰፊ ህዝባዊ ንቅናቄ የሚገቡበት ነበር›› ይላሉ፡፡ የውህደቱ መሳካት ጥሩ ሆኖ ውህደቱም ሆነ ትብብሩ ዘለቄታ ላለው ዴሞክራሲያዊ ለውጥ ለማምጣት ወይስ ምርጫ ስለደረሰ ብቻ? የሚል ጥያቄ አንስቶ መመለስ ተገቢ ነው፡፡

ጎልማሳው ሰው ቀበል አድርጎ ለተቃዋሚው ጎራ ቅርበት አለው ብሎ ስላመነ ይመስለኛል አይኖቹን እንደ ቆመህ ጠብቀኝ መሳሪያ ፊቴ ላይ ወድሮ ‹‹በተቃውሞ ጎራው በኩል ተቀራርቦ፣ ተባብሮና ተዋህዶ የመስራቱ ነገር እምብዛም ባለመለመዱ ወይም እስካሁን ባለመሳካቱ ይመስለኛል ውህደት እንዳንድ አደረጃጀትን የሚያጠነክር የፖለቲካ ስራ ሳይሆን እንደግብ ይታያል፡፡ ከፖለቲካ ጠቀሜታ አንፃር ሳይሆን ከምርጫ፣ ከግል ጥቅምና ዝና አንፃር ይታል፡፡ ውህደት እንዳንድ የለውጥ ማምጫ ስትራቴጅ ባለመታየቱ በህዝቡ ዘንድ በጉጉት የሚጠበቅ ነው፡፡ መጠላለፍና ሴራ በብርቱ የሚያጠቃው የፖለቲካ ባህላችን ግን ‹‹እኔ ብቻ አዋቂ፣ እኔ ብቻ ንጉስ›› ከሚል ጨፍላቂ ሰርዓት ጋር ሲደመር ግራ ማጋባቱ ላይገርም ይችላል፡፡ በአጠቃላም የተቃውሞ ጎራውን ከአሮጌና ምርጫን ግብ ካደረገ አስተሳሰብ አላቅቀው የራሱ መነሻና መድረሻ ያለው ስትራቴጅ የሚነድፉ መሪዎች ያስፈልጉታል›› አለ፡፡

ጎልማሳው ሁለታችንም ዝም ብለን የልቋጨውን ሀሳብ እንዲጨርስ እየጠበቅነው እንደሆነ ሲረዳ፡- ‹‹ለነገሩ መምራት የሚችሉ ግለሰቦች ለመምጣት ቢሞክሩም በጥርጣሬና በሴራ ፖለቲካ ተስተካካይ የሌላቸው ግለሰቦች እንዲርቁ ያደርጓቸዋል፡፡ ከነሱ ተረፉትን ደግሞ ኢህአዴግ ‹‹አሸባሪ›› ብሎ ያስራል፡፡ ስለዚህ ውህደት ብቻ ሳይሆን ውህደቱን የሚመራ ጥብቅ መሪ ያስፈልጋል፡፡ ምርጫ ሞክሮ የሚሄድ ሳይሆን ከምርጫ ባሻገርም ለውጥ የሚመጣበትን መንገድ የሚቀይስ ብርቱ ሰው›› በማለት ሃሳቡን ጠቀለለ፡፡

ያነሳው ሃሳብ ጥቅል ቢሁንም ለውይይታችን ማጠናከሪያ መሆኑ አልቀረም፡፡ የጨዋታችንም ጭብጥ ሰፋና የተለያዩ ጋዜጦች ላይ ስለተቃዋሚው የሚፃፉትን አሉታዊ ትንታኔዎችን እያነሳን ነበር፡፡ የተቃዋሚ ጎራው መተቸት አለበት ወይስ የለበትም፤ ትችቱ ምን አይነት ቢሆን ለሀገር ይጠቅማል፤ ገዥው ፓርቲ ለተቃዋሚ ፓርቲዎች ምን አይነት ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል፤ ለምን? የሚሉ ጉዳዮችም ተነሱ፡፡ መቼስ ተቃዋሚው መተቸት የለበትም የሚል ድምዳሜ ላይ መድረስ አይቻልም፡፡ ኢህአዴግ ካቴና ይዞ የሚመጣው ‹‹ለምን ነካችሁኝ፤ ለምን ተቻችሁኝ›› ብሎ አይደል እንዴ? ታዲያ እንዴት አሁን ካለው ስርዓት የተሻለ ሀገር መምራት እችላለሁ ብሎ እየታገለ ያለውን ተቃዋሚ አይነካ ማለት ይቻላል? እያልን ስናነሳ ጋዜጠኛው ወዳጄ የተቃውሞ ጎራ አሁን ባለበት አቋም የሚያስፈልገው ገንቢ ትችት ነው የሚል ነገር ዱብ አደረገ፡፡ በድማሜ ውስጥ ሆኜ ‹‹ለምን?›› የምትል ቤሳ ጥያቄ ማቅረቤ አልቀረም፡፡ እሱም እንዲህ መለሰልኝ፡፡

‹‹አየህ ተቃዋሚው ባጠቃላይ ከአፈጣጠሩ በርካታ ችግሮች ያሉበት ነው፡፡ ኢህአዴግ የሚፈጥረው ችግር ደግሞ ብዙ ነው፡፡ ለባለፉት 23 ዓመታት ተቃዋሚው በተበታተነ አሰላለፍ፣ ምርጫን ብቻ ግብ አድርጎ ቆይቷል፡፡ ይህ አሰላለፍም ዘላቂነት ላለው ድልና የማይናድ የተቃዋሚ ግንብ ለመገንባት አላስቻለውም፡፡ ግልፅ ራዕይና ስትራቴጅ በማስቀመጥ፣ ተተኪ ፖለቲከኞችን በማፍራትና በውስጡ ተሰግስገው እንደ አሜባ የሚራቡትን ሰርጎ ገቦች ማጥራት አልቻለም፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ኢህአዴግ ‹‹ተቃዋሚዎች እግር እስከሚያወጡ መጠበቅ ተገቢ አይደለም›› በሚለው የተበላሸ አመለካት የተነሳ ከፍተኛ ወጭ መድቦ ተቃዋሚ ጎራውን በአይነ ቁራኛ ይጠብቃል፡፡ ከተራ ስም ማጥፋትና በውስጥ ክፍፍል ለመፍጥር ከመስራት ጀምሮ እስከ ‹‹ሽብርተኛ›› ብሎ እስከማሰር የደረሰ መዋቅር ዘርግቷል፡፡ ስለዚህ አሁን መሆን ያለበት ተቃዋሚውን ሃይል መተቸት ሳይሆን  መደገፍ ነው፡፡ በህጋዊ መንገድ ተመዝግቦ፣ በሰላማዊ ትግል አምኖ እየታገለ ያለን ሃይል እንደ ጠላት የሚቆጥር መንግስት ባለበት ሀገር፤ ተቃዋሚው የስብሰባ አዳራሽ፣ የሚከራይ ቢሮ ለማግኘት በሚቸገርበት ሁኔታ፤ አባሎቹን እየተከታሉ ‹‹ወይ ከስራህ አሊያም ከተቃውሞህ አንዱን ምረጥ›› በሚባልበት ስርዓት ውስጥ ቀዳሚው ነገር ተቃዋሚውን መተቸት ሳይሆን ተቃዋሚው እግር እንዲያወጣ ማገዝ ነው፡፡ እግር አውጥቶ የቡጢ ሚዛኑ ሲስተካከል ግን ገንቢ ትችት ብቻ ሳይሆን አሁን ኢህአዴግ በሚተችበት ደረጃ መተቸት ነው›› የሚል ትንሽ ትንታኔ አቀረበ፡፡

በርግጥ በጋዜጠኛው ወዳጄ በጎ ሃሳብ የሚስማሙም የማይስማሙም ይኖራሉ፡፡ አንዳንዶች መጠንከርም ሆነ መልፈስፈስ የተቃዋሚው የራሱ ምርጫ ነው የሚሉ አጋጥመውኛል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ተቃዋሚው ጠንካራም ሆነ የተልፈሰፈሰ እንዲሆን የሚያደርገው ህዝቡ ሊሆን ይገባል የሚሉም አሉ፡፡ የፖለቲካ ፓርቲ የሚቋቋመው ለህዝብና ለሀገር አገለግላለሁ ተብሎ ነው ስለዚህ ባለድርሻው ህዝብ ከሆነ ጠንካራ ለሚለው ድጋፍ በመስጠትና በአጉል አቅጣጫ ለሚነጉደው ትብብር በመንፈግ ለተቃዋሚው አቅም ሊፈጥር ይችላል፡፡ እኔም አዳምጨ ሳበቃ ይህንን ሃሳብ ተመርኩዤ የራሴን ምልከታ ለመሰንዘር ወደድሁ፡፡

‹‹ጋንግስተሪዝም››

አስቀድሞ ትውስ ያለኝ ጋንግስተሪዝም ነው፡፡ ለሀሳቤ መነሻ ሆነኝ ጋዜጠኛ ዮናስ በላይ በቅርቡ ያሳተመው ‹‹የትግራይ ሕዝብ፤ ወያኔዎቹና ሽፍቶቹ›› የሚለው መፅሀፍ ነው፡፡በመፅሐፉ በ1993 ህወሃት ለሁለት ስትሰነጠቅ መሰረታዊ ልዩነቶች ምን እንደነበሩ ስብሃትን ጠይቋቸው ሁለት ነገር አስቀምጠዋል፡፡ በተለይም በኤርትራ ጉዳይ አንደኛው እነ ስየ መለስን ‹‹ተንበርካኪ ሆናችኋል›› የሚል ሲሆን የነ መለስ ቡድን በበኩሉ በመልሶ ማጥቃት ተንበርካኪነትን ባለመቀበል ዴሞክራሲያዊ አመለካከት ጠፍቷል ‹‹ጋንግስተሪዝም›› እያደገ ነው በማለት ለመመከት ተገድደዋል፡፡ የፖለቲካ ጉዳይ ስለሆነ እንጅ እነ መለስ ለዴሞክራሲ ተጨንቀው እንዳልሆነ አሁን ያለው ተጨባጭ ሁኔታ ምስክር ነው፡፡ ጋንግስተሪዝም በተገላቢጦሽ በክፍፍሉ አሸናፊ ሆኖ የወጣው የነ መለስ ቡድን መለያ መሆኑ ፈገግ ያሰኛል፡፡

ጋንግስተሪዝም (ቦዘኔነት) ዋናው የተቃዋሚ ጎራ ችግርም ነው፡፡ ቦዘኔዎች ዋና ተግባራቸው ስራ መስራት አይደለም የሚሰሩትን እየተተከተሉ ማጥቃት እንጅ፡፡ አሁን ያለው ወጣት ትውልድ ግን ከጋንግስተሪዝም ይልቅ ዴሞክራሲ ልዩ መለያው እንደሆነ መመስከር ይገባኛል፡፡ ጋንግስተሪዝም በዋናነት የአባቶቻችን ትውልድ መለያ ነው ብሎ መከራከር ይቻላል፡፡ የሃሳብ ልዩነትን በውይይት ከመፍታት ይልቅ ማጥፋት የተለመደ ነው፡፡ በተቃዋሚው ጎራም አባራሪና ተባራሪ አለ፡፡ ‹‹የተቃዋሚዎች እናት አንድ ናት›› እንዲል አስራት አብርሃም በቅርቡ እንኳን ታዋቂውን ፀሃፊና ፖለቲከኛ አስገደንና ሌሎችን አረና አባሯል፡፡ አረና ወደ ማባረሩ የገባው ሌላው በአጭር ጊዜ በፖለቲካ ስራውና በሚያቀርባቸው ፅሁፎቹ እውቅና ያተረፈው አብርሃ ደስታ ከታሰረ በኋላ ነው፡፡ ታዲያ የተያዘው ማጠናከር ወይስ ማላላት? ፕሮፌሰር እንዳሉት የስላሴዎች እርግማን ይሆንን? አደህይቶ መግዛት፤ አጎሳቁሎ ተስፋ ማሳጣት፤ ባዶ ማድረግ፡፡ ጋንግስተሪዝም፡፡ ይሄ የትውልድ ውልቃት መጠገን አለበት፡፡ ቅድሚያ ለውጥ ፈላጊነት ጋንግስተሪዝምን ማሸነፍ አለበት፡፡

በመቀጠል የተቃውሞ ጎራው ከተከላካይነትና ከተጠቂነት ወደ አጥቂነት የሚሸጋግርበትን የፖለቲካ ስትራቴጂ የሚነድፍ መሪ ያፈልገዋል፡፡ ትግሉን ከምርጫ ፖለቲካ በላይ አሻግሮ የሚመለከትና የኢህአዴጋውያኑን የጠቅላይ አምባገነንነት አባዜ ተረድቶ የመስበሪያ ስልት የሚቀይስ የፖለቲካ ማሃንዲስ መፍጠር ይገባል፡፡ የተቃውሞ ጎራው እስካሁን በመጣበት መንገድ ከፍተኛ መስዋዕትነት ተከፍሎበታል፡፡ አሁንም ስለለውጥ ከፍተኛ ዋጋ ዕየተከፈለ ነው፡፡ ነገ ትልቅ መሪ የሚሆኑ የኢትዮጵያችን ተስፋዎች ጨለማ ክፍል ውስጥ ተጥለዋል፡፡ እነ አንዷለም አራጌ፣ ኦልባ፣ በቀለ ገርባ፣ ሀብታሙ አያሌው፣ ናትናኤል መኮንን፣ የሽዋስ አሰፋ፣ አብርሃ ደስታ፣ ዳንኤል ሺበሺና ሌሎች በፖለቲካ እምነታቸው ብቻ ወደ ጨለማ ክፍል የተወሰዱ ዜጎች የከፈሉት ዋጋ ፍሬው መታየት አለበት፡፡ ይህ ሊሆን የሚችለው ደግሞ ምርጫ ስለደረሰ ብቻ ሱፋቸውን አሳምረውና ጫማቸውን ወልውለው ከተቻለ ፓርላማ፤ ካልተቻለ ደግሞ ሌላ አምስት አመት እስከሚመጣ እቤታቸው በሚቀመጡ ፖለቲከኞች አይደለም፡፡ ለውጡ ሊመጣ የሚችለው ያለ ፋታ በሚሰሩ ለውጥ ፈላጊ ሃይሎች እንጅ፡፡

ጋንግስተሪዝምን (ቦዘኔነትን) አሸንፎ ምርጫ ካለና በአግባቡ ከተጠቀሙበት የለውጥ ማምጫ መሳሪያ ነው፡፡ አሁን ያለው ገዥ ፓርቲ ፍትሃዊ ምርጫ ለማካሄድ ቁርጠኝነቱ አለው ተብሎ አይገመትም፡፡ ነገርግን የተቃዋሚው ስራስ ምን መሆን አለበት? አፋኝነቱን ከመተንተን ያለፈ የማስገደድ ሃይል ያለው ጡንቻ ያስፈልገዋል፡፡ በምርጫው መሳተፍ ይገባል ወይስ አይገባም፤ ብንሳተፍ ምን ምቹ ሁኔታዎች አሉ፤ ምን ተግዳሮቶች አሉ፤ በአማካይ ስንት ወንበር አሸንፈን ስልጣን መያዝ እንችላለን፤ ምርጫው ኢፍትሃዊ እንዳይሆን ምን ምን ርምጃዎች መወሰድ አለባቸው፤ ህዝቡን የማንቂያ ስትራቴጅዎች፣ ህዝባዊ ንቅናቄ የመፍጠሪያ ስልቶች፣ የችግር አፈታት ስልቶችና የታሰሩ አመራሮች ለምርጫው ያላቸው አጋርነት መፈተሽ ይገባል፡፡

በአመራር ደረጃም በምርጫው ተቃዋሚ ጎራው ሞካሪና አዳማቂ ሆኖ ሳይሆን አሸናፊ ሆኖ የሚወጣበትን ስትራቴጅ የሚነድፉ፤ የተነደፈውን ስልት ወደ ውጤት የሚቀይሩ የኦፕሬሽን ሰዎች፤ ይህንን የሚደግፉና የሚያሰርፁ አባላት በብዛት ያስፈልጋሉ፡፡ የዚህ ፅሁፍ አቅራቢዎ አንደታዘበው ግን በተቃውሞ ጎራው ስለ ግልፅ የማሸነፊያ ስትራቴጅና ስለ ስልት እምብዛም አይወራም፡፡ ሕዝቡ ካለበት የኑሮ ጫና፣ የነፃነት እጦትና የስርዓቱ ሹማምንት ከሚያደርሱበት ምሬት አንፃር የተቃውሞ ጎራውን በስፋት ይደግፋልና ይመርጣል የሚለውን ግምት በተግባር መፈተሽና በአግባቡ የዚህን የተገፋ ህዝብ ይሁንታ የሚያገኙበትን ተክለ ቁመና መፍጠር ያስፈልጋል፡፡

ዞሮ ዞሮ ከላይ ለመግለፅ በሞከርኩት መንገድ የተቃውሞ ጎራው ከውህደት ባሻገር ከአመራር አንፃርና አጠቃላይ ትግሉ ያለበትን ነባራዊ ሁናቴ ፈትሾ፤ የሚፈለገውን ቁርጠኝነት አሳይቶ ለውጥ ከማምጣት አንፃር መሰራት እንዳበት አንስተን የኢ-ወጋዊ ውይይታችን ማጠቃለያ የሆነው በሚቀጥለው ዓመት ይካሄዳል ተብሎ የሚጠበቀው ሃገራቀፍ ምርጫ ነበር፡፡ (በነገራችን ላይ ምርጫ፣ ምርጫ ስል ምርጫ አለ እንዴ! በ2002 ምርጫ ተደርጎ ነበር እንዴ! በማለት ታማኝነትን ያተረፈ ምርጫ ካልተደረገ እንደተደረገ አይቆጠርም በማለት ጠንከር ያለ መከራከሪያ የሚያቀርቡ እንዳሉ ሳይዘነጋ ማለት ነው) በአንፃራዊነት ጠንካራ የሚባሉ ፓርቲዎች 2007ን እንዴትና ለምን ግብ ሊጠቀሙበት እያሰቡ ነው? ምርጫውን ለመሞከር ወይስ ዘለቄታዊ ጠቀሜታ ላለው ዴሞክራሲያዊ ለውጥ ለማምጣት? የሚለው ዋና ጥያቄ ነው፡፡

የምርጫ ጊዜ ወፎች

ከጋንግስተሪዝም ለጥቆ የሚመጣው የምርጫ ግርግር ፈጣሪው ነው፡፡ ስለ ሰላማዊ ትግል ስናስብ ስለ ውጤትም ማሰብ ይገባል፡፡ ኢህአዴግን ብቻ ሳይሆን እንደ መስቀል ወፍ ምርጫና የምርጫ ወሬ ሲሰማ የሚሉትን የምርጫ ጊዜ ወፎች መታገል ይገባል፡፡ የነዚህ ወፎች ግብ ከላይ እንደገለፅኩት ዘለቄታዊ ለውጥ በማምጣት የሚፈለገውን ዴሞክራሲ መገንባት አይደለም፡፡ ዘላቂነት ያለው የለውጥ ስሜትም ሆነ ስትራቴጅ ስለሌላቸው በምርጫ ጊዜ ብቻ ብቅ ይሉና ‹‹ሲያቃጥል በማንኪያ ከበረደ በእጅ›› የምትል የጮሌ ስትራቴጅ በመያዝ ምርቻ ላይ ለመሳተፍ የሚፈልጉት ናቸው፡፡ እነዚህ ሃይሎች ካራባት በማሳመር ምርጫ ማሸነፍ ይቻል ይመስል ‹‹የ2007ን ምርጫማ መሞከር አለብን›› ይላሉ፡፡ መሞከር ብሎ ትግል፡፡ ሰው የሚወዳደረው ለመሞከር ሳይሆን ለማሸነፍ ነው፡፡ የምርጫ ጊዜ ወፎች ግን ‹‹ኸረ እባካችሁ ህዝብና ሃገር መሞከሪያ አይደለም፤ ኢህአዴግ በዚህ ጭቁን ህዝብ ላይ የሞከረበት ይበቃል፤ ዘላቂነት ያለው ስትራቴጅና ራዕይ ካላችሁ ወዲህ በሉ›› ሲባሉ ያኮርፋሉ፡፡ ይፈርጃሉ፡፡ ያችኑ የሚውቋትን የሴራ ጨዋታ ከች ያደርጓታል፡፡ ያ የፈረደበት ምርጫ 97 ይጠቀስና ‹‹ስንት ዋጋ ከፍለን፤ ደማችን ፈስሶ አጥንታችን ተከስክሶ…›› የምትል ‹ፉከራ› በማምጣት ጉዞ ወደ ምርጫ ሙከራ ይሆናል፡፡

ዋናው ቁምነገር የተከፈለውን ዋጋ ለማሳነስ አይደለም፡፡ በ97 ደግሞ የስርዓቱን አስከፊ ገፈት ያልቀመሰና ዋጋ ያልከፈለ የለም፡፡ ዳሩ ግን ከታሪክ መማር እንጅ በታሪክ መኖር አይቻልም፡፡ በታሪክ መኩራት እንጅ በታሪክ ማሸነፍ አይቻልም፡፡ ማሸነፍ የሚቻለው ዛሬ ላይ አቅዶ፣ እቅዱን ወደ ተግባር ለውጦ፣ ህዝቡን አሳትፎ መጓዝ ሲቻል ነው፡፡

አንድነትና መኢአድ ጀምረውታል፡፡ ቢያንስ የሁለቱን ትላልቅ ፓርቲዎች ሃይል በአንድ መስመር ማስገባት የሚቻልበት ታሪካዊ ስራ ነው፡፡ ግን በቂ አይደለም፡፡ አሁንም ዳርላይ የቆሙ ፓርቲዎች አሉ፡፡ የተናጠሉ ጉዞ አያዋጣም እየተባለ ነው፡፡ 2007ን በአግባቡ ለመጠቀም የተሰባሰበ አንድ የተቃውሞ ሃይል መፍጠር አንዱ ነው፡፡ ለዚህ ትልቅ የተቃውሞ ሃይል የሚመጥንና ወደ ፊት የሚያራምድ አመራርም ያፈልገዋል፡፡ የምርጫ ጊዜ ወፎች ምርጫ መግባትን እንደ ግብ ስለሚያዩ ከተቻለ ትግሉ ምርጫ የመሞከር ሳይሆን ትግሉ እየተካሄደ ያለው ለውጥ ለማምጣትና ለትልቋ ሀገራችን የሚመጥን ዴሞክራሲያዊ ስርዓት የማስፈን ስለሆነ ወደ ትክክለኛ መስመር እንዲገቡ ማድረግ ነው፡፡ አልገባም ካሉ እነሱንም መታገል ነው፡፡

የዚህ ፅሁፍ አቅራቢዎ በድጋሚ እንደታዘበው አሁን በተቃውሞ ፖለቲካው ውስጥ ሁለት አይነት የውስጥ ትግል እየተካሄደ ነው፡፡ ይሄ ትግል የሚካሄደው በለውጥ ፈላጊ ሃይሎችና (ይሄ በብዛት የወጣቱን ቀልብ የሳበ ይመስላል) በቀደመው መንገድ ማዝገም በሚፈገልጉ፣ የኢትዮጵያን ፖለቲካ ከእኛ በላይ ላሳር ብለው የሚምኑ፤ ነገርግን በተግባር ውጤት ያላስመዘገቡ ሃሎች መካል ነው፡፡ በዚህ መልኩ መታገል መብት ነው፡፡ ፖለቲካ ውስጥ የውስጥ ትግልና የውጭ ትግል መኖሩ የተለመደ ነው፡፡ የሚዳኘው ግን አባላትና ህዝቡ ይሆናል፡፡

የግል ይዞታነት

በመጨረሻ ማንሳት የምፈልገው ትግሉን ፍሬያማ ለማድረግ እንቅፋት እንደሆነ የሚታመነው የግል ዞታ አመለካከት ነው፡፡ አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ ከምርጫ ባለፈ የምንመለከት ከሆነ በተቃዋሚ ጎራው የሚታየውን ፓርቲን እንደግል ንብረት የመመልከት ዝንባሌ ማጥራት ያስፈልጋል፡፡ በትግል ውስጥ ዋጋ መክፈል ማለት ፓርቲውን የግል ንብረት ማድረግ ማለት አይደለም፡፡ ከላይ እንደጠቀስኩት ፓርቲ የሚቋቋመው ለህዝብና ለሀገር የሚጠቅም ርዕዮተ ዓለምና የማስፈፀሚያ ስልት ይዞ እሱን ተግባራዊ ለማድረግ እንጅ የግል ዝናና ሞገስ ለማግኘት አይደለም፡፡

እኔ አይነኬ ነኝ የሚሉ እንዳንድ ግለሰቦች ‹‹እኔ አንደዚህ፣ እንደዚህ አድርጌ በመሰረትኩት ፓርቲ…›› የምትል መከራከሪያ ሲያቀርቡ ይሰማል፡፡ ፓርቲ ውስጥና ፖለቲካ ውስጥ ‹‹እኔ›› የምትል የግለኝነት ሃሳብ መነሳት ከጀመረች ህዝብና ሀገር ተዘንግቷል ማት ነው፡፡ ፓርቲን እንደ ግል ዞታ መመልከት የሚመጣው እኔ ከሚል ያልተባረከ ሃሳብ ነው፡፡ ማንም ሰው ማወቅ የሚገባው ወደ ኢትዮጵያ የተቃውሞ ፖለቲካ የሚመጣው ሊሰጥ እንጅ ሊቀበል አይደለም፡፡ ፖለቲካ ውስጥ ገብቶ መስጠት ሳይሆን መቀበል የሚፈልግ ካለ ወደ ኢህአዴግ ዘንድ ቢሄድ ውጤታማ ይሆናል፡፡ ተቃዋሚው ጎራ ያለው ግን መስጠት ብቻ ነው – ያውም ክቡር የሆነውንና የመጨረሻ ውዱን ህይወት፡፡ ስለዚህ በተቃውሞ ጎራ ያለውን የግል ይዞታ አመለካከት መታገል ወደሚፈለገው የለውጥ ግብ ያደርሳል፡፡

ለማጠቃለልም አሁንም ከፊት ለፊታችን የሚጠብቀን ሀገራቀፍ ምርጫ አለ፡፡ በኢህአዴግ በኩል ግልፅ የሆነ  የመጠቅለል አካሄድ እየታየ ነው፡፡ ይህንን የአፈና አካሄድ መስበር የሚቻለው የምርጫ ግርግር ውስጥ በመግባት ወይም ለመሳተፍ በመጓጓት ብቻ አይደለም፡፡ በቅድሚያ ምርጫ እንዲኖር መታገል ያስፈልጋል፡፡ 2007ን ለዴሞክራሲያዊ ለውጥ መጠቀም የሚቻለው እስከ ምርጫ ብቻ በማሰብ አይደለም፡፡ ከምርጫ ባሻገርም ተቃውሞ ጎራው ላይ አስተማማኝ መሰረት ጥሎ ዴሞክራሲያዊ መንግስት መመስረቱም ሊታሰብበት ይገባል፡፡ ሁለንተናዊ ችግሮችን ፈትሾ፣ አካዶችን በግልፅ ተችቶ መድረሻ ጎል ማስቀመጥ፡፡ አዎ ጊዜው እየሮጠ ነው፡፡ ህዝቡም የተጫነበት ቀንበር ከብዶታል፡፡ ስለዚህ በዚህ ልክ መሮጥ ያስፈልጋል፡፡ ጎበዝ እንሩጥ፡፡


“ያልተሄደበት መንገድ” –ሊነበብ የሚገባው ድንቅ መጽሐፍ! (ነፃነት ዘለቀ)

$
0
0

ነፃነት ዘለቀ
freeandualemaragie.org

ይህን የአንዱአለም አራጌን በራሱ አገላለጽ ከጠባቧ የቃሊቲ እስር ቤት የተጻፈ ግሩም መጽሐፍ ሳነብ የተሰማኝን ስሜት ባጭሩ ለመግለጽ እንጂ ሥነ ጽሑፋዊ ደንብ የተከተለ ሂስ ወይም የመጽሐፍ ግምገማ ለመስጠት አለመነሳቴን መግለጽ እፈልጋለሁ – መሆኑን እንዴት ከረማችሁ?

ከሁሉ በፊት ግን ከሰሞነኛ ጉዳዮች መካከል ቂላቂሉ ወያኔ በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ላይ የሠራውን አስቂኝ ድራማ ስመለከት እያዘንኩ የታዘብኩትን በዓለም ወደር የማይገኝለት ምርጥ የምርመራ ውጤት በሚመለከት ትንሽ ልበል፡፡

Yeltehedebet Menged

የኢትዮጵያን ቴሌቪዥን በውነቱ አልመለከትም፤ አለመመልከቴ ስህተት መሆኑ ቢገባኝም ጤንነቴን አጥብቄ ስለምፈልገው ይሁነኝ ብዬና ቁም ነገር አገኝበታለሁ ብዬ ኢቲቪን አላየውም – ብዙዎች እኔን መሰሎች ስላሉ “የዐዋጁን በጆሮ” እንዳትሉኝ እንጂ፡፡ የሆኖ ሆኖ በቀደምለታ ከሰዎች ጋር የሆነ ቦታ ቁጭ ብዬ ቁርስ ቢጤ ስንቀምስ በፖሊስ ፕሮግራም የተከታተልኩት በዓይነቱም ሆነ በይዘቱ ድንቅ የሆነ የወያኔ የወንጀል ምርመራ ቴክኒክና ውጤት ያጫረብኝን ልዩ ስሜት በዚህ አጋጣሚ ሳላነሳው መቅረት አልፈለግሁም፡፡ ከእውነት ሰው መሆኔን ጠላሁ፡፡

“መርማሪው” ወያኔ አይታይም፤ ይህን የለመድነው ነው፡፡ ወያኔዎች ራሳቸውን እንደወንጀለኛ አድርገው ስለሚቆጥሩና ከአልቃኢዳ ጋር የሚያመሳስሏቸውን ድርጊቶች የሚፈጽሙ መሆናቸውን ሕዝቡ የተረዳው መሆኑን ስለለተገነዘቡ ይመስለኛል የመንግሥትን ሥልጣንና ኃይልም የጨበጡ “ምሁራኑ መርማሪዎች” በግልጽ በሚዲያ መታየትን የሚወዱ አይመስሉም ፤ እነዚህ ጭራቅ ገራፊዎችና ሀዘን አምላኪዎች (ሳዲስቶች) በራሳቸውም በመንግሥታቸውም የሚተማመኑ እንዳልሆኑና በሆዳቸውና በዘረኝነት ቁርኝታቸው ብቻ ተለክፈው በስሜት ፈረስ የዕውር ድምብር ግልቢያ ዜጎችን የሚያሰቃዩ ናቸው – ቀናቸው ሲደርስ ምን እንደሚውጣቸው ፈጣሪ ብቻ ነው የሚያውቀው፤ አሣር አለባቸው – የቁናው ሥፍር እየተንደረበበ ይጠብቃቸዋል – እዚህ ወይም እዚያ፡፡ ከሞራል ዕሤቶቻችንና ከምርመራ ህግ በወጣ ሁኔታ አቡበከር የሚባለውን የሙስሊም ተቃውሞ አመራር አባል እጆቹን በእጀሙቅ አስረው የሚያካሂዱትን “ምርመራ” በአደባባይ በቲቪ ለዓለም ሕዝብ ሲያሳዩም “መርማሪው ሊቅ” መታየትን አልወደደም – አስጠሊታ ሣቁ ግን ከአንጀቱ ጥርስ ሳይሆን ከማተብ የለሽ አንገቱ ይሰማ ነበር፡፡ ስለዚህ የአንዲ ልዩነት እጆቹ አለመታሰራቸው እንጂ ሂደቱ ልክ እንደአቡቦከር ነው፡፡ ይህ የምርመራ ሂደትና ውጤቱ የሀገራችን የለየለት ውርደትና የወያኔን ማንአለብኝነት ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው፡፡ ወያኔዎች ከግዑዝ ድንጋይ የማይሻሉ የመጨረሻ ደደቦች መሆናቸውን ምናልባትም ለሚሊዮንኛ ጊዜ የገለጡበት ማፈሪያ ድርጊት ነው፡፡ የሚታዘነው በተመርማሪዎቹ ሳይሆን በመርማሪ ተብዬዎቹ ነው፡፡ ከመነሻው የዘረኝነት ልክፍት ያሽመደመደውና ከዘር ማዕቀፍ ውጭ የማያስብ ደንቆሮ ማይምና ሳዲስት እንዴት አንድን የተማረን ሰው ይመረምራል? እንዲያው ትንሽም ቢሆን የተማረ ዘረኛ ወያኔ ጠፍቶ ነው ወይ? ይህ ዓይነቱ የአደባባይ ግፍ ሄዶ ሄዶ የሚያስከትለውን መዘዝ እንዴት አጡት? ድንቁርና ይህን ያህል በጀብደኝት ያሳውራል?

ወደአስቂኙ ድራማ ልለፍ፡፡ አንዳርጋቸው በ“ነፃ ኅሊናው” የሰጠውና ለኢትዮጵያ ሕዝብ በደናቁር የወያኔ ወንበዴዎች እሳቤ ሊተላለፍ የተፈለገው መልእክት ይህን ይመስላል፤ “የግንቦት ሰባት ኅልውና ከእንግዲህ ግፋ ቢል ለሁለት ወራት ቢዘልቅ ነው፤ ወዲያም አለ ወዲህ ዕድሜው ከሁለት ወር አይበልጥም፡፡ የአውሮፓና አሜሪካ ምቾቱን ትቶ እንደኔ በረሃ ወርዶ የሚያታግል ቆራጥ ሰው አይኖረውም፡፡…”  የግንቦት ሰባት ቀሪ ዕድሜ ሁለት ቀንም ይሁን ሁለት ወር እሱ ሌላ ጉዳይና ወደፊትም የሚታይ ሆኖ ይህን የተናገረው ግን አንዳርጋቸው ጽጌ መሆኑን ልብ ይሏል – አንዲን በሚዲያም ቢሆን ባላውቀው ኖሮ ከአሁን በፊት “የተናገረውን”ና ገና ወደፊት “እንደሚናገረው በጉጉት” የሚጠበቀውን ሁሉ በበኩሌ ሳላንገራግር በሙሉ ልቤ አምኜ በተቀበልኩና ከወያኔ የሸፈተውን ልቤን ወደወያኔ በመለስኩ ነበር – ይህ ሁሉ ድካማቸው ታያ የማንን ቀልብ ለመሳብ ? በመሠረቱ እስካሁን ወያኔ የነበረ በአንዳርጋቸው ንግግር ምክንያት የወያኔነት ደረጃው አይጨምርም – በተቃራኒውም እስካሁን ወያኔ ያልነበረ በዚሁ የአንዲ ንግግር ምክንያት ንዴቱና ቁጭቱ ይጨምርና ወደድርጊት ይገባ እንደሆነ እንጂ ከተቃዋሚነቱ የሚያፈገፍግ አይመስለኝም፤ እናም የወያኔዎች የጅልነት ምጥቀት ያሳዝነኛል ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያውያንንና ዓለምን በጠቅላላው እስከዚህን ያህል መናቃቸው ምን ያህል ወራዳዎች – እደግመዋለሁ ምዕመናን – ምን ያህል ወራዳዎች መሆናቸውን ከማሳየት በስተቀር የአንዲ ስቃይና የሙሌት ኑዛዜ የሚጨምርላቸው አንዳችም አወንታዊ ነገር የለም – ይህን ነባራዊ እውነት ለመናገር ደግሞ የክር ወይም የሃቂቃ ጉዳይ እንጂ የግንቦት ሰባት አባልም ሆነ ደጋፊ መሆንን አይጠይቅም፡፡ የወያኔዎችን ውስጠ ምሥጢርና የግፍ ታሪክ በየመድረኮች ሲዘከዘክ ሚሊዮኖችን በዕንባ ሲያራጭና በትካዜ ባህር ሲያሰምጥ የምናውቀው አንዳርጋቸው ጽጌ በምትሃታዊ ፍጥነት ወደማፊያው መንግሥት ተገልብጦ ተናገረው የተባለውን እንዲያ ሲናገር ይታያችሁ፡፡ የምናውቀው አንዳርጋቸው የምናውቅለትን ጽኑ ፀረ-ወያኔ አቋሙን በሻጥርና በብዙ ገንዘብ ክፍያ በየመኖች ተይዞ በወያኔዎች እጅ በገባ በሁለት ሣምንታት ጊዜ ውስጥ ሲለውጥ በዐይነ ኅሊናችሁ ይታያችሁ፡፡

ግሩም የምርመራ ውጤት! ዓለምን የሚያስደምም ሣይንሳዊ የወንጀል ምርመራ ግኝት! በዚህ በአንዳርጋቸው ቃልና የመከራ ኑዛዜ ማፈር ያለበት ቀደም ሲል ለመጠቆም እንደሞከርኩት ወያኔ ብቻ ነው፡፡ ከወያኔ ውጭ ማንንም ሊያሳፍር አይችልም፡፡ እንዲያውም እኔ ብሆን ኖሮ “ግንቦት ሰባት የሚባል ድርጅት ከነአካቴው በሕይወት አለ እንዴ? አሁን እናንተ ስትሉ ሰማሁ፡፡ ማን ተናገር እንዳለኝ አላውቅም ዝም ብዬ ነበር እኮ በኢሳት ያንን ሁሉ ንግግር የምዘባርቀው፡፡ ደግሞ ብርሃኑን ብሎ ግንቦት ሰባት! ከመነሻው ግንቦት ሰባት ብሎ ነገር ሲኖር አይደለም ወርቆቼ! …” ብዬ አስደስታቸው ነበር እንጂ የሌለን ምሥጢር ለመደበቅ በመሞከር ሰውነቴን ለስቃይ አልዳርግም – ሊያውም በዚያ ኑዛዜየም ስቃዩን ቢቀንሱልኝ አይደል? ግን አይቀንሱልኝም – ስለዚህ ብናገርም ባልናገርም ለውጥ የለውም፤ ጠባችን በደም የሚጠራ እንጂ በውሃ ታጥቦ የሚጸዳ አይደለምና፡፡

እንደውነቱ ታዲያ አንዳርጋቸው ሊሰጠው የሚችለው የማይታወቅ የተከደነ አዲስ ምሥጢር ሊኖር ይችላል? ሁሉም ነገር እኮ ግልጽ ነው፤ ወያኔ የሚባል ሀገር አጥፊና ፀረ-ሕዝብ የሆነ የማፊያዎች ቡድን አራት ኪሎ ቤተ መንግሥት ውስጥ መሽጎ አለ – እሱን ለማስወገድ ደግሞ ዜጎች በተበታተነ ሁኔታም ቢሆን በየፊናቸው ጥረታቸውን እያደረጉ ነው፤ ምሥጢር ከተባለ ይህ ነው ምሥጢሩ፡፡  አንዳርጋቸው የትግል መስመሩ ስላበሳጫቸውና እየሠራ ያለው ነገር ለኅልውናቸው አስጊ ሆኖ ክፉኛ የሚያሳስባቸው በመሆኑ እርግጥ ነው እሱን ከመድረክ ገለል እንዲል ማድረግ ቢፈልጉ ያንን መቀበል ይቻላል – ሰይጣናዊ ፍላጎታቸውን ለማርካት የሄዱበት ርቀት ብዙ የሕግና የሞራል ችግር ማስነሳቱ እንዳለ ሆኖ፡፡ ከዚያ ውጪ ምሥጢር አውጣ ብሎ የዓለማችን ቤት ባፈራው የማሰቃያ ዘዴ ሁሉ ሰውን ማሰቃየት፣ በዚያም ሂደት ራስን ለትዝብትና ለስላቅ የሚያጋልጥ ነውረኛ የምርመራ ሂደት ማካሄድና ተመርማሪዎች የማያምኑበትን ነገር እንዲናገሩ ማድረግ በእግረ መንገድም “በሰላም አንገዛም፣ አንገብርምም ያሉንንና ሕዝብን የሚያሳምጹብንን ቀንደኛ ጠላቶቻችንን ‹እንዲህ አሸናናቸው!›፣ የወንዶች ወንዶች መሆናችንን ብልታቸውን እየቆረጥን አሳየናቸው…” በማለት ስብዕናን ለማዋረድ መሞከር ወደራስ የሚዞር አሉታዊ ውጤትን መጋበዝ መሆኑን መረዳት ይገባቸው ነበር፡፡ ለነገሩ ወያኔ ልብሱም ጉርሱም ቅሌትና ውርደት በመሆኑ በዚህ ረገድ የሚሰማው አንድም የሀፍረትም ሆነ የይሉኝታ ስሜት የለም፡፡ ጃዝ ብለው የለቀቁት 13 እና 33 ቁጥሮችም እየሳቁበትና እየተዝናኑበትም ቢሆን ወያኔ ለሚሠራው ግፍና በደል ሁሉ ቡራኬያቸውን አይነፍጉትም፡፡ እነሱስ ቢሆን በጭፍሮቻቸው አማካይነት በጓንታናሞና ኢራቅ ውስጥ አስከሬኖች ላይ እስከመሽናት በሚዘልቅ ኢሰብአዊነት ስንትና ስንት ግፍ ይፈጸሙ የለም? ልጅ ከአባት ቢማርና የጭካኔ ደረጃውን አዘምኖ ምሥኪን ኢትዮጵያውያንን ምድራዊ ገሃነም ውስጥ ቢዘፍቃቸው ዋኖቹ ሀዘን አምላኪዎች ይደሰታሉ እንጂ ከከንፈር ሽንገላ ባለፈ ሕዝቡን ሊታደጉት አይፈልጉም – ይህንንም አሳምረን እናውቃለን፡፡ ጭምብሉን ፖለቲካዊ የተለሳለሰ የሚመስል አካሄድም አንዘነጋም – አገም ጠቀሙን፡፡

በነገራችን ላይ 13 እና 11 ወይም 33 ደግሞ ተመሳሳይነት አላቸው፡፡ ለሚያምንበት ሁሉም የትልቁ ቁጥር የአውሬው መገለጫ የ666 ቅንስናሾች ናቸው፡፡ አሥራ አንዶች በ110 የለበጣ ቀመር ቢያላግጡም እውነቱ ቀፎ የመለዋወጥ – የትሮይን ፈረስ ቅርጽ የማሻሻል ጉዳይ እንጂ ሲሙ ያው ነው – አሥራ አንድ፡፡ ለነገሩ ዝናር ባንገቴም ይሁን 11 ወይም ዜሮም ይሁን አንድ ሽንትር ዋናው ነገር ተግባር ነው፡፡ ሌላው ትርፍና ጨዋታን ለማሳመር ያህል በአጃቢነት የገባ ነው፡፡ እናም በሀገራችን ሁኔታ የሰውዬው ማንነት ምንም ይሁን ምን በስቃይና በግድያ የሚያምን ሁሉ እናት ክፍሉና ጥንተ አመጣጡ ከአውሬው መሆኑን ልብ ይሏል፡፡ ክፉና ደግ መንፈሶች ኅብረት የላቸውም፡፡ ሩህሩህ መሐሪና አረመኔ/ጨካኝ ገዳይ አንድነት የላቸውም፡፡ መጽሐፉም ጣፋጭ ፍሬ በዛፍ ላይ ሳለ ይታወቃል እንደሚል ማን የማን ወገን መሆኑ በተለይ በዘመናችን በግልጽ ይታወቃል፡፡ ማን ነው የበሽታ ሕዋሳትን በቤተ ሙከራ እየፈለሰፈና እያራባ ለዓለም በተለይም ለኋላቀር ሀገሮች እንደ ዕርዳታ ስንዴ የሚያከፋፍል? ማን ነው የዓለማችንን የአየር ንብረት እያዛባና ዕድሜዋን በብርሃን ፍጥነት እያሳጠረ የሚገኘው? የዓለምን ጠቅላይ ገዢነት በትረ መንግሥት በጉልበት የተቆጣጠረውና “ለኔ ካልሰገዳችሁ ሀብትና ሥልጣን አይኖራችሁም” ብሎ ሁሉን እያስደገደገ የሚገኘውና በትዕምርተ ኅቡኣታዊ ባለአንድ ዐይን ፒራሚዳዊ ቅርጽ ወይም በፔንታጋራማቲን የኮከብ ቅርጽ የሚታወቀው ምሥጢራዊ ኃይል ማን ነው? ማን ነው አሁንም ሆነ ከአሁን በፊት መካከለኛውን ምሥራቅ እያተራመሰ ያለው? መፍለቂያው የሆነችን የአንዲት ትንሽዬ ሀገር ኅልውናና የበላይነት ለማስጠበቅ ሲል ድምጽን በድምጽ የመሻር መብቱ የዓለምን የመንግሥታት ኅብረት እንደአሽከር ሰጥ ለምበጥ አድርጎ የሚገዛ ማን ነው? አይኤም ኤፍ፣ ዩኤን፣ ወርልድባንክ፣ ኔቶ፣ ሲአርኤፍ፣ … የማን አድቃቂ ክንዶች ናቸው? ለመሆኑ የዚህ ሞገደኛ የወቅቱ የዓለማችን ገዢ ዋና መሥሪያ ቤትና ቅርንጫፍ ቢሮዎቹ የት የት ናቸው? ጽዮንና ሀማስ የማን ልዑካን ናቸው? የግጭቶች መንስኤና የምክንያታዊነት ሚዛኑ ለማንም ያጋድል ዋናው የሁለቱም ተልእኮ ግና ለአውሬው ግብር የሚሆን ብዙ የደም ባህር ማቆር መሆኑን መዘንጋት የዓለም ነገር አያገባኝም ብሎ እንደመመነን ይቆጠራል፡፡ በየትኛውም የዓለም ክፍል – ማን ነው የጦር ኃይሎችን በሁለት ጎራ እየከፈለ በተፃራሪነት በማሰለፍ የሚሊዮኖችን ደም በከንቱ እያፋሰሰ ያለው? ኢራንና አሜሪካ በርግጥም ባላንጣዎች ይሆኑ እንዴ? በፍጹም፡፡ ጠላቶች መስለው ትያትር በመከወን ለአንድ ዓላማ ስኬት የሚተጉ የአንድ ገዢ አንድ አምሳል አንድ አካል ናቸው፡፡  ማን ነው በአራት ወራት ጊዜ ውስጥ ብቻ ከአፍ እስከገደፋቸው በንጹሃን ተሣፋሪዎች ጢም ብለው የሞሉ የሲቪል አውሮፕላኖችን(የማሌዥያን) ባልታወቀ ዕፀ መሠውርና በሚሳኤይል ድራሻቸውን ያጠፋው? ምን ዓይነት ወያኔያዊ ጨካኝ አንጀት ያለው ፍጡር ይሆን ይህን ያደረገ? ለምን ዓላማ? ቫቲካንንና መለስተኛ አውሮፕላን የምታህል የነጭ እርግብ ምስል ለማስመሰል ያህል በሰላም ምልክትነት በዋና የፓትርያርክ ጸ/ቤቱ በር ላይ ያቆመውን የኛኑ ኦርቶዶክስ ሳይቀር ከሞላ ጎደል ሁሉንም የሃይማኖት ተቋማት ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ ተቆጣጥሮ ሁሉንም ሃይማኖት አለኝ ባይ በአውሬው ትዕዛዝ ሥር ያደረገው ማን ነው? ለመሆኑ በአሁኑ ሰዓት ቅዱስ ሊባል የሚችል ቦታና ሰው አለ ወይ? ፖፕ ጆን ፖል አንደኛ፣ ፖፕ ቤኔዲክት 16ኛ፣ ‹አቡነ› ጳውሎስ የኛ… ሌሎችም የማን ወኪል ነበሩ? ፍየሎች በበጎች ጋጣ ውስጥ መሽገዋል፡፡ በጎች እያለቁ ነው፡፡ አውሬው ሆሊውድና ቦሊውድን ብቻ ሳይን ገዳማትንና ካቴድራሎችንም ከተቆጣጠረ ምዕተ ዓመታት ተቆጥረዋል፡፡ ጭካኔን በሚያስተምሩ ፊልሞች፣ በልቅና ባልተገሩ ኢ-ሞራላዊም በሆኑ ፖርኖግራፊዎች በተለይ የዓለምን ወጣት ትውልድ ጡጦ ከመጣሉ በእንጭጩ ለማምከን  ይህችን ዓለም ማንና ከየትስ ሆኖ እየገዛት እንዳለ መች አጣነው? የዚያ ‹ታላቅ› የጨለማ ንጉሥ የእጅ ሥራዎች የሆኑ ወያኔዎችም ባቅማቸው ቅድስቲቱን ሀገር ድራሽዋን ቢያጠፏት ከድጋፍ በስተቀር ማን ከልካይ አላቸው? በጎችስ ቢጮኹ አለጊዜው ማን ይደርስላቸዋል? ግን ግን አይዞን፤ የፍየሎችና የበጎች የመጨረሻ ዕድል ተለይቶ የሚታወቅበት የፍርድ ቀን በፍጥነት እየመጣ ነው፡፡ ብሎም ቢሆን ሥጋዊም ሆነ መንፈሳዊ ድል በምኞት ሊገኝ እንደማይችል ልብ ማለት ይገባናል፡፡ ብቻ ይህን መሰሉን ነገር በሆድ ይፍጀው ለሌላ ቀን በይደር ማቆየቱ ሳይሻል አይቀርም፡፡ ለነገሩ እኛን ምን አገባን? ሁሉም ከልኩ አይዘል፡፡

 

ከሰው ተውሼ እያነበብኩት ነበር – “ያልተሄደበት መንገድ”ን፡፡ በቅርብ ካነበብኳቸው በሀገር ችግር ዙሪያ ከሚያጠነጥኑ የቅርብ ጊዜ መጻሕፍት ውስጥ በኔ ዕይታና ለኔ ፍጆታ ይሄኛውን ወደር አላገኘሁለትም፡፡ አንዱአለም አራጌ ዋለ የተዋጣለት መጽሐፍ በመጻፉ – ሊያውም በዚህ አፍላ የጎልማሳነት ዕድሜውና በመከራ ውስጥ ሆኖ – ባለበት አድናቆቴ ይድረሰው፡፡ ወላድ በድባብ ትሂድ የሚባለው በዚህ ዓይነት አጋጣሚ ነው፡፡ ሚሊዮኖች ፈርተንና ለሥጋችን አድረን በየሽርንቁላው ተወትፈን በፍርሀት ቆፈን ስንርድ ሊያውም በእስር ቤት ውስጥ ሆኖ ይህን የመሰለ አብሪ መጽሐፍ ካለበቂ ማጣቀሻና ዋቢ መጻሕፍት በአዩኝ አላዩኝ ሰቀቀን ሌሊት ሌሊት እየተደበቁ መጻፍ ልዩ ጀግንነትና ተሰጥዖም ነው፡፡ አንዱአለምና መሰል የብዕርና የፖለቲካ ታጋዮች ለነፃይቱ ኢትዮጵያ በሕይወት እንዲደርሱ እግዚአብሔር ይታደገን፤ ይታደጋቸው፡፡ ቤተሰባቸውንም ይባርክ፡፡ ለእኛም ለባከንነውና ለራሳችን ጥቅምና ፍላጎት ስንል በ‹እስኪያልፍ ያለፋል› ተረት ራሳችንን እያታለልን የወያኔ ባርያ ሆነን ለጠፋነው ዜጎችም ፈጣሪ ረድኤቱንና ወኔውን ይስጠን፡፡ እንደዚህ ያሉ ዜጎች ባይኖሩን ኖሮ ሕይወት በጠቅላላው ለይቶላት ጨለማ በሆነች ነበር፡፡ ከዚህ አንጻር እግዜር የተመሰገነ ይሁን፡፡ እርሱን መሰል ሌሎች ጸሐፊዎችንና ታሳሪዎችንም ጭምር እግዜር ይባርክልን፡፡ ለቤታቸውም ያብቃልን፡፡ የሚሳነው ነገር የሌለው የኢትዮጵያ አምላክ የመከራ ደብዳቤያችንን የሚቀድድና ሃራ የሚያወጣን አንዳች ኃይል ይዘዝልን፡፡ አሜን፡፡

ይህ መጽሐፍ የዋቢ መጻሕፍትን ገጽ ጨምሮ በጠቅላላው 320 ገጾች አሉት፡፡ በአራት ዋና ዋና ክፍሎች ሥር የተካተቱ 18 ርዕሶችንም ይዟል፡፡ ጠቅጠቅ ብሎ የተጻፈ በመሆኑ እንደሌሎች በርካታ መሰል መጻሕፍት በቀላሉ አይገፋም፡፡ የሆኖ ሆኖ በተለይ እስከማገባደጃው ድረስ ስሜትን ቆንጥጦ በመያዝ መነበብ የሚያስችለው ሥነ ጽሑፋዊ ውበትና ይዘታዊ ግርማ ሞገስ አለው፡፡ እናም አንብቡት፡፡ በነገራችን ላይ ይህን መጽሐፍ እያነበብኩ ወደ ገጽ 100 አካባቢ ስደርስ የተዋስኩትን እንደምመልስ ገባኝና ወዲያውኑ ከተማ ወጥቼ ገዛሁት፡፡ ተውሼ ያነበብኩትን ወይም እያነበብኩት ያለሁትን መጽሐፍ ስገዛ ይህ የመጀመሪያ ጊዜየ ነው፡፡ አንጡራ ሀብቴና የመጻሕፍት መደርደሪያየ አንዱ ፈርጥ እንዲሆን ተመኘሁ፡፡ ተመኝቼም አልቀረሁ፡፡ ለልጆቼ ውርስ ይሆናል፡፡ እናንተም አሁኑኑ ግዙና ንብረታችሁ አድርጉት፡፡ መጽሐፉ “ኩሎ አመክሩ ወዘሰናየ አጸንዑ” እንዲል፡፡

አመስጋኝ አማሳኝ እንዳልባል በዚህ መጽሐፍ የታዘብኳቸውን አንዳንድ ግድፈቶችም በዚሁ አጋጣሚ ብጠቁም ደስ ይለኛል፡፡ ጥቂት የማይባሉ የአርትዖት ችግሮች አሉበት፡፡ አሉታዊ መሆን ያለበት በአወንታዊ ወይም የዚህ ተቃራኒ ሆኖ የሚጻፍበት አጋጣሚ አልፎ አልፎ ይስተዋላል፡፡ አማርኛ ላይ ብዙውን ጊዜ የምታስቸግር ነገር አለች – ለምሳሌ “እኔን እንደሚያገባኝ እንዴት ረሳኸው?” በሚለው ዐረፍተ ነገር ውስጥ “ሚ”ን “ማ” ብናደርጋት ትርጉሙ ሙሉ በሙሉ ይለወጣል፡፡ “ጽንፍ” ለማለት “ቅንፍ” ብንል አንዳንዶችን ግር ሊያሰኝ ይችላል፡፡ የአርትዖት ሥራ ሽንፍላ እንደማጠብ ነው፡፡ በተቻለ መጠን ብዙ ሰዎች በብዙ አዳዲስ ዐይኖች ሊተባበሩበት የሚገባው አስቸጋሪ ሥራ ነው፡፡ እንዲያም ሆኖ የማይጠራበት ጊዜ አለ፡፡ ከዚህ አኳያ ይህን ቆንጆና ለታሪክ የሚቀመጥ መጽሐፍ ዐዋቂ ሰው እንደገና “ኤዲት” ቢያደርገው የበለጠ ማለፊያ ይሆናል፡፡ የግሌ አስተያየት ነው፡፡ (አንድ ወዳጄ የነገረኝ አንድ አርትዖታዊ ስህተት በጭንቅላቴ ብልጭ እያለ ‹እዚህ ላይ ካልጻፍከኝ ሞቼ እገኛለሁ!› ብሎ አስቸገረኝ፡፡ ነገሩ እንዲህ ነው፡፡ የመሥሪያ ቤቱ የብድር ኮሚቴ ስብሰባ ይጠራል፡፡ ለተሰብሳቢዎችም “ከብድር ኮሚቴ…. ለጠቅላላ አባላት” የሚል ጽሑፍ ተበትኗል፡፡ ሁሉን ያስፈገገው ግን ጸሐፊዋ “ከብድር ኮሚቴ” ከሚለው ሐረግ ውስጥ የአንዱን ቃል የመጨረሻ ፊደል ሳትጽፈው መቅረቷና እስከዚያን የስብሰባ ጊዜ ድረስ ማንም ጉዳዩ የሚመለከተው አካል ስህተቱን ልብ አለማለቱ  ነበር፡፡ ያቺ “ነገረኛ” ጸሐፊ የትኛዋን ሆሄ እንደዘነጋቻት እኔም አሁን ዘነጋኋት፡፡ )

ከሆሄያት ግድፈትና ሞክሼ ፊደላትን  በነባሩ ሰዋስዋዊ ልማድ ከመጠቀም አኳያ ከሚታዩ አንዳንድ ጥቃቅን “ስህተቶች” በተጓዳኝ ጥቂት የመረጃ መዛባትና የዘይቤና ፈሊጥ አጠቃቀም እጅግ አነስተኛ ችግር ሳይኖር እንደማይቀር እገምታለሁ፡፡ ለምሳሌ “ኢሕአፓ” የሚለው ምሕጻረ ቃል ሲፈታ እኔ የማውቀው “የኢትዮጵያ ሕዝብ አብዮታዊ ፓርቲ” በሚል ነው፡፡ በዚህ መጽሐፍ ግን “የኢትዮጵያ ሕዝብ አደራጅ ፓርቲ” በሚል ከአንዴም ሁለቴ ገደማ ቀርቧል፡፡ ፈሊጥን በተመለከተ “ለያዥ ለገራዥ” ለማለት “ለያዥ ለገናዥ” ተብሏል፡፡ በተጨማሪም የሃሳብ ድግግሞሽ በስፋት ይታይበታል፡፡ በዚያም ምክንያት አንድ አንባቢ በጀመረበት የስሜት ሞቅታ መጨረስ ባይችል ችግሩ ከዚህ የሃሳቦች መደጋገም የሚመነጭ ይመስለኛል፡፡ የሆኖ ሆኖ የመጽሐፉ አጻጻፍና ለኅትመት መብቃት በብዙ ችግር የታጠረ በመሆኑ የአሁኑ ይዘቱ ራሱ ከሚጠበቀው በላይና በአንጻራዊ ሁኔታ ከሌሎች በርካታ መሰል ጸሑፎች(እኔ ካነበብኳቸው) በጣም የተሻለ መሆኑን በበኩሌ ልገነዘብ ችያለሁ፡፡ በመሆኑም ይህ ጥረቱ ደራሲውን በእጅጉ ያስመሰግነዋል፡፡ እዬዬም ሲደላ ነው ጓዶች፡፡ እነኚህንና መሰል ሌሎች እንከኖችን አስተካክሎ በቀጣይ ኅትመት ለንባብ የሚያበቃው ወገን ከተገኘ መልካም ነው፡፡ ደግሞም የማይቻል አይመስለኝም፡፡

 

አንዱአለምን በዚህ መጽሐፉ ደርቤ እንዳነበብኩት የፕሮፌሰር መስፍን ደቀ መዝሙር ይመስለኛል፡፡ ይህን የምለው ፕሮፌሰሩ አንድ ወቅት እነብርሃኑ ነጋ “ሁለገብ ዘዴን በመጠቀም ወያኔን እንታገላለን” ባሉ ወቅት ክፉኛ ይተቿቸውና “እኛ ወደዚህ ‹የማይረባና ውዳቂ› የአስተሳሰብ ደረጃ አንወርድም”  ማለታቸውን በማስታወስና አንዱአለምም በዚያው ቅኝት አሁንም ድረስ በዚህ በኢትዮጵያ ውስጥ ወንዝ ቀርቶ የደረቀ ምንጭ በማያሻግር የሰላማዊ ትግል ሥልት ወያኔን እንጥላለን ብሎ የሚያምን በመሆኑ ነው፡፡ እርግጥ ነው አንዱአለም አሁን ባለበት ሁኔታ በኃይል ወይም በጦር መሣሪያ ወያኔን እንታገል ብሎ ቢጽፍ የሚደርስበትን ተጨማሪ መከራና ፍዳ ስለምንገነዘብ ይህን አቋም ያርምድ ብለን በሰው ቁስል እንጨት አንሰድም፡፡ ይሁንና ቢያንስ ዝም ማለት ሲገባ ወያኔ የፈጠረው የኢትዮጵያ ውጥንቅጥ ችግር የሚፈታው ወያኔን በሰላማዊ መንገድ በመታገል ብቻ ነው የሚል እምነት በጭፍን ማራመዱን አልወደድኩለትም፡፡ (በነገራችን ላይ ኤርምያስ ለገሰ ቅድም በኢሳት አንድ ውይይት ላይ ሲናገር እንደሰማሁት የአንዳርጋቸውን በወያኔዎች መያዝ ኔልሰን ማንዴላ በኢዲያሚን ዳዳ እንደተያዘ ያህል እቆጥረዋለሁ ማለቱን እኔም በጣም እደግፋለሁ፡፡) ሰው ከሰው ጋር ቢታገል አሸናፊውና ተሸናፊው ይለያል፡፡ ከአውሬ ጋር ግን እንዴት መታገል ይቻላል? ውሾች በ“አስተሳሰብ” ከሚበልጡት ወያኔ ጋር እንዴት ስለሰላም መወያየት እንደሚቻል አንዱአለም ቢያስረዳኝ ደስ ባለኝ፤ ውሾ ሲሸናነፉ በሚያሳዩት ተፈጥሯዊ ምልክት ይግባቡና ጦርነቱን ያቆማሉ፤ ከዚያም በመካከላቸው ሰላም ይሰፍናል፡፡ ሁኔታዎችም ወደጥንቱ (statusquo ante) ይመለሱና ማኅበረከልባዊ ሕይወት ትቀጥላለች (“ከልብ” ውሻ ማለት ነው – “ል” ጠብቃ አትነበብም)፡፡ ወያኔ ግን ያሸነፈውን ሁሉ በሕይወት ያለውን ብቻም አይደለም የሞተውን ሳይቀር እስከመቃብር ድረስ የፕሮፓጋንዳ ሠራዊት እያዘመተ የቅርብ አጥንቶችንና የሩቅ አፅሞችን የሚፋለም ዶንኪሾት ነው፡፡ ይህን ባሕርዩን ለማወቅ በግድ እንደነአሥራት ወ/የስ መሞትና እንደነእስክንድር ነጋ መታሰር አያስፈልግም፡፡ ዛሬ ላይ ቁጭ ብሎ ወያኔን በሰላማዊ መንገድ ከሥልጣን አስነሳለሁ ብሎ መቃዠት በርግጥም ቅዠትና ሲያንስም የዋህነት እንጂ አንዱአለምን ከመሰለ በሳል የፖለቲካ ሰውነት የሚጠበቅ አይመስለኝም፡፡ ከዚህ ውሱን ነጥብ አኳያ ምን እንደነካው ሊገባኝ አልቻለም፡፡

አክራሪ ኦርዶቶክሳውያን እንዳይቀየሙኝ እንጂ የአንዱአለም የዋህነት (naivety?) ከ‹ቅድስት› ክርስቶስ ሠምራ ጋር ይመሳሰልብኛል፡፡ ‹ቅ.› ክርስቶስ ሠምራ – በገድሏ ላይ ተጽፎ እንደሚነበበው – ሰይጣንን ከእግዚአብሔር ለማስታረቅ ዕቅድ ትነድፋለች አሉ፡፡ … እርሱ ወዳለበት ሲዖል በቀጥታ ትሄዳለች፡፡ “ስፈልግሽ ኖሮ እዚሁ መጣሽልኝ?” ይላትና የክርስቶስ ሠምራን ነፍስ ይዞ ወደግዛቱ ሊያስገባት ሲል መላእክት ደርሰው ወደመጣችበት ወደገነት ይወስዷታል፡፡ በአጋጣሚው ግን 78 ሺህ የተኮነኑ የሲዖል ነፍሳት በቅድስቲቷ መንፈሳዊ አካል ላይ በመጣበቅ ወደገነት ይገባሉ፡፡ እምነት ነው፡፡ በየዘመናቱ በገዢዎችና በሃይማኖት መሪዎች ፈቃድ እንዲካተቱ የተደረጉና እነዚህን አሳሳች ይዘት ያላቸውንና እርስ በርስ የሚቃረኑ፣ “በእግዚአብሔር መንፈስ የተነዱ” ሰዎች ስለመጻፋቸው የሚጠቁም አንዳችም ማስረጃም የሌላቸውን በመጽሐፍ ቅዱስ የተካተቱ አንዳንድ ጽሑፎችንና ሰይጣናዊ ሳጋዎችን ሳይቀር ላለመቀበል አንድ ሰው መብት ያለው መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ ይህን ኢትዮጵያዊ ሃይማኖታዊ ድርሰት ማመን አለማመን የማንም ውዴታ እንጂ ግዴታ ሊሆን አይገባም – እዚያው ውስጥ በሚገኙት ዘንድም ቢሆን፡፡ ታርጋ ሳይለጠፍብኝ ስለሃይማኖቴ ልናገር እንዴ? አይ፣ ለማንም አይጠቅምም፡፡ ግን ማንኛውንም ሃይማኖታዊ አክራሪነትና ጽንፈኝነት የምጠላ አማኝ(theist) መሆኔን ብገልጽ ደስ ይለኛል፡፡ አነሳሴ ወዳልሆነ ነገር በመንሸራተቴ ይቅርታ – ምን ላድርግ ሁሉም ነገር አንሸራታች ሆኖ ዐረፈው እኮ፡፡ ብቻ አንዱአለም የዚህችን ቀና ሴት ባሕርይ የተላበሰ ግን በአፀደ ሕይወት የሚገኝ የማይቻልን ነገር ለመሞከር የሚተጋ የወንድ ክርስቶስ ሠምራ ይመስለኛል፡፡  

ሰላማዊ ትግል የራሱ መደላድል አለው፡፡ በቅድሚያ የሀገርህ ሰው ከሆነ ሰው ጋር፣ ዜጋህ ከሆነ ሰው ጋር፣ እንደዜጋው ከሚቆጥርህ ወይም ከሚመለከትህ የአገዛዝ ኃይል ጋር፣ በትንሹ ደግሞ ሰው መሆንህን አምኖ ከሚቀበል ሰው ጋር እንጂ ከአውሬና ከለዬለት የዲያብሎስ መንጋ ጋር በሰላማዊ መንገድ እታገላለሁ ብለህ ወርቃማ የመቶዎች ዓመታት ጊዜህን አታባክንም – አንዱአለም የሚለው ግን ዝንታለሙን እየታሰርንና እየተገደልን ነፃነታችንን ከወያኔ በችሮታ እንቀበል ነው – ምናልባትም በወዲያኛው የምፅዓት ዘመን፡፡ ሰዎች ወያኔን መረዳት እንዴት እንዳልቻሉ ወይም እንደማይችሉ ሳስበው ይገርመኛል፤ እንዲያውም ወያኔዎች፣ ሰዎች እንዲህ እንዲሆኑ – ማለትም በሰላማዊ መንገድ ከነሱ ጋር መታገል እንደሚቻል እንዲያምኑና እንዲያሳምኑ – የሚያደርግ ድግምት ቢጤ ሳይኖራቸው የሚቀር አይመስለኝም፡፡ አለበለዚያስ የሰላማዊ ትግልን ገፈት ቀማሽ ከሆነ አንዱአለምን ከመሰለ ብርቅዬ ዜጋ እንዲህ ያለ ተሳስቶ የሚያሳስት አነጋገርና እምነት ሊደመጥ ባልተገባ ነበር፡፡ ይቅርታ ይደረግልኝና ዝምታ ማንን ገደለ? በከንቱ መነቃቀፍ ከትዝብት በስተቀር ምን አወንታዊ ውጤት ያስገኛል? እንዳለመታደልና እንደርግማንም ሆኖ በኅብረት መታገል ቢያቅት ሁሉም ባመነበት ቢንቀሳቀስ ምን ክፋት አለው? ከአድማስ ማዶ ሊኖር ይችላል ተብሎ በሚታሰብ ሥጋት ከወዲሁ መቆራቆስ አግባብ ነው ወይ? ለዚህማ ወያኔ አለ አይደል? ይህን ስል አንዱአለማውያንና መስፍናውያን – በተወሰነ ደረጃ እኔንም ጨምሮ – ስሜታችን እንደሚጎፈንን ይሰማኛል፡፡ ግን ምርጫ የለኝም፡፡ የሚሰማኝን መናገሬ እንደወንጀል ሊቆጠርብኝ አይገባም፡፡ አውቃለሁ – አንዱአለም እሳት ውስጥ ነው፡፡ አልክድም – እኔም ከርሱ ባልተናነሰ ሁኔታ እሳት ውስጥ አለሁ፡፡ ልዩነታችን እርሱ ባመነበት ገብቷል፡፡ “ደስ”ም ያለው ይመስላል፡፡ የኔ ግን ከሁሉ ያጣ ሆኜ በዕብደትና በስክነት መካከል አንዴ ሰው አንዴ ዐፈር በመሆን እየተቀያየርኩ መረጋጋትና ሰላም የሌለው ሕይወት እገፋለሁ፡፡ ኅሊናህን አፍነህ መኖር ከመታሰር በበለጠ እንደሚጎዳ አውቄያለሁ፡፡ ሰው እንኳን ሳያውቅልህ በአእምሮ ስቃይ ምክንያት ከቤተሰብህም ከጓደኞችህም ‹እየተናጀስክ› ሰላምህን አጥተህ በትልቁ እስር ቤት መኖር በትንሹ እስር ቤት ከመኖር የበለጠ እንደሚያሰቃይ ተረድቻለሁ፡፡ መብላት፣ መጠጣት፣ መዳራትና በሰፊ ጎዳና መመላለስ ትርጉም የሚያጡበትና አንጎልህ ተቀፍድዶ ተይዞ ሰዎችን ሰላም በምትነሳበት ሁኔታ ለመኖር ያህል ብቻ መኖር ከለዬለት ከርቸሌ ያልተሻለ መሆኑን ከተረዳሁ ቆይቻለሁ፡፡ ስለሆነም ከአንዱአለም ባልተናነሰ የኔም እስረኝነት የዋዛ አይደለምና ሁላችንም አንድ ነን፡፡ እንዲህ የምለው ስለኔ ብቻ አይደለም – ስለሌሎች እኔን መሰሎችም እንጂ፡፡ እንዲህ የምለው ግን ለምንድነው? የማንን አንጀት ለማላወስ? ማንስ ነው ሆዴ ላይ ቆሞ ያናዘዘኝ? ሆ!   

በውሸት መከሰሱን፣ በውሸት ምሥክር (አዳፍኔ በሚላቸው) ዘብጥያ መውረዱን፣ በውሸት የግንቦት ሰባት አባልና የሽብር ጥቃት ሊፈጽም ከምንደኞች ጋር እያቀነባበረ ነው መባሉን፣ …. ሁሉንም ዘንግቶ ከእባብ ዕንቁላል እርግብ እንደሚፈለፈል ሊያስረዳን መሞከሩ አንዱአለም ወያኔን ለማወቅ ገና ብዙ ጊዜ የሚፈጅበት መሆኑን አመልክቶኛል – ጠሊቅ ሀገራዊና ታሪካዊ ዕውቀት ያለው መሆኑ ተይዞልኝ፡፡ እናም እላለሁ – ሰማይ ዝቅ መሬት ከፍ ቢሉ ወያኔ በሰላማዊ ትግል ሥልጣን አይለቅም፡፡ ይህን ፀሐይ የሞቀውንና ሀገር ያወቀውን ሃቅ በመካድ ከዚህ የተለዬ ህልም ማለም – እንደአካሄድ ባይከለከልም – ትዝብት ላይ ይጥላል፡፡ በነገራችን ላይ ክርስቶስም ለትግስቱና ለፍቅሩ ገደብ ነበረው፤ ለዚህም ነው በመሳም አሳልፎ የሰጠውን ይሁዳን የረገመው – በአንገቱ የወፍጮ መጅ ታስሮ ወደጥልቅ ባህር ቢወረወር እንደሚሻለው በምሬት በመናገር፡፡

ይቅርታችሁንና በዚህስ አንዱአለምን ተናድጀበታለሁ፡፡ ምን ነካው ግን? እንግዲያውስ ያበጠው ይፈንዳ በኢትዮጵያ እንደእስካሁኑ የስግብግብነትና ራስ ወዳድነት በሽታችንና የሥልጣን አራራችን ከሆነ በሰላማዊ መንገድ እንኳንስ ወያኔ ኢንጂኔር ግዛቸው ሽፈራውም ሥልጣን አይለቅም፤ እንኳንስ ወያኔ ኢንጂኔር ኃይሉ ሻውልም አይለቅም (በጤና ምክንያት …ካልሆነ)፤ እንኳንስ ወያኔ ፕሮ. በየነ ጴጥሮስም አይለቅም፤ እንኳንስ ወያኔ ዶር. መረራ ጉዲናም አይለቅም፤ እንኳንስ ወያኔ ዶር. ፍስሐ እሸቱም አይለቅም፤ እንኳንስ ወያኔ በቁሙ የሞተው ከሃዲው ልደቱ አያሌውም አይለቅም … (ዝርዝሩ ብዙና ብዙ ነው – ስንተዋወቅ? ግን እባብ ልቡን ዐይቶ እግሩን ነሣው ሆነና …)፡፡ የኢትዮጵያ መሬት አዲስ በሚፈልቅ ፍቱን ጠበል ካልተረጨ ይሄ የሥልጣንና የገንዘብ እንዲሁም የሴሰኝነት ጠንቆች በቀላሉ አይለቁንም – በኛ ባሱብን እንጂ እርግጥ ነው እነዚህ መሰናከያዎች የአጠቃላዩ የሰው ዘር መደናቀፊያዎች መሆናቸው የታወቀ ነው (ለምሳሌ የሰሞኑንና የቅርብ ሩቅ ጊዜውን የኢራቁን አልማሊኪንና የግብጹን አልሲሲን የሥልጣን ሱስ ብናይ በሰው ልጅ ራስ ወዳድነት መገረማችን አይቀርም – ይህ ነገር ወደኛ መጥቶ ከማይምነታችን፣ ከሥልጣን ወዳድነታችንና ከቦክሰኛው አስተዳደጋችን ጋር ሲደመርማ ምን ያሳይ፡፡) በኛ ሀገር ለሁሉም ነገር በተለይም ለጥላቻችንና ለራስ ወዳድነታችን ልጓም አጣን፤ ለከት ጠፋ፤ በቃኝን ተጸየፍን፤ ጠገብኩን ጠላን፤ ከይሉኝታና ሀፍረት ተፋታን – ስንገርም፡፡ እናም ለነዚህ ነገሮች ያለን ጥብቅ ቀረቤታ ከሌሎች የጥፋት ሰበዞች ጋር ተደማምሮ እንደሀገርም እንደሕዝብም ከናካቴው ከምድረ ገጽ ልንጠፋ – መለኮታዊ ጣልቃገብነት በቅርብ ጊዜ ውስጥ ካልተከሰተ –  ዘመኑ ቀረበ፡፡ ውሸት ነው? ውሸት ነው ካልክ እውነት ነው ማለት ነው፡፡ “አልሞትኩም ብዬ አልዋሽም” የሚል መጽሐፍ ዱሮ አነበብኩ ልበል? አዎ፣ ‹ፀጉራም ውሻ አለ ሲሉት ይሞታል› እንዲሉ ካልሆነ ለይቶልን ጠፍናል፡፡ አንወሻሽ፡፡

አንዱአለም ወያኔ በሰላማዊ መንገድ ሥልጣን እንደማይለቅ አሳምሮ ያውቃል፡፡ መጽሐፉ ላይ በገደምዳሜ ገልጾታል፡፡ እንደመፍትሔ በየገጾቹ የሚያቀርበው ግን ያንኑ የሰላማዊ መንገድ የትግል ሥልት ነው፡፡ “የሰላማዊ መንገዱ ካልሠራ” ይላል አንዱአለም ፈገግ ባደረገኝ ሁኔታ “የሰላማዊ መንገዱ ካልሠራ ሌላ የሰላማዊ መንገድ መሞከር ነው፡፡” ከመሰነባበታችን በፊት በመጽሐፉ መጨረሻ አካባቢ ገጽ 312 ላይ የሚገኘውንና ወያኔን በሰላማዊ መንገድ ማስወገድ ባይቻል በማስከተል ምን ማድረግ እንደሚገባ አንዱአለም የመጨረሻ መፍትሔ ብሎ የሚሰነዝረውን እንመልከት – ወጣቱ ፖለቲከኛ አይፈረድበትም፡፡ የት ነው ያለውና? አያድርስ ነው – እነዚህ ሰዎች አስጨንቀው ያዙንና እምንለውንም እያሳካሩ ግራ አጋቡን እኮ፡፡ አንዱ ለጓደኛው “ያዋስኩህን ዕቃ ባትመልስ ዋልህ! አሳይሃለሁ!” ይለዋል፡፡ “ምናባህ ልታደርገኝ አንት የውሻ ልጅ!” ብሎ ቢያፈጥበት “አይ፣ ምን አድርግሃለሁ ያው ታዝቤህ እቀራለሁ እንጂ” አለው ይባላል፡፡ እርግጥ ነው መናገር የማድረግን ያህል እንደማይከብድ አውቃለሁ፡፡ “አይ መሬት ያለ ሰው!” ብሏል አሉ የሚጋልበው ፈረስ የደነበረበት አንድ ሰው – “እንዲህ አድርገው፤ እንዲህ ያዘው” ባሉት ጊዜና፡፡ አሁንም እርግጥ ነው – ለተቀማጭ ሰማይ ቅርብ ነው፡፡ እርግጥ ነው – አታሞ በሰው እጅ ስታምር በገዛ እጅግ ግን ልታደናግር ትችላለች፡፡ ቢሆንም የሚሰማኝን ብናገር ቢያንስ ዴሞክራሲያዊ መብቴን “ባልተሸራረፈ” መልኩ እንደተጠቀምኩበት ከመረዳቴም በተጨማሪ የተወሰነ እፎይታን አገኛለሁ፡፡ ለማንኛውም ወደአንዱአለም የመጨረሻ የችግሮቻችን መፍትሔ እናምራና ለአፍታ እንመልከትለት፤

 

ትልቁ ጥያቄ ኢሕአዴግ የብሔራዊ ዕርቁን ጥያቄ አሁንም “የባልና የሚስት ፀብ አይደለም” ብሎ ቢያጣጥለው ምን ማድረግ ይቻላል? የሚለው ነው፡፡ በእኔ እምነት ኢሕአዴግ ከዚህ በኋላም (እስካሁን) ለ21 ዓመታት የዳከረበትን መንገድ የሚመርጥ ከሆነ ተቃዋሚዎች ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር ሆነው የሚጓዙ(በ)ት የራሳቸው አዲስ መንገድ መፈጠሩ አይቀሬ ይመስለኛል፡፡ ኢትዮጵያን በአስተማማኝ መሠረት ላይ ለመገንባት (የ)ሚያስችለውን የብሔራዊ ዕርቅ መንገድ በመጓዝ ለፍትሃዊ ነፃና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ መንገድ መጥረግ የማይፈልግ ኃይል በኢትዮጵያ ሕዝብ ሰቆቃ ላይ የራሱን ግላዊ ወይም ቡድናዊ ጥቅም ብቻ የሚያስቀድም መሆኑን ያመለክታል፡፡ ኢሕአዴግም ይሄን መንገድ እስከመረጠ ድረስ የኢትዮጵያን ሕዝብ በኃይል ረግጦ የመግዛት ፍላጎቱን አሁንም ለመቀጠል እንደሚፈልግ ያሳያል፡፡ የማንወጣው መንገድ ቢሆንም ከተገደድን ግን ኢትዮጵያውያን በፀና ሰላማዊ ትግል ኢሕአዲግን ልኩን እንዲያውቅ ብሎም ለኢትዮጵያ ሕዝብ ፈቃድ እንዲገዛ ማድረግ አማራጭ የለውም፡፡ … (መስመር የተጨመረ) 

 

 

ወያኔ ልኩን የሚያውቀው በሰላማዊ ትግል ነውን? ይህ ነገር እውነት ይሆን? ይህች ነገር አጭር የክበበው ገዳን ቀልድ ትመስለኛለች፡፡

 

 

በመሠረቱ ጥሩ መመኘት በራሱ መጥፎ አይደለም፡፡ ነገር ግን የምኞትን ገደብ ማወቅ ተገቢ ነው፡፡ አንዱአለም ከዕድሜ አንጻርም ይሁን ከገጠመኝ ማጠጥ/ማጠር የተነሣ በኢትዮጵያ ምድር አይመኙትን ምኞት በመመኘት እርሱን መሳይ የዋሃንን በተስፋ ዳቦ ለመቀብተትና በከንቱ ለማስገሳት ሲጥር እንመለከታለን፡፡ እዚህም ላይ ወያኔን አለማወቁ ያሳዝነኛል፡፡ ማንበብ ጥሩ ነው፤ ማወቅና መመራመርም ጥሩ ነው፡፡ ተስፈኝነት መልካም ነው፡፡ ተስፋ አለመቁረጥና ሩቅ ማሰብም ደግ ነው፡፡ ይሁንና ጓዳችን ውስጥ እንደመዥገር ተለጥፎ በመርዘኛ ጥርስና ምላሱ እያንገበገበን የሚገኘውን ወያኔ በሰላማዊ ትግል ይወገዳል ብሎ ማሰብና መስበክ አንድም ባለማወቅም ቢሆን የወያኔን ዓላማ የማራመድ ያህል ነው አለዚያም ሞኝነት ነው፡፡ ቢሆን በወደድን፡፡ ግን ፈጽሞ አይሆንም – ተምኔታዊነት (ዩቶፒያን መሆን) ነው፡፡ ኔልሰን ማንዴላ ለኢትዮጵያ አብነት ሊሆን አይችልም፤ ማኅተመ ጋንዲ ለኢትዮጵያ አብነት ሊሆን አይችልም፡፡ እነዚህ ምርጥ የዓለማችን ዜጎች የታገሉት ከሰዎች ጋር ነው፡፡ የኛን የሚለየው ትግላችን ከድፍን ቅል ዘረኞችና መቼም በማይበርድ እንዲያዉም እየሰላ በሚሄድ የጥላቻና የቂም በቀል አባዜ ከተሞሉ የባንዳ ልጆች ጋር ነው፡፡ ምናልባት አንዱአለም ያልተገነዘበው ይህንን ሃቅ ሊሆን ይችላል ብዬ እገምታለሁ፡፡ በዚያ ላይ በሰላማዊ ትግል ቀርቶ በመሣሪያም የሚነቀንቃቸው እንዳይኖር ሕዝቡን በማይምነት ጋርደው፣ ፍጹም ከደረጃ በታች በሆነና “A,B,C,D”ን በቅጡ በማያስለይ እንዲሁም ዜጎችን በሚከፋፍል የትምህርት ሥርዓት ትውልድን አደድበው፣ ጥቂት የማይባሉ ኢትዮጵያውያንን በማይረባ የጥቅም ፍርፋሪ ከፋፍለው፣ በዘረኛ የፌዴራል ፖሊስ፣ በደንቆሮ ካድሬና መከላከያ አፍነው፣ በቅንድብ ጥቅሻና በስልክ ቀጭን ትዕዛዝ ወንበዴዎቹ የሚፈልጉትን ፍርድ በሚያስተላልፍ ኮንዶም ዳኞችና ፍርድ ቤቶች ሀገር ምድሩን ሞልተውት፣ ዜጎችን በጎጠኛ የፀጥታና ደኅንነት መዋቅር ቀፍድደው፣ በድህነት ኮድኩደው፣ በተለይ ወጣቱን በልዩ ልዩ ሱሶችና በወሲብ የአዶከብሬ ዛር ዳንኪራ አስረግጠው፣ በመርዘኛ የጎሰኝነትና የዘረኝነት በሽታ ሕዝበ አዳምን በክለው፣ … ከጠማማ ጎጆው ባለፈ – የሰኞን ነፍሱን ወደማክሰኞ በማሳደሩ ከመደሰት በዘለለ ለሀገርና ለወገን የሚቆረቆር ዜጋ እንዳይኖር አድርገው የሀገሪቱን ኅልውና ገደል ጫፍ ላይ ጥለውታል፡፡ ይህን ኃይል በሰላማዊ መንገድ እጥላለሁ ብሎ ማሰብ ዕብደት ነው የምለውም ለዚህ ነው፡፡ የደቡብ አፍሪካው አፓርታይድ ሥርዓት የመጨረሻ ፕሬዝደንት ኤፍ ደብልይው ደክለርክ ጭንቅላቱ ውስጥ ተሸክሞት ይዞር የነበረው ሊማር የሚችል ጤናማ ነጭ አንጎል እንጂ እንደወያኔ በድንቁርና የታጀለ ከመግደልና በሰው ስቃይ ከመደሰት ውጪ ምንም የማያውቅ የገማና የበሸቀጠ ጥቁር ጭቃ አልነበረም፡፡ ወያኔን በሰላማዊ መንገድ እታገላለሁ ማለት ለወያኔ አዲስና ለራሳቸው ለአባላቱም ቢሆን ግርታን የሚፈጥር ልዩ ተፈጥሮን እንደማላበስ ይቆጠራል፡፡…     

አፄ ኃ/ሥላሴ ለጉብኝት ይሁን ለሥራ ወዳንድ ቦታ ሲሄዱ አንዲት ችግረኛ ሴት ከነልጆቿ መንገድ ዳር ቆማ “ወድቃ በተነሳችው ባንዲራችን፣ በልዑል እግዚአብሔር ይሁንብዎ…” በማለት ባንዴራ ዘርግታ ታስቆማቸዋለች፡፡ ያኔ እንደዛሬው ዘመን መሪ ሲወጣና ሲገባ ግድግዳ እያስደገፉ (የሚገርም እኮ ነው!) ለገዢዎች የኅለውና መሠረት ከመሆናቸው አንጻር ውድና ብርቅ ሊሆኑ የሚገባቸውን ዜጎች በኢሰብአዊነት ማሰቃየት አልነበረምና ጃንሆይ መኪናቸውን አስቁመው በመውረድ “ችግርሽ ምንድነው?” ብለው ይጠይቋታል፡፡ ሴትዮዋም፣ “ጃንሆይ፣ ለምግብ ያላነሱ ለሥራ ያልደረሱ ስድስት ልጆችን ጥሎብኝ ባለቤቴ ሞተ…” ብላ ችግሯን መናገር ስትጀምር በቀልደኛነት የሚታወቁት የቀድሞው ንጉሣችን አጠገባቸው አጅበዋቸው ወደቆሙ መኳንንት ዘወር ብለው “አግባኝ ነው የምትለው?” ብለው እንደዋዛ ጣል ያደረጓት ቀልድ በሴትዮዋ ጆሮ ገብታ ኖሮ ድሃ መቼም ሞኝ ነውና “ጃንሆይ! ሆኖልኝ ነው! አ’ርጎት ነው!” አለች ይባላል፡፡ ቀልድ በአግባቡ ጥሩ ነው፡፡ ኃ/ሥላሴ ሴትዮዋን እንደማያገቧት ግልጽ ነው – ሴትዮዋ ግን ድሃና በዕውቀትም ዝቅተኛ ናትና በጣለችው ተስፋ አንፈርድባትም፡፡ ከወያኔ ጉያ ሕዝባዊ ሥልጣን በሰላማዊ መንገድ ይገኛል ተብሎ ተስፋ ማድረግ ግን ከሴትዮዋ የበለጠ ጅል መሆንን የሚያመለክት እንጂ የወያኔን ተፈጥሮ ከመገንዘብ የሚመነጭ ገምቢ ዕውቀትና ጥበብ አይመስለኝም፡፡ ይህን የሚመር ቀልድ የሚቀልዱ ሰዎች ራሳቸውን ቢመረምሩ የተሻለ ነው፡፡ ሰላማዊ ትግል ደግሞም በኢትዮጵያ – ሆ!

በጦርነት የሚገኝ ነገር መልካም ነው እያልኩ እንዳልሆነ ግን ይመዝገብልኝ፡፡ ምርጫ ከጠፋ ግና ምን ይደረጋል? ከሁለት መጥፎዎች የተሻለውን መምረጥ የምንገደድበት ጊዜ ይኖራል፡፡ እናም ሰው ካልሆነ አውሬ ጋር እየታገሉ ከማለቅ ቢያንስ የራሴ ነው ከሚሉት ጨካኝና አምባገነን መሪ ጋር መፋለም ይመረጣል – ለዚያም መብቃት እኮ መታደል ነው፡፡ እንደሚመስለኝ አሁን ሰዎችን እያሳሰባቸው ያለው የማያሳስብ ነገር ነው፡፡ ቀድሞ የመቀመጫየን ያለችው ፍጡር ወድዳ እንዳልሆነ መረዳት ተገቢ ነው፡፡ “ሌላውን እሾህ በመቀመጫየ ተቀምጬ ራሴው እነቅለዋለሁ” ማለቷ ነው፡፡ እና ያልበላንን የሚያኩልን ወገኖች አደብ ቢገዙልን ብዙ እንደረዱን ይቆጠራል፡፡ ለነገሩ ወያኔን ማንም ደገፈው ማን – በማወቅም ይሁን ባለማወቅ -  ወቅቱን ጠብቆ ወረደ መቃብሩን ሳይወድ በግዱ መቀበሉ አይቀርም፡፡ አንድዬ በመንበሩ ካለ – አለም- ይህን ሁሉ ግፍና በደል የፈጸሙ ሰው መሳይ “ሰዎች” የቁናቸውን ሳይከፈሉ ይቀራሉ ብሎ ማሰብ የታሪክንና የፈጣሪን ፍርድ አለመረዳት ነው፡፡ የሞተ ይነሳል፤ የተኛ ይነቃል፤ የቆመ ይቀመጣል፤ የተጋደመ ይቆማል፡፡ ለሁሉም ጊዜ እንዳለው ዛሬ አይደለም የምናውቀው፡፡ ታሪክና እግዜሩ ወያኔ ላይ ሲደርሱ ሥራቸውን ያቆሙ ይሆን? ለጅላጅሎቹ ወያኔዎች እንዲያ ሳይመስላቸው የሚቀር አይመስለኝም፡፡ ለኔ ግን በፍጹም! ጊዜው ቀርቧል፡፡

አገባቤና አወጣጤ የተምታታ ነገር ያለበት መሆኑ ይሰማኛል፡፡ ለዚህ የተምታታ ነገሬ ማንን ይቅርታ መጠየቅ እንዳለብኝ ግን አላውቅም፡፡ የሆኖ ሆኖ የዚህ ዘመን እውነት ባብዛኛው የተዘበራረቀ በመሆኑ አላግባብ ሊፈርድብኝ የሚቃጣ እንደማይኖር እገምታለሁ፡፡ ሁሉን ቢናገሩት ሆድ ባዶ ይቀራልና ወደማይቀረው ድል እየተጠጋን ስንመጣ እንጫወታለን፡፡ ማርቲን ሉተር ባይቀድመኝ እኔም “ህልም አለኝ!” ብል በወደድኩ፡፡

 

“ቀኒቷን ማንም አያውቅም፡፡ ከጥቂቶች በስተቀር ብዙኃኑ ጎጋም እንኳን የምፅዓትን የመጨረሻ ቀን አያውቃትም፡፡ እናንተ የሚገባችሁ ታጥባችሁ ታጥናችሁ መጠበቅ ነው – ከሙስናና ከዕድፍ ርቃችሁ፤ ከዘረኝነት አረንቋና ከሆዳምነት ተቆጥባችሁ፤ አስተዋይነትን ተላብሳችሁ፣ በወረተኛ ወጀባዊ ንፋስ እንዳትወሰዱ ተጠንቅቃችሁ … ፡፡ ይሁንና ምልክቶቹን ስታዩ የቀኒቷን መቅረብ ትረዳላችሁ፡፡ ምልክቶቹን ያዬ ትውልድ ከምፅዓት በፊት የምትገለጠዋን የኢትዮጵያን ትንሣኤ ቀን ያያታል፡፡ …” (‹መጽሐፈ ትንሣኤ ኢትዮጵያ› ፣ ምዕራፍና ቁጥር የማይነበብ!)  

በየነ

 More on —-http://www.freeandualemaragie.org/?p=359

የኢትዮጵያና የሱዳን የጦር ስምምነት

$
0
0

ትዮጵያና ሱዳን የጋራ የመከላከያ ኃይል ለመፍጠር ስምምነት ላይ መድረሳቸውን የሁለቱም ሃገሮች የመከላከያ ሚኒስትሮች አስታውቀዋል፡፡
ኃይሉ ሥራ የሚጀምረው የፊታችን መስከረም ላይ እንደሚሆን የኢትዮጵያው የመከላከያ ሚኒስትር ሲራጅ ፈጌሣ ተናግረዋል፡፡
ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

[jwplayer mediaid="33539"]

Source: voanews

Ethiosudan

ባዕት ዕንባ በልታ። (ከሥርጉተ ሥላሴ)

$
0
0

ከሥርጉተ ሥላሴ 13.08.2014 ( ሲዊዘርላንድ – ዙሪክ)

xxe

በትቢያ – ድሪቶ

በቋሰኛው – ጉቶ

ተመተረ ዘመን – በቅንቅን ተበልቶ፤

በበደል ተቁላልቶ

በግለት ተወግቶ

በቁርሾ ተሰልቶ።

ሲናሳ መራራ – የአስተሳሰብ ንቅዘት

ሲሰነብት እሬት – የባንዳነት ስባት

- ብነት።

ትናትን – ገደለ

ዛሬን – ረሸነ

ነገን – አተነነ

ዬበነነ።

ዞጋማ ቁሌቱ

ቅብረት ነው ስሌቱ

የወያኔ ማቱ

ጥፋቱ።

ዬት ሳውቅህ – በምንህ!?

ቃር=== ማ —- ነው ቃርሚያህ

የደም ሲቃ ግብርህ።

ዘረፋ – ሰርዴታህ

ዕበለትም – አትራፊህ፤

ሲካዳህ – ዕለትህ

የቆዬ ሰው፤ – ይይህ

ትነቱ ዘመድህ – የዘለአለም ስንቅህ

ፍልሰትህ —።

ኤሉሄ! ትላለች እናት ልጇን አጥታ፣

ኤሉሄ! ትላለች ባዕት ዕንባን በልታ፣

ኤሉሄ! ይለዋል ምጣድ የድርቅ ዋልታ

ኤሉሄ ትላለች – እንሥራ ተጠምታ፤

የሲሳዩ ማሳ በዕንባ እዬተፈታ

በጫካ -  ገበጣ።

ሸንተረር አነባ – በጉልበት ሲመታ

ወንዙም ሆዱ ባባ – በእርግጫ ሲለጋ

አፈር አለቀሰች – ተግርፋ በአለንጋ ….

… በበቀል ተወራ – ለድርቡሽ ተሰጥታ

ከውስጧ – ተራቁታ።

ጥንት – ከጥዋቱ፤ ልጇ ተቆላምጦ

የሚፈልገውን እንዳዬው መራርጦ …

ታዬ በወያኔ – ቀኑ ተገልብጦ —-

…. ተቀማ ዕህሉን፤  ወገን በወረንጦ

አምጦ።

ወያኔ የሚሉት —- የመከራ ጥሪት

ወያኔ የሚሉት —  የአሳሩ ስሌት

ወያኔ የሚሉት —- የመጋኛ ሌሊት

ወያኔ የሚሉት — የአሲድ እፉኝት

ህማማት።

የዋህነት – ቀብሮ

ቅንነትን – ቀብሮ

አብሮነት – ተቀብሮ

ትህትናንም – ቀብሮ

መተዛዘን – ቀብሮ

ነፃነት ተባሮ

መርዛማው ወያኔ – ውሳጣችን – ቆፍሮ

አዬነው እራሱን በጥፋት ተቀብሮ፤

በመንደር ተዋቅሮ

እሮ!

አመዳማ — ጉዞ

ጎርብጥባጣ — አዞ

ሳጥናኤል — ተመዞ

ለጥፋትም — ታዞ፤

ታሪክን – አንቅዞ

ትውፊትን – አፍዝዞ

ባህልን – ጠምዝዞ

መንፈስ –  ተገንዞ

ናውዞ።

ሞት ቢሞት ሞቱ ነው

ቢኖርም ሞቱ ነው

ሰኔልና ቹቻ

ስለት ለቋቁቻ።

 

 

28.06.2014 ሲዊዘርላንድ ቪንቱርቱር ተጣፈ።

 

መከራን ሳዳምጠው ደሜን አገኘዋለሁ!

 

እግዚአብሄር ይስጥልኝ።

 

 

 

 

ወያኔ በተቃዋሚ ፓርቲዎች ላይ የሚያደርሰው ቅጥ ያጣ አፈናና በደል

$
0
0

ፋሲል አያሌው

 

cartoon_HMD

አሁን በስልጣን የሚገኘው የወያኔው ስርአት ላለፉት 22 አመታት የዲሞክራሲ ስርአት ግንባታ እያለ ጆሮአችንን ቢያደነቁረውም እሱ የሚለው የዲሞክራሲ ስርዓትና ትክክለኛው ዲሞክራሲያዊ ስርአት አራምባና ቆቦ መሆናቸው ብቻ ሳይሆን ዲሞክራሲያዊ ስርአትን በገመድ ለክቶና መጥኖ የናንተ መብትና ነጻነት እስከመጨፈር እንጂ የኔን ስልጣንና ጥቅም የሚነካ ከሆነ ቢላ ባንገቴ ካለን ሰነባበተ:: ለዚህም ይመስላል በተለይም ህገ መንግስታዊ መብታቸውን ተጠቅመው የተቃውሞ ድምጻቸውን ለሚያሰሙ ጋዜጠኞችም ሆነ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ምንም አይነት መፈናፈኛ እንዳያገኙ ሌት ተቀን ደፋ ቀና የሚለው::


ከዚህም የነጻነት እጦት እና ፍጹም አምባገነናዊ አፈናዎች መካከል እንደ አንድ ማሳያ የሚሆነው በተቃዋሚ ፓርቲዎች ላይ የሚያደርሰው ቅጥ ያጣ አፈናና በደል ሲሆን ዛሬ በወያኔው ስርዓት ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚታዩት እንደ ተፎካካሪ ፓርቲ ሳይሆን ሃገርን ለማፍረስ እንደተዘጋጁ አሸባሪዎች ተደርገው ነው:: በጣም የሚያሳዝነውነና አደገኛው አካሄዱ ደግሞ ይህን እምነቱን ቀሪው የኢትዮጵያ ህዝብ እንዲያምንና እንዲቀበል ፍጹም ህገወጥ በሆነና ከዕውነት በራቀ ውንጀላ ተቃዋሚዎችን ለማጠልሸት የሚያደርገው እልህ አስጨራሽ ትግሉ ነው::


ስርዓቱ በተለይም ከ1997 ዓ.ም ወዲህ ተቃዋሚዎችን ለማዳከምና ለማጥፋት ፍጹም ኢ-ፍትሃዊና ህገወጥ በሆነ መልኩ የሚያደርገው እንቅስቃሴ በሁለት ስትራቴጂዎች የተዋቀረ ነው::
የመጀመሪያውና ቀጥተኛው ስትራቴጂ ተቃዋሚ ፓርቲዎችን አሸባሪና እሱ ራሱ አሸባሪ ናቸው ብሎ ከፈረጃቸው ድርጅቶች ጋር ማያያዝ (ማዛመድ) ነው:: ይህንንም ለማሳካት የተቃዋሚ ድርጅት አባሎችን ከአሸባሪ ድርጅቶች ጋር ግንኙነት አላችሁ በሚል የፈጠራ ክስ መወንጀል ሲሆን በጣም በሚያሳፍርና በሚያሳዝን መልኩ በዚህ ስትራቴጂ ውስጥ ይቃወሙኛል ብሎ ያሰባቸውን የነጻው ሚዲያ ጋዜጠኞችንም ይጨምራል:: እንግዲህ ይህ ስትራቴጂ የተወሰኑ ግለሰቦችን በአሸባሪነት ክስ ወደ ዘብጥያ በማውረድ ብቻ የተገታ ወይም የተቋጨ ነው ብሎ የሚያስብ የዋህ ይኖራል ብዬ አላስብም ዋናው አላማ አማራጭ ሚዲያና እውነተኛ መረጃ የተነፈገው ቀሪው የኢትዮጵያ ህዝብ በፍርሃት ውስጥ እንዲሸማቀቅና ለትክክለኛ የዲሞክራሲያዊ ስርአት ግንባታ የሚኖረውን የጋለ የህዝብ ስሜት ጥቁር ጥላ እንዲያጠላበት የሚያደርግ እንጂ::


በዚህ ስትራቴጂ የኢትዮጵያ ህዝብ የወያኔውን ስርአት የሃሰት ውንጀላ ጠንቅቆ የሚያውቅ ቢሆንም ውሸት ሲደጋገም እውነት ይመስላል እንዲሉ አንድ ለናቱ በሆነው የገዢው ስርአት ሚዲያ በየቀኑ የሚቀርበው የሃሰት ፕሮፓጋንዳ ህዝቡ ለተቃዋሚዎች፣ ለገዢው ፓርቲም ይሁን ለጠቅላላ የፓለቲካው ድባብ የሚኖረው ስሜት በፍራቻ፣ በጥርጣሬና ቀላል በማይባል ሁኔታ በፓለቲካው ተስፋ የመቁረጥ ስሜት ውስጥ እንዲገባ የማድረግ ሃይሉ እጅግ ከፍተኛ ነው::


ከዚህም በተጨማሪ ይህንን አደገኛ አካሄድ የከፋ የሚያደርገው ደግሞ ተቃዋሚዎች ምንም አይነት ሃሳባቸውን የሚገልጹበት ነጻ ሚዲያ ሰለሌላቸው (ፍኖተ ነጻነት ጋዜጣ እንኳን እንደታፈነች ነች)በፈጠራ ክስ ለታሰሩ አባሎቻቸውም ሆነ ለደረሰባቸው የመልካም ገጽታ (Good Will) መበላሸት ማስተባበያ የመስጠትም ሆነ የመከላከል አቅሙ የሌላቸው መሆኑ ነው::
ሁለተኛውና ቀጥተኛ ያልሆነው ስትራቴጂ ከመጀመሪያው ስትራቴጂ ጋር የሚያያዝ ሲሆን ተቃዋሚዎች የመሰብሰብ፣ የመደራጀት ከህዝቡና ከደጋፊዎቻቸው ጋር የመገናኘትና የመቀስቀስ ስራዎቻቸውን እንዳይሰሩ በእጃዙርም ይሁን ባስ ሲልም በቀጥታ የማፈንና የማሰናከል ተግባር ነው::


ይህንን እቅዱን እውን ለማድረግም ተቃዋሚዎች የመሰብሰቢያ አዳራሾችን እንዳያገኙ የተለያዩ መሰናክሎችን መፍጠር፣ ራሳቸውን በገቢም ይሁን በተለያዩ ነገሮች ለማጠናከር የሚደረጉ ዝግጅቶችን ማስቆም፣ ማሰናከል፣ ተቃዋሚዎች የሚጠሩትን ሰላማዊ ሰልፎች አለመፍቀድ ወይም መሰረዝ፣ ምንም አይነት ነጻ ሚዲያ እንዳያገኙ መዝጋትና ሌሎችንም ዘዴዎች ይጠቀማል:፡


ሌላውን ሁሉ ትተን ዛሬ በጣም በሚሳዝን ሁኔታ በሃገራችን ለተቃዋሚዎች አንዱ ከባዱ ስራ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ማግኘት ነው:: ከተወሰኑ ጊዚያቶች በፊት ሰማያዊ ፓርቲ የመመስረቻ ጠቅላላ ጉባኤውን የሚያደርግበት አዳራሽ አጥቶ ምን ያህል እንደተቸገረ የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነው::ዛሬ ለአንድ ህጻን ልጅ ልደት ለማክበር እንኳን አዳራሽ በሽ በሆነበት ሃገር ተቃዋሚዎች መሰብሰቢያ አዳራሽ አጥተው በሰው ቤት ጓሮ ዳስ እየጣሉ ግማሹ ተሰብሳቢ ጸሃይ እየበላው ነው ስብሰባቸውን የሚያካሂዱት:: የሆቴል ቤት ባለቤቶችና አዳራሽ አከራዮች በወያኔው ስርዓት በሚደርስባቸው ከባድ ተጸዕኖ ለተቃዋሚዎች አዳራሾቻቸውን ለማከራየት ፈቃደኞች አይደሉም::


የሃገሪቷ ሃብት በወያኔዎች እጅ በወደቀበት በዚህ ሰዓት ኣንድ የሆቴል ቤት ባለቤት አዳራሹን ለተቃዋሚዎች ቢያከራይ በህብረተሰቡ ውስጥ በዘሩት የተቃዋሚዎችን ስም በሀሰት የማጠልሸት ተግባር፣ ፍራቻና የስጋት ድባብ እንዲሁም ወያኔዎችና ደጋፊዎቻቸው በሆቴሉ ላይ በሚጀምሩት የሃሰት አሉባልታ ሆቴሉ ቀስ በቀስ ከገበያ ውጭ ሊሆን ስለሚችልና ምናልባትም ካስፈለገ ሆቴሉን እስከማሳሸግ ሊደርሱ እንደሚችሉ ስለሚታወቅ ነው ( በ1997 ዓ.ም ምርጫ ወቅት የመርካቶው ምዕራብ ሆቴልና ሌሎችም ሆቴሎች ተቃዋሚዎችን ትረዳላቹ ተብለው ታሽገው እንደነበር አይዘነጋም::)


እንግዲህ ኢትዮጵያ ውስጥ በተቃውሞው ጎራ መሰለፍ እንደ ሃገር ጠላት የሚታይበት ደረጃ ላይ መድረስ ብቻ ሳይሆን ባስ ካለም አሸባሪ የሚል ታርጋ አስለጥፎ ወህኒ ሊያስወረውር የሚያስችልበት ሁኔታ ኢትዮጵያውያኖችን በነጻነት የሚፈልጉትን ደግፈው ወይም ተቃውመው መኖር እንዳይችሉ ብቻ ሳይሆን በፍርሃት እንዲሸማቀቁና እንዲሰጉ ምክንያት ሆኗል:: ዛሬ በኢትዮጵያ ውስጥ የወያኔን ስርዓት መቃወም ስትጀምር በዚያውም ወደ እስር ቤት መቃረብህን ትረዳለህ:: አንተን ለመክሰስ የማስረጃ ጉዳይ ብዙም አያስጨንቅም በኢ- ማይልህ ላይ አንዳንድ መረጃዎችን ወይም ሞባይልህ ላይ ጥቂት መልእክቶችን መላክ (SMS) ማድረግ አንተን ዘብጥያ ለማውረድ በቂ ናቸው:: ( ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ ከወንድሙ ጋር በኢ-ሜይል ስለአባታቸው የህክምና ኦፕሬሽን (Operation) የተጻጻፉትን ኦፕሬሽን የሚለው ቃል ሌላ አላማ ተብሎ እንደማስረጃ የቀረበበት ሁኔታን ልብ ይሏል::)


በተጨማሪም እስር ቤቶቻችን ጥፋተኛን ወይም ወንጀል የሰራን ጸባዩን ከማረም ይልቅ በፓለቲካ አቋማቸው በግፍ የታሰሩ ወገኖቻችንን ቅስምና ሞራል ለመስበር በእስረኞች ላይ የሚደረገው ግፍ ለማመን የሚከብድ ነው:: ለዚህም ይመስላል ሁለቱ ስዊድናውያን ጋዜጠኞች እንዲህ ያለ የእስር ቤት ግፍ በአሜሪካዊው ፊልም ዳይሬክተር ስቴቨን ስፒልበርግ ፊልሞች ላይ እንጂ በእውን በዚህ ምድር ላይ ያለ አይመስለንም ነበር ያሉት::

በጋዜጠኞች ላይ የተከፈተው የክስ ዘመቻ ቀጠለ፤ እንቁ እና ጃኖ መጽሄቶችና አዘጋጆች ተከሰሱ (የክስ ቻርጁን ይዘናል)

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) የሕወሓት አስተዳደር የፍትህ ሚ/ር ሃሳብን የመግለጽ መብታቸውን ተጠቅመው በመሥራት ላይ የሚገኙት ጋዜጠኞች ላይ የክስ ፋይል መክፈቱን ተያይዞታል። ከትናንት በስቲያ በሎሚ መጽሔትና በአዘጋጁ ግዛው ታዬ፣ ትናንት በአፍሮ ታይምስ እና በአዘጋጁ ቶማስ አያሌው ላይ የተከፈተው ክስ ዛሬ ቀጥሎ በእንቁ መጽሔትና አዘጋጁ አለማየሁ ማህተመወርቅ እና በጃኖ መጽሔትና በአዘጋጁ አስናቀ ልባዊ ላይ ክስ ተመስርቶ የክስ ቻርጅ ደርሷቸዋል።

የክስ ቻርጆቹን ተመልከቷቸው።

ምርጫ እየደረሰ ባለበት በዚህ ወቅት በጋዜጠኞች ላይ እንዲህ ያለው አፈና መፈጸሙ ብዙዎችን እያስቆጣ ይገኛል።

enqu 1

enqu 2

enqu 3

jano 1

jano 2

Viewing all 8745 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>