Quantcast
Channel: ዘ-ሐበሻ – Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 8745 articles
Browse latest View live

በእነ ሀብታሙ አያሌው የክስ መዝገብ አንድነት ፓርቲ ያቀረበው ክስ ውድቅ ተደረገ

$
0
0

Habtamu abrhayeshiwas daniel

በዛሬው ዕለት በአራዳ ምድብ ፍታብሔር ችሎት ሀምሌ 8 ቀን 2006 ዓ.ም በሰጠው ትዕዛዝ መሰረት የማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ የፀረ ሽብር ዲቪዚዮን ኃላፊ ኮማንደር ተክላይ መብራህቱ የእስር ትዕዛዙንና የጊዜ ቀጠሮ የተጠየቀበትን ሰነድና ታሳሪዎቹን ይዘው እንዲቀርቡ ቢያዝም ኃላፊው ታሳሪዎቹን ሳይዙ ቀረቡ፡፡
ችሎቱ በ4፡30 ተሰይሞ ዳኛው ከሳሽና ተከሳሽ መቅረባቸውን ካረጋገጡ በኋላ እስረኞቹ መቅረባቸውን ዳኛው ጠየቁ፤ ተከሳሽ እስረኞቹን አለማቅረባቸውንና የሰነድ ማስረጃዎቹን ስላቀረብኩ እስረኞቹን እንዳቀርብ አይጠበቅብኝም በማለት ለፍ/ቤቱ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ ዳኛው የእስር ማዘዣና የፍርድ ቤት የጊዜ ቀጠሮ ሰነዶች ተከሳሽ ማቅረባቸውን ከገለጹ በኋላ ከሳሾች ያቀረቡት ክስ ውድቅ ሆኗል በማለትይህንን አቤቱታ ለማየት ስልጣን እንደሌለውና ለተከሰሱበት ችሎት አቤቱታችሁን ማቅረብ ነው ያለባችሁ በማለት ክሱ መዘጋቱን ገልጸዋል፡፡
ከአራዳ ፍረድ ቤት 6 የአንድነት አባላት ታፍነው ተወሰዱ
በዛሬው እለት በነሀብታሙ አያሌው የክስ መዝገብ አንድነት ፓርቲ ላቀረበው አቤቱታ የፍርድ ቤቱን ውሳኔ ለማድመጥ በችሎት ተገኝተው የነበሩ 6 የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ አባላት
1ኛ.ደንኤል ፈይሳ
2ኛ.አብነት ረጋሳ
3ኛ.ጥላዬ ታረቀኝ
4ኛ.ፋሲካ አዱኛ
5ኛ.ብርሀኑ ይግለጡ እና
6ኛ.መሰለ አድማሴ በደህነቶች ታፍነው በቶዮታ ደብል ጋቢና ኮድ 3-50559 መኪና ወደ ማዕከላዊ መወሰዳቸውን የፍኖተ ነፃነት የማዕከላዊ ምንጮች ገልጸዋል።

Source- Finote nestanet


በአውሮፓ በድምጻዊ ማዲንጎ አፈወርቅ ላይ ቦይኮት ተጠራ

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) በሕወሓት አስተዳደር ስር የሚመራው ሜጋ አምፊ ትያትር ስር በአባልነት ሲያገለግል የቆየውና በጀርመን ሃገር ለ12ኛ ጊዜ በሚደረገው የስፖርት ዝግጅት ላይ የሙዚቃ ሥራዎቹን ለማቀረብ የሚያቀናው ማዲንጎ አፈወርቅ ከፍተኛ የሕዝብ ተቃውሞ ገጠመው፤ የሙዚቃ ኮንሰርቱ እንዳይደረግ ከፍተኛ ጥረት እናደርገጋለን ብለዋል።
madingo
በተለይ ከገዢው ፓርቲ ጋር ለመስራት ፍላጎት የሌላቸውን አርቲስቶች ለመንግስት ሃይሎች በመሰለል ይታወቃል የተባለው ማዲንጎ በተለይ በቅርቡ አማሮች ከደቡብ ክልል ሲባረሩ የመንግስት እርምጃ ትክክል ነው በሚል በግልጽ ተናግሯል በሚል ማህበራዊ ድረገጾች ወቀሳ ሲሰነዘርበት እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነው።

በአላሙዲ/ወያኔ ኮንሰርቶች ጋር በመሳተፍ ብዙሃኑን የኢትዮጵያ ሕዝብ አስቀይሟል፤ የወያኔ ሰላይ ነው፤ በሚል ተቃውሞ የገጠመው ማዲንጎ የፊታችን ኦገስት መጀመሪያ በጀርመን የሙዚቃ ኮንሰርት እንደሚያቀርብ ከተሰማ ወዲህ በዛው አካባቢ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በአርቲስቱ ስም ላይ ቀይ መስመር በማስመርና የወያኔን ባንዲራ በማልበስ ሕዝብ እርሱ በሚገኝባቸው ኮንሰርቶች ላይ እንዳይታደም ጥሪ ተደርጓል።

በዚህ ዙሪያ ዘ-ሐበሻ ድምጻዊ ማዲንጎ አፈወርቅን ለማነጋገር ያደረገችው ጥረት አልተሳካም።
boycott madingo

የጁሙዓ መርሃ ግብር! –ከድምፃችን ይሰማ የተላለፈ ጥሪ

$
0
0

muslim1
ረቡእ ሐምሌ 9/2006

የፊታችን ጁሙዓ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከባድ ተቃውሞ ይደረጋል፡፡ ይህ ደግሞ ተምሳሌታዊ አብሮነታችንን በሃገራችን በሁሉም አቅጣጫ ከወትሮው በተለየ መልኩ የምናሳይበት ወሳኝ አጋጣሚ ነው፡፡ የፊታችን ጁሙዓ ህዝባዊነታችን ጎልቶ የሚታይበት፣ ለፍትህ፣ ለሰላም እና ለእምነት ነፃነታችን መከበር ያለንን ቁርጠኝነት እና ፅናት ደግመን ደጋግመን ለዓለም የምናሳይበት ታላቅ ተቃውሞ ነው፡፡ ተምሳሌታዊ አብሮነታችን በአገር ደረጃ ብቻ ሳይሆን በዓለም አቀፍ ደረጃም የሚገለጽ ነው፡፡ በተለያዩ አገራት የሚገኙ ኢትዮጵያውያንም ከፍተኛ ዝግጅት እያደረጉ ሲሆን በሳምንቱ ውስጥም የሚፈጸሙ እንቅስቃሴዎችን አዘጋጅተዋል፡፡

በሃገር ቤት የሚኖረን በሰላማዊ ትግላችን ውስጥ ዋና የሚባሉ አጀንዳዎቻችንን በሙሉ ያካተተ ብርቱና የተቀናጀ ሃገር አቀፍ ተቃውሞ ነው፡፡ ከሃገር ውጭ ደግሞ ጁሙዓን ጨምሮ በቀሪዎቹ ቀናት የተለያዩ መርሃ ግብሮች ለማካሄድ ዝግጅቶች እየተደረጉ እንደሆነ መረጃዎች ደርሰውናል፡፡
ይህ አገር አቀፍ ተቃውሞ በአዲስ አበባ በታላቁ አንዋር መስጂድ ይካሄዳል፡፡ (የሚከተለው መርሃ ግብር የአዲስ አበባ ሲሆን ክልሎችም ካሉበት ሁኔታ ጋር አዛምደው ከወትሮው የተለየ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ዝግጅቶች እየተካሄዱ ነው፡፡)
በነገው ጁመዓ ከሚከተሉት 5 መፈክሮች መካከል የገራልንን መፈክር በወረቀት ላይ አስፍረን ይዘን በመምጣት በተቃውሞው ላይ ከፍ አድርገን እናሳያለን፡-
‹‹የአገር መሰረት የሆነውን ህዝብ መናቅ ይቁም!!››
‹‹የህዝብ ድምፅ ይደመጥ!!››
‹‹የሙስሊም ተማሪዎች በነፃነት የመማር መብት ይከበር!!››
‹‹ከትምህርታችን ወይ ከሃይማኖታችን አታስመርጡን!!››
‹‹የሃይማኖት ነፃነትን ማክበር ግዴታ እንጂ ምርጫ አይደለም!!››
> የጁሙዓ ሰላት እንደተጠናቀቀ እጅ ለእጅ ተያይዘን ባለንበት ቦታ በመቆምና በፅሁፍ ይዘን የምንመጣቸውን መፈክሮች ከፍ አድርገን በማሳየት የሚከተሉትን መፈክሮች በድምጽ እናሰማለን፡፡
1. ‹‹አላሁ አክበር!›› ለ 2 ደቂቃ
2. ‹‹ድምፃችን ይሰማ!›› ለ 2 ደቂቃ
3. ‹‹ሕገ መንግስቱ ይከበር!›› ለ 2 ደቂቃ
4. ‹‹ኮሚቴው ይፈታ!›› ለ 2 ደቂቃ
5. ‹‹የታሰሩት ይፈቱ!›› ለ 2 ደቂቃ፤ በየክልልሉና በየማረሚያ ቤቱ ታጉረው የሚገኙ በሺዎች የሚቆጠሩ ሙስሊሞች ፍትህ ብትረሳቸውም ህዝበ ሙስሊሙ እንዳልረሳቸው ለማሳየት፡፡
6. ‹‹ጣልቃ ገብነት ይቁም!›› ለ 2 ደቂቃ
7. ‹‹ኢማሞቻችን ይመለሱ!›› ለ 2 ደቂቃ
8. ‹‹የመንግስት ገዳዮች ለፍርድ ይቅረቡ!›› ለ 2 ደቂቃ
9. ‹‹መማር መብታችን ነው!›› ለ 2 ደቂቃ፤ ህዝበ ሙስሊሙ የመማር መብቱ ህገ መንግስታዊ እና ዓለማቀፍ የሰብዓዊ መብት ድንጋጌዎች ያፀደቁት ሰብዓዊ መብታችን መሆኑን ለማሳየት፡፡
በመጨረሻም ካለንበት ቦታ ሳንንቀሳቀስ እጆቻችንን ወደ አላህ በመዘርጋት ዱዓ በማድረግ ወደየመጣንበት እንመለሳለን – ኢንሻ አላህ!
ትግላችን እስከ ድል ደጃፎች ድረስ ይቀጥላል!
ድምፃችን ይሰማ!
አላሁ አክበር!

የ‹‹ተምሳሌታዊ አብሮነት›› ሳምንትን ስኬታማ ለማድረግ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚደረጉ ዝግጅቶች ተሟሙቀው ቀጥለዋል፡፡ በየትኛውም የዓለም ክፍል ሆነው ከስራ እና ከሰዓት እጥረት ጋር እየታገሉ በአገር ቤት ወንድሞቻቸውን ለማገዝ ሰንፈው የማያውቁት የዳያስፖራው ማህበረሰብ እህትና ወንድሞቻችን ዛሬም እንደተለመደው ከፍተኛ ዝግጅት እያደረጉ ነው፡፡ እስካሁን ድረስ በዋሽንግተን ዲሲ፣ በዳላስ፣ በሲያትልና በቺካጎ ለፊታችን ቅዳሜ ዝግጅት እያደረጉ መሆናቸውን ማወቅ የተቻለ ሲሆን በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን በሚኖሩባት ሳዑዲ ዓረቢያም እንዳለፉት ሁለት ሳምንታት ሁሉ በሶስተኛው ሳምንትም የተለያዩ ዝግጅቶች እየተደረጉ መሆኑ ታውቋል፡፡

በሌሎች ሃገራት የሚገኙ የዳያስፖራ ማህበረሰቦችም በቀሪዎቹ ጊዜያት የጁሙዓውን ዓለም አቀፍ መርሃ ግብር እና ካሉበት ሁኔታ ጋር የሚጣጣሙ ሌሎች ፕሮግራሞችን ለመተግበር አስፈላጊውን ዝግጅት እንዳገባደዱ ተስፋ እያደረግን በዓለም አቀፍ ደረጃ ድምጻችን ጎልቶ እንዲሰማ ለማድረግ ሲያደርጉት የቆዩትን፣ አሁንም እያደረጉ ያሉትን ጥረት አላህ ይቀበላቸው ዘንድ ምኞታችን ነው! እኒህን መሰል ዓለም አቀፍ መርሃ ግብሮችና ዝግጅቶች ሰላማዊ ትግላችንን የበለጠ ዓለምአቀፋዊነት በማላበስ ድምጻችን የበለጠ ጎልቶ እንዲሰማ ያደርጋሉ፡፡ ‹‹ተምሳሌታዊ አብሮነት›› ሊገለጽበት የሚችልበት ሌላ የተሻለ መንገድ ከቶስ ይኖር ይሆን?
ጥቆማዎች

በውጭ ለምትኖሩ ሙስሊሞች ተግባራቱን ማዕከላዊ በሆነ መልኩ ማቀድ ካላችሁበት ሁኔታ ጋር ላይዛመድ ስለሚችል ዋና ዋና ዓላማዎችን እና በሃገር ቤት ያለን ሙስሊሞች በይበልጥ እናንተ ብትሳተፉበት ብለን የምንመኛቸውን አንኳር ተግባራትን ለመጠቆም እንሞክር፡-
1. አለምዐቀፍ መርሃ ግብሮች ሰላማዊ ትግላችን አሁንም በጥንካሬ የመቀጠሉና የሁሉም የህብረተሰብ አንገብጋቢ ጉዳይ የመሆኑ ትልቅ ማሳያዎች ናቸው፡፡ እንቅስቃሴውም የሚፈጥረው ጫና እና የሚያስተላልፈው መልእክት በራሱ በትልቅ ዓላማነት የሚያዝ ነው፡፡ በመሆኑም በሰፊም ሆነ በአነስተኛ መርሃ ግብር በዚህ ሳምንት ቢያንስ አንድ ተግባር አቅዳችሁ ትተገብራላችሁ ብለን እንጠብቃለን፡፡
2. የዲያስፖራው ማህበረሰብ ዋና ትኩረት እንዲሆን የምንሻው የዓለም አቀፉን ማህበረሰብ ትኩረት የሚስቡ እና የሚዲያ አጀንዳ የሚፈጥሩ ለየት ያሉ ተግባራት ላይ ትኩረት እንድታደርጉ ነው፡፡

3. ባላችሁበት አካባቢ ለሚኖሩ ማህበረሰቦች እና ተቋማት ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ላይ የሚደርሱ ኢፍትሃዊ ተግባራትን እንድታጋልጡ እና የተቻለውን ያክል ለማስቆም ጫና የሚያሳድሩ እና ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶች ከእናንተ በዋናነት ይጠበቃሉ፡፡ በዚህ አጋጣሚ ኡስታዝ በድሩ ሁሴን ከመታሰሩ ጥቂት ደቂቃዎች አስቀድሞ ከቢቢኤን ሬዲዮ ጋር ባደረገው ቃለ መጠይቅ የዲያስፖራው ማህበረሰብ ዋነኛ ሚና ምን ሊሆን እንደሚገባ የጠቆመውን በማስታወስ የበኩላችሁን እንድትወጡ ይጠበቃል፡፡
4. ከሌሎች እምነት ተከታዮች ጋር መልካም ግንኙነት እና በቀጣይ ሃገራዊ ጉዳዮች ላይ እጅ ለእጅ ተያይዞ መስራት የሚያስችሉ ጤናማ ግንኙነቶችን መፍጠር ይጠበቅባችኋል፡፡

በመሆኑም ከላይ የተቀመጡትን አራት ዋና ዋና ከእናንተ የምንጠብቃቸውን ዓላማዎች ታሳቢ በማድረግ በረመዳን ሶስተኛ ሳምንት ውስጥ በንቃት እና በጠንካራ የአጋርነት ወኔ ወደተግባር የሚያስገባ እቅድ እንድታዘጋጁ እና ወደተግባር እድትገቡ እንጠቁማለን፡፡ እንደመነሻ መሆን የሚችሉ ተግባራት እንደሚከተለው ተዘርዝረዋል፡-
• ኮንፈረንስ ብታዘጋጁ እና የተለያዩ ተቋማትን፣ በተለይም የሚዲያ ባለሙያዎችን በመጋበዝ ስለትግሉ፣ በይበልጥም ስለቀጣዩ የትግል አቅጣጫ ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራ ብትሰሩ፤
• በመካከላችሁ አንድነትን የሚያጠናክሩ እና ተባብሮ ቁም ነገር ያለው የሚታይ ስራ ለመስራት የሚያስችሉ የአንድነት የኢፍጣር ፕሮግራሞች ብታዘጋጁ፤
• የጎዳና ላይ ሰልፍ (አመቺ ከሆነ) እና ለየት ያሉ በግል እና በቡድን ሊሰሩ የሚችሉ ትኩረት ሳቢ የጎዳና ላይ ትዕይንቶች እና በእናንተ ተጨባጭ አመቺ የሆኑ መርሃ ግብሮችን በመቅረፅ የታሰበው እንዲሳካ ሰፊ ርብርብ እንድታደርጉ እንጠይቃለን፤
ለምታደርጓቸው እቅስቃሴዎች ስኬት በቂ የሚዲያ ሽፋን እንዲያገኙ በልዩ ትኩረት እንድትሰሩ እየጠቆምን ወደእኛ የምትልኳቸውን ዜናዎች በተሻለ መጠን ሽፋን እንዲያገኙ ለማድረግ የምንጥር መሆኑን እንገልጻለን፡፡
በደማቅ ተምሳሌታዊ አብሮነት ድምጻችንን በዓለምአቀፍ ደረጃ ለማጉላት እንረባረብ!
ትግላችን እስከድል ደጃፎች ድረስ ይቀጥላል!
ድምጻችን ይሰማ!
አላሁ አክበር!

አገራዊ ጥሪ ለመከላከያና የፓሊስ ሠራዊት አባላት

$
0
0

ግንቦት 7፡ የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ የኢትዮጵያ የመከላከያና የፓሊስ ሠራዊት አባላትን ከአለቆቻቸው ለይቶ ይመለከታል።

G7የመከላከያና የፓሊስ ሠራዊት ከፍተኛ ሹማምንት ከህወሓት የተቀዱ፣ ለህወሓት ሥልጣን የቆሙ፣ ዘረኞች፣ ፋሽስቶችና ሙሰኖች መሆናቸው በገሃድ የሚታወቅና በተደጋጋሚ ጥናቶችም የተረጋገጠ ጉዳይ ነው። በዘመነ ወያኔ የሠራዊት አዛዥነት ሹመት መሥፈርቶች ዘር፣ የፓለቲካ አመለካከትና ለህወሓት ያላቸው ታማኝነት ነው። በዚህም ምክንያት ሁሉም ቁልፍ የአዛዥነት ቦታዎች የተያዙት ሙሉ በሙሉ የህወሓት አባላት በሆኑ የትግራይ ተወላጆች ነው። እነዚህ የጦርና የፓሊስ ሹማምንት ኢትዮጵያን ወረው እንደያዙት አገር ሲዘርፉ፣ ሕዝቧንም ሲገሉና ሲገርፉ እንሆ 23 ዓመታት አልፈዋል።

በእነዚህ 23 ዓመታት ትግራይን ጨምሮ በደል ያልደረሰበት የኢትዮጵያ ግዛት እና የኅብረተሰብ ክፍል የለም። ሁሉም ኢትዮጵያዊ በእነዚህ ፋሽስቶች ተረግጧል፣ ተዋርዷል፣ ተግዟል። የንቅናቄዓችን ዋና ፀሐፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ጨምሮ በርካታ ኢትዮጵያዊያን የነፃነት አርበኞች በእነዚህ እኩይ የሠራዊቱና የፓሊስ አዛዦች ሰቆቃ እየተፈፀመባቸው ነው። የወያኔ የጦርና የፓሊስ አዛዦች እና ሰላዮች አገራችን እያደሙ፤ ሕዝባችንን እያስለቀሱ ነው። በወያኔ ፋሽስት የጦርና የፓሊስ አዛዦች እና ሰላዮች ጥምረት ሰቆቃ የሚፈፀምበት የኅብረተሰብ ክፍል በየጊዜው እየጨመረ ይገኛል። የወያኔ ማሰቃያዎችን የሞሉት የፓለቲካና የሀይማኖት መሪዎች፣ ጋዜጠኞችና ብሎገሮች መሆናቸው ለዚህ አንድ ማሳያ ነው።

የሠራዊቱ የበታች ሹማምንትና ተራ አባላት ጥንቅር ግን ከአዛዦቹ ፈጽም የተለየ ነው። የመከላከያና የፓሊስ ሠራዊት አባላት ከመላው የኢትዮጵያ ግዛቶች የተውጣጡ፤ እንደሌላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ሁሉ በነፃነት እጦት፣ በመብቶች መገፈፍ እና በኑሮ ውድነት የሚሰቃዩ ዜጎች ናቸው። የኢትዮጵያ ወታደር በወያኔ አዛዦቹ እየታዘዘ ወገኑን የሚበድል ቢሆንም ራሱ ከመበደል ግን አይድንም። የኢትዮጵያ ወታደር በወያኔ አዛዡ ታዞ ሌላኛውን ወገኑን ቢያስርም ሹሙ ፊቱን ባዞረበት ጊዜ እራሱ ደግሞ ከመታሰር አይድንም። የኢትዮጵያ ወታደር ወያኔ አዞት ምስኪኖችን ይደበድባል፤ ራሱ ደግሞ በወያኔ ይደበደባል። የኢትዮጵያ ፓሊስ በወያኔ ትዕዛዝ ንጹሀን ዜጎችን ያስራል፣ ያሰቃያል፤ እራሱ ደግሞ በወያኔ ይታሰራል፣ ይሰቃያል። ይህ ምን የሚሉት ባርነት ነው? የወያኔ ሹማምንቶች በሚመሩት የመከላከያና የፓሊስ ሠራዊት ውስጥ ያሉ ወገኖቻችን በህወሓት የሚደርስባቸው በደል ሌላው ኢትዮጵያዊ ከሚደርስበት ይብስ እንደሆን እንጂ የሚያንስ አይደለም።

ግፍ መብቃት አለበት። በጥቂት የህወሓት ሹመኖች ትዕዛዝ በኢትዮጵያዊው ወታደር ላይ የሚደርሰው ውርደት ማብቃት አለበት። ሠራዊቱ የኢትዮጵያ እንጂ የህወሓት ሠራዊት አይደለም፤ ሊሆንም አይገባውም። ሠራዊቱ ለራሱ ነፃነት ብቻ ሳይሆን ለአገርና ለሕዝብ ደህንነት ዘብ የመቆም ኃላፊነት አለበት። የኢትዮጵያ ሠራዊት የህወሓት የባንዳ ሠራዊት ሆኖ ሕዝብን በማሰቃየትና ሀገርን በመበደል ተግባር ላይ ተሠማርቶ ማየት አንሻም። ይህንን ለራሱ ክብር ያለው፤ አገሩንና ሕዝቡን የሚወድ የሠራዊቱ አባልም የሚፈቅደው ጉዳይ አይደለም።

ስለሆነም ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ የሚከተለው ሀገራዊ ጥሪ ለመላው የመከላከያና የፓሊስ ሠራዊት አባላት ያቀርባል።

ውድ የኢትዮጵያ የመከላከያ ወይም የፓሊስ ሠራዊት አባል! በጥቂት የህወሓት ፋሽስቶች መዳፍ ውስጥ ሆነህ የገዛ ራስህን፣ የቤተሰቦችህን፣ የወገንህን እና የአገርህን ስቃይ ማራዘምህን አቁም። አንተ የኢትዮጵያ ሕዝብ አለኝታ እንጂ የጥቂት ጎጠኞች ሎሌ ልትሆን አይገባም። አንተ የኢትዮጵያ ሕዝብ መከታ እንጂ የእያንዳንዱ ቤተሰብ ስጋት መሆን የለብህም። አንተ የመጪው ትውልድ አርዐያ እንጂ ሕፃናትንና ወጣቶችን ማስፈራሪያ መሆን የለብህም።

የኢትዮጵያ ወታደር ሆይ! ራስህን ተመልከት! ራስህን ታዘብ! ዛሬ ያለህበት ሁኔታ አሳፋሪ ነው። አዛዦችህ አገርን፣ ትውልድንና ታሪክን ለማጥፋት የተነሱ ናቸው። አንተን ተጠቅመው ነው ይህንን ዓላማቸውን የሚያስፈጽሙት። ይህ ላንተ ብቻ ሳይሆን ለልጅ ልጆችህ ውርደት ነው። ከወያኔ ባርነት ራስህን ነፃ አውጣና የነፃነት ታጋዮችን ተቀላቀል። ወያኔ መጥፋቱ አይቀርም። ወያኔ የቀድሞውን ጦር እንደበተነው አንተን ለመበተን የሚሻ የለም። አንተ ዛሬ ከወገን ጋር ወገንተኛነትህን ካሳየህ ከአገዛዙ ጋር እጠፋለሁ ብለህ አትስጋ። ለዚህም ነው አንተ ዛሬ በግልም ሆነ በቡድን የምትወስደው እርምጃ የአገራችንን ብቻ ሳይሆን የሠራዊቱን እጣ ፈንታ ይወስናል ብለን ወገናዊ ጥሪ የምናቀርብልህ።

ውድ የኢትዮጵያ የመከላከያና የፓሊስ ሠራዊት አባላት ወገናችን!ከበዳዮች ጎን ሳይሆን ከተበዳዮች ጎን ቁም። ከገራፊዎችና ገዳዮች ጎን ሳይሆን ከነፃነት ታጋዮች ጎን ሁን። ዛሬውኑ ወስን። አሁን የነፃነት ታጋዮችን መቀላቀል ቀላል ሆኗል። ያሉበትን ታውቃለህ፤ ተቀላቀል። አልያም የጠመንጃህን አፈሙዝ በፋሽስት አለቆችህ ላይ አዙር። ይህንን እርምጃ በመውሰድ ከታሪክ ተወቃሽነት እራስህን በመታደግ ለአገርህና ለወገንህ አለኝታህን አረጋግጥ።

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ !!!

የፖለቲከኞቹ እስር እና ያስከተለው ሕገመንግሥታዊ ጥያቄ

$
0
0

በመልካሙ አበበ

ሰንደቅ

Wektawi62ጠ/ሚኒስትር ኃ/ማርያም ደሳለኝ ከቢቢሲ ፎከስ ኦን አፍሪካ ጋር ሰሞኑን ባደረጉት ቃለምልልስ የግንቦት 7 ዋና ጸሐፊ የሆኑት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ከየመን ወደኢትዮጵያ ተላልፈው የመሰጠታቸው ጉዳይ በማንሳት “የኢትዮጵያ መንግስት የፖለቲካ ፓርቲዎችን ሽፋንአድርጎ የሚመጣአሸባሪነትንአይታገስም”ማለታቸውን ዘግቧል።

     የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌን መያዝ ተከትሎ በሀገር ውስጥ በሕጋዊ መንገድ ተመዝግበው የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ከፍተኛ አመራሮች ከሆኑት መካከል አቶ ሐብታሙ አያሌው እና አቶ ዳንኤል ሺበሺ ከአንድነት፣ አቶ የሺዋስ አሰፋ ከሰማያዊ ፓርቲ፣ አቶ አብርሃ ደስታ ከአረና ትግራይ (ዘግይቶም ቢሆን ፍ/ቤት ቀርቧል)፣ ባለፈው ሳምንት ማክሰኞ በፖሊስ ቁጥጥር ሥር መዋላቸው ይታወሳል። የጸረ ሽብር ግብረሃይል የግንቦት 7 ልሳን ከሆነው ኢሳት ቴሌቪዥን ጋር ግንኙነት ያላቸው የተቃዋሚ ፓርቲ አባላትን በቁጥጥር ስር ማድረጉን በደፈናው በዕለቱ የገለጸ ሲሆን የተያዙት የአንድነት፣ የሰማያዊና የአረና አመራሮች መሆናቸው ሲታይ መግለጫው እነሱን በቀጥታ የሚመለከት ስለመሆኑ የብዙዎች ግምት ሆኗል።

እስሩ እና የፓርቲዎች ምላሽ

     አንድነትና ሰማያዊ ፓርቲዎች በተናጠል ሰሞኑን ባወጡት መግለጫ እስሩን ከመጪው ዓመት ምርጫ ጋር በቀጥታ አስተሳስረውታል። አንድነት በመግለጫው ኢህአዴግ የአንድነትን ከፍተኛ አመራሮች በማሰር የምርጫ ዘመቻውን ይፋ አድርጓል ብሏል። ሰማያዊ ፓርቲም በበኩሉ እስሩ ኢህአዴግ ቀጣዩን ምርጫ ያለተቀናቃኝ ለማለፍ የሚያደርገው ሕገወጥ እንቅስቃሴ አካል ነው ሲል ነቀፌታውን ሰንዝሯል።

   ጠ/ሚኒስትር ኃ/ማርያም ደሳለኝ ለቢቢሲ በሰጡት መግለጫ ላይ በሕጋዊ መንገድ በፖለቲካ ፓርቲ በመደራጀት እናሽፋን በማድረግህገወጥ እንቅስቃሴን በማካሄድ መንግስትን በኃይል ለመለወጥ እየተንቀሳቀሱ ያሉ ግለሰቦች አሁንም ከተጠያቂነት አያመልጡም ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

ሕግ አስከባሪው፤ ሕግ ያለማክበር ጥያቄ ሲነሳበት፣

     የሕጎች ሁሉ የበላይ ሕግ የሆነው ኢትዮጵያ ህገመንግስት አንድ ሰው በሕግ ጥላ ስር ከዋለ በኋላ ቢበዛ በ48 ሰዓታት ፍርድቤት መቅረብ እንዳለበት ይደነግጋል። በተለይ የአንድነት እና የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ማክሰኞ ሐምሌ 1 ቀን 2006 ዓ.ም በቁጥጥር ስር ከዋሉ በኋላ ፍ/ቤት ሳይቀርቡ ሰባት ቀናት ተቆጥረዋል። ይህም ብቻ አይደለም፤ በመረጡት ጠበቃ የመወከል መብታቸውንም ተጠቅመው ከጠበቆቻቸው ጋር የመገናኘት ዕድል መነፈጋቸውን ከፓርቲዎቹ የወጡ መረጃዎች ያሳያሉ። አንድነት ይህን ድርጊት ሕገወጥ በማለት አካልን ነጻ የማውጣት ክስ በፍርድ ቤት መመስረቱን አስታውቋል። ይህም ሆኖ እስከትላንት(ማክሰኞ ሐምሌ 8 ቀን 2006) ማምሻውን ድረስ ተጠርጣሪዎቹ ፍ/ቤት ስለመቅረባቸው የታወቀ ነገር የለም።

አንድ የህግ ባለሙያ በዚህ ጉዳይ ላይ በሰጡት አስተያየት “የሕግ የበላይነት በሚከበርበት ሀገር መንግሥት መረጃ አለኝ እስካለ ድረስ በሽብር ተግባር የተጠረጠሩ ሰዎችን ይዞ ማሰሩ አዲስ ነገር አይደለም። ነገር ግን ህግና ስርዓት እንዲከበር እተጋለሁ የሚል መንግሥት ራሱ ያወጣውን ሕገመንግስትን ጥሶ ያሰራቸውን ተጠርጣሪዎች በወቅቱ ወደፍርድ ቤት ማቅረብ ሳይችል ሲቀር የሕግ በላይነት የሚባለው ጉዳይ ያበቃለታል። በዚህ ምክንያት ዜጎች በመንግሥትና በሕግ ላይ ያላቸው አመኔታ የሚያጡ ሲሆን በቀጣይ ሕግና ስርዓትን አስከብራለሁ ብሎ የሚሞክራቸው ወይንም የሚናገራቸው ነገሮች ሁሉ በሕዝብ ዘንድ ተአማኒነትን ስለማይኖራቸው ትልቅ ችግር ይገጥመዋል” ሲል አስተያየቱን ሰጥቷል።

በሰሞኑ ክስተት፤ የኢዴፓ አቋም

የኢትዮጽያዊያን ዴሞክራሲዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) “በሽብርተኛነት ስም የሚወሰደው እርምጃ ግልጽነት ይኑረው” በሚል ርዕስ ከትላንት በስቲያ ባወጣው መግለጫ የመንግሥት እርምጃ እንዳሳሰበው ጠቁሟል። መግለጫው እንዲህ እያለ ይቀጥላል «በሀገር ውስጥ በሕጋዊ መንገድ ተመዝግበው የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች ሐምሌ 1 ቀን 2006 ዓ.ም መንግሥት በሽብር ጠርጥሮ በቁጥጥር ስር ማዋሉ በሚዲዎች ተገልጿል። እነዚህ አመራሮች ከ48 ሰዓታት በላይ ፍርድ ቤት አለመቅረባቸውና የሚመለከታቸው የመንግስት አካላት በጉዳዩ ላይ ዝርዝር መረጃ አለማቅረባቸው አመራሮቹ የታሰሩት በሚያራምዱት የፖለቲካ አቋም እንዳይሆን ፓርቲያችን ሥጋት አድሮበታል።

የኢዴፓ ስራ አስፈጻሚ ኮምቴ በጉዳዩ ላይ ጥልቅ ውይይት ካደረገ በኋላ የሚከተለውን አቋም ወስዷል።

  1. 1. መንግሥት የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች የተያዙበትን ምክንያት ለህብረተሰቡ በዝርዝር እና ግልጽ መረጃ እንዲሰጥ፣
  2. 2. የታሰሩት የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች በሕገመንግስቱ አንቀጽ 21 መሠረት ለዜጎች የተሰጠው መብት እንዲከበርላቸው፣
  3. 3. በአስቸኳይ ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ፣ የፍርድ ሒደታቸውም ተአማኒ፣ ግልጽ እና ፈጣን በሆነ መንገድ እንዲታይ እያሳሰብን ይህ ሳይሆን ቀርቶ ግን አገሪቱ ሕግ አክብረን በሰላማዊ ትግል ከምንቀሳቀስ ፓርቲዎች ይልቅ በተቃራኒ የሚንቀሳቀሱ ጽንፈኛ ኃይሎች የሚያጠናክር፣ ክርክራቸውንም ምክንያታዊ የሚያደርግ እና የዴሞክራሲ ግንባታውን ወደኋላ የሚመልስ በመሆኑ ጉዳዩ በእጅጉ እንደሚያሳስበን እንገልጻለን። ስለዚህም መንግስት የጉዳዩን አሳሳቢነት ተገንዝቦ አስቸኳይ መፍትሄ እንዲሰጥ ኢዴፓ ያሳስባል።”

የፍረጃ ፖለቲካ

    የደርግ መንግሥትን በኃይል ለመጣል በተደረገው የትጥቅ ትግል ወቅት ደርግ ታጋዮችን “ገንጣይ፣ አስገንጣይ፣ የእናት ጡት ነካሽ ወንበዴ….” እያለ የህዝብ ድጋፍ እንዳያገኙ ሌተቀን የመንግስት መገናኛ ብዙሃንን መሣሪያ በማድረግ ያወግዝ እንደነበረው ሁሉ አሁንም በተመሳሳይ ሁኔታ ኢህአዴግ ተቀናቃኞቹን በተደጋጋሚ በጠላትነት ሲፈርጅ፣ ሲያጥላላ ይታያል። በተቃዋሚ ፓርቲዎችም በኩል ተመሳሳይ ዝንባሌዎች የሚታዩ መሆኑ መቻቻልና በጋራ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ እንኳን አብሮ የመሥራት ባህል እንዳያድግ እንቅፋት ሆኖ ቆይቷል።

    በዚህ ምክንያት ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ እና ብዙዎቹ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ግንኙነታቸው በጠላትነት መንፈስ ላይ የተመሰረተና መተማመን የሌለበት፣ ጥላቻ የነገሰበት ሆኖ እስከአሁን ዘልቋል። ኢህአዴግ በ2002 ምርጫ ከ99 በመቶ በላይ ወንበሮችን ካሸነፈ በኋላ ለንባብ የበቃው “አዲስ ራዕይ” መጽሔት በሐምሌ-ነሐሴ ወር 2002 ዓ.ም ዕትሙ ስለተቃዋሚዎች እንዲህ ይላል። “…አንዳንዶቹ ተቃዋሚዎች የተለመደውን የቀለም አብዮተኞች ስልት በመጠቀም የምርጫ ሕጎችን ሆን ብለው በመጣስ በሕጉ መሰረት እርምጃ ሲወሰድባቸው በነጻ መወዳደር አልቻልንም ብለው ኡኡ እንደሚሉ ሳይታለም የተፈታ ጉዳይ ነበር። እናም ስትራቴጂያችን እንደነዚህ ዓይነት ድርጊት ሲፈጸም መዋቅራችን የተሟላ መረጃ በቪዲዮ ጭምር እንዲይዝ፣ ይህንኑ መሠረት አድርጎ ድርጊቱን በሕዝብ ፊት እንዲያጋልጥና ሆን ተብሎ ምርጫውን ለማበላሸትና ብጥብጥ ለመፍጠር የተደረገ ተግባር መሆኑን እንዲያስረዳ፣ ሕጉ የተፈቀደለትን እርምጃ ከመውሰድ ተቆጥቦ ነገሩን ለበላይ አካል ሪፖርት እንዲያደርግ ነበር የሚያስቀምጠው። በዚሁ መሠረት የተቃዋሚዎች ሕገወጥ ድርጊት በየአካባቢው እንደነገሩ ሁኔታ በአገር አቀፍ ደረጃ በሰፊው የሚጋለጥበት ሁኔታ ተፈጠረ” ሲል የመተጋገሉን ደረጃ ያሳያል።

    እንዲህ ዓይነት አንዱ አጋላጭ ሌላው ተጋላጭ፣ አንዱ ሕግና ስርዓትን አክባሪ፣ ሌላው ጸረ ሕገመንግሥት፣ አንዱ ሽብርተኛ ሌላው የሠላም አቀንቃኝ አድርጎ የመሳሉ ጉዳይ ሞቅ በረድ እያለ አሁን ድረስ መቀጠሉ በሁለቱ ኃይሎች መካከል ያለው የፖለቲካ ልዩነት ወደአላስፈላጊ ጠርዝ የሚገፋ ሆኖ ይታያል።

    ከምንም በላይ ደግሞ መንግሥት በወንጀል ጠርጥሮ የያዛቸውን ሰዎች በወቅቱ ፍርድ ቤት ከማቅረብ መቆጠቡ ሕገመንግሥታዊ ሥርዓቱን አክብሮ የማስከበር ኃላፊነቱን አለመወጣቱን ያሳያል። ሕግና ሥርዓትን የማክበር ጉዳይ ደግሞ በምንም ዓይነት ምክንያት ሊስተባበል የማይችል መሆኑንም መንግሥት ይስተዋል ተብሎ ስለማይገመት ስህተቱን በፍጥነት ሊያርም ይገባል።

ከእስሩም በላይ –“ሽብርተኝነት” –እስረኞቹ በሽብር መከሰሳቸውን አያውቁም

$
0
0

ጽዮን ግርማ
tsiongir@gmail.com

አንድ ዓመት ከአንድ ወር ኾኖታል፡፡ እስክንድር ነጋ ከታሰረ ከዐስራ ስምንት ወራት በኋላ ከባለቤቱ ከጋዜጠኛ ሰርካለም ፋሲል እና ከልጁ ከናፍቆት በተጨማሪ ለመጀመሪያ ጊዜ ሌላ ሰው እንዲጠይቀው በሰኔ የመጀመሪያ ወር ላይ በ2005 ዓ.ም እንደተፈቀደለት ነው፡፡ በወቅቱም እስክንድርን ልጠይቀው ቃሊቲ ወደሚገኘው እስር ቤት አምርቼ ነበር፡፡
zone 9
ተገናኝተን ሰላምታ ከተለዋወጥን በኋላም እንዲህ አለኝ፤‹‹ሽብርተኛ አይደለኹም፤ሀገሬ በማንም እንድትሸበር አልፈልግም አልፈቅድምም እኔ የምፈልገው የሀገሬ ሕዝቦች በነጻነት የሚያስቡባትና የሚንቀሳቀሱባት ሰላማዊ ሀገር እንድትኾን ነው››፤እስክንድር ‹‹ሽብርተኛ›› አይደለምና ከእስሩም በላይ ያንገበገበው ‹‹አሸባሪ›› መባሉ ነበር፡፡

እስክንድር ‹‹ጋዜጠኛ›› ነው፡፡ እስክንድር ሲጽፍ ሀገሪቱ ላወጣችው ሕግ ራሱን አስገዝቶ፣በሀገሪቱ ሕግ ማዕቀፍ ሥር ራሱን ገድቦ ነው፡፡ ይህም ኾኖ ግን ሲጽፍ ሕግ ተጥሶ አደጋ ሊደርስበት እንደሚችል፣ሲጽፍ ሕግ ተጥሶ ሊታሰር እንደሚችል ያውቃል፡፡ ግን ደግሞ ቢታሰር በቀጫጭን መስመርም ቢኾን በሀገሪቱ ሕግ ተዳኝቶ ከእስር ሊለቀቅ እንደሚችል ያምን ነበር፡፡በዚህ እምነቱም የመጣበትን ለመቀበል ተዘጋጅቶ ሀገሩ ላይ ቁጭ ብሎ ይጽፋል፡፡
ከመጻፍ እና ሐሳቡን በአደባባይ ከመግለጽ ውጭ ያሉት መንገዶች እስክንድርን አይመቹትም፡፡ እስክንድር ሐቀኛና ቀጥተኛ የኾነ አስተሳሰብ ያለው ላመነበት ነገር የታመነ ንጹህ ኢትዮጵያዊ ነው፡፡ ምናልባት ይህን ‹‹እስክንድርን›› ለመረዳት እስክንድርን ማወቅ ሊጠይቅ ይችላል፡፡ እስክንድርን ያኔ ቃሊቲ ሳገኘው ሽብርተኛ አለመኾኑን ደጋግሞ ነገረኝ፡፡ ‹‹እስክንድር ለማነው የምትነግረው ሽብርተኛ አለመኾንህን ከቀረበብህ ክስ ጋር አንዳችም ግንኙነት እንደሌለህ እኮ ዓለም ያውቃል፤አሳሪዎችህም ይህን ጠንቅቀው ያውቃሉ›› አልኩት፡፡ እርሱን ግን ያበሳጨው ከታሰረውም፣ከተንገላታውና ከተፈረደበትም በላይ በውሸት የተወነጀለበት “ሽብርተኝነት’’ ነበር፡፡

አሁንም ሽብርተኝነት

አሁን እስክንድር ከታሰረ ሁለት ዓመት ከሰባት ወር ኾኖታል በእርሱ የተጀመረው ጋዜጠኛን፣ጸሐፊዎችንና መብቱን በአደባባይ የሚጠይቀውን ሁሉ ሰብስቦ ‹‹ሽብርተኛ›› ብሎ መክሰስ ዕለት በዕለት እየጨመረ የታሳሪዎቹን ቁጥር አበራክቷል፡፡ ላለፉት ሰማንያ ሦስት ቀናት በማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ታስረው የሚገኙትና በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አንደኛ ወንጀል ችሎት በጊዜ ቀጠሮ መዝገብ በቀጠሮ ሲመላለሱ የቆዩት ጋዜጠኛ ተስፋዓለም ወልደየስ፣ ጋዜጠኛ አስማማው ኃይለ ጊዮርጊስና፣ ጋዜጠኛ ኤዶም ካሳዬ፣ የሕግ መምሕርና የዞን ዘጠኝ ጦማሪ ዘለዓለም ክብረት፣ የዞን ጦማሪዎቹ ናትናኤል ፈለቀና አጥናፉ ብርሃኑ ለቅዳሜ ሐምሌ 5 ቀን የዞን ዘጠኝ ጦማሪዎቹ ማኅሌት ፋንታሁን፣ በፍቃዱ ኃይሉና አቤል ዋበላ በዚሁ በፈረደበት ‹‹ሽብር›› ተጠርጥረው የታሰሩ ናቸው፡፡
የምርመራ መዝገቡ በሌሉበት መዝገቡ ተዘግቶ ከሕግ ውጪ በእስር የከረሙት እነዚህ እስረኞች ግንቦት ዘጠኝ በነበረው ቀጠሮ ቀን ፖሊስ ፍርድ ቤት ቀርቦ ተጠርጣሪዎችን በሽብር መጠርጠሩን ሲናገር ወጣቶቹ በድንጋጤ አንገታቸውን ሲሰብሩ ታይተው ነበር፡፡ የሚያስደነግጠው እስሩ አይደለም ሕግን አስከብራለሁ የሚል አንድ ተቋም ወጣቶችን ሰብስቦ አስሮ ባልዋሉበት የሚያውል የፈጠራ ክስ ሲጭን መስማቱ ነው፡፡ማንነቱን ጠንቅቆ የሚያውቅ ሰው እንዲህ ያለ የውሸት ክስ ሲቀርብበት የሚሰማውን ስሜት ለመገመት ያስቸግራል፡፡ እናም ወጣቶቹ በሽብር ተግባር አለመሳተፋቸውን ያውቃሉና የቱንም ያህል ኢሕአዴግን ባህሪ ጠንቅቀው ቢያውቁት ‹‹በሽብር እንከሰሳለን›› የሚል ቅንጣት ያህል ጥርጣሬ ሊኖራቸው አይችልም፡፡ ምናባት የመጨረሻውን ጣሪያ ቢገምቱ እነርሱን አስሮ ሌሎች ጸሐፊዎችን ለማስፈራራት የተነደፈ ስልት ይኾናል ከሚል ግምታዊ መላምት ‹‹ምርጫው እስኪያልፍ ታስረን እንቆያለን›› የሚለውን ነው፡፡
ዛሬ ጠዋት ልደታ በሚገኘው ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛው ወንጀል ችሎት ሲቀርቡም ከዚሁ ሐሳብ ሊኖራቸው እንደማይችል እገምታለሁ፡፡ ወጣቶቹ ከታሰሩ ጀምሮ ጉዳያቸውን ሲከታተሉ የቆዩት ጠበቃ፣ቤተሰብና ሌሎች ሰዎች ከትናንት ጀምሮ ፍርድ ቤት ሊቀርቡ ይችላሉ በሚል ይቀርቡበታል በተባለው ፍርድ ቤት ግቢ ክትትል ሲያደርጉ ቢቆዩም ዛሬ ጠዋት ማንም ሰው ባልተገኘበት ዐቃቤ ሕግ የክስ መዝገብ ከፍቶባቸዋል፡፡ ነገር ግን የክስ ቻርጁ እንዲሰጣቸውና መቃወሚያ ካላቸው እንዲናገሩ ተጠይቀው ዘጠኙም እስረኞች ጠበቆቻቸው ባልተገኙበት ክሱ እንዲነበብላቸው እንደማይፈልጉ ያቀረቡት አቤቱታ ተቀባይነትን አግኝቶ ጠበቆቻቸው በተገኙበት ነገ ጠዋት እንዲቀርቡ ታዟል፡፡

በሌላም በኩል ዛሬ ጠዋት እስረኞቹን ለመጠየቅ ማዕከላዊ ሄደው የነበሩ ቤተሰቦችና ጠያቂ ወዳጆች መግባት እንደማይችሉ ተነግሯቸው ተመልሰው ነበር፡፡ ከሰዓት በኋላም ሊጠይቋቸው በሄዱ ጊዜ ስለተከሰሱት ክስ የሚያውቁት ነገር አልነበረም፡፡ አብዛኞቹም (አብዛኞቹ ስል ስለ አስተያየታቸው መረጃ ያገኘኹት ማለቴ ነው) በሽብርተኝነት እንከሰሳለን የሚል እምነት አልነበራቸውም፡፡ነገ የሚኾነውን ለማየት በይደር አቆይተው ቤተሰቦቻቸውን ተሰናብተው ወደ ማደሪያቸው ወደ እስር ቤት ተመልሰዋል፡፡

የሽብርተኝነት ክሱ

የሪፖርትር ጋዜጣ ዘጋቢ ታምሩ ጽጌ ደግሞ ሰበር ዜና በሚል በጋዜጣው ድረ ገጽ ላይ፤ ሶልያና ሽመልስ (በሌለችበት)፣ በፍቃዱ ኃይሉ፣ ናትናኤል ፈለቀ፣ ማህሌት ፋንታሁን፣ አጥናፉ ብርሃኔ፣ ዘለዓለም ክብረት፣ አቤል ዋበላ፣ እንዲሁም ጋዜጠኞቹ አስማማው ኃይለ ጊዮርጊስ፣ ኤዶም ካሣዬና ተስፋለም ወልደየስ ላይ ዐቃቤ ሕግ በሽብርተንነት ክስ መመስረቱን አስነብቦናል፡፡

ዜናው እንደሚለው፤ ተጠርጣሪዎቹ በሕቡዕ በመደራጀት፣ የአጭርና የቅርብ ጊዜ ግብ በማቀድና በመንደፍ ከግንቦት 2004 ዓ.ም. ጀምሮ እጃቸው እስከተያዘበት ጊዜ ድረስ በፓርላማ ሽብርተኛ ተብለው ከተሰየሙት የግንቦት 7 እና የኦነግ ድርጅቶች መመርያና ሐሳብ ሲቀበሉ መቆየታቸው ተገልጿል፡፡
ከተጠርጣሪዎቹ አንዷ የሆነችው ሶሊያና ሽመልስ የቡድኑ መሥራችና አስተባባሪ በመሆን ከ2004 እስከ 2006 ዓ.ም. መቆየቷና ከ2006 ዓ.ም. ጀምሮ በውጭ አገር አስተባባሪና የውጭ ግንኙነት ሆና ከመሥራቷም በተጨማሪ፣ ከግንቦት 7 ጋር ግንኙነት ለመፍጠር ተልዕኮ በመቀበል፣ አባላትን በማደራጀትና በመመልመል ስትሠራ መቆየቷን ክሱ ያስረዳል፡፡የህቡዕ ቡድኑ ከ2004 እስከ 2006 ዓ.ም. ‹‹ሴኩሪቲ ኢን ቦክስ›› የተባለ ሥልጠና እንዲሠለጥንና እንዲደራጅ ስትመራ መቆየቷም በክሱ ተካቷል፡፡
ሌላኛው ተጠርጣሪ በፍቃዱ ኃይሉ የአገር ውስጥ የሽብር ቡድንን በመምራትና የሥራ ክፍፍል በማድረግ፣ እንዲሁም ግብ በማስቀመጥና ስትራቴጂ በመንደፍ ከሽብርተኛ ኃይሎች ጋር ግንኙነት ሲፈጥር መቆየቱ በክሱ ተጠቅሷል፡፡
የዓቃቤ ሕግ ክስ እንደሚያስረዳው ከሆነ ተጠርጣሪ ናትናኤል ፈለቀ ከ2004 ዓ.ም. ጀምሮ ካልተያዙ ግብረ አበሮቹ ጋር በመሆን የህቡዕ ድርጅቱ የአገር ውስጥ አስተባባሪ በመሆን በሥሩ ላሉት አባላት የሥራ ክፍፍል መመርያ በመስጠት፣ ከግንቦት 7 ጋር ግንኙነት በመፍጠር መመርያ ከመቀበሉ በተጨማሪ፣ ለአመፅ ተግባር የሚውል የተላከለትን 48,000 ብር ማከፋፈሉንም ክሱ ያብራራል፡፡

ሌሎቹ ተጠርጣሪዎች በህቡዕ ድርጅቱ ውስጥ ከ2004 ዓ.ም. ጀምሮ መሥራችና አባል በመሆን የግንቦት 7 እና የኦነግን ስትራቴጂና ዕቅድ በመቀበል በውጭና በአገር ውስጥ ባሉ የቡድኑ አባላት ጋር ግንኙነት በመፍጠር፣ በውጭና በአገር ውስጥ ሥልጠና በመውሰድ፣ በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን የሽብርተኝነት ድርጊት ለመፈጸም በማቀድ፣ በመዘጋጀት፣ በማሰርና በማነሳሳት ወንጀል መከሰሳቸውን ዓቃቤ ሕግ ያቀረበው ክስ ያስረዳል፡፡

በሁሉም ተጠርጣሪዎች ላይ ዓቃቤ ሕግ ያቀረበው ሁለተኛ ክስ እንደሚያስረዳው ተጠርጣሪዎቹ በወንጀሉና በሚያስገኘው ውጤት ተስማምተው በሕገ መንግሥት ሥርዓት የተቋቋመን መንግሥት በአመፅ፣ በሁከትና በብጥብጥ ለመለወጥ በማሰብ ከግንቦት 2004 ዓ.ም. እስከተያዙበት ዕለት ድረስ በህቡዕ ተደራጅተው፣ የሥራ ክፍፍል በመፍጠር፣ ሥልጠናዎችን በመውሰድ፣ አመፅ የሚቀሰቅሱ ጽሑፎችን በመበተን፣ የአመፅ ቡድኖችን በማደራጀት ሕገ መንግሥቱና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን በአመፅና በሁከት ለመለወጥ በመሞከር ወንጀል መከሰሳቸውን የዓቃቤ ሕግ ክስ ያስረዳል፡፡

በመጨረሻ

ይህን ክስ የሰማ ማንም ሰው እነዚህ ወጣቶች ሽብርተኛ አለመኾናቸውን እንደሚረዳው ኹሉ ከሳሻቸው ዐቃቤ ሕግም የውሸት ክስ እንደመሰረተባቸው ልቦናው ያውቀዋል፡፡ በተለይ ደግሞ ወጣቶቹን በቅርበት ለሚያውቃቸው ሰው በእነሱ ላይ እንዲህ ያለ ክስ ሲመሰረትባቸው ምን ዐይነት ስሜት እንደሚፈጥር ለመግለጽ ያስቸግራል፡፡ጠንካራና ሀገር ወዳድ ወጣቶች በሽብርተኝነት ሲከሰሱ መስማት የሚፈጥረውን ቁጭት ከቃላትም በላይ ነው፡፡ይህ ስሜት እነርሱ ላይ ሲደርስ ምን ሊኾን እንደሚችልም መገመት ያስቸግራል፡፡ እስክንድርን ከመታሰሩም በላይ ያስከፋው እንኳን ክፉ ሊያደርስባት ክፉ እንዳይነካት ቀን ከሌሊት የሚጸልይላትን የሚወዳትን ሀገሩን ገንዘብ ተቀብለህ ልትበጠብጣት ነው መባሉ ነበር፡፡
‹‹ዴሞክራሲያዊነቷ›› የታወጀላት ታሀገር ስትበደል ሕግ በሚፈቅድላቸው መሰረት ተቃውሟቸውን በጹሑፍ ያሰሙ፣ለሀገሪቱ ሕግ ራሳቸውን አስገዝተው የጋዜጠኝነት ሥራን የሠሩ በሽብርተኞች እጅ የወደቁ እንጂ ‹‹ሽብርተኛ›› ያልኾኑት ወጣቶች ነገ ጠዋት በሽብርተኝነት መከሰሳቸውን ሲሰሙ ምን ይሉ ይኾን

(ሰበር ዜና) በአንዋር መስጊድ ፖሊስ እና ሕዝበ ሙስሊሙ ተጋጩ፤ በአካባቢው ውጥረት ነግሷል

$
0
0


(ፎቶ ፋይል)

(ፎቶ ፋይል)

(ዘ-ሐበሻ) የእለተ አርብ ጸሎት ለማድረስ አንዋር መስጊድ የከተመው ሕዝበ ሙስሊም እና የፌድራል ፖሊስ ግጭት መፍጠራቸው ተሰማ። ፖሊስ ትንኮሳ በመፍጠር በተለይ በኤሌክትራ ሙዚቃ ቤት አካባቢ ሰላማዊውን ሕዝብ መደብደብና በፖሊስ መኪና መጫን ሲጀምር ሕዝቡ ቁጣውን በመግለጽ በፖሊስ ላይ ድንጋይ መወርወሩን ለዘ-ሐበሻ የደረሰው መረጃ አመልክቷል።

የፌደራል ፖሊስ ለአርብ ጸሎት በመስጊድ የተገኘው ሕዝን በመክበብ ከመስጊድ እንዳይወጣ ለማገድ ሙከራ ሲያደርግ ነበር ያሉት የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች በራሱ የመንግስት ካድሬዎች አማካኝነት ብጥብጥ በማስነሳት ጉዳዩን ከሙስሊሞቹ ጋር ለማያያዝ ሙከራ ማድረጉን ጠቅሰዋል። በፖሊስ ላይ ድንጋይ መወረወር የጀመሩት መንግስት ያዘጋጃቸው ካድሬዎች ናቸው የሚሉት ዘጋቢዎቻችን ፖሊስ ይህን ተከትሎ በርካታ ሙስሊሞችን ማሰሩን እና አስለቃሽ ጭስ መጠቀሙን ምንጮቻችን ጠቁመዋል።

ፖሊስ በሕዝቡ ላይ ከፍተኛ ድብደባ እየፈጸመ እንደሚገኝ የሚገልጹት የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች አካባቢው በጥይት እሩምታ እየታመሰ እንደሚገኝና ውጥረቱም እንዳየለ አስታውቀዋል።

ፌደራል ፖሊስ ሕዝቡን ሲቀጠቅጥ፣ ሲያሸብር፣ አንዋር መስጊድን ሲከብና ሙስሊሙን ሲያስር የሚያሳዩ ፎቶዎች

$
0
0

ከድምጻችን ይሰማ

ሰላማዊው ሙስሊም እረፍት የነሳቸው የመንግስት ሃይሎች ዛሬም የጎዳና ላይ ነውጥ ፈጥረው እየደበደቡ እና ያለምንም ልዩነት መንገድ ላይ ያገኙትን ሁሉ እያሰሩ ነው፡፡ ፖሊሶች ከተክለሃይማኖት ጀምሮ አንዋር መስጂድ ድረስ መንገድ ዘግተው ቆይተዋል፡፡ አደባባይ ላይም ያገኙትን እያሰሩ ነው፡፡ አንድ ፖሊስ በተፈጠረው ግርግር በራሳቸው በፖሊስ መኪና ተገጭቶ ከፍተኛ አደጋ ደርሶበታል። መንግስታዊ ሽብር ዜጎች ሰላም እንዳይሆኑ የሚያደርግ ፀረ ህዝብ አቋም ነው! ህዝበ ሙስሊሙ ዛሬም በቀደሙት መንግስታት ይደርስበት እንደነበረው በእምነቱ እየተጨቆነ በአምልኮ ቤቱ እርምጃ እየተወሰደበት ነው፡፡ ህዝበ ሙስሊሙ ዲኑን እስከዛሬ ያቆየው በመስዋእትነት ነው! ለዚህ ድንቅ ትውልድ ምስጋና ቢያንሰው እንጂ አይበዛበትም!

demtschin yesema 1

demtschin yesema 2

demtschin yesema 3

demtschin yesema 4

demtschin yesema 5

demtschin yesema 6

demtschin yesema 7


Health: ያልተመለሱ ወሲብ ነክ ጥያቄዎቻችሁ እና አዳዲስ የሕክምናው ሳይንስ ምላሾች

$
0
0


የ‹‹ጂስፖት›› አገር ከወዴት ነው?
ወሲብ በብርሃን ወይስ በጨለማ?

sex-good-for-healthበሴቶች በኩል የሚደፈር ርዕሰ ጉዳይ አይሁን እንጂ በርካታ ወንዶች በጋራ ሲሰበሰቡም ሆነ አንድ ለአንድ ሲያወሩ ወሲብ ነክ ጉዳዮችን አንዴ ወይም ሌላ ጊዜ ማንሳታቸው አይቀርም፡፡ በሴቶቹ ክብ ውስጥ ተገኝቼ ውይይታቸውን ባላዳምጥም እነርሱም ቢሆኑ ከጓደኞቻቸው ጋር ይህን ስሱ ርዕስ ሲያነሱና ሲጥሉ እንደሚቆዩ እገምታለሁ፡፡ በኛ አገር በወሲብ ነክ ጤና ጉዳዮች ላይ የህክምናው ሳይንስ ሰዎችም ይሁኑ ሚዲያው በግልፅ የመነጋገር እና ችግሮችን የማቅለል ልምዱ አነስተኛ በመሆኑ ወደ ጤና ተቋማት ለመሄድ እና የባለሞያን ሀሳብ ለማግኘት ተነሳሽነቱ ባይኖር ብዙ አይገርምም፡፡ ‹‹ቄሱም ዝም፣ መፅሐፉም ዝም›› በሆነበት የወሲብ ጤና ጉዳይ በውጪው ዓለም ለቁጥር የሚያታክቱ አማካሪ ባለሞያዎችና የፃፏቸው መፅሐፍት ለሰዎች የእለት ተዕለት ጭንቀቶች መፍትሄን ቢሰጡም እኛ አገር ገና ብዙ የሚቀረን እርምጃ አለ፡፡ ይህንን መነሻ አድርገን የተለያዩ ሴክስ ኤክስፐርቶች የፃፏቸውን መፅሐፍትና መጣጥፎች በማጣቀሻነት በመጠቀም በተለያየ ጊዜ የሚገጥመው ወሲብ ነክ ችግሮች እና ያልተመለሱ ጥያቄዎችን በመመለስ ግንዛቤን የሚያሲዝ አጭር ምልከታ ልናደርግ ወደናል፡፡

ምን ያህል ወሲብ? በየስንት ጊዜው?
በዚህ ለኑሮ መሮጥ የሁሉም ሰው ዕለታዊ የቤት ስራ በሆነበት ጊዜ በፍቅርም ይሁን ትዳር ውስጥ ያሉ ጥንዶች እርስ በእርሳቸው ፍቅራቸውን ለመግለፅ እና ወሲብ ለመፈፀም በቂ ጊዜ ላያገኙ ይችላሉ፡፡ ወሲብ መፈፀም አካላዊ ግንኙነት ብቻ ባለመሆኑ ሁለቱም ተጣማጆች አእምሮአቸው አሪፍ እና ዘና ብሎ ቅርርቡንም ፈልጎ ወደ ወሲብ ሲያመራ በእርካታ የሚያጥለቀልቅ እና አዝናኝ ጥምረትን ይፈጥራሉ፡፡ አንዳንድ ጥንዶች ግንኙነት ከፈፀሙ ረጅም ጊዜ ሆኗቸው ሊሆን ይችላል፡፡ ሌሎች ጥንዶች በሳምንት አሊያም በወር ምን ያህል ጊዜ ይሆን ወሲብ የሚፈፅሙት? ሲሉ በውስጣቸውም ይጠይቃሉ፡፡ በሳምንት፣ በወር ይህን ያህል ጊዜ ወሲብ ሊፈፅም ይገባል የሚል ምትሃታዊ ቁጥር የለም፡፡ የህክምና ሳይንስ ባለሞያዎችም ቁርጥ ያለ መልስ አይሰጡም፡፡ ‹‹ይህ በግንኙነቱ ጤናማነት ደረጃ እና በጥንዶች ቅርርቦሽ የሚወሰን ነው›› ባይ ናቸው፡፡
ሆኖም ግን ጤናማ ግንኙነት ውስጥ ያሉ ጥንዶች ወሳኝ ጉዳዮች መካከል ፍቅር መስራት ዋነኛው እንደመሆኑ በግንኙነት ቆይተው ለበርካታ ወራት ወሲብ ካልፈፀሙ ጥያቄ ማንሳቱ ጤናማ ነው፡፡ ለምን ያህል ድግግሞሽ እና መቼ የሚለውን ለማጥናት ሙከራ ያደረጉ ተመራማሪዎች ያሳተሙት ውጤት መነሻ ሀሳብን ሊሰጥ ይችላል፡፡ ዱሬክስ ኩባንያ 2006 ላይ ያወጣው ዓለም አቀፍ ሴክስ ሰርቬይ ላይ ዝቅተኛ ወሲብ ይፈፅማሉ የተባሉት የሲንጋፖር ሰዎች ሲሆኑ በወር 6 ጊዜ ነው ወሲብ የሚፈፅሙት፡፡ ባለሞያዎች በመጨረሻ የሚያጠቃልሉት ወሲብ የሚፈፀምበት ድግግሞሽ በሁለቱ ጥንዶች ስምምነት ያለው ከሆነ በፍቅር ግንኙነቱ አለዚያም ትዳሩ ላይ የሚፈጠር ችግር የለም፡፡ ይሁንና ከሁለቱ አንዱ ወሲብ እየፈለጉ ሌላኛው ወገን የሚያዘገየው ከሆነ በጉዳዩ ላይ በግልፅ ተወያይተው ሁለቱንም የሚያስማማ የጊዜ ርቀት እንዲያስቀምጡ እና ስሜታቸውን ተረድተው ቢዝናኑበት መልካም ነው ይላሉ፡፡

በወሲብ ስንት ደቂቃ ይቆያሉ? ቀድሞ የመጨረስ ጣጣ
በርካታ ወንዶች ወሲብ እየፈፀሙ በርካታ ደቂቃዎችን መቆየትን በፍቅር እና ትዳር አጋራቸው ዘንድ ነጥብ ያስቆጥርልናል ብለው ያስባሉ፡፡ አሳዛኙ ነገር ግን በዚህ መነሻነት በሚፈጠር መጨናነቅና የስነ ልቦና ውጥረት ገና እንደደረሱ ጨርሰው ለማቆም የሚገደዱት ናቸው የሚበረክቱት፡፡
በወሲብ የመቆየት ጊዜ ምን ያህል መሆን አለበት ለሚለው የተለያዩ የህክምና ሳይንቲስቶችና መፃህፍት የተለያዩ ምላሾችን ይሰጣሉ፡፡ በህክምናው ቋንቋ Intravaginal Ejaculatiry Latency Time (IELT) የሚባለው የቆይታ ጊዜ የሚቆጠረው ወንዱ በሴቷ ብልት ውስጥ ብልቱን ከከተተበት ደቂቃ ረጭቶ እስከሚወጣበት ድረስ ያለው ነው፡፡ ‹‹ይህ ጊዜ ልክ አንድ ደቂቃም ይሁን አንድ ሰዓት ወሳኝ ሊሆን የሚገባው በዚህ ጊዜ ሁለቱም ተጣማጆች እኩል እርካታን ከወሲብ ተጎናፅፈዋል ወይ የሚለው ነው›› ይላሉ ዶ/ር ሄለን ኦኮኔል የተባሉት የኒውሮሎጂ ባለሞያና የወሲብ ጉዳዮች አማካሪ፡፡ በደቂቃ ልኬን ማወቅ አለብኝ ለሚሉ ወንዶች መልስ ቢሆን ብለው በአማካይ አንድ ወንድ በወሲብ መቆየት ያለበትን የደቂቃ ርዝመት ያጠኑ ባለሞያዎች እ.ኤ.አ 2005 ላይ ጆርናል ኦፍ ሴክሹዋል ሜዲስን በተሰኘ የምርምር መፅሔት እንደፃፉት በአማካይ አንድ ወንድ ወሲብ እያደረገ ሊቆይ የሚችለው ለአምስት ደቂቃ ከ30 ሰከንድ ያህል ነው፡፡ ይህ ቆይታ ታዲያ ቅድመ ዝግጅቱን መተሻሸቱን እና መሳሳሙን አይጨምርም፡፡ ብልቱ ከሴቷ ብልት ገብቶ ስፐርሙን እስካፈሰሰበት ቅፅበት ያለውን ብቻ ይመለከታል፡፡ የጥናቱ አድራጊዎች ገና እንደገቡ የሚያፈሱ ሰዎችን አስመልክተው ሲፅፉ ‹‹ወሲብ መዝናኛ ነው፣ ዘና ብለው ከሴቷ ብልት መቆየታቸውን እንደ ደስታ እያሰቡ ሳይጣደፉ የሴቷ ደግሞ ስሜት እያደመጣ ወሲብ ማድረግን ይልመዱ›› ሲሉ መክረዋል፡፡ ከፍርሃት፣ ከጭንቀት እና መጠራጠር የፀዳ ንፁህ ግንኙነት ውስጥ ያሉ ጥንዶች የሚቆዩበትን ጊዜ እንዳሻቸው ሊለጥጡት ይችላሉ፡፡ ‹‹ወሳኙ የስነ ልቦናዊ ጥምረታቸው ልክ ነው›› ይላሉ የጥናቱ መሪ አያን ኬርነር፡፡ አካላዊ እና ከብልት ጡንቻዎች ጋር የተያያዘ ችግር ካለ ይህን በህክምና ማስታገስ እንደሚቻልም ያክላሉ፡፡

በወር አበባ ጊዜ ሴክስ ይፈቀዳል?
ሴቶች የወር አበባ ላይ በሚሆኑበት ወቅት አንዳንድ ጊዜ ተጣማጆቻቸውን ሴክስ ይከለክላሉ፡፡ ‹‹አሞኛል›› ይላሉ፡፡ እውን በወር አበባ ጊዜ ወሲብ መፈፀም ህመም ይሆናል? የጎንዮሽ ጉዳትስ ይኖረው ይሆን? የሚል ጥያቄ የሚያነሱ ወንዶችም ሴቶችም መልስ እንዲሆን ታዋቂዋ የሴክስ ኤክስፐርት እና የጉድቫይብስ መፅሔት ፀሐፊ ካሎል ኩዊን ያቀረቡት ፅሑፍ የሚለውን እንመልከት፡፡ ኤክስፐርቷ እንደሚሉት በወር አበባ ጊዜ ወሲብ መፈፀም ችግር የለውም፡፡ ይሁንና በአንዳንድ ሀይማኖታዊ ምክንያቶች የተነሳ ብዙ ሴቶች ከወሲብ ሲታቀቡ እንዳስተዋሉ ተናግረዋል፡፡ በሳይንሱ ግን አይከለከልም፡፡ እንዲያውም በወር አበባ ወቅት ከሚከሰተው ህመም የሚገላግልና የመዝናናት ስሜትን የሚፈጥሩት ኢንደርፊን የተባሉት ሆርሞኖች ሴክስ በሚፈፅሙ ወቅት በሰውነታቸው ስለሚለቀቅ ራስ ምታት፣ ድብርት እና ቀርጠት የመሳሰሉት የወር አበባ ህመሞችን ማስታገስ እንደሚችሉ ባለሞያዋ ያብራራሉ፡፡ ይሁንና የወር አበባ ወቅት የማህፀን ጫፍ ደሙን ለማስወጣት ከፈት የሚልበት በመሆኑ እንዲሁም የብልታቸው አካባቢ ከወትሮው በተለየ አሲዳማነቱ የሚቀንስ በመሆኑ ለተለያዩ ኢንፌክሽኖች እና አባላዘር በሽታዎች የሚጋለጡበትም ወቅት ስለሚሆን ሁልጊዜም ኮንዶም መጠቀምን አይርሱ ሲሉ ሀሳባቸውን ያጠቃልላሉ፡፡

ወሲብ በጠዋት የጤና ነው?
የባለቤቷ የወሲብ ፍላጎት ጉዳይ ያሳሰባት ሴት ባቀረበችው ጥያቄ እርሱ ወደ ቤት ማታ ሲመጣ ደካክሞ ይመጣና ይተኛል፡፡ ጠዋት ላይ ግን አፈፍ ያደርገኝና ወሲብ መፈፀም እንጀምራለን፡፡ ይሄ የሌሎች ወንዶች ተፈጥሮ ይሆን ወይ? የጤናስ ነው? ስትል ትጠይቃለች፡፡ ለእርሷና ሌሎች ተመሳሳይ ጥያቄ ለሚኖራቸው ሰዎች ኤክስፐርቶቹ የሚሉት አላቸው፡፡ በእርግጥም የወንዶች ተፈጥሯዊ የሆርሞን ስርዓት የሚፈጥረው ፍላጎት አለ፡፡ የወንዶች የወንዴ ሆርሞን ቴስቴስትሮን መጠን በቀን ውስጥ ከፍ እና ዝቅታ ይገጥመዋል፡፡ በተለይ ከጠዋቱ 12 ሰዓት እስከ 4 ሰዓት መጠኑ ከፍ ብሎ የሚገኝበት በመሆኑ ወሲብ ቢጠይቅ አትፍረጂበት ይላሉ ዩሮሎጂስት ሐኪሟ፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ያደረ ሽንት በሽንት ከረጢት ስለሚጠራቀም ግፊቱ ደም ወደ ብልቱ በብዛት እንዲደርስና ብልቱ እንዲወጠር ያደርጋል፡፡ እነዚህ የሆርሞኖችና በደም ፍሰቱ የብልት መወጠር ምክንያቶች በጠዋት ለወሲብ መነቃቃቱ ተፈጥሯዊ ነው፡፡ የጠዋት ጉልበትና ብርታቱም ሳይነዘጋ፡፡

የ‹‹ጂስፖት›› አገር ከወዴት ነው?
ሴቶችን የማርካት ፈተና
ሴቶች በወሲብ መርካታቸው ጉዳይ እንደ ሁለተኛ ነገር ሲወሰድ የነበረበት ዘመን አብቅቶ ዛሬ ዛሬ አብዛኛዋ ሴት ከፍቅር እና ትዳር ግንኙነቷ ከወንድ እኩል የወሲብ እርካታን ትፈልጋለች፡፡ የሴክስ ኤክስፐርቶች ይህን የእርሷን እርካታ ለማረጋገጥ የሚሻ ወንድ ሰውነቷን፣ ስሜቷ የሚቀሰቀስበትና ከእርካታም የሚያደርሷትን ቦታዎች ልቅም አድርጎ ማወቅ ይገባዋል ይላሉ፡፡ ሴቷን ብልት ቁልፍ የእርካታ ስፍራ ‹‹ጂስፖት› ማወቅ የሁሉም ወንድ የቤት ስራ መሆን አለበትም ይላሉ፡፡ ትክክለኛ ቦታውን በመጠቆም በኩል እንዲሁም ከነጭራሹ ስለመኖሩ የሚጠራጠሩ ባለሞያዎች ቢኖሩም በአመዛኙ ግን ጂ ስፖት ቁልፍ የሴቷ የእርካታ ማዕከል ተደርጎ ይወሰዳል፡፡ ይህ ስፍራ ጥንት በህንድና ቻይና ፅሑፎች በግምት ሲገለፅ የኖረ ቢሆንም በዘመናዊ የህክምና ሳይንስ የታወቀው በጀርመናዊው የማህፀን ስፔሻሊስት ዶ/ር ኸርነስት ግራፊንበርግ እንደነበር መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ በእርሱ በመታወቁም ይህ የሴቶች የእርካታ ማዕከል በአባቱ ስም የእንግሊዝኛ ፊደል ‹ጂ› በመውሰድ ‹ጂ ስፖት› ተባለ፡፡ እርሱ እንደሚገልፀው ጂስፖት የሚገኘው በሴት ብልት ፊት ግድግዳ በብልቷ የላይኛው ጫፍ እና በብልቷ ስንጥቅ መካከል ነው፡፡ ይህ ስፍራ በጣትም ሆነ በወንድ ብልት በሚነካካበት ወቅት በሚፈጠር የነርቮች መነቃቃት ወደ እርካታ ጫፍ ትስፈነጠራለች፡፡ የወንዱ ብልት ሲገባና ሲወጣም ይህን ስፍራ እንዲነካካ ካልሆነለትም በጣቱ ጭምር እንዲያነቃቃው የሴክስ ኤክስፐርቶቹ ይመክራሉ፡፡

ወሲብ በብርሃን ወይስ በጨለማ?
በርካቶች ወሲብ ሲፈፅሙ መብራት ያጠፋሉ፡፡ ከፊሎች ደግሞ መብራት በርቶ እርስ በእርስ እየተያዩ ሁለ ነገራቸውን እያደነቁ መፈፀሙ የተሻለ እርካታ ይሰጣቸዋል፡፡ በወሲብ ጉዳዮች የሜንስ ሄልዝ መፅሔትን የሚያማክሩት ክሊኒካል ሳይኮሎጂስት እንደሚሉት በብርሃን ወይም በመብራት ወሲብ መፈፀም ዝግጁ የሆኑ ጥንዶች በግንኙነታቸው ጥልቀትና ግልፅነት የሚተማመኑ፣ ተጣማጃቸውን የሚያፈቅሩ፣ የወሲብ አካላቶቻቸውን ብቻ ሳይሆን መላ አካላትና መንፈሳቸውም ጥምረት እንዲፈጠር የሚፈልጉና የሚፈቅዱ በመሆናቸው ሊደሰቱ ይገባል፡፡ ግን ደግሞ ጭለማው እና መብራቱ መጥፋቱም በመጥፎ ምልክትነት ሊወሰድ አይገባም፡፡ አንዳንድ ተፈጥሮ ይህን አይፈቅድም፡፡ ሁለታችሁ ብቻ ባላችሁበት ክፍል ሁልጊዜ መብራት እንዲጠፋ የምትፈልጉ ከሆነ ግን እስቲ አብርታችሁ ሞክሩት፡፡ ስለግንኙነታችሁ አንዳንድ ነገር ሊገልጥላችሁ ይችላል፤ ሌሎች በርካታ ጉዳዮችን ከወሲብ ህይወት ጋር ተያይዘው ሊነሱ እንደሚገባቸውና ምላሽ እንደሚፈልጉ እንረዳለን፡፡ በሌላ ጊዜ ርዕሰ ጉዳዩን ልናነሳው ቀጠሮ ይዘን የዛሬን እናብቃ፣ ሰላም!

ውጥረት በአንዋር መስጅድ –ቢቢኤን በሰበር ዜናው ዘገባ ሊንኩን ዳውንሎድ በማድረግ ያድምጡ

$
0
0

ውጥረት በአንዋር መስጅድ

እዚህ ይጫኑ ለማዳመጥ

 

 

በአንዋር መስጊድ ሰጋጆች ላይ ፖሊስ የማሽበር ተግባር እየፈጸመ ነዉ ሲሉ ምእምናንን ገለጹ ድምጻችን የሰማ ያወጣዉን ሰላማዊ የተቃዉሞ መርሃ ግብር ተከትሎ ዛሬ ጁመዓ ለመስገድ ወደ መስጊድ በሚያመሩ ሰጋጆች ላይ ፖሊስና ደህንነቶች በመቀናጀት ጸብ አጫሪ ተግባራትን መፈጽማቸዉን እማኞች ያስረዳሉ። በሴቶች በኩል ባደረጉትም መተናኮስ ግጭት አስነስተዉ በሴት ምእምናን ላይ ጭካኔ የተሞላበት ድብደባ መፈጸማቸዉን የጥቃቱ ሰላባ የሆኑ ወገኖች ገልጸዉልናል። ባሁን ሰዓት ፖሊሶች የ አንዋር መስጊድን በሮች በመዝጋት ምእምናንን ያገቱ ሲሆን በመስጊዱም ዙሪያ ከፍተኛ የጦር መሳሪያ የታጠቁ ፖሊሶች እየተርመሰመሱ መሆኑ ታዉቋል።

 

በመስጊዱ ዙሪያ የጭነት መኪናዎች የተደረደሩ ሲሆን፤ አፈሳ ለማድረግ አስበዉ ነዉ የሚል ግምት አለ። በመስጊዱ ቅጥር ግቢ የድምጽ ተቃዉሞ መደረጉን የገለጹልን ተሳታፊዎች ከመስጊዱ ዉጪ ስላለዉ እንቅስቃሴ እንደማያዉቁም ገልጸዉልናል። አንዋር ዉስጥ ያለዉ ምእምንም ተረጋግቶ ዱዓ (ጸሎት) እያደረገ መሆኑን ለማወቅ የቻልን ሲሆን ቀጣዩ የፖሊስ እርምጃ ምን ሊሆን እንደሚችል የታወቀ ነገር የለም። እኛ በ አካል ተገኝተን በደልና ጭቆናን ለመጋፈጥ ባድረግነዉ ጥረት እየተደበደብን እየታሰርን ነዉ፤ ብዚህ በተቀደሰዉ የረመዳን ወር በመላዉ አለም ያለዉ ወገናችን በዱዓ ይተባበረን ሲሉ በአንዋር መስጊድ በፖሊስ የታገቱት ምእምናን መልእክታቸዉን አስተላልፈዋል።

http://goo.gl/PVz4wa

http://goo.gl/PVz4wa

 

i2 i4 i3 demtschin yesema 3 demtschin yesema 3

የፕሬስ አፈናው በ”ሎሚ” መጽሔት ተጀመረ

$
0
0

ሐምሌ 7 ቀን 2006 ዓ.ም ከመንግስት በተላኩ ኃይሎች የ‹‹ሎሚ›› መጽሔት ቢሮ ‹‹ያለ ንግድ ፍቃድ›› በሚል ሠበብ ታሸገ፡፡ እነዚህ ከየትኛው ወገን እንደተላኩ ያልታወቁት ኃይሎች በቢሮ ውስጥ የነበሩትን የሂሳብ ሠነዶች ‹‹ይዘን እንሄዳለን፣ አትሄዱም›› በሚል በተፈጠረው እሰጥ አገባ ምክንያት ስልክ ደውለው ቁጥራቸው ከ20 ያላነሱ የታጠቁ የፌደራል ኃይሎችን በመጥራት እንዲሁም በድርጅቱ ውስጥ የሚገኙትን ንብረቶችና ወረቀቶችን ጨምሮ እንዳናወጣ በመከልከልና በማስፈራራት አስቀድመው ታዘው ይዘውት የመጡት ወረቀት “ያልታሰደ ንግድ ፍቃድ” የሚል ቢሆንም፣ ንግድ ፍቃዱ የታደሰበትን ማጋገጫ ሲመለከቱ ደግሞ ፊት ለፊታችን ወረቀቱን በመሠረዝ “ያለ ንግድ ፍቃድ” በሚል ጽፈው አሽገውታል፡፡ በወቅቱ ሐምሌ 12 ቀን 2006 ዓ.ም ለንባብ የምትበቃው ‹‹ሎሚ›› መጽሔት ወደ ማተሚያ ለመግባት በዝግጅት ላይ እንዳለች ይህ ችግር መፈጠሩ በሎሚ አባላቶች ላይ ግሬታን ቢፈጥርም፣ በተወሰደው ሕገ-ወጥ እርምጃ ሳንደናገጥ ከምንገባበት አንድ ቀን ዘግይተንም ቢሆን በተከፈለው ከፍተኛ መስዋዕትነት ማተሚያ ቤት ልናስገባ ችለናል፡፡ በወቅቱም ቢሮአችን እንደሚታሸግ ለምን አስቀድማችሁ በደብዳቤም ሆነ በስልክ አላሳወቃችሁንም ቢባሉም ‹‹የእናንተ ስፔሻል ኬዝ ነው፤ እኛ ከላይ ታዘን ነው›› የሚል ምላሽ ሠጥተዋል፡፡
lomi megazine
ከዚህም በተጨማሪ የሎሚ መጽሔት አጋር ሆና በሣምንት ሁለቴ ለንባብ የምትበቃው ‹‹አፍሮ ታይምስ›› ጋዜጣም ከወዲሁ ልትዘጋ እንደምትችል አሁን በእስር ላይ የሚገኙት የዞን 9 አባሎች ያውቁ እንደነበር መረጃዎች እየጠቆሙ ይገኛሉ፡፡ ይኸውም እነዚሁ ኃይሎች ከመጀመሪያው ቀን በተለየ ሁኔታ በበነጋታው ተደራጅተው በመምጣት “ሠነዶችን እንፈልጋለን” በሚል ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ በፌደራል ኃይሎች የታገዘ የ5 ሠዓታት ፍተሻ (ከብርበራ አይተናነስም) ከአካሄዱ በኋላ በቢሮ ውስጥ የሚገኙትን የሂሳብ ሠነዶች በሙሉ ሰብስበው ወስደዋል፡፡ ሆኖም ግን የምንፈልገው የሂሳብ ሠነዶችን ይበሉ እንጂ፣ በቢሮው ውስጥ የሚገኙትን በተለያዩ ጊዜ የታተሙ የሎሚ መጽሔቶች፣ የአፍሮ ታይምስ ጋዜጦችና በእጅ ጽሁፍ የተተየቡ ወረቀቶችን አንድ በአንድ ሲፈትሹ ተስተውሏል፡፡ ይሄ ሕገ-ወጥ እርምጃ የእኛ የፕሬስ ውጤቶች በሆኑት ሎሚ መጽሔትና አፍሮ ታይምስ ጋዜጣ ላይ ሆነ ተብሎ ለማጥቃት የታለመ መሆኑን የሚያመለክተው እነዚሁ ያልታወቁት ኃይሎች አስቀድመው ከመምጣታቸው በፊት ‹‹የአፍሮ ታይምስ ቢሮን ለማሸግ እየመጣን ነው›› በማለት የደወሉ ቢሆንም፣ ቢሮ ድረስ መጥተው የነበሩትን ሠነዶች ከወሰዱ በኋላም ከአለቆቻቸው ጋር በስልክ በመነጋገር ሊያሽጉበት ይዘውት መጥተው የነበረውን የማሸጊያ ወረቀት ሳያሽጉበት ተመልሰዋል፡፡

በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ከአንድ ወር በፊት ገዢው መንግስት ነፃውን ፕሬስ ጥላሸት በመቀባትና እርምጃ እንደሚወስድ (ሎሚ መጽሔትን ጨምሮ) በፈበረካቸው የተለያዩ ዶክመንተሪዎቹ ሲዝት የቆየ ሲሆን፣ አሁን አፈናውን በሎሚ መጽሔት ‹‹አሃዱ›› ብሎ ጀምሯል፡፡ ሎሚ መጽሔትም ሆነ አፍሮ ታይምስ ጋዜጣ እራሱ ገዢው መንግስት ባወጣው የፕሬስ አዋጅ መሠረት ሕግና ደንቡን ተከትለን ለኢትዮጵያ ሕዝብ አማራጭ ድምጽ በመሆን ተገቢውን መረጃ በወቅቱ እያደረስን ቢሆንም፣ ይህንን ያልወደደው ገዢው መንግስት ነፃ ፕሬሱን ከነአካቴው ለማጥፋት የተለያዩ ወጥመዶችን እያዘጋጀ መሆኑን አንባቢያን እንድታውቁልን እንፈልጋለን፡፡ ውድ አንባቢዎቻችንም ይሄንን ተገንዝባችሁ እስከመጨረሻው ድረስ የሚከፈለውን መስዋዕትነት ለመቀበል ከጎናችን እንድትቆሙ እናሳስባለን፡፡

በብጥብጥ የተቋጨው የጁምዓ ስግደት በአንዋር መስጊድ

$
0
0

ከኤልያስ ገብሩ (አዲስ አበባ)

መጽሐፍ ሳነብ ስለነበር በጣም አምሽቼ የተኛሁት፡፡ ጠዋት አረፍጄ ተነሳሁ፡፡ ቁርሴንም ሳልበላ ወደ አንዋር መስኪድ አመራሁ፡፡ ከፒያሣ ጀምሮ መንገድ የተዘጋጋ ስለነበረ፤ ከሦስት ሙስሊም ወንድሞቼ ጋር አንድ ላዳ ታክሲ ኮንትራት ይዘን አቆራረጥን ታላቁ አንዋር መስኪድ ደረስን፡፡ አካባቢው በሙስሊሙ ማኅበረሰብ ተሞልቷል፡፡ አብዛኛው ምንጣፍ እና ካኪ ወረቀት አንጥፈው ለጁምዓ ጸሎት እና ለስግደት ተቀምጠዋል – አስፋልቱን ጭምር ተጠቅመውበታል፡፡ ለመቀመጫ ቦታ ያላገኙት ቆመው ከመስኪዱ በአረብኛ ቋንቋ የሚነገረውን ምስጋና (ትምህርት) በጥሞና እየተለታተሉ ነው፡፡
በርከት ያሉ ፖሊሶች በመስኪዱ አቅርቢያ የተለያዩ ቦታዎች ላይ ቆመዋል – ረዥም ሽመል ይዘዋል! እኔም እንደ ጋዜጠኛ የሙስሊሞቹን ሰላማዊ ተቃውሞ ለመከታታል በማሰብ ነው አንዋር መስኪድ የተገኘሁት፡፡ ከመስኪዱ ራቅ ብዬ በመቆም ሁኔታውን መከታተል ጀመርኩ፡፡ ነገሮች ሰላማዊ ነበሩ፡፡ ከሥፍራው ከተገኘሁ ከአሥራ አምስት ደቂቃ በኋላ በመስኪዱ ዋና በር አካባቢ ወረቀቶች ወደ ላይ ይበተኑ ጀመር፡፡ ሦስት፣ አራት ቦታም ተመሳሳይ ወረቆች መበተናቸውን ቀጠሉ፡፡
demtschin yesema 2
ወዲያው፣ ከርቀት ከመስኪዱ በስተቀኝ በኩል ረብሻ ነገር ተመለከትኩ፡፡ ድንጋይ ሲወረውር እና ፖሊሶች ዱላ እንደያዙ ሲሯራጡም ማየት ችያለሁ፡፡

አፍታም ሳይቆይ አካባቢው በሰዎች ሩጫ፣ በረብሻና በፖሊሶች ማሳደድ ትርምስምሱ ወጣ፡፡ ብዙ ሰው በአካባቢው ወደሚገኙ የመኖሪያ እና የንግድ ቤቶች እየዘለለ መግባት ጀመረ፡፡ ነገሮች ለአፍታ ጋብ ያሉ ቢመስሉም ሁኔታው በድጋሚ ተቀሰቀሰ፡፡ በርካታ ፖሊሶች ወደ መኖሪያ ሰፈሮች እና ግቢዎች ውስጥ ዱላቸውን ይዘው በመግባት ሰዎች ማባረር፣ ማሳደድና በዱላ መማታት ጀመሩ፡፡

እኔም ከሦስት ፖሊሶች ጋር ከአንድ መኖሪያ ግቢ ውስጥ ተፋጥቼ ነበር፡፡ አንድ ዱላ ሲሰነዘርብኝ በእጄ ተንቀሳቃሽ ኮምፕዩተር (ላፕቶፕ) ይዤ ስለነበረ እሱ ከፍ በማድረግ ዱላው የላፕቶፕ ቦርሳዬ ላይ አረፈ፡፡ የቀኝ እጄ ጠቋሚ ጣት ግን ከበትሩ ማምለጥ ሳይቻለው ቀረ፡፡
… ከበሩ ፊት ለፊት የነበሩት ፖሊሶች ጥለውን ሄዱ፡፡ ወደ አሜሪካን ግቢ በጉራንጉር ውስጥ አልፌ ብሄድም ድብደባው እና ወከባው በዚህ አለ፡፡ ብዙ ወጣቶች ተደብድበው፣ ጭንቅላታቸው ተበረቃቅሶ ደም በደም ሆነው ተመልክቻለሁ፡፡
በዛሬው ዕለት ምስቅልቅሏ የወጣውን መርካቶ በቻልኩት አቅም ለማየት ችያለሁ፡፡ ሱቆች ተዘጋግተዋል፡፡ አንዋር መስኪድ በፌዴራል ፖሊስ ባልደረቦች እና መኪኖች ተከብቦ ነበር፡፡ አድማ በታኝ ፖሊሶችም በምዕራብ ሆቴል ቁልቁል በሰልፍ ሲያዘግሙ እና ሰፊዋ መርካቶ በፌዴራል ፖሊሶች ተወርራ ነበር፡፡
በጥቅሉ በዛሬው የአንዋር መስኪድ የጁምዓን ጸሎት ተከትሎ የተፈጠረው ሁኔታ አሳዛኝ እና ዘግናኝ ሆኖብኛል፡፡

ሽንፍላ –ተንሳፎ የሚፈላ! (ሥርጉተ ሥላሴ)

$
0
0

ከሥርጉተ ሥላሴ –  ሲዊዘርላንድ ዙሪክ

2

እያዘንኩ ብዕሬን አነሳሁ። የእስልምና ዕምነት ተከታይ ወገኖቻችን በፆማቸው እንኳን እንዲህ ሰላም ማጣታቸው የኢትዮጵያን መከራ ሃሞት ያደርገዋል። ፆም ላይ አኮ ምዕመኑ ከፈጣሪያቸው ጋር የሚገናኙበት የአደብ፤ የተደሞ፤ የጭምትነት ጊዜያቸው ነበር። ለዚህ ደግሞ ኢትዮጵያን አጋድሞ እያረዳት ያለው ወያኔ ሽንፍላ በመሆኑ አቅል አልፈጠረለትም። ኑሮትም አያውቅም። ወያኔ በሁሉም መሰፈርት ከላይ ተነሳፎ የሚፈላ ሽንፍላ ነው። እርምጃው ሸውሻዋ፤ ትንፋሹ ከልካላ። አቅሙ ጭድ – ራዕዩ ንፋስ – አካሉ ብክነት – ህሊናው አሲድ ነው። ከንቱ!

የወገኖቻችን ዬአካሎቻችን ናፍቀውና ጓጉተው በምልዕት በሚታደሙት ፆመ – ሮመዳን የዛሬ ዓመት አሳርን አብዝተው የተቀበሉበት ወቅት ነበር። ዓውዳመታቸውም በደም ነበር የተወራረደው። በዐለም ላይ ያሉ ህዝበ እስልምና እምነት ተከታይ ሁሉ በሰላም ፍስካቸውን ሲከውኑ፤ ደስ ብሏቸው የተሰጣቸውን ጸጋ ለነድያን ሲራሩ፤ ኢትዮጵያ ላይ ግን በአደባባይ ዬዕምነቱ አዛውንታት የተደበደቡበት፤ ህፃናት ሳይቀሩ የተገደሉበት የመከራ ድቅድቅ የጨለማ ቀን ነበር።  ቀንበር! የኢትዮጵያ እስልማ እምነት ተከታዮች ከሌሎች ሀገር ሙስሊሞች በፍጹም ሁኔታ የተለዬ ሥነ ምግባርና ጨዋነት ያላቸው ሲሆኑ፤ በፋሽስቱ ወያኔ ግን በጠላትነት ተፈርጀው፤ መተንፈሻ ቧንቧቸውን ዘግቶና አስሮ አሳራቸውን – ፍዳቸውን እንሆ ቀን እዬቆጠረ ያበላቸዋል። ዬኢትዮጵያ የእስልማ ዕምነት ተከታዮች ሀገራችን ኢትዮጵያ በጠራቻቸው ማናቸውም ጊዜያት ሁሉ በግንባር ቀደምትነት እናታቸው ከእነሱ የምትጠብቀውን ግዴታ ሲወጡ ኖረዋል። ታሪካችን- ነፃነታችን፣ የጥቁር ገድላችን ሁሉ በዚህ ቅመም የተቀመመ ነው። በጠቀራው በወያኔ ዘመን ደግሞ የኢትዮጵያ የእስልምና እምነት ተከታዮች መብታቸው እንዲህ ተረገጦ፤ እንዲህ ተቀጥቅጦ በሰላምና በሥርዓት ሊፈታ የሚገባው ጥያቄዎቻቸው እንዲህ ባላፈለጉትና ባላሰቡት መልክ አቅጣጫውን እንዲቀይር ረብሻ የፈጠረው ፋሽስቱ ወያኔ እንጂ እነሱ በፍጹም ሊሆኑ አይችሉም። ይህ የፋሽስቱ ባህሬ መገለጫ በመሆኑ ደም መዲናዋ ላይ ስለጠማው ለዚሁ አቅዶ የተነሳበት እንጂ እነሱ ለምዕተ ዓመቱ የሰላማዊ ትግል ሐዋርያ ናቸው። ሰላማዊ ትግል ስልቱና አፈጻጸሙ፤ የሰላማዊ ትግል መሪና ተመሪ፤ የሰላማዊ ትግል ትሩፋትና ፋይዳ በስክነት አምሮበት የተከወነው ታሪክ አንድ የገደል መጽሐፍ ብቻ ሳይሆን ተቋምም ነው። መጸሐፍ ተጽፎበት በት/ቤት ደረጃ ተማሪዎች ሊማሩት የሚገባ። ዜግነትንት አከበረ – ኢትዮጵያዊነትን ከበከበ – አብሮነት በተግባር ኳለ። አዎን! የፋሽስቱ ወያኔ መሰረታዊ የግለት መንገዱ  እንዲህ እሰኪ ላብራራው። ምሳሌ። ሀ/// ለ//// ሐ/// መ//// ሠ/// ቢኖሩ። የመጀመሪያ የጥቃቱ ሰለባ ሀ/// ከሆነ ወያኔ ለ – ለ/// ለ –  ሐ///  ለ – መ//// ለ – ሠ/// የተለዬ እንክብካቤና ግልብ ፍቅር ይለግሳል። ለ/// ሐ/// መ/// ሠ/// እውነት ይመስላቸውና በሀ/// ላይ ክንዳቸውን – ኃይላቸውን  - አቅማቸውን ከወያኔ ጋር አዳምረው ሀን//// ይከተክታሉ። ጦሩ ወደ እነሱ መዝመቱን ነገን ፈጽሞ አያቅዱትም። የወያኔ ዘመን ጠገብ እኩይ ረቂቅ መሰሪ ተግባሩ አንዱን ለማጥቃት ሌለውን በማስተባበር በሚያጠቃው ላይ ማናቸውንም ዬግለት ዘመቻ በመፈጸም ነው። ሽፍታው ወያኔ – ሀ/// ጥሩ ሁኖ መድቀቁን – ዳግም አገግሞ ሊነሳ አለመቻሉን ስያረጋግጥ ቀጣዩን  ዒላማ ለስለስ ብሎ እዬሰረሰረ ይጀምራል። በፋረሰው ሀ ላይ ሌላ ሸንኮፍ ሀን ይለብጣን ተለጣፊ ይፈጥራል። ይህም ቢሆን እዬተመነጠረ የሚወገድበት ቀን የሚጠብቅ የደለበ ሰንጋ ነው። የሆነ ሆኖ መተንፈሻ ቧንቧውን ከፍት አድርጎ እንዲያንቧርቅ ይፈቅድለታል – ለተለጣፊው። ከዚህ በኋላ ደግሞ ወደ ሌላው ጉልበታም የማንነት ተቋም ከዘራውን ይዞ ይዘምታል – አረሙ ወያኔ። ወደ ለ//// ይሄዳል። መጀመሪያ ለን/// ተርተር እያረገ አቅሙን ይሸረሽራል፤ እንደ ሥጋ ቀረምት በተመቸው መልክ ትናንሽ መደብ – ይሠራል። መደቡ በአፈር ሆነ በአሸዋ ይሆናል።። ከዛ በኋላ የለ/// አቅም መከፋፈሉን ሲያረጋግጥ ተለጣፊውን ሀን///  ከነተፈጥሯቸው ያሉትን  ሐ//// መ//// ሠ/// ያሰልፍና በእውነተኛው   ላይ ጦር ያውጃል። ሐ// መ/// ሠ/// ወደ እንሱ የሚመጣ ስለማይመስላቸው ጋሻ ጀግሬ ሆነው ጎሽ በርታ! እያሉ ሽፍታውን ይከብክቡና ዕውነተኛውን ለን//// በጠላትነት ፈርጀው አብረው ከጠላታቸው ጋር ይከተክቱታል። ለ/// የሚባል ነገር ድብዛው መጥፋቱን ሲያረጋግጥ ወያኔ ሌላ ተለጣፊ ለን/// ሞሽሮ የክህደት ካባ አለብሶ፤ ትንሽ እንደ ከብት አሞሌ መላሾ ሰጥቶ፤ ቀባብቶ ይጠፈጥፍና ያስጨፍረዋል። ለተወሰነች ጊዜ ያስዳንሰዋል። እሱ እራሱ ወያኔ እኮ  ቀፎውን አራት ኪሎ ልቡን ታላቋ ትግራይ ዶክተሪን ላይ አስቀምጦ በጅል አጃቢዎቹ ሸምቆ በቆረቆንዳ ተከታዮቹ ከትክት ብሎ ይስቃል። በዚህ መልክ አቅም ያለው ማናቸውም የማንነት ማማሳከሪያ ሰነድ ሆነ ውስጠት ሁሉ በዬተራ ደመራ የዶግ አመድ ይሆናል። ቲያትሩ ይህ ነው። ወያኔ አንድም የሚምረው ኢትዮጵያዊ ዘለላ አይኖርም ቁርጣችሁን እወቁ። የሚቀር የለም። ሆድ አደሩም ነገ ስሎ ወይንም ሰልቶ ወይንም ተስሎ በቀል ይጠብቀዋል። ልብሰህን እያወለቀ እርቃንህን ሲዘለዝልህ እያንዳንድህ ነገ ታገኘዋለህ። ብጣቂ ብናኝ እፍረት – ይሉኝታ ያልሰራለት የዘመኑ የአራዊት ተሰምሳሌት ቢኖር ወያኔ ብቻ ነው። የወያኔ ልብ በድንጋይ የተሰራ የበቀል ማሰሮ ነው። በዬትኛውም ዘመንን ትውልድ፤ በዬትኛውም ሁኔታ በህልም እንኳን የማይታሰብ ረግረግ ገደል ጉድጓድ ነው ወያኔ ማለት። የሚያረቃቸው አናቂ እሾኃማ ህግጋቶቹ የሚሞሽሩት ቋሳን ብቻ ነው። ነገር ግን በዚህ የቋሳ – ዝልል ጠማቂውም ጠጩም የነገ ተረኛ ተጠቂ መሆኑ ነው ሊመረምር የሚገባው ቁም ነገር። ሊፈተሽ የሚገባው እውነት። ሊታሰብበት የሚገባው አምክንዮ። ግን ህሊና ልብ ተግባራቸውን እንዲከውኑ ስንፈቅድ ብቻ። እማዝነው ለአፋሽ አጎንባሾች አሁንም ለወያኔ አንጣፊዎች ሆድ አደሮች ነው። ጅብ ዘመድ የለውም። እያንዳንዱ የወያኔ አባል ለህልውናው ተግቶ በተከታታይነት ይሠራል። በትጋት ሰይፉን በማናቸውም የወያኔ መንፈስን በሚጻረሩ ኃይሎች ላይ ይሰነዝራል። ትንሿን ነገር አይንቁም። የተሰባሰበ ፍላጎት ነው ያላቸው። ለማፍረስ ተልዕኮቻው ቃል ጠባቂዊች ናቸው። አጃቢው ደግሞ በማለቅለቅ ሸር ጉድ ይላል። ይህ ነው መፈታት ያለበት እንቆቅልሽ። የሰው ልጅ የቆመበትን መሬት ከመራመዱ በፊት አስተውሎ ሊያው ይገባል። መሬቱ ገደል ወይንስ ለጥ ያለ ሜዳ ስለመሆኑ? የወያኔ ማናቸውም እርምጃ በድልድይ ላይ ሳይሆን በገደል ላይ ነው። ድልድይ የሆኑት ደግሞ ከሌላ ብሄረሰብ የተወለዱ የባንዳ አበልጆች ናቸው። አሁን ደመ ነፍሱ  ጠ/ሚር ኃይለማርያም ደስ አለኝ አንዱ አሻንጉሊት ናቸው። ቀን ወያኔ የሚጠብቅላቸው። ነገ ወያኔ ያሾልካቸዋል። አዋርዶና ጎራርዶ። አሁንም የተሰበረ ቅል ታውቃላችሁን ወገኖቼ? አዎን ለወያኔ ሃርነት ትግራይ አቶ ሃይለማርያም ማለት የተሰበረ ቅል ማለት ናቸው። ነገ ከጉብራቸው ላይ ሆኖ ወያኔ ያስተንፍሳቸዋል። ደመንፈስነታቸውን በሚገባ የተገነዘበው ወያኔ ዕቃ – ዕቃ እዬተጫወተባቸው ነው። ዝልብ! በተከበሩ የጀግና ጽላት አቶ አንዳርጋቸው እስር ላይ አቶ ሃይለማርያም እኮ ድርጊቱን ወያኔ ከፈጸመው በኋላ እኛ እንደሰማነው ነው የሚሰሙት። አሁንም ያሉበትን አያውቁም። የአቶ አንዳርጋቸውን ማናቸውንም የተከደኑ የበቀል እርምጃዎች ሲፈጸሙ ከጠባቂዎቻቸው ጀምሮ ከትግራይ ልጅ ውጪ ፈጽሞ ሊሆን እንዳማይችል በጣም በእርግጠኝነት መናገር እችላላሁ። ለወያኔ ሃርነት ትግራይ የታማኝነት መለኪያው ዘር ነው። ትግራዊነት። ከዚህ ያመለጡት እንደ ጋዜጠኛ አብርሃም ደስታ ያሉት ደግሞ በእጥፍ የወያኔ ጭካኔ የሚጨቀጭቃቸው ለወያኔ የበቀሉ ቁርሾ ተጠቂዎች ናቸው። ስለምን? የወያኔን የናዚ መንገድ የተጸዬፉ ጀግኖቻችን ለእኛ  ስለሆኑ። በዚህ የባንዳ ዘመን የአሉላ ማሾ ስለሆኑ! ከመከራችን – ከችግሮቻችን – ከእንባችን ጋር ቤተኛ ስለሆኑ። የበቀልን የደም ጽዋ በአረመኔነት የሚያስፈጽሙ ባላሟሎች የፊት ለፊት ረድፈኞች የወያኔ ሃርነት አባላት ጭምር ናቸው። ነገም ለእያንዳንዱ የሚደርሰው የፈተና ጅረት ከዚህ አንጻር መፈተሽ አለበት።  ይህንን ያመረቀዘ – እጅግ የረቀቀ  - እጅግም በበቀል የበሰለ፤ እጅግም በበቀለ የተጠና፤ እጅግም በሳጥናኤላዊነት ግብር የተበከለ፤ የመርዝ ዘመን ከልብ ሆኖ መርምሮ፤ ቢያንስ አሁን ከ40 ዓመት ጥቃት በኋላ የጠላትን ጉርቦ አንቆ ደም ለማስተፋት መቁረጥ ያስፈልጋል። ቢያንስ ሥር ሰደዱ በቀል መነሻውና መድረሻውን በማስተዋል ማገናዘብ ያስፈልጋል። ንክኪ – ይሉኝታ – ዝምድና – ጋብቻ ይበቃ! ጥርት ብሎ የወጣው ጠላት የወያኔ ሃርነት ትግራይ ማኒፌስቶና አራማጁ ፖሊሲ ነው። ሌላው ጭራሮ ነው። አሁንም የወያኔ ገበርዲን ለባሽ የእስልምና ዕምነት ተከታዮች የዛሬ የአካላችሁ ጥቃት ምንጩን ዕወቁት። ተራችሁ እስኪደርስ ከመጠበቅ አሁኑኑ ወያኔን አራግፋችሁ ከተጎዱ – ከተጎሳቆሉ – ከግፉዕን ጋር ሁኑ! ሌሎቻችሁም ብትሆን ተረኝነታችሁ የጊዜ ጉዳይ ነው። ከዛ በፊት መስመርን አስተካካሎ በጠላት ላይ አቅምን መሰንዘር ይገባል እላለሁ። የወያኔ ሃርነት ትግራይ አባላት እኮ በጣም ነው የሌላውን ዝርያ የሚጸዬፉት። ምርጥ ዘሮች ናቸው። ደማቸው ተልይቶ የተፈጠረ¡ ማስጠጋትም አይፈልጉም። ከደማቸው ጋር እንዲቀራረብ አይሹም። እዬተጠላ የሚያጎነብስ – የሚያረብርብ ግልብ እንደ ሰው ለማዬት ይቀፋል። የሚያናድደኝ እኔ በግሌ ስጠላው የሚወደኝ ነው። አዎን የሌላ ዘር አባላትን የወያኔ አሽቃባጮችን የወያኔ ሃርነት ትግራይ አባላት እንዴት እንደሚጠሏችሁ ማን በነገራችሁ?! አስተውሉ! ፉከራ አይደለም ከልባችሁ ሁኑ ለማላት ነው። አረም እያለ በወገኑ የሚስነቀለው ወገን ጠላቱ ወያኔ ነገ የነቀላው ተባባሪ የሆነውን አረም ብሎ መነቀሉን ፈጽሞ አስቦት አያውቅም። ትዝም አይለውም። እያንዳንዱ የወያኔ ጋሻ ጀግሬ የታላቋ ትግራይ ራዕይ አስፈጻሚ ስለመሆኑ ምን አልባት ከእንቅልፉ ሲነቃ – ሀገር አልባ ሆኖ አፈር ለማኝ ሲሆን – ይገባው ይሆናል። እስካ ዛ ድረስ ግን የወያኔ አሲድ አዚም ተጠቂ ነው …. እራስን ማቃጠል ….. ማንደድ ….. ለትምህክት ሰለባነት፤ ዘር ለማጥፋት ተልዕኮ አባሪና ተባባሪ መሆን። ነገም በተረኝነት እራስን እረስቶ ወይ ፍቆ መጠበቅ። ሃፍረት! ይቋጭ። እጅግ የማከብራችሁ የሀገሬ ኢትዮጵያ ልጆች የእስልምና ዕምነት ወገኖቼ ሀዘኔ ከልብ፤ ዕንባዬም ከውስጥ ነው። እግዚአብሄር አምላክ ብርታትና ጥንካሬውን ይላክላችሁ። አሜን!   Radio Tasegaye or www.tsegaye.ethio.info aktuell sendung www.lora.ch.tsegaye   መራራውን ዘመን ጣፋጭ ለማደረግ ሁሉም በጠላቱ ላይ ይቁረጥ። እግዚአብሄር ይስጥልኝ።

“የእናቶች ምርቃት ለእኔ ህይወት ሆኖኛል”–ጆሲ ኢን ዘ ሃውስ (ቃለምልልስ)

$
0
0

jossy gebre
በራሱ የሙዚቃ ስልት በመጫወት ተወዳጅነት ለማትረፍ የቻለ ድምፃዊ ነው፡፡ እስከዛሬም በተለያዩ አገራት እየዞረ የሙዚቃ ስራዎችን በማቅረብ አድናቂዎቹን በማዝናናት ላይ ይገኛል፡፡ ከድምፃዊነቱ በተጨማሪ ከአንድ ዓመት በፊት ‹‹ጆሲ ኢን ዚ ሃውስ›› (Jossy in the house) የሚል የራሱን ቶክ ሾው የኢቢኤስ የቲቪ ጣቢያ ማቅረብ ከጀመረ በኋላ የፕሮግራሙ ይዘት የብዙ የኢቢኤስ ተመልካቾችን አይን ሊስብ የበቃ ባለሙያ ለመሆን ችሏል፡፡

በተለይ በዚህ ዓመት በትንሣኤ በዓል ላይ አቅርቦት በነበረው ፕሮግራሙ ላይ የቀድሞዋን ተወዳጅ ድምፃዊ ማንአልሞሽ ዲቦ ልጆች ገጥሟቸው በነበረው የህይወት ፈተና ዙሪያ በሰራው ዘጋቢ ፊልም ምክንያት ልቡ ያልተሰበረ የፕሮግራ ተከታታይ አልነበረም ማለት ይቻላል፡፡

ዛሬ መተሳሰብና መረዳዳት እንደሰማይ በራቀበት ዘመን ዮሴፍ (ጆሲ) በፕሮግራሙ ላይ እንዲህ የተረሱና የወገን ድጋፍ የሚያሻቸው ወገኖችን ከህዝቡ ጋር በማገናኘት ህይወታቸው እንዲለወጥ ያደረገው አስተዋፅኦ የተከታተሉ ተመልካቾች እደግ፣ ተመንደግ፣ ተባረክ በማለት ላይ ይገኛሉ፡፡ በዚህ ዙሪያ ከድምፃዊና የቶክ ሾው አዘጋ ዮሴፍ ገብሬ ጋርየተደረገው ቆይታን እንሆ።

ጥያቄ፡- አዲሱ አልበምህ ከምን ደረሰ?

ዮሴፍ፡- አልበሙ ከሞላ ጎደል አልቋል፡፡ ለፋሲካ ይደርሳል የሚል ሃሳብ ነበረን፡፡ አንዳንድ የስፖንሰር ሺፕና ሌሎች ጉዳዮች ነበሩን፡፡ እነዚያን ጉዳዮች ፋሲካ ከመድረሱ በፊት ነበር የጨረስነው፤ ከዚያ በኋላ ያሉት ነገሮች ለማስተካከል እየሞከርን ነው ያለነው፡፡ የጆሴ ሾው ምዕራፍ 3 ልጀምር ስለሆነና ትንሽ ለየት ባለ መልክ ይዘን ለመውጣት ስለፈለግን ትንሽን ድካሞች ነበሩበት፡፡ ያንን አስተካክለን አልበሙ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ለ1 ወር ከ15 ቀን ውስጥ ለአድማጭ ወደ መልቀቁ እንሄዳለን፡፡

ጥያቄ፡- አልበሙን ዜማ፣ ግጥምና ቅንብር ከእነማን ጋር ነበር የሰራኸው?

ዮሴፍ፡- በርካታ ሰዎች አሉበት፡፡ ይልማ ገ/አብ፣ ጌትሽ ማሞ፣ መለሰ ጌታሁንና ሙያው ላይ ይሰራሉ የሚባሉ የተለያዩ ሰዎች ጋር ነው የሰራሁት፡፡ ዜማውና በቅንብርም ሁሉም ጋር ነው የተሰራው ማለት ይቻላል፡፡

ጥያቄ፡- በዚህ አልበም ላይ የበፊቱን ስታይል ይዘህ ነው የመጣኸው ወይስ የተለየ?

ዮሴፍ፡- የበፊቱ እስታይል 6 ወይም 7 ዓመት በፊት ነው ይዤ የወጣሁት፡፡ ያኔ ደግሞ ወታት ነበርኩ፣ አሁን ወደ መብሰሉ ስለሆንኩ በዚያው ልክ በሰል ያሉ ዜማዎች ናቸው፡፡ ለበፊቱ አድናቂዎችም የሚሆኑና እንዲሁም አገራዊ ፋይዳ ያላቸው መልዕክት ማስተላለፍ የሚችሉ፣ ሀገርኛ ባህልን የሚያስተዋውቁ ሆነው የዕድሜዬን ያህል አልበሙም አድጎ ይወጣል፡፡

ጥያቄ፡- የአልበሙ ርዕስ ታውቋል?

ዮሴፍ፡- የተመረጡ ርዕሶች አሉት፡፡ ግን ሊወጣ ሲል ነው አንዱ ርዕስ የሚመረጠው፡፡

ጥያቄ፡- አልበሙን የገዛው ወይም የሚያከፋፍለው ማነው?

ዮሴፍ፡- ያንን ለጊዜው ምስጢር ላድርገውና ስፖንሰርሽፕ ከአንድ ካምፓኒ ጋር ጨርሰናል፡፡ ከዚ ባለፈ ግን የማከፋፈል ስራው እንዴት እንደሚሆን እያሰብንበት ስለሆነ ለጊዜው ይፋ አልሆነም፡፡

ጥያቄ፡- በአንተ እይታ አሁን እንደሚታወቀው የሙዚቃው ኢንዱስትሪ የገጠሙት ተግዳሮቶች ምንድን ናቸው?

ዮሴፍ፡- ምክንያቶቹ በጣም ብዙ ናቸው፡፡ ሁልጊዜ እንደሚባለው የኮፒራይት ያለመከበር ችግር ዋነኛው ነው፡፡ ነገር ግን የሙዚቃው ኢንዱስትሪ ሙሉ ለሙሉ እንዳልተቀዛቀዘ የሚያመላክቱ እንደ ብዙአየሁ አይነት ስራዎች አሉ፡፡ የብዙአየሁ አልበም በደንብ ተሰምቶ ነበር፡፡ አልፎ አልፎም ቢሆን ተሰርተው መቅረብ የሚችሉ አልበሞች አሉና ከእነኛ አንዱ የመሆን ዕድል አልመህ ያለውን ስራ በደንብ አጠንክረህ ሰርተህ ማቅረብ እንጂ ከሙያው ጨርሶ መራቅ አያስፈልግም፡፡ ምናልባት ከሚሰሙ ስራዎች መካከል አንዱ ትሆናለህ፡፡ አለበለዚያም ሪስኩን ወስደህ የሚመጣውን መቀበል ነው፡፡

ሌላው ግን ሁሉ ነገር ጨምሯል፣ ዛሬ አንድ ማኪያቶ አንዳንድ ቦታ 13 ብር ገብቷል፡፡ ከጓደኛህ ጋር ሆነህ ሁለት ማኪያቶ ከጠጣህ 26 ብር ነው፡፡ የእኛን ሲዲ በ25 ብር ለመግዛት እንደ ከባድ ይቆጠራል፡፡ አብዛኛው ሰው ለሙያው የሚሰጠው ቦታ ከደብል ማኪያቶ በታች ሆኗል፡፡ ለሙያው ክብር ብንሰጥ መልካም ነው፡፡ ድሮ እኛ ልጅ እያለን አዲስ ዘፈን ሲወጣ በየሙዚቃ ቤቱ ደጃፍ እንሰባሰብ ነበር፡፡ ሌላው ችግር ብዙ በመፅሔትና ጋዜጦች ላይ አላግባብ የአርቲስቱ ይሰጥ የነበረው ያልሆኑ ስም ማጥፋቶች ይወጡ ነበር፡፡

ወደ መፍትሄው ስንሄድ ያንን ገፅታ ለመቀየር አርቲስቱ ዝም ብሎ ከመዝፈን ባለፈ በማህበራዊ ስራዎች ውስጥ ራሱን ማሳተፍ አለበት፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ እኔም የጀመርኩት ነገር አለ፡፡ እኔ ብቻም ሳልሆን የሙያ ባልደረቦቼም በዚህ እንቅስቃሴ ውስጥ ተሳትፈው ያ ገፅታ ከተቀየረ በኋላ ህዝቡ ውስጥ የእኔነት ስሜት ፈጥሮ ገበያውን የመመለስ ነገር ይኖራል ብዬ አስባለሁ፡፡

ጥያቄ፡- አንተስ ለአዲሱ አልበም ከአድማጮችህ ምን ትጠብቃለህ?

ዮሴፍ፡- መልካም ነገሮችን እጠብቃለሁ፤ ጥሩ ነገሮች ይሆናሉ ብዬ አስባለሁ፡፡ ጥሩ ነገር ሰርቻለሁ፡፡ በተለያዩ ባለሙያዎች አሰምቼ በጣም ቀና የሆነ ምላሽ ነው ያገኘሁት፡፡ አድማጩ ሰምቶት ደግሞ የሚሰጠውን ምላሽ አብረን እናየዋለን፡፡

ጥያቄ፡- ‹‹ጆሊ ቶክ ሾው››ን እንዴት ጀመርከው?

ዮሴፍ፡- ት/ቤት ውስጥ እያለሁ ሚኒ ሚዲያ ውስጥ እሰራ ነበር፡፡ ከ9-12ተኛ ክፍል ስማር በጣም ታታሪ ጋዜጠኛ ስለነበርኩ ይመስለናል የሚኒ ሚዲያው ኃላፊ ጭምር ነበርኩኝ፡፡ 10ኛ ክፍል ላይ የህዝብ ግንኙነትና የተማሪዎች ተወካይ ተብዬ ከ3 መምህራን ጋር የሹመት ደብዳቤ ደርሶኛል፡፡

ጥያቄ፡- የት ነበር የምትማረው?

ዮሴፍ፡- ናዝሬት አዳማ አጠቃላይ 2ተኛ ደረጃ ነበር የምማረው፡፡ እዚያ ነበር የጋዜጠንነት ህይወት የጀመርኩት፡፡ በየእረፍቱ እየገባሁ አምስቱን ቀናት ሙዚቃ ማሰማት፣ ስነ ፅሑፍ ማቅረብና ፕሮግራም መምራት የመሳሰሉትን እሰራ ነበር፡፡

መርካቶ ከወንድሜ ጋር ቢዝነስ እየሰራሁ ኢትዮ-ኒውስ፣ ዘ ፕሬስ፣ አዲስ አድማስ ላይ ከ60 በላይ አርቲክሎችን ጽፌያለሁ፡፡ ስለዚህ ጋዜጠኝነት ከዚያ ጀምሮ ያደገ ሙያ ነው፡፡

ወደ ቶክሾው ስንመጣ ለምሳሌ ክዊን ላቲቫ ዘፋኝ ናት፡፡ የራሷ ቶክሾውም አላት፡፡ ሌሎችም እንደዚያው፡፡ እኔም የራሴ ቢኖረኝ ብዬ አልም ነበር፡፡ ኢቢኤስ ቲቪ ሲመጣ ፕሮግራሞች ይፈልግ ነበርር፡ ከባለቤቶቹ ጋር ተገናኝተን ለመጀመር አሰብኩኝ፡፡ በወቅቱ አልበሙ ትንሽ ያዝ ስላደረገና ልጀምር አልቻልኩም ነበር፡፡ ከቆይታዎች በኋላ ጀመርኩኝ፡፡

ጥያቄ፡- የፕሮግራሙ ፎርማት ምንድነው?

ዮሴፍ፡- ሲጀመር የታዋቂ ሰዎች የህይወት ሂደት ምን ይመስላል፣ አንድ ሰው ከመሬት ተነስቶ ታዋቂ አይሆንም፡፡ እነዚያ ታዋቂ ሰዎች እዚያ እውቅና ላይ የደረሱበት መንገድ እንዴት ነው? የሄዱበት መንገድ ለሌሎች መማሪያ መሆን በሚቻልበት መልኩ ማቅረብ ነው፡፡

ስለ አርቲስቶቹ የነበረን ገፅታ ጥሩ ስለነበር አርቲስት ከተጠቀምንበት በጣም ብዙ ነገር የማድረግ አቅም አለው፡፡ ብዙ ነገር ማድረግ ይችላል፡፡ የአርቲስቶችንና የታዋቂ ግለሰቦችን ያልታዩ ማንነቶችን እያሳዩ ያለውን መንፈስ ሊቀየር የሚችል መንፈስ ይዞ ነበር የተነሳው፡፡ ያንንም ስናደርግ የታመሙት፣ የተጎዱ፣ የተረሱትን፣ የትኛቸው ያሉት ብለን የመጠየቅ መንፈስ ይዘን መጣን፡፡ ከዚያም የበዓለት ዘመድ ጥየቃ የሚል ፕሮግራ ጀመርን፡፡ እያልን አሁን ያሉት ደረጃ ላይ ደርሷል፡፡

ፕሮግራ ኢትዮጵያዊ ጨዋነት የተላበሰ፣ ከቋንቋ አጠቃቀም ጀምሮ፣ ከአቀማመጥ፣ በእያንዳንዱ ነገር ከልጅ እስከ አዋቂ የሚከተለው የቤተሰብ ፕሮግራም እንደሆነ ነው እየሰራን ያለነው፡፡

ጥያቄ፡- ምን ያህል ፕሮግራሞች ሰራችሁ?

ዮሴፍ፡- እስካሁን ዓመቱን ሙሉ ስንሰራ ነበር፡፡ ሶስት ልዩ የበዓል ፕሮግራሞች ሰርተናል፡፡ ለአዲስ ዓመት፣ ለገና እና ለፋሲካ፣ ከእነሱ ሌላ በእርግጠኝነት ከ3-4 ፕሮግራሞች ካልሆነ በስተቀር ዓመቱን ሙሉ አዳዲስ ፕሮግራሞችን ነበር ስናቀርብ የነበረው፡፡ ስኬታማ ያደረገንም ፕሮግራም ያለመድገማችን ነው፡፡ ዓመቱን ሙሉ አዲስ ነገር እያሳየን ነው እዚህ የደረስነው፡፡

ጥያቄ፡- ሰዎችን መርዳት እና ማገዝ የፕሮራሙ አካል እንዴት ልታደርገው ቻልክ?

ዮሴፍ፡- ሰዎችን የማገዝና የመርዳት ነገር አሪፍ ፕሮግራም አዘጋጅ ስለሆንክ ወይም እውቀት ስላለህ ስለዚህ ብቻ ሳይሆን ልብ ይፈልጋል፡፡ አንተ ትንሽ በመስጠት የምትደሰት ከሆንክ ያንን ትሰራለህ፣ ለምሳሌ 5 ብር ኖሮህ 1 ብር በመስጠት የምትደሰት ከሆንክ እንደዚህ አይነት ፕሮግራም ትሰራለህ፡፡ እንደዚህ አይነት ልብ ከሌለህ የፈለገው ጎበዝ ጋዜጠኛ ብትሆን አትሰራውም፡፡ ይሄ የልብ ነገር ነው፡፡

ጥያቄ፡- የማንአልሞሽ ቤተሰቦች ህይወትን በፕሮግራም ላይ ለማቅረብ ምን አነሳሳህ?

ዮሴፍ፡- የእኔ ታላላቆች ወይም በዘመዶቼና ቤተሰቦቼ በተለይ በዳግማይ ትንሣኤ ወቅት ‹‹አክፋይ›› በሚባለው ስነ ስርዓት ውስኪ እና በግ ይዘው ይጠይቃሉ፡፡ ይሄ የክብር መገለጫ ነውና ያንን ሃሳብ ይዤ ነው ወደዚህ ያመጣሁት፡፡

ፕሮግራሙ ላይ በዓል ከተለመደው ፕሮግራም ውጭ የተለየ ነገር መሰራት አለበት አልኩኝ፡፡ ትዝ የሚልህ ከሆነ ለ2006 አዲስ ዓመት እነ ማንአልሞሽ ቤተሰቦች ቤት ሄጄ ነበር፡፡ በሁኔታው እኔ ብቻ ሳልሆን ተመልካቾችም በጣም ነበር ያዘኑት፡፡ ከዚያ በኋላ የአባባ ተስፋዬም የአርቲስት ዘሪቱ (እንቁጣጣሽ) ጉዳይም ነበር፡፡ ስለዚህ የማንአልሞሽ ልጆች ጥሩ ኑሮ የሚኖሩ፣ አሪፍ ት/ቤት ይማሩ የነበሩ፣ የአንዲት ታዋቂ ዘፋኝ ልጆች ነበሩ፡፡ አሁን ያሉበት ህይወታቸው ሲታይ በጣም ያሳዝናል፡፡ ቤታቸው በጣም ሩቅ ነው፣ በተለይ የማንአልሞሽ ዲቢ ሁለተኛ ልጅ ምስጢረ የተናገረችው ንግግር በጣም ልብ ይሰብር ነበር፡፡ እንደማንኛውም ሰው እኔም ልብ ተነክቶ ነበር፡፡ ከዚያ በኋላ የምችለውን ነገር ሁሉ አድርጌ ህይወታቸው የሚስተካከልበት ነገር ልፈልግ በማለት ተነሳሁ፡፡

ጥያቄ፡- ልጆቹ የት ነበሩ አሁን የት ደረሱ?

ዮሴፍ፡- የሚኖሩበት አካባቢ በጣም ሩቅ ነበር፡፡ የት/ቤት እና የመኖሪያ ቤት ችግር ነበረባቸው፡፡ አንደኛዋ ልጅ የጤና ችግር ነበረባት፡፡ ወንድየው ት/ቤት ቢገባም የመማሪያ ቁሳቁስ ችግር ነበረበት፡፡ ከዚህ አንፃር በቂ ነው ባይባልም ዛሬ ሩቅ ከሚባል ሰፈር ወጥተው እዘህ ግሎባል ሆቴል አካባቢ ከዋናው አስፋልት 150 ሜትር ገባ ብሎ ከሚገኝ ንፁህ ቤት ውስጥ ነው ያሉት፡፡ ቤቱ አንዳንድ ነገሮች ቢቀሩትም እየተስተካከለ ነው፡፡ አንዳንድ ሰዎችም እያገዙን ነው፡፡ አሁን ህይወታቸውን ከሞላ ጎደል በጣም ደስ በሚል ሁኔታ ተቀይሯል፡፡ እነሱም ህይወታችን እንደ አዲስ ጀመረ ብለው ነው ደስታቸውን የገለፁት፡፡

ጥያቄ፡- ፕሮግራሙ ከተላለፈ በኋላ ምን ምላሽ አገኘህ?

ዮሴፍ፡- ከፕሮግራሙ በኋላ ያለው ነገር ማመን ያቅትሃል፡፡ ፕሮግራ የተላለፈ ቀን ባህሬን ዝግጅት ነበረኝ፡፡ ሰው ሾውን ካየ በኋላ ነው ማታ ወደ የሙዚቃ ዝግጅቱን ለመከታተል የመጣው፡፡ የነበረው ምላሽ በታም የሚገርም ነበር፡፡ በነጋታው ሰኞ ፌስ ቡክ ስከፍት ከነበረው የፌስ ቡክ ፋን ከነበረው 94 ሺ ገደማ በአንድ ቀን ልዩነት ወደ 106 ሺ ከዚያም በተከታታይ ቀናት ከ120 ሺ በላይ ሆነ፡፡

እዚህም ስመጣ በየመንገዱ የሚያልፈኝ ሰው አልነበረም፡፡ እግዚአብሔር ይክበር ነው ያልኩት፡፡ ይሄ ብርታት ሆኖኝ እኔ ላይ የነበሩ ፕሮግራሞች የበለጠ እንድገፋበት ጉልበት ሆነኝ፣ የእናቶች ምርቃት ለእኔ ህይወት ሆኖኛል፣ ምርቃት በጣም ነው የምወደው፣ ያደኩበት ቤተሰብ እንደዚ ስላሳደገኝ ምርቃት በጣም ነው የምወደው፡፡ ከገንዘብ በላይ ምርቃት ደስ ይለኛል፡፡

አንዳንድ ሰዎች በቃል መግለፅ የማይችሉት ፍቅር አሳይተውኛል፡፡ የፍቅር አምላክ እግዚአብሔር ፍቅሩን በፍቅር ይመልስልኝ ነው የምለው፡፤ መልካም ነገር ስሰራ ለራሴ ብዬ ነው ያደረግኩት፡፡ እንደ ፕሮግራምም ስታየው ጥሩ ነገር እንደሆነ አውቃለሁ፡፡ ግን እንደዚህ ህይወትህ ግልብጥ ብሎ እስኪቄር ድረስ ይሆናል ብዬ በፍፁም አልጠበቅኩም ነበር፡፡ ይህን ክብር መልሼ ለእግዚአብሔር ነው የምሰጠው፡፡

ጥያቄ፡- ከዚህ በኋላ እኛም አግዘንህ እንርዳ ያሉ በጎ አድራጊዎች የሰጡ ካሉ?

ዮሴፍ፡- በቂ ነው ባይባልም የመጡ ሰዎች አሉ፡፡ የመጡትን እናመሰግናለን፡፡ አሁንም እጄ ላይ ያሉ ጥቂትም ቢሆኑ መታገዝ የሚገባቸው ሰዎች በእነዚህ ፕሮግራሞች ለመርዳት እንሞክራለን፡፡ እኔም አቅሜ በሚችለው ሁሉ ከማገኘው ነገር ላይ ለማገዝ እሞክራለሁ፡፡

ጥያቄ፡- የወደፊት እቅድህስ ምንድን ነው?

ዮሴፍ፡- ምዕራፍ 3 ባይ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ በተለያየ መልኩ የማህበረሰቡ ችግሮችን የሚቀርፉ ምክሮች ወይም ትምህርቶች፣ ምሳሌ መሆን የሚችሉ ፋይዳዎችን የፕሮግራማችን አካል ለማድረግና የበለጠ የፕሮግራሙን ይዘት አሳድጎ የማህበረሰቡ ጉዳዮች ላይ የሚሰሩ ነገሮች እንዲሆኑ አቅደናል፡፡

እስካሁን የሠራናቸውን ፕሮግራሞች በተመለከተ ተመልካች አስተያየት እንዲሰጡን እናደርጋለን፡፡ የምዕራፍ 3 ፕሮራሞች በአዲስ አቀራረብ፣ በጥራት ሰርተን ለእይታ እናበቃለን፡፡

ጥያቄ፡- የማን አልሞሽ ልጆች የወደፊት ህይወት የት ሊሆን እንደሚችል ይታወቃል?

ዮሴፍ፡- ልጆቹ ጎበዝ ተማሪዎች ናቸው፡፡ በትምህርታቸው ታታሪ ናቸው፡፡ አንደኛው ልጅ የትምህርት መሳሪያ ያስፈልጉት ነበር፡፡ ላፕቶፕ በስጦታ አግኝተንለታል፡፡ ከዚያ ውጭ ደግሞ በትምህርቱ ሂደት ውስጥ የሚያስፈልጉት ነገሮች እንደ ወንድም አግዘዋለሁ ብዬ አስባለሁ፡፡ ምስጢረም ትምህርቷን እስክትጨርስ የስኮላርሺፕ እድል አግኝታለች፡፡ ፍቅርተም (የማንአልሞሽ ወንድም ልጅ) ጤናዋ ተስተካክሎ ወደ ትምህርቷ የምትመለስበት ሁኔታ ተመቻችቶላታል፡፡ ቲጂም (የማንአልሞሽ እህት) ያቋረጠችው የዩኒቨርሲቲ ትምህርቷን ትቀጥላለች፡፡ መሰረታዊው ነገር እራሳቸውን ችለው ጥረው ነገ ለሰው የሚተርፉበት ህይወት ላይ ያቆምናቸው ይመስለኛል፡፡ ቀሪው ነገር የራሳቸው ጥረት ይሆናል ማለት ነው፡፡

ጥያቄ፡- ስኬታማ ነህ?

ዮሴፍ፡- እንደ ጀማሪ ጥሩ ነው፡፡ ግን የስኬት መጨረሻ ይሄ አይደለም፡፡ ገና ብዙ ይቀረኛል፡፡ እዚያ ደረጃ ላይ ከእግዚአብሔር ጋር እንደምደርስ እምነት አለኝ፡፡

ጥያቄ፡- ደስተኛ ነህ?

ዮሴፍ፡- የምፈልገውን ነገር ስለምሰራ፣ የምፈልገውን ስላደርግ በጣም ደስተኛ ነኝ፡፡ በህይወት ውስጥ ስትመላለስ ማድረግ የምፈልጋቸው ነገሮች አሉ፡፡ እኔ የምሰራው የህዝብ ስራ ነው፡፡ ከማህበረሰቡ የምታገኘው ምላሽ ደግሞ ጥሩ እየሆነ ሲመጣ ከዚህ በላይ ደስተኛነት የለም፡፡ ከራስህም አልፈህ በሰዎች ህይወት ውስጥ ምክንያት መሆንህ በራሱ ከማንም በላይ ደስተኛ ያደርግሃል፡፡

ጥያቄ፡- የምትጨምረው ነገር ካለ?

ዮሴፍ፡- በመጀመሪያ አክብራችሁ ስለጋበዛችሁኝ በጣም አመሰግናለሁ፡፡ እግዚአብሔር ይስጥልኝ፡፡ በአዲስ አልበም፣ በአዲስ የቲቪ ሾው ሲዝን ጥሩ ነገሮችን ይዘን ራሳችንን አሻሽለን የምናርመውን አርመን፣ የምናዳብረውን አዳብረን ለማህበረሰቡ ይጠቅማል በምንለውና ባደገ የስራ አካሄድ ወደ ህዝቡ እንመጣለን የሚል እምነት አለኝ፡፡

 

 

የአንድነት ፓርቲ የወላይታ ዞን አመራር በዞኑ አቃቤ ህግ ይግባኝ ዛሬ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ

$
0
0
10329778_አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) በደቡብ ክልል የወላይታ ዞን የፓርቲው አመራር የሆኑት ወ/ሪት ሀዲያ መሀመድ ዓሊ አንድነት ፓርቲ በወላይታ ለሚያደርገው ሕዝባዊ ስብሰባ በፓርቲው የተዘጋጀ ፍላየር ከፓርቲው አባሎች ጋር በመሆን ሲያሰራጩ በፖሊስ ተይዘው መታሰራቸው የሚታወስ ሲሆን ጥር 8 ቀን 2006 ዓ.ም በወላይታ ዞን ፍ/ቤት ቀርበው በ1000. 00 /አንድ ሺህ ብር/ ዋስትና መለቀቃቸውን ፍኖተ ነፃነት መዘገቧ ይታወሳል፡፡

በወላይታ ዞን ከ/ዐ/ህግ ይግባኝ ባይነት ጥር 8 ቀን የተሰጠው ውሳኔ ተከሳሿ ጥፋተኛ የተባሉበት ወንጀል በዓለም አቀፍ ሽብርተኞች አስተሳሰብ ሲቀሰቅሱ የነበሩትን እንዳለ በመውሰድ ከአስተሳሰብ ባለፈ መልኩ በተግባር በአገራችን ውስጥ ተቻችሎ የመኖር ሁኔታ የሚያቃውስና ወደ ጦርነት የሚያመራ ጽሑፍ በርካታ ገፆች ይዛ የተገኙትን ግለሰብ በጥፋታቸው ልክ መቅጣት ሲገባ በጣም ዝቅተኛና ተመጣጣኝ ያልሆነ ቅጣት በመሰጠቱ ቅር ብሎኛል በማለት የስር ፍርድ ቤቱን ውሳኔ በማሻሻል ከጥፋታቸው ጋር የሚመጣጠን ቅጣት እንዲሰጣቸው በማለት በወላይታ ከተማ ለሚያስችለው መደበኛ ተዘዋዋሪ ችሎት እንዲቀርቡ አዟል፡፡

በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የገዢው ፓርቲ ካድሬዎች የተቃዋሚ ፓርቲ አባሎችን በማስፈራራት፣ በመደብደብና በማሰር ሀሰተኛ ምስክር አዘጋጅቶ ክስ መመስረት ለማሸማቀቅ የሚደረገው ሙከራ አባላትን እያጠናከረ እንጂ እነሱ እንደሚያስቡት እንዳልሆነ ለፍኖተ ነፃነት የገለጹት የፓርቲው አባላት ወደፊትም ሰላማዊ ትግላችንን አጠናክረን እንቀጥላለን ሲሉ በአጽንኦት ገልጸዋል፡፡
10347545_

10408794_6

10505522_66


እስረኞቹ በሽብር መከሰሳቸውን አያውቁም (ጽዮን ግርማ)

$
0
0

Stion Girmaአንድ ዓመት ከአንድ ወር ኾኖታል። እስክንድር ነጋ ከታሰረ ከዐስራ ስምንት ወራት በኋላ ከባለቤቱ ከጋዜጠኛ ሰርካለም ፋሲል እና ከልጁ ከናፍቆት በተጨማሪ ለመጀመሪያ ጊዜ ሌላ ሰው እንዲጠይቀው በሰኔ የመጀመሪያ ወር ላይ በ2005 ዓ.ም. እንደተፈቀደለት፤ እስክንድርን ልጠይቀው ቃሊቲ ወደሚገኘው እስር ቤት አምርቼ ነበር።

ተገናኝተን ሰላምታ ከተለዋወጥን በኋላም እንዲህ አለኝ፤ ”ሽብርተኛ አይደለኹም፤ ሀገሬ በማንም እንድትሸበር አልፈልግም አልፈቅድምም እኔ የምፈልገው የሀገሬ ሕዝቦች በነጻነት የሚያስቡባትና የሚንቀሳቀሱባት ሰላማዊ ሀገር እንድትኾን ነው”፤ እስክንድር ”ሽብርተኛ” አይደለምና ከእስሩም በላይ ያንገበገበው ”አሸባሪ” መባሉ ነበር።

እስክንድር ”ጋዜጠኛ” ነው። እስክንድር ሲጽፍ ሀገሪቱ ላወጣችው ሕግ ራሱን አስገዝቶ፣ በሀገሪቱ ሕግ ማዕቀፍ ሥር ራሱን ገድቦ ነው። ይህም ኾኖ ግን ሲጽፍ ሕግ ተጥሶ አደጋ ሊደርስበት እንደሚችል፣ ሲጽፍ ሕግ ተጥሶ ሊታሰር እንደሚችል ያውቃል። ግን ደግሞ ቢታሰር በቀጫጭን መስመርም ቢኾን በሀገሪቱ ሕግ ተዳኝቶ ከእስር ሊለቀቅ እንደሚችል ያምን ነበር። በዚህ እምነቱም የመጣበትን ለመቀበል ተዘጋጅቶ ሀገሩ ላይ ቁጭ ብሎ ይጽፋል።
zone 9

ከመጻፍ እና ሐሳቡን በአደባባይ ከመግለጽ ውጭ ያሉት መንገዶች እስክንድርን አይመቹትም። እስክንድር ሐቀኛና ቀጥተኛ የኾነ አስተሳሰብ ያለው፤ ላመነበት ነገር የታመነ ንጹህ ኢትዮጵያዊ ነው። ምናልባት ይህን ”እስክንድርን” ለመረዳት እስክንድርን ማወቅ ሊጠይቅ ይችላል። እስክንድርን ያኔ ቃሊቲ ሳገኘው ሽብርተኛ አለመኾኑን ደጋግሞ ነገረኝ። ”እስክንድር ለማነው የምትነግረው ሽብርተኛ አለመኾንህን ከቀረበብህ ክስ ጋር አንዳችም ግንኙነት እንደሌለህ እኮ ዓለም ያውቃል፤ አሳሪዎችህም ይህን ጠንቅቀው ያውቃሉ” አልኩት። እርሱን ግን ያበሳጨው ከታሰረውም፣ ከተንገላታውና ከተፈረደበትም በላይ በውሸት የተወነጀለበት “ሽብርተኝነት’’ ነበር።

አሁንም ሽብርተኝነት

አሁን እስክንድር ከታሰረ ሁለት ዓመት ከሰባት ወር ኾኖታል በእርሱ የተጀመረው ጋዜጠኛን፣ ጸሐፊዎችንና መብቱን በአደባባይ የሚጠይቀውን ሁሉ ሰብስቦ ”ሽብርተኛ” ብሎ መክሰስ ዕለት በዕለት እየጨመረ የታሳሪዎቹን ቁጥር አበራክቷል። ላለፉት ሰማንያ ሦስት ቀናት በማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ታስረው የሚገኙትና በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አንደኛ ወንጀል ችሎት በጊዜ ቀጠሮ መዝገብ በቀጠሮ ሲመላለሱ የቆዩት ጋዜጠኛ ተስፋዓለም ወልደየስ፣ ጋዜጠኛ አስማማው ኃይለ ጊዮርጊስና፣ ጋዜጠኛ ኤዶም ካሳዬ፣ የሕግ መምሕርና የዞን ዘጠኝ ጦማሪ ዘለዓለም ክብረት፣ የዞን ጦማሪዎቹ ናትናኤል ፈለቀ እና አጥናፉ ብርሃኑ ለቅዳሜ ሐምሌ 5 ቀን የዞን ዘጠኝ ጦማሪዎቹ ማኅሌት ፋንታሁን፣ በፍቃዱ ኃይሉ እና አቤል ዋበላ በዚሁ በፈረደበት ”ሽብር” ተጠርጥረው የታሰሩ ናቸው።

የምርመራ መዝገቡ በሌሉበት መዝገቡ ተዘግቶ ከሕግ ውጪ በእስር የከረሙት እነዚህ እስረኞች ግንቦት ዘጠኝ በነበረው ቀጠሮ ቀን ፖሊስ ፍርድ ቤት ቀርቦ ተጠርጣሪዎችን በሽብር መጠርጠሩን ሲናገር ወጣቶቹ በድንጋጤ አንገታቸውን ሲሰብሩ ታይተው ነበር። የሚያስደነግጠው እስሩ አይደለም፤ ሕግን አስከብራለሁ የሚል አንድ ተቋም ወጣቶችን ሰብስቦ አስሮ ባልዋሉበት የሚያውል የፈጠራ ክስ ሲጭን መስማቱ ነው። ማንነቱን ጠንቅቆ የሚያውቅ ሰው እንዲህ ያለ የውሸት ክስ ሲቀርብበት የሚሰማውን ስሜት ለመገመት ያስቸግራል። እናም ወጣቶቹ በሽብር ተግባር አለመሳተፋቸውን ያውቃሉና የቱንም ያህል የኢሕአዴግን ባህሪ ጠንቅቀው ቢያውቁት ”በሽብር እንከሰሳለን” የሚል ቅንጣት ያህል ጥርጣሬ ሊኖራቸው አይችልም። ምናባት የመጨረሻውን ጣሪያ ቢገምቱ እነርሱን አስሮ ሌሎች ጸሐፊዎችን ለማስፈራራት የተነደፈ ስልት ይኾናል ከሚል ግምታዊ መላምት ”ምርጫው እስኪያልፍ ታስረን እንቆያለን” የሚለውን ነው።

ዛሬ ጠዋት ልደታ በሚገኘው ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛው ወንጀል ችሎት ሲቀርቡም፤ ከዚሁ ሐሳብ ሊኖራቸው እንደማይችል እገምታለሁ። ወጣቶቹ ከታሰሩ ጀምሮ ጉዳያቸውን ሲከታተሉ የቆዩት ጠበቃ፣ ቤተሰብና ሌሎች ሰዎች ከትናንት ጀምሮ ፍርድ ቤት ሊቀርቡ ይችላሉ በሚል ይቀርቡበታል በተባለው ፍርድ ቤት ግቢ ክትትል ሲያደርጉ ቢቆዩም ዛሬ ጠዋት ማንም ሰው ባልተገኘበት ዐቃቤ ሕግ የክስ መዝገብ ከፍቶባቸዋል። ነገር ግን የክስ ቻርጁ እንዲሰጣቸውና መቃወሚያ ካላቸው እንዲናገሩ ተጠይቀው ዘጠኙም እስረኞች ጠበቆቻቸው ባልተገኙበት ክሱ እንዲነበብላቸው እንደማይፈልጉ ያቀረቡት አቤቱታ ተቀባይነትን አግኝቶ ጠበቆቻቸው በተገኙበት ነገ ጠዋት እንዲቀርቡ ታዟል።

በሌላም በኩል ዛሬ ጠዋት እስረኞቹን ለመጠየቅ ማዕከላዊ ሄደው የነበሩ ቤተሰቦችና ጠያቂ ወዳጆች መግባት እንደማይችሉ ተነግሯቸው ተመልሰው ነበር። ከሰዓት በኋላም ሊጠይቋቸው በሄዱ ጊዜ ስለተከሰሱት ክስ የሚያውቁት ነገር አልነበረም። አብዛኞቹም (አብዛኞቹ ስል ስለ አስተያየታቸው መረጃ ያገኘኹት ማለቴ ነው) በሽብርተኝነት እንከሰሳለን የሚል እምነት አልነበራቸውም። ነገ የሚኾነውን ለማየት በይደር አቆይተው ቤተሰቦቻቸውን ተሰናብተው ወደ ማደሪያቸው ወደ እስር ቤት ተመልሰዋል።

የሽብርተኝነት ክሱ

የሪፖርትር ጋዜጣ ዘጋቢ ታምሩ ጽጌ ደግሞ ሰበር ዜና በሚል በጋዜጣው ድረ ገጽ ላይ፤ ሶልያና ሽመልስ (በሌለችበት)፣ በፍቃዱ ኃይሉ፣ ናትናኤል ፈለቀ፣ ማህሌት ፋንታሁን፣ አጥናፉ ብርሃኔ፣ ዘለዓለም ክብረት፣ አቤል ዋበላ፣ እንዲሁም ጋዜጠኞቹ አስማማው ኃይለ ጊዮርጊስ፣ ኤዶም ካሣዬና ተስፋለም ወልደየስ ላይ ዐቃቤ ሕግ በሽብርተኝነት ክስ መመስረቱን አስነብቦናል።

ዜናው እንደሚለው፤ ተጠርጣሪዎቹ በሕቡዕ በመደራጀት፣ የአጭርና የቅርብ ጊዜ ግብ በማቀድና በመንደፍ ከግንቦት 2004 ዓ.ም. ጀምሮ እጃቸው እስከተያዘበት ጊዜ ድረስ በፓርላማ ሽብርተኛ ተብለው ከተሰየሙት የግንቦት 7 እና የኦነግ ድርጅቶች መመርያና ሐሳብ ሲቀበሉ መቆየታቸው ተገልጿል።

ከተጠርጣሪዎቹ አንዷ የሆነችው ሶሊያና ሽመልስ የቡድኑ መሥራችና አስተባባሪ በመሆን ከ2004 እስከ 2006 ዓ.ም. መቆየቷና ከ2006 ዓ.ም. ጀምሮ በውጭ አገር አስተባባሪና የውጭ ግንኙነት ሆና ከመሥራቷም በተጨማሪ፣ ከግንቦት 7 ጋር ግንኙነት ለመፍጠር ተልዕኮ በመቀበል፣ አባላትን በማደራጀትና በመመልመል ስትሠራ መቆየቷን ክሱ ያስረዳል። የህቡዕ ቡድኑ ከ2004 እስከ 2006 ዓ.ም. ”ሴኩሪቲ ኢን ቦክስ” የተባለ ሥልጠና እንዲሠለጥንና እንዲደራጅ ስትመራ መቆየቷም በክሱ ተካቷል።

ሌላኛው ተጠርጣሪ በፍቃዱ ኃይሉ የአገር ውስጥ የሽብር ቡድንን በመምራትና የሥራ ክፍፍል በማድረግ፣ እንዲሁም ግብ በማስቀመጥና ስትራቴጂ በመንደፍ ከሽብርተኛ ኃይሎች ጋር ግንኙነት ሲፈጥር መቆየቱ በክሱ ተጠቅሷል።

የዓቃቤ ሕግ ክስ እንደሚያስረዳው ከሆነ ተጠርጣሪ ናትናኤል ፈለቀ ከ2004 ዓ.ም. ጀምሮ ካልተያዙ ግብረ አበሮቹ ጋር በመሆን የህቡዕ ድርጅቱ የአገር ውስጥ አስተባባሪ በመሆን በሥሩ ላሉት አባላት የሥራ ክፍፍል መመርያ በመስጠት፣ ከግንቦት 7 ጋር ግንኙነት በመፍጠር መመርያ ከመቀበሉ በተጨማሪ፣ ለአመፅ ተግባር የሚውል የተላከለትን 48,000 ብር ማከፋፈሉንም ክሱ ያብራራል።

ሌሎቹ ተጠርጣሪዎች በህቡዕ ድርጅቱ ውስጥ ከ2004 ዓ.ም. ጀምሮ መሥራችና አባል በመሆን የግንቦት 7 እና የኦነግን ስትራቴጂና ዕቅድ በመቀበል በውጭና በአገር ውስጥ ባሉ የቡድኑ አባላት ጋር ግንኙነት በመፍጠር፣ በውጭና በአገር ውስጥ ሥልጠና በመውሰድ፣ በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን የሽብርተኝነት ድርጊት ለመፈጸም በማቀድ፣ በመዘጋጀት፣ በማሰርና በማነሳሳት ወንጀል መከሰሳቸውን ዓቃቤ ሕግ ያቀረበው ክስ ያስረዳል።

በሁሉም ተጠርጣሪዎች ላይ ዓቃቤ ሕግ ያቀረበው ሁለተኛ ክስ እንደሚያስረዳው ተጠርጣሪዎቹ በወንጀሉና በሚያስገኘው ውጤት ተስማምተው በሕገ መንግሥት ሥርዓት የተቋቋመን መንግሥት በአመፅ፣ በሁከትና በብጥብጥ ለመለወጥ በማሰብ ከግንቦት 2004 ዓ.ም. እስከተያዙበት ዕለት ድረስ በህቡዕ ተደራጅተው፣ የሥራ ክፍፍል በመፍጠር፣ ሥልጠናዎችን በመውሰድ፣ አመፅ የሚቀሰቅሱ ጽሑፎችን በመበተን፣ የአመፅ ቡድኖችን በማደራጀት ሕገ መንግሥቱና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን በአመፅና በሁከት ለመለወጥ በመሞከር ወንጀል መከሰሳቸውን የዓቃቤ ሕግ ክስ ያስረዳል።

በመጨረሻ

ይህን ክስ የሰማ ማንም ሰው እነዚህ ወጣቶች ሽብርተኛ አለመኾናቸውን እንደሚረዳው ኹሉ፤ ከሳሻቸው ዐቃቤ ሕግም የውሸት ክስ እንደመሰረተባቸው ልቦናው ያውቀዋል። በተለይ ደግሞ ወጣቶቹን በቅርበት ለሚያውቃቸው ሰው በእነሱ ላይ እንዲህ ያለ ክስ ሲመሰረትባቸው ምን ዐይነት ስሜት እንደሚፈጥር ለመግለጽ ያስቸግራል። ጠንካራና ሀገር ወዳድ ወጣቶች በሽብርተኝነት ሲከሰሱ መስማት የሚፈጥረውን ቁጭት ከቃላትም በላይ ነው። ይህ ስሜት እነርሱ ላይ ሲደርስ ምን ሊኾን እንደሚችልም መገመት ያስቸግራል። እስክንድርን ከመታሰሩም በላይ ያስከፋው እንኳን ክፉ ሊያደርስባት ክፉ እንዳይነካት ቀን ከሌሊት የሚጸልይላትን የሚወዳትን ሀገሩን ገንዘብ ተቀብለህ ልትበጠብጣት ነው መባሉ ነበር።

”ዴሞክራሲያዊነቷ” የታወጀላት ሀገር ስትበደል ሕግ በሚፈቅድላቸው መሰረት ተቃውሟቸውን በጹሑፍ ያሰሙ፣ ለሀገሪቱ ሕግ ራሳቸውን አስገዝተው የጋዜጠኝነት ሥራን የሠሩ በሽብርተኞች እጅ የወደቁ እንጂ ”ሽብርተኛ” ያልኾኑት ወጣቶች ነገ ጠዋት በሽብርተኝነት መከሰሳቸውን ሲሰሙ ምን ይሉ ይኾን?

የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ታላቅ እህት በ24 ሰአታት አገር ለቀው እንዲወጡ ታዘዙ

$
0
0

ethsatየአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ታላቅ እህት በ24 ሰአታት አገር ለቀው እንዲወጡ ታዘዙለሰአታት በቁም እስር ላይ የነበሩት የታዋቂው ፖለቲከኛና የሰብአዊ መብት ታጋይ የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ታላቅ እህት ወ/ሮ ብዙአየሁ ጽጌ የወንድማቸውን ጉዳይ ለመከታተል በሚል ከ10 ቀናት በፊት ወደ ኢትዮጵያ ቢያመሩም፣ ከትናንት በስቲያ ደህንነት ጽ/ቤት ከተጠሩ በሁዋላ አገሪቱን በአስቸኳይ ለቀው እንዲወጡ ተነግሯቸዋል። በታዘዙበት ሰአት ለመመለስ እንደሚቸገሩ የተናገሩት ወ/ሮ ብዙአየሁ፣ የ 24 ሰአት ጊዜ የጊዜ ገደብ ከተሰጣቸው በሁዋላ ዛሬ ወደ አሜሪካ ተመልሰዋል። ወ/ሮ ብዙአየሁ የአቶ አንዳርጋቸውን ቤተሰቦች በመወከል ጉዳዩን ለመከታተል በሚል መሄዳቸውን ከቤተሰቦች የተገኘው መረጃ ያመለክታል። 


ኢህአዴግ የአቶ አንዳርጋቸው ጉዳይ የእግር እሳት እንደሆነበት የሚደርሱን መረጃዎች ያመለክታሉ። አቶ አንዳርጋቸው የህዝቡ የመነጋገሪያ አጀንዳ መሆናቸውና ከዚሁ ጋር ተያይዞ የግንቦት7 ዝናም ከምንጊዘውም በላይ በመጨመሩ የገዢውን ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮችን እያበሳጨ ነው። 


ይህ በእንዲህ እንዳለ ለአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ያላቸውን አክብሮት ለመግለጽ በአገር ውስጥም በውጭም የሚገኙ ኢትዮጵያውያን አሁንም በተከታታይ ስልኮችን እየደወሉ አስተያየቶችን እየሰጡ ነው። (ድምጽ ) በፐርዝ አውስትራሊያ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንም ከእንግሊዝ ቆንስላ ጽህፈት ቤት ፊት ለፊት የተቃውሞ ሰልፍ አድርገዋል። ኢትዮጵያውያኑ ለቆንስላው ላቀረቡት ጥያቄ የፐርዝ የእንግሊዝ የቆንስላ ሃላፊ፣ አገራቸው የአቶ አንዳርጋቸውን ጉዳይ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥታ እየተከታተለችው ነው የሚል መልስ ሰጥተዋል። 


በሱዳን የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ለኢሳት በላኩት ደብዳቤ የአቶ አንዳርጋቸው መታፈን ” ወያኔ ፍጹም አወሪነቱን ያሳየበት እና ዘላአለም የነጻነት ታጋዮችን ለማስፈራራት እና ከትግሎ ሜዳ ለማስውጣት የተጠቀመበት የትእቤት ስራ ነው። ” መሆኑን ያሳያል ካሉ በሁዋላ፣ የተወሰደው እርምጃ ህዝቡን ለትግል እንደሚያነሳሰው ገልጸዋል። 


በሌላ ዜና ደግሞ በሽብርተኝነት ወንጀል ተከሰው ማእከላዊ እስር ቤት እንዲታሰሩ የተደረጉት የአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ሀብታሙ አያሌው፣ የድርጅቱ የድርጅት ጉዳይ ምክትል ሃላፊ አቶ ዳንኤል ሽበሺ፣ የሰማያዊ ፓርቲ ምክትል የምክር ቤት ሰብሳቤ አቶ የሽዋስ አሰፋ እንዲሁም አረና ፓርቲ የስራ አስፈጻሚና ታዋቂ ጸሃፊ መምህር አብርሃ ደስታ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ ተብሎ ቢጠበቅም፣ ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ቀርተዋል። አንድነት ፓርቲ የተያዙት ሰዎች በ48 ሰአታት ውስጥ ፍርድ ቤት አለመቅረባቸውን በመግለጽ ክስ መስርቶ ነበር። ይሁን እንጅ ፍርድ ቤቱ የቀረበውን ክስ ውድቅ አድርጎታል።

 

የሰማያዊ ፓርቲዋ ወጣት ወይንሸት ሞላ ተፈንክታ፣ እጆቿ በፋሻ ጠቅልሎ፣ ሰውነቷ ዝሎ ፍርድ ቤት ቀረበች

$
0
0
(ፎቶው የተገኘው ከሰማያዊ ፓርቲ ነው)

(ፎቶው የተገኘው ከሰማያዊ ፓርቲ ነው)

(ዘ-ሐበሻ) በትናንትናው እለት የአንዋር መስጊድ አካባቢ የሕወሓት አስተዳደር በንጹሃን የእስልምና እምነት ተከታዮች ላይ አሰቃቂ እርምጃ እየወሰደ በሚገኝበት ወቅት መርካቶ አካባቢ ለሥራ ጉዳይ ሄዳ የነበረችው የሰማያዊ ፓርቲ የብሄራዊ ምክር ቤትና የሴቶች ጉዳይ አባል ወጣት ወይንሸት ሞላ በደህነንቶች ታፍና ከተወሰደች በኋላ ከፍተኛ ድብደባ ሲፈጸምባት ቆይቶ በዝግ ችሎት ቀርባ 14 ቀን የምርመራ ቀጠሮ ተጠየቀባት።

የነፃ አሳቢ ዜጎች መሰቃያ በሆነውና ከማዕከላዊ አጠገብ በሚገኘው የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን እስር ቤት ውስጥ የምትገኘው ወጣት ወይንሸት ማንም ሰው እንዳይጠይቃት በፖሊሶቹ መከለከሉ ለዘ-ሐበሻ የደረሰው መረጃ ያመለክታል።

ዛሬ ረፋዱ ላይ ሜክሲኮ አካባቢ ያለ ፍርድ ቤት የቀረብቸው ወጣት ወይንሸት ምንም እንኳ ችሎቱ በዝግ ቢደረግም ጭንቅላቷ ተፈንክቶ፣ ቀኝ እጇ በፋሻ ተጠቅልሎና አንገቷ ታስሮ የተመለከቷት ሲሆን የህግ አማካሪ እንዳታገኝም ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ መከልከሉን የዘ-ሐበሻ ምንጮች አረጋግጠዋል።

ጠ/ሚ ኃይለማርያም ደሳለኝ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ የሰጡት መግለጫ –ክፍል 1&&2 (ሐምሌ 11/2006 ዓ.ም)

ቋሚ ሲኖዶስ ለፓትርያርኩ ከፍተኛ ማስጠንቀቂያ ሰጠ

$
0
0
  • አስቸኳይ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ለመጥራት ታቅዶ ነበር፡፡
  • ፓትርያርኩ በአ/አበባ የአድባራት አለቆች ዝውውት ስሕተት መፈጸማቸውን አምነዋል፡፡
  • ‹‹የቤተክርስቲያንን ሥራ ይጎዳል በሚል እንጂ ተመራጩ ነገር ከእሳቸው ጋር(ፓትርያርኩ) ጋር መሥራት ማቆም ነበር፡፡›› የቋሚ ሲኖዶስ አባል የተናገሩት

1af06-patriarch-ab-mathias

  • ፓትርያርኩ ከአሁኑ መንገዳቸው ካልተጠቆማቸው ፤ ስህተታቸው ካልተነገራቸው ቤተክርስቲያኒቱን አደጋ ላይ ሊጥሏት ይችላሉ፡፡

አንድ አድርገን ሐምሌ 12 2006 ዓ.ም፡- 

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕግን የመተርጎምና የማስፈጸም መብት ያለው ቋሚ ሲኖዶስ ፤ ውሳኔዬን አክብረው አላስከበሩኝም ፤ ጠብቀው አላስጠበቁኝም ላላቸው ብጹዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ ከፍተኛ ማስጠንቀቂያ መስጠቱ ተገለጸ፡፡

ቋሚ ሲኖዶሱ ፓትርያርኩን ያስጠነቀቀው ፤ ባለፈው ሳምንት ረቡዕ ባካሔደው ሳምንታዊ ስብሰባ ወቅት ነው፡፡ የቤተክህነቱ የፋክት ምንጮች  እንደተናገሩት  የማስጠንቀቂያው መንስኤ ፤ አቡነ ማትያስ ምክራቸውን ለስልጣነ ፕትርክናቸው አይመጥኑም ከተባሉ ግለሰቦችና የቤተ ክርስቲያኒቱን ተቋማዊ ክብርና ነጻነት በመጋፋት ከሚወቀሱ አካላት ጋር ግንባር በመፍጠራቸው ፤ የቅዱስ ሲኖዶስን ውሳኔንና ልዕልና የሚጻረር ተግባር በየጊዜው በመፈጸማቸውና የቅዱስ ሲኖዶስ አባላቱን ክፉኛ በማሳሰቡ ነው፡፡

ከፍተኛ ገቢና አገልግሎት አቅም ባላቸው የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ገዳማትና አድባራት ሙስናንና ብልሹ አሰራርን በመዋጋት የተመሰገኑ አለቆችን ከሓላፊነት በማንሳት በተመለከተ አገልጋዩና ምዕመኑ ላቀረባቸው ጥያቄዎች ተገቢ ምላሽ ባልሰጡበት ኹኔታ ፤ የቋሚ ሲኖዶሱን ውሳኔ በመጻረር በአቡነ ማትያስ ትእዛዝ የተፈጸሙ ዝውውሮች ፤ ቋሚ ሲኖዶሱ ሳይወስንና የሚመለከታቸው አካላት ሳያውቁ ልዩ ጸሐፊያቸውን በማንሳት በሌላ መተካታቸውና የመሳሰሉት ጉዳዮች የቋሚ ሲኖዶሱ አባላት ከፓትርያርኩ ጋር በከፍተኛ ደረጃ የተጠየቁባቸው ዐበይት ነጥቦች እንደነበሩ ምንጮች አስታውቀዋል፡፡

በስብሰባው ላይ ለፓትርያርኩ ጥያቄ ያቀረቡት የቋሚ ሲኖዶስ አባላቱ ፤ ሳይገባቸውና ደረጃቸውን ሳይጠብቁ ‹ፓትርያርኩን ያማክራሉ› ያሏቸውን ግለሰቦች ስም በመጥቀስ ‹ከማን ጋር ነው የሚሰሩት? ማንን ነው  የሚሰሙት ? ከእኛ ጋር ይሰራሉ ወይስ አይሠሩም ?  › በሚል ጠንክረው እንደጠየቋቸው በምንጮቹ መረጃ ተመልቷል፡፡

አቡነ ማትያስ ስማቸው በሊቃነ ጳጳሳቱ ከተጠቀሱት ሰዎች ጋር የሚመክሩትና የሚሠሩት ‹አላማዬን ስለሚያስፈጽሙልኝ ነው›› በማለት አቋማቸውን ለመከላከል ቢሞክሩም ‹‹ አገልጋዩና ምዕመኑ የሚዘረፍበትና የሚሰቃይበት ዓላማ ሊኖርዎት አይችልም›› በሚል ጠንካራ ምላሽ እንደተሰጣቸውና በኹኔታውም መደንገጣቸው ተሰምቷል፡፡

st-urael-parish-head-row02‹‹የቤተ ክርስቲያንን ሥራ ይጎዳል በሚል እንጂ ተመራጩ ነገር ከእሳቸው ጋር(ፓትርያርኩ) ጋር መሥራት ማቆም ነበር፡፡›› ማለታቸውን የተጠቀሰላቸው አንድ የቋሚ ሲኖዶስ አባል ፤ ቋሚ ሲኖዶሱ ፓትርያርኩ በአጋጣሚው በብጹአን አባቶችና በወዳጆቻቸው ጭምር ቢመከሩም ሊያርሙት ስላፈቀዱትና ከሚገኙበት አሳሳቢ የአሰራር ኹኔታ አንጻር የቅዱስ ሲኖዶስ አስቸኳይና ድንገተኛ ጉባኤ ስብሰባ ለመጥራት የሚገደዱበት ደረጃ ላይ ደርሶ ነበር ማለታቸው ተነግሯል፡፡

አቡነ ማትያስ በቋሚ ሲኖዶስ አባላቱ በተጠየቁባቸው ጉዳዮች ስሕተት  መፈጸማቸውን አምነው መቀበላቸውና  ‹‹ከእኛ ጋር ይሰራሉ ወይስ አይሰሩም›› በሚል በቁርጥ ተጠይቀውበታል ለተባለው አዎንታዊ መልስ መስጠታቸው ፤ በቃለ ጉባኤውን የአስቸኳይ ስብሰባ ጥሪ ለጊዜው እንደገታው ጠቁመዋል፡፡ ቋሚ ሲኖዶሱ የቅዱስ ሲኖዶሱን ልዕልናና የቤተ ክርስቲያኒቱን መብትና ጥቅሞች ከመሰል ተግዳሮቶች የማስጠበቅ ርምጃውን በተተኪ ተለዋጭ አባላቱ አጠናክሮ እንደሚቀጥልበትም አስታውቀዋል፡፡

በተያያዘ ፓትርያርኩ የቅዱስ ሲኖዶሱን ውሳኔ በመጋፋት ስሕተት መፈጸማቸውን አምነው ከተቀበሏቸው ርምጃዎቻቸው መካከል ፤ ብልሹ አሰራርንና ሙስናን በመዋጋት የአገልጋዩና ምእመኑ ከፍተኛ ተቀባይነት ማትረፋቸው የሚነገርላቸው የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ደ/ጽጌ ቅ/ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ ዝውውር ዋንኛው ነው ተብሏል፡፡

Source- andadirgen.blogspot.com

Viewing all 8745 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>