Quantcast
Channel: ዘ-ሐበሻ – Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 8745 articles
Browse latest View live

ግንቦት 7 ለብሔራዊ አንድነትና ነፃነት ህወሓትን ከትግራይ ሕዝብ መነጠል ያስፈልጋል አለ

$
0
0

ግንቦት 7 በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ያወጣው ር ዕሰ አንቀጽ እንደሚከተለው ተስተናግዷል።

በአለፉት ጥቂት ሣምንታት በወያኔ የተፈፀሙ የእብደት ተግባራትን ስናጤን ከፊት ለፊት ኢትዮጵያችንን እየጠበቀ ያለው መንታ መንገድ አመላካች ነው። ይህ ከፊት ለፊት የሚጠብቀን መንታ መንገድ አንዱ ወደ ብሔራዊ አንድነት፣ ነፃነትና ብልጽግና ሌላው ወደ እርስ በርስ ትርምስና ውድቀት የሚያመሩ ናቸው። የአንድነት፣ የነፃነትና የብልጽግና መንገድ ለመያዝ መስመራችንን ማስተካከል ያለብን ከአሁኑ ነው።

ለመሆኑ ከላይ ያልነውን ለማለት ያስቻሉን በአለፉት ጥቂት ሣምንታት በወያኔ የተፈፀሙት ተግባራት ምንድናቸው?

ginbot 7አንደኛ፤ ወያኔ፣ ዓለም ዓቀፍ ህግንና ሥርዓትን በጣሰ መንገድ ከየመን ባለሥልጣናት ጋር በማበር የንቅናቄዓችንን ዋና ፀሐፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ማፈኑ በአለፉት ጥቂት ሣምንታት ውስጥ ውስጥ የተደረገ አብይ ክስተት ነው። ይህ የወያኔ የውንብድና ተግባር ኢትዮጵያዊያንን በእጅጉ አስቆጥቷል። ወያኔ፣ ለሀገር ነፃነትና ለእኩልነት የሚታገልን አንድ ታላቅ ሰውን ማፈንኑና ከእይታ ከልሎ እያሰቃየው መሆኑ በሕዝቡ ውስጥ ያለው ቁጣ ወደ መገንፈል አስጠግቶታል። አቶ አንዳርጋቸው በጠላት እጅ ከወደቀም በኋላ ኢትዮጵያዊያንን አሰባሳቢ ኃይል ሆኗል።

ሁለተኛ፤ ሰላምተኞቹን ብሎገሮችንና ጋዜጠኞችን በሽብርተኝነት በመክሰስ በቋፍ ላይ የነበረውን የወጣቶች ትዕግሥት እንዲሟጠጥ አድርጓል። ስለኢንተርኔት አጠቃቀምና ጥንቃቄ ሥልጠና መውሰድ በክስ ቻርጁ ውስጥ መካከቱ ሥርዓቱ ከእውቀት ጋር የተጣላ መሆኑ በግልጽ አሳይቷል። ከዚህም በተጨማሪ በህጋዊ ፓርቲዎች ውስጥ በንቃት የሚሳተፉ ወጣት መሪዎችን መርጦ በማሠርና በሽብርተኝነት በመወንጀል የወያኔ የአፈና መዋቅር ወጣቱ ላይ ማነጣጠሩ ግልጽ ሆኗል።

ሦስተኛ፤ እጅግ ሰላማዊና ጨዋነት በተሞላበት መንገድ አቤቱታቸውን በማቅረብ ላይ የነበሩትን ሙስሊም ወገኖቻችንን ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ በመደብደብ እና በጅምላ በማሠር በወያኔ መድብለ ቃላት ውስጥ “ሰላማዊ ትግል” የሚባል ነገር አለመኖሩ፤ ተቃውሞ ሁሉ “ሽብር” እንደሚባልና በሽብርተኝነት እንደሚያስከስስ በማያሻማ ሁኔታ አረጋግጧል። ይህም የሥርዓቱ አውሬዓዊ ባህሪ መገለጫ ሆኗል።

አራተኛ፤ አፈናውና እስሩ ወደ ትግራይም በመዛመቱ ወያኔ የቆመበት ምድር እየራደ መሆኑ አመላካች ሆኗል። ትግራይ ውስጥ የነበረው አፈና ድብቅ የነበረ ከመሆኑም በላይ ከወያኔ የውስጥ ሽኩቻ ጋር ሲያያዝ ቆይቷል። አሁን ግን ሁኔታዎች እየተቀየሩ ነው። አገራዊ ርዕይ ያነገቡ፤ ወያኔን በጽናት ለመታገል የቆረጡ የትግራይ ወጣቶች ወደፊት እየመጡ ነው። እነዚህ ወጣቶች የተጫነባቸውን ድርብርብ ጫና በመበጣጠስ ከተቀረው ኢትዮጵያዊ ወገናቸው ጎን መቆማቸውን በተግባር እያረጋገጡ፤ ለዚህም መስዋዕትነት እየከፈሉ ናቸው።

ከላይ የተዘረዘሩት አራት ጉዳዮች በጋራ ሲታዩ የተበታተነ የሚመስለው እና በተለያዩ ስልቶች የሚደረገው ትግል የሚሰባሰብበትና የሚቀናጅበት ወቅት ላይ መደረሱ አመላካቾች ናቸው። ዛሬ የምንገኘው የተለያዩ የትግል ስልቶች እንዲናበቡና እንዲደጋገፉ ማድረግ እጅግ አስፈላጊ የሆነበት ወቅት ላይ ነው።

በተለይም ወያኔ፣ መሸሸጊያ ምሽጉ አድርጎ በሚቆጥረው ትግራይ ውስጥ እየዳበሩ የመጡት የአመጽም አመጽ-የለሽ ትግሎችም አስተዋጽኦ ከፍተኛነት ሌላው ኢትዮጵያዊ እንዲረዳ ማድረግ ጊዜ የማይሰጠው ተግባር ነው። የወያኔ የአፈናና የመጨቆኛ መዋቅሮች የህወሓት አባላት በሆኑ የትግራይ ዘውጌ ማኅበረሰብ አባላት የሚዘወሩ መሆኑ እውነት ነው። ይህ ማለት ግን ህወሓት የትግራይ ሕዝብ ወኪል ወይም ጠበቃ ነው ማለት አይደለም። ትግላችን ከወያኔ ፋሽስታዊ አገዛዝ ጋር መሆኑ እና የትግራይ ሕዝብ የዚህ ትግል አጋር፣ የውጤቱም ተጠቃሚ መሆኑ ማስረገጥ ተገቢ ነው።

ከፊት ለፊታችን ካሉት መንታ መንገዶች መካከል የአንድነትን፣ የነፃነትና የብልጽግናን መንገድ ለመምረጥ የትግራይ ሕዝብ በስፋት ትግሉን እንዲቀላቀል ማድረግ ተገቢ ነው። ትግራይ የህወሓት የግል ጓዳ መሆኗ የማብቂያ ጊዜ ማፋጠን ይቻላል። በዲሞክራሲያዊ ትግል ውስጥ ያሉ ሁሉ በዚህ ጉዳይ ላይ የጋራ ግንዛቤ ከያዙ ወያኔን ማንሳፈፍ የሚቻልበት እድል በስፋት ተከፍቷል።

ስለሆነም፣ ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ዘረኛውና ፋሽስታዊው ህወሓትን ከትግራይ ሕዝብ መነጠል አንዱ የትግላችን ስትራቴጂ ሊሆን ይገባል ይላል።

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!


መኢአድ የሕዝበ ሙስሊሙን ጥያቄዎች መንግሥት በአስቸኳይ እና በተገቢው ሁኔታ መልስ እንዲሰጣቸው ጠየቀ

$
0
0

ከመላው ኢዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) የተሰጠ መግለጫ

(ፎቶ ከፋይል)

(ፎቶ ከፋይል)


ለረዥም ጊዜ በሰላማዊና በሰለጠነ መንገድ ጥያቄዎቻቸውን ሲያቀርቡ በነበሩ የእስልምና እምነት ተከታዮች ላይ ህውሓት/ኢህአዴግ የወሰደውን የኃይል እርምጃ አጥብቀን እናወግዛለን ፡፡ እንደ መኢአድ እምነት ለጥያቄዎቻቸው ተገቢውን መልስ መስጠት ሲገባ በግልባጩ መላው የኢትዮጵያን ሕዝብ ያሳዘነና ያስቆጣ የኃይል እርምጃ መወሰዱ የህውሓት/ኢህአዴግን ማንነት በተግባር ያሳየ ድርጊት ነው፡፡

ሐምሌ 11 ቀን 2006 ዓ.ም የእስልምና እምነት ተከታዮች በአንዋር መስጊድ በፀሎት ሥነ-ሥርዓታቸው ላይ ለጥያቄዎቻቸው መልስ እንዲሰጣቸው በመጠየቃቸው ጥያቄዎቻቸውን ወደጐን በመተው የኃይል እርምጃ በመወሰዱ ችግሩ ይፈታል ብለን አናምንም፡፡ ሆኖም በእለቱ በእምነቱ ተከታዮች ላይ እና በአካባቢው በነበሩ ሰላማዊ ሰዎች ላይ የፀጥታ ሃይሎች የወሰድትን የሀይል እርምጃ አጥብቀን እናወግዛለን፡፡ አሁንም ቢሆን ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ጥያቄዎቻቸው በሰላማዊና ኢትዮጵያዊ ጨዋነት መፈታት አለበት ብለን እናምናለን፡፡ የህውሓት/ኢህአዴግ አባገነን ሥርዓት በእምነት ተቋማት ላይ እጁን አስረዝሞ የሚያደርገውን የአፈና ተግባር ማቆም አለበት፡፡

መኢአድ ለእስልምና እምነት ተከታዩችም የሚያስተላለፈው መልዕክት ከአሁን ቀደም በሰላማዊ መንገድ ጥያቄዎቻችሁን እንዳቀረባችሁት ሁሉ መፍትሔ እስክታገኙ ድረስ በሰላማዊ መንገድ መቀጠል እንዳለባችሁ ያሳስባል፡፡ በመጨረሻም መኢአድ የሚያምነው ችግሩ ስር ነቀል መፍትሔ የሚያገኘው የህውሓት/ኢህአዴግ አባገነን ሥርዓት በዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ሲተካ ብቻ ነው፡፡ በመሆኑም መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ እና የሙስሊሙ ማህበረሰብ መኢአድ የሚያደርገውን ሰላማዊ ትግል በመቀላቀልና በመደገፍ የበኩላችሁን አስተዋፅኦ እንድታደርጉ ጥሪያችንን እናስተላልፉለን፣፣
አንዲት ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!!!
ሐምሌ 17 ቀን 2006 ዓ.ም

ዘረኛው የትግሬ-ወያኔ ቡድን በሰሜን ጎንደር የዐማራ ሕዝብ ላይ የፈጸመው የዘር ማጽዳት እና የዘር ማጥፋት ወንጀል

$
0
0

moreshየትግሬ-ወያኔ ኢትዮጵያን እና ኢትዮጵያዊነትን ለማጥፋት አቅዶ ሲነሳ፣ የግቡ መረማመጃ ያደረገው የኢትዮጵያዊነት መገለጫ የሆኑ ተቋሞችን፣ ኃይማኖቶችን፣ ዕሴቶችን እና በተለይም «ዐማራ» የተሰኘውን ነገድ ተወላጆች ነጥሎ ማጥፋት የሚል ሥልት በመከተል እንደሆነ ይታወቃል። በዚህም መሠረት የጥፋቱ ቅድሚያ ዒላማ ያደረገው ለትግራይ ሕዝብ በችግሩ ጊዜ ደራሽ እና የተራበ አንጀታቸውን ዳሳሽ በሆነው የወልቃይት፣ የጠገዴ፣ የጠለምትና የሠቲት ወረዳዎች ሕዝብ ላይ ነው። ወያኔ በእነዚህ የትግሬ አዋሣኝ ወረዳዎች ሕዝብ ላይ የጥፋት ክንዱን የዘረጋው በሦስት መሠረታዊ ምክንያቶች ነው።

የመጀመሪያውና ታላቁ ምክንያት የእነዚህ ወረዳዎች ሕዝብ ዐማራ በመሆኑ እና የትግራይ አዋሳኝ ስለሆነ የትግራይን ታሪክ ክፉውንም ሆነ ደጉን ጠንቅቆ የሚያውቅ በመሆኑ ነው። በዚህም ምክንያት የዚያ አካባቢ ሕዝብ የትግሬ-ወያኔ ለተነሳለት ፀረ-ኢትዮጵያ እና ፀረ-ዐማራ እንቅስቃሴ የማይተኛ እንደሆነ ስለሚረዳ ይህን ሕዝብ ብቻውን አቁሞ ማጥፋት ለወደፊቱ ግሥጋሴው ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥርላቸው በማመን የችግር ጊዜ ደራሻቸውን ሕዝብ ያለርኅራኄ ጨፍጭፈውታል። ሁለተኛው ምክንያት «ታላቋን ትግራይ» ለመመሥረት ባላቸው ዕቅድ ለውጭ ግንኙነታቸው መውጫ መግቢያ እንዲሆናቸው ከሱዳን ጋር የሚዋሰኑትን እነዚህን ወረዳዎች ወደ ትግራይ ማጠቃለል ስለነበረባቸው ነው። ሆኖም የአካባቢው ሕዝብ «ነገዳችን ዐማራ፣ ጠቅላይ ግዛታችን ጎንደር ነው።» እያለ እንዳያስቸግራቸው በቅድሚያ ነባር ነዋሪውን ጎንደሬ አጥፍቶ በሠፋሪ ትግሬ ማስያዝ ለዓላማቸው ሥምረት ያገለግላል ብለው በማመናቸው ነው። –-– [ሙሉውንለማንበብእዚህይጫኑ]—–

Ethiopians in Houston ready to confront Andargachew Tsige’s kidnappers on July 29

$
0
0

Ethiopians residing in Texas, Oklahoma, and Louisiana will head to Houston on July 29 to confront PM Hailemariam Desalegn, Ambassador Girma Biru and other representatives of the ethnic apartheid regime in Ethiopia that has abducted Ethiopian opposition leader Andargachew Tsige last month, recently massacred Oromo students, savagely attacked peaceful Muslim protesters, thrown in jail journalists and opposition leaders, committed genocide in Ogaden and Gambella, conducted ethnic cleansing against Amhara farmers in southern Ethiopia, to mention just a few of their recent atrocities. Come join us and give voice to the voiceless.

10568825_804808072885368_1797225688132079506_n

Health: በእንቅልፍ ልቤ ከብልቴ የሚወጣውን ፈሳሽ እንዴት መቆጣጠር እችላለሁ?

$
0
0

(በዘ-ሐበሻ ጋዜጣ ቁጥር 51 ላይ ታትሞ የወጣ)
ጂቲ እባላለሁ፡፡ የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ነኝ፡፡ ዋነኛ ችግሬ ምን መሰላችሁ? በእንቅልፍ ልቤ በተደጋጋሚ የዘር ፍሬዬ እየፈሰሰ ተቸግሬያለሁ፡፡ ይህ ችግር በተደጋጋሚ መከሰት ከጀመረ አንድ ዓመት ይሆነኛል፡፡ በሳምንት ቢያንስ ሶስት ቀን ይህ ችግር ይከሰትብኛል፡፡ ሁሌም ከእንቅልፌ ስነቃ በተደጋጋሚ የሌሊት ልብሴ፣ የውስጥ ሱሪዬ እና አንሶላዬ ረጥቦ እና አልጋዬ ባልተለመደ ጠረን ታውዶ አገኘዋለሁ፡፡ ይህ ነገር ደግሞ ለሀፍረት ስሜት ያጋልጠኛል፡፡ ለራስ ምታት ህመምም ይዳርገኛል፡፡ ገና ተማሪ ስሆንኩ እስካሁን የሴት ጓደኛ የለኝም፡፡ ወሲብም ፈፅሜ አላውቅም፡፡ አልፎ አልፎ ግን ማስተርቤት አደርጋለሁ፡፡ ስለዚህ ውድ የዘ-ሃበሻ አዘጋጅ ይሄ ነገር የሚከሰትብኝ ለምንድን ነው? ወሲብ ብጀምርስ ይህ ነገር ይጠፋል? ከዚህ ነገር መላቀቅ የምችለው እንዴት ነው? እባክህ ለችግሬ መልስ ፈልግልኝ፡፡ ጂቲ ነኝ
ask your doctor
የዶ/ር ዓብይ ዓይናለም ምላሽ፡- በተፈጠረብህ ነገር ብዙ አትደናገጥ፡፡ ምክንያቱም ይህ ችግር ያንተ ብቻ ሳይሆን የብዙ ወንድ እና ሴት ወጣቶች እንዲሁም ጎልማሶች ችግር ነው፡፡ እንደ የተለየ ጤና ችግር በመቁጠርም አትረበሽ፡፡

በእንግሊዝኛ ኖክቱርናል ኢሚሽን (Nocturnal Emission) በመባል የሚታወቀው በሌሊት የሚከሰት የዘር ፍሬ በዘፈቀደ መፍሰስ በአብዛኛው በወጣትነት ዕድሜ ላይ በሰውነት ውስጥ የሚከሰት ባይኮሎጂካል እና የሆርሞን ለውጦችን ተከትሎ በስፋት የሚከሰት ጤናማ የጉርምስና ምልክት ነው፡፡ በተደጋጋሚ የሚከሰት ከሆነ ግን ተጨማሪ ምርመራ ለማድረግ እንገደዳለን፡፡ ነገር ግን ይህ ችግር በአነስተኛ መጠንም ቢሆን በጎልማሶች እና በአረጋዊያን ላይም ሊከሰት ይችላል፡፡ ጥናቶች እንደሚጠቁሙት በእንቅልፍ ልብ የዘር ፍሬ የሚፈሰው በሁለት መልኩ ነው፡፡ የመጀመሪያው እና በአብዛኛው የሚከሰተው በእንቅልፍ ልብ የብልት መወጠርን (መቆምን) ተከትሎ ነው፡፡ ይህ ነገር በአብዛኛው ወሲባዊ ህልሞችን በመመልከት እና በወሲባዊ ሀሳብ መወጠርን ተከትሎ የሚከሰት ነው፡፡ በአንዳንድ ሰዎች ላይ ደግሞ ብልት ሳይወጠርም የዘር ፍሬ ሊፈስ ይችላል፡፡ ይህ ነገር ደግሞ ከወሲባዊ ሀሳቦች ጋር የተገናኘ አይደለም፡፡ ስለዚህ የአንተ ችግር ከሁለቱ በየትኛው ውስጥ እንደሚወድቅ ለራስህ መልስ ስጥ፡፡

ጥናቶች እንደሚያሳዩት በወጣትነት የዕድሜ ክልል ውስጥ ከሚገኙ ወንዶች 84 በመቶ የሚሆኑት ቢያንስ በወር አንድ ጊዜ ይህ ችግር ይከሰትባቸዋል፡፡ በተደጋጋሚ የማስተርቤሽን ተግባር የሚፈፅሙ ወጣቶች በእንቅልፍ ልብ የዘር ፈሳሽ ለመፍሰስ ችግር የተጋለጡ ናቸው፡፡ በመንስኤው ዙሪያ የተደረጉ ጥናቶች እንደሚገልፁት በእንቅልፍ ልብ የሚከሰተው የዘር ፍሬ መፍሰስ ወሲብ ካለመፈፀም ጋር እንደማይገናኝ ይጠቁማሉ፡፡ በእንቅልፍ ልብ ዘር ፍሬ የመፍሰስ አጋጣሚ የሚፈጠረው በተለያዩ ምክንያቶች ነው፡፡ በሰውነታችን ውስጥ በሚከሰት የሆርሞኖች ለውጥ የመጀመሪያው ሲሆን ከፍተኛ የሆነ የዘር ፍሬ ክምችት በሰውነታችን ውስጥ መኖር ደግሞ በሁለተኛነት ሊጠቀስ ይችላል፡፡ ከላይ ከተጠቀሱት ምክንያቶች በተጨማሪ ወሲብ እና ተያያዥ ጉዳዮችን ሲፈፅሙ ህልም ማየት እና ስለወሲብ ደጋግሞ ማሰብ እንዲሁም ከመኝታ በፊት ወሲብ ቀስቃሽ ፊልሞችን መመልከት እንዲሁም መጽሐፍትን ማንበብ በእንቅልፍ ወቅት ዘር ፍሬ የመፍሰስ ችግርን እንደሚያስከትል ይጠቁማሉ፡፡
men
ወድ ጠያቂያችን ጂቲ በወር አንድ ጊዜ እና ሁለት ጊዜ በእንቅልፍ ልብ የዘር ፍሬ የመፍሰስ ችግር ጤናማ እንዲሁም ተፈጥሯዊ እና ምንም አይነት ችግር የሌለው ነው፡፡ ነገር ግን በየቀኑ እና እንደ አንተ በሳምንት ሁለት ሶስቴ የሚከሰት ከሆነ እና እሱን ተከትሎ መደበርን፣ ራስ ምታትን፣ አቅም እንዲሁም እንቅልፍ ማጣትን የሚያስከትል ከሆነ ግን ጤናማ ስላልሆነ በፍጥነት ባለሞያን ማማከር ያስፈልግሃል፡፡ ምክንያቱም ይህ ነገር በሰውነታችን ወስጥ የሚኖረውን የቴስቴስትሮን መጠን በማሳነስ ለተለያዩ ሆርሞን ችግሮች ሊያጋልጥ ይችላል፡፡
ከዚህ በተጨማሪ የዘር ፍሬ በብዛት መፍሰስ በሰውነታችን ውስጥ ጤናማ ያልሆነ የዘር ፍሬ ፈሳሸ ምርት ምልክት ሊሆን ይችላል፡፡ ጤናማ ያልሆነ የዘር ፍሬ ምርት ደግሞ በተለይ ወንዶችን ለመሀንነት ችግር ሊያጋልጥ ይችላል፡፡ የዘር ፍሬ ብዛት በመመረቱ የተነሳ የዘር ፍሬ በብዛት የሚፈስ ከሆነ የሚፈሰው የዘር ፍሬ በአብዛኛው ትክክለኛ ቅርጽ እና መጠን ያለው ስለማይሆን ከሴት እንቁላል ጋር ተገናኝቶ ጽንስ የመፍጠር አቅሙ እጅግ አነስተኛ ይሆናል፡፡

በተመሳሳይ ይህ ነገር በሰውነታችን ውስጥ ያለው የዘር ፍሬ ክምችት አነሰተኛ እንዲሆን ያደርጋል፡፡ በአንድ ጊዜ በሚፈስ የዘር ፍሬ ውስጥ ከ20 ሚሊዮን በላይ ሴሎች ይገኛሉ፡፡ በአንድ ሚሊ ሊትር የዘር ፈሳሽ ውስጥ የሴሎች ብዛት ከ20 ሚሊዮን በታች ከሆነ ጽንሰ የመፍጠር አቅም አይኖረውም፡፡
ከዚህ በተጨማሪ በእንቅልፍ ልብ የዘር ፍሬን መፍሰሰ በወሲብ ወቅት ከሴቷ በፊት ቀድሞ የመርካት ችግርን እና ሌሎች ስንፈተ ወሲብ ችግሮችን ያስከትላል፡፡ የሰውነት ክብደት መቀነስን እና በራስ የመተማመን መንፈስንም ያሳጣል፡፡ ለራሳችን የምንሰጠውን ግምት በመሸርሸርም የፀፀት እና የጥፋተኝነት ስሜት እንዲሰማን ያደርጋል፡፡

ወደ መፍትሄው ስንመጣ የመጀመሪያው በጀርባ አለመተኛት ነው፡፡ ወደ መኝታ ከመሄድ በፊት ወተት አለመጠጣት እና ብዙ ምግብ አለመመገብም ይመከራል፡፡ በተለይ ደግሞ እራት ወደ መኝታ ከመሄዳችን ቢያንስ ከ3 ሰዓት በፊት መመገብ እና እራት ላይ ብዙ ቅመም የበዛበት ምግብን፣ ከመጠን በላይ ወይን ከመጠጣት፣ እንቁላል፣ ስጋ እና ሌሎች አነቃቂ ነገሮች የበዛባቸው ምግቦችን ከመመገብ መቆጠብ ቢቻል እራት ላይ አትክልት እና ፍራፍሬዎችን ማዘውተር ጠቃሚ ነው፡፡ ሌላው መፍትሄ ደግሞ ምግብን በደምብ አድቅቆ መመገብ እንዲሁም የፈሳሽ አወሳሰዳችንን ማስተካከል ነው፡፡ በተለይ ከእራት በኋላ ብዙ ፈሳሽ አለመውሰድ፣ ቀን ላይ ብዙ ውሃ መጠጣት፣ ከመኝታ በፊት ሽንትን መሽናት ጠቃሚ ነው፡፡ ብዙ ጊዜ የዘር ፍሬ የሚፈሰው ሊነጋጋ ሲል ስለሆነ በጠዋት የመነሳት ልማድን ማዳበርም ይመከራል፡፡

ውድ ጂቲ ፈረስ መጋለብን እና ሳይክል መንዳትን የመሳሰሉ ችግሮችንም ለዚህ ችግር ያጋልጣል፡፡ ስለዚህ መሰል ተግባራትን መቀነስም ጠቃሚ ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የእግር ጉዞ ማድረግ፣ ከመኝታ በፊት ወሲብ ቀስቃሸ ፊልሞችንም ሆነ ጽሁፎችን ከመመልከት እና ከማንበብ መቆጠብ፣ እለታዊ የአካል ብቃት እንቅስቃሴን ማዘውተር እንዲሁም ብልት እና አካባቢውን በየቀኑ በአግባቡ ማጽዳት እና የተመጣጠነ የአመጋገብ ስርዓትን ማዳበር ጠቃሚ ነው፡፡

በእንቅልፍ ልብ ካለፍቃድ እና ካለፍላጎት የዘር ፍሬ የመፍሰስ ችግርን ከላይ በመፍትሄነት የተዘረዘሩትን ነገሮች በአግባቡ እና ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ በማድረግ ካለብህ ችግር መላቀቅ ትችላለህ፡፡ በእነዚህ መንገዶች የምትፈልገውን ለውጥ ማምጣት ካልቻልክ ግን በአፋጣኝ ባለሞያዎችን ማማከር ይገባሃል፡፡

(በዘ-ሐበሻ ጋዜጣ ቁጥር 51 ላይ ታትሞ የወጣ)

የተዓማኒነት ጉድለት ያለበት መንግስት…ከግርማ ሰይፉ ማሩ

$
0
0

ከግርማ ሰይፉ ማሩ

መንግሰት የሚባለው ነገር ምን እንደሆነ ግራ ገብቶኋቸው ግራ የሚያጋቡን የመንግሰት ኃላፊዎች ያሉበት ሀገር ውስጥ ነው የምንገኘው፡፡ በሃላፊነታቸው ደረጃ የሚመጥን ማስተካከያ ለመውሰድ አቅምም ፍላጎትም የላቸውም፡፡ የተሸከሙት ሃላፊነት መንግሰት ብለው ለሚያስቡት አንድ ግዑዝ ነገር ለአገልጋይነት እንጂ፤ እነርሱ የመንግሰት አካል እንደሆኑ አይረዱትም፡፡ ይህን እንድንል የሚያደርገን መንግሰታችን ብለን በኩራት ግብር የምንከፍለው፤ መንግሰታችን ዜጎች በሰላም ወጥተው በሰላም አንዲገቡ የሚያደርግልን ተቋም ነው፤ ሀገራችን በልማት በልፅጋ ዜጎች የልማቱ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር ስርዓት ነው፣ ይህ ሁሉ ሆኖም ችግር ቢገጥመን በገለልተኝነት በፍትህ ስርዓት ዳኝነት የምናገኝበት ነው፤ ብለን ማመን ቢቸግረን ነው፡፡ እነዚህ የመንግሰት ሃላፊ ተብዬዎች እነርሱ የተጣለባቸውን ኃላፊነት መወጣት ሲያቅታቸው እኛ በእንድ ወይም በሌላ መንገድ ችግራቸውን በጠቆምናቸው ወደ ትክክለኛ ደረጃ ማደግ ትተው እኛ ወደ እነርሱ እንድንወርድ፣ እንድንዋረድ፣ ለሆዳችን እንድናድር ወደ ገደል ይጎትቱናል፡፡

(ግርማ ሰይፉ)

(ግርማ ሰይፉ)


እውነቱን ለመናገር የኢትዮጵያ መንግሰት የሚባለውን አካል ለመደገፍ፤ በህግ የተሰጠውን ተግባር አንዲወጣ ማገዝ እንደ ዜጋ መብቴ ነው ብቻ ሳይሆን እንደ ግዴታም የምመለከተው ነው፡፡ አሁንም የማደርገው ነገር ሁሉ የማድረገው በዚሁ መንፈስ ግዴታዬን ለመወጣት ነው፡፡ እንዳለመታደል ሆኖ የሚደረግለትን ድጋፍ መቀበል የማይችል መንግሰት ሆኖዋል፣ ልክ ጥሩ ምግብ ሲያጎርሱት እንደሚያስመልሰው በከፍተኛ ደዌ እንደተያዘ በሽተኛ፣ ወይም ቤት እንዲጠብቅ ጠላት ሲመጣ እንዲያነቃን ያሳደግነው ውሻ በተቃራኒው ቤተኛውን በሙሉ መናከስ እንደጀመረ ውሻ ሆኖዋል፡፡ መንግስት ምክር አይሰማም ብቻ ሳይሆን በተቃራኒው ምክር የሚሰጡትን ለማጥፋት በከፍተኛ ትጋትና ከፍተኛ በጀት መድቦ እየተንቀሳቀሰ እንደሆነ ነው እየተሰማን ያለው፡፡ ይህ ድርጊቱ በቀጣይ ዜጎች ከመካሪነት ወጥተው ሀገርን ወደማይጠቅም አውዳሚ አማራጭ መስመር እንዲገፉ እንደሚያደርግ ምንም ጥርጥር የለውም፡፡ እሰከ አሁን የተገፉትን ሳይጨምር፡፡

ዛሬ የመረጥኩትን ርዕስ እንድመርጥ ያደረገኝ መንግሰት ሰሞኑን እያሳየ ያለው ባሕሪ ነው፡፡ መቼም መንግሰት የሚገለፀው በመንግሰት ሃላፊዎች ነው የሚል እምነት አለኝ፡፡ መንግሰትን የሚመሩት ግለሰቦችም ሆኑ አካላት በመንግሰት ሃላፊነት ላይ የሚመድቧቸውን ሰዎች በህዝብ ፊት እንዲቀሉ ማድረግ ያለባቸው አይመስለኝም፡፡ እነዚህ ግለሰቦች እንዲቀሉ ሲያደርጉ የሚቀሉት አበረው መሆኑን እንዲሁም መንግስት የሚባለውን ሰርዓት የሚመራው አካል ጭምር ነው፡፡ እራሱ የሾመውን አካል ጭምር ማለት ነው፡፡

ይህን ሀሳብ ያነሳሁት አቶ ጌታቸው ረዳ የተባሉ የጠቅላይ ሚኒሰትሩ ቃል አቀባይ “መንግሰት አቶ አንዳርጋቸውን አልተረከበም” ብለው በአሜሪካ ድምፅ ሬዲዮ ለህዝብ ይፋ አደረጉ፡፡ የፀረ ሽብር ግብረ ኃይል በመግለጫው “የየመን መንግሰት እንዲይዛቸው አደረግን የዚያኑ ዕለት ተረከብናቸው” አለ፡፡ የፀረ ሽብር ግብረ ኃይሉ ጅግንነቱን ለመግለፅ የመንግሰት ቃል አቀባዩን ማዋረድ ለምን አስፈለገ? ከዚህ ቀደም እንደልምድ ሆኖ የመንግሰት ኮሚኒኬሽን ፅ/ቤት ከፍተኛ ሹም የሆኑት አቶ ሽመልስ ከማል ሆን ተብሎ በሚመስል ሁኔታ እንዲህ ዓይነት ተቃርኖ ያለበት አሰተያየት እንደሚሰጡ ይታወቃል፡፡ በዚህ የተነሳም እኝህን ከፍተኛ የመንግሰት ሹም የሚያምን ለማግኘት እጅግ አስቸጋሪ ነው፡፡ ይህ ግለሰቦችን የማዋረድ ድርጊት መንግሰትን የሚጠቅመው እንዳልሆነ ግን ግልፅ መሆን አለበት፡፡ የመንግሰትን አቋም እንዲነግሩን የተመደቡ ሰዎች “አይታመኑም” ማለት አጭር እና ግልፅ በሆነ ቋንቋ “መንግስት አይታመንም” ማለት ነው፡፡ የተዓማኒነት ጉድለት ያለበት መንግሰት ሲመራን ደስ አይለንም፤ ለዚህም ነው መንግስት አንዲታመን የምንወተውተው፡፡ ይህ የምንሰጠው አሰተያየት በምንም መልኩ የሀገርን ገፅታ ማበላሸት ሳይሆን፤ ሀገራቸንን ወክለው የሚዋሹትን የመንግሰት ሹማምንት በመምከር ለሀገር ገፅታ ግንባታ መትጋት ነው፡፡ ብንዋሽም ለሀገር ገፅ ግንባታ ሲባል ዝም በሉን ከሆነ መርዕ አልባነት ስለሚሆን መስማት ቢቻልም መስማማት አይቻልም፡፡ ያለምግባባታችን ምንጩ በመርዕ ጉዳይ ያለመስማማት ነው፡፡

የመንግስ ተዓማኒነት የሚጎዱ ብዙ ድርጊቶች ማንሳት ቢቻልም፤ አሁን ደግሞ የፓርቲያችን አባል የሆነውን ሀብታሙ አያሌውን በምንም ምክንያት ቢይዙት መንግሰትን ለመማን በፍፁም ዝግጁ አይደለንም፡፡ መንግሰት ሁሌም እንደሚለው ክምር ማስረጃ አይደለም አንድ ገፅ ማስረጃ ያቀርባል ብለን አንጠብቅም፡፡ ይህን ለማለት የሚያሰደፍር በቂ ተሞክሮ አለን፡፡ ከብዞዎቹ አንዱ አንዱዓለም አራጌን ለእስር ያበቁበት መረጃ ነው፡፡ በህይወቴ ከደነገጥኩበት ቀን አንዱ አንዱዓለም አራጌ የታሳረ ዕለት ነው፡፡ ምከንያቱም የቀረበበት ክስ “ከግንቦት ሰባት” ከሚባለው “ሁሉን አቀፍ” የሚበል የትግል ስልት ከሚከተል በውጭ ሀገር ከሚገኝ ፓርቲ ጋር ግንኙነት አለው የሚል ስለ ነበር ነው፡፡ በወቅቱ አንዱዓለም አራጌ ላይ የሚያቀርቡትን መረጃዎች በጉጉት ነበር ስጠብቅ የነበረው፡፡ ነገር ግን አንድም ማስረጃ ሳይቀርብበት፣ አዳፍኔ ምስክሮችም እንደሰለጠኑት አሟልተው ሳይመሰክሩ የሰላማዊ ትግል ጓዳችን “በአሸባሪነት” ጥፋተኛ ነው ተብሎ እድሜ ልክ ተፈረደበት፡፡ ከዚያን ቀን ወዲህ ማንም ላይ ማስረጃ አለኝ ቢሉ ለማመን እቸገራለሁ፡፡ መንግሰት በሚፈፅማቻው ተግባራት ምክንያት ተዓማኒነቱን እየጎዳው ይገኛል፡፡ ቀበሮ መጣ እንደሚለው ውሽታም እረኛ ማለት ነው፡፡

በእኔ እምነት ከሳሾቹም ሆነ ፈራጆቹ የሰጡት ውሳኔ “ክምር ማስረጃ” አለን ያሉትን የቀድሞውን ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ቃል ለማክበርና ለማስደሰት እንደነበር መጠራጠር አያሰፈልግም፡፡ እርሳቸውም ደስታቸውን ሳያጣጥሙት በተፈጥሮ ህግ ተለይተውናል፡፡ የቀረበውን ክምር ማስረጃ ታሪክ መዝግቦ ይዞታል ከሳሹችም ሆኑ ፈራጅች በታሪክ ፍርድ ፊት እንደሚቆሙበት ቅንጣት ያህል ጥርጥር የለኝም፡፡ ይህንን ጉዳይ አስመልክቶ አሁን በምንፅፈው፣ በምንናገረውም ሆነ ከዚህ በፊት በያዝነው አቋም ሁላችንም የታሪኩ አካል ነን፡፡ ሊፈርድብን ወይም ሊፈርድልን፡፡

የዛሬ ዓመት አካባቢ በደሴ ከተማ ሰላማዊ ሰልፍ ለማስተባበር ከተመደበ ቡድን ጋር ተንቀሳቅሼ ነበር፡፡ ወቅቱ ደግሞ አንድ የሙስሊም የሀይማኖት አባት የተገደሉበት ነበር፡፡ በወቅቱ በደሴ ከተማ የተገነዘብኩት ነገር ቢኖር አብዛኛው የከተማ ነዋሪ “የሀይማኖት አባቱን የገደላች መንግሰት ነው” የሚል መደምደሚያ ላይ ደርሶ ነበር፡፡ በሰልፍ ላይ የተገኙ ሰዎችም “እየገደሉ ገደሉ አሉን” የሚል መፈክር በከፍተኛ ሰሜት እያሰሙ ቅሬታቸውን ሲገልፁ ነበር፡፡ በግሌ መንግሰት በዚህ ደረጃ ወርዶ በግለሰቦች ግድያ መጠርጠሩ ምቾት አልሰጠኝም፡፡ በተለያየ አጋጣሚ ያገኘኋቸውን የመንግሰት ሹሞች በዚህ ደረጃ መንግሰት መጠርጠሩ እንደሚያሳዝን አሁንም ቢሆን መስራት ያለባቸው የተቃዋሚዎች ስራ ነው እያሉ በአላስፈላጊ ፕሮፓጋንዳ ከሚጠመዱ፤ መንግሰትን በዚህ ደረጃ ለመጠርጠር ገፊ የሆነው ችግር ምንጭ ምን እንደሆነ እንዲመረምሩ አሳቤን አካፍያቸው ነበር፡፡ ነገሩ የተገላቢጦሽ ሆኖ እኔንም ከአሽባሪና አክራሪነት ጋር ደምረው ልወደድ ባይ ጋዜጠኞች ዶክመንተሪ ፊልም ሰሩብኝ፡፡ ሀይ የሚል አልነበረውም ይልቁንም በተለያየ አጋጣሚ የማገኛቸው ኢህዴጎች የኢቲቪን ድራማ እያዩ እኔን መኮንን ነው የያዙት፡፡ እኔን በዚህ ደረጃ ከመጠርጠር እራሳቸውን መጠርጠር የሚቀላቸው ይመስለኛል፡፡ የእኔ ጥያቄ መንግስት ለምን በዚህ ደረጃ ይጠረጠራል? የመንግሰት ተዓማኒነት መጎደልን ለማሳየት ከዚህ የተሻለ ማስረጃ ማቅረብ ይከብዳል፡፡ እንዴት መንግሰት በግለሰብ ግድያ ይጠረጠራል? ሹሞቹ ግን ይህ አላሳፈራቸውም ቅድሚያ የሰጡት ለፕሮፓጋንዳው ነው፡፡

የተለያዩ ሀገሮቸን ለመጎብኝት እድል አጋጥሞኛል መንግስት ሊገድልህ፤ ሊያስገድልህ፤ በማጅራት መቺ ሊያስመታህ ይችላል ተብሎ የሚታመንባቸው ሀገሮች እጅግ ጥቂቶች ናቸው፡፡ የወደቁ ወይም በመውደቅ ላይ ያሉ መንግሰታት ናቸው፡፡ የሀገሬ መንግሰት እንዲህ እንዲሆን አልፈልግም፡፡ እንዲህ ዓይነት ግምት የሚሰጡ ሪፖርቶች ሲወጡ መንግትን ስለማልደግፍ ጮቤ አልረግጥም፡፡ ይልቁንም አዝናለሁ፡፡ በቅርቡ አንዲት ሴት መኖሪያ ቤቴ ድረስ መጥታ በከፍተኛ የመንግሰት ሹም ፆታዊ በደል እንደደረሰባት ነገረችኝ፡፡ ለነገሩ ጉዳዩ የግል ግንኙነት ከመሆኑ አንፃር ብዙም ፍርድ ቤት የሚያስኬድ ባሕሪ እንዳለው ባይገባኝም፤ የተነፈገ መብት አለኝ ካለች ፍርድ ቤት እንድትሄድ ነገርኳት፡፡ “ፍርድ ቤት ብሄድም ትርጉም የለውም፤ ይህን ማድረጌን ከሰሙ ያስገድሉኛል፤ አንተ በደንብ አታውቃቸውም አለቸኝ፡፡” ደነገጥኩ!! እውነት ነው ከሷ በላይ አላውቃቸውም፤ በግልፅ አንሶላ ተጋፋ ውስኪ ተራጭታ የሚያደርጉትን ታውቃለች፡፡ በመጨረሻም ከእኔ የምትፈልገው ነገር እኔ ላድርግላት እንደማልችል፤ እኔም ከመስመር አልፎዋል ያሉ ቀን ሊገድሉኝ፣ ሊያስገድሉኝ ካዘኑልኝ ደግሞ እስር ቤት ሊወረውሩኝ እንደሚችሉ አምኜ በድፍረት እንደምንቀሳቀስ ነገርኳት፡፡ ይህን ታሪክ ያነሳሁት መንግስት ከለላ የሚሰጠን ጠባቂያችን ሳይሆን ሊገድለን፣ አደጋ ሊያደርስብን የሚችል ነው ብለን ተዓማኒነት እንድንነፍገው ለምን ሆነ? ብዬ ለመጠየቅ ነው፡፡ የመንግሰት ተቃዋሚ ሆኖ አይደለም፤ መንግሰትን ከሚወክሉት ሹሞች ጋር ሲዳሩ መክረም እንደ ውለታ ተቆጥሮ ዋስትና አይሆንም፡፡ የፈለጉ ቀን ከህግ ሰርዓት ውጭ ማሰገደል የሚችሉ ናቸው፡፡ መንግሰትን የሚወክሉት ሹሞች፡፡ ግን ለምን አንዲህ ሆነ?

መንግሰት ለሚያደርጋቸው ነገሮች፣ ለሚወሰደው እርምጃ ተገማችነት አለመኖር ለተጠርጣሪነት እና ተዓማኒነት ጉድለት እንደሚያጋልጠው እርግጥ ነው፡፡ ይህን መከላከል ሲገባ ደግሞ ይህን የሚያጠናክሩ ድርጊቶችን በተደጋጋሚ ማየት መንግሰት ተዓማኒ አይደለም ብቻ አይደለም አንድ አንድ ሰዎች በድፍረት እንደሚሉት “መንግሰታዊ ውንብድና” ነው፡፡ ያሰገድሉናል የሚባል አቋም ሲያዝ ፍርድ ቤት አቅርበው አንዳለሆነ ግልፅ ነው፡፡ በአህአዴግ መንግሰት ከሁለት ሰዎች በላይ በህግ ውሳኔ በሞት የተቀጣ እንደሌለ እናውቃለን፡፡

ይህንን “የመንግሰትን ተዓማኒነት ጉድለት” የሚመለከት ፅሁፍ እያዘጋጀሁ ሳለ የግሌ አስተያየት እንዳይሆን የፌስ ቡክ ጓደኞቼ አስተያየት እንዲያዋጡ መጠየቅ ፈለጉህ፡፡ እንዲህም ብዬ በፌስ ቡክ ላይ ለጠፍኩ “እባካችሁ የመንግሰትን ተዓማኒነት ጉድለት የሚያሳይ አሳብ አዋጡ!! ከሌላችሁ በእውሽት ላይ የተመሰረተ ክስ ወይም ጠቅላላ አስተያየት ተቀባይነት የለውም፡፡ አመሰግናለሁ ……” የሚል ነበር፡፡ ተቀባይነት የሌላቸው አጠቃላይ አሰተያየቶችን ጨምሮ እጅግ ብዙ አስተያየት በአጭር ጊዜ ቀረበልኝ፡፡ በመሰረታዊነት ህገ መንግስቱን እና ህገ መንግሰታዊ ሰርዓቱን እንዲያከብሩ የሚጠይቅ ሲሆን፤ በግልፅ ምሳሌ ተደርገው ከተጠቀሱት ዋና ዋናዎቹ ከኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ማግስት ባድመን አሰመልክቶ የተሰጠው መግለጫ፣ ዜጎች መንግሰት ላይ እምነት ቢኖራቸው በሚሊዮን ለምን ይሰደዳሉ?፣ ኢቲቪን ተመልከት፣ ፍርድ ቤቶች ምን እየሰሩ ነው፣ የደህንነት ተቋም ለማን ነው የሚሰራው? ምርጫ ቦርድ ገለልተኛ ነው ብለህ ታምናለህ? የሚሉና ከነአካቴው መንግሰት አለ ወይ? የሚሉት ይገኙበታል፡፡ አሰተያየቶቹ ሁሉንም የመንግስት አካላት የዳሰሱ ናቸው፡፡ መንግሰት ዜጎች በዚህ ደረጃ ተዓማኒነት እንዲነሱት ለምን ይተጋል ብለን መጠየቅ የለብንም ትላላችሁ?

ምኞቴ መንግሰታቸን ብለን የምናከብረው መንግሰት አንዲኖረ ነው፡፡ ግልፅ ነው በአሁኑ ስዓት የለንም እያልኩ ነው፡፡ ይህ ደግሞ የሚገለፀው መንግሰትን ወክለው በሚታዩት ሹማምንቶች ባህሪና ተግባር ነው፡፡ የሀገርን ገፅታ ለመግንባት ከሊቅ እስከ ደቂቅ ኃላፊነት እንዳለብን እና ግዴታችን እንደሆነ ባምንም ይህን ከፍተኛ ኃላፊነት ግን ያለምንም ማወላወል በተግባር ሊያውል የሚገባው እና ሞዴል ሊሆነን የሚገባው መንግሰት ነው፡፡ መንግሰት ደግሞ በኃላፊዎቹ ይወከላል፡፡ የእኛ ተግባር ትክክለኛ ስራ ሲሰሩ ሞዴሎቻችን አድርገን መውስድና ትክክለኛ ተግባራቸውን ማስፋት፤ ካልሆነ ደግሞ ያልሆኑትን ናቸው ብለን መቀለድ ሳይሆን አትመጥኑንም ብለን መንገር ነው፡፡ ጆሮ ያለው ይስማ!!!!!

ቸር ይግጠመን

ሁለት ከአማራው ክልል በመጡ የደህነንት የበታች ሃላፊዎች በአቶ ኢሳያስ ጠባቂዎች መገደላቸው ተዘገበ

$
0
0

ምኒልክ ሳልሳዊ እንደዘገበው፦

ባለፈው ማክሰኞ ከምሽት ጀምሮ ቦሌ መስመር ወሎ ሰፈር ከአይቤክ ሆቴል ፊትለፊት ገባ ብሎ ከሚገኘው የደህንነት ቢሮ ውስጥ በተደረገ ስብሰባ ላይ በተፈጠረ የፖለቲካ አለመግባባት ከአቶ ኢሳያስ ወ/ጊ ጠባቂዎች በተተኮሱ ጥይቶች ሁለት ከአማራው ክልል በመጡ የደህንነት የበታች ሃላፊዎች ላይ ግድያ መፈጸሙን ታውቋል።
news
በአማራው ክልል ያሉ እና በህግ በተመዘገቡ ፓርቲዎች ሽፋን የህገወጥ ዲያስፖራ ፓርቲዎችን አላማ የሚያራምዱ የተቃዋሚ አመራሮች ላይ ከምርጫው ቀደም ብሎ ሊወሰድ ስለሚገባው እርምጃ ለመወያየት የተሰበሰበው የደህንነት ጓድ በስብሰባው ወቅት ከፍተኛ አለመግባባት ፈጥሮ እንደነበር የታወቀ ሲሆን በወቅቱም ከአዲስ አበባ ከ13 አመት በፊት ተመልምለው ወደ አማራው ክልል የተላኩት በክልሉ ምስጢራዊ የሆኑ የግድያ እና የአፈና እንዲሁም የስለላ መመሪያዎችን በመቀበል ለጽጥታ ሃይሎች በማስተላለፍ ሲያስፈጽሙ እና ሲፈጽሙ የነበሩ እና በደህንነት ኮድ ስማቸው (አለልኝ እና ብቸናው) የተባሉ የደህንነት የበታች ሹሞች እዛው ስብሰባው መሃል በጸጸት እና በብሶት በቁጣ የተሞላ ጠንካራ ጥያቄዎች በማቅረባቸው በተፈጠረ አለመግባባት የማያዳግም እርምጃ እንደተወሰደባቸው ታውቋል።

የሕወሓት የደህንነት ከፍተኛ ሹሞች ምን ያህል በጥጋብ እና በትእቢት እንደተወጠሩ የሚያመለክተው ይህ ግድያ በስብሰባው ላይ ያሉትን የደህንነት ጓዶች ለማሸበር እና ለመጪው ምንም ዓይነት ጥያቄ እንዳያነሱ እና አለመግባባት እንዳይፈጥሩ ለማስደንገጥ የተደረገ እንደሆነ በግልጽ ያሳያል።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሰራዊቱ ውስጥ እና በደህንነት ተቋማት ውስጥ ያሉ አገልጋዮች ጥያቄዎችን እያነሱ ሲሆን እንዲሁም ከአገር በሚወጡበት አጋጣሚ ሁሉ ወደ ሃገር ቤት እንደማይመለሱ ታውቋል። ባለፈው አመት ለደህንነት ትምህርት ወደ እስራኤል ከተላኩ 67 ጓዶች ውስጥ 23 ወዴት እንደጠፉ የማይታወቅ መሆኑን መረጃውን ያደረሱን ምንጮቻችን ገልጸውልናል።

ኢትዮጵያ በፍርሀት የሞት እና ሽረት ትግል መካከል የምትንጠራወዝ ምስኪን አገር፣

$
0
0

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም

ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ

zone_9_blogger_101405801474

(የጸሐፊው ማስታወሻ) በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ገዥ አካል በቅርቡ ገንቢ ያልሆነእና በእራስ አሸናፊነት ጎልቶ ለመውጣት በሚልዕኩይ ምግባር በተቃዋሚዎቹ እናትችት በሚያቀርቡበት ወገኖች ላይ እየወሰደ ያለውን የቅጣት እርምጃ አሳፋሪ ነው::ገዥው አካልበተደጋጋሚ በሚሰራቸው አስቂኝ የስህተት ቀልዶች (በሚከተላቸውብልሽቶች እና ድሁር አቅመቢስነትእና በሚፈጽማቸው የመድረክትወናዎች(ለአጭር ጊዜ እኩይ ፍላጎቱ እርካታ ሲል በሚያራምዳቸው ውዥንብሮቹበሁለቱምድርጊቶቹ የሚያስደንቅ እና ግራ የሚያጋባሆኗል ፡፡ ገዥው አካል ለምንድን ነው 20እና ከዚያ በላይ የሚሆኑ ጦማሪያንን እና በጣት የሚቆጠሩ ሃያሲ ጋዜጠኞችን ሸፍጥበተመላበትሁኔታ በሀሰት በተፈበረከ እራሱ “አሸባሪነት” እያለ በሚጠራው ክስ ከሶበእስር ቤት አጉሮ ንጹሀን ዜጎችን እያማቀቀ ያለውለምንስነው ክቡር የሆነውንየጋዜጠኝነትን ሙያ እየወነጀሉት ያለውለምንድን ነው ገዥው አካል የአገሪቱንኢኮኖሚ በመዳፉ ስር ጨምድዶይዞ በተጠንቀቅ በአንድ ቦታ ቆሞ የሚጠባበቅወታደራዊ ኃይል እያለው እና ብዛት ያላቸው ጠብመንጃዎች፣ ታንኮች እናየጦርአውሮፕላኖች በእራሱ ቁጥጥር ስር እያሉት በጥቂት ጦማርያን እና ጋዜጠኞች ልቡበፍርኃት እየራደ በጭንቀት ማዕበል ውስጥእየዋኘ የሚገኘውጉልበትን እንጅ ህግንእና ስርዓትን የሚጠየፈው ገዥ አካል በነጋ በጠባ ያዙኝ ልቀቁኝ እያለ በመፎከር የራሱ ጥላ አያስበረገገው ተሸበሮ የሚሸበረው?

በገዥው አካል በኢትዮጵያ የፕሬስ እና ሀሳብን በነጻ የመግለጽ መብት እየተሸረሸረበማለቁ እና በመቶዎች የሚቆጠሩ የነጻው ፕሬስጋዜጠኞችን ወደ እስር ቤት እያጎረያለበት ሁኔታ በመፈጠሩ ምክንያት ኢትዮጵያ “13 የብርሀን ወራት ያላት አገር “መባሏ ቀርቶይልቁንም በጨለማው አህጉር “13 ወራት የጨለማ አገር” ተብላለች ፡፡ በጣም ያስገርመኛል ገዥ አካል በእራሱ የፖለቲካ ምህዋርየሚዞር እና እንደገደል ማሚቶ እያስተጋባ የሚኖር የእራሱ ነጻነት የሌለው ግኡዝ አካል ነውንከዚህአንጻር በኢትዮጵያ ስርዓቱንየሚያሽከረክረው ገዥው አካል በፍርሀት ቆፈን ውስጥተወሽቆ የሞት ሽረት ትግል እያደረገ ያለ ሆኖም ግን በዞን 9 ጦማርያን እናሰላማዊህዝብ እንቅስቃሴ እያወደመ የሚኖር የሽብር መንግስት ሆኗል፡፡ )

በሞት ሽረት ትግል ውስጥ የሚገኙት የዞን 9 ትንታግ ወጣት ጦማርያን

የኔ ጥያቄ እውን በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ ያለው ስርዓት “የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ መንግስት ሬፐብሊክ መንግስት” ነው ወይስ በሽብር ተግባር ላይ ተዘፍቆ የሚገኝ “የፖሊስ መንግስት”? ኢትዮጵያ በሌላ ጠፈር (ህዋ) የምትገኝ አገር ናትን? እነዚህን ጥያቄዎች በጥሞና የማነሳቸው ጥያቄዎች ናቸው፡፡

ኢትዮጵያ በአሁኑ ጊዜ “የፖሊስ ሬፐብሊክ መንግስት” ተብላ ልትጠራ ትችላለች፡፡ በ20ዎቹ አካባቢ የዕድሜ ጣሪያ ላይ የሚገኙ ወጣት ወንዶች እና ሴቶች በፌስቡክ እና በሌሎች የማህበረሰብ ድረገጾች ያለምንም ፍርሀት በመጻፋቸው እና ሀሳባቸውን በነጻ በመግለጻቸው ምክንያት ብቻ በገዥው አካል ሽብርተኛ በሚል የሸፍጥ ፍረጃ እና ክስ በቁጥጥር ስር ውለው በእስር ቤት በመማቀቀቅ ላይ ይገኛሉ፡፡ ባለፈው ሳምንት በኢትዮጵያ ያለው ገዥ አካል 6 ጦማሪያንን እና 3 ጋዜጠኞችን (የዞን 9 ጦማርያን እየተባሉ የሚጠሩትን) በተለምዶ ቃሊቲ እየተባለ በሚጠራው በአስፈሪው የመለስ ዜናዊ የማሰቃያ እስር ቤት ከሚማቅቁት የፖለቲካ እስረኞች የእስር ቤት ቁጥር 8 ቀጥሎ በተሰየመው የማጎሪያ እስር ቤት ለ80 ቀናት ያህል ሲያማቅቅ ከቆየ በኋላ ህገወጥ በሆነ መልኩ ሽብርተኛ የሚል ታፔላ በመለጠፍ መሰረተቢስ የሆነ የሸፍጥ ውንጀላ ክስ መስርቶባቸዋል፡፡

ሀሳባቸውን ያለምንም ፍርሀት በፌስቡክ እና በማህበረሰብ ድረገጽ ነጻ በሆነ መልኩ ከገለጹት ውሰጥ የሚከተሉት ትንታግ ወጣት ጦማሪያን ይገኙበታል፤ አቤል ዋቤላ(በኢትዮጵያ አየር መንገድ በመሀንዲስነት ተቀጥሮ የሚሰራ)፣ አጥናፍ ብርሀኔ(በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሙያ በክፍለ ከተማ ተቀጥሮ የሚሰራ)፣ ማህሌትፋንታሁን (በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር በስታቲስቲክስ ባለሙያነት ተቀጥራ የምትሰራ)፣ናትናኤል ፈለቀ (በኮንስትራክሽን እና ቢዝነስ ባንክ በማኔጀርነት ተቀጥሮ የሚሰራ የኢኮኖሚክስ ባለሙያ)፣ ሲሆን ከዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከሆኑት ጆን ኬሪ ጋር ከዚህ በታች የተነሳውን ፍቶግራፍ ማየት ይቻላል፣ዘላለምክብረት (በአምቦ ዩኒቨርስቲ የህግ ትምህርት መምህር)፣ እና በፈቃዱ ኃይሉ(በቅድስት ማሪያም ዩኒቨርስቲ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ባለሙያ እና በቅርብ ጊዜ ደግሞ የዕንቁ መፅሔት አርታኢ በመሆን ሲያገለግል የነበረ)፡፡ ሌሎቹ በገዥው አካል ህገወጥ ውሳኔ እስረኛ ጦማሪያን የሚከተሉትን ያካትታል፤ ጋዜጠኛ አስማማው /ጊዮርጊስ (ከአዲስ ጉዳይ ጋዜጣ)፣ እና ፍሪላንሰሮች ተስፋሁንወልደየስ (ከአዲስ ስታንዳርድ መጽሔት) እና ኤዶም ካሳዬ (የቀድሞ የአዲስ ዘመን ጋዜጣ ሰራተኛ የነበረች) ናቸው፡፡ ኢትዮጵያውያን/ት ጋዜጠኞች እና ጦማርያንን (ከዚህ በላይ የተጠቀሱትን ጥቂቶችን ጨምሮ) በተጨባጭ እውነታ ላይ በመመስረት የሰጡትን ቃለ መጠይቅ በሚመለከት መሰረቱን በእንግሊዝ አገር ያደረገ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት ቡድን አንቀጽ 19 በሚል ርዕስ በድረገጽ ላይ ያደረገውን ቃለመጠይቅ ከእዚህ ጋ በመጫን ማዳመጥ ይቻላል)፡፡

የሽብርተኝነት ክሱ ዋና ጭብጥ ጦማሪያኑ “በውጭ ከሚንቀሳቀሱ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች ነን ከሚሉ ድርጅቶች ጋር ህብረት በመፍጠር በአገር ውስጥ ሁከት እና እረብሻ ለመፍጠር“ እና “ከውጭ የእርዳታ ገንዘብ በመቀበል ህዝባዊ አመጽ ለመቀስቀስ የማህበረሰብ ድረገጾችን ይጠቀማሉ“ የሚል ነው፡፡

በአማርኛ ተዘጋጅቶ ይፋ የሆነውን የክስ ሰነድ ለማየት ከእዚህ ጋ ይጫኑ፡፡ (በባለአርማ የተጻፈው የመጻጻፊያ ቋሚ ወረቀት ላይ “ኢትዮጵያ” የሚለው የንግሊዘኛ ቃል ቃል በስህተት “ኢትዮያ” ተብሎ መጻፉን ልብ ይሏል)፡፡ አገሪቱ በይፋ በምትጠቀምበት በባለአርማ ወረቀት በታተመው የመጻጻፊያ ደብዳቤ ላይ የአገሪቱን ስም በትክክል መጻፍ ያቃተው ገዥ አካል በጦማሪያኑ ላይ የመሰረተው ክስ ትክክል ይሆናል ብሎ መውሰድ እንደምን ይቻላል? ምን ዓይነት አሳፋሪ ሁኔታ ነው!!!

በሽብርተኝነት ስም የተመሰረተው የውንጀላ ክስ በርካታ ዝርዝር ጉዳዮችን የሚያካትት ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ ሽብርተኝነትን ለመፈጸም ከሌሎች ጋር አብሮ መዶለት፣ የማህበረሰብ መገናኛ ድረገጾችን በመጠቀም የአመጽ ቅስቀሳ ማካሄድ፣ ለኢትዮጵያ ሳቴላይት ቴሌቪዥን/ኢሳት እና ሬዲዮ ዘገባዎችን ማቅረብ፣ ለግንቦት ሰባት የሚሆኑ አባላትን በመመልመል የትብብር አገልግሎት መስጠት፣ በሰው እና በንብረት ላይ አደጋ ሊያስከትሉ የሚችሉ ፍንዳታዎችን ለማካሄድ የአሸባሪነት ስልጠናዎችን መውሰድ፣ ለአሸባሪ ኃይሎች ስልት መንደፍ እና የአሮሞ ነጻነት ግንባርን ፕሮፓጋንዳ መንዛት የሚሉት ናቸው፡፡ ለውንጀላው አስረጅ ይሆናሉ የተባሉ ዝርዝር ሰነዶች በዋናነት በተከላካዮች እጅ የሚገኙትን ብዙ ዲጂታል የኤሌክትሮኒክ መገናኛ ዘዴዎችን መሰረት ያደረገ ነው፡፡ የዩናይትድ ስቴትስ መንግስት መምሪያ በዞን 9 ጦማሪያን ላይ የቀረበውን የክስ ውንጀላ ያለውን ስጋት በመግለጽ ለገዥው አንዲህ ስል አስገንዝቧል፣ “ኢትዮጵያ ነጻ ሀሳብን ከመግለጽ የሚገድበውን የጸረ ሽብርተኝነት ህግ ከመተግበር እንድትቆጠብ“ በማለት መግለጫው የሚከተለውን አውጇል፣ “ሀሳብን በነጻ መግለጽ እና የነጻው ፕሬስ ነጻነት የዴሞክራሲያዊ ማህበረሰብ መሰረታዊ ምርጫዎች ናቸው፡፡ ነጻ ጋዜጠኞችን እና ጦማሪያንን በቁጥጥር ስር በማዋል በጸረ ሽብርተኝነት ህግ ወንጀል ክስ መስርቶ ዜጎችን በፍርድ ቤት ቀጠሮ ማንገላታት በመላ የኢትዮጵያ ህዝቦች ሰብአዊ መብት ጥበቃ እና በመገናኛ ብዙሀን ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ያሳድራል፡፡“ ከዚህም በተጨማሪ ሂዩማን ራይትስ ዎች፣ የጋዜጠኞች ጥበቃ ኮሚቴ እና ሌሎች የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች የዞን 9 ጦማሪያን ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በአስቸኳይ እንዲፈቱ መግለጫ በማውጣት ጥያቄ አቅርበዋል፡፡

በሀሰተኛዋ ሬፐብሊካዊት ኢትዮጵያ

በሀሰተኛዋ ሬፐብሊካዊት ኢትዮጵያ ጋዜጠኞች በእስር ቤት ታጉረው ይጠበቃሉ፣ እናም የሙያ ስነምግባራቸውን በመተግበራቸው ብቻ በእስር ቤት እንዲማቅቁ ይደረጋሉ፡፡ እ.ኤ.አ የ2014 ትልቅ ክብር ያለውን እና ዓመታዊ ለፕሬስ ነጻነት አሸናፊዎች የሚሰጠውን ወርቃማውን የብዕር ሽልማት ከዓለም ጋዜጦች እና ዜና አታሚዎች ማህበር (ሌሎች በርካታ ዓለም አቀፍ የፕሬስ ሽልማቶች አሸናፊ የሆነው) በቅርቡ የተሸለመው እስክንድር ነጋ በነጻ በመጻፉ ብቻ የ18 ዓመታት እስራት ተበይኖበታል፡፡ የ34 ዓመቷ ሴት ጀግና ወጣት እና የኢትዮጵያ ፕሬስ ነጻነት ቀንዲል የሆነችው እንዲሁም በዓለም አቀፍ ደረጃ ዕውቅናን የተጎናጸፈችው “እውነት ተናጋሪዋ እስረኛ“ እየተባለች የምትጠራው እና የበርካታ ዓለም አቀፍ የፕሬስ ሽልማቶችን አሸናፊ የሆነችው ርዕዮት ዓለሙ የገዥውን የፖለቲካ ፓርቲ በአገር አቀፍ የግድብ ፕሮጀክት የገንዘብ ማሰባሰቢያ ዘዴ ላይ የሰላ የጽሁፍ ትችት በማቅረቧ እና በሞት በተለዩት በመለስ ዜናዊ እና አሁን በህይወት በሌለው በሊቢያው አምባገነን መሪ በሞአማር ጋዳፊ መካከል ምንም ዓይነት ልዩነት የሌላቸው አምባገነኖች ናቸው በማለቷ ብቻ የ14 ዓመታት እስራት ተበይኖባታል፡፡ ሌላው የዓለም ዓቀፍ የፕሬስ ሽልማት አሸናፊ የሆነው ትንታግ ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ ሲያዘጋጀው በነበረው ጋዜጣ ላይ የገዥው አካል በሙስና የበከተ መሆኑን እና የያዘውን ስልጣንም ከህግ አግባብ ውጭ እየተጠቀመ መሆኑን በመግለጹ ብቻ የ14 ዓመታት እስራት ተፈርዶበታል፡፡ በዚህ ዓይነት ጉዳይ ላይ የሚጽፉ እና የዜግነት ግዴታቸውን ለመወጣት ሲሉ ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ የሚፋለሙ ሌሎች በርካታ የነጻው ፕሬስ ጋዜጠኞች አሉ፡፡

በሀሰተኛዋ ሬፐብሊካዊት ኢትዮጵያ ጋዜጠኞችን፣ ጦማሪያንን፣ የተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችን እና ሰላማዊ አማጺያንን በመወንጀል፣ ስማቸውን ጥላሸት በመቀባት እና ኢሰብአዊ ድርጊትን በመፈጸም አሸባሪዎች፣ አመጸኞች እና ሌላ ሌላም በመሰየም ይፈርጇቸዋል፡፡ አሁን በህይወት የሌለው የገዥው አካል ቁንጮ መሪ እና ዘዋሪ፣ አድራጊ እና ፈጣሪ የነበረው አምባገነኑ መለስ ዜናዊ እ.ኤ.አ የ2005 አገር አቀፍ ምርጫን ተከትሎ በተፈጠረው ቀውስ የበርካታ ጋዜጦች አታሚዎችን በእስር ቤት ካጎረ በኋላ በነጻው ፕሬስ ላይ ጦርነት በማወጅ እንዲህ የሚል መግለጫ ሰጥቶ ነበር፣ “ለእኛ እነዚህ ጋዜጠኞች አይደሉም፣ የፕሬስ ህጉን ጥሰዋል ተብለው ክስ አይመሰረትባቸውም፡፡ እንደ ለቅንጅት ለአንድነት እና ለዴሞክራሲ አመራሮች በአገር ክህደት ወንጀል ይከሰሳሉ“ በማለት ሲሳለቅ የነበረ መሆኑ የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነው፡፡ እ.ኤ.አ በ2011 ፈላጭ ቆራጩ መለስ ዜናዊ ጆን ፔርሰን እና ማርቲን ሽብዬ የተባሉትን ስዊድናዊ ጋዜጠኞች በቁጥጥር ስር በማዋል ወደ ዘብጥያ ከወረወረ በኋላ እንዲህ በማለት ፈርጇቸው ነበር፣ “የሽብርተኛ ድርጅት ተላላኪዎች“ እንዲህ ሲል ተሳልቋል፣“እነዚህ ወንጀለኞች አሁን እየሰሩት ያለው ጋዜጠኝነት የሚያሰኝ ከሆነ እኔ እራሴ ሽብርተኝነት ምን እንደሆነ አላውቅም ማለት ነው“ በማለት የተለመደውን የቅጥፍና ፍልስፍና አሰምቶ ነበር፡፡

በሀሰተኛዋ ሬፐብሊካዊት ኢትዮጵያ ጋዜጠኝነት ማለት አሸባሪነት ማለት ነው፡፡ ጋዜጠኞች ለመንግስት ጠላቶች ናቸው፡፡ መጦመር ወይም መጻፍ የሀገር ክህደት ወንጀል ነው፡፡ ጦማሪያን የመንግስት ደመኛ ጠላቶች ናቸው፡፡

በሀሰተኛዋ ሬፐብሊካዊት ኢትዮጵያ የእንግሊዝ ዜግነት ያለው የተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲ አመራር በየመን በአውሮፕላን በትራንዚት ላይ እያለ አስነዋሪ እና አሳፋሪ የሆነ የጠለፋ ወንጀል ተፈጽሞበታል፣ እናም ከህግ አግባብ ውጭ በሆነ መልኩ ዓለም አቀፍ ህግን በመደፍጠጥ ወደ ዘብጥያ እንዲወረወር ተደርጓል፡፡

በሀሰተኛዋ ሬፐብሊካዊት ኢትዮጵያ ሰዎች ኢሰብአዊነት ድርጊት ይፈጸምባቸዋል፣ ስልጣኔ ወደ ኋላቀርነት ይቀየራል፣ ፍትህ በሙስና ይጣመማል፣ የጎሳ ማጥራት ዘመቻ ይካሄዳል፣ ህዝቦች በድህነት እንዲማቅቁ እና የረሀብ ሰለባ እንዲሆኑ ይደረጋል፣ ወጣቶች በችግር እንዲጠረነፉ ይደረጋል፣ የግዳጅ ስራ እንዲሰሩ ይደረጋል፣ ሰካራም እንዲሆኑ እንዲሁም የጫት እና የሌሎች ሱሶች ተገዥዎች እንዲሆኑ ስልታዊ ስራ ይሰራል፣ ተፈጥሯዊ ከባቢያችን እንዲወድም ይደረጋል፣ ግድቦች በዘላቂነት በአንድ ቦታ አካባቢ የሚኖሩትን የወገኖቻችንን ህይወት በሚጎዳ መልኩ በመገደብ በህብረተሱ ዘንድ መቅሰፍታዊ አደጋ እንዲመጣ ይደረጋል፣

በሀሰተኛዋ ሬፐብሊካዊት ኢትዮጵያ ድህነት ሀብታምነት ማለት ነው፣ ረሀብ ማለት በጥጋብ መወጠር ማለት ነው፣ የመንግስት በስህተት መዘፈቅ የሰብአዊ መብት ማክበር ማለት ነው፡፡ ጭቆና ፍትሀዊነት ነው፣ እናም ወሮበልነት ዴሞክራሲያዊነት ማለት ነው፡፡

በሀሰተኛዋ ሬፐብሊካዊት ኢትዮጵያ ድንቁርና ምሁርነት ነው፡፡ የመንግስት ዋና ዓላማ ህዝቡን አደንቁሮ ለማቆየት እና በህገወጥነት መንገድ ለመግዛት እውነታውን ማጣመም፣ መወጠር እና እውነታውን ማፍተልተል፣ ጸጥ ማድረግ እና ምንም ሳያስቡ ባላወቁት እና ባላመኑበት ነገር ላይ ስምምነት እንዲያደርጉ ማስቻል ነው፡፡

በሀሰተኛዋ ሬፐብሊካዊት ኢትዮጵያ ወሮበሎች ይገዛሉ! ወሮበሎችን መፍራት የህግ የበላይነት ማለት ነው!

በዞን 9 ሰላማዊ እንቅስቃሴ ምክንያት የሚደረግ የፍርሀት የሞት ሽረት ትግል፣

በ196ዎቹ አመታት ሮድ ሴርሊንግ በተባለ በአንድ ታዋቂ እና ተወዳዳሪ በሌለው “የሞት ሽረት ትግል” በተሰኘ ተከታታይ የቴሌቪዥን የተውኔት ደራሲ አስፈሪ ተውኔቶችን፣ ጭንቀት የተሞላበት እና በጣም አስቸጋሪ የሆነ የአውዳሚነት ባህሪን የተላበሰ የሳይንስ ልብወለድ ድርሰት ተዘጋጅቶ ቀርቦ ነበር፡፡ በአንድ ትርኢት ያቀርበው ታሪክ የቤተመጽሐፍት ባለሙያ ሰው ላይ የተመሰረተ ነበር:: ይህ የቤተመጽሐፍት ባለሙያ “አታስፈለግም” የሚል ክስ ቀርቦበት ነበር:: በዚህ በቀረበበት ክስ ምክንያት የሞት ፍርድ ሊበየንበት እንደሚገባ የግዛቱ አስተዳዳሪ የሆነው ባለስልጣን በችሎት በተሰየመው የዳኞች ስብሰባ ፊት በመገኘት ችሎቱን ለማሳመን ሞከረ፡፡ በፍርድ አሰጣጥ ሂደቱ ወቅት ባለስልጣኑ ( ቻንስለሩ) እና የቤተመጽሐፍት ባለሙያው በሰው ልጅ ክብር ላይ በሚከተለው መልኩ ጠንካራ የሆነ ክርክር በማድረግ ስራ ላይ ተጠመዱ፣

ባለስልጣኑ (ቻንስለሩ) (ለቤተመጽሐፍት ባለሙያው)፡ “አንተ የማታስፈለግ ባለሙያ ነህ!

የቤተመጽሐፍት ባለሙያው፡ የመጽሐፍ ገጾችን በማቃጠል እውነታውን ልታወድም እንደማትችል ከማሳሰብ የዘለለ ሚና የለኝም!

ባለስልጣኑ፡ አንተ ትኋን ነህ፡፡ በመሬት ላይ የምትሳብ ነብሳት፡፡ አስቀያሚ እና ምንም ዓይነት ቅርጽ የሌለህ ዓላማ ቢስ አናሳ ፍጡር ነህ! ምንም ዓይነት ስራ የለህም…“

የቤተመጽሐፍት ባለሙያ፡ “እኔ ሰብአዊ ፍጡር ነኝ…”

ባለስልጣኑ፡ “አንተ የመጽሐፍት አከፋፋይ ነህ፣ በመጽሐፍት ማውጫ መደርደሪያው መስመር ላይ ትርጉም የለሽ የሆኑ ቃላትን በኃይል በማውጣት በተዘጋጀው የመጽሐፍት መደርደሪያ ላይ ሁለት ሳንቲም የሚያወጡ ጥራዞችን እያወጣህ የምትደርድር ከንቱ ፍጡር ነህ፡፡ ምንም ዓይነት ዋጋ የሌላቸው ቃላት፣ እንደ ነፋስ፣ ምንም ዓይነት አቅጣጫ የሌላቸው ናቸው፡፡ እንደ ባዶ ህዋ በትንሽ ካርድ ላይ አመልካች ቁጥሮችን በመደርደር ትርጉም የለሽ ምልክት በማድረግ ህልውና እንዳለህ በመቁጠር እምነት እንዲያድርብህ ታደርጋለህ፡፡“

የቤተመጽሐፍት ባለሙያው፡ “እኔ ደንታዬ አይደለም፡፡ ነግሬሀለሁ፣ ደንታዬ አይደለም፡፡ ሰብአዊ ፍጡር ነኝ፣ እኖራለሁ… እናም አንድን ሀሳብ ከፍ በማድረግ በተናገርሁ ጊዜ ያ ሀሳብ በዘላቂነት ይኖራል ወደ መቃብር ከተወረወርኩ በኋላም ቢሆን እንኳ፡፡“

ባለስልጣኑ፡ እነዚህ ሁሉ ከንቱ የውሸት እምነቶች ናቸው!! የማተሚያ ቀለሙን በደምህ ውስጥ በማዋሀድ መጽሐፍ ቅዱስ፣ ግጥም፣ ድርሰት እና ሌላም ነገር ሁሉ ስነጽሁፍ እያልክ የምትጠራውን አደንዛዥ ዕጽ በመውሰድ ምንም ዓይነት ኃይል ሳይኖርህ ኃይል እንዳለህ አድርገህ እራስህን ትቆጥራለህ!!! አንተ ምንም ማለት አይደለህም፣ ሆኖም ግን አንተ ማለት የሚንቀሳቀሱ የእጆች እና እግሮች ቅርጽ አንዲሁም ህልም ብቻ ያሉህ ፍጡር ነህ፡፡ እናም መንግስት አንተ የዋህ በመሆንህ የሚያገኘው አንዳችም ጥቅም የለም!!! ጊዚያችንን አቃጥለሀል፣ እናም ያቃጠልከውን ጊዜ ያህል ጠቀሜታ የሌለህ ከንቱ ፍጡር ነህ፡፡

ፍርድ ቤቱ የሞት ቅጣቱን ውሳኔ የቤተመጽሐፍት ባለሙያ ላይ ተግባራዊ አደረገ፡፡

የቤተመጽሐፍት ባለሙያው ድፍረት በተመላበት መልኩ የሞት ቅጣቱን ዕጣ ፈንታ በጸጋ ተቀበለ፡፡ ጨካኝ አረመኔዎቹ ምህረትን እንዲያደርጉለት ከመጠየቅ ይልቅ የእራሱን ሰብአዊ ክብር እና ነጻነት ለማስጠበቅ ሲል ከኃይለኞቹ ጉልበተኞች ፊት በጽናት ቆመ፡፡ ሁለት ልዩ የሆኑ ጥያቄዎችን አቀረበ፣ 1ኛ) በምን ዓይነት መንገድ የሞት ቅጣቱ ሊፈጸምበት እንደሚገባ እንዲመርጥ የሞት ቅጣቱን የወሰኑበት እብሪተኞች ዕድል እንዲሰጡት ጠየቀ፣ 2ኛ) የሚፈጸምበት የሞት ቅጣት እና በመሬት ላይ በህይወት የሚቆይባቸው የመጨረሻዎቹ ጥቂት ሰዓታት በቴሌቪዥን ለህዝብ ይፋ እንዲደረግ ጠየቀ፡፡ ሁሉም ዝግጅት ከተጠናቀቀ በኋላ የቤተመጽሐፍት ባለሙያው የሞት ቅጣቱን የሚያስፈጽመውን ባለስልጣን ወደ ማቆያ ክፍሉ ለመጨረሻ ጊዜ እንዲመጣ ጋበዘው፡፡ ባለስልጣኑ/ቻንስለሩ የሞት ቅጣቱ ከሚፈጸምበት ጊዜ ጥቂት ደቂቃዎች ቀደም በማለት ደረሰ፡፡ ለጥቂት ደቂቃዎች ተወያዩ፡፡ የውይይታቸው ዳህራ እንደሚከተለው ቀርቧል፣

የቤተመጽሐፍት ባለሙያ፡ እዚህ ድረስ ጥያቄዬን አክብረው በመምጣትዎ አመሰግናለሁ፡፡

ባለስልጣን፡ ለመሆኑ ለምን እንደመጣሁ ታውቃለህ?

የቤተመጽሐፍት ባለሙያ፡ አዎ እንዲመጡ ስለጋበዝኩዎ ነው፡፡

ባለስልጣን፡ እዚህ አንተ ጋ ለምን እምደመጣሁ ልነግርህ እፈልጋለሁ፡፡ ምናልባት ስለአንተ ጉዳይ አንድ ነገር ለማረጋገጥ ነው፡፡

የቤተመጽሐፍት ባለሙያ፡ እና ያ….?

ባለስልጣን፡ መንግስቱ ምንም ዓይነት ፍርሀት የለውም፣ ይህንን ላረጋግጥልህ ነው የመጣሁት፡፡ በምንም ዓይነት መልኩ ቢሆን ምንም ፍርሀት የሚባል ነገር የለም፣ ምንም…

የቤተመጽሐፍት ባለሙያ፡ ክቡር ባለስልጣን እንደዚህ ላለ የተለቀቀ ፌዝ ይቅርታ እንዲያደርጉልኝ እጠይቃለሁ…ማለቴ ወደ እኔ ማቆያ ክፍል የመጡት መንግስት… እኔን የማይፈራኝ መሆኑን ለመግለጽ ነውን!? እኔ ለምንድን እንደዚህ ያለ የማይታመን ሸክም ለመሆን እንደቻልኩ የሚገርም ጉዳይ ነው! መንግስት አንድ እንደ እኔ ያለውን ያረጀ የቤተመጽሐፍት ባለሙያ የማይፈራ መሆኑን ለማረጋገጥ እዚህ ድረስ መምጣቱ የሚያስደንቅ ነው፡፡ ኦ! አይደለም፡፡ እዚህ ድረስ የመጡበትን ምክንያ በግልጽ ልነግርዎት እፈልጋለሁ… እርስዎ ለእራስዎ ለመቀበል ፈቃደኛ ባይሆኑም እንኳ ምክንያቱን እንግረወታለሁ፡፡

ባለስልጣን፡ ያ ለምን መሆን እንዳለበት አሁን ጥያቄ የማቅረብ ተራው የእኔ መሆን የለበትምን?

የቤተመጽሐፍት ባለሙያ፡ የእርስዎን መስፈርት አላሟላም፡፡ የእርስዎ መንግስት ሁሉንም ነገር ፈርጆ አስቀምጧል…መለያ ቁጥር እና ኮድ ሰጥቷል፣ እንደዚሁም የመለያ ተለጣፊ ጸሑፍ/ታግ ሰጥቷል፡፡ እንደ እርስዎ ያሉ ሰዎች ኃያል ናቸው፡፡ እንደ እኔ ያሉ ሰዎች ደግሞ ደካሞች ናቸው፡፡ እርስዎ ስርዓትን ይቆጣጠራሉ፤ እናም ያስገድዳሉ… እኔ እና መሰል ደካሞች ፍጡራን ደግሞ እርስዎን መከተል እና መታዘዝ ነው፡፡ ሆኖም ግን አንድ ነገር ስህተት ተሰርቷል፣ አይደለምን? ለዚህ ጉዳይ ተስማሚ አይደለሁም፣ ነኝ እንዴ?

የቤተመጽሐፍት ባለሙያው ለባለስልጣኑ ማሳየት የፈለገው ህዝቦች በምን ዓይነት መንገድ ክብራቸው እና ሰብዕናቸው መጠበቅ እንዳለበት መከራከር እና መብትን መጠየቅ ለሞት ቅጣት እንደሚያደርስ አየተከራከረ ከዳዊት መዝሙር ምዕራፍ 23 እና 53ን ማንበብ ጀመረ ፡፡ በቴሌቪዥን ህዝቡ የቤተመጽሐፍት ባለሙያው እና ባለስልጣኑ ክርክር ሲያደርጉ ይመለከታል፡፡ የሞት ቅጣት የሚፈጸምበት ጊዜ እየተቃረበ ሲመጣ ባለስልጣኑ የቤተመጽሐፍት ባለሙያውን ክፍል ለቅቆ ለመውጣት ሞከረ፡፡ ሆኖም ግን የክፍሉ በር ተዘግቶ አገኘው፡፡ የሞት ቅጣቱ ሰዓት እኩለ ሌሊት መሆኑን ከማመልከቱ በፊት ባለስልጣኑ በጭንቀት ማዕበል ውስጥ ሰምጦ የሚይዝ የሚጨብጠውን አጣ፡፡ የቤተመጽሐፍት ባለሙያው ግን በተረጋጋ መንፈስ እና ከፍርሀት በጸዳ መልኩ ይመለከት ነበር፡፡ ባለስልጣኑ የቤተመጽሐፍት ባለሙያው የተቆለፈውን በር እንዲከፍትለት እና መውጣት እንዲችል እንዲህ በማለት ለመነው፣ “በእግዚአብሔር ስም ይዠሀለሁ ከዚህ ክፍል ውስጥ ልውጣ!“ የቤተመጽሐፍት ባለሙያው ደስታ በተቀላቀለበት ሁኔታ ሆኖም ግን መንግስት “እግዚአብሔር እንደማይኖር ያረጋገጠውን” ቃል ሳይደግም ባለስልጣኑ እንዲወጣ በሩን ከፈተለት፡፡ ከዚያ በኋላ ባለስልጣኑ በደረጃው ላይ አድርጎ ከክፍሏ በመውጣት ቁልቁል እየወረደ ከውስጥ ባለው የቤተመጽሐፍት ባለሙያ ክፍል ላይ የእሳት ቃጠሎ ተነሳ፡፡ በመጨረሻው ሁኔታ ባለስልጣኑ እንደ ወንጀለኛ የተፈረጀ እና አስፈላጊ አንዳልሆነ ወደ ፍርድ ሰጭ ጉባኤው ተመለሰ፡፡ የምክንያቱም ፍርሃት በማሳየት ያለዉን መንግስት መሳቂያ ስላደረገ:: ፈራጆቹ ባለስልጣኑን በጠረጴዛ ላይ በመጎተት እስከሚሞት ድረስ ጨፈጨፉት፡፡

በኢትዮጵያ ያለው ገዥ አካል ጋዜጠኞችን እና ጦማሪያንን አሸባሪ ብሎ በመፈረጅ ጭካኔ በተመላበት ሁኔታ እያሰቃዬ በተጨባጭ እነርሱ “የማያስፈለጉ” ናቸው በማለት በመዘባበት ላይ ይገኛል፡፡ እንዲሁም “ትኋኖች እና የሚሳቡ ነብሳት ናቸው” ይላል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ “እነርሱ መጥፎዎች፣ የተበላሸ ቅርጽ ያላቸው፣ ምንም ዓይነት ዓላማ የሌላቸው እና ትርጉምየለሽ ፍጡሮች ናቸው!” ይላል፡፡ ገዥው አካል እንዲህ በማለት ይነግራቸዋል፣ “በሳንቲም የሚሸጡ ጋዜጦች፣ መጽሔቶች እና በድረገጽ የሚለቀቁ ኃይል ያዘሉ ትርጉም የለሽ ጽሑፎች አከፋፋዮች ናቸው፡፡“ “ምንም ዓይነት ጥራት የሌላቸው እንደ ነፋስ እና እንደ አየር ምንም ዓይነት ቅርጽ የሌላቸው፣ እንደ ህዋ ባዶ የሆኑ፣ ጋዜጠኞች እና ጦማሪያን ቃላትን በጋዜጦች፣ በድረገጾች እና በብሎጎች ላይ በመሞነጫጨር የሚኖሩ ትርጉመ ቢስ ፍጡሮች ናቸው” በማለት በህዝቡ ዘንድ እምነት እንዳይጣልባቸው ይዘባበታሉ፡፡

በሴርሊንግ ታሪክ እንደ የቤተመጽሐፍት ባለሙያው ሁሉ በእስር ላይ የሚገኙት የዞን 9 ጦማሪያን እና የነጻው ፕሬስ ጋዜጠኞች ጸጥታ በተላበሰ መልኩ እንዲህ በማለት ሀሳባቸውን ይገልጻሉ፣ “እኛ ሰብአዊ ፍጡሮች ነን… ገዥው አካል ስለሚናገራቸውም ሆነ ስለማይናገራቸው ነገሮች ደንታ የለንም፡፡ አለን፣ እንኖራለን… እናም አንድ ነገር ድምጻችንን ከፍ አድርገን በተናገርን ቁጥር ያ ሀሳብ ለዘለቄታው ይኖራል፣ እኛ ወደ መቃብር ከተወረወርን በኋላ እንኳ ቀጣይነት ይኖረዋል፡፡“ ገዥው አካል “ስርዓትን መቆጣጠር እና ማስገደድ” ይችላል፣ ሆኖም ግን የዞን 9 ጦማሪያን እና ጋዜጠኞች “እንደ ቀላል ነገር በዘፈቀደ የሚከተሉ እና የሚታዘዙ አይደሉም” በውሸታሟ ሬፐብሊካዊት ኢትዮጵያ ላይ አንድ መሰረታዊ የሆነ ስህተት ተከስቷል! በእስር ላይ የሚገኙት ጋዜጠኞች እና ጦማሪያን መስፈርቱን አያሟሉም፡፡

“የማያስፈለጉት” የውሸታሟ ሬፐብሊካዊት ኢትዮጵያ ወንዶች እና ሴቶች ወይስ የማያስፈለጉት የውሸታሟ ሬፐብሊካዊት ኢትዮጵያ መሪዎች?

ሮድ ሴርሊንግ አሁን ቢኖር ኖሮ የውሸታሟ ሬፐብሊካዊት ኢትዮጵያ የጽሑፉ ትረካ መግቢያ በሚከተለው መልክ ይናገር ነበር:

(የተራኪው ድምጽ፡፡) በአሁኑ ጊዜ የአፍሪካ የፖሊስ መንግስት ገዥ የወሮበላ ስብስብ በብረት ጡንቻቸው ህዝብን ቀጥቅጠው በመግዛት ላይ ይገኛሉ፡፡ በግልጽ ለመናገር “የአፍሪካ የወሮበላ አገዛዝ” ነው በአህጉሪቱ ተንሰራፍቶ ያለው፡፡ ዋናው ዓላማቸው፣ “የተቃዋሚ ቡድኖች ምርጫችንን ዋጋ የሚያሳጣ የኃይል እርምጃ የሚወስዱ ከሆነ በሙሉ ኃይላችን እንደመስሳቸዋለን፡፡ ለዘላለም በእስር ቤት ውስጥ ሆነው ይበሰብሳሉ፡፡“ በዚህ የወሮበላ አገዛዝ ስርዓት ውስጥ በህሊና መኖር እና ማሰብ ወንጀል ነው፡፡ በስልጣን ላይ ላሉት ሸፍጠኞች እውነቱን መናገር ወንጀል ነው፡፡ ሰላማዊ ተቃውሞ ወንጀል ነው፡፡ የአንድን ሰው ህይወት ለመሸጥ ተቃውሞ ማሰማት ወንጀል ነው፡፡ ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ እና ለሰብአዊ መብት ጥበቃ መከበር መቆም ወንጀል ነው፡፡ የህግ የበላይነት እንዲጠበቅ መሟገት እና መከራከር ወንጀል ነው፡፡ ሰላማዊ በሆነ መልክ መንግስታዊ ሽብርተኝነትን ለማስቆም መታገል ወንጀል ነው፡፡

በዚህ የአፍሪካ የወሮበላ አገዛዝ ጋዜጠኝነት በሞት የሚያስቀጣ ወንጀል ነው፡፡ ጦማሪነት ወይም ጸሐፊ መሆን በሞት የሚያስቀጥ ወንጀል ነው፡፡ ማንም ቢሆን በዥው አካል ላይ ትችት ካቀረበ በጆሮ ጠቢ ደህንነት ወይም በጦር ኃይል ይታፈናል፣ ይታሰራል፣ ይሰቃያል፣ እንዲሁም ይሰወራል፣ ይገደላል፡፡ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ባመጹ ጊዜ በአነጠጥሮ ተኳሾች በጥይት ይደበደባሉ፡፡ ሰላማዊ አመጸኞች በተጭበረበረ የምርጫ ውጤት ምክንያት ተቃዎሟቸውን ለማሰማት ወደ አደባባይ በወጡ ጊዜ በይፋ በጥይት በመንገዶች ላይ ይደበደባሉ፡፡ የወሮበላ አገዛዝ ስርዓት እድሜውን ለማራዘም እና በስልጣን ላይ እንደ መዥገር ተጣብቆ ለመቆየት ሲል ከውጭ የሚገኝ የገንዘብ እና የማቴሪያል እርዳታ ይጠቀማል፡፡

(ተራኪው የካሜራ እይታ፡፡) በእራስህ ኃላፊነት አዝሂች የውሸታሟ ሬፐብሊካዊት አገር ትገባለህ ፡፡ ይህ አዲስ አገዛዝ አይደለም፡፡ ይልቁንም ከዚህ በፊት የነበረው የቀድሞው ያፍዝ ያደንግዝ አገዛዝ ስርዓት ቅጥያ ነው፡፡ ከእያንዳንዱ አምባገነን መሪ በኋላ በታሪክ ሂደት ውስጥ የእራሱን አምባገነናዊ ስርዓት እና ባህል ጥሎ ካለፈው አምባገንን የሚመነጭ ነው፡፡ በአሁኑ ጊዜ የሰብአዊ መብትን እና ነጻነትን ለማፈን የቴክኖሎጂ መስፋፋትን እና ምጥቀትን በመሳሪያነት ይጠቀማሉ፡፡ ሆኖም ግን ከእነርሱ በፊት እንደነበሩት አገዛዞች ሁሉ እነዚህም አንድ ዓይነት የመቀጥቀጫ የብረት ጡንቻ አላቸው፡፡ ምክንያታዊነት ጠላት ነው እናም እውነት አደጋ ላይ ወድቋል፡፡ (ካሜራ ወደ ተከሰሱት ተከላካዮች ፊቱን ያዞራል፡፡) እነዚህም የዞን 9 ጦማሪያን፣ ጋዜጠኞች፣ ዜና ዘጋቢዎች፣ አታሚዎች እና አርታዒኦች በወሮበላው አገዛዝ በአሸባሪነት ተከስሰው በእስር ቤት በመማቀቅ ላይ ይገኛሉ፡፡ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሊወገዱ የሚችሉ የአንድ መንግስት ዜጎች ናቸው ምክንያቱም ከስጋ የተሰሩ ፍጡሮች እና የሚያስቡበት አእምሮ እና ስቃይን የሚመለከቱበት ልብ አላቸው፡፡

“ባላስፈላጊ ሰው” ተራኪው እንዲህ በማለት ማጠቃለያ ሰጠ፣ “ባለስልጣኑ/ቻንስለሩ አሁን በህይወት የሌለው ባለስልጣን ብቻ ነበር ትክክለኛው ሰው፡፡ እርሱ አስፈላጊ ሰው አይደለም፣ እንዲሁም ያመልክበት የነበረው አሁን በስልጣን ላይ ያለው መንግስትም አስፈላጊ አይደለም፡፡“ በስልጣን ላይ ያለ ማንም መንግስት፣ የትኛውም አካል ቢሆን እና የትኛውም የአመለካከት ፍልስፍና ጠቃሚነትን፣ ክብርን፣ የሰውን ልጅ መብት መጠበቅ ከግምት የማሰያስገባ ወዳቂ ከሆነ ያ መንግስት አስፈላጊ አይደለም፡፡

በህይወት የተለየው የውሸታሟ ሬፐብሊካዊት ኢትዮጵያ ባለስልጣን/ቻንስለር እና የመሰረተው መንግስት እና አምልኮ አስፈላጊ አይደለም!

ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!

ሀምሌ 17 ቀን 2006 ዓ.ም


ምርጫ በአንድነት ዉስጥ፣ ለአቶ በላይ ፍቃደ ድጋፌን እሰጣለሁ ( ግርማ ካሳ)

$
0
0

ምርጫ በአንድነት ዉስጥ፣ ለአቶ በላይ ፍቃደ ድጋፌን እሰጣለሁ ( ግርማ ካሳ)

 

10537095በኢትዮጵያ አንጋፋ ከሚባሉ የፖለቲካ ድርጅቶች መካከል የሚገኙት፣ መኢአድ እና የአንድነት ፓርቲ ዉህደት በቅርቡ ይፈጽማሉ ተብሎ ይገመታል።

በዚህ ዙሪያ፣ ይችን ሰሞን በሶሻልሜዲያዎች፣  አንዳንድ ጤናማ ዉይይቶችን  እያነበብኩኝ ነው። የአንድነት ፓርቲ በቅርቡ ከመኢአድ ጋር ሲዋሃድ ፣ መጀመሪያ የአንድነት እና የመኢአድ ጠቅላላ ጉበኤ፣  የምርጫ ቦርድ ሃላፊዎች ባሉበት በተናጥል ይደረጋሉ።  ለዉህዱ ፓርቲ የሚቀርቡ ተወካዮችን እና ዉህዱ ፓርቲን የሚመሩ እጩ  ተወዳዳሪዎች ንያቀርባሉ።በነጋታዉ ከሁለቱም ፓርቲዎች እኩል የተወጣጡ ተወካዮች ያሉበት የዉህዱ ፓርቲ  ጠቅላላ ጉባኤ፣  የዉህዱን ፓርቲ ሊቀመንበር ይመርጣል።

የተከበሩ  ኢንጂነር ግዛቸው ከስድስት ወራት በፊት የአንድነት ፓርቲን እንዲመሩ መመረጣቸው  ይታወቃል።  የመኢአድ እና  የአንድነት  ዉህደት  ሲጠናቀቅ ፣  አንድነትም፣  መኢአድም  እንደ  ድርጅት  ይከስማሉ።  አዲስ  ድርጅት  ነው የሚፈጠረው።  በመሆኑም የኢንጂነር ግዛቸው ምሊቀመንበርነት ከአንድነት  ፓርቲ  ጋር አብሮ  ይከስማል። ኢንጂነር ግዛቸው የዉህዱፓርቲ ሊቀመንበር መሆንከፈለጉ፣  እንደገና ተወዳድረው  መመረጥ ይኖርባቸዋል። ለዚህም ነው ለዉህዱ ፓርቲ ሊቀመንበርነት ለመወዳደር፣  በአንድነት ፓርቲ በኩል እጩ ሆኖ ለመመረጥ፣ ራሳቸዉን ለእጩነት ያቀረቡት።

ከኢንጂነር ግዛቸው በተጨማሪ፣ የአንድነት ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር አቶ በላይ ፍቃዱ እንዲሁም የአንድነት ሥራ አስፈጻሚ አባል እና የቀድሞ የአንድነት የአዲስ አበባ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ትእግስቱ አወል እጩዎች ሆነው ቀርበዋል።

ይህ ፓርቲዉን ለመምራት በአንድነት ዉስጥ እየተደረገ ያለው የምርጫ ፉክክር፣ በጣም የሚያስደስትና የሚያኮራ ነው። «ይሄኛው ይመረጥ፣ ያ ይሻላል» እያሉ አባላትና ደጋፊዎች ሲከራከሩ ማየት፣ በዉጭ አገርም ሆነ ከአገር ዉጭ ባሉ የኢትዮጵያ ተቃዋሚዎች ሆነ በገዢዉ ፓርቲ ዘንድ ያልተለመደ ነው።

የአንድነት ፓርቲ አባል ባለመሆኔ፣  በምርጫዉ ለመሳተፍ አልችልም። ነገር ግን የአንድነት ፓርቲ የመሪዎቹና የአባላቱ ብቻ ሳይሆን፣  በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ደጋፊዎቹም ነው ብዬ ስለማምን፣ እኔም እንደ አንድ ፣ በዉጭ አገር የሚኖር ተራ ደጋፊ፣ በቀረቡ እጩዎች ዙሪያ አንዳንድ አስተያየት ለመስጠት እሞክራለሁ።

ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራዉን  የማያውቅ ሰላማዊ ታጋይ አለ ብዬ አላስብም። የቀድሞ ቅንጅት የድርጅት ጉዳይ ሃላፊ ነበሩ። ትዝ ይለኛል፣  በፓልቶክ፣ ቃለ መጠይቅ በመስጠት ላይ እያሉ ነበር፣ ፖሊሶች መጥተው  ወደ እሥር ቤት የወሰዷቸው።  ሁለት አመት ከሌሎች የቅንጅት አመራሮች ጋር በቃሊቲ ተሰቃይተዋል። ሌሎች ስደትን ወይንም የግል ኑሯቸውን መርጠው ፖለቲካዉን ሲተዉ፣  ኢንጂነር ግዛቸው እና እንደ ዶር ሃይሉ አርአያ ያሉ ጥቂቶች ግን፣   ትግሉ ቀጣይነት እንዲኖረው ያደረጉ አንጋፋ መሪዎች ናቸው። ወ/ት ብርቱካን በታሰረች ጊዜ አንድነትን በተጠባባቂ ሊቀመንበርነት የመሩ ሲሆን፣ ከመድረክ መመስረት አንስቶ፣ በርካታ ወጣቶችን ወደ አንድነት እስከ ማምጣት ድረስ፣  ትልቅ ስራ ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራው ሰርተዋል። በአጭሩ የአንድነት ፓርቲ አሁን ያለበት ደረጃ እንዲደርስ ካደረጉት ሰዎች መካከል ኢንጂነር ግዛቸው  በዋናነት የሚጠቀሱ ኢትዮጵያዊ ናቸው። ኢንጂነር ግዛቸው ከዚህ በፊት ላበረከቱት አስተዋጾ አክብሮትና አድናቆቴን ከማቅረብ ዉጭ ሌላ የምለው ነገር አይኖረኝም።

ከዚህ በኋላ ላለው ጉዞ ግን፣ በቅንጅት ጊዜ ከነበረው በተለየ መንፈስ፣ በተለየ ራእይ፣  ሰላማዊ እንቅስቃሴዉን መምራት የሚያስፈልግ ይመስለኛል። ማንዴላ ለነ ኢምቤኪ፣ ሃላፊነቱን እንዳስረከበው፣ ኢንጂነር ገዛቸውም፣ ላፈሯቸው፣  ብቃት ላላቸው አዳዲስ አመራር አባላት፣  ቦታዉን ቢለቁ ጥሩ ይሆናል ብዬ አስባለሁ። ከነዚህ አመራር አባላት መካከል፣ እጩ ተወዳዳሪ ሆኖ የቀረበው ፣ አቶ በላይ ፍቃዱ አንዱ ነው።

አቶ በላይ ፍቃደ፣ የአንድነት ፓርቲ ም/ሊቀምነበር ሲሆን፣ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ የፍኖት ኤዲቶሪአል ቦርድ ሰብሳቢ ሆኖ ሰርቷል። ለሹመትና ለስልጣን የማይቸኩል፣  ከበስተጀርባ ሆኖ መስራት የሚወድና በፓርቲዉ ዉስጥ ትልቅ ከበሬታ ያለው አንጋፋ የአንድነት አመራር አባል ነው። ኢንጂነር ግዛቸው እራሳቸው፣  አቶ በላይ፣  ፓርቲዉን ለመምራት ብቃት፣ እውቀትና ብስለት ያለው እንደሆነ ብዙ ጊዜ መስክረዉለታል። የሚሊዮኖች ንቅናቄ ክፍል አንድ ወቅት ከዋና አስተባባሪዎች መካከል አንዱ ሲሆን፣ ከሌሎች አገር ቤት ካሉ የፖለቲካ ድርጅት መሪዎች ጋርም የቀረበ ግንኙነት ያለው፣ የአንድነት አመራር አባል ነው። በዉጭ አገር ባሉ የአንድነት ደጋፊዎች ዘንድም ትልቅ ድጋፍና ከበሬታ አለው። ወጣቱን ክፍል ፣ የእድሜ ባለጸጎችን፣ በአገር ዉስጥ ያለውን፣ ከአገር ዉጭ ያለውን የአንድነት አባልና ደጋፊ ማሰባሰብ የሚችል ተግባቢ አመራር እንደሆነ ይነገርለታል።

በዚህም ምክንያት፣ እንደ አንድነት ደጋፊ ፣ አቶ በላይ ፍቃደ፣ አንድነትን ወክሎ ለዉህዱ ፓርቲ ሊቀመንበርነት እጩነት ቢቀርብና የዉህዱን ፓርቲ ቢመራ፣ ፍላጎት እንዳለኝ ለመግለጽ እወዳለሁ። አቶ በላይንም  በዚህ አጋጣሚ ኢንዶርስ አደርገዋለሁ።

እኔም ሆንኩኝ ሌሎች መራጭ ያልሆኑ ደጋፊዎች አንዱ ወይንም ሌላዉ እጩ ኢንዶርስ ብናደርግም፣ ወሳኙ ግን አገር ቤት ያሉት የአንድነት ጠቅላላ ጉባኤ ተወካዮች ናቸው። አቶ በላይን  ቢመርጡ በጣም ደስተኛ ብሆንም፣   ሌሎች እጩዎች ከተመረጡ ግን ፣ ሙሉ ለሙሉ የጠቅላላ ጉባኤዉን ዉሳኔ እንደማክበር፣ አዲስ ለተመረጠዉ አመራር ድጋፌን እንደምሰጥ ለማሳወቅ እወዳለሁ።

ከሚስጥራዊና ዉስጣዊ አሰራር ወጥቶ፣ ዉድድሮችን ይፋ በማድረግ እንደ እኛ አይነት ደጋፊዎች ሐሳባችንን መግለጽ የምንችልበትን ሁኔታ፣  የአንድነት ፓርቲ በማመቻቸቱም፣ ያለኝ አድናቆትና ምስጋና በማቅረብ አቆማለሁ።

 

በቸር እንሰብት !

 

 

የክብር ዶክትሬት ድግሪ መጠሪያ ይሆናል?

$
0
0

ቅዳሜ ሰኔ 28 ቀን 2006 ዓ.ም የተመሰረተበትን 60ኛ ዓመት የአልማዝ ኢዮቤልዩ በዓሉን ያከበረው የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ምረቃ ሥነ ሥርዓት አካሂዷል፡፡ በዚሁ የተማሪዎች የምረቃ ስነ ሥርዓት ላይ በተሰማሩበት ሙያ ለህብረተሰቡ አይነተኛ አገልግሎት አበርክተዋል ላላቸው አራት ሰዎች የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ሰጥቷል፡፡ የክብር ዶክትሬት ከተሰጣቸው ሰዎች መካከል 3ቱ ሴቶች ናቸው፡፡ ዝነኛዋ ድምጻዊት አስቴር አወቀ፣ አትሌት መሠረት ደፋር፣ የዩኒቨርሲቲው ምሩቅና የማህፀንና ፅንስ ሐኪም የሆኑት ዶ/ር ሙሉ ሙለታ እንዲሁም የኢህዴን ታጋይ የነበሩት አቶ ተፈራ ዋልዋ በዩኒቨርሲቲው የክብር ዶክትሬት የተሰጣቸው ሰዎች ናቸው፡፡ ከነዚህ ሰዎች መካከል ስማቸው ለአብዛኞቻችን አዲስ የሆኑት ዶ/ር ሙሉ ሙለታ በማህፀንና ፅንስ ህክምና በርካታ ስራዎችን ያከናወኑ ሲሆን የዓለም አቀፉ ሬስቱላ ማህበር (International Fistula Assocaition ) ፕሬዚዳንት በመሆን በማገልገል ላይ ናቸው፡፡ ወደ ጎንደር ከተማ እየተመላለሱ በፌስቱላ ህክምና ላይ እገዛዎችን ያደርጋሉ፡፡

በአጠቃላይ እነዚህ አራት ግለሰቦች በየሞያቸው ለሀገር ባበረከቱ አስተዋጽኦ ላይ ተመስርቶ ዩኒቨርሲቲው የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ሰጥቷቸዋል፡፡ ከአራቱ ሰዎች መካከል በስፍራው ተገኝተው የክብር ዶክትሬታቸውን የተቀበሉት ዶ/ር ሙሉ ሙለታና አቶ ተፈራ ዋልዋ ብቻ ናቸው፡፡
ድምጻዊት አስቴር አወቀና አትሌት መሠረት ደፋር በዚህ ወቅት የሚገኙት በአሜሪካ ሀገር በመሆኑ በጎንደር ዩነቨርሲቲው ስርዓት ላይ መታደም አልቻሉም፡፡ አስቴር ነዋሪነቷ በአሜሪካ ሲሆን መሠረት ደግሞ ወደስፍራው ያቀናችው በወሊድ ምክንያት ነበር፡፡

Aster aweke Ewedehalew
‹‹ሁሉንም ያስማማ ክብር››

ድምጻዊት አስቴር አወቀ በ1951 ዓ.ም ደቡብ ጎንደር ውስጥ ሃሙሲት በተባለች ትንሽዬ የገጠር ከተማ ነው የተወለደችው፡፡ በ1960 ዎቹ ወደ አዲስ አበባ መጥታ ሙዚቃን የጀመረችው አስቴር ከ40 ዓመት በላይ በሙዚቃው ዓለም ላይ ነግሳበታለች፡፡ ዛሬም ድረስ ተወዳጅ ስራዎቿን ስቱዲዮ ገብታ እየሠራች ለአድናቂዎቿ ከመልቀቋ ባሻገር በተለያዩ ሀገራት በመዘዋወር የሙዚቃ ኮንሰርቶችን ታቀርባለች፡፡

አስቴር ሙዚቃን የጀመረችው ገና የ13 ዓመት ታዳጊ እያለች እንደነበር ይገለጻል፡፡ በዝነኛው ሀገር ፍቅር ቴያትር ቤት ተቀጥራ ሙዚቃን መስራት የጀመረችው አስቴር ከተለያዩ የሙዚቃ ባንዶች ጋር ተወዳጅ ስራዎቿን በሆቴሎችና በምሽት ክበቦች ታቀርብ ነበር፡፡
አስቴር በ1960ዎቹ የሙዚቃ ስራዎቿን ስታቀርብ ካጀቧት ባንዶች መካከል ኮንቲኔንታል ባንድ፣ ሆቴል ዲ አፍሪክ ባንድ፣ ሸበሌ ባንድና አይቤክስ ባንድ ይገኙበታል፡፡
በአስቴር የሙዚቃ ህይወት ውስጥ ትልቁን ሚና ከተጫወቱ ሰዎች መካከል አሊ ታንጎ አንዱና ዋናው ነው ማለት ይቻላል፡፡ አሊ የታዋቂው ታንጎ ሙዚቃ ቤት ባለቤት የነበረ ሠው ሲሆን አስቴር አወቀ የመጀመሪያ የሙዚቃ ካሴቷን ለአድማጮች እንድታደርስ ያደረገው አቶ አሊ ነበር፡፡ የአስቴር አወቀ 5 የመጀመሪያ የሙዚቃ አልበሞች የተሠሩትና ለገበያ የቀረቡት በታንጎ ሙዚቃ ቤት በኩል ነበር፡፡

በፍጥነት ተቀባይነትትን ያገኘችው ተወዳጇ ድምጻዊት አስቴር አወቀ ወደ አሜሪካ ተጉዛ ኑሮዋን በዚያ ከመሠረተች ከ30 በላይ ዓመታት አልፈዋል፡፡ በደርግ ጊዜ የነበረውን ፓለቲካዊ እንቅስቃሴ በመሸሽ ወደ አሜሪካ ያቀናችው አስቴር መጀመሪያ ኑሮዋን በካሊፎርኒያ አድርጋ የነበረ ሲሆን ኋላ ላይ ግን ብዙ ኢትዮጵያዊያን በሚኖሩበት ዋሽንግተን ዲሲ ህይወቷን መስርታለች፡፡ በዚያም በመዝናኛ ቦታዎችና በሬስቶራንቶች እንዲሁም በምሽት ክበቦች ተዘዋውራ የሙዚቃ ስራዎቿን ታቀርብ ነበር፡፡
አስቴር አወቀ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሳ በ1989 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲም 50 ሺህ ገደማ የሚገመቱ ተመልካቾች በተገኙበት ያቀረበችው የሙዚቃ ኮንሰርት አይረሴ ነው፡፡ በ1995 ዓ.ም ደግሞ ለእርዳታና ለትምህርት ቤቶች ግንባታ የሚውል ገንዘብ ለማግኘት የሚያስችሉ ሁለት ኮንሰርቶች በአዲስ አበባ ስታዲየምና በሸራተን አዲስ ሆቴል አቅርባ ነበር፡፡

በኢትዮጵያ ሙዚቃ ታሪክ በርካታ የሙዚቃ አልበሞችን ለገበያ ካበቁ ድምጻዊያን መካከል አንዷ አስቴር አወቀ ናት፡፡ ከክቡር ዶ/ር ጥላሁን ገሠሠ በመቀጠል በአልበም ብዛት ሁለተኛ ናት፡፡ 24 የሙዚቃ አልበሞችን ለሙዚቃ አፍቃሪዎች አድርሳለች፡፡ የመጨረሻ አልበሟ ባለፈው ዓመት ለጆሮአችን የደረሰው ‹‹እወድሃለሁ›› የተሰኘው አልበሟ ነው፡፡

አስቴር አወቀ በሙዚቃ ስራዎቿ ስኬታማ ጊዜን ብታሳልፍም፣ በብዙ ኢትዮጵያዊያን ልብ ውስጥ ብትቀመጥም ተገቢው ቦታና ክብር ግን የተሰጣት አይመስልም ነበር፡፡ አሁን የሚገባትን አግኝታለች፡፡የሚሉ አድናቂዎች ብዙ ናቸው፤ የጎንደር ዩነቨርሲቲ የክብር ዶክትሬት ዲግሪን ሰጥቷታል፡፡ የተዘነጋችውን ዘመን ተሻጋሪ ድምጻዊ አስታውሷታል፡፡

የዩኒሴፍ የበጎ ፍቃድ አምባሳደር የሆነችው አስቴር ከልጅነቷ ጀምሮ በሙዚቃው ዓለም ያደረገችው አስተዋጽኦና አገሯን በማስተዋወቅ የተወጣቸው ሚና ለዚህ ክብር እንድትበቃ እንዳደረጋት ዩኒቨርሲቲው ገልጿል፡፡

መሰረት ደፋር

meseret defar
የ30 ዓመቷ ውጤታማ አትሌት መሠረት ደፋር በተለይ በ3ሺና በ5ሺ ሜትር በተደጋጋሚ ሻምፒዮን መሆን የቻለች አትሌት ናት፡፡ በኦሎምፒክና በዓለም ሻምፒዮና ኢትዮጵያን ወክላ የወርቅ ሜዳሊያ ለሀገሯ ማስገኘት ችላለች፡፡ በአቴንስና በለንደን ኦሎምፒክ በ5ሺ ሜትር የሩጫ ውድድር የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ የሆነች ሲሆን በዓለም ሻምፒዮናም ኦሳካና ሞስኮ ላይ የሀገሯን ባንዲራ እንዲውለበለብ አድርጋለች፡፡
ውልደትና እድገት

ህዳር 9 ቀን 1976 ዓ.ም በአዲስ አበባ ልዩ ስሙ ጉለሌ አካባቢ የተወለደችው መሠረት ደፋር እንደ እድሜ እኩዮቿ በሰፈር ጨዋታ ላይ ተሳታፊ የነበረች ሲሆን፤ ሩጫ ነክ ጨዋታዎች ያስደስቷት ነበር፡፡ አንድ ሜትር ከ55 ሳንቲ ሜትር ቁመት እና 46 ኪሎ ግራም የምትመዝነው መሠረት ለመጀመሪያ ጊዜ ለሩጫ በኢንተርናሽናል ውድድር ላይ ለመካፈል ወደ ትራክ ስትገባ ተፎካካሪዎቿን ጥላ ቀድማ ትገባለች የሚል ግምት በብዙዎች ዘንድ አልነበረም፡፡ ለዚህም ምክንያቱ መሠረት ቀደም ሲል በተመሳሳይ ውድድሮች ላይ አለመታየቷ ነው፡፡
ለመጀመሪያ ጊዜ በአቴንስ ኦሎምፒክ ላይ ተሳትፋ ለሀገሯና ለራሷ የወርቅ ሜዳልያ የ5ሺህ ሜትር ርቀት ስታስመዘግብ አዲስና ፈጣን አትሌት ኢትዮጵያ ማፍራቷን ግልፅ ሆነ፡፡ ሁሌም ፊቷ ላይ የእልህና የአልበገርባይነት ስሜት የሚነበብባት መሰረት የመጀመሪያዋ አፍሪካዊት በ5 ሺህ ሜትር የወርቅ የኦሎምፒክ አሸናፊ በመሆን የማይደበዝዝ ታሪክ አስመዝግባለች፡፡ ውጤቷ ከእሷ ቀደም ብላ በኮሎኔል ደራርቱ ቱሉ የተከፈተው የሴቶች አትሌቶቻችን የአሸናፊነት ስሜት መስመር እየያዘ መምጣቱን የሚያረጋግጥ ሆኗል፡፡

ሪኮርዶቿ

መሠረት ከኦሎሚፒክ ድሏ በተጨማሪ የተለያዩ የሶስት ርቀቶች ሪኮርዶች በእጇ ነበሩ፡፡ በ2007 ካደረገቻቸው በርካታ ዓለም አቀፍ ውድድሮች መካከል የሶስቱን ሪከርዶ በመስበር ብቃቷን አስመስክራለች፡፡ የመጀመሪያው ሪከርዷን የሰበረችው በየካቲት 3 ቀን 2007 እ.ኤ.አ በጀርመን በርሊን በተካሄደው የ3 ሺህ ሜትር የቤት ውስጥ ውድድር በ8 ደቂቃ 23 ሰከንድ በመግባት አሸናፊ ሆናለች፡፡
ከሶት ወራት በኋላም ሜይ 20 ቀን 2007 እ.ኤ.አ በአሜሪካ ካሊፎርኒያ በተዘጋጀው የ2 ማይል ውድድር ላይ 9 ደቂቃ 10 ነጥብ 47 ሰኮንድ በመግባት ተጨማሪ ድልን ተጎናፀፈች፡፡ ከአንድ ወር በኋላ ሰኔ 15 ቀን 2007 እ.ኤ.አ በኖርዌይ ኦስሎ የ5ሺህ ሜትር ርቀትን ሪከርድ 14 ደቂቃ 26 ነጥብ 63 በሆነ ሰዓት በመግባት ኦሎምፒክ ድሏን አድሳለች፡፡ ይህ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ የያዘቻቸው ሪከርዶችና ያሳየቻቸው ብቃቶች ከፍተኛ ትኩረት ሊሰጣት የሚገባ አትሌት መሆኗን አመላክቷል፡፡
መሠረት ከ2007 እ.ኤ.አ በፊትም ባደረገቻቸው ውድድሮች ማንነቷን አሳታለች፡፡ ከ2003 ጀምሮ እስከ 2006 እ.ኤ.አ ድረስ በበርሊን፣ በአቴንስ፣ በቡዳቬስት፣ በሄልሲንኪ፣ በሞኮና በኦሳካ ተደራራቢ ድሎችን በ3 ሺህ እና በአምስት ሺህ ሜትር ርቀቶች ተቀዳጅታለች፡፡ የ5 ሺህ ሜትር የዓለም ሪከርድን በኦስሎ የሰበረችው መሠረት ከውድድሩ በኋላ እንደተናገረችው ‹‹የዓለም ሪኮርድን በሁለት ወይም በሶስት ሰኮንዶች አሻሽላለሁ የሚል እምነት ነበር የነበረኝ አሁን ግን በ8 ሰኮንዶች ነው ያሻሻልኩት ይህም አስደናቂ ነው ብላለች፡፡ መሠረት የ5ሺህ ሜትርን የኦሎምፒክ ውድድር በአሸናፊነት ካጠናቀቀች በኋላ በተደረጉት ውድድሮች ሁሉ የበላይነተቷን እንዳስጠበቀች ሲሆን በ5ሺ ሜትር ውድድር የተሸነፈችው አንድ ጊዜ ብቻ ነው፡፡ መሠረት የ5 ሺህ ሜትር ርቀትን ተወዳድራ የተሸነፈችው በ2005 እ.ኤ.አ በሄልሲንኪ በተካሄደው የዓለም ዋንጫ ውድድር ላይ በሀገሯ ልጅ በጥሩነሽ ዲባባ ነው፡፡

የበጎ አድራጎት ተሳትፎ
መሠረት በአትሌቲክስ ካላት ተሳትፎ በተጨማሪ በበጎ አድራጎት ተግባራት ላይ ተሳትፎ ታደርጋለች፡፡ በ2005 እ.ኤ.አ የተባበሩት መንግስታት የህፃናት መርጃ ድርጅት (ዩኒሴፍ) የበጎ ምግባር አምባሳደር አድርጎ የሰየማት ሲሆን በዚሁ ዙሪያ በህፃናት ክትባትና በህፃናት የጉልበት ብዝበዛ ላይ በሚዘጋጁ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሰሚናሮች ላይ በመገኘት ተሳትፎ አድርጋለች፡፡
‹‹ሴቶች ከድህነት ራሳቸውን ማላቀቅ እንዲችሉ የበኩሌን ጥረት አደርጋለሁ›› የምትለው መሠረት በተለይ እንደ ኤች አይ ቪ ባሉ ህመሞች የሚጠቁ ህፃናትንና እናቶችን በመርዳት ከወገኖቻቸው ጋር መቀላቀል እንደሚገባ ተናግራለች፡፡ አትሌት መሰረት ደፋር የዩኒሴፍ የበጎ ፍቃድ አምባሳደር በመሆን ታገለግላለች፡፡

ሽልማቱ
በ2007 ማብቂያ ላይ በፈረንሳይ ሞናኮ በሚገኘው ባለ አምስት ኮከብ ሞንቴ ካርሎ ልዩ ሆቴል ውስጥ በ2007 እ.ኤ.አ ባሳየችው ምርጥ ብቃት የዓመቱ ምርጥ አትሌት የተባለችውን መሠረት ደፋር ስሟ ሲጠራ ‹‹ይገባታል›› በሚል ስሜት አዳራሹ በጭብጨባ ተሞላ፡፡ ወደ መድረክ ያመራችው መሠረት ደፋር የመጀመሪያዋ ኢትዮጵያዊትና አፍሪካዊት የዚህ ክብር ባለቤት ሆነች፡፡ አስቀድማም መሰረት ታሪክ ሠርታለች፡፡ በአቴንስ ኦሎምፒክ በአምስት ሺህ ሜትር የወርቅ ሜዳልያ በማግኘት የመጀመሪያዋ አፍሪካዊት ኢትዮጵያዊ አትሌት ነች፡፡ የአቴንስ ኦሎምፒክ በኋላ 5ሺህ ሜትር ርቀትን የግል ሀብቷ አድርጋ ይዛዋለች፡፡ በ2012 የለንደን ኦሎምፒክ የ5ሺ ሜትር የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤትም ነች በየተወዳደረችባቸው ቦታዎች ሁሉ የ5ሺ ሜትር ወርቅ የመሠረት ደፋር ብቻ መሆን ከጀመረ ውሎ አድሯል፡፡
በ2008 የፈረንጆች ዓመት ባሳየችው ድንቅ ብቃት የዓመቱ ኮከብ አትሌት ተብላ የተመረጠችው መሠረት ደፋር ሽልማቱን ለመቀበል ወደ መድረክ በወጣችበት ወቅት ያደረገችው ንግግር የብዙዎችን ትረኩረት ስቧል፡፡ ‹‹ይህንን ሽልማት በማግኘቴ የተሰማኝን ደስታ ለመግለፅ ቃላት የሉኝም፡፡ ሽልማቱ የእኔ ብቻ ሳይሆን የመላ ኢትዮጵያውያን ሴቶች ነው፡፡ ይህንን ሽልማት ወደ አትሌቲክስ መንደር ለማምጣት ለሚጣጣሩ ወጣት ሴቶች መታሰቢያ እንዲሆንልኝ እፈልጋለሁ›› ብላለች፡፡
ከረዥም ጊዜ ፍቅረኛዋ ቴዎድሮስ ሀይሉ ጋር ትዳር የመሰረተችው መሠረት በአሁኑ ወቅት የመጀመሪያ ልጇን ለመውለድ በአሜረካን ትገኛለች፤ ትዳሯ ለስኬቷ አስተዋፅኦ እንዳደረገላት ትናገራለች፡፡ ጊዜና ቦታ ሳይመርጡ ለዚህ ስኬት እንድበቃ ላደረጉኝ ሁሉ ምስጋናዬ አቀርባለሁ ያለችው መሠረት ሽልማቱ የባለቤቷና የእሷ የጋራ ሊሆን እንደሚገባ መስክራለች፡፡

አትሌት መሠረት ደፋር ከ3ሺ ሜትር ጀምሮ እስከ ግማሽ ማራቶን ድረስ ሻምፒዮን በመሆን በርካታ ስኬቶች ያስመዘገበች ሲሆን ገና በወጣትነቷ የክብር ዶክትሬት ተሰጥቷታል፡፡ ወጣቷ አትሌት መሰረት ደፋር ቀደም ሲል ጅማ ዩኒቨርሲቲ ለሁለቱ አንጋፋ አትሌቶች ሀይሌ ገ/ስላሴና ደራርቱ ቱሉ ከሰጠው የአትሌቶች የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ቀጥሎ ሶስተኛዋ አትሌት ናት፡፡

የክብር ዶክትሬት ድግሪ መጠሪያ ይሆናል?

የክብር ዶክትሬት ዲግሪ በአንድ ተቋም የሚሰጥ እውቅና ይሁን እንጂ ይዞት የሚመጣው የሞራል ጥያቄ አለ፡፡ የዩኒቨርሲቲ በር የመርገጥ ዕድሉ የሌላቸው ግለሰቦች ብቻ ሳይሆኑ ዩኒቨርሲቲ ገብተው ተምረው ዲግሪ ያገኙ ግለሰቦችም በዚህ ስም ለመጠራት ፍላጎት ሲያጡ በተለያየ ጊዜ ተስተውሏል፡፡ ያም ሆኖ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ያገኙ ግለሰቦች ክብሩንና እውቅናውን ያገኙት በስራቸው መሆኑን በማመን በየትኛውም ቦታ ከስማቸው በፊት ሲጠሩበት ይታያል፡፡ አንዳንዶቹ ደግሞ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ በትምህርት እንደተገኘ የአካዳሚክ ማዕረግ ለመቁጠር በመቸገር በመደበኛ ስማቸው ብቻ እንዲጠሩ ያደርጋሉ፡፡

ሳሙኤል ጆንሠን በችግር ምክንያት የኮሌጅ ትምህርቱን ያቋረጠ ደራሲ ነው፡፡ ጆንሰን በፃፋቸው የድርሰት ሥራዎች መሠረት እ.ኤ.አ በ1965 የTrinity college of Dubline የህግ የዶክትሬት ዲግሪ ሰጥቶት ነበር፡፡ ጆንሠን ከዚህ ጊዜ በኋላ በማንኛውም ህዝባዊ የስብሰባዎችና የሚዲያ መድረኮች ላይ ራሱን እንደ ዶክተር ነበር የሚያስተዋውቀው፡፡ ቤንጃሚን ፍራንከሊንም ራሱን ‹‹ዶክተር ፍራንክሊን›› ብሎ ይጠራ እንደነበር መዛግብት ያወሳሉ፡፡
የክብር ዶክትሬት ዲግሪ የሚሰጠው ከነሙሉ ክብሩ ጥቅሙና መብቶቹ ጋር እንደሆነ ህግ ይደነግጋል፡፡ መብቶቹ በስያሜው መጠራትን ያካትታል፡፡ በእርግጥ በክብር ዶክትሬት ዲግሪ መጠራት የምርጫ ጉዳይ ነው፡፡ ሰዎች በዚህ የማዕረግ ስም የሚጠሩት እስከፈለጉ ድረስ ብቻ መሆኑ በብዙዎች ዘንድ ይታመናል፡፡
ከኢትዮጵያ መሪዎች መካከል የክብር ዶክትሬት ዲግሪ በማግኘት በኩል ቀዳሚው አፄ ሀይለስላሴ ናቸው፡፡ ግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ሀይለስላሴ እ.ኤ.አ በ1964 ከሀዋርድ ዩኒቨርሲቲ በአካባቢ ጥበቃና በደን ጥበቃ ላይ ላደረጉት አስተዋጽኦ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ሰጥቷቸዋል፡፡ ፕሬዚዳት መንግስቱ ኃ/ማርያምም ከሞስኮ ዩኒቨርሲቲ ተመሳሳይ ዲግሪ ደርሷቸዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ከኮሪያ ሀናን ዩኒቨርሲቲ በ1994 ዓ.ም በፖለቲካል ሳይንስ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ሲቀበሉ ፕሬዚዳት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ (እሳቸው ስሙን ከማያስታወሱት ) አንድ የአሜሪካ ዩነቨርሲቲና ከአምቦ ዩኒቨርሲቲ አግኝተዋል፡፡ ሆኖም ሁሉም መሪዎች በኦፊሻል በዚህ ማዕረግ ሲጠሩ አይሰማም፡፡፡ ከፕሬዚዳት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ በስተቀር ለምን እንደማይጠሩበት የተናገሩ ስለመኖራቸው መረጃ የለኝም፡፡ ፕሬዚዳት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ ግን በህዳር ወር 2000 ዓ.ም ለቁም ነገር መፅሔት በሰጡት ቃለ ምልልስ ላይ ‹‹ዶክተር ተብዬ መጠራት አልፈልግም፤ ተምሬ ስላላገኘሁት ደስታ አይሰማኝም›› ብለው ነበር፡፡
በክቡር ዶክትሬት ዲግሪ መጠራት የምርጫ ጉዳይ ነው ብለናል፡፡ የምርጫ ጉዳይ ቢሆንም ግለሰቦቹ ፈልገውም ሆነ ሳይፈልጉ እንዴት ነው መጠራት ያለባቸው የሚለው ጉዳይ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል፡፡ በተለይ የመገናኛ ብዙሀን ባለሙያዎች የክብር ዶክትሬት ዲግሪና ፕሮፌሽናል ዲግሪን ባለመለየት አንዱን ከሌላው ጋር ቀላቅሎ የማቅረብ ሁኔታ ይታያል፡፡ የጥላሁን ገሠሠን የሙት ዓመት መታሰቢያን በተመለከተ ፕሮግራም የሚመራ የአንድ ኤፍ ኤም ጋዜጠኛ ‹‹ የዶ/ር ጥላሁን ገሠሠ 1ኛ ዓመት የመታሰቢያ ዝግጅት በሙዚቃ ኮንሰርት ይካሄዳል›› ሲል ማድመጤን አስታውሳለሁ፡፡ አሁንም ድረስ በተመሳሳይ መልኩ የሚጠሩ ጋዜጠኞች አሉ፡፡ የክብር ዶክትሬት ዲግሪውን ያገኙ ግለሰቦች የሚጠሩበትን አግባብ በተመለከተ ቁም ነገር መፅሔት የቀድሞው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት የነበሩትን ፕሮፌሰር አንድርያስ እሸቴን ጠይቃ ነበር፡፡ (ደብዳቤውን ይመልከቱ) ፕሮፌሰር እንድርያስ እሸቴ እንዳሉት የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ያገኙ ግለሰቦች የክብር ዶክተር ተብለው መጠራት እንደሚችሉ በምሳሌ አስደግፈው አብራርተዋል፡፡

በመሆኑም የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ያገኙ ሰዎችን በትምህርት የዶክትሬት ዲግሪ እንዳገኙ ሰዎች አስመስለን መጥራት ተገቢ እንዳልሆነ (ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ማለት ይቻላል፤ ዶ/ር ጥላሁን ገሠሠ ማለት ግን እንደማይቻል፤ጥላሁን የሚጠራው የክብር ዶ/ር ተብሎ እንደሆነ) መረዳት ያስፈልጋል፡፡

‹‹በጥርጣሬ ውስጥ የወደቀው ክብር››

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክትሬት ከሠጣቸው ሰዎች መካከል በአንዳንዶቹ ላይ ጥያቄዎች እያሳረፈ ነው፡፡ በተለይ በማኅበራዊ ድረገፆች ላይ አስተያየታቸውን የሚሠጡ ሰዎች በአቶ ተፈራ ዋልዋ የክብር ዶክትሬት ላይ ተገቢነቱን የተጠራጠሩ ስለመሆናቸው ሲገልፁ ነበር፡፡ እኝህ ሰው ያበረከቱት አስተዋጽኦ ከተሰጣቸው ክብር ጋር የሚጣጣም ስለመሆኑ ጥርጣሬ አላቸው፡፡ ለአቶ ተፈራ ዋልዋ የተሰጠውን የክብር ዶክትሬት ፖለቲካዊ ትርጉም በመስጠት ተገቢነት የሌለው ብለውታል፡፡ በርግጥ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ዩኒቨርሲቲዎቹ የክብር ዶክትሬት የሚሰጧቸው ሰዎች ፖለቲካዊ አንድንድምታ ያላቸው ይመስላሉ፡፡ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለቀድሞው ለደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ለታቦ ምቤኪ የሰጠውና ዘንድሮ የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ለቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት ለኦሊሴጎን ኦባሳንጆ ክብሩን መስጠቱ ለዚህ ሃሳብ መነሳት አንዱ ምክንያት ነው፡፡ቁ

ምንጭ በአዲስ አበባ የሚታተመው ቁምነገር መጽሔት

የ53 አመቱ አባት የጥቁር ሽብር ሰለባ አስገራሚ ክስተት

$
0
0

ቢቢኤን ራድዮ እንዳቀረበው፦

መንግስት ሀምሌ 11 በወሰደው የጭካኔ ተግባር ወጣቱ ወንዱ ሴቱ ህጻናቱ አዛውንቱ የጥቁር ሽብሩ ሰለባ ሁነዋል፡፡ የዚህ ጥቃት ሰለባ ከሆኑት መካከል የ53 አዛውንት ሰው ይገኙበታል፡፡ ይህ በምስሉ ላይ የምትመለከቱት የርሳቸውን በከፍተኛ ድብደባ የቆሰለ ሰውነት ነው፡፡
የ53 አመቱ ሰው ከቢቢኤን ሬድዪ ጋር የደረሰባቸውን ነገር አስመልክቶ ቆይታ አድረግዋል፡፡ ሙሉዉን ቆይታ ከራሳቸው አንደበት የምትሰሙት ይሆንና በመጠኑ ቀንጭበን በጽሁፍ እናካፍላችሁ፡፡
Muslim abat
የጁምአን ሶላት በአንዋር መስጅድ ለመስገድ ዘግየት ብለው ስለደረሱ ውጭ አስባልት ላይ ነበር መስገጃ ካኪ ያነጠፉት፡፡ ምንም ተቃውሞ ባልተጀመረበት ሶላትም ባልተሰገደበት ሁኔታ ፖሊሶች መስግጃውን አንሱ በማለት ትንኮሳ ጀመሩ ይላሉ ግለሰቡ፡፡ እርሳቸውም ከእድሚያቸው አንጻር ሁኔታዎቹን ለማረጋገት ይሞከራሉ፡፡ በዚህ ሰአት ግን የፖሊሶቹ ምላሽ ያልጠበቁት ነበር ፡፡ በያዙት ዱላ ለሶላት የተሰበሰበውን ምእምናን መደበደብ ጀመሩ፡፡ እኚህ አባትን በርካታ ፖሊሶች ከበው ይደብድቡዋቸው ጀመር፡፡

የዱላ ውርጅብኝ የበዛባቸው አባትም ወደ መዲና ህንጻ ሩጠው ይገባሉ፡፡ ፖሊሶች ተከትለው ከገቡ በሁላ እየጎተቱ መሬት ላይ በመዘርጋት ዘግናኝ ድብደባ እንደፈጸሙባቸው ይናገራሉ፡፡ በዚህ ብቻ አላበቃም፡፡ ከእድሜያቸው አንጻር በዚሁ እንኩዋን አልተዋቸውም፡፡ በጾመኛ አንጀታችው እየደበደቡ ወደ ልኩዋንዳ ፈጥኖ ፖሊስ ማሰልጠኛ ወሰዱዋቸው፡፡

ልኩዋንዳ ሲደርሱ እሳት እየነደደ ነበር ይላሉ፡፡ ከዛም የሴቶችን ጅልባብ ሀይማኖታዊ አልባሳት የሳቸውም ኮፍያ ጭምር በሳት ተቃጠለ፡፡ ወደ ሰፊ ሜዳ ከወሰዱዋቸው በሙሉ በግራና በቀኝ ዙርያውን ፖሊሶች ተደርድረው በመሃል እየቀጠቀጡ ከፍተኛ ድብደባ ተፈጸመባቸው፡፡ በ120 በ90 ሜትር የሚሆነውን ሜዳ እያዞሩ ቀጠቀጡን ሲሉ ይናገራሉ አዛውንቱከድብደባውም ሌላ ኮፍያቸው ጫማቸው ተቃጥልዋል፡፡ አጸያፊ ስድብም ተሰድበዋል፡፡ ዱላቸው ተሰባብሮ ሲያልቅ እሳት ረመጡን እንዲረግጡ አድረገዋቸው፡፡ እስከ ሌሊቱ 9 ሰአት ይህ ሁሉ ሲፈጸምባቸው ጾመኛ ነበሩ፡፡
ዘጠኝ ሰአት ላይ አውጥተው ጣልዋቸው፡፡ ሌሊት ለተሃጁድ ሶላት የሚሄዱ ሰዎች ሲያገኙዋቸው አለቀሱ፡፡ የ53 አመቱ አባት ጀርባቸው በምስሉ እንደሚታየው ቆስሉዋል:: ራሳቸው ተፈርክስዋል፡፡

በመጨረሻም ምን ይላሉ ሲል የቢቢኤን ጋዜጠኛ አብዱረሂም ላቀረበላቸው ጥያቄ አዛውንቱ አስገራሚ ምላሽ ሰጡ፡፡ እንዲህም አሉ ”የደረሰብኝ ነገር የሰው ልጅ በወገኑ ላይ የሚፈጸመው ተግባር አይደለም፡፡ ይህም ሁኖ ግን ሰላማዊነታችንን በፍጹም መተ ው የለብንም፡፡ ድምጻችን ይሰማ ጁምአ ቢጠራ ሰባራ እጄን ወንድሞቼ ጋር እሰለፋሉ የምንፈልጋት ሰላማዊ ትግል ውጤት እስክትመጣ ሌላ ምን አደረጋለሁ፡፡ ለሙስሊሙ የማስተላልፈው ሰላማዊ ትግላችን መቀጠል አለበት፡፡ ይህን ስል ሁሉም ይደብደብ ማለቴ ሳይሆን እውነተኛ ነጻነታችን የምትከበርባት ሀገር እስክትመጣ መታገል አለብን፡፡ አንድነታችን ይዘን ጥያቄያችን እስኪመለስ እነሱ ይግደሉን እነሱ ይጨፍጭፉን እኛ በሰላማዊ ትግል አሻራችንን እናሳረፍ፡፡ በኔ የደረሰው ኢምንት ነው በጥይትም የተመቱ አሉ እንበርታ ይላሉ የ53 አመቱ አባት፡:

ለመስማት ተከታዩን ሊንክ ይጫኑ
http://goo.gl/pYP0hD
በጣም አነስተኛ መጠን ያለው ሊንክ
http://goo.gl/NBc1Kx

“በኢትዮጵያዊነት ማንም ከኦሮሞዎች አይበልጥም፤ ኦርጅናል ኢትዮጵያውያን ነን”–አቶ ቡልቻ ደመቅሳ

$
0
0

አቶ ቡልቻ ደመቅሳ ለረጂም ዓመታት በኢትዮጵያ ፖለቲካ ተሳትፏቸው ይታወቃሉ፤ በተለይም የኦሮሞን ህዝብ መብት እናስከብራለን ብለው የፖለቲካ ፓርቲ መስርተው ከታገሉት ሰዎች መካከል ከፊተኞቹ አንዱ ናቸው፡፡ አቶ ቡልቻ አሁን ስላሉበት የፖለቲካ ተሳትፏቸውና ስለተለያዩ አንኳር ሀገራዊ ጉዳዮች ከጋዜጠኛ በላይ ማናዬ ጋር ቆይታ አድርገዋል፤ እንዲህ ይቀርባል፡-

Ato Bulcha
ነገረ ኢትዮጵያ፡- አቶ ቡልቻ በተለያዩ መድረኮች ላይ በፖለቲካ ተሳትፎዎ ነው የሚታወቁት፤ ነገር ግን አሁን ላይ ከፓርቲ ፖለቲካ ተሳትፎ የራቁ ይመስለኛል፡፡ በዚህ ወቅት ስላልዎት የፖለቲካ ተሳትፎዎ በአጭሩ ቢነግሩኝ?
አቶ ቡልቻ፡- እኔ ከመድረክ የገባሁት የኦፌኮ መሪ ሆኜ ነው፡፡ አሁን የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረንስ (ኦፌኮ) እስኪ ወጣቶቹ ይስሩ፣ እነሱ ሲሰሩ የሚቻለኝን እርዳታ አደርጋለሁ ብዬ በራሴ ፈቃድ ከፓርቲ ፖለቲካ ወጥቻለሁ፡፡ ‹‹Retire››  አድርጌያለሁ፡፡ እግዚአብሄር ይመስገን ጤናማ ነኝ፡፡ በእድሜየ በኩል 83 አመቴ ነው፡፡ በትምህርትም ሆነ በተፈጥሮ ስጦታ ትልቅ አቅም ያላቸው ልጆች ስላሉ እኔ በዚህ እድሜዬ መድከም የለብኝም ብዬ ነው የለቀቅኩት፡፡

ነገረ ኢትዮጵያ፡- ስለዚህ አሁን የቱንም የፖለቲካ ድርጅት አይወክሉም ማለት ነው?
አቶ ቡልቻ፡- ልክ ነው! በግሌ ነው የምንቀሳቀሰው፡፡ አሁን ምንም አልወክልም፡፡ አስተያየትም የምሰጠው፣ ንግግርም የማደርገው በግሌ ነው፡፡

ነገረ ኢትዮጵያ፡- መድረክ በቅርቡ አዲስ አበባ ውስጥ ሰላማዊ ሰልፍ ባደረገበት ወቅት ንግግር ሲያደርጉ በቦታው ነበርኩ፡፡ ‹‹በጋራ መምጣት ከፈለግን አንድ መሆን አለብን›› የሚል ንግግር አድርገው ነበር፡፡ ምን ለማለት ፈልገው እንደሆነ ሊያብራሩልኝ ይችላሉ?
አቶ ቡልቻ፡- እኔ ማለት የፈለኩት፤ የኢትዮጵያ ብሄሮች (ብሄሮች አሉ፡፡ የሉም ማለት አይቻልም፡፡ ብሄሮች እንደለሉ መናገር ችግር የለውም የሚሉ ቢኖሩም ተሳስተዋል፡፡ እኛ አይደለም የምንፈጥራቸው፡፡ እነሱ አሉ፡፡) መኖራቸውን አውቆ ከእነሱ ወኪሎች ጋር መነጋገር ነው፡፡ ኢትዮጵያ መነጋገሯ
አይደለም፡፡ የብሄሮች ወኪሎች ተነጋገሩ ማለት ኢትዮጵያ ተነጋገረች ማለት ነው በውስጧ፡፡ የተለያዩ የፖለቲካ መስመር የሚከተሉ ሰዎች አሉ፡፡ ይህ ማለት የአንድ ማህበረሰብ ሰዎች አንድ አይነት ፖለቲካ ይከተሉ ማለት አይደለም፡፡

ነገረ ኢትዮጵያ፡- በጎሳ ወይም በብሄር የተደራጁት አካላት ትክክል አይደሉም የሚሉ ሰዎች አሉ፤ ብሄር ማለት ሀገር ማለት ነውና ከቃሉ ጀምሮ ትክክል አይደለም ይላሉ፡፡ እርስዎ ምን ይላሉ…ለእርስዎ ብሄር ማን ነው? ብሄረሰብስ የትኞቹ ናቸው?
አቶ ቡልቻ፡- እኔ ‹‹ብሄር›› የሚባለውን ቃል የሰማሁት የ19ና 20 አመት ሆኜ ነው ለመጀመሪያ ጊዜ የሰማሁት፡፡ አንድ አራት ኪሎ ይገኝ የነበር ተስፋ ገብረስላሴ የተባለ ሰው ማተሚያ ቤት ነበር፡፡ ያ ማተሚያ ቤት ‹‹ተስፋ ገብረስላሴ ዘ ብሄረ ቡልጋ›› ይል ነበር፡፡ ይህ ምን ማለት እንደሆነ ጠይቄ አሁን የምረዳውን ተረዳሁ፡፡ ብሄር ማለት አሁንም እንደምንሰማው የአንድ ብዙ ወይንም አነስ ያለ ህዝብ አንድነት፣ ወይንም ማንነት ማለት ነው፡፡ ምንም አያስቸግረኝም፣ አስቸግሮኝ አያውቅም፡፡ ብሄር ማለት የህዝብ መገለጫ ማለት ነው፡፡
bulcha_demeksa
ነገረ ኢትዮጵያ፡- ህዝብ የተለያየና አንጻራዊ መገለጫዎች ይኖሩታል፡፡ በዚህ መሰረት እንደ ኢትዮጵያ የጋራ መገለጫ አይኖረንም? ‹ብሄር› የሚባሉት ቡድኖች መገለጫቸው ድንበር ሲያጣ ይታያል፡፡ ስለዚህ በጋራ የምንጋራቸውን ማንነቶችስ ምን ልንላቸው ነው?
አቶ ቡልቻ፡- ኢትዮጵያ ብቻ አይደለችም በዓለም ላይ ብዙ ሀገራት አሉ፡፡ በተባበሩት መንግስታት ላይ ያየኸው እንደሆነ 198 ነው ሀገራት አሉ፡፡ ኢትዮጵያ ከእነዚህ ሀገራት አንዷ ናት፡፡ እኔ ከእነዚያ መካከል አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ ዜጋ ነኝ፡፡ ልክ አንድ ቤተሰብ ብዙ ሰው እንደሚኖረው እኛም ሀገራችን ውስጥ ስንገባ ብዙ አይነት ኢትዮጵያውያን አሉ፡፡

ነገረ ኢትዮጵያ፡- እገሌ ብሄር፣ እገሌ ደግሞ ብሄረሰብ ነው ብለው በምሳሌ ሊያስረዱኝ ይችላሉ?
አቶ ቡልቻ፡- እኔ እንደሚገባኝ ነው የምሰጥህ፡፡ ኦሮሞ ማለት ኦሮምኛ የሚናገር፣ በምስራቅ፣ መካከለኛውና ምዕራብ ኢትዮጵያ የሚኖር፣ አብዛኛውን ጊዜ ግብርና መኖሪያቸው የሆነ መልካቸው (ከሌላው ኢትዮጵያውያን ይለያል አልልም) ጥቁርም አይደሉም፣ ቀይም አይደሉም፡፡ ብዙው የኢትዮጵያ ህዝብ እንደዚህ ነው፡፡ ኦሮሞ እንዲህ አይነት ህዝብ ነው፡፡ ውስጥ የገባህ እንደሆነ ስነ ልቦና፣ የጋራ አመለካከት የመሳሰሉ የእያንዳንዱ ሰው ፍርድ አለ፡፡

ነገረ ኢትዮጵያ፡- አንዳንድ ፖለቲከኞች ‹‹ብሄር›› የሚባሉትን ጎሳ፣ እንዲሁም ድርጅቶችን ‹‹የጎሳ ድርጅት›› ይሏቸዋል፡፡ እርስዎ ይስማማሉ?
አቶ ቡልቻ፡- አልስማማም! ጎሳ ሌላ ነው፡፡ እኔ የአማርኛ ሊቅ ባልሆንም መናገር እችላለሁ፡፡ ጎሳ የሚባል ቃል፤ እኔ እንጃ?! ኦሮሞ ጎሳ ነው እንዴ? ኦሮሞ ጎሳ አይደለም! አንድ ህዝብ ነው፣ ጎሳ አይደለም፡፡ ምን አልባት የሚዛመዱትን ከሆነ ኦሮሞ ውስጥ ብዙ እርስ በእርሳቸው የሚዛመዱ አሉ፡፡ እኔ በተወለድኩበት ወለጋ ውስጥ በራሱ ብዙ ብዙ ጎሳዎች አሉ፡፡ ጎሳ እንኳ ብዙም ትርጉም የለውም፡፡

ነገረ ኢትዮጵያ፡- እንደ ሩዋንዳ ያሉ ሀገራት አንድን ህዝብ ቋንቋን ወይም ጎሳን መሰረት አድርጎ በፖለቲካ ማደራጀት በህግ ከልክለዋል፡፡ በጎሳ መደራጀት በተለይ በፖለቲካ ፓርቲ ደረጃ ምን ያህል ያስኬዳል? ለሀገር አንድነትስ ተጽዕኖ አይኖረውም?

bulcha_demeksaአቶ ቡልቻ፡- እኔ እንደሚመስለኝ፣ ኢትዮጵያ ውስጥ ዘጠና ሚሊዮን ህዝብ ነው የሚኖረው፡፡ እግዚአብሄር ይመስገን መታወቂያ ስለሰጠን እንጂ ካለዚያማ ማን ምን እንደሆነም አይታወቅም፡፡ አሁን ግን አማራ፣ ኦሮሞ፣ ትግሬ.. በጣም ደስ የሚል መግለጫ፡፡ እሱማ ባይኖር ማን ነበር የምንባለው? የትግሬ ህዝብ በራሱ መሪዎቹን መርጦ ወደ ዋናው ከተማ ይመጣል፡፡ ኦሮሞ በራሱ ክልል የራሱን መሪዎች መርጦ ወደ አዲስ አበባ ይመጣል፡፡ እነዚህ መሪዎች ኢትዮጵያን እንዴት እንምራት ብለው ሊስማሙ ይችላሉ፡፡ ሊነጋገሩ ይችላሉ፡፡ አንድ ህዝብ በስሙ መጠራቱ ምን ከፋ? ችግሩ እኛ ኢትዮጵያውያን አይደለንም ሲባል ነው፡፡ ህወሓት፣ ኦነግና አሁን ኢህአዴግ ውስጥ ያለው የአማራ ድርጅት ኢትዮጵያዊ አይደለንም ይሉ ነበር፡፡ ችግሩ የሚመጣው እንዲህ ሲሆን ነው፡፡ ይህ ሳይሆን በስሙ ተጠርቶ፣ ከሌሎች የኢትዮጵያ ዜጎች ጋር ተዋዶና ተፋቅሮ፣ እየተረዳዳ፣ እየሰራ ቢኖር ምን
ችግር አለው?
ነገረ ኢትዮጵያ፡- እርስዎ በፓርቲ ደረጃና በግል እንደሚታገሉለት የሚናገሩለት የኦሮሞ ህዝብ ሰፊ መሰረት ያለው መሆኑ ይታወቃል፡፡ የኦሮሞ ህዝብ ሰፊ መሰረት ያለው ሆኖ እያለ በቋንቋ በመደራጀት መብቱን አስከብራለሁ ማለት ለክብሩ የሚመጥን አይደለም የሚሉ አካላት አሉ፡፡ የኦሮሞ ህዝብ በቋንቋ ከመደራጀት ይልቅ በህብረ ብሄራዊነት ተደራጅቶ በኢትዮጵያ የተሻለ ለውጥ ማምጣት አይችልም? በአንድ ክልል፣ በአንድ ማዕቀፍ ብቻ ተወስኖ መደራጀት ለክብሩ የሚመጥን ነው ብለው ያስባሉ?

አቶ ቡልቻ፡- የኦሮሞ ህዝብ ከ37 እስከ 40 ሚሊዮን የሚሆን ህዝብ ነው፡፡ ግን አዋቂዎችና የተማሩት የሚሉትን ልንገርህ፡፡ እኛ የኢትዮጵያ አካል ነን፡፡ የትም መሄድ አንፈልግም፡፡ ኦሮምኛ እንናገራለን፡፡ ግን ኢትዮጵያውያኖች ነን፡፡ በኢትዮጵያዊነት ማንም ከእኛ አይበልጥም፡፡ እኩል ነን፡፡ እገዛችኋለሁ፣ እበልጣችኋለሁ፣ ቋንቋችሁን አፍናለሁ፣ የሚሉ ካሉ እንታገላቸዋለን፡፡ እንጂ የትም አንሄድም፡፡ አገራችንን ትተን የት እንሄዳለን? ዛፍ እንኳ ስታየው ቅርንጫፉ ነው የሚወድቀው፡፡ ዋናው ግንድ ይቆማል፡፡ ኦሮሞ ግንድ ነው፡፡ ማንም ሰው ለኦሮሞ አንተ እንዲህ ነህ፣ አንተ እንዲህ ነህ ብሎ ሊነግረው አይችልም፡፡ ኦሮሞ ምን እንደሆነ ራሱን ያውቃል፡፡ እንዲያውም ኦሮሞ ይህ ሀገር የእኔ ነው፣ ከሌሎች ጋር ተጋርቼ እኖራለሁ ብሎ ነው የሚያምነው፡፡ ስለዚህ ነው እንገነጠላለን የሚሉ ሰዎች ያልተሳካላቸው፡፡

ነገረ ኢትዮጵያ፡- ታዲያ ኦሮሞ ግንድ ሆኖ እያለ እንደ ቅርንጫፍ ነጥሎና ጠበብ አድርጎ መደራጀት ለምን አስፈለገ?
አቶ ቡልቻ፡- ኦሮሞዎች፣ እኛ ኦርጅናል ኢትዮጵያውያን ነን፡፡ ኢትዮጵያውያን ሆነን ግን ለፖለቲካና ማህበራዊ ህይወት እንደራጃለን፡፡ ቋንቋችን ስንናገር ነው የምንግባባው፡፡ አማርኛም እንናገራለን፣ ነገር ግን አማርኛም የማያውቅ አለ፡፡ የኢትዮጵያ ህዝብ ለምን ኦሮሞ፣ ትግሬ፣ አማራ፣ ጉራጌ ተብሎ ይጠራል
ብለው የሚከራከሩት አብዛኛውን ጊዜ የቀድሞ የሹማምንት ልጆች ናቸው፡፡ የግራአዝማቹ፣ የቀኝአዝማቹ፣ የራሱ የቀኝአዝማቹ ዝምድና ያላቸው ሰዎች ናቸው፡፡ እነሱ የሚመኙት ወደ ድሮው፣ ወደመሪነት፣ ወደማዘዝ ቦታ ነው የሚመኙት፡፡ የፌደራል ጉዳይ ደግሞ ይነሳል፡፡ ለምንድን ነው ሁላችንም አንድ አዳራሽ ውስጥ የማንኖረው? ለምንድን ነው እያንዳንዱ ሰው ከሌላው ተወዳድሮ ቆንጆ ቤት ሰርቶ ለብቻው የሚኖረው? ፌደሬሽን የሚጠሉ ሰዎች ምንድን ነው የሚፈልጉት? በ1983 ዓ.ም ፌደራሊዝም ከመገንጠል ይሻላል ተብሎ እኮ ነው የመረጥነው፡፡ ያኔ ሁሉም፤ ኦነግም፣ ህወሓትም፣ አማራም፣ ሲዳማም… ሁሉም ብሄር ፌደራሊዝምን የመረጥነው እንገነጠላለን የሚሉትን ሰዎች ለማሸነፍ ነው፡፡ እኔ ኢትዮጵያ ከፌደራሊዝም ውጭ ተስፋ አላት ብዬ አላምንም፡፡
bulcha
ነገረ ኢትዮጵያ፡- አሁንም ቢሆን ከፌደራሊዝም ውጭ አማራጭ ይዞ የመጣ የፖለቲካ ፓርቲ ያለ አይመስለኝም፡፡ ልዩነቱ በቋንቋ/ጎሳ/ብሄር ከሚሆን ይልቅ አስተዳደራዊ አመችነትና ሌሎች መስፈርቶች መታየት አለባቸው የሚል ነው፡፡ እርስዎ አሁን እንደሚናገሩት ግን ኢህአዴግ የሚጠቀምበት ቋንቋን መሰረት ያደረገ አወቃቀር እንዲቀጥል የፈለጉ ይመስለኛል?

አቶ ቡልቻ፡- አዎ! አማራጭም የለውም፡፡ ታዲያ በምን የተመሰረተ ድርጅት ሊሆን ነው? በቋንቋው፣ በባህሉ፣ በሚኖርበት አካባቢ የፖለቲካ ድርጅት ቢያቋቁም ምን ይጎዳል? ለምንድን ነው የሚጠላው? አሁን እነሱ የሚሉት በዘር ሳይሆን በወንዝ፣ በተራራ፣ አንዳንድ ዳርቻዎችን በመጥቀስ ነው፡፡ ለምሳሌ በአጼ ኃይለስላሴ ጊዜ ሸዋ አማራም፣ ኦሮሞም ነበረበት፡፡ በዛን ጊዜ ሀገረ ገዥው ራስ መስፍን ነበሩ፡፡ እኔ አውቃቸዋለሁ፡፡ በጣም ጥሩ ሰው ነበሩ፡፡ በጣም ትሁት፣ ሩህሩህና ፍትህ የሚያውቁ ሰው ነበሩ፡፡ እሳቸው አማራ ነበሩ፡፡ ኦሮሞዎቹ እንደልባቸው ራስ መስፍን ጋር አይመሩም፣ ራስ መስፍንን አያማክሩም፡፡ አማራ የሆኑት የሸዋ ሰዎች ግን ራስ መስፍንን እንደራሳቸው መሪ፣ እንደራሳቸው ሀገረ ገዥ፣ እንደራሳቸው እንደራሴ አድርገው ነበር የሚያዩት፡፡ ይህ ራሴ በህይወቴ ያየሁት ገጠመኝ ነው፡፡ ህዝብ የሚፈልገውን ያውቃል፡፡ ከፌደራሊዝም ውጭ አማራጭ የለንም፡፡ ፌደራሊዝምን በደንብ መምራት የመንግስት ፋንታ ነው፡፡ ፌደራሊዝም በሚመራበት ወቅት የኦሮሞ ህዝብ ‹ራስ መስፍን የእኛ አይደሉም› እንዳሉት እንዳይሆን መደረግ አለበት፡፡ የአዲስ አበባ መንግስት ሁሉንም ሰው በእኩልነትና በፍርድ የያዘ እንደሆነ ፌደራሊዝም ጥሩ አማራጭ ይሆናል፡፡

ነገረ ኢትዮጵያ፡- ፌደራሊዝሙ በቋንቋ መዋቀሩ እንደ ችግር ተብሎ የሚነሳው ኢትዮጵያውያን በሀገራቸው ‹‹ሀገራችሁ አይደለም ውጡ›› እንደሚባሉ በመጥቀስ ነው፡፡ በደቡብና ቤንሻንጉል እየታየ ያለውንም እንደማሳያ ይጠቅሳሉ፤ እና…
አቶ ቡልቻ፡- እሱን በጭራሽ አልደግፍም፡፡ እሱን በመመካከር፣ በአስተዳደር፣ በፖለቲካ፣ አንድም ነገር ሳይደበቅ መነጋገርና መወያየት ያስፈልጋል፡፡ ግልጹን ማውጣት ነው የሚጠቅመው፡፡ ለምሳሌ ከወለጋ አማራዎችን አንስተዋቸዋል ይባላል፡፡ ውሸት መሆኑን አውቃለሁ፡፡ ግድ የለም አስነሷቸው እንበል፡፡ ታዲያ ለምንድን ነው የምታስነሷቸው ብሎ መጠየቅ ነው? ኢትዮጵያውያን የትም ሄደው መስራትና መኖር አለባቸው፡፡ በመሆኑም ማፈናቀል ካለ ለወደፊት ወንጀል ተደርጎ መወሰድ አለበት፡፡ አንድ ብሄር ሌላኛውን ይህ ያንተ አይደለም፤ ከሌላ ነው የመጣኸው ብሎ ሲያፈናቅል የሚቀጣበትን አግባብ መፈለግ ነው ያለብን፡፡

ነገረ ኢትዮጵያ፡- በአንቦና በሌሎች አካባቢዎች ግጭት ለመነሳቱ ቀዳሚው ምክንያት የኦሮሚያ መሬት ሊወስድ ነው፣ አርሶ አደሮች ሊፈናቀሉ ነው በሚል ነበር ይታወል፡፡ በአንድ በኩል አዲስ አበባ የኦሮሞ ነች እየተባለ በሌላ መልኩ ደግሞ የኦሮምያ መሬት ለአዲስ አበባ ሊሰጥ ነው ማለት እርስ በእርሱ አይጋጭም?

አቶ ቡልቻ፡- እንደ እኔ ይህንን ጣጣ ያመጡት በፌደራል መንግስቱ ውስጥ የሚሰሩ አንዳንድ ባለስልጣናት ናቸው፡፡ እርግጥ ነው ኦሮሞ መሬቱ በአዲስ አበባ እንዲወሰድ አይፈለግም፡፡ ምክንያቱም የጋራ ጥቅም ነው፡፡ አሜሪካም ውስጥ እንዲህ አይነት ጭቅጭቅ አለ፡፡ ትልልቅ የመንግስት ስራዎች ሲሰሩ አንዱ ስቴት ይመረጣል፡፡ ለመንግስት ስራ የተመረጠው ስቴት የስራ አጥነትና ሌሎች ችግሮች እንደሚፈጠሩ በመግለጽ ይከራከራሉ፡፡ ታዲያ ምን አለ የኦሮሞ ወጣቶች እኛ ሳንጠየቅ ይህን ያህል መሬት ለምን ይወሰድብናል? ቢሉ ምን ችግር አለው፡፡ አሜሪካ ዋና ከተማው ዋሽንግተን ዲሲ ነው፡፡ ዋሽንግተን የቨርጂኒያና የሜሪላንድን መሬት ዝም ብሎ ይከልላል? የማይታሰብና የማይደረግ ነገር ነው፡፡ ለማንም ሳይናገሩ ልዩ ዞኖችን እንደወሰዱት አይደለም፡፡ ይህ እኮ ሰውን መናቅ ነው፡፡ ከህዝቡ ጋር ተማክረዋል? መንግስት የህዝብ ወኪል ከሆነ ህዝብን መናቅ አይችልም፡፡ በሰለጠነ መንገድ ቢደረግ ኖሮ ማን ይቃወም ነበር?
ነገረ ኢትዮጵያ፡- በቅርቡ ‹‹ሰማያዊ ፓርቲ አይገባኝም!›› ማለትዎትን አንብቤያለሁ፡፡ ሰማያዊ አይገባኝም ሲሉ ምን ማለትዎት ነው?
አቶ ቡልቻ፡- አንድነትን አውቀዋለሁ፡፡ መኢአድን አውቀዋለሁ፡፡ ሰማያዊን ግን አላውቀው ማለቴ ነው፡፡ ይህ ግልጽ ነው አላውቃቸውም ማለት ነው፡፡ እነሱም አላማቸውን ለማሳወቅ ፓምፕሌት አይበትኑም፡፡ እኔ ለምሳሌ ኦፌኮ በነበርኩበት ጊዜ ስለ አላማችን በርካታ ፓምፕሌቶችን እያሳተምኩ እበትን ነበር፡፡ ህዝብ አላማችን እንዲያውቅ እናደርግ ነበር፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ ይህንን ሲያደርግ አላየሁም፡፡ እና ሰማያዊ ከአንድነት ምን ያህል ልዩነት ኖሮት ነው ሰላማዊ ሰልፍ የተፈቀደለትና አንድነት ሰላማዊ ሰልፍ የተከለከለው? አይገባንም፡፡ እውነቴን ነው ፖለቲካም እውነት ሊሆን ይችላል አንዳንዴ፡፡ ይህን አላውቅም የምለው ከልቤ ነው፡፡ አንድነት ከኦሮሞ የሚለይበትን አንዳንድ ምክንያቶች አውቃለሁ፡፡ ይህ ከቅን ልቦና የማደርገው ንግግር ነው፡፡ ቢፈልጉ ፓምፕሌት ይላኩልኝ አንብቤ እረዳዋለሁ፡፡

ነገረ ኢትዮጵያ፡- እርስዎስ በግልዎ ለማወቅ ጥረዋል?
አቶ ቡልቻ፡- አዎ! ጠየኩ! ቢሮ ውስጥ እባካችሁ የሰማያዊ ፓርቲ ፓምፕሌት፣ መግለጫ ካላችሁ ብዬ ጠይቄያለሁ፡፡ አሁንም እጠይቃለሁ፡፡ ለምሳሌ ከአንድነት ልዩነታቸው ምንድን ነው? አንድነት አማራ፣ ኦሮሞ፣ ትግራይ ሳይሆን ኢትዮጵያ መባል እንዳለበት እንደሚፈልጉ አውቃለሁ፡፡ የሰማያዊ ምን እንደሆነ አላውቅም፡፡

ነገረ ኢትዮጵያ፡- ሰማያዊ አቋሞቹን፣ መግለጫዎቹንና ሌሎቹንም በዚህ ጋዜጣ ያሳውቃል፡፡ ለምሳሌ ነገረ ኢትዮጵያን አንብበው ያውቃሉ?

አቶ ቡልቻ፡- እስካሁን አላየሁም፡፡
ነገረ ኢትዮጵያ፡- ለ2007 ሀገራዊ ምርጫ እየተቃረብን ነውና ከምርጫው ምን ይጠብቃሉ?

አቶ ቡልቻ፡- በአሁኑ ጊዜ የህዝቡን የኢኮኖሚ ችግር፣ የኑሮ ውድነት፣ የስራ አጥነት፣ በተለይም የምግብ ዋጋ መናር አለ፡፡ ይህን ሁሉ ህዝቡ ያውቃል፡፡ ታዲያ ህዝቡ ይህን እያወቀ ኢህአዴግን እንመርጣለን ይላል? እንግዲህ እያንዳንዱ ሰው መፍረድ አለበት፡፡ ይህ ሁሉ ችግር እያለ በማን አገር ነው አንድ ፓርቲ 20ና 30 አመት ስልጣን ላይ የሚቆየው? ቻይና ብቻ ነው አይደለም?! እንደ ቻይና ኮሚኒስት እንሁን ብሎ የኢትዮጵያ ፓርላማ ፈቅዷል? ያለ ፓርላማ ፈቃድ የኢትዮጵያ መንግስት እንደፈለገ የሚንቀሳቀስ፣ የፈለገውን ገንዘብ የሚያወጣ፣ የፈለገውን የሚገዛ፣ የፈለገውን የሚሸጥ፣ ዴሞክራሲ እንደሌለ አድረጎ ነው የሚያስተዳድረው፡፡ እንደ ፖለቲከኛ ሳይሆን እንደ ዜጋ ሳየው ተቃዋሚዎች በሚቀጥለው ምርጫ ትልቅ እድል አላቸው፡፡

ነገረ ኢትዮጵያ፡- እርስዎ የሚገልጹት ብሶት መኖሩን ነው፡፡ ግን ተቃዋሚዎች የሚሉትን እድል ለመጠቀም የቤት ስራቸውን እየሰሩ ነው ብለው ያምናሉ?

አቶ ቡልቻ፡- ተቃዋሚዎች የማይፈታ ችግር አለባቸው፡፡ አሁን በቀደም በጋዜጣ ላይ ሳነብ ኢህአዴግ በደግነቱ ለተቃዋሚዎች ገንዘብ ሰጠ የሚል አይቼ በጣም ተደነኩ፡፡ ጋዜጣው ላይ ቃል በቃል ‹‹ለግሷል!›› ይላል፡፡ ይህ እኮ ድንቁርና ወይንም ክፋት ነው፡፡ በየትኛውም ሀገር ምርጫ ሲደርስ መንግስት ለተቃዋሚዎች ገንዘብ መስጠት ግዴታው ነው፡፡ ዋናው የመንግስት ስራ እኮ ነው፡፡ በጀት ያስፈልጋቸዋል፡፡ ካለ በጀት ምንም ነገር አይሰሩም፡፡ የኢትዮጵያ ተቃዋሚዎች አንድ ቦታ ላይ ለመድረስ የኢትዮጵያ በጀት እንዲደርሳቸው ያስፈልጋል፡፡ ይህ ደግነት አይደለም፡፡ የማንም ሀገር ተቃዋሚ በመንግስት በጀት ይንቀሳቀሳል፡፡ ተቃዋሚ አስተያየቱን በግልጽ በጋዜጣ፣ በቴሊቪዥንና በመሳሰሉት ካልገለጸ ማን ይመርጠዋል? እሱ እኮ ነው ኢትዮጵያ ውስጥ የተዘጋው በር፡፡ በሩ ከተዘጋ ተቃዋሚዎች እንዴት ይንቀሳቀሳሉ? በሬድዮና ቴሌቪዥን አትናገሩ ከተባለ፣ ሰላማዊ ሰልፍን ለህዝብ በቴሌቪዥን እንዳይታይ ከተደረገ ተቃዋሚዎች እንዴት ይንቀሳቀሳሉ? እንደዛም ሆኖ ግን ተቃዋሚዎች አሁንም ትልቅ እድል አላቸው ባይ ነኝ፡፡

ነገረ ኢትዮጵያ፡- በመጨረሻ መናገር እፈልጋለሁ የሚሉት መልዕክት ካለ?
አቶ ቡልቻ፡- እንዴት የኢትዮጵያ ህዝብ ዝም ብሎ አንድ ጥያቄ ሳይጠይቅ ይኖራል? ተቃዋሚዎችን በራዲዮና በቴሌቪዥን ያሰሙን ብሎ በሰልፍ አይጠይቅም? እንደዚሁም ደግሞ መንግስት መረጃ አልሰጥም እያለ ሲያስቸግር ህዝቡ አይጠይቅም? የመንግስትን ንብረት አጠቃለሁ፣ የሚገዙበት፣ የሚዙት የኢትዮጵያ ባለስልጣናት ብቻ ናቸው፡፡ የመንግስት ኩባንያዎች ሁሉ በኢህአዴግ ስር ነው የሚተዳደሩት፡፡ ድሮ በአጼ ኃይለስላሴ ጊዜ እንደዚህ ነበር፡፡ ነገር ግን በእርሳቸው ጊዜ እንደዛ የሆነው የግል ባለሀብት ስለጠፋ ነው፡፡ ዛሬ የግል ባለሀብት እንደ ልብ ነው፡፡ ለምንድን ነው የኢትዮጵያ መንግስት ይህን ሁሉ ንብረት የሚቆጣጠረው? የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ ቴሌ፣ አየር መንገድን ሁሉ ለምንድን ነው በስሩ ያደረገው? እኛ ኮሚኒስት ነን እንዴ? ፓርላማ ኢትዮጵያ ኮሚኒስት ነች ብሏል፡፡ ይህ የኢህአዴግ የራሱና የውስጥ አሰራር ነው፡፡ ይህን ለህዝብ መናገር እፈልጋለሁ፡፡

ምንጭ፡ ነገረ ኢትዮጵያ ጋዜጣ ከአዲስ አበባ

የተከበሩ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ብሄራዊ አጀንዳው ያደረገ 4ኛው የኢሳት ክብር በዓል ሲዊዘርላንድ በበርን ከተማ በድምቀት ተከበረ።

$
0
0

ሥርጉተ ሥላሴ (ሲዊዘርላድ –  ዙሪክ)

456

የኢሳት ክብር በዓል ሲዊዘርላንድ በበርን ከተማ

ዕለተ ቅዳሜ 26.07.2014 በጭምቷ ሲዊዝ ርዕሰ መዲና በበርን ከተማ የአንዳርጋቸው ዓላማን ከግብ እናደርሳለን ያሉ የቆረጡ – የወሰኑ – ለቀጣዩ የትግል ጥሪ ሁሉ አለንልሽ ኢትዮጵያ ያሉ ኢትዮጵውያን በተደራጀላቸው የጋራ መጓጓዣ እንዲሁም በግልም አብዛኞቹ ወደ በርን ያመሩት በጥዋቱ ማልደው ነበር።

በእለቱ ከኢሳት አርቲስት ታማኝ በዬነ፤ አርቲስት መታሰቢያ ቀጸላና የስፖርት ጋዜጠኛው ፍሰሃ ተገኘ በአካል ተገኝዋል። በስካይፒ ደግሞ ከግንቦት 7 ከፍተኛው አመራር አካል ዶር. ታደሰ ብሩ ታዳሚ ነበሩ። ስብሰባውን በንግግር የከፈቱት የሲዊዝ የኢሳት አሰተባባሪ ኮሜቴ ሰብሳቢ ወ/ት ሂሩተ ገብርኤል ነበሩ። ከዚህ በመቀጠለም የኢትዮጵያን ዬዕንባ ዘመን ያገናዘበ በምስል የተቀነባበረ ትረካ ፤ የነጻ ሚዲያ  ምስረታና ዕድገት በኢትዮጵያ፤ ሥነ ግጥም  ከሲዊዘርላንድ የኢሳት ዝግጅት ክፍል በቅደም ተከተል ቀርቧል።

ቀጣዩ የኢሳት የገለጻ ክፍል አህዱነት በአርቲስት መታሰቢያ ቀጸላ „አቅምን በመገንባት እረገድ የታላቋ ኢትዮጵያን መከራ በንጽጽር ከአደጉት አገሮች ጋር በማቀረብ ቅድሚያ ሊሰጣቸው በሚገቡ መሠራታዊ ጉዳዮች ላይ አትኮሮት የመስጠትን  አስፈላጊነት በማብራራት፤ ኢሳትን ቋሚ በሆነ መልኩ እራሱን ለማስቻል ሊከወኑ በሚጋባቸው አቅጣጫዎች ላይ   ከእነአስፈላጊነት ዕሴታቸው ጋር አብራርታለች።  አርቲስት መታሰቢያ ቀጸላ ታላቋ ኢትዮጵያ ያልተሰራች ሀገር ናት ባይ ናት። ስለሆነም ትውልዱን በሚጠበቁ የገዘፉ ሃላፊነቶች ላይ መራባረቡ ቀጠሮ አያስፈልገውም ብላለች“።  በቀጣይነት ጋዜጠኛ ፍሰሃ ተገኝ በበኩሉ „የነፃነት አስፈላጊነት ትግል ሁሉንም የመኖር መስኮች የሚመለከት ስለመሆኑ በማውሳት ለጤነኛ የእስፖርት ዕድገትና ለጠንካራ ተዋዳዳሪነት የአንዲት ሀገር የዲሞክራሲ ሥርዓት ተስተካክሎ በእኩልነት መስፍን አዎንታዊነቱን፤ እንዲሁም አለመስፈኑ ደግሞ በሙያው ላይ ያለውን አሉታዊና ገጽታዎች አብራርቷል።“

459

ታማኝ በየነ በሲዊዘርላንድ በበርን ከተማ

በስካይፒ በነበረው የዶ/ር ታደስ ብሩና የአቶ ሥነ ጊዮርጊስ ቃለ ምልልስ ጭብጥም „ዬዘመቻ አንዳርጋቸውን ተሳትፎ በሙቀቱ እንዲቀጥል ለማድርግ ሊተኮር ስለሚገባቸው አምክንያች ገንቢ አስተያዬቶችን አክሎ የቀረበ ነበር። ዶር ታደስ ብሩም በተረጋጋ መንፈስ የዘመቻ አንዳርጋቸው የአጭርና የረጅም ጊዜ መርኃ ግብሮች እንዲሁም ሁለቱን የሚያይዘውን የመካከለኛ ጊዜ ወሳኝ የተግባር ትልሞችን በማስገንዘብ ለተጨባጭ ተግራዊነታቸው የሁሉንም የተዋህደ ተስትፎ  በእጅጉ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ዶር ታደሰ ብሩ የተከበሩ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን እኔ ተማሪው እሱ ደግሞ አስተማሪዬ ነው፣ ሁሉን የሰጠው እያዬህ የምትማርበት የተግባር ሰው ነበር በማለት በአውሮፓ ኮሚሽንን በብርቴን መንግሥት ሊደረግ ስለሚገባው ጫና በተመሰጠ አገላላጽ ሃሳባቸውን ገልጸዋል።“

457

ወ/ት ቅድስት ብሩክ የአንገት ወርቋን ውልቅ እድርጋ ለኢሳት የሰጠች የተግባር እመቤት

በአርቲስት ታማኝ በዬነ በኩል „አንዳርጋቸው ኑሮው በጽናት ላይ የተመሰረተ ተግባርን ያሰበለ በመሆኑ፤ ወያኔ እጥፍ ተግባር ከውነን እናቅጥለዋለን ሲል ገልፆል። የአርቲስት ታማኝ በዬነ የገለጻው ፍላሎት፣ የድምጹ ግርማ ሞገስና የቁጭቱ ግለት ዬወጣቶችን ህሊና በቅጡ የሚያሰናዳ ነበር ማለት ይቻላል።“  እንደ አርቲስት ታማኝ በዬነ ገለጻ „የቆረጠና የነጠረ ትግል ወቅቱ የጠዬቀን ግዴታ በመሆኑ በጠላት ላይ ሊሰነዘር በሚገባው ማናቸውም የማጥቃት እርምጃ ድርድር የለም ብሏል።“

ከዚህ በመቀጠል በነበረው የኢሳት ፈንድ ራይዚንግ ፕሮግራም ጨረታውን የመራው እራሱ አርቲስት ታማኝ በዬነ ስለነበር እጅግ በለሰለሰ – በሚያዝናና – ውብ በሆነ አቀራረቡ የስብሰባውን መሰረታዊ መርሃ ግብር ነፍስ ዘርቶ ሲያስፈልገው ዕንባን – ሲያሰኘው ሳቅን  – ሲለው ወኔን – እንዲያም ሲል እልህን – ሁሉንም ዓይነት ኢትዮጵያዊ ስሜት ፈጥሮ ታዳሚውን በማክበርና በጥሩ አያያዝ ሳይጠገብ ነበር የጨረታው ሂደት የተጠናቀቀው። ወርቅ ዝግጅት ነበር።  ገለጻው በመረጃ የተደገፈ ስለነበርም ጭብጡ ወደ ተግባር ሰራዊቱን ለማሰማራት ልዩ አቅምና ጉልበት ነበረው። ስለሆነም ጨረታው በተግባር ቤቱ የከረንት አፊርስ የመወያያ መድረክ 1300.00 የሲዊዝ ፍራንክ አካባቢ ተጀምሮ በዙሪክ አራት ወጣት አንበሶች በ12.000.00 /አስራ ሁለት ሺህ የሲዊዝ ፍራንክ/ ተጠኗቋል።  የተለያዩ ለሽያጭ የቀረቡ መጸሐፍት፣ ፒኖች፤ አርማዎች ነበሩ። የሲዊዝ የኢሳት አመራር አካላት በሰሞናቱ በተካሄዱ ተከታታይ ሰላማዊ ሰልፎች ሁሉ የተቀናጀ ተግባር የከወኑ ስለነበሩ መሰናዶቸው አንቱ ነበር ማለት ይቻላል። ውጤቱም የሚያመረቃ።

የጨረታው የክብር ታላቅ እንግዳ የነጻነት ትግሉ የጭንቅላት ልብ፤ የመሆን መቻል አድባር፤ የእርቅ ድልድይ፤ የአርቆ ማሰብ አባወራ፤ የማስተዋል ባዕት የሆኑት የተከበሩ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ፎቶ ግራፍ ነበር። ዙሪኮች ስንመለስ ከነክብራችን ነበር የተመለስነው። ስለምን? ወጣቶቻችን ሊቀድሙን  – ሊረከቡን አደራውን – በግንባር ቀደምትንት ተሰለፉልን። በማሸነፍ ውላችን በተግባር አስረው ነበር ወደ ባዕታችን የተመለስነው። ዙሪክ የጀግና አባወራውን ምስል በክብር አክብሮ በተግባር ሊያከበር አብሮን መጣ። በውስጣችንም ነጥሮ ጽላታችን ሆነ የመንፈሳችን ዜማ የአንዳርጋቸው ጽናት ሆነ!

458ስብሰባው ሁለንትናው ሙሉዑና ብቁ ነበር። ኢትዮጵያዊነት ፍቹ በድምቀት ታይቶበታል። እንደሚታወቀው በዚህ ወር ብቻ ሲዊዝ ውስጥ ሁለት ሰላማዊ ሰልፍና አንድ ህዝባዊ ስብሰባ መካሄዱ ነው። የሰዉ ጽናት ከብረት ቁርጥራጭ የተሰራ ነው። ዛሬ እንዲህ የሚያኮሩና የሚያስመኩ ኢትዮጵውያን አዳራሹን ሙሉት አድርገው፤ በተሟላ ተሳትፎ አንደበተ -ኢሳት ፈክቶ የአርበኛ አንዳርጋቸው ቋያ ሳይበርድ እዩኝ እዩኝ ይል ነበር። እውነት ያስደስት ነበር። ያጽናና ነበር። የሚገርመው ነገር የተከበሩት የሰላማዊ ትግል የስልትና የቅንብር መዲናዎች ድንቆቹ የእስልምና እምነት ተከታይ ወገኖቻችን ያፈጠሩት አዳረሽ ውስጥ በተዘጋጀላቸው ልዩ ቦታ የተገባውን ከውነው ነበር። ሃሰተኛ ሳልሆን ይህችን ሥንኝ ስጽፋት በሲቃ ዕንባ እዬተናነቀኝ ነው። ይህቺ ቀን ለእምነቱ ተከታዮች የተከበረችና የተቀደሰች ሆና፤ ነገር ግን መከራ ላይ ስለሆኑ እንዲህ ተሚራቸውንና ማናቸውንም የሚያስፈልገውን ነገር በስንቅ ቋጥረው በወል ማዕዶት የእናት ሀገር ዕንባ እዬታሰበ ተከበረ። ይህ ለሲወዘርላንድ ብቻ ሳይሆን በመላ ዓለም ለተበተኑ ህዝብ እስልምና እምነት ተከታዮች አብነቱ ዘመን የሚያሻግር፤ ዘመንም የማይሽረው ጉልት ነው እላላሁ በጣም በበእርግጠኝነት እኔ ዘጋቢዋ ሥርጉተ  ሥላሴ። በሌላ በኩል የነፃነት ትግሉ ዬተዋህዶ ልጆችም ዓመታዊ የቅዱስ ገብርኤል በአላቸውን ሉዛን

ቅዱስ ገብርኤል አክብረው ታቦታቸውን አንግሠው፤ የተገባውን ከውነው በኋላም ልባቸውን እንጥልጥል ወደ አደረገው ሀገራዊ ጉዳይ ነበር የገሰገሱት። ወደ ዬቤታቸው አልተመለሱም ነበር።  እነሱም ወደ ዕናባቸው መጡ። አያስደስትም? አያስመርቅም? እውነት አፍርቶ ጽናት እንዲህ አስብሎ ማዬት ነገን ያበጃል። ትውልድንም ይገነባል።

እጅግ የማከብራችሁ የሀገሬ ልጆች አብራችሁኝ እንደምትሆኑ በማመን ሌላም እህታችን ወ/ት ቅድስት ብሩክ ለኢሳት  ዬአንገት የወርቅ ሃብሏን ውልቅ አድርጋ ሰጠች። የተግባር እመቤትንት – ሴቶች!  በቃ! እኛ ጨክነናል! ቆርጠናል! ወስነናል! አንዳርጋቸው የእኛ –  እኛም  የአንዳርጋቸው አሉ ሲዊዞች።

በተረፈ መስተንግዶው ሙሉ ነበር። ጠጁ  - ቡናው – እንጀራው – ዝግኑ – አልጫው  - ድፎው ምን ይቀራቸዋል የሲዊዝ ሴቶች – የሴት አርቂዎች እኮ ናቸው – ፍቅሮች። የዛሬ የሴቶች ተሳትፎ ጎምርቷል። ድምቋል። ዬኢትዮጵያ መከራ የሚያልቀው ሴቶች በነቂስ ወጥተው በባንዳው ወያኔ በሽፍታው ወያኔ ላይ ሲሸፍቱ ብቻ ነው። ቁልፉ ይህ ነው። ፍላጎት ከጸዳ መነገዱ እረዳ

 

 

 

 

 

 

 

 

የቻይናው ሁጂያን ግሩፕ በ2.2 ቢሊዮን ዶላር የኢንዱስትሪ ዞን ሊገነባ ነው

$
0
0

-138 ሔክታር መሬት ተረክቧል

China.በአዲስ አበባ ዙሪያ የኦሮሚያ ልዩ ዞን አካል በሆነችው ዱከም ከተማ በሚገኘው የቻይና ኩባንያዎች ኢንዱስትሪ ዞን ውስጥ በጫማ ማምረት ላይ የተሰማራው ሁጂያን ግሩፕ የተባለው ኩባንያ፣ የራሱን የኢንዱስትሪ ዞን በለቡ አካባቢ ሊገነባ ነው፡፡

ኩባንያው የኢንዱስትሪ ዞን ፈቃድ በማውጣት ግንባታውን በ2007 ዓ.ም. ለመጀመር ማቀዱንና ለዚህም ተግባር 2.2 ቢሊዮን ዶላር መመደቡን፣ ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ለመረዳት ተችሏል፡፡

ሁጂያን ግሩፕ ለመገንባት ያቀደው የኢንዱስትሪ ዞን የኢትዮጵያ መንግሥት እያዘጋጀ ከሚገኘው ሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ጋር እንዲጣጣም ተደርጎ የተሠራ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡

ኩባንያው በአሁኑ ወቅት ከተሰማራበት የጫማ ምርት በተጨማሪ በሚገነባው የኢንዱስትሪ ዞን ውስጥ በጨርቃ ጨርቅና ልብስ ስፌት፣ በቆዳና ቆዳ ውጤቶች፣ በአግሮ ፕሮሰሲንግ፣ በብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ፣ በኬሚካልና በፋርማሲዩቲካል የመሰማራት ዕቅድ አለው፡፡

በኩባንያው ዕቅድ መሠረት በኢንዱስትሪ ዞኑ ውስጥ 45 ኩባንያዎች እስከ 2012 ዓ.ም. ድረስ ይሰማራሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ በሚገነባው ኢንዱስትሪ ዞን ውስጥ ሁሉም ኩባንያዎች ሥራ ሲጀምሩ በዓመት እስከ 250 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሪ የማስገኘት ዕቅድ አለው፡፡

ለዚሁ ተግባር እንዲረዳው መንግሥት 53 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲያቀርብለት ኩባንያው ይፈልጋል፡፡ በተጨማሪም 15,555 ሜትር ኪዩብ ውኃ በቀን ኢንዱስትሪ ዞኑ እንደሚፈልግ ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡

በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ መንግሥት ኩባንያው የሚፈልገውን ለቡ አካባቢ የሚገኝ 138 ሔክታር መሬት አቅርቦ ርክክብ መካሄዱን ለመረዳት ተችሏል፡፡ የኢንዱስትሪ ዞኑ ግንባታ የሚካሄደው በምዕራፎች ሲሆን፣ በመጀመርያው ምዕራፍ ማለትም በ2008 ዓ.ም. ሦስት የቆዳ ፋብሪካዎች ሥራ የሚጀምሩ መሆኑና በዚህም ሦስት ሺሕ ዜጎች የሥራ ዕድል ያገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

በ2009 ዓ.ም. የፋብሪካዎቹ ቁጥር ወደ ስድስት እንደሚያድግና የተቀጣሪ ሠራተኞች ቁጥርም ስምንት ሺሕ እንደሚሆን፣ በኢንዱስትሪ ዞኑ የሚካተቱ 45 ፋብሪካዎች ሙሉ በሙሉ ሥራ ሲጀምሩ ደግሞ ለ30 ሺሕ ዜጎች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥሩ ዕቅዱ ያስረዳል፡፡

በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ የሚገኘው አንድ የኢንዱስትሪ ዞን ነው፡፡ ይህ የኢንዱስትሪ ዞን ኢስተርን የኢንዱስትሪ ዞን የሚባል ሲሆን፣ በቻይና ኩባንያዎች የተመሠረተ ነው፡፡ ሁጂያን ግሩፕ የተባለው ኩባንያም በዚህ የኢንዱስትሪ ዞን በጫማ ማምረት ላይ የተሰማራ ነው፡፡ ኩባንያው አሁን ባለው ፋብሪካ 500 ሠራተኞችን መቅጠሩና ከዚህ ውስጥም 250 ሠራተኞች ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡ በየቀኑም አንድ ሺሕ ጥንድ ጫማዎችን በማምረት ላይ ነው፡፡

የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ከግብርና ወደ ኢንዱስትሪ ለማሸጋገር የኢንዱስትሪ ዞኖችን ማልማት በኢትዮጵያ መንግሥት እንደ ስትራቴጂ ተይዟል፡፡

ከተማ የሚያክሉ የኢኮኖሚ ዞን የሚል ስያሜ የተሰጣቸው የኢንዱስትሪ ዞኖች የማልማቱ ሥራ በቦሌ ለሚ አካባቢ የተጀመረ መሆኑን የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡

በዚህ የኢንዱስትሪ ዞን ልማት ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ላይ ያመነው የዓለም ባንክም 250 ሚሊዮን ዶላር ብድር በቅርቡ ፈቅዶ የኢትዮጵያ ፓርላማ ብድሩን አፅድቆታል፡፡ የኢኮኖሚ ዞን የተባሉትን ግዙፍ የኢንዱስትሪ ማዕከሎችን የመገንባቱ ሥራ በድሬዳዋና በኮምቦልቻ ከተሞች የመቀጠል ዕቅድ ተይዟል፡፡ የቻይና ኩባንያዎችም በድሬዳዋ የኢኮኖሚ ዞን የመሳተፍ ፍላጎት ማሳየታቸውን ለመረዳት ተችሏል፡፡

Source: Ethiopian Reporter

የኤሌክትሪክ አገልግሎት መቆራረጥ መሠረታዊ ችግር ሆኗል

$
0
0

ከዕለት ወደ ዕለት ችግሩ እየተባባሰ የቀጠለው የአገሪቱ የኤሌክትሪክ ኃይል ሥርጭት አገልግሎት የአገሪቱ መሠረታዊ ችግር መሆኑን ተጠቃሚዎች እየተናገሩ ነው፡፡

eepco-logoከኃይል ማመንጫው በቀጥታ አገልግሎትቱን በማግኘት እየሠሩ ከሚገኙት ጥቂት ኢንዱስትሪዎችና ፋብሪካዎች በስተቀር፣ ሁሉም በሚባል ሁኔታ በቀን ከሁለት እስከ አምስት ጊዜያት ኤሌክትሪክ ኃይል የማይቋረጥበት መለስተኛ፣ አነስተኛና ጥቃቅን ድርጅቶች እንደሌሉ ሁሉም በተመሳሳይ ቋንቋ ‹‹የኤሌክትሪክ ኃይል የለም›› በማለት እየተናገሩ ነው፡፡

ከአሥር ወራት በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎት የተቋረጠባቸው ከአዲስ አበባ በቅርብ ርቀት ላይ ከሚገኙት አነስተኛ ከተሞች ጀምሮ፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በሚል ለሁለት ከተከፈለው ፒያሳ ደጐል አደባባይ ከሚገኘው የቀድሞው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን ዋና መሥሪያ ቤት አካባቢ ጀምሮ፣ በመላው አዲስ አበባ እስከ አንድ ወር ድረስ የኃይል መቋረጥ የሚገጥማቸው ነዋሪዎች ወዴት ሄደው አቤት እንደሚሉ ግራ መጋባታቸውን ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

በአነስተኛ ኢንዱስትሪ ሥራ ላይ የተሰማራው የንግዱ ማኅበረሰብ ለሚሰጠው አገልግሎት፣ ደንበኞቹን በአግባቡ ቀጥሮ የሚሠራውን ሥራ በጊዜና ባለበት ሰዓት ለማስረከብ ፈተና እንደሆነበት ለመግለጽ ‹‹መብራት ካልተቋረጠብኝ በዚህ ቀን አደርሳለሁ፡፡ ለማንኛውም እዚህ ድረስ ለፍተው እንዳይመለሱ ስልክ ደውለው ይጠይቁኝ፤›› በማለት የእሱ ጥፋት እንዳልሆነ እንዲገነዘቡት የሚማፀንበት ጊዜ ላይ እንዳለ ነዋሪዎች እየገለጹ ነው፡፡

ኮርፖሬሽኑ ለሁለት ተከፍሎ የኤሌክትሪክ አገልግሎቱን ዘርፍ በዋናነት የተረከበው የህንዱ ኩባንያ፣ ኢትዮጵያውያን በምክትል ሥራ አስፈጻሚነት መሾሙንና ቀደም ብሎ የነበረውን የኃይል ማስተላለፊያ መስመር በአዲስ የመተካት ሥራ እየሠራ መሆኑ በመግለጹ፣ የተሻለ አገልግሎት እንደሚያገኙ ተስፋ አድርገው እንደነበር የሚናገሩት ሁሉም ተጠቃሚዎች፣ ‹‹ትሻልን ፈትቼ ትብስን አገባሁ›› እንዲሉ አገልግሎቱ እንኳን ሊሻሻል ባለበት መቀጠል አለመቻሉ እንዳሳዘናቸው እየተናገሩ ነው፡፡

ሌላ መሄጃ ስለሌላቸው ፒያሳ በሚገኘው የአገልግሎቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ቢሮ ሲመላለሱ አንዴ ካሳንቺስ፣ ሌላ ጊዜ መካኒሳ፣ አራት ኪሎ፣ ቄራና ኮተቤ ሄደው እንዲያመለክቱ በተላላኪ ወይም በማይመለከተው ሠራተኛ እንደሚነገራቸው የሚገልጹት የመሥሪያ ቤቱ ደንበኞች፣ የሌሊቱን ጨለማና ምግብ ማብሰሉን በሻማ፣ በላምባና በእንጨት ለመጠቀም የተገደዱ ቢሆንም፣ ሥራዎችን ከኤሌክትሪክ ኃይል ውጪ መሥራት ባለመቻላቸው ለከፍተኛ ኪሳራ እየተጋለጡ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ለጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝና ለሁሉም የመንግሥት አካላት አስቸኳይ ደብዳቤ በመላክ ችግራቸውን ለማሳወቅ ቢሞክሩም፣ በተለይ ላለፉት አምስትና ስድስት ወራት ምንም ምላሽ እንዳላገኙ የሚናገሩት የድርጅቱ ደንበኞች፣ አሁን አሁን እንኳን በደብዳቤ በአካል ተገኝተው ባመለከቱበት መሥሪያ ቤት አግባብ ያለው ምላሽ ስላልተሰጣቸው ተስፋ መቁረጣቸውን አስረድተዋል፡፡

መንግሥት ሁሉንም ዜጐች የማስተዳደር፣ መብታቸውን ማክበርና የሚፈልጉትን የማቅረብ ግዴታ እንዳለበት ገልጸው፣ አስቸኳይ መፍትሔ እንዲሰጣቸው እንዲያደርግ ጠይቀዋል፡፡

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ሥራው ከአቅሙ በላይ ሆኖበት ከሆነ መንግሥት ጠይቆ አስፈላጊውን እገዛ ሊያደርግለት እንደሚገባ የሚናገሩት ደንበኞቹ፣ ኢትዮጵያውያኑ ‹‹የበለጠ ዕውቀት እያለን እንዴት በውጭ ዜጐች እንታዘዛለን?›› ማለታቸው እንዳሰጋቸው አንዳንዶቹን ሲያነጋግሯቸው ‹‹ገብታችሁ አነጋግሩት›› የሚል ምላሽ እንደሚሰጧቸውና ይኼ ችግር የኃይል እጥረት ሳይሆን ቀናነት ማጣትና የማኩረፍ ሁኔታ ሳይሆን እንደማይቀር ደንበኞቹ ግምታቸውን ተናግረዋል፡፡

የኤሌክትሪክ ኃይል መቋረጥ ችግር በአንድ ቦታ ብቻ ራሱን ችሎት የቆመ አለመሆኑን የሚጠቁሙት ደንበኞች፣ ኃይል በተቋረጠ ቁጥር የውኃና የስልክ አገልግሎትም እንደሚቋረጥ አስረድተዋል፡፡ ችግሩ መልከ ብዙ በመሆኑ መንግሥት ትኩረት ሰጥቶ አፋጣኝ መፍትሔ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል፡፡

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ደንበኞች የሚያነሱትን ዘርፈ ብዙ ችግሮች በሚመለከት የሚመለከተው ኃላፊ ምላሽ እንዲሰጥ ሪፖርተር ሰኔ 27 ቀን 2006 ዓ.ም. በደብዳቤ ማብራሪያ ጠይቆ ‹‹በአካል ተገኝታችሁ መጠየቅ ትችላላችሁ›› የሚል ምላሽ ተሰጥቶት ነበር፡፡ ኃላፊዎቹ በአካል ለመነጋገር ፈቃደኛ በመሆናቸው ምክንያት የሪፖርተር ዘጋቢዎች ፒያሳ ደጐል አደባባይ አጠገብ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሚስተር ቪ.ኬ ካሬ ቢሮ ሲገኙ፣ ደብዳቤው ለሥርጭት ዋና ኦፕሬሽን ኃላፊ ስለተመራ ሄደው እንዲጠይቁ ተነገራቸው፡፡ የሥርጭት ዋና ኦፕሬሽን ኃላፊ ሚስተር ዲፓክ ማቱርና ደግሞ ለሥርጭት ምክትል ሥራ አስፈጻሚ አቶ ቢትወደድ ገብረአሊፍ መመራቱን በመናገራቸው፣ እሳቸውን ለማግኘት በተደጋጋሚ በቢሮአቸው በመገኘት ማብራሪያ ለማግኘት ቢሞከርም ‹‹የሉም፣ አሁን ወጡና ስብሰባ ላይ ናቸው፤›› በሚሉ ምክንያቶች የድርጅቱን አስተያየት ማካተት አልቻለም፡፡

 

Source: Ethiopian Reporter


በርገር የወያኔ አሎሎ –ከሄኖክ የሺጥላ

$
0
0

ከኢትዮጵያ ውጭ በምንኖር ስለ ኢትዮጵያ ዝም ማለት ያቃተንን ኢትዮጵያውያኖች ወያኔ እንደ አሎሎ የሚጠቀምበት በርገርን ነው።ስለ- መብታችን ስንናገር በርገር እየበላህ ነው ፣ ስለ ግፍ ስናወራ በርገር እየበላህ ነው ፣ ስለ አፈና እና ግድያ ስናወራ በርገር እየበላህ ነው ፣ እስክንድር ለምን ታሰረ ፣ ርዮት ትፈታ ፣ የበቀለ ገርባ እስር ኢ’ፍታዊ ነው ፣ እነ አንዱዓለም አራጌ ስለነጻነት፣ ስለ ፍትሕ እና ርትዕ ምክንያታዊ ጥያቄ ነው ያነሱት ማለት ፣ ህውሃትን የጥያቄውን ስር እንዲመለከት ሳይሆን ይልቁንም በተጣመመ አስተሳሰብ ፣ ነገሩን በመጠምዘዝ ” በርገር እየበላህ” ወደሚል ክርክር እና አግቦ መሰል ፍሬ ከርስኪ ወሬ እንዲምዘገዘጉ አድርጎዋቸዋል ።
andargachew Tsege
ለምሳሌ እኔ አማሪካ ነው የምኖረው ፣ የምኖርበት ሀገር ደሞ የራሱ የሆነ የአመጋገብ ባህል አለው ፣ ከዚያ የአመጋገብ ባህል ውጭ ራስን ሙሉ ለሙሉ ነጻ ማውጣት አይቻልም ፣ የዚያ የምኖርበት ሀገር የ ምጣኔ ሀብት ጥንካሬ ፣ የአስተሳሰብ ሆኔታ ፣ ያ የአስተሳሰብ ሁኔታ ያፈለቃቸው መሳሪያዎች ብሎም እነዚህ መሳሪያዎች የሚያመርቱዋቸው ምርቶች ሁሉ ተጠቃሚ መሆን ብርቅ አይደለም ። ለምሳሌ የእጅ ስልኬ በ አፕል የሚሰራው (አይ ፎን) የተባለው ነው፣ ከቤቴ ፊት ለፊት የመዋኛ ገንዳ አለ፣ ሁለት አዳዲስ ሞዴል መኪኖች አሉኝ ፣ በአሜሪካ የኑሮ ደረጃ የመካከለኛ ገቢ እርከን ላይ ካሉት ውስጥ ልመደብ እችላለሁ ፣ ለልጄ በዓመት ለሞግዚት የምከፍለው በአሁኑ የኢትዮጵያ ብር ሲሰላ ከ ሁለት መቶ ሺ ብር በላይ ነው ፣ ማቀዝቀዣዬ ውስጥ ( ለጌጥም ቢሆን እንኩዋ ) ብዙ አይነት መጠጦች፣ ፍራፍሬዎች አሉ ፣ ቅዳሜ ቅዳሜ በል ካለኝ የመርከብ ላይ ጉብኝት አደርጋለሁ ፣ ከፈለኩ የፈለኩትን ጸሐፊ መጽሐፍ ከአማዞን ላይ ገዝቼ ማንበብ እችላልሁ፣ በርገር ብቻ ሳይሆን ፣ ላዛኛ ፣ ሱሺ ፣ ሚት ቦል፣ ስቴክ ፣ ቺክን ክባብ ወዘተ ወዘተ እበላለሁ ። እንግዲህ ይሄ የምኖርበት ሀገር ራስን ለመርሳት የተመቸ ፣ እጅግ በጣም ልብ የሚሰልብ ፣ ቀልብ የሚስብ ፣ በሕልቅ ውበት የተሞላ መንደር ነው ማለት ነው ። ግን ያም ሆኖ ስለ ኢትዮጵያ እጮካለው ፣ ስለ ሀገሬ ዝም አላልኩም ፣ የመጨረሻውን መስዋትነትም ልከፍል መንገዴን ሀ ብዬ ጀምሬያለሁ ።

አንተ ግን እስከ አሁን ከተናገርኩት ፣ እስከ ዛሬም ይሄን ሁሉ ምቾት ጥሶ ፣ ከዚህ ሁሉ ሙቀተ ሕይወት ገዝፎ ስለተናገርኩት ማንነት ፣ ሃገሬ ስለምላት ሀገሬ ስላወራሁት እውነት ሳይሆን በርገር መብላቴ ያስቆጨህ ይመስላል ፣ ያሳዝናል ። ባታውቀው ነው እንጂ እኮ አንተ ያለህበት ሀገር ጨጨብሳ ፣ ስልጆ፣ ክትፎ፣ ዶሮ፣ ሃምባሻ፣ ሕብስቲ፣ ጠላ፣ ጠጅ፣ ቁርጥ ፣ ሸክላ ጥብስ ፣ ተጋቢኖ ፣ አረ ስንቱ ስንቱ አለ መሰለህ ፣ ግን እሱን እንኩዋ እየበላህ አይደለም ። ቢገባህ በርገር እየበሉ ነው የሚሉህ አለቆችህ ፣ እነሱም ከላይ የጠቀስኩትን ምግብ እየበሉ ነው አንተን ወታደር ፣ ድንጋይ ፈላጭ ፣ ህገ መንግሱትን ጠባቂ ፣ ልማታዊ ፣ ሕዳሴያዊ ፣ ገለመኔ ገለመኔ ሁን የሚሉህ። ደሞ በርገር እኮ ምንም የተለየ ነገር አይደለም ፣ በ ዘይት የተጠበሰ ሙዳ ስጋ ነው ፣ ታዲያ ሙዳ ስጋ ኢትዮጵያ የለም? አለ ! አንተ ግን አይተኸው ታውቃለህ ? አታውቅም ፣ ምክንያቱም በርገር እየበሉ የሚሉህ አለቆች ወጥ አርገው እየበሉት ስለሆነ አንተን አይታይህም። አየህ በርገር በ ቀይ ወጥ መልክ እየበሉ ፣ በርገር በክትፎ መልክ እየበሉ ፣ በርገር በጥብስ መልክ እየበሉ ፣ አንተን ድንጋይ እያስፈለጡ ፣ ወታደር አርገው ጸሓይ እያሥቀጠቀጡ ፣ በርገር እየበሉ ይሉሃል ። እኔ ዝም ብል ምን የማጣ ይመስልሃል ( እንደው ቁም ነገሩ ለራስ መሆን፣ ለራስ መኖር ከሆነ )፣ ምን እንዳይጎልብኝ ነው ስላንተ የምጮኸው? ምን እንዳላጣ ። ከገባህ ነጻነት የምግብ ጥያቄ አይደለም ፣ ግን የምግብ ጥያቄ ነጻነት በሌለው ስርዓት ውስጥ የሚጠየቅ ጥያቄ እንጂ። አየህ እኔ በርገር እየበላሁ ዝም ብዬ መተኛት አልቻልኩም ፣ ያንተ ቁርጥ አለመብላት አሳስቦኛል ማለት ነው ፣ የሀገሬ የወደፊት ዕጣ ፈንታ አስጨንቆኛል ማለት ነው ፣ መናቅ አብሽቆኛል ማለት ነው ።

እስኪ ማን ይሙት ስለ ሀገር መጮህን በርገር ከመብላት ጋ ምን አገናኘው ? ወይስ ባዶ ሆዳችሁን ተቃወሙን እያሉ ነው ያሉት ? አልገቡኝም ፣ አይገቡኝም ። ጉራ ፈርዳ ላይ ስለተፈናቀሉት ዘመዶቼ መናገር በርገር ከመብላት ጋ ምን ያገናኘዋል ፣ የኦሮሞ ገበሬን መሬት በግፍ መቀማት አግባብ አለመሆኑን ማጋለጥ ከበርገር ጋ ምን ያገናኘዋል ፣ እስክንድር ነጋ እኮ የታሰረው ማክዶናልድ ዘይት ሰርቆ አይደለም፣ የአንዱዋለም ጥያቄ ጃክ እን ዘ ቦክስ ወይም ኬ-ኤፍ-ሲ አስቀጥሩን የሚል አልነበረም፣ ርዮት አለሙ እኮ የታሰረችው ፣ ቀኑ ያለፈበት ምግብ ( በርገር ) ስትሸጥ አይደለም ፣የሕዝበ ሙስሊሙ የመጅልስ ጥያቄ ከበርገር ጋ ምን አገናኘው ? አቡበከር የጣልያን ባሬስታ ልሁን እኮ አላለም፣ የጣልያን እንቁላል አዙዋሪ ልሁን አላለም ! ብሎዋል እንዴ? ማወቅ ከፈለክ ይህንን ጽሑፍ ስጽፍም ፒዛ እየበላሁ ነሁ ( ፒዛ ማለት ምን ማለት መሰለህ ፣ ጨጨብሳ ታውቃለህ ፣ ወይም ፈታ አዋ በቃ እሱ ነው )፣ እመነኝ እንጀራ ስበላ ግን ወያኔን ውሃ ውሃ የሚያስብል ግጥም ነው የምጽፈው ! ደሞ ተጋዳላይ ለመሆን የግድ አንበጣ መብላት ፣ ድንጋይን እንደ ግብር ውሃ መጠቀም ፣ ሰውነቴ ላይ ቅማል መፍላት አለበት ብለህ አታስብ ፣ መሆን ሲኖርበት ደሞ እናደርገዋለን ፣ እመነኝ ቅማል ብርቄ አይደለም ፣ ከቅማላሞች ጋ 20 ዓመት ኖረያለሁ ! ታዲያ ምንደን ነው ይሄ በርገር እየበሉ ፣ በርገር እየበሉ ።

ይቺ ” በርገር እየበሉ ” የወያኔ አሎሎ ናት ፣ ግን ወንጭፍ የሆንከው አንተ ነህ ፣ እስቲ ረጋ ብለህ አስበው ፣ እኔ ለምን እጮኸለው ? ታማኝ ለምን ይጮሃል ፣ እያሱ አለማየሁ ለምን ይጮሃል? ብርሃኑ ነጋ ለምን ይጮሃል ? ሲሳይ አጌና ለምን ይጮሃል ? መሳይ መኮንን ለምን ይጮሃል ? ተክሌ የሻው ለምን ይጮሃል ? ቡልቻ ደመቅሳ ለምን ይጮሃል ? አበበ ገላው ለምን ይጮሃል ? ( ልዩነታችን እንዳለ ሁኖ፣ ሲገባኝ ይሄ ሁሉ ሰው ግን የሚጮኸው የሚቀጥለው ወር የበርገር አገልግሎት እንዳይቁዋረጥ ብሎ አይመስለኝም

ዒድ አልፊጥርን አስመልክቶ በእስር ከሚገኙት የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎች የተላከ ወቅታዊ መግለጫ

$
0
0

 

እሁድ ሐምሌ 20/2006

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ በጣም አዛኝ (በሆነው)

343ምስጋና ለዓለም ችግሮች ሁሉ መፍትሄ ላወረደና በእርሱ መንገድ ላይ ጥረት የማድረግን ክብር ላጎናፀፈን የዓለማት ፈጣሪ አላህ (ሱ.ወ) ይሁን! ክብርና ሰላም የሰው ልጆችን ከጨለማዎች ወደ ብርሃን ለማውጣት በአላህ በታጩትና የነብያቶች ቁንጮ እና መደምደሚያ በሆኑት ነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ)፣ በባልደረቦቻቸውና በተከታዮቻቸው ላይ ይሁን!

ውድ የነብያት ወራሽ የሆናችሁ ዑለሞች፣ ውድ አላህ ጀነትን በእግራችሁ ስር ያደረገላችሁ እናትና አባቶች፣ ውድ ለእንክብካቤያችሁ አደራ የተባልንባችሁ እህቶች፣ ውድ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) እንድናከብራችሁ ያዘዙን ታላቆቻችን፣ ውድ እንድናዝንላችሁ ያዘዙን ታናናሾቻችን፣ ውድ አላህ (ሱ.ወ) ከስጋ ወንድምነት በላይ ወንድምና እህት እንድናደርጋችሁ ያዘዘን ወንድሞቻችን እህቶቻችን፣ ‹‹ከስሜታችን እና ስጋችን በላይ ለመሆን እና ነፍስያችንን ድል ለማድረግ ስላበቃን ለምናከብረው እና የደስታ ቀናችን ለሆነው ለ1435ኛው የዒድ አል-ፈጥር አደረሳችሁ›› እንላለን!

ይህን መልዕክት ስናስተላልፍ ሰላማዊ የመብት ጥያቄ አንስተን ነጭ ሶፍት በማውለብለባችን ዱላ በመምዘዝና ጥይት በማርከፍከፍ ደማችንን ያፈሰሱና ያስፈሰሱ፣ ያሰሩና ያሳሰሩ፣ የደበደቡና ያስደበደቡ፣ የሃይማኖታችንን እና የእህቶቻችንን ክብር የነኩና ያስነኩ የመንግስትና የህገ ወጡ መጅሊስ አካላት ‹‹እንኳን አደረሳችሁ!›› በማለት የሚያስተላልፉት የስላቅ መልዕክት የሚፈጥርባችሁን ህመም በመጋራት ነው።

የ1435ኛው ዓመተ ሂጅራ የዒድ አል-ፈጥር በዓል በአላህ መንገድ ላይ ፀንተን በመታገል ላይ እያለን መድረሱ ልዩና አስደሳች ዒድ ያደርገዋል። በመሆኑም የዘንድሮው ዒድ በታላቅ ደስታና አላህ (ሱ.ወ) ለዋለልን ለዚህ ታላቅ ውለታ ምስጋና በማቅረብ የምናሳልፈው ዒድ ይሆናል።

የተከበራችሁ ምእመናን!

ባለፉት ሶስት ዓመታት በእያንዳንዱ ሰላማዊ የመብት ጥያቄ እንቅስቃሴያችን የአላህን የቅርብ እርዳታና እገዛ፣ እንዲሁም እዝነት በግልጽ እና በተጨባጭ አይተናል። ሂደቱንም ወደ ታላቅ እና መልካም ደረጃ ሊያደርሰው እንዳጨው እርግጠኛ እንድንሆን ያደረጉንን በርካታ ክስተቶችንም አስተውለናል። ህዝባችንን አላህ (ሱ.ወ) እንደመረጠው፣ እንደወደደውና በእዝነት አይኑ እንዳየው የሚያረጋግጡ ምልክቶችንም ተመልክተናል።

እኛ ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች አዲስ ምዕራፍ የከፈትንበትን ሕጋዊና ሰላማዊ የመብት ጥያቄ ካነሳን ሁለት ዓመት ከመንፈቅ ሆኖናል። ከዚህ እልህ አስጨራሽ ጊዜ በኋላም ከታላቁ ረመዷን ባህሪ እና ትክክለኛ ትርጉም ጋር የሚጣጣም የፅናት ወኔ ተላብሶ ድል እያስመዘገበ መቀጠል ችሏል። በርካታ ታሪካዊ ድሎች ሙስሊሞች በተቅዋ (ፈሪሃ-አላህ) ለመሆን በሚታነፁበትና ወደ አላህ ይበልጥ በሚቀርቡበት በዚሁ ታላቁ ወርሃ ረመዷን መመዝገባቸው ይታወቃል።

ህዝባችንም ሕጋዊና ሰላማዊውን የመብት ጥያቄ ካነሳበት ጊዜ አንስቶ በነበሩት ሦስቱ ረመዷኖች ከስሜቱ በላይ በመሆንና ለኢስላም መስዋዕትነትን ለመክፈል በመዘጋጀት፣ ነፍሱን ድል በማድረግ እና የመንግስትን ክፉ ምኞት በማኮላሸት ታላላቅ ድሎችንና ታሪኮችን አስመዝግቧል። ሦስቱ ረመዷኖች ታሪካዊ፣ እጅግ ጣፋጭና አስደሳች፣ እንዲሁም በምድራዊም በሰማያዊም ሂሳብ ትልቅ ድሎችና ታሪኮች የተመዘገቡባቸው ናቸው። መንግስት ንፁህና ሰላማዊ በሆነው ውድ ህዝባችን ላይ የፈፀማቸው ኢ-ሕገመንግስታዊ እና ሰብዓዊነት የጎደላቸው ተደጋጋሚ እርምጃዎች ለሙስሊሙ ጥንካሬን፣ ብስለትን እና አንድነትን ሲያጎናፅፉት በሌላ በኩል መንግስት ምን ያህል ኢስላምንና ሙስሊሙን፣ በአጠቃላይም ሃይማኖትን ለማጥቃት ታጥቆ እንደተነሳ እንዲገነዘብ አድርገውታል። ይህም መንግስት ሽፋን ያደረገው ጥቁር መጋረጃ ተገፍፎ እርቃኑን እንዲቀርና ማንነቱ እንዲጋለጥ አስችሏል።

የተከበራችሁ ውድ ኢትዮጵያዊ ወገኖቻችንና ወንድሞቻችን!

መንግስት ላይ ከተጣሉ ኃላፊነቶች ውስጥ ዋናው እና መሠረታዊው በአንድ ሀገርና ባንዲራ ስር በተጠለሉ የተለያዩ እምነት ተከታይ ወንድሞች መካከል መልካም ግንኙነት እና ትብብር እንዲኖር ማድረግ መሆኑ ይታወቃል። ነገር ግን ሁሉም ኢትዮጵያዊ በግልፅ በአደባባይ እንዳየው ተቃራኒ በሆነ እና ፍፁም ኃላፊነትና ሰብዓዊነት በጎደለው መልኩ በአንዳንድ የተለየ ዓላማ ባነገቡ ሚኒስትሮች መሪነት መንግስት ያለውን ኃይልና ስልት በመጠቀም በሁለቱ ታሪካዊና ጥንታዊ ሃይማኖቶች መካከል ግጭትና አለመግባባት ለመፍጠር ተንቀሳቅሷል። ሆኖም ይህ እጅግ አሳዛኝና ኃላፊነት የጎደለው ፀያፍ ተግባር ጨዋና አስተዋይ በሆኑት የሁለቱ እምነት ተከታዮች ጠንካራና ተከታታይ ጥረቶች ሊከሽፍና መልካም ውጤቶችንም ሊያስመዘግብ ችሏል።

አንድ ወገን የሆኑት የሁለት እምነት ተከታዮች እርስ በእርስ ተጋጭተው በደማቸው የመንግስትን የስልጣን እድሜ እንዲያረዝሙት ቢታጩም ለዓለም ምሳሌ የሚሆኑና የመከባበር እና የመፈቃቀር መገለጫ የሆኑ ተግባራትን በማከናወን የመንግስትን ሰይጣናዊ ምኞት መና አስቀርተውታል። ክርስትያኑ ማህበረሰብ ሙስሊሙንና ኢስላምን ለማጠልሸት መንግስት የከፈተውን ዘመቻ ንቆ በመተው እና ሀሰትነቱን በመረዳት መንግስት እርምጃ ሊወስድባቸውና ደማቸውን ሊያፈስ ያሳድዳቸው የነበሩ ሙስሊሞችን ቤቱንና ቤተ-ክርስትያኑን ከፍቶ ሸሽጓል፤ አስጠግቷልም። በዚሁ ረመዷን በሌሊት መንግስት የተከበረ ገላቸውን አራቁቶ በሌሊት የላካቸውን ጥብቅ እህቶቻችንን ልብስ በማልበስና ለቆሰሉ አካሎቻቸው እርዳታ በመስጠት ሰብዓዊነት በተሞላበት ሁኔታ ሃይማኖታዊና ሀገራዊ ግዴታቸውን ተወጥተዋል። በዚህም መላው የክርስትያን ማህበረሰብ ሙስሊሙ የማይረሳውን ታሪካዊ ውለታ የዋለ ሲሆን የመከባበርና የመቻቸል ተምሳሌት የሆነ ተግባርም ፈፅሟል። ለዚህም የክርስትያን ወገኖቻችን ምላሽ መንግስት ሊፈጥረው ያሰበውን ብዥታ ሙስሊሙ ለመቅረፍና ቅንና ንፁህ አመለካከቱን ለማሳወቅ ያደረገው በሳል ጥረት፣ እንዲሁም ሙስሊሙ ያነሳው የመብት ጥያቄ ሁለቱም በጋራ ሊቆሙለት የሚገባ ሕጋዊ፣ ሃይማኖታዊ፣ ሕገ-መንግስታዊና ሰላማዊ መሆኑ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ማበርከቱን መገመት አያዳግትም። መንግስት ህዝቡን አክብሮ የህዝብን ጥያቄና ሃሳብ ለመስማት እንደማይችልና ለመስማትም ዝግጁ እንዳልሆነ ለዓመታት በተግባሩ ቢያረጋግጥልንም አሁንም በሃይማኖቶች መካከል ግጭት እንዲፈጠር መጣር ሀገሪቱን ለውድቀት፣ ህዝቡንም ለእልቂት የሚዳርግ የክፋት መንገድ ነውና መንግስት ልቦና ገዝቶ ከዚህ ዓይነቱ ተግባር እንዲቆጠብ አጥብቀን እንጠይቃለን።

የተከበራችሁ ምእመናን!

በባርነትና በውርደት ለመኖር ፈቃደኛ ያልሆነ ማንኛውም የተከበረ ህዝብ ሊያሳካው የተንቀሳቀሰለትን ክብር የሚመጥን መስዋዕትነት መክፈሉ ግዴታ መሆኑ ተረድታችሁ መስዋዕትነት እየከፈላችሁለት ያለው መንገድ ትክክለኛው የእውነት መስመር መሆኑን ልናበስራችሁ እንወዳለን። ዛሬ ጥቂት መስዋእትነት ከፍለን ይህንን ግፍ ማስቆም ካልቻልን ነገ መጪውን ትውልድ ለህሊና ለሚዘገንን ስቃይና መከራ እንዳርገዋለን። መስዋእትነት ባደረ ቁጥር በእጥፍ የሚከፈል እንጂ እየቀነሰ የሚመጣ አይደለም። ዛሬ መስዋእትነት ላለመክፈል ብናፈገፍግ ነገ በእጥፍ የምንከፍለው በመሆኑ አሳድረነው በሚፈጠረው ተጨማሪ ጥፋትና አደጋ በታሪክም በአላህም ፊት ከመጠየቅ ዛሬ መስዋእትነትን ለመክፈል የመረጥነው መንገድ ከተጠያቂነት የሚያድን ትክክለኛ ውሳኔ መሆኑ ለማረጋገጥ እንወዳለን።

በዚህ ሦስት ዓመት ውስጥ ያስመዘገብናቸውም ሆነ በቀጣይ የምናስመዘግባቸው ስኬቶችና ድሎች ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ በመንግስት በተወሰደባቸው ኢ-ሕገመንግስታዊ እርምጃዎች መገኖቻችን በከፈሏቸው የተለያዩ መስዋዕትነቶች የተገኙና የሚገኙ ናቸው። እያንዳንዱ ሰው ላይ የደረሰው ጉዳት እና የደም ጠብታ ስኬት እና ድላችን ላይ የራሱን ተጨማሪ አስተዋፅኦ አበርክቶ አልፏል። ወደ ስኬትም እንድንቃረብ እገዛ አድርጓል።

በከንቱ ተከፍሎ የቀረ መስዋትነት የለም፤ አይኖርምም። በመንግስት የተወሰዱ እና የሚወሰዱ እርምጃዎች ወኔያችንን እና ጥያቄያችንን ከፍ ያደርጉታል እንጂ ፈፅሞ በሞራላችንም በአቋማችንም ላይ ለውጥ አያመጡም። የእስከዛሬው የህዝባችን ምላሽም ለዚህ በቂ ምስክር ነው!

የተከበራችሁ ምእመናን!

በሙስሊሙ ላይ ሴራውን ከመጠንሰስ ጀምሮ እስከ መተግበሩ የተሳተፉ እና በንዋይና በስልጣን ፍቅር ታውረው ከተቃራኒ ወገን ጋር የተሰለፉ ጥቂት ሙስሊሞችን ሙስሊሙ ማህበረሰብ እና መላው የኢትዮጵያ ህዝብ የሚፋረዳቸው ጊዜ ሩቅ እንደማይሆን ያለንን ተስፋ ልንገልፅላችሁ እንወዳለን። በተቋማችን መጅሊስ ውስጥ የተኮለኮሉት አመራሮች እና የመንግስት አካላት ባጠቃላይ ጸረ-ሃይማኖት የሆነ አቋም በመያዛቸው እና ለመብትና ነፃነት ደንታ የሌላቸው ከመሆናቸውም በተጨማሪ ባላቸው አቅም ሁሉ ለመጅሊስ እንዲዋትቱ ያደረጋቸው በየአመቱ በሃጅ ጉዞ ምክንያት ከሙስሊሙ የሚመዘብሩት በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ በመሆኑ መላው ሙስሊም ማህበረሰብ ለችግሩ መፍትሔ እንዲፈልግለትና አፋጣኝ እርምጃ እንዲወስድ ለመጠቆም እንወዳለን።

የተከበራችሁ ሙስሊሞች!

በማንኛውም ጉዳይ ላይ አንድነታችንን ጠብቀን በጋራ የምንጓዝ ከሆነ ማንም መብታችንን ሊገፍ እና ሊያጠቃን እንደማይችል ግልፅ እንደመሆኑ እና በቁርአን እና በሃዲስ በጥብቅ የታዘዝንበት በመሆኑ አንድነታችንን አጠንክረን መያዝ እንዳለብን አበክረን ለማሳሰብ እንወዳለን። በተለይ ባለፉት ሶስት ዓመታት ውስጥ በሃገር ውስጥም ሆነ በዲያስፖራው ሙስሊም ማህበረሰብ መካከል የሚታየው አንድነት ተስፋ ሰጪ በመሆኑ ኡለሞች (የሃይማኖት ሊቃወንት)፣ ዳዒዎች (ሰባኪያን)፣ ምሁራን እና መላው ሙስሊም ማህበረሰብ በመረባረብ መሰረት ማሲያዝ እና ወደሚፈለገው ደረጃ ከፍ ማድረግ ጊዜ የማይሰጡት ሃላፊነታቸው ሊሆን ይገባል።

ሃይማኖትም ሆነ ሌላ ሽፋን በመላበስ ሙስሊሙን ለመከፋፈል የሚደረጉ ጥረቶችን ሙሉ በሙሉ በፅኑ እናወግዛለን። አንድነትን በምኞት ብቻ እውን ማድረግ የሚቻል ባለመሆኑ፣ እንዲሁም ብዙ ጥረት እና ጥንቃቄ የሚጠይቅ በመሆኑ አንድነታችንን ከሚያናጉ ነገሮች መራቅ እና አንድነታችንን ሊያጠነክሩ የሚችሉ ተግባራትን ደግሞ በቆራጥነት መፈጸም እንደሚገባን አደራ ለማለት እንወዳለን።

የተከበራችሁ የሙስሊሙ ማህበረሰብ አባላት!

ለመብት እንቅስቃሴው ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረከቱ በርካታ ሰዎች ለእስር፣ ለማህበራዊ ቀውስ፣ ከስራ ለመፈናቀልና ለሌሎችም ችግሮች መዳረጋቸው ይታወቃል። እነዚህን ወገኖቻችንን መዘየር፣ አስፈላጊውን ትብብር እና እገዛ ማድረግ የአላህን ውዴታ የሚያስገኝ፣ አንድነታችንን የሚያጠናክርና የመብት ትግላችንን በድል ዙፋን ላይ ለማስቀመጥ የሚያግዝ በመሆኑ ሁላችንም በየአካባቢያችን የበኩላችንን አስተዋፅኦ እንድናበረክት ጥሪያችንን እናስተላልፋለን። ከዚህም በተጨማሪ ሁሉም ሙስሊም ደስተኛ ሆኖ እንዲያሳልፍ ሁላችንም በዙሪያችን የሚገኙትን ሚስኪኖች፣ የቲሞች፣ ኡለሞች፣ ታማሚዎች እና የተለያዩ ችግሮች የደረሱባቸውን የማህበረሰቡን ክፍሎች መንፈሳዊ እና ቁሳዊ ድጋፍ በማድረግ መርዳት ይኖርብናል።

የተከበራችሁ ሙስሊሞች!

አምባገነን መንግስታት ማንኛውንም ሰላማዊ የመብት ጥያቄ ለማደናቀፍ በሚያደርጉት ጥረት በዋነኝነት ሊያሳኩ የሚፈልጉት ሁለት መሰረታዊ ስኬቶችን ነው። አንደኛው ለመብት ጥያቄው ፈፅሞ ምላሽ እንደማይሰጡ ለማሳመን በመሞከር የመብት ጠያቂውን ተስፋ ማሰቆረጥ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ በሚወስዷቸው አምባገነናዊ እርምጃዎች ህዝቡ ተበሳጭቶ ሰላማዊነቱን ጥያቄ ውስጥ የሚከት የሃይል ምላሽ ውስጥ እንዲገባ ማድረግ ነው። ይህ የአምባገነኖች ፍላጎት እንዳይሳካ በማድረግ እስከፍፃሜው መንቀሳቀስ የቻለ ማንኛውም እንቅስቃሴ ጉዞውን በስኬት ያጠናቅቃል። የእኛ ሰላማዊ እና ህጋዊ የመብት እንቅስቃሴም የመንግስትን ምኞት እንዳይሳካ በማድረግ ተስፋ ሳይቆርጥ እና ስሜታዊነት ውስጥ ገብቶ ህግ ሳይጣስ በራሱ ድል መስመር መጓዝ ችሏል፤ ወደፊትም ይበልጥ በሰከነ እና በበሰለ ሁኔታ በመጓዝ በአላህ ፈቃድ ስኬትን ይጎናጸፋል።

የተከበራችሁ መብት ጠያቂዎች!

ሙስሊሙ ማህበረሰብ ከመነሻው ያቀረባቸው ሶስቱ ህጋዊ የመብት ጥያቄዎች በማንኛውም የመብት ጥያቄ እንደሚመከረው ቀላል እና ከመንግስት ጋር ውይይት በማድረግ የተጀመሩ ናቸው። የመብት ጥያቄውም አመክንዮአዊ ሆኖና የመብት ጥያቄ ህግን እና ሳይንስን ተከትሎ ሲጓዝ በተቃራኒው የመንግስት ምላሽ ግን በተሳሳተ እርምጃ የታጀበ በመሆኑ መንግስት የራሱን አባላት እንኳን ማሳመን ሲሳነው ተስተውሏል። የመብት ጥያቄ እንቅስቃሴውም ሃያል እና ብቸኛ በሆነው ፈጣሪ ፈቃድ ዋነኛ ስኬት የሆነውን ህዝብን ከጎን የማሰለፉን አላማ ለማሳካት ችሏል።

መንግስት ተቋማችንን በመቆጣጠርና ትክክለኛውን አስተምህሮ የሚቃረን ርእዮተ አለም (Ideology) ወይም ቡድን (Sect) በማዘጋጀት፣ የዕውቀት ማሰራጫ ማዕከላት የሆኑትን መስጂዶች፣ መድረሳዎች፣ መርከዞች ወዘተ በመቀማት፣ እንዲሁም በዩኒቨርስቲ፣ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች፣ በተለያዩ የንግድ እና የሙያ ዘርፎች ላይ የተሰማሩ ለሃይማኖታቸው ተቆርቋሪ የሆኑ ሰዎችን በማስወገድ እና በማሽመድመድ ይዞት የተነሳውን ለሃይማኖት ደንታቢስ የሆነ ማህበረሰብ የመፍጠር አላማ ለማሳካት ቢንቀሳቀስም የሙስሊሙ የመብት ጥያቄ መነሳት መንግስት ህዝባዊ መሰረት እና ተቀባይነት እንዳይኖረው በማድረጉ ይህ ለሃገርም ለወገንም ጎጂ የነበረ ክፉ ውጥን ሳይሳካ ሊቀር ችሏል። ይህ ለሙስሊሙ ብቻ ሳይሆን ለመላው ሃይማኖት ወዳድ ለሆነው ኢትዮጵያዊ ትልቅ ስኬት ነው።

መንግስት ሙስሊሙ ላይ የከፈተውን ዘመቻ በስኬት ቢያጠናቅቀው ለጥቃት በተመቸው ታሪካዊ እና ቀደምት በሆነው የክርስትና እምነት ላይ በሙሉ ሃይል ይከፍት የነበረውን ዘመቻ አና ጥቃት መገመት አያዳግትም። ከዚህም አንፃር ሙስሊሙ ማህበረሰብ ላነሳቸው ሶስት የመብት ጥያቄዎች መላው ሃይማኖት ወዳድ ኢትዮጵያዊ ምንም አይነት አስተዋፅኦ ቢያደርግ እና መስዋት ቢከፍል አግባብነት ያለው ነው ብለን እናምናለን።

ከዚህ ጋር ተያይዞ ተራ የመንግስትን ፕሮፖጋንዳዎች እና ማጠልሸቶች ንቆ በመተው፣ ሃገሪቷን እየመሩ ከሚገኙ አካላት በላይ በሳል እና አስተዋይ በመሆን ህጋዊ፣ ህገ መንግስታዊ እና ሰላማዊ የሆነውን የሙስሊሙን የመብት ጥያቄ የሁሉም ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ ጥያቄ ነው ብላችሁ፣ ጥያቄያችንን ጥያቄያችሁ በማድረግ ከጎናችን የተሰለፋችሁ እና የበኩላችሁን አስተዋፅኦ ያበረከታችሁ ወገኖቻችንን እና ወንድሞቻችንን ሁሉ ከልብ እናመሰግናለን። የክርስትና እምነት ተከታይ ጋዜጠኞች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሃገር ውስጥ እና የአለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች፣ ምሁራን፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የለውጥ ሃዋርያት (Activists) እና የተለያዩ ሚዲያዎች ይህ ምስጋና ይበልጥ የሚገባችሁ እና ቀዳሚዎች መሆናችሁ አያጠራጥርም!

ከዚህ ጋር በማያያዝ ሙስሊሙ ላይ የሚታየው መብቱን የማስከበር ጠንካራ ፍላጎት እና መነቃቃት ለሙስሊሙ ብቻ ሳይሆን በሃገራችን ፍትህ፣ ነፃነት፣ እድገት እና ብልፅግና እንዲሰፍኑ ለማድረግ እጅግ ጠቃሚና ወሳኝ በመሆኑ በሃገር ደረጃ ሊጠቅሙ የሚችሉ ህልሞችን በመሰነቅ እና አርቆ በማሰብ ዛሬ መሰረት መጣል፣ እንዲሁም ነገሮችን ፈር በማስያዝ ህዝባችን ሃይማኖቱን ጠብቆ እና ተከባብሮ ስልጣኔን እውን የሚያደርግባቸውን ሁኔታዎች ማመቻቸች እንደሚያስፈልግ የኢትዮጵያ የወደፊት እጣ ፈንታ ለሚያሳስበው ቅን ዜጋ ሁሉ ለመጠቆም እንወዳለን።

ማንኛውንም መብት ለማስከበር ጥያቄውን የሚመጥን መስዋእትነት መክፈል የግድ ነው። በመሆኑም መብቱ እንዲከበርለት የሚፈልግ ሁሉ መክፈል ያለበትን ለመክፈል ዝግጁ መሆን ይጠበቅበታል። በተለይ ሙስሊሙ ይዟቸው የተነሳቸው ዓይነት ሀይማኖታዊ ጥያቄዎች ሲሆኑና ጉዳዩ የሃይማኖት ሲሆን ደግሞ የእምነቱ ተከታዮች ሌላ የመብት ጥያቄ ይዘው ከተነሱ ፍትህ ናፋቂዎች በላይ መስዋዕትነት ለመክፈል መዘጋጀትና መክፈልም ይጠበቅባቸዋል።

አሳሳቢው ጥያቄ ‹‹ዛሬ እኛ ለሃይማኖታችን እና ለህዝባችን ፍትህ እና ነፃነት ስንል እና በታሪክም በፈጣሪም ፊት የተጣለብንን ኃላፊነት ለመወጣት መክፈል ያለብንን እንከፍላለን? ወይስ መጪው ትውልድ ሊሸከመው የማይችለውን መከራ እና ስቃይ እናሳድርለታለን?›› የሚለው ነው። አሁን ሙስሊሙ ማህበረሰብ እየከፈለ ያለው መስዋእትነት ለተተኪው ትውልድ የከፋ መከራና ስቃይን ላለማስረከብና በምትኩ ፍትህ እና ነፃነትን እውን በማድረግ መጪው ትውልድ ሀይማኖቱን በነፃነትና እና በእኩልነት እያራመደ ለሀገራችን እድገትና ስልጣኔ የበኩሉን አስተዋፅኦ ማበርከት የሚችልበትን ምቹ አየር ለመፍጠር ነው።ለዚህም ነው ህዝባችን ከጥቁር መጋረጃ ጀርባ በመንግስት አካላት የሚፈጸሙ ጥቁር ሽብሮችን ሁሉ በፅናት ተቋቁሞ የመብት ጥያቄውን መቀጠል የቻለው!

መንግስት በየትኛውም ዘመን ከነበሩ አምባገነን መሪዎች እና የሃይማኖት ጠላቶች በላይ የሁለቱን ታሪካዊ ሀይማኖቶች አከርካሪ ለመስበር በመወሰን የሙስሊሙን ደም ማፍሰስ ጀምሯል። ሁሉንም ሰማያዊም ምድራዊ ህግጋት በመፃረር የሃይማኖታችን ምልክት የሆኑትን ሂጃብ፣ ኒቃብ፣ መስጂድና መድረሳዎችን አዋርዷል። የሃይማኖት መመሪያችን የሆነውን ቁርአን አቃጥሏል። ሊከበሩ የሚገባቸውን የሃይማኖት አባቶች እና ሰባኪያን እርቃናቸውን በመግረፍ፣ ፂማቸውን በመንጨት፣ አካላቸውን በማጉደል እና ፀያፍ ስድብ በመስደብ አዋርዷል። የተከበረውን የእህቶቻችንን ገላ አራቁቷል፤ ደፍሯል። እንክብካቤ የሚፈልገውን ስስ ገላቸውን ለጠላት በፈረጠሙ ጡንቻዎች እና ለጠላት በተዘጋጁ መሳሪያዎች አድምቷል፤ ደብድቧል። ነጭ መሃረም እያውለበለቡ ሃይማኖታዊ መብታቸውን በጠየቁ ሰዎች ላይ ጥይት በማርከፍከፍ የንፁሀን ሙስሊም ወገኖችችንን ደም አፍስሷል። እጁን በደም አጨማልቋል። መስጂዶቻችንን አርክሷል። ሂጃብ፣ ቁርዓን እና ኒቃብ በማቃጠል ለሃይማኖታችን ያለውን ስር የሰደደ ጥላቻና ንቀት አሳይቷል። ‹‹አላህ የለም! እስቲ መጥቶ ያድናቸው!›› በማለት ሃገር ከሚመራ አካል የማይጠበቅ ወራዳ ንግግር በመናገር የፈጣሪያችንን ክብር ነክቷል።

ይህ በድቅድቅ ጨለማ ህዝባችንን በአወልያ በመደብደብ ተጀምሮ በድቅድቅ ጨለማ ሴት እህቶቻችንን በማራቆት እና በማዋረድ ከሀምሌ እስከ ሀምሌ የዘለቀውን ‹‹ጥቁር ሽብር›› የመሩና የተባበሩ በመጅሊስ መዋቅር ውስጥ የሚገኙ አካላት ሁሉ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ የሚፋረዳቸው መሆኑን እና በደረሰው ግፍና በፈሰሰው ደምም ተጠያቂዎች መሆናቸውን ደጋግመን ልናሳውቃቸው እንወዳለን። የፈፀማችሁትን ዘግናኝ እና አሰቃቂ ወንጀል እኛም ሆንን ታሪክ ፈፅሞ የማይረሳው፣ ሀያልና ሁሉንም ቻይ የሆነው ፈጣሪም የማይዘነጋው መሆኑን ልናረጋግጥላችሁ እንወዳለን – ‹‹ኣላህንም በዳዮች ከሚሰሩት ዝንጉ አድርገህ አታስብ›› ይላልና ቅዱስ ቁርአናችን! ጥቁሩን ሽብር የጠነሰሱ፣ የተባበሩና የፈጸሙ ሁሉ ማንነታቸው ተጣርቶ በህዝብና በፍርድ ፊት መቅረብ እንዳለባቸው ጽኑ እምነት ያለን በመሆኑ ከአገር ውስጥ እስከ ዓለም አቀፍ ፍርድቤቶች ድረስ ጉዳዩን ለማስኬድ ወስነናል። በመሆኑም መላው ኢትዮጵያዊና ለሃይማኖት መብት ተቆርቋሪ የሆነው መላው ዓለምአቀፍ ማህበረሰብ ከጎናችን እንዲሰለፍ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

በእርግጥ በጥቁር ሽብር ዘመቻው የተፈጸመው ኢ-ህገመንግስታዊ እና ኢሰብዓዊ ድርጊት ዘግናኝ እና አሳዛኝ ቢሆንም ውርደቱ ግፉን ለፈጸመው መንግስት እንጂ መስዋዕትነቱን ለከፈለው ኢትዮጵያዊ ሙስሊም ክብር እና ድልም ነው። እስከዛሬ በከፈልነው መስዋዕትነት ከፍተኛ ውጤት አግኝተናል። በመክፈላችንም ደስተኞች ነን። ምናልባትም ወደ ስኬት በቀረብን ቁጥር የምንከፍለውም እየጨመረ እንደሚመጣ እናውቃለን፤ ለዚህም ዝግጁ ነን! የሰው ልጅ ህይወቱ ጣዕም የሚኖረው ያለውን ሁሉ ሊሰዋለት የተዘጋጀ ዓላማ ሲኖረው ብቻ መሆኑን ህዝባችን የተገነዘበና ይህንኑ ህይወትም ማጣጣም የጀመረ በመሆኑ ፈጽሞ ከዚያ በታች ወደሆነ የውርደት ህይወት አይመለስም።

ህዝባችን በፊርማው ከጣለብን ከባድ ሃላፊነት በላይ ስሜታችንን የነካው እና ይህ ህዝብ ምንም ዓይነት መስዋዕትነት ሊከፈልለት የሚገባው መሆኑን እንዲሰማን ያደረገን ለሶስት ዓመታት ያለምንም ክፍተት እና ጉድለት የዘለቀው ስሜቱ፣ ፅናቱ እና ፍቅሩ፣ እንዲሁም ቃልኪዳኑን ማክበሩ ነው። ይህ የመብት እንቅስቃሴ የህዝባችን ፍቅር በደማችን ውስጥ እንዲሰርጽ፣ መላውን የኢትዮጵያን ህዝብ እንድናከብርና ከባድ ሃላፊነት እንዲሰማን አድርጎናል። በዚሁ አጋጣሚ ያጎደልነውን አስተካክለንና ሞልተን ለውዱ ህዝባችን ማድረግ ያለብንን ለማድረግና መክፈል ያለብንን ለመክፈል ያለንን ጠንካራ ስሜት ልንገልጽም እንወዳለን። ብቸኛ፣ ሃያልና ታላቅ የሆነው ፈጣሪ ጽናት፣ ኢኽላስና ቃልኪዳን የማክበርና የመፈጸም ዕድልን እንዲያጎናጽፈን ትማጸኑልን ዘንድ እንጠይቃለን።

በመጨረሻም የመብት ጥያቄያችንም ሆነ የኢትዮጵያ ህዝብ አጠቃላይ የፍትህና የነጻነት ጥያቄ የስኬት ዙፋን ላይ ማረፍ የሚችለው በጥቂት ጀግኖች ወይም ሰዎች ከፍተኛ ጥረት እና መስዋዕትነት ሳይሆን በመላው የማህበረሰቡ አባላት ጥቂት አስተዋጽኦ መሆኑን ተረድተን ጥቂት ነው ብለን የምንንቀው ሳይኖር ሁላችንም የበኩላችንን አስተዋጽኦ እንድናበረክት አጽንኦት ሰጥተን እንጠይቃለን።

ድልም ከአላህ እንጂ ከሌላ አይደለም!

ልባቸው ላይ ፕላስቲክ ትቦ የተገጠመላቸው አቶ በረከት ስምኦን በጂዳ ሕክምና ላይ ናቸው።

$
0
0

Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)

 

አቶ በረከት

አቶ በረከት

አቶ በረከት ስምኦን በሳኡዲ አረቢያ ጅዳ ከተማ እሁድ ሌሊት ጀምሮ ከቤተሰቡ ጋር ቡግሻን ሆስፒታል 4 ፎቅ ሲዊት ሩም 501 ክፍል የልቡ ህክምና በአላሙዲን አማካይነት ከአ/ አ የመጣው ከዶክተሩ ጋር ሚስቱና 1 ሴት ልጅ ጭምር በህከምና ላይ ይገኛል። አቶ በረከት አርቴፊሻል የፕላስቲክ ቧንቧ ከልባቸው ጋር በድጋፍ ተገጥሞ እንደሚኖሩ ይታወቃል። አላሙዲ ይህ ምስጢር እንዳይወታ ሆስፒታል ውስጥ ለሚሰሩ ሃበሾች 1000 ሪያል በነብስ ወከፍ ሰቷቸዋል። የአቶ በረከት የልባቸው ምት የሚልካ ጊስትር ተገጥሞላቸዋ…ል።

ክዚህ ቀደም ደቡብ አፍሪካ ለህክምና ሄደው የነበሩት አቶ በረከት መቸም ሰው ይሙት አይባልም ባህላችንም አይደለም ። እግዜር ይማርህ ነው ; ከፖለቲካ ወጣ ስንል ለክፉ መልካም አይመለስም ..እኒ ግን እንደ ፖለቲከኛ ሆኜ ነው የማስበው ግን ቀኝህን ሲመታህ ግራህን አታስደግመው በተቻለህ መጠን በፍጥነት መልሰህ አጩኸው ነው። በወያኔ ወገኖቻችን የሚሰቃዩትን ስቃይ አሰቃዮች በተፈጥሮ ሕመም ሲያገኙት የወገንን ስቃይ ምን ያህል እንደሆነ ማወቅ እና መረዳት አለባቸው፡፤
ተጨማሪ መረጃዎች እንደደረሱን እናቀርባለን ይጠብቁን።

ሕወሓት አቶ አንዳርጋቸውን በቲቪ ስታቀርብ ራሷን በራሷ ያጋለጠችባቸው 4 ቅጥፈቶች

$
0
0

ስንታየሁ ከሚኒሶታ

እንደተጠበቀው በሕወሓት መንግስት በሚመራው የኢትዮጵያ ፖሊስ ፕሮግራም ላይ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ እንዲቀርቡ ተደርጓል። የአቶ አንዳርጋቸው በቲቪ መቅረብ ከዚህ ቀደም በአንዷለም አራጌ፣ በብርቱካን ሚደቅሳ፣ በደበበ እሸቱ፣ በአቡበከር አህመድ ላይ የተለመደ በመሆኑ ብዙም አስገራሚ አልሆነም። ሆኖም ግን ቪድዮውን ልብ ብሎ ለተመለከተው ወያኔ እንዳሰበው ትርፍ ሳይሆን የበለጠ ኪሳራ እንዳገኘበት ለመረዳት ችያለሁ። ለዚህም ነው ወያኔ አቶ አንዳርጋቸውን በቲቪ ስታቀርብ የረሳቻቸው 4 ቅጥፈቶች ስል ለዚህ አስተያየቴ ር ዕስ የሰጠሁት።

ወያኔ አቶ አንዳርጋቸውን በቲቪ ስታቀርብ ራሷን በራሷ ያጋለጠችባቸው 4 ቅጥፈቶች1ኛ. ቪድዮው በጣም ኤዲት እንደተደረገ ያስታውቃል

ሕወሓት ያዘጋጀው የቪድዮ ካሜራ ማንና አቀናባሪው ደንጋጣ እንደሆነ ቪድዮው ያስታውቅበታል። በጣም ተቆራርጦ መቀጣጠሉ ከማስታወቁም በላይ ቢያንስ ከዚህ የተሻለ ኤዲቲንግ ሥራ መሥራት ይችል የነበረ ቢሆንም ይህን ባለማድረጉ ለፕሮፓጋንዳ ሥራ የተዘጋጀውን ቪድዮ ኪሳራ ላይ ጥሎታል። ቪድዮ አቀናባሪው ሆን ብሎ ሕዝብ መቆራረጡን እንዲያውቅ ያደረገ ከሆነ ልናደንቀው የሚገባ ሲሆን፤ ሆኖም ግን ለፕሮፓጋንዳ ፍጆታ ከሆነ ይህ ቪድዮ ቅንብሩ አይመጥንም።

2ኛ. ቪድዮው በተደጋጋሚ የተቀረጸ መሆኑ ያስታውቃል።

ቪድዮውን ልብ ብላችሁ ከተመለከታችሁት በተለያየ ጊዜ የተቀረጸ መሆኑ ያስታውቃል። ይህም የሚፈልጉትን ለማግኘት ብዙ ማይል እንደተጓዙ ያሳያል። ምንም እንኳ ተመሳሳይ ቀን የተቀረጸ ለማስመሰል አንድ ዓይነት ቱታ ቢያስለብሱትም 3 የተለያዩ የውስጥ ቲሸርቶች ይታያሉ። አንዱ ነጭ፣ ሌላኛው ሰማያዊና 3ኛው ቀይ ቲሸርቶች። በሌላ በኩል ቪድዮው ሊያልቅ ሲል የምታዩት ቱታ ደግሞ የተለየ ነው።

3ኛ. ውሃዋ የለችም።

እንግዲህ ወያኔ ሌላው የረሳችው አቶ አንዳርጋቸውን በጥሩ ሁኔታ እንዳሉ ለስመሰልና ንጹህና የተገዛ ውሃ አጠገባቸው አስቀምጣ ነበር። ቪድዮው ግን በተለያየ ጊዜ የተቀረጸ ለመሆኑ የሚያስታውቀው በሌላኛው የቪድዮ ክፍል ውስጥ ውሃዋ የለችም።

4ኛ. ቶርች የሚደረግ ሰው እንዳለ ይሰማል

ይሄ ትልቁ ወያኔን ራሱን በራሱ ያጋለጠበት ክፍል ነው። ቪድዮው ተጀምሮ ከ1 ደቂቃ በኋላ ያለውን ስትመለከቱት አንዳርጋቸው በሚናገርበት ወቅት ከጀርባው የድብደባና የሲቃ ድምጽ ይሰማል። ይህም ምን ያህን በወያኔ እስር ቤቶች የሚደረጉትን ቶርቸሮች የሚያሳይ ነው። ይህ ለወያኔ ትልቁ ኪሳራ ሊባል የሚችል ደካማው የፕሮፓጋንዳ ቪድዮው ሊባል ይችላል። ራሱን በራሱ ቶርቸር አድራጊ መሆኑን መስክሯልና ይህንን የሚመለከታቸው አካላት ለዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተከራካሪ ድርጅቶች ማሳየት ይኖርባቸዋል፤ አንዳርጋቸውም እንዲህ ያለው ቶርቸር እንደደረሰበት ማሳያ ሊሆነን ይችላል እላለሁ።

ቪድዮውን ተመልከቱትና ፍረዱ። በመጨረሻም ለወያኔ የማስተላልፈው መል ዕክት አለኝ – እንደሁልጊዜው ለዛሬውም አልተሳካም!

አንዳርጋቸው ምን አዲስ ነገር ተናገረ ( ሄኖክ የሺጥላ)

$
0
0

ሄኖክ የሺጥላ

andargachew-tsige-on-p (1)ሰሞኑን ወያኔ እንደ አናጤ ሱሪ አስር ቦታ ለጣጥፎ (በእንግሊዘኛው edit and copy paste ) አድርጎ ያቀረበልንን እና በፖሊስ ፕሮግራም ያስተላለፈልንን ቪዲዮ ተመለከትኩ። በጣም የገረመኝ ነገር ግን እኔ የማላውቀውን ፣ ወያኔ የሆነና አማሪካ ወይም አውሮፓ ሀገር የሚኖር ( እሱም ቢሆን ላያውቀው ይችላል ብዬ የማልገምተውን ነገር እንዳልተናግውሩ እሙን ነው )። 
እጅግ የገረመኝ ግን ይሄን ሁሉ ቀን (ጊዜም አጥፍተው ) ከ ፍላሹ ላይና ሃርድ ድራይቭ ላይ ያገኙትን ነገር ሊያሳዩን አልፈቀዱም ? ለምን ? አንዳንድ አዳዲስ መረጃዎችን ጨመርመር አድርጎ ግንቦት ሰባትን ለመውቀስ ይሆን ? ( ምናልባት ግንቦት 7 ኢትዮጵያ ያለውን የአማሪካን እምባሲ ለማፈንዳት እንዳሰበ በማሳየት ፣ ደሞ እነ ዶክተር ብርሃኑ ነጋ ተላልፈው የሚሰጡብትን ነገር እየቆፈሩ እንደሆነም ሹክ ተብየአለሁ )። አውሮፓ ያሉትንም እንዲሁ ! ግን ትንሽ ስለ ፎረንሲክ ሳይንስ እውቀት ያለው ታጋዳላይ ካለ ምክር ቢሰጣችሁ ከጉድ ትድናላችሁ !

የአቶ አንዳርጋቸው ቃለ መጠይቅ ግን ለኔ ምንም አዲስ ነገር አላየሁበትም ። ከዚያ ባለፈ ምንም ማለት አልፈልግም ። እንደሚሉን ግንቦት ሰባት አቅመ ቢስ ድርጅት ነው ወይ ? መልሱን ራሱ ወያኔው ይመልስ !

Viewing all 8745 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>