Quantcast
Channel: ዘ-ሐበሻ – Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 8745 articles
Browse latest View live

ኤሊኖ ወይስ አውሮቦሮሶች?

$
0
0

ነጋ አባተ ከእስራኤል

ሰሞኑን ድኅረ- ገፆቻችንን ያጥለቀለቀው ዓቢይ ጉዳይ “ርሃብ” በሚባል ጨካኝ ምጣድ ላይ ተዘርግፈው እየተቆሉ ላሉ ወገኖቻችን የእንድረስ ጩኽትን የሚያስተጋባ የፌስ ቡክ “የክፉ ቀን” ዘመቻ ይመስለኛል። ምንም እንኳን ዕንቅስቃሴአችን ከጩኽት መዝለሉን እርግጠኛ ባልሆንም እኔም በጓደኞቼ አማካኝነት ተሳታፊ ሆኛለሁ። ቆይ ግን ጎበዝ! ቆም እንበል በእውነት ክፉ ቀን ወይስ ክፉ ጠላት? ኤሊኖ ወይስ አውሮቦሮሶች?። “አህያውን ሲፈሩ መደላድሉን” እንዳይሆን ብየ ነው።

hanger
የፌስ ቡኩን ዘመቻ የከፈቱት ወገኖቼ በንጉስ በአጤ ምኒልክ ዘመነ- መንግስት ከ1880-1884 የተከሰተውንና ወገናችንን በመሮ ጥርሱ አድቅቆ በትውልድ መካከል የማይደብስ ጠባሳ ጥሎብን ያለፈውን እነኝያ “ክፉ ቀን” በመባል የሚታወቁትን ድርብርብ አሰቃቂና ማቅ-ለበስ ዐመታት ስያሜ በመውሰድ የተጀመረ ዕንቅስቃሴ ይመስለኛል። አዎ! ከባድ ዓመታት ነበሩ ክፉ ቀን የሚል መጠሪያ ይዘውም በታሪክ መዝገብ ከነግሳንግሳቸው ሰፍረዋል። ሌላው ሳይቀር ወራሪው የጣሊያን ጦርም ስለርሃቡ መረጃው ስለነበረው ይህንን ክፉ አጋጣሚ ተጠቅሞበታል ይባላል። ግን ወዴት ወዴት“ዱባና ቅል አበቃቀሉ ለየቅል ይባል የለ” ያ ክፉ ቀን ወዴት የአሁኑ (?) ወዴት።
በዚያ ክፉ ቀን ህዝቡ በሞት የተሸነፉ ዘመዶቹን እየቀበረም እየጣለም እሱም ከሞት ጋር ግብግብ እየገጠመና በነፍስ ውጭ ነፍስ ግቢ እየተጣደፈ ከአራቱም የኢትዮጵያ አቅጣጫ ወደ ንጉሱ ዓጤ ምኒልክ ቤተ-መንግስት በጥቁር እንግዳነት ከአሸለቱ ቁመናዎቹ ጋር የተገጠገጠው ችግረኛ ቁጥር እንዲህ ቀላል የሚባል አልነበረም። በዘመኑ ይህንን የሰቆቃ ትዕይንት በዓጤ ምኒልክ ቦታ ሆኖ ላየው ይጨንቃል አቅል ይሰውራል። ይሁን እንጅ ንጉሱ ከእውነቱ ዘወር አላሉም ይልቁኑም በተሰበረ ልብ እንዳመጣጡ ተቀበሉት እንጅ። እዚህ ላይ ልብ ልንለው የሚገባን ነገር ምንድነው ህዝብ የሚያምነው መሪ ሲያገኝ የአባት ያክል ያምነዋል። ህመሙን ፤ ጭንቀቱን፤ የሆዱን ብሶት ሊያካፍለው ይፈልጋል። ከእግዚአብሄር ቀጥሎ ህዝብ ልቡን የሚጥለው በእርሱ ላይ ነዋ!። ዓጤ ምኒልክ ይህ ግርማ ሞገስ በህዝባቸው ላይ ነበራቸው እምየ የሚለውን ስም ያገኙትም በነኚህ የጭንቀት ቀናት ነው ይላሉ ብዙዎቹ። ለሩህሩህነታቸውና ለደግነታቸው ከህዝብ የተሰጠ የፍቅር ስጦታ!።
ደጉ ንጉስ በርሃብ አለንጋ እየተገረፈ ከባድማው የተሰደደውን መፃተኛ እንደዛሬዎቹ ጅቦችና ዘግቶ በላዎች፤ ሲቀጥልም የዘመናችን ኦውሮቦሮሶች፤ ክቡሩን የሰውን ልጅ በስቃይ ጅራፍ እይነረተ እመሬት ላይ ስለሚደባልቀው፤ ብሎም እነርሱ ራሳቸው ጎትተው ስላነገሱት የችጋር ጭራቅ መስማት እንደማይፈልጉት የአፍ ጉልበተኞች የመስቃን ቃል አልተናገሩም ፈሪሃ እግዚአብሄር አላ!። በእኔ የንግስና ዘመን ? የምን ርሃብ? ብለው የአካኪ ዘራፍ ምላስ አልወነጨፉም። ከዚህ ይልቅ በቅርባቸው ለነበሩት የሃይማኖት አባቶች እግዚአብሄር ምህረቱን ይልክ ዘንድ አጥብቀው እንዲለምኑ አሳስበዋቸው እሳቸው ግን ከዙፋናቸው ወርደው በእጃቸው የተገኘውን ያድሉ ገቡ። በአካልም በአስተሳሰብም የሸመገሉት ንጉስ ምኒልክ ያደረጉት ይህንን ነው።
የእኛዎቹ የዘመናችን አውሮቦሮሶች ግን በመለኮት እቅድ ምክኒያት ግንዘተ-ልቦና ሆኖባቸዋልና ክፉ ዘርን ይዘሩ ዘንድ በመርዝ በተሞሉ አለብላቢት ምላሶች ላይ በመቆማቸው፤ መልካም ዜና ከነርሱ ዘንድ ላይሰማ እነርሱ ለጸባዖት የራቁትን ያህል ለእነርሱም የራቀ ነው። ከዚያ ይልቅ በደደቢቱ ፍልስፍና ላይ የተመሰረተው፤ ነገር ግን ጠረጴዛ ላይ ተፈትኖ ለመውጣት በምሁራን መካከል ለመገኘት የሚቅለሰለሰውንና የዓይን-ዐፋሩን የኢኮኖሚክስ ስሌታቸው የ”ላም አለኝ በሰማይ ወተቷን የማላይ” ድምር በሁለት አሃዝ ተመንድገናል እያሉ እንደልጅ ይቧርቃሉ። ወደ ጉልምስና የማይመጣ የተፈጥሮ ህግጋትን የናደ ውበት አልባው ልጅነት! ድንክየነት! ይሏል እንግዲህ ይህ ነው። ለዚህ ነው ታላቁ መጽሓፍ መጽሓፍ ቅዱስ “ንጉሶቿ ህጻናት ለሆኑ ለዚያች ሃገር ወዮላት” የሚለን በልጅነት አዕምሮ መጡ በልጅነት አዕምሮ አረጁ በልጅነት አዕምሮ ወደ መቃብር መውረዱን ተያይዘውታል። የሸመገለና የተፈታ ልብማ እርቅ እርቅ ይሸተዋል፤ ሁሉን የሚሸከምበት ሰፊ የፍቅር ቋት ይኖረዋል፤ ማንም ያለጭንቀት የሚያርፍበት የመንፈስ ጥላ ይኖረዋል።
ምድራችን ለቁጥር የሚታክቱ ለስልጣናቸው የሚንሰፈሰፉ ነገስታትንና አምባገነኖችን አስተናግዳለች ይሁን እንጅ የህዝባቸውንና የሃገራቸውን ክብር የሚነካ ጉዳይ ሲገጥማቸው ግን ሁሉም ማለት ይቻላል ግንባር ቀደም ሆነው ዘብ በመቆም አያስነኬዎች ናቸው። ከእነዚህም መካከል አንዱ አጤ ምኒሊክ ናቸው። ንጉሱ ስልጣን ይገባኛል ብለው ታግለዋል ተራራ ወጥተው ወርደዋል። በህዝብ ላይ ርሃብ በመጣ ጊዜ ግን ህዝቤ፤ ድሆቼ ብለው ከልብ በተሰበረ መንፈስ አነቡ አንጅ የተሟገገውን ገላ አይተው ጎሽ የኔ ልጅ በእኔ የንግስና ዘመን ጠግበኸልኛል ብለው የሳሳውን ገላውን በፕሮፐጋንዳ ሳማ አልገሸለጡትም። እንደ ወንጭት የተጠረበውን ባቱን አይተው እንዲያ እንጅ ጠብደሃል በል በሚል የግፍ ቃል አንገቱን አስደፍተው ባይተዋር አላደረጉትም።
እዚህ ላይ እንደ ዋቢ የምጠቅሰውና “እውነት” የሚለው ክቡር ቃል ይገልጠዋል ብየ የማስበው የሶፎክለሱ ንጉስ ኤዲፕስ ትዝ አለኝ። በእርሱ ዘመን የአቴናን ምድር ያንቀጠቀጠ አንዳች የመቅሰፈት ምች ከተማዋን ያደቅቃት ያልማት ጀምሯል ። ህዝቡም በደረሰበት አደጋ ተደናግጦ፤ ተጎሳቁሎና እንደሞት ሰራዊት በአስፈሪ ድባብ ታጅቦ ወደ ቤተ መንግስቱ ይተም ይዟል። ይህን የተረዳው እውነተኛውና አስተዋዩ ንጉስም ህዝቡን ለመቀበል ከነሞገሱ ወደ ሰገነቱ ይወጣል። በሚያየው ነገር ግን ልቡ ይናጥ ይደማ ጀምሯል። አይን-ስውሩን ነቢይ የዚህ መቅሰፍት መንስኤና መፍትሄው ምን እንደሆነ እንዲነግረው አጥብቆ ይጠይቀዋል። ከብዙ የዙሪያ ንግግርና ከሽማግሌዎቹ መዘምራን ምክር በኋላ ንጉሱ እውነቱ ካልወጣ መፍትሄ የለም በሚል እሳቤና ፤ እውነትንና ፍትህን በአደባባይ ለማቆም ቆርጦ በመነሳቱ ምክኒያት አውጫጭኙ ከሯል። ሁሉም ክርክሩ በፈጠረው ግለት በፍርሃት እየተለበለበ ጥግጥጉን ይዟል ይባስ ብሎም ንጉሱ ችግሩና መፍትሄው ካልተገኘ ደግሞ በየደረጃው ያሉትን ሃላፊዎችን ተገቢውን ቅጣት እንደሚያከናንባቸው ዛተ። የነገሩ ስር ከግራ ከቀኝ እየተቧካ በስተመጨረሻው ፍርጥርጡ ወጣና ንጉሱ የመርገሙ ምክኒያት ሆኖ ተገኘ። እዚህ ላይ ነው የኤዲፐስ ማንነት የሚታየው ከተጠያቂነት ለመዳን ልሸፍን ላዳፍን፤ ስልጣኔን ንግስናየን ላስጠብቅ አላለም በራሱ ላይ አስቃቂውን እርምጃ በመውሰድ ስልጣኑን ለቆ ከምቹው ቤተ-መንግስት በመውጣት የእውነትንና የፍትህን ጫፍ አሳየ። እዚህ ላይ ከንጉሱ አስገራሚ ባህሪዎች ሁለት ዋና ዋና ቁምነገሮችን ልናይ እንችላለን በመጀመሪያ ከኔ የተሻለ ዕውቀት ሌሎች ይኖራቸዋል ብሎ ማሰብና ሌላው ደግሞ እውነት እንዳትዳፈን መድከሙ ናቸው። የአቀባበላቸው ዳኝነት እውነት መሆኑ ደግሞ ሁለቱን ንጉሶችን አመሳሰለብኝ።
የመጣጥፌ ዋና ዓላማ የዘመናችንን አውሮቦሮሶች ጥላሸት በመቀባት የፖለቲካ ትርፍ በማግኘት በጭንቅ ውስጥ ባሉ ወገኖቼ ህይወት ላይ ቁማር ለመጫወት እንዳልሆነና ሰውን ያክል ክቡር ፍጥረት እንደሰው በስፍራችን መገኘት አቅቶን በነገር ዘባተሎ እየተጠላለፍን በወደቅንበት በዚያ ቁመናውም ልኩም በማይታወቅ የውዝግባችን ቅርቃር በመሸንቆር ያስተሳሰብ ብልግና ውስጥ ራሴን ለመጣል በመፈለግም አይደለም።
ጥያቄየ ግን እውነቱ ወዴት ነው ? ነው። የርሃባችን አቢይ ምክኒያት ብዙዎቻችን እንዳልነው የቀኑ ክፋት ወይስ የገዥዎቻችን ክፋት ? ወይስ እነሱ እንዳሉት ኤሊኖ?። ኤሊኖ! አይ ቅጥፈት! ነገ ደግሞ የሆነ ችግር ቢፈጠር የዚህ ችግር ዋና ምክኒያት የህዳሴው ግንባታ ያመጣብን ጣጣ ነው ሊሉን ይችላሉ ምን ችግር አለው? ባፈጠጠ የህሊና ጥሰት ለሚኖር እጓለ ምዑት ሰፈር እኮ ውሸት አንድ ሙዚቃ ነው። ምነው ገዥዎቻችን ራሱን እንደሚበላ አውሬ አረመኔነቱን አጦዙትሳ? የዚህ በለየለት የህዝብ የጠላትነት ጫፍ ላይ መቆም ጉዳይስ የሂሳብ አወራረዱን ምን ያስመስለው ይሆን?። ደግሞስ በዚሀ በሰለጠነ ዘመን ሰለ ርሃብ ማውራት አይቀፍም ወይ?። ለገባውማ ይቀፋል ይጎፈንናል እንጅ! ለደደቢት ምሩቃን ግን ይህ የመርህ ጉዳይ ነውና እንደ ታላቅ ስኬት ይቆጠራል።
በአጤ ምኒልክ ዘመን ከደረሰብን ርሃብ አርባ ዓመት ቀደም ብሎ በድንች ላይ ጥገኛ በነበረው የአየርላንድ ህዝብ ላይ የደረሰው አሰቃቂ ርሃብ አየርላንዶቹ ታሪካቸውን በሃዘን የሚገልጡት ምዕራፋቸው ነው። “ The great famine” ተብሎ በተሰየመው በዚህ ርሃብ “The potato blight” የሚባል የድንች በሺታ ተከስቶ በሚሊዮን የሚቆጠር የአየር ላንድን ህዝብ አርግፏል አሰድዷል። ለዚያ ርሃብ በህዝቡ በኩል የቀረበው ምክኒያት በጊዜው በነበረው የአስተዳደር ብልሹነት ነው ሲል በሹሞቹ በኩል ግን የለም በጊዜው የተከሰተውን የድንች በሺታ ነው በሚል የተነሳው ውዝግብ ቀጥሎ ግን ሳይቋጭ እንደተንጠለጠለ የቀረ ጉዳይ ነው። ይሁን እንጅ ያ የርሃብ ምች እንደኛ እያሰለሰ አዚም ላይሆን ዳግመኛም ተከሰቶ የአየርላንድን ህዝብ ላይቀጥፍ አሸልቦ በአየርላንዳዊያን ግብዓ- ተመሬቱ ተፈጽሟል። የእኛ የርሃብ አዙሪት ግን እኛኑ ሊቀብረን እየሰለለን ይመስላል እውነተኛውን መንሰኤውንና መፍትሄውን ገና አላገኘነውማ!።
በዚህ በምኖርበት በእስራኤል ሃገር እስራኤላውያኖቹ የሚሉት እኔንም የሚገርመኝ ነገር አለ። ይኸውም መሬታቸው በአብዛኛው አሽዋማ ነው ግን ይሰሩበታል፤ የተስተካከለ የዝናብ ወቅት የላቸውም እነርሱ በዚያም ጥገኛ አይደሉም፤ የመሬታቸው የቆዳ ስፋት ትንሽ ነው ግን ከሚበላው የሚደፋው ይበልጣል። እነርሱም በኩራት የሚናገሩት እዚህ ላይ ነው። “በካርታ ላይ እስራኤል ብሎ ለመጻፍ ቦታ እንደሌለ ሁሉ መሬታችንም ጠባብ ናት ግን እስራኤል ሃገር ርሃብ የለም።” ይላሉ። ስለአንዱ የገጠር መሬታቸው ትንሽ ልንገራችሁ ትንሿ ገጠር יוטבטה’’ (ዮትባታ) ትባላለች በሃገሪቱ ደቡብ ምስራቃዊ ክፍል ትገኛለች። የዚህች መንደር መሬት አሽዋ ነው የመንደሯ ነዋሪዎች አርሰው ለማምረት ሲፈልጉ መጀመሪያ መሬቱን አጥበው ጨውን ማስወገድ አለባቸው ከዚያ በኋላ ነው ዘር የሚዘሩት ታዲያ የዚህች ትንሽ የገጠር መንደር ገበሬዎች በመላ እስራኤል የእርሻ ምርታቸውንና የወተት ተዋጾዖቻቸውን በማቅረብ ይታወቃሉ። እስኪ በስራኤል ዓይነት የእኛን ሁኔታ እንመልከት።
ወደ ጉዳያችን ስመለስ የዘንድሮው ጠኔ ገድ አልባ ሆኖና እንደ ቀላዋጭ እንግዳ ተሰልችቶ ነው ብቅ ያለው። በም ዕራባውያን በኩል ከሰራተኛው ህዝብ ከሚሰበሰበው ግብር እየተቆረሰ የሚላከው ገንዘብ የገዥዎቻችን የብልግና ጡንቻ ማፋፊያ እንደሆነና አውሮቦሮሶችም መናጢ ደፍቶ በላ ትዝቢዎች መሆናቸውን ከተገንዘቡ ውለው አድረዋል። እናም የሚራራው ልባቸው ተዘግቷል። እዚህ ላይ አንድ ገጠመኜን በምሳሌነት ላንሳ በስደት ከሃገሬ ከመውጣቴ በፊት በሙያየ ለአንድ መያድ (NGO) የ 30 ደቂቃ አጭር ተውኔት እንዳዘጋጅላቸው እየተነጋገርን ባለንበት ጊዜ ድርጅቱን በገንዘብ አቅርቦት የሚደግፍው የኖርዌይ ልዑካን ቡድን ለግምገማ ኢትዮጵያ ውስጥ የገቡበት ወቅት ነበር። ልዑኩ የስራ ግምገማውን ከጨረሰ በኋላ የደርሰበት ድምዳሜ ከሚንቀሳቀሱት ጣቢያዎች መካከል ሰባቱን መዝጋት መወሰኑን አሳወቀ ምክኒያቱስ ተብሎ ሲጠየቅ ልዑኩ የሰጠው አጭር መልስ “ የሃገራችሁ ባለጠጎች የሚይዟቸውን መኪኖች ስንመለከት በእኛ ሃገር በብዙ ሰዎች የማይያዙ ንብረቶች ናቸው እኛ ይህንን የኢትዮጵያ ፕሮጀክት ስናንቀሳቅስ ከድሆች እየለመንን ነው። በእኛ ግንዛቤ እነዚህ ባለጠጎቻችሁን በታግባቧቸው ይህን ፕሮጀክት ሊያንቀሳቅሱ ይችላሉ ብለን እናምናለን።” በማለት ውሳኔአቸውን አጸኑ።
አስተውሉ እነዚህ የኖርዌይ ሰዎች እየተናገሩ ያሉት ሰው ስለሚባለው ሰው ነው። ወገኖቹ በርሃብ ሲያልቁ ከአልጋው ወርዶ መሬት በመተኛት ያለውን ስለሚያካፍለው ሰው!። ከሚያማርጠው ውስኪ ወጣ ብሎ ለወገኖቹ አንድ ጣሳ ውሃ ማቅረብ ስለሚችል ሰው!። ልቦናውን እንደተሰረቀውና እንደ አለሌ የሜዳ አህያ ከሚፋንንበት ርቆና ከህሊናው ጋር ታርቆ ስለሚኖረው ሰው!። በነርሱ ሃገር የህሊና ግዴታ የሚባል ነገር አላ!። ይህማ ባይሆን ከሃገራቸው ኢትዮጵያ ድረስ ምን አንከራተታቸው?። እነዚህ እንግዶች የኢትዮጵያ ባለጠጎች ይሳተፉ ማለታቸው በሰው ውስጥ ሊኖር የሚገባውን ህሊና መሰረት አድርገው ነው። ህሊናውን በጣለ የወዲኒ መንጋ መካከል መኖራቸውን አላወቁም ነበር።
የወደቅንበትን እናስተውል የማዕድ በጀት አልባ ሆኖ በቆሻሻ ገንዳ ከውሻ እና ከአሞሮች ጋር እየተናጠቀ ጉሮሮውን ዘግቶ በሚያድርባት ሃገር ሌላው የሁለት ሚሊዮን ብር ይዞ ሲንፈላሰስ የህሊና ህግ ስለተጣሰ አይጠየቅም!። የፋራ ነው!። ውሃ ባአግባቡ ማቅረብ ባልቻለች ሃገር ውስጥ ጥቂቶች ውስኪ እንደ ውሃ የሚራጩባት የጉድ ሃገር መሆንዋን ስናይ የሰው ያለህ ብለን በባይተዋርነት እንንገደገዳለን። ምንጩ ሲመረመር ደግሞ አይን ያወጣ ሌብነት በሃገሪቱ በመንሰራፋቱ ነው። የወረድንበት የዝቅጠት ልክ ሲለካ አራዊትን እንኳን አልመጠነም ቀልለን ተገኜን። ምን ማለቴ ነው በቡድን የሚጓዝ የአራዊት መንጋ ዞጉን አይነካም ነውር ነው ህገ-አራዊት ወሰናይ አላቸውና! ቢጣሉ እንኳን አይገዳደሉም ። ኃይላቸውን ለሌላው ባላንጣቸው ይጠብቁታል እርስ በርሳቸው ቢገዳደሉ ለነገ የመኖር ዋስትና እንደሌላቸው ያውቁታል ይህ ዕውቀት አላቸው። ያደኑትን ተካፍለው ይበላሉ ከመሃከላቸው አውራ የተባለው እንኳን ኃላፊነት ተሰምቶት ከርሱ ለሚያንሱት ትቶላቸው ዘወር ይላል። ሃገራችን ግን በአውሮቦሮሶች ተውርራለች።
በግሪካውያን ጥንተ-እምነት ጥናት መሰረት አውሮቦሮስ የሚባል የድራጎን አይነት ነበር። ፕሌቶ ስለዚህ ዝርያ ሲናገር “ዝርያው ዓይን ስለሌለው አድኖ የሚበላውን አያይም ፤ ጆሮም ስለሌለው አዳምጦ የሚጎመርበት ፍጥረት የለም አፈርና ውኃ ሲልስ አድጎ በመጨረሻ ከጅራቱ በመጀመር ራሱን እየበላ ወደ ግብዓ- ተመሬቱ ያዘግማል። እናም ፕሌቶ ስለዚህ አሳዛኝ አውሬ ሲደመድም ራሱን የሚበላ ፍጥረት በዚህች ምድር ህልውና የለውም።’’ ይህን የድራጎን ዘር ከእኛዎቹ ወዲኒዎች ጋር ያመሳሰልኩበት ምክኒያትም የሚሰሙበት ጆሮ የሚያዩበት ዓይን ስለሌላቸው ነው። ያላቸው አፍ ብቻ ነው። ያ ነው ጉልበታቸው። ያንም ህዝባቸውን ለመብላት እየተጠቀሙበት ነው ሌላውን ለማሸነፍ አፍ ብቻውን ጉልበት አይሆንም ። ግን ርቀቱ እስከየት ነው?። ህዝብ በስደት ውኃና በርሃ እየበላው አንድ ወፍ የሞተ ያክል እንኳን የዚያን ህዝብ ዕልቂት ከቁብ አይቆጥሩትም የዕልቂቱ ምክኒያትም እነርሱ መሆናቸውን ባለመቀበል በክህደት ይደመድሙታል። ከዚህ በላይ የራስን ህዝብ ራስንም ከመብላት የበለጠ አረመኔነት በየትኛው ፍጥረት ይታያል?። 15 ሚሊዮን ህዝብ ተርቦ ውሸት ነው ብለው በፕሮፐጋንዳቸው ለማፈን ተሯሯጡ በርሃብ እየተጠበሰ ካለው ህዝብ ይልቅ የእንቧይ ካብ ስልጣናቸው በልጦባቸው በተራበው ህዝብ ላይ ቀለዱ። ይባስ ብለው በቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ በመበጀት ህወሐትና ብአዴን (EPRDF) ለአስረሽ ምቺውና ለሴሰኝነታቸው ማስገሪያ እየበተኑ ነው። የመጀመሪያ ደረጃ ዜጋ በሚል ፈሊጥም ፊታቸውን በአሞሌ ታጥበው ለአንድ ሰው 25 ሚሊዮን ብር ግምት ያለው ቤት እየሰሩ እንደሆነ ነግረውናል። እነዚህ ሰዎች የህዝብን ገንዘብ ሰርቀው የግላቸው ሲያደርጉ ኢሞራላውነትና ኢሰብዓዊነትን እያነገሱ ነው ይህንም ሲያደርጉ ህዝብንም ትውልድንም እየበሉ እንደሆነ አላወቁም ትውልድን ሲበሉ ራሳቸውን እየበሉ መሆኑንም ገና አልተገለጠላቸውም ። ከዚህ በላይ በህዝብ ላይ ንቀትና ጥላቻስ በምን ይገለጣል?። የናረ የህዝብ ጠላትነት!። ግን አንድ ነገር እመኛለሁ ደብቶ ከያዘን ከዚህ አዚም ስንወጣ! ያኔ ለጠላቶቻችን ዕድሜ የሰጠናቸው እኛ መሆናችን ሲገባን ራሳችንን እንወቅሳለን።
The enemy of the people (የህዝብ ጠላት) ከሚለው የኢብሰን ተውኔት ትንሽ ማለት ፈለግሁ። በኢብሰን ተውኔት ውስጥ ከህዝብ ጎን በቆመው ሃኪም እና በህዝብ ጠላትነት በቆመው የከተማዋ ከንቲባ ገጸ፟-ባህሪያት መካከል ያለውን ፍትጊያ በአጭሩ ስናይ ሃኪሙ የከተማዋን ነዋሪ እያረገፈው ያለውን ሞት ምክኒያት ለማወቅ ሲወድቅ ሲነሳ ይቆይና ምክኒያቱን ያገኘዋል ያም የከተማዋ ህዝብ የሚጠቀምበት ውኃ በመመረዙ ነው። ሃኪሙ መንስኤውን በማግኘቱ ትንሽ ተደስቶ ወደ መፍትሄው ሲዞር ደግሞ መፍትሄ ብሎ ያገኘው የከተማዋን ህዝብ ወደ ሌላ ስፍራ ማዞር ነው ይህንንም ለከተማዋ ከንቲባ ያማክረዋል። የከተማዋ ከንቲባም ለሃኪሙ ምክኒያቱንም መፍትሄውንም እንዳይናገር ይከለክለዋል ይባስ ብሎ በከተማዋ ከሚገኘው ታዋቂ የጋዜጣ ኤዲተር ጋር በመመሳጠር የፕሮፕጋንዳውን ስራ ያጧጡፉታል። ለህዝቡ ሞት ደንታ ያልሰጠው ከንቲባ የሃኪሙንም የመናገር መብቱን ከለከለው። የከንቲባው ዋና ዓላማ ህዝብ አይደለም ስልጣንን ማስጠበቅ ነው ለዚህም የፕሮፕጋንዳውን ስራ ማጧጧፍ ነው። ትንቅንቁ ይቀጥላል። የህዝብ ጠላት የሆኑ ሹሞች ጉዳያቸው ከስልጣናቸው ጋር እንጅ ከህዝብ ጋር አይደለም ይህ ስራቸው ደግሞ በህዝብ ጠላትነት ጎራ ያስፈርጃቸዋል።

 

ቸር ያገናኘን።

The post ኤሊኖ ወይስ አውሮቦሮሶች? appeared first on Zehabesha Amharic.


Hiber Radio: የሱዳን ዲፕሎማት አወዛጋቢው መሬት ቀድሞም የኢትዮጵያ ሳይሆን እኛ የሰጠናችሁ ነው ሲሉ ተናገሩ |የአማራ ክልል ባለስልጣናት ታጣቂዎችን እያደራጁ አስወጉን ሲሉ አወገዙ |የአባይ ወንዝን በተናጠል መገንባት እና መጠቀም ጦር ሊያማዝዝ ይችላል ተባለ |የጋሞ ብሄርን የሚያንቋሽሽ መጽሐፍ መውጣቱን ከተቃወሙ ውስጥ ዋና ዋና አስተባባሪ የተባሉት 69 ሰዎች በግንቦት ሰባት ስም ተወንጅለው መታሰራቸው ተገለጸ

$
0
0
ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

የህብር ሬዲዮ  ህዳር 19 ቀን 2008 ፕሮግራም

 <…በረሃቡ ሳቢያ ለተጎዳው ወገን ቅድሚያ መድረስ አለብን ገና ለገና መንግስት ገንዘብ ይበላል ተብሎ ሰው ለቤተሰቡ ሳይልክ አይቀርም ።ለነዚህ ወገኖቻችንም በአፋጣኝ መድረስ አለብን።ለተራበ ሰው ችግሩን ማን እንደፈጠረው ከምትነግረው መጀመሪያ ምግብ የሚያገኝበትን ሁኔታ ማድረግ ቀጥሎ ችግሩን ማን ፈጠረው በሚለው ላይ ተወያይቶ የፖለቲካ አቋም መውሰድና ያን ለመለወጥ መታገል ይቻላል…ለተጎዱት ለተራቡት በተለይ ለእናቶችና ህጻናት ከዚሁ ከአገር ውስጥ አልሚ ምግብ ገዝተን ከቀይ መስቀል ጋር አካባቢው ድረስ ሄደን ለመስጠት እቅድ አለን…>

ጋዜጠኛ አናኒያ ሶሪ የ<<ቤዛ እንሁን ለወገን>> ለረሃቡ የተጎዱትን ለመደገፍ  በአገር ቤት በበጎ ፈቃድ የተቋቋመው ኮሚቴ ቃል አቀባይ ከሰጠን ቃለ መጠይቅ የተወሰደ(ቀሪውን ያዳምጡት)

በመምህር ግርማ ላይ የቀረበው አዲስ የነፍስ ማጥፋት ወንጀል እና ከዚህ ቀደም የቀረቡት ውንጀላዎች ማስረጃ አልባ መሆን ጉዳዩን ወዴት አመራዋል( ልዩ ወቅታዊ ዘገባ)

<…ሃያ ሰባት ዓመት ቬጋስ ላይ ታክሲ ሳሽከረክር የሚያስከፋ ነገር ገጥሞኝ አያውቅም በእርግጥ አንድ ጊዜ አደጋ ደርሶብኝ ራሴን እስከመሳት ደርሼ በማግስቱ ነው የነቃሁት።አደጋ እንዴት እንደደረሰ ዛሬም ድረስ አላውቅም። የሚአስቀኝ ገጠመኝ ግን አለ…>  አቶ ገዛኘኘኝ ተፈራ ሃያ ሰባት ዓመት በቬጋስ ታክሲ አሽከርክረው በጡረታ ላይ ካሉበት አነጋግረናቸዋል(ክፍል አንድን ያዳምጡ)

የሩሲያና የቱርክ ወታደራዊና ዲፕሎማሲያዊ ፍጥጫ ወዴት ያመራል? (ልዩ ጥንቅር )

ሌሎችም 

ዜናዎቻችን

የሱዳን ዲፕሎማት አወዛጋቢው  መሬት ቀድሞም የኢትዮጵያ  ሳይሆን እኛ የሰጠናችሁ ነው ሲሉ   ተናገሩ 

የአማራ ክልል ባለስልጣናት ታጣቂዎችን እያደራጁ አስወጉን ሲሉ አወገዙ

የአባይ ወንዝን በተናጠል መገንባት እና መጠቀም ጦር ሊያማዝዝ ይችላል ተባለ

በኢትዮጵያ የተከሰተው ድርቅና ረሃብ አገሪቱንና ሕዝቧን እየተፈታተነ መሆኑ ተነገረ 

 የጋሞ ብሄርን የሚያንቋሽሽ መጽሐፍ መውጣቱን ከተቃወሙ ውስጥ ዋና ዋና አስተባባሪ የተባሉት 69 ሰዎች በግንቦት ሰባት ስም ተወንጅለው  መታሰራቸው ተገለጸ

የአርበኞች ግንቦት ሰባት ሊቀመንበር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ አውሮፓ ፓርላማ ድርቁን አስመልክቶ ለንግግር መጋበዝ ምዕራባውያን ለሚደረገው የትጥቅ ትግል ያላቸውን  ድጋፍ ያሳያል ተባለ

 

ሌሎችም ዜናዎች አሉ

The post Hiber Radio: የሱዳን ዲፕሎማት አወዛጋቢው መሬት ቀድሞም የኢትዮጵያ ሳይሆን እኛ የሰጠናችሁ ነው ሲሉ ተናገሩ | የአማራ ክልል ባለስልጣናት ታጣቂዎችን እያደራጁ አስወጉን ሲሉ አወገዙ | የአባይ ወንዝን በተናጠል መገንባት እና መጠቀም ጦር ሊያማዝዝ ይችላል ተባለ | የጋሞ ብሄርን የሚያንቋሽሽ መጽሐፍ መውጣቱን ከተቃወሙ ውስጥ ዋና ዋና አስተባባሪ የተባሉት 69 ሰዎች በግንቦት ሰባት ስም ተወንጅለው መታሰራቸው ተገለጸ appeared first on Zehabesha Amharic.

መምህር ግርማ በተጠረጠሩበት የግድያ ክስ የሟች አስከሬን በድጋሚ እንዲመረመር ታዘዘ

$
0
0

girma wendimu

(ዘ-ሐበሻ) መምህር ግርማ ወንድሙ ዛሬ ፍርድ ቤት ቀረቡ:: ፖሊስ በመምህሩ ላይ ከግድያ ወንጀል ጋር በተያያዘ ያቀረበው ክስ የተሰማ ሲሆን የተከሰሱበት አስከሬን ጉዳይንም ፍርድ ቤቱ ተመለከተው::

ፍርድ ቤቱ እንዳዘዘው መምህር ግርማ በተጠረጠሩበት የግድያ ክስ አስከሬኑ በድጋሚ እንዲመረመር ፍርድ ቤቱ ማዘዙን የዘ-ሐበሻ ምንጮች አስታውቀዋል::

የአስከሬን ምርመራው ተጠናቆም መምህር ግርማ ታህሳስ 4, 2008 ዓ.ም ፍርድ ቤት ተመልሰው እንዲቀርቡ ታዟል::

በመምህር ግርማ ላይ ከግድያ ወንጀል ጋር በተያያዘ ክስ ለመመስረት ዝግጅት እንዳለ ከአንድ ወር በፊት ዘ-ሐበሻ ቀድማ ምንጮቿን ጠቅሳ መዘገቧ አይዘነጋም::

The post መምህር ግርማ በተጠረጠሩበት የግድያ ክስ የሟች አስከሬን በድጋሚ እንዲመረመር ታዘዘ appeared first on Zehabesha Amharic.

በኦሮሚያ የተለያዩ ከተሞች የሕዝብ ተቃውሞ በአደባባይ ቀጥሏል * ፌደራል ፖሊስ በሃሮማያ ዩኒቨርስቲ 3 ተማሪዎችን ገደለ

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) የአዲስ አበባ አዲሱን ማስተር ፕላን በመቃወም በኦሮሚያ የተለያዩ ከተሞች የተቀሰቀሰው የሕዝብ ቁጣ አድማሱን እያሰፋ መሆኑ ተሰማ:: የዘ-ሐበሻ ምንጮች እንዳሉት ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ላይ የተጀመረውና ጎማ ጭምር በአደባባይ በማቃጠል የተስፋፋው የሕዝብ ቁጣ ትናንት እና ዛሬ በተለያዩ ከተሞች ቀጥሏል::

[ፍቶዎች: የህዝብ ቁጣ በተለያዩ የኦሮሚያ ከተሞች – ሃሮማያ. ነቀምቴ እና አምቦ]

haroma haromaya nekemt oromia oromia2 police

በሃሮማያ ዩኒቨርሲቲ በሰላማዊ መንገድ ቁጣቸውን ለመግለጽ የተሰበሰቡ ተማሪዎች ከፌደራል ፖሊስ በቆመጥና በጠመንጃ ሰደፍ የተደበደቡ መሆኑን በስፍራው የነበሩ የአይን እማኞች ለዘ-ሐበሻ ገልጸው በተፈጠረው ብጥብጥ ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ የ3 ሰዎች ሕይወት አልፏል ብለዋል::

በሃሮማያ ዩኒቨርሲቲ የተደረገው የተቃውሞ ሰልፍ ተማሪዎቹ በሰላማዊ መንገድ ምንም ዓይነት ንብረት ሳያወድሙ ጥያቄያቸውን ቢያቀርቡም ፖሊስ እርምጃ ሊወስድ ችሏል:: አሁንም በዩኒቨርሲቲው አካባቢ አለመረጋጋት እንዳለ ዘገባዎች ጠቁመዋል::

የኦሮሞ ተማሪዎች ቁጣ በአምቦ እንዲሁም በነቀምቴ ከተሞችም ቀጥሎ ተማሪዎቹ ድምፃቸውን ሲያሰሙ ውለዋል:: የአይን ዕማኞች ለዘ-ሐበሻ እንደገለጹት በአምቦ ፌደራል ፖሊስ መንገድ በመዝጋት የተማሪዎቹን ቁጣ ለማብረድ ጥረት ቢያደርግም ከከፍተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እስከ መለስተኛ ትምህርት ቤቶች የተማሪዎቹ ተቃውሞ ገንፍሎ ወጥቷል::

አዲሱን የአዲስ አበባን ማስተር ፕላን በመቃውም በሃገሪቱ የተለያዩ ከተሞች የሚደረገው ቁጣ አሁንም እየተስፋፋ ሲሆን ሕዝቡ ይህ ማስተር ፕላን እንዳይተገበር የሕይወት መስ ዋዕትነት ሳይቀር እንደሚከፍል በመዛት ላይ ይገኛል::

በአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ማስፋፋት ስም በሰበታ ከተማ ለመለስ ዜናዊ መንደር ግንባታ በከተማው ለባለሃብት የተሰጠ የመሬት ፈቃድን የሚያሳይ ምስጢራዊ ደብዳቤ ዘ-ሐበሻ ከቀናት በፊት ለሕዝብ ይፋ ማድረጓ ይታወሳል::

The post በኦሮሚያ የተለያዩ ከተሞች የሕዝብ ተቃውሞ በአደባባይ ቀጥሏል * ፌደራል ፖሊስ በሃሮማያ ዩኒቨርስቲ 3 ተማሪዎችን ገደለ appeared first on Zehabesha Amharic.

በሃሮማያ ዩኒቨርሲቲ በፌደራል ፖሊስ ተደብደበው ጉዳት ከደረሰባቸው ውስጥ የተወሰኑት ፎቶዎች ተለቀዋል (ይዘናቸዋል)

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) በሃሮማያ ዩኒቨርሲቲ በተነሳ የተማሪዎች ተቃውሞ የፌደራል ፖሊስ ግቢ ውስጥ ገብቶ በርካታ ተማሪዎችን በሰደፍ እና በዱላ ሲቀጠቅጥ ነበር:: ከፖሊስ ጥይትና ዱላ ለማምለጥ ከ3ኛ ፎቅ የዘለሉ ተማሪዎችም ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰባቸው ከስፍራው ለዘ-ሐበሻ የሚመጡ መረጃዎች ያስታውቃሉ:: እስከሁን ከ40 የማያንሱ ተማሪዎች ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰባቸው የአይን እማኞች ሲገልጹ የሞቱት ቁጥር እስካሁን የታወቀው 3 ብቻ ነው::

የአዲስ አበባን አዲሱን ማስተር ፕላን በመቃወም ተማሪዎቹ ባነሱት ተቃውሞ ከፍተኛ የሆነ መደናገጥ ውስጥ የገባው ሕወሓት የሚመራው መንግስት በፌደራል ፖሊሶች አማካኝነት ጉዳት ማድረሱን ቀጥሎበታል:: የተማሪዎቹ አመጽ በተለያዩ የሃገሪቱ ከተሞች እየተንሰራፋ ሲሆን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ውጥረቱ እንዳየለ ለዘ-ሐበሻ የሚደርሱ መረጃዎች አስታውቀዋል::

በሃሮማያ ዩኒቨርሲቲ ጉዳት የደረሰባቸው ተማሪዎች በሆስፒታል – ፎቶዎች ይመልከቱ

Haromaya 2 haromaya 3 Haromaya 4 Haromaya 5 Haromaya 6 Haromaya

The post በሃሮማያ ዩኒቨርሲቲ በፌደራል ፖሊስ ተደብደበው ጉዳት ከደረሰባቸው ውስጥ የተወሰኑት ፎቶዎች ተለቀዋል (ይዘናቸዋል) appeared first on Zehabesha Amharic.

“አጼ ኃይለ ሥላሴ በጣሊያን ጦርነት ወቅት ቢያዙ ኢትዮጵያ ነፃነቷ እየፈነፈነ ምናልባትም መጨረሻውም ድረስ አታገኘውም ነበር ለማለት እንችላለን።” –ልዑል ዶ/ር አስፋ ወሰን ዓሥራተ

$
0
0

ልዑል ዶ/ር አስፋወሰን ዓሥራተ፤ ስለ አዲሱ መጽሐፋቸው King of Kings: The Triumph and Tragedy of Emperor Haile Selassie I of Ethiopia ይናገራሉ። ልዑል ዶ/ር አስፋወሰን የእቴጌ መነን የልጅ ልጅ፣ የልዑል አሥራተ ካሣና የንግሥት ዙሪያሽ ወርቅ ገብረ እግዚአብሔር ልጅ ናቸው።

አጼ ኃይለ ሥላሴ በጣሊያን ጦርነት ወቅት ቢያዙ ኢትዮጵያ ነፃነቷ እየፈነፈነ ምናልባትም መጨረሻውም ድረስ አታገኘውም ነበር ለማለት እንችላለን።

–      ልዑል ዶ/ር አስፋ ወሰን ዓሥራተ


“አጼ ኃይለ ሥላሴ በጣሊያን ጦርነት ወቅት ቢያዙ ኢትዮጵያ ነፃነቷ እየፈነፈነ ምናልባትም መጨረሻውም ድረስ አታገኘውም ነበር ለማለት እንችላለን።”  – ልዑል ዶ/ር አስፋ ወሰን ዓሥራተ

The post “አጼ ኃይለ ሥላሴ በጣሊያን ጦርነት ወቅት ቢያዙ ኢትዮጵያ ነፃነቷ እየፈነፈነ ምናልባትም መጨረሻውም ድረስ አታገኘውም ነበር ለማለት እንችላለን።” – ልዑል ዶ/ር አስፋ ወሰን ዓሥራተ appeared first on Zehabesha Amharic.

የባሌ መደወላቡ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ሲቃወሙ አመሹ * በሃሮማያ ዩኒቨርስቲ የፌደራል ፖሊስ የፈጸመውን ግድያ አወገዙ

$
0
0
ፎቶ ከፋይል

ፎቶ ከፋይል

(ዘ-ሐበሻ) የአዲስ አበባን አዲሱን ማስተር ፕላን በመቃወም የተነሳው የሕዝብ ቁጣ ወደ ተለያዩ ከተሞች እየተዛመተ ሲሆን የመንግስት ሚድያዎች በበኩላቸው ምንም እንዳልተፈጠረ መረጃዎቹን በማፈን ስለ እንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ እያወሩ ይገኛሉ::

በሃሮማያ ዪኒቨርሲቲ የተማሪዎቹን ሰላማዊ ጥያቄ ፖሊስ በኃይል ለመበተን ባደረገው ጥረት ሰዎች መሞታቸውና መቁሰላቸውን ዘ-ሐበሻ ቀደም ብላ መዘገቧ የሚታወስ ሲሆን ይህን ተከትሎም በባሌ መደወላቡ ዩኒቨርሲቲ አመሻሹ ላይ ተማሪዎች ቁጣቸውን መግለጻቸው ተሰምቷል::

በመደወላቡ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎቹ ቁጣቸውን ከገለጹ በኋላ ወደ መኝታቸው እንደሄዱ የገለጹት ምንጮቻችን በተለይ በሃሮማያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ላይ በመንግስት ኃይሎች የተወሰደውን እርምጃ ተቃውመዋል::

መደወላቡ ዩኒቨርሲቲ በከፍተኛ ውጥረት ውስጥ እንደሚገኝ የሚገልጹት ምንጮች አካባቢው በፖሊስ መወረሩም ተዘግቧል::

The post የባሌ መደወላቡ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ሲቃወሙ አመሹ * በሃሮማያ ዩኒቨርስቲ የፌደራል ፖሊስ የፈጸመውን ግድያ አወገዙ appeared first on Zehabesha Amharic.

የኢትዮጵያዊቷ “ባለህ ነገር አመስግን”ባለች ከቀናት በኋላ በሜሪላንድ ሕይወቷ አለፈ

$
0
0

 

 

ethiopia yesew lik

(አድማስ ራድዮ) ሲልቨር ስፕሪንግ ሜሪላንድ ነዋሪ የሆነችው የሰውልክ እንዲህ ነው፣ ህይወቷ ያለፈው ትናንት ሰኞ፣ ኖቬምበር 30 ቀን ሌሊት 3 ሰአት ላይ ነው። የዜና አውታሮች እንደዘገቡት፣ እሷና አብሯት ያለ ሰው ቼሪ ሂል የተባለ መንገድ መታጠፊያ ላይ ሲደርሱ፣ ትልቅ የፖስታ ቤት ትራክ ከሌላ አቅጣጫ በመምጣቱ ሊጋጩና ትራኩም የነ የሰውልክ ኢንፊኒቲ መኪና ላይ በመውደቁ ነው። አብሯት የነበረውና ስሙ ያልተገለጸው ወጣት ፣ እንዲሁም የፖስታ ቤቱ ትራክ ሾፌር ተጎድተው ሆስፒታል ናቸው።

የሰውልክ እንዲህነው፣ ባለፈው ዓመት ከሜሪላንድ ዩኒቨርሲቲ በጤና ትምህርት ተመራቂ ነበረች። ከመሞቷ ከሁለት ቀን በፊት የመጨረሻዋ የነበረው የፌስ ቡክ ገጿ ጽሁፍ “ባለህ ሁሉ አመስግን፣ መልካም የምስጋና ቀን” የሚል ነበር።

በደጀን ከተማ የመጀመሪያው ዘመናዊ ሆቴል ባለቤት ልጅ ናት:: የሰውልክ እንዲህነው ትዝአለ የ24 ዓመት ወጣትና ከ6 ወር በፊት ከሜሪላንድ ዩኒቨርስቲ በዲግሪ የተመረቀች ነበረች።

በዚህች ወጣት ሕይወት ማለፍ የተሰማቸውን ሃዘን ከገለጹት መካከል አንዱ አርቲስት መስፍን በቀለ ይገኝበታል:: መስፍን በፌስቡክ ገጹ የሚከተለውን መል ዕክት አስተላልፏል::

እኔ ይህንን አምኖ ለመቀበል አልቻልኩም። የሰው ልክ እንደ ስምሽ የሰዋችን ልክ የምታውቂ፣ አንድ ሰው ህይወቱ ሲያልፍ መባል ስላለበት ብቻ ሳይሆን መናገር የምፈልገው እንደው ስላንቺ እንደ ሰው ከብዙዎቹ በጥቂቱ…..በህይወት በዚህች ምድር ላይ በቆይሽባቸው ዘመኖችም ሆነ ከኔም ጋር እስከተዋወቅንባቸው ዓመታት ድረስ በጣም የሚደንቅ እና እጅግ የሚወደድ በሀሪ ያላትና፣ሰው የምትወድ፣ የምታከብር፣ እጅግ ሲበዛ ሀይማኖተኛ፣ቤተሰቦን አክባሪ፣እንዲህ ነው ተብሎ ተነግሮ የማያልቅ ዓላማና በ ዓይን የሚታይ ተስፍ ያለት፣ለ ጎደኝነት ትልቅ ቦታ የምትሰጥ፣ ከፀብ ይልቅ ፍቅርን የምታስቀድም፣እንደ ስሟ የኖረች፣” የሰውልክ” ትናንትን ያልጥገበች፣መሽቶ እሲኪነጋ ብዙ ስራዎችን ለመስራት የምትጎጏ ነበረች። ከእንግዲህ ወድያ ነች እያልን ሳይሆን: ነበረች እያልን: ልንመሰክርላት: በደረሰባት ከባድ ድንገተኛ የመኪና አደጋ አተንናታል። ይህ ባይሆን መልካም ነብር.!!! እግዚአብሔር ግን በባህሪው ስተት የሌለበት አምላክ ነውና። ይህ ለምን ሆነ ተብሎ እሱን መውቀስ አይቻልም እና። አንተ ባለህ ጥበብ ባለህ ፀጋ ቤተሰቦቾንም ወዳጅ ዘመዶቾንም ታፅናናልን እና ታበረታልን ዘንድ የ እህታችንንም ነብስ በገነትህ ታኖርልን ዘንድ እንለምንሀለን አሜን።።።

The post የኢትዮጵያዊቷ “ባለህ ነገር አመስግን” ባለች ከቀናት በኋላ በሜሪላንድ ሕይወቷ አለፈ appeared first on Zehabesha Amharic.


በጎንደር እስር ቤት ተቃጠለ * እስረኞች እያመለጡ ነው * የሞቱም የተጎዱም አሉ ተብሏል

$
0
0

gonder
(ዘ-ሐበሻ) በጎንደር ከተማ የሚገኘው ትልቁ እስር ቤት ውስጥ ከፍተኛ የ እሳት ቃጠሎ ተነስቶ እስረኞች እያመለጡ
መሆኑ ተሰማ:: የዘ-ሐበሻ የጎንደር ምንጮች እንደዘገቡት በከተማዋ ከፍተኛ የጥይት ድምጽ ይሰማል::

በጎንደር ከተማ የሚገኘው ባህታ የተሰኘው ወህኒ ቤት የተነሳው የ እሳት ቃጠሎ መነሻ ያልታወቀ ሲሆን ቃጠሎው በወንጀል ተጠርጥረው የታሰሩ በርካታ እስረኞችን እንዲያመልጡ ምክንያት ሆኗቸዋል:: በተለይ ከግድያ ወንጀል ጋር በተያያዘ ተፈርዶባቸው የነበሩ እስረኞች ማምለጣቸው በተለይ በቂም በቀል በሚፈላለጉ ቤተሰቦች ላይ ትልቅ የሆነ ፍራቻን እንደሚፈጥር አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች ይናገራሉ::

ፖሊስ እያመለጠ የሚገኘውን እስረኛ ለማስቆም በሚተኩሰው ጥይት ከተማዋ በከፍተኛ ሁኔታ መረበሿን የሚጠቁሙት የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች እስካሁን ወደ 380 የሚጠጉ እስረኞች ማምለጣቸውን ገምተዋል:: ፖሊስ በሚተኩሰው ጥይት የተጎዱ እስረኞች በአካባቢው በሚገኙ የጤና ጣቢያዎች ህክምና እየተደረገላቸው ሲሆን ቁጥራቸው ያልታወቁ እስረኞችም ሊያመልጡ ሲሉ መገደላቸው ተሰምቷል:

በሌላ በኩል በእሳት ቃጠሎው ምክንያት ከእስር ክፍላቸው መውጣት ያልቻሉ እስረኞች የቃጠሎ ጉዳት እንደደረሰባቸው ምንጮቻችን ገልጸዋል::

The post በጎንደር እስር ቤት ተቃጠለ * እስረኞች እያመለጡ ነው * የሞቱም የተጎዱም አሉ ተብሏል appeared first on Zehabesha Amharic.

(ይናገራል ፎቶ) የፌደራል ፖሊስ ወረራ በሃሮማያ ዩኒቨርሲቲ

$
0
0

የአዲስ አበባን ማስተር ፕላን በመቃወም በሃሮማያ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ያነሱትን ሰላማዊ ጥያቄ ፖሊስ በሃይል ለመግታት በመሞከሩ 3 ሰዎች መሞታቸውን እና በርካቶች መቁሰላቸውን ዘ-ሐበሻ ትናንት መዘገቧ አይዘነጋም:: ፖሊስ በዩኒቨሪስቲው ውስጥ ያደረገውን ወረራ የሚያሳዩ ምስሎች ተለቀዋል – ለግንዛቤ እነሆ::
haromaya 2 haromaya jawar

The post (ይናገራል ፎቶ) የፌደራል ፖሊስ ወረራ በሃሮማያ ዩኒቨርሲቲ appeared first on Zehabesha Amharic.

(ይናገራል ፎቶ) በጎንደር ቤቱ ከተቃጠለ በኋላ አካባቢው በፌደራል ፖሊስ ታጥሯል

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) ከሰዓታት በፊት ጎንደር ከተማ ውስጥ ባታ የተሰኘው እስር ቤት ተቃጥሎ በርካታ እስረኞች ማምለጣቸውን እና የቆሰሉና የሞቱ ሰዎች እንዳሉ ዘ-ሐበሻ መዘገቧ ይታወሳል:: ከጎንደር አካባቢ ለዘ-ሐበሻ የተላኩ ፎቶዎች እንደሚያሳዩት ፌደራል ፖሊስ ከተማዋን እያሸበረው ይገኛል:: በየቦታው ፖሊስ ሰፍሮ አካባቢውን በማሰስ ላይ ሲሆን ያመለጡ እስረኞችን ለመያዝም የተለያዩ እንቅስቃሴዎች እየተደረጉ ይገኛሉ:: ዘ-ሐበሻ የሟቹቹን ቁጥር ለማጣራት እየሞከረች ነው:: እስከዚያው የጎንደር ከተማን የዛሬውን ውሎዋን የሚያሳዩ 3 ፎቶዎች ይመልከቱ::

gonder 2 gonder 4 gonder

The post (ይናገራል ፎቶ) በጎንደር ቤቱ ከተቃጠለ በኋላ አካባቢው በፌደራል ፖሊስ ታጥሯል appeared first on Zehabesha Amharic.

አርበኞች ግንቦት 7 ዛሬ ዋልድባ ላይ መዋጋቱንና ጉዳት ማድረሱን ገለጸ * 29 ወታደሮችን ገደልኩ አለ

$
0
0

birhanu nega

(ዘ-ሐበሻ) መነሻውን ኤርትራ ያደረገው አርበኞች ግንቦት 7 ከቀናት በፊት በኢትዮጵያና ኤርትራ ድንበር አካባቢ በሚገኙ ከተሞች በምሽት ቀስቃሽ ወረቀቶችን ሲበትን መክረሙን ከገለጸ በኋላ ዛሬ በለቀቀው መረጃ ዋልድባ ላይ ከመንግስት ኃይሎች ጋር መዋጋቱን ገለጸ::

ዘ-ሐበሻ ከአርበኞች ግንቦት 7 ራድዮ ያገኘችው መረጃ እንደሚጠቁመው ሰራዊቱ ዛሬ ዲሴምበር 1, 2015 ከቀኑ 10 ሰዓት ጀምሮ ከመንግስት መከላከያ ሰራዊት እና ልዩ ጦር ጋር ተዋግቶ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱን ነው:: ከመንግስት በኩል ከአርበኞች ግንቦት 7 ጋር ስለመዋጋቱ ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ የተሰጠ መግለጫ የለም::

የአርበኞች ግንቦት 7 በራድዮው በኩል እንዳሰራጨው መረጃ በድንገት በከፈትኩት ጥቃት ዋልድባ ላይ ለሰዓታት ያህል ሰራዊቴ ሲዋጋ ውሎ በትሹ 29 ወታደሮችን ገድያለው እንዲሁም ከ40 በላይ ደግሞ አቁስያለሁ ብሏል::

The post አርበኞች ግንቦት 7 ዛሬ ዋልድባ ላይ መዋጋቱንና ጉዳት ማድረሱን ገለጸ * 29 ወታደሮችን ገደልኩ አለ appeared first on Zehabesha Amharic.

የአርበኞች ግንቦት ሰባት መሪ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የዛሬዉ የአዉሮፓ ሕብረት ንግግራቸዉ – VOA

$
0
0

nega
(VOA Amharic) የአርበኞት ግንቦት ሰባት መሪ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ዛሬ ብረስልስ ቤልጄም በሚገኘዉ የአዉሮፓ ፓርላማ በኢትዮጽያ ስለተከሰተዉ ድርቅና ረሃብ ማብራሪያ መስጠታቸዉ ታዉቋል።
ዋሽንግተን ዲሲ —
የኢትዮጵያን መንግሥት በትጥቅ ከሥልጣን የማዉረድ ዓላማ ያነገበዉን ግንቦት ሰባት በመምራት በጎሬቤት ኤርትራ እንደሚገኙ የሚታወቀዉ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ስብሰባዉን ባዘጋጁት የፓርላማዉ አባላት እንደተጋበዙ ገልጸዋል። በኢትዮጵያ አሁን በድርቅ ምክንያት ስለተከሰተዉ የምግብ እጥረት ያደረጉት ንግግርም ድርቅ ተፈጥሮአዊ ክስተት፣ ረሃብ ግን የመንግስት የኢኮኖሚ ፖሊሲ ዉድቀት መሆኑን የሚያመለክት ነዉ ብለዋል።

“ከኢትዮጵያ ረሃብን ማስወገድ ከባድ አይደለም” ያሉት ፕሮፌሰር ብርሃኑ ፤ መንግሥት ሁሉን ነገር የመቆጣጠር አባዜ ይዞታል፣ገበሬዉን መፈናፈኛ አሳጥቶ ከእለት ጉርስ ያለፈ የኢኮኖሚ ሕይወት እንዳይኖረዉ አድጓል” ብለዋል፡፡ አያይዘውም እየጨመረ የሄደዉ የኢትዮጵያ ሕዝብ ብዛትና እንዲሁም ፤ ኬሚካል ማዳበሪያ እየፈጠረ ያለዉ ችግር እንደ ምግብ እጥረት ምክንያትነት ጠቁመዋል። የኢትዮጵያ መንግስት የአሁኑን ድርቅ ኢልኒኖ የተባለዉ የአየር መዛባት እንዳስከተለዉና እስካሁን ድርቁ ባሰከተለዉ ረሃብ የሞተ ሰዉ እንደሌለ ለአስቸኳይ ጊዜ የመደበዉን ርዳታም ድርቅ ላጠቃዉ ሕዝብ እያደለ መሆኑን ይናገራል።

የአርበኞች ግንቦት ሰባት መሪ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የዛሬዉ የአዉሮፓ ሕብረት ንግግራቸዉ በኢትዮጵያ ወቅታዊ ፓለቲካ ጉዳዮችም ላይ ያተኮረ መሆኑን ጠቅሰዋል። የኢትዮጵያ መንግስት ለለዉጥ አሻፈረኝ በማለት ተቃዋሚዎች ጋር የገባዉ ፍጥጫ ለአዉሮፓ ሕብረት አሳሳቢ በመሆኑ አባላቱ ሰለ ወቅታዊ የአገሪቱ የፓለቲካ ሁኔታም እንደተወያዩ ተናግረዋል።

ቃለ-ምልልሱን ለመስማት የተያያዘውን የድምጽ ፋይል ያዳምጡ።
[jwplayer mediaid=”48656″]

The post የአርበኞች ግንቦት ሰባት መሪ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የዛሬዉ የአዉሮፓ ሕብረት ንግግራቸዉ – VOA appeared first on Zehabesha Amharic.

የመምህር ግርማ ወንድሙ አዲሱ የግድያ ወንጀል መጠርጠር ክስ ከየት መጣ? |የጋዜጠኛ ታምሩ ገዳ ትንታኔ በድምጽ

$
0
0

በመንፈሳዊ አባትነታቸውና አጥማቂነታቸው የሚታወቁት መምህር ግርማ ወንድሙ ላይ ከዚህ ቀደም የስምንት መቶ ሺህ ብር አጭበርብረዋል በሚል ክስ ቀርቦባቸው የነበረ ሲሆን ፖሊስ ክሱን በበቂ ሁኔታ ሊያሳምን ባለመቻሉ በዋስ እንዲለቀቁ ተወስኖ ነበር። ከመጀመሪያም በመምህሩ መያዝ ላይ አንዳች ጥርጣሬ ያደረባቸው አንዱ ክስ ሲወድቅ ሌላ መምጣቱ የበለጠ ጥርጣሬያቸውን አጠናክሯል። በተለይም አስቀድሞ በዘሐበሻ እንደተዘገበው የተደበቀው በነፍስ ማጥፋት ወንጀል ለመክሰስ ማሰብ – ይፋ ሆኗል። አዲሱ ክስ ከየት መጣ!? ወቅታዊ ጉዳዩን ጋዜጠኛ ታምሩ ገዳ በሕብር ራድዮ ዳሶታል – ያድምጡት::

The post የመምህር ግርማ ወንድሙ አዲሱ የግድያ ወንጀል መጠርጠር ክስ ከየት መጣ? | የጋዜጠኛ ታምሩ ገዳ ትንታኔ በድምጽ appeared first on Zehabesha Amharic.

Sport: በቼልሲ ዙሪያ የተዘጋጀ ልዩ ዘገባ |ጉስ ሂድኒክ የቼልሲ ስራን ለመያዝ ተዘጋጅተዋል

$
0
0

ቼልሲ ያለፈውን የውድድር አመት ያጠናቀቀው ሁለት የዋንጫ ሽልማቶችን በማግኘት ማለትም ለፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮንነት ክብር በመብቃትና የካፒታል ዋን ውድድር ድልን በመቀዳጀት ነበር፡፡ ዘንድሮ ግን በእነዚህ ሁለት ውድድሮች የዋንጫ ሽልማቶችን የማግኘት ተስፋው ዝቅተኛ ሆኗል፡፡ ምክንያቱም ከስቶክ ሲቲ በመለያ ምት ተሸንፎ የካፒታል ዋን ውድድር ዘመቻውን ወደ ሩብ ፍፃሜው ደረጃ ለማሸጋገር ሳይችል ቀርቷል፡፡ በአሁኑ ወቅት ከሊጉ መሪዎች ማንችስተር ሲቲና አርሰናል ጋር ያለው የነጥብ ልዩነት 11 በመሆኑም የፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን ክብሩን የማስከበሩ ተስፋ ዝቅተኛ ሆኗል፡፡
chealsea

ይህንን እውነታን ከግንዛቤ በማስገባትም በፖርቹጋላዊው አሰልጣኝ ምትክ የቼልሲ ስራን ለመረከብ በግንባር ቀደምትነት ሆላንዳዊው ጉስ ሂድንኪና ጣሊያናዊው ካርሎ አንቾሎቲ ታጭተዋል፡፡ የእነዚህ ሁለት ባለሙያዎች ስም ከቼልሲ ስራ ላይ እንዲያያዝ በዋነኝነት የሚጠቀሰው ምክንያት ሁለቱም በአሁኑ ወቅት ካለስራ መቀመጣቸው ነው፡፡ በተለይም ከዚህ በፊት ቼልሲን ለአጭር ጊዜ በተጠባባቂ ዋና አሰልጣኝነት የመሩት ጉስ ሂድኒክ ከሰሞኑ በሰጡት አንድ መግለጫቸው በሞውሪንሆ ምትክ የቼልሲ አዲሱ ዋና አሰልጣኝ ሆነው ለመሾም ዝግጁ መሆናቸውን የሚጠቁም ሆኗል፡፡

ሂድንኪ የፊታችን ሰኔ ወር በፈረንሳይ አዘጋጅነት ለሚካሄደው ዩሮ 2016 ውድድር የሆላንድ ብሔራዊ ቡድንን ተሳታፊ የማድረግ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ለመፈፀም ስለተሳናቸው ከአሰልጣኝነት ራሳቸውን ማግለላቸው ይታወቃል፡፡ በሰሞኑ መግለጫቸው ለ2ኛ ጊዜ ሊመሩት መመኘታቸውን የጠቆሙት ቼልሲን በ2009 ለስድስት ወራት ያህል በተጠባባቂ ዋና አሰልጣኝነት በመምራት ለኤፍ.ኤ.ካፕ ድል ያበቁት ከመሆኑም ባሻገር በፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮንነት ፉክክሩ እስከመጨረሻዎቹ ጥቂት ሳምንታት ድረስ በጠንካራ አቋም ሆኖ ለመዝለቅ እንዲችል ረድተውት ነበር፡፡

ያንን መልካም ጊዜቸውን መለስ ብለው በማስታወስ ሂድኒክ ደግሞ የቼልሲ ስራን ለመያዝ መመኘታቸውን የጠቆሙበት መግለጫን ሲሰጡ ተደምጠዋል፡፡ ‹‹ፉትቦል ኢንተርናሽናል›› የተባለው የሆላንድ ጋዜጣ ከሰሞኑ ‹‹ከስድስት ዓመታት በኋላ ወደ ቼልሲ በመመለስ በዋና አሰልጣኝነት የመስራት ፍላጎቱን አሳድረዋል በሚል ላቀረበላቸው ጥያቄ ሂድኒክ ምላሻቸውን ሲሰጡ የተደመጡት ‹‹በትልቅ ደረጃ በሚደረግ ውድድር የሚሳተፍ ትልቅ ክለብን በዋና አሰልጣኝት የመምራት ፍላጎትን የማሳደር ባህል አለኝ፡፡ ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ በርካታ ጥሪዎችንም ቀርበውልኛል፡፡ የቀረበልኝ ጥሪዎችን ሳልቀበላቸው የቀረሁት የትልቅ ክለብ ሥራን ለመያዝ በመመኘት ነው፡፡ ለምሳሌ እንደ ቼልሲ አይነቱ ትልቅ ክለብ ጥያቄ የሚያቀርብልኝ ከሆነ ካለምንም ማመንታት መልሴን የምሰጠው እንደሚሆን አልደብቅም፡፡ በአሁኑ ወቅት ግን ቀጣዩ ሥራዬ ምን እንደሚሆን እርግጠኛ ሆኜ የምናገረው ጉዳይ የለኝም›› በማለት ነው፡፡
በአሁኑ ወቅት ዕድሜያቸው 68 የደረሰው ሂድኒክ ከዚህ በፊት ለመጀመሪያ ጊዜ የቼልሲ ስራን በፌብርዋሪ 2009 የተረከቡት የብራዚሉ አሰልጣኝ ሉዊስ ፍሊፕ ስኮላሪ ለሰባት ወራት ከዘለቁበት የስታምፎርድብሪጅ ስራ መነሳትን ተከትሎ ነበር፡፡ ሃዲንኪ ስታምፎርድ ብሪጅ እንደደረሱም ቼልሲ እስከሲዝኑ መጋመስ ድረስ የነበረው የአቋም አለመረጋጋት የ2008-09 ሲዝን ዘመቻውን በፕሪሚየር ሊግ የደረጃ ሰንጠረዥ በ3ኛ ስፍራ ላይ ተቀምጦ እንዲጨርስ አስችለውታል፡፡

የቻምፒዮንስ ሊግ ዘመቻውን እስከ ግማሽ ፍፃሜው ደረጃ ድረስ ለመዝለቅ እንዲችልም አድርገውታል፡፡ በወቅቱ በቻምፒዮንስ ሊግ ግማሽ ፍፃሜ የደርሶ መልስ ግጥሚያ ቡድናቸው በባርሴሎና በአጠቃላይ ውጤት ተሸንፎ በሮም ከተማ ከተደረገው የውድድሩ ፋይናል የቀረውን ግልፅ የሆኑ የዳኝነት በደሎች ተፈጽሞበት እንደነበር የሚታወስ ነው፡፡ ሂድኒክ ያንን ፀፀታቸውን ግን በሜይ 2009 በዌምብሊ ስቴዲየም ከኤቨርተን ጋር የተደረገው የኤፍ.ኤ.ካፕ ፋይናልን 2ለ1 በሆነ ውጤት በማሸነፍ የዋንጫውን ሽልማትን በማግኘት በመጠኑም ቢሆን ሊረሱት ችለዋል፡፡ ይህ የሚያሳየው ሂድኒክ ቼልሲን ለአጭር ጊዜ በተጠባባቂ አሰልጣኝነት በመሩበት ግማሽ ሲዝን ለቡድኑ ጠንካራ አቋምን አስገኝተውለት እንደነበር ነው፡፡ ከዚህ አንፃር የቼልሲው ባለቤት ሮማን ኢብራሞቪች በሚጠበቀው መልኩ ጆሴ ሞውሪኖን ከስራቸው ካነሷቸው ጉስ ሂድኒክን አዲሱ የክለባቸው ዋና አሰልጣኝ አድርገው መቅጠርን በቅድሚያ ምርጫቸው ቢያደርጉት አስገራሚ ሊሆን አይችልም፡፡
mourinho

ሂድኒክ የ2008-09 ሲዝን ከተጋመሰ ወዲህ የቼልሲን ስራ ተረክበው የቡድኑ ያልተረጋጋ አቋምን በፍጥነት ለማረም የቻሉበትን ያንን ተደናቂ ተግባራቸውን በማስታወስ በርካታ የፉትቦል ተንታኞች በዘንድሮ ሲዝን የቼልሲ የእስካሁን ችግሮች ትክክለኛው የመፍትሄ እርምጃን ሊያበጁለት የሚችሉበት ተደናቂ ተሰጥኦን ተላብሰዋል የሚል እምነት አሳድረውባቸዋል፡፡ ከዚህ ባሻገር ለበርካታ ዓመታት በዘለቀው የአሰልጣኝነት ሙያቸው በርካታ ክለቦችና የተለያዩ አገሮችን ብሔራዊ ቡድኖችን በዋና አሰልጣኝነት የመሩት ሂድኒክ በቼልሲ ደጋፊዎችና በክለቡ አባላት በጠቅላላ እስካሁንም ድረስ ከፍተኛ የሆነ ከበሬታን አሳድረው ዘልቀዋል፡፡

‹‹እንደ ቼልሲ ያለው ትልቅ ውድቀትን በሌላ ክለብ አላስታውስም››
አለን ሽረር
ፖርቹጋላዊው አሰልጣኝ ጆሴ ሞውሪኖ ባለፈው ሲዝን ቼልሲ ከፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮንነት ክብር ጋር ያገናኙት ሙሉው ሲዝንን በደረጃው ሰንጠረዥ አናት ላይ በማስቀመጥና የቅርብ ተቀናቃኙ ማንችስተር ሲቲን በስምንት ነጥቦች በልጦት እንዲጨርስ በማስቻል ነው፡፡ በዘንድሮው ሲዝን ግን ገና የመጀመሪያዎቹ 10 የፕሪሚየር ሊግ ግጥሚያዎች ከመደረጋቸው ከሊጉ መሪ ማንችስተር ሲቲ በ11 ነጥቦችና በአስር ደረጃዎች ላይ ተቀምጦ ይገኛል፡፡
ከእስካሁኑ 10 የሊጉ ግጥሚያዎች 15 ጎሎችን አስቆጥሮ መረቡን በ19 ጎሎች ማስደፈሩም ሌላው የቼልሲ አስደንጋጭ የአቋም መውረድ ችግር እንዲከሰትበት የሚያሳይ ጉዳይ ነው፡፡ ከዚህ አንዱ ምክንያት አብዛኛዎቹ የቡድኑ ተሰላፊዎች አቋም ወርዶ መገኘት ነው፡፡ ባለፈው ሲዝን የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ድሪም ቲም ምርጫ ከተካተቱት 11 ተጨዋቾች ውስጥ ስድስቱ የቼልሲ ተጨዋቾች ነበሩ፡፡ በዘንድሮ ሲዝን ግን አንድም በጥሩ አቋም ሊጠቀስ የሚችል ተጨዋች እስከመጥፋት ደረጃ ደርሷል፡፡

እነዚህ እውነታዎችን በመተንራስ የቀድሞው የኒውካስል ዩናይትዱ ስታር አለን ሽረር ሰሞኑን በሰነዘረው አስተያየቱ የቼልሲ በፍጥነት የአቋም መውረድን ‹‹ከዚህ በፊት በሌላ ክለብ ያልታየ አስደንጋጭ አጋጣሚ›› በማለት ገልፆታል፡፡ የቀድሞው የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ዝነኛ የአጥቂ መስመር ተጨዋች በመቀጠልም ‹‹እኔ እስከማስታውሰው ድረስ እንደ ቼልሲ ሁሉ በጥቂት ወራት ውስጥ ከነበረበት ትልቅ አቋም በፍጥነት ሙሉ ለሙሉ ወደ ታች የወረደ ክለብ በእንግሊዝ ክለብ አልታየም፡፡ የቼልሲ በአስደንጋጭ ሁኔታ ወርዶ መገኘት በክለቡ ውስጥ አንድ ግልፅ ያልታየ ከፍተኛ ችግር ተፈጥሯል የሚል ጥርጣሬን እንዳሳድር አስገድዶኛል፡፡ ከእነዚህ ችግሮች ውስጥ ምናልባትም አንዱ ሞውሪንሆ በስኳዳቸው የሚመኙት ትክክለኛዎቹ ተጨዋቾች አለማግኘታቸው ሊሆን ይችላል፡፡ ሆኖም ግን ማንኛውም የፉትቦል አፍቃሪና አስተያየት ሰጪ ቢሆን በዘንድሮው ሲዝን በቼልሲ ላይ የተፈጠረውን መሰረታዊ ችግሮች ምንነትን በትክክል ይረዳዋል የሚል እምነት በጭራሽ የለኝም›› የሚል አስተያየት ሰጥቷል፡፡

የስፖርትስ ሜይል የፉትቦል ተንታኞች በበኩላቸው ጆሴ ሞውሪኖ በኦገስት ወር በቼልሲ የዘንድሮ ሲዝን የመጀመሪያው ከስዋንሲ ሲቲ ጋር 2ለ2 ሲለያይ ለክለባቸው ዶክተር ኢቫ ካርኔሮ ጋር ግጭትን ከፈጠሩ ወዲህ ቡድናቸው ካደረጋቸው ግጥሚያዎች ግማሽ ያህሉን መሸነፉን ከግንዛቤ በማስገባት ከዛ ወዲህ በምዕራብ ለንደኑ ክለብ ላይ የተፈጠሩትን ችግሮችን ከዚህ በታች ባለው መልኩ ዘርዝረዋቸዋል፡፡

ኦገስት 8፡-
ጆሴ ሞውሪኖ የክለባቸው ዶክተር ኢቫ ካርኔሮና ረዳቷን ጆን ፍርንን የሚተች መግለጫን በመስጠት በክለባቸው ችግር እንዲቀሰቀስ በር ከፋች ሆነዋል፡፡ በሞውሪኖና በህክምና ባለሙያዎቹ መካከል ተፈጠረው ግጭት ተካርሮ በመዝለቁ ፖርቹጋላዊው አሰልጣኝ በእንግሊዝ ፉትቦል ማህበር እስከመከሰስ ደረጃ ደርሰዋል፡፡ ሆኖም ግን ካርኔሮን በብልግና ቃላት ሰድበዋል በሚል ከቀረበባቸው ክስ ካለምንም ቅጣት አምልጠዋል፡፡ በዚህ በመበሳጨት የህክምና ዶክተሯ በቼልሲ የነበራትን ስራ በራሷ ፈቃድ ለመልቀቅ ወስናለች፡፡

ኦገስት 16
ቼልሲ በኢትሃድ ስቴዲየም በማንችስተር ሲቲ 3ለ0 በተረታበት የፕሪሚየር ሊግ ግጥሚያው ወቅት ጆሴ ሞውሪኖ ባልተለመደ መልኩ የቡድናቸው አምበል ጆን ቴሪን ቀይረው አስወጥተውታል፡፡ ከዛ በኋላ ባሉት ጥቂት ግጥሚያዎች ላይም ቴሪን በመደበኛ ቋሚ አሰላለፋቸው ውጪ በማድረግ የክለባቸው ደጋፊዎችን ቅር አሰኝተዋቸዋል፡፡ ቼልሲ የፕሪሚየር ሊግ ውድድር የመጀመሪያዎቹ ሁለት ግጥሚያዎችን ለማሸነፍ ሲሳነው ዘንድሮ ከድፍን 17 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው፡፡

ኦገስት 29
ሞውሪኖ ቼልሲን በስታምፎርድ ብሪጅ የመሩበት 100ኛው የፕሪሚየር ሊግ ግጥሚያው በሽንፈት ተደምድሟል፡፡ በክሪስታል ፓላስ 2ለ1 የተሸነፈበትን ጨምሮ ሞውሪኖ በራሳቸው ሜዳ ባደረጓቸው 100 የፕሪምየር ሊግ ግጥሚያዎች ሽንፈት ሲደርስባቸው ያ ለሁለተኛ ጊዜ ብቻ ነው፡፡ በዛ ግጥሚያ ኮሎምቢያዊው ኢንተርናሽናል ራዳሜል ፉልካኦ ለቼልሲ በውሰት ውል ከፈረመ ወዲህ የመጀመሪያውን ጎሉን ለማስቆጠር ቢችልም በስሙ ያስመዘገባት ጎል ግን ቼልሲን ከሽንፈት ሳታድነው ቀርታለች፡፡

ሴፕቴምበር 13
የሞውሪኖ ቡድን የጉድሰን ፓርክ ስቴዲየም ከኤቨርተን ጋር ያደረገው የፕሪሚየር ሊግ ግጥሚያውን 3ለ1 በሆነ ውጤት በሽንፈት ለማጠናቀቅ ተገድዷል፡፡ በዛ ግጥሚያ የኤቨርተን አጥቂ ስቴቨን ሃይስሚዝ ሶስት ጎሎችን በማስቆጠር ሃትሪክ የሰራው የቼልሲው የተከላካይ መስመር ከተሰለፉት ጆን ቴሪና ለፈረንሳዊው ወጣት ተከላካይ ኩርትዙማ ከአቅማቸው በላይ የሆነ እጅግ ውጤታማ የማጥቃት እንቅሰቃሴን በማድረግ ነው፡፡ እስከዛ ደረጃ ድረስም ቼልሲ በመጀመሪያዎቹ 5 የሊጉ ግጥሚያዎቹ በእያንዳንዱ ላይ ቢያንስ ሁለት ጎሎች ተቆጥረውበታል፡፡ ከአምስቱ ግጥሚያዎች በአጠቃላይ ያገኘው ነጥብ አራት ብቻ ነበር፡፡

ሴፕቴምበር 19
ቼልሲ አርሰናልን 2ለ0 በረታበት የፕሪሚየር ሊግ ግጥሚያ ወቅት የቡድኑ የፊት አጥቂ ዲያጎ ኮስታ ከሎረን ኮስኒሌይ ጋር በፈጠረው ግጭት ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ በእንግሊዝ ፉትቦል ማህበር የሶስት ተከታታይ ግጥሚያዎች የእገዳ ውሳኔ ተላልፎበታል፡፡ እስከዚህ ጨዋታ ድረስ ኮስታ ከአንድ የፕሪሚየር ሊግ ጎል በስተቀር ለማስቆጠር አልቻለም፡፡ ሆኖም ግን ሞውሪኖ ኮስታ ለሶስት ግጥሚያዎች የታገደበት ውሳኔን በመተቸት በእንግሊዝ ፉትቦል ማህበር ላይ የሰላ ትችትን ሲሰነዝሩ ተደምጠዋል፡፡

ሴፕቴምበር 29
ጆሴ ሞውሪኖ በ2004 ለአውሮፓ ሻምፒዮንነት ክብር ወደመሩት ፖርቶ ሜዳ ተመልሰው ባደረጉት የቻምፒዮንስ ሊግ ግጥሚያ ቡድናቸው 2ለ1 በሆነ ውጤት ተሸንፏል፡፡ በዛ ግጥሚያ ሞውሪኖ ኤደን ሃዛርድና ኔማኒያ ማቲችን ለቡድናቸው መደበኛ ቋሚ አሰላለፍ ውጪ ያደረጉበት ተግባር ስህተት የፈፀሙበት ተደርጎ ተቆጥሯል፡፡ ከፖርቶ ጎሎች ለአንዷ መገኘት ጥፋትን የፈፀመው ኩርት ዙማን በመደበኛ ቋሚ ተሰላፊነት በማስጀመር ጆን ቴሪን በተጠባባቂ ወንበር ላይ ያስቀመጡበት ተግባራቸውን ለቡድናቸው ሽንፈት ተወቃሽ የሆኑበት ሌላው ጉዳይ ሆኗል፡፡

ኦክቶበር 3
ቼልሲ በሳውዝአምፕተን 3ለ1 በተረታበት የዘንድሮ ሲዝን የፕሪሚየር ሊግ ውድድር 4ኛው ሽንፈቱ በኋላ ለሞውሪኖ ኃላፊነት ለትልቅ አደጋ ተጋልጧል፡፡ ከግጥሚያው ሶስት ቀናት በኋላ የቼልሲ ቦርድ ባወጣው ይፋዊ መግለጫው ግን ለሞውሪኖ ሙሉ ድጋፍን መስጠትን ምርጫው አድርጎታል፡፡ ሞውሪኖ በሳውዝአምፕተን የተረቱበት ግጥሚያ የመሩት አርቢትር ሮቤርቶ ማድሌይን በይፋ በመተቸታቸው በእንግሊዝ ፉትቦል ማህበር 50 ሺ ፓውንድ የገንዘብ ቅጣት ተላልፎባቸዋል፡፡

ኦክቶበር 17
ያለፈው ሲዝን የፕሪሚየር ሊግ ኮከብ ተጨዋች የሆነው ኤደን ሃዛርድ ቡድናቸው አስቶንቪላን 2ለ0 በረታበት የፕሪሚየር ሊግ ግጥሚያ ከመደበኛ ቋሚ አሰላለፋቸው ውጪ አድርገውታል፡፡ በኋላ ላይ በሰጡት መግለጫም የቤልጂየሙ ኢንተርናሽናል የዘንድሮው ሲዝን አቋሙን ከወትሮ በብዙ መልኩ የወረደ በማለት ተችተውታል፡፡

The post Sport: በቼልሲ ዙሪያ የተዘጋጀ ልዩ ዘገባ | ጉስ ሂድኒክ የቼልሲ ስራን ለመያዝ ተዘጋጅተዋል appeared first on Zehabesha Amharic.


Health: የውብ ወገብ ባለቤት የሚደርጉሽ 7 ምስጢሮች

$
0
0

by Lili Moges

ሴት ከሆንሽ የፋሽን ኢንዱስትሪው በየጊዜው ከሚያቀርባቸው አልባሳት ጋር ለመዋሃድ አካልሽን በሚገባ አስተካክለሽ መጠበቅ ሳያስፈልግሽ አልቀረም፡፡ ለፋሽን ፍላጎቱ ሳይኖርሽ በተገኘው ተሸፋፍኖ መውጣቱን ምርጫሽ ካላደረግሽ በቀር፡፡ ያልተስተካከለው አካላዊ ቅርፃችንን ሲሸፍኑልን ብዙ ምዕተ ዓመታትን ያሻገሩን የባህል ልብሶቻችንም ቢሆኑ እኮ፣ ዛሬ ላይ በፋሽን ኢንዱስትሪው ተመዝግበው ወዝወዝ ለሚሉት ቆነጃጅት እየተዘጋጁ በስፋት እየቀረቡ ነው፡፡ አንቺ የባህል ልብሳችን እንደነበሩ መቆየት አለባቸው ለውጥ ባህላዊነታቸውን ያሳጣቸዋል ከሚሉት ጎራ ከሆንሽና ተቆርቋሪነትሽ ከልብሽ ከሆነ የእኔም ድጋፍ እንዳለሽ እንዳትዘነጊ ነገር ግን ክርክርሽ ከባህሉ ባሻገር ከሆነው ችግሩ፡፡ ተመራማሪዎች ውለው ይግቡና ለችግሮቻችን መፍትሄ የሚሉትን በየጊዜው ያቀርቡልናል፡፡ ለዛሬም የሆድ ቅርፃችንን በመሰረታዊነት ከሚያስተካክሉልን ቀላል ከሚሆኑ መንገዶች ጋር እንተዋወቃለን፡፡
no soda
1.እያወራሽ ተራመጂ

ከጓደኞቻችን ጋር በምግብ እና መጠጥ ክፍለ ጊዜ ብቻ ከመገናኘት የእንቅስቃሴ ወዳጅነት እንዲኖረን ያስፈልጋል፡፡ በዚህ ወቅት የግድ ቁም ነገር ያዘሉ ወሬዎችን መወያየት ላይጠበቅብን ይችላል፡፡ የባጥ የቆጡንም እያወራን የእግር መንገድ ብናደርግ የሆዳችን ጡንቻ መስራቱን አጠናክሮ ይቀጥላል፡፡ በዚህ ሂደት ውስጥ ካለን በ10 ፐርሰንት በሰውነታችን የጥንካሬ ላይ ለውጥ እናመጣለን፡፡ እያወሩ የመራመድ እንቅስቃሴን ቢያንስ በሳምንት አንድ ጊዜ ማድረግ በፍፁም መዘንጋት የለበትም፡፡

2. በፋይበር የበለፀጉ ምግቦችን ጨምረሽ ተመገቢ፡-
በቀን ቢያንስ 10 ግራም ፋይበር ወደ ሰውነትሽ ብታስገቢ ሆድሽ ከ4 ፐርሰንት በታች ብቻ ፋት ነው የሚሸከመው የፋይበር ክምችትሽን በቀን ውስጥ ሁለት የአፕል ፍሬዎችን፣ ግማሽ ኩባያ ባቄላ ወይም ሁለት ኩባያ አበባ ጎመን በመመገብ የሆድ ቅርፅሽን የሚያስተካክል 10 ግራም ፋይበር ታገኛለሽ፡፡

3. በቃኝን አስቀድሚ፡-

በምግብ ቤቶች ከሴት ጓደኞችሽ ጋር ጠረጴዛ ሞልታችሁ ስትቀመጡና አስተናጋጅ መጥቶ ተጨማሪ የምግብ ክምችት ያመጣ እንደሁ ሲጠይቅ ምንጊዜም ዝቅተኛ ፍላጎት ይኑርሽ፤ ራስሽን የምታውቂው አንቺው እንደመሆንሽ ግዴታ ካልሆነብሽ መመገቡ በቃኝ ማለቱንም እወቂበት፡፡ በቅርብ የወጡ ጥናቶች እንዳመለከቱት መካከለኛ ክብደት ያላቸው ሴቶች ከወፍራም ሴቶች ይልቅ የቀጭን ሴቶችን የአመጋገብ ባህል የመቅዳት ዝንባሌ አላቸው፡፡
4. የምንጠቀመውን የጨው መጠን በተመለከተ እንደገና እናስብ
ከፍተኛ መጠን ያለው ጨው በተጠቀምን መጠን በዛው ልክ ፈሳሽ እንድንወስድ እንገደዳለን፡፡ ይሄም ለበለጠ ሰውነት እና ተጨማሪ ውሃ አምጪ ክብደት የተጋለጥን ያደርገናል፡፡

5. የመቅለብ ስፖርትን አዳብሪ

ጉልበትሽ ወደላይ በማጠፍ መሬት ላይ ተኚ፡- ጀርባሽ የተስተካከለ መሆኑን ስታረጋግጪ አንገትሽ ከተኛሽበት መሬት ላይ ቀና አድርጊ፡፡ የመጫወቻ ኳስ ቆሞ የሚወረውርልሽ ሰው ካዘጋጀሽ በኋላ የሚወረወርልሽን ኳስ አንገትሽና ጉልበትሽን በነበሩበት ሆነው ወገብሽ አንዴ ወደ ግራ ሌላ ጊዜ ወደ ቀኝ በማንቀሳቀስ የመቅለብ እና መልሶ የመወርወር እንቅስቃሴን ምቾትሽ እስካልተጓደለ ድረስ ደጋግመሽ አከናውኚ፡፡ የእንቅስቃሴውን ድግግሞሽ በየሳምንቱ እያሳደግሽ ፈጣኑን ለውጥ መጠበቅ ነው፡፡

6. ከሶዳ መጠጦች ራቂ፡-
የምትጠጪያቸው በሶዳ ኬሚካል የበለፀጉ መጠጦችን በተቻለ መጠን ቀንሺ አደገኛ ኬሚካል በውስጣቸው ያለመጠጦች በመጨረሻ ማረፊያቸው የት ይመስልሻል? ሆድሽ ላይ ነው፡፡ ደንደን ያለ ቦርጭ ባለቤት ያደርጉሻል፡፡ እነዚህን መጠጦች ሳትወስጂ በውሃ መተካት ይኖርብሻል፡፡
7. አልኮል ሌላው በሆድ ላይ ለሚመጣ ውፍረት (ቦርጭ) ምክንያት ነው
ከምግብ ጋር የሚቀርበው ብርጭቆ ወይን ብቻውን የለበሽው ሱሪ እንዲያጣብቅሽ ሊያደርግሽ ይችላል፡፡ የአልኮል ፍጆታችን ከፍ ማለት ወደ ሆዳችን በቀጥታ ፋታ የሚያሰራጨውን የብርቲሶል ሆርሞን መጠንን የሚያሳድግ በመሆኑ ከአልኮል መጠጦች እንራቅ አልያም እንቅስቃሴ እናድርግ፡፡

The post Health: የውብ ወገብ ባለቤት የሚደርጉሽ 7 ምስጢሮች appeared first on Zehabesha Amharic.

ወያኔዎች ይገድላሉ ያገዳድላሉ |ይገረም ዓለሙ

$
0
0

ኢትዮጵያዉያን በፍቅር በሰላምና በአንድነት ከኖርን በኢትዮጵያ ሥልጣነ መንበር ላይ መቆየት አንደማይችሉ ገና ሀ ብለው ትግል ሲጀምሩ የተረዱት ወያኔዎች ለዚህ መላ ዘይደው እቅድ ነድፈው ነው የተነሱት፡፡ በሀይማኖት በቋንቋ በጎሳ በአካባቢ ወዘተ በማለያየት በኢትዮጵያውያን መካከል ፍቅር ሰላምና አንድነት እንዳይኖር ማድረግ የዚሁ እቅዳቸው አንዱና ዋናው ክፍል መሆኑን ላለፉት ሀያ አራት ዓመታት የፈጸሙትና አሁንም የቀጠሉበት ተግባራቸው በቂ ምስክር ነው፡፡ የጥላቻ መርዝ እየረጩ ርስ በርስ ያናክሳሉ፣ አጀንዳ እየሰጡ በሰላምና በፍቅር አብረው የኖሩ ዜጎች በጥርጣሬ አንዲተያዩ ያደርጋሉ፤ ከዚህ አልፎም ራሳቸው የሚገድሉት አልበቃና አላረካ ሲላቸው ለአመታት አብረው የኖሩ ርስ በርስ እንዲገዳደሉ ያደርጋሉ፡፡

TPLF leaders
ይህ በ1984 ዓም በበደኖ ወተር አርባ ጉጉ ወዘተ ተጀምሮ ጊዜና ሁኔታ እየጠበቀ በበብዙዎቹ የሀገራችን አካባቢዎች ተግባራዊ ሲደረግ የኖረ የወያኔ እቅድ ሰሞኑን ደግሞ ጎንደርን ወር ተረኛው አድርጓል፡፡ በስፍራው የተፈጸመውና በማህበራዊ ድረ ገጾች ተሰራጭቶ የተመለከትነው ግድያ እጅግ ሰቅጣጭ ነው፡፡ ለምንም ዓላማ ይሁን በማንም ይፈጸም አንዲህ አይነቱ የግፍ አገዳደል ለዛሬ የሚወገዝ ቀን ሲወጣ ደግሞ ለፍርድ የሚያስቀርብ ነው፡፡ ለነገሩ እኛ ነን እንጂ ሁሌ አዲስ የምንሆን ወያኔዎች ለደደቢቱ ዓላማቸው ስኬት ማናቸውንም ነገር ከመፈጸም ወደ ኋላ እንደማይሉ በሀያ አራት ዓመታት የአገዛዝ ዘመናቸው ያቀዱትንና የቻሉትን ሁሉንም ነገር አድርገው አሳይተውናል፡፡አሁንም እያሳዩን ነው፡፡ ለወያኔ ከምንም ነገር ቀዳሚው በሥልጣን መቆየት ነውና፡፡

ሀገር ቆርሰው ሰጥተዋል፤ አሁንም መሬት ለመስጠት እየተዘጋጁ ነው፤ዜጎችን ገድለዋል፤አገዳድለዋል፤አስረዋል አሰቃይተዋል፤ንብረት ዘርፈዋል ሌላም ሌላም፡፡ ሥነ ልቦናችንን ተረድተዋል ደካማ ጎናችንን አውቀዋልና፡ በየግዜው አዳዲስ ነገር እየፈጠሩ ሲግቱን እየተቀበልን ርስ በርስ ከመጠላላት አልፎ ይሄው ሰሞኑን ዘግናኝ በሆነ ሁኔታ እንደተፈጸመው ርስ በርሳችን አንገዳደላልን፡፡ በዚህ አድራጎታችንም የወያኔን የደደቢት ትልም በዘላቂነት አንዲሳካ መሳረያ በመሆን ምቹ ሁኔታ አንፈጥራለን፡፡

በግልጽ የሚታወቀው እስከዛሬ ያልተለወጠው ስማቸውም የሚያረጋግጠው የወያኔ የደደቢት ትልም የትግራይ መንግሥት መሆን ነው፡፡ ኢትዮጵያን በሙሉ የመያዝ በለስ ሲቀናቸው አንድም ሁሉን መያዝ ከቻልን ለምን በጠባብ እንወሰናለን ብለው ሁለትም ኢትዮጵያን ጎጆ መውጫና መበልጸጊያ ብሎም የዘላቂ ዓላማቸው ማደላደያ ለማድረግ እንጂ የተነሱበትን ዓላማ የሻሩ ላለመሆናቸው ድርጊቶቻቸው በቂ ማስረጃዎች ናቸው፡፡

የሚያሳዝነው ወያኔዎች ለከፋፍለህ ግዛው ስልታቸው ማስፈጸሚያ የፈጠሩዋቸውን ስመ ድርጅቶች የሚመሩ ሰዎች ራሳቸውን ከመጥቀም የዘለለ ምንም ዓላማና ግብ ሳይኖራቸው ለወያኔ የደደቢት ህልም አስፈጻሚ ሆነው መሰለፋቸው ነው፡፡ ሌላው ወያኔን በመቃወም የተሰለፈው ደግሞ ጠንክሮ በመታል ወያኔን ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጫንቃ ላይ ማንሳት መቻሉ ቢቀር የወያኔን ጥፋት ለመግታት የሚያስችል እንቅስቃሴ ከማድረግ በወያኔ ከፋፋይ መርዝ ተመርዞ ሆድና ጀርባ ሆኖ በመኖር የሚቃወመውን ሀይል እድሜ የሚያራዝም ተግባር ይፈጽማል፡፡አንዳንዱም ለወያኔ የማገዳደል እቅድ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በአስፈጻሚነት ያገለግላል፡፡

ወያኔዎች ገና ደደቢት እያሉ ያወጡትን እቅድ ደረጃ በደረጃ ግዜ እየጠበቁና የእኛን ሙቀት እየለኩ ተግባራዊ ሲያደርጉ በፈጻሚነት የምንሰለፈው እኛው ነን፡፡የሕዝቦችን ራስ በራስ የማስተዳደር መብት ከወረቀት ጌጥነትና ከፕሮፓጋንዳ መሳሪያነት ተሻግሮ ተግባራዊ አለማድረጉን ሀያ አራት አመታት በተግባር ያየነው ነው፡፡ ከህውኃት ውጪ ያሉት የኢህአዴግ አባል የሚባሉት ድርጅቶች ብአዴን ኦህዴድ ደአህዴንም ሆኑ አጋር የሚሰኙት ድርጅቶች የያዙዋቸውን ክልሎች በነጻነት እንደማያስተዳድሩ በግልጽ ይታወቃል፡፡በዚህ ሁኔታ በይስሙላ ፌዴራሊዝም ሀገሪቱን እየገዛ ያለ አንድ ፓርቲ ለአመታት መለስ ያላገኘን የቅማንት ጥያቄ ዛሬ ድንገት ተነስቶ ጥያቄአችሁ ተቀባይነት አግኝቷል ራሳችሁን በራሳችሁ ታስተዳድሩ ዘንድ ተፈቅዷል ሲል ጎንደሬው “ጠርጥር ከገንፎም አለ ስንጥር” በአንድ ክልል ውስጥ ከዞንም ያነሰ አካባቢ የራስ አስተዳደር መብት ተጎናጽፎ ከወያኔ ፍላጎትና አመራር ውጪ ራሱን ማስተዳደር ይችላል ተብሎ ታምኖ ለዘመናት አብረው በኖሩ ተጋብተው ተዋልደው ክፉንም ደጉንም አብረው እያሳለፉ የአንድ አካባቢ ነዋሪዎች መካከል አለመግባባት መፍጠሩ፤ አለመግባባቱንም ለዘመናት በዘለቀው አካባቢያዊ ዘየ ለመፍታት ከመሞከር መሳሪያ ወደ መማዘዝ ተኪዶ ዘግናኝ ግድያ መፈጸሙ ወያኔ ለዓላማው ስኬት ምን ያህል እኩይ ተግባር አንደሚፈጽም ያሳየ ነው፡፡ በአንጻሩም መለስ ብለው የኋላውን ማስታወስ ቀና ብለውም የዛሬውን ማሰብ የማይችሉ ሰዎችን ወያኔ በመብራ እየፈለገ እንዴት እንደሚጠቀምባቸው አሳይቶናል፡፡

የውድቀታችን ክፋት የመክሸፋችን ስፋት በወያኔ እኩይ ሴራ ትናንትም ሆነ ዛሬ የሰው ልጅ የገዛ ወገኑን በአሰቃቂ ሁኔታ ሲገድል ጠብ የሚያበርድ ሽማግሌ፣ እርቅ የሚፈጥር የሀይማኖት አባት መጥፋቱ ነው፡፡ የመንግሥት ባለሥልጣናትን ሕገ ወጥና ኢሰብአዊ ድርጊት ማውገዝ ቢያቅታቸው፣ መንግሥትን ለእርቅና ለሰላም መጠየቅ ቢያስፈራቸው ወዘተ እንዴት ታች ቀበሌና ወረዳ ላይ የሚፈጸሙ እጅግ ዘግናኝ የሆኑ አረመኔያዊ ድርጊቶችን ማውገዝና ጸብ አብርደው እርቅ ለማውረድ መንቀሳቀስ ይቸግራቸዋል፡፡ እነርሱም እንደኛ የነገሩ ወጣኝ ወያኔ መሆኑን ተረድተው የነገሩን ጫፍ ይዘን ሀረጉን ቢመዙት ከወያኔ እጅ ላይ እንደሚወድቁ ገብቷቸው ይሆን፡፡ አሳዛኝ፡፡ ከዚህ የባሰ ምን መክሸፍ አለ፤ ከዚህ በላይስ ምን የሀገር ሞት ይኖራል፡፡

ወያኔ በሥልጣን ላይ እስካለ አንድም ለጥቅም እያደሩ፤ሁለትም በወያኔ ፕሮፓጋንዳ እየሰከሩ ለጥፋት የሚሰለፉ መኖራቸው አይቀሬ ነው፡፡ ወያኔ ለደደቢት ትልሙ ተግባራዊነት እነዚህን በመሳሪያነት በመጠቀም ጊዜና ሁኔታ እየጠበቀ በሚፈጽማቸው ተግባራት ልዩነታችን አሁን ካለውም እየበሳ በመንደር ደረጃ ሊወርድ የመቻሉን ምልክት ነው ያየነው፡፡አማራ ኦሮሞ ትግሬ ሲዳማ ጉራጌ ወዘተ የሚለው ክፍፍል አላንስ ብሎ ትናንት ስልጤ ጉራጌ አይደለሁም ብሎ ተለየ፡፡ ይህን በማሳካት ግንባር ቀደሙን ሚና የተጫወቱት አቶ ሬዲዋን ሁሴን ከተቀዋሚ ፓቲ መሪነት የመንግሥት ባለሥልጣንነትን አገኙ፡፡ ይሄው ዛሬ ደግሞ ቅማንት ከአማራ ልለይ እያለ ነው፡፡ ወያኔ እስካለ ነገም በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ይሄው መለያየትና መናቆር ይቀጥላል፡፡

ወያኔዎች የማይወዱትንና ለሥልጣናቸው ጠንቀቅ አድርው የሚያዩትን ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነትን በአንድ ግዜ ለማጥፋት ብዙ ሞክረው አልተሳካላቸውም፡፡ ስለሆነም ለህዝብ ግልጽ ሆኖ በማይታይና ፈጥኖ በማይታወቅ መንገድ ቀስ በቀስ የማመንመንና የማክሰም ስራ እየሰሩ ነው፡፡ እነርሱ የሀገር መሪነቱን ሥልጣን ባጡ ማግስት ኢትዮጵያ አስራ ምናምን ብጥስጣሽ እንድትሆን እየሰሩ ስለመሆኑ እንደ ቅኝ ገዢዎች በየቦታው የሚቀብሩዋቸው ግዜ ጠብቀው የሚፈነዱ ፈንጂዎች እያሳዩን ነው፡፡

ወያኔን ለመገላገል ከሚደረገው ትግል ባልተናነሰ ይህ ሴራ ከዚህ በላይ ሰፍቶና ከፍቶ አንዳይሄድ በጽኑ መስራት ያስፈልጋል፡፡ስለሆነም ጎንደር ውስጥ ያለውን ውጥረት በቅጡ ሳይረዱ የጠቀሙ መስሏቸው ያልሆነ መልእክት በማስተላለፍ “የእብድ ገላጋይ ድንጋይ ያቀብላል” አይነት ተግባር የፈጸሙና አሁንም በመፈጸም ላይ ያሉ ወገኖች ቆም ብለው በማሰብ ጠብ እንዲበርድ ውጥረት አንዲተነፍስ በሚያስችል ተግባር ላይ ሊሰማሩ ይገባል፡፡ በጉዳይ ላይ የጠለቀ እውቀት ያላቸውና ነገሩን ከመሰረቱ የሚያውቁም የአካባቢው ሕዝብ እውነቱን ተረድቶ ከወያኔ ሴራ በማምለጥ ለጉዳዩን ራሱ ሰላማዊ መፍትሄ የሚያገኝበትን መንግድ ማመላከት ይጠበቅባቸዋል፡፡ ከተለያየ ጥቅምና ፍላጎት አንጻር ነገሩ እንዲከር የሚያደርጉ ሰዎች ካሉም ተለይተው መታወቅና መጋለጥ ይኖርባቸዋል፡፡

ወያኔ ራሱ የጫረውን እሳት ራሱ መልሶ አጥፊ መስሎ የሚቀርበው ነዳጅ እየጨመረ ይበልጥ ለማቀጣጠል ነውና በተለይ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ወገኖች በጥንቃቄና በንቃት ሊከታተሉት ይገባል፡፡ራስን በራስ የማስተዳደር መብት ጠያቂው ስለፈለገ ብቻ የሚያገኘው ሌላው ስለተቃወመውም የሚያስቀረው አይደለም፡፡ እንዴት ለምንና በምን ሁኔታ እንደሚጠየቅና ተግባራዊም አንደሚሆን በህግ የሚታወቅ በመሆኑ ባለሙያዎች ይህን ያብራሩ ያስረዱ፡፡

ራስን በራስ የማስተዳደር ቀልብ አማላይ ጥያቄ ትናንት የኢትዮጵያ ተማሪዎችን አማልሎ በውስጥ የተጠነሰሰውን ሴራ ሳይረዱና ከጀርባ ያለው ተልእኮ ሳይገባቸው ለኤርትራ መገንጠል አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ እንዳባቃቸው ሁሉ ዛሬም ብዙዎች ከቅማንት የማንነት ጥያቄ በስተጀርባ ሊኖር የሚችለውን የወያኔ ስውር ደባ ሳያውቁ ለወያኔ ዓላማ ማስፈጸሚያ መሳሪያ አንዳይሆኑ ማንቃት ማትጋትና ከዚህ የሚያልፉትን ማጋለጥ ይገባል፡፡ ሰሞኑን ያየነው ዘግናኝ ግድያ እንዳይቀጥልም ሁሉም በሚችለው መጣር ይኖርበታል፡ስሙን እንጂ ግብሩን ላልያዙት የሁልም እምነት አባቶችም እስቲ በዚህ ግዜ አንኳን ድምጻችሁ ይስማ የአስታራቂነት ግብራችሁ ይታይ አንበላቸው፡፡

The post ወያኔዎች ይገድላሉ ያገዳድላሉ | ይገረም ዓለሙ appeared first on Zehabesha Amharic.

የአዲስ አበባን ማስተር ፕላን በመቃወም የተነሳው ተቃውሞ ወደ ቱሎ ቦሎና ወሊሶ አካባቢ ተዳረሰ

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ላይ አዲሱን የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን በመቃወም እንደገና በምዕራብ ወለጋ የተቀሰቀሰው የተማሪዎች ቁጣ በተለያዩ የኦሮሚያ ክልሎች እየተዛመተ ይገኛል:: የዘ-ሐበሻ የዜና ምንጮች እንደሚሉት በተለይ ፖሊስ በሃሮማያ ዩኒቨርሲቲ በተማሪዎች ላይ የፌደራል ፖሊስ ግድያ ከፈጸመና ካቆሰለ በኋላ ይበልጥ ቁጣው እየናረ መጥቷል::
Zehabesha News

በተለያዩ የኦሮሚያ ክልሎች እየተዳረሰ የሚገኘው ተቃውሞ ዛሬ በቱሉ ቦሎና በወሊሶ አንዳንድ አካባቢዎች ደርሷል:: በነዚህ አካባቢዎች አዲሱን የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን በመቃወም ወጣቶች ድምጻቸውን ሲያሰሙ ውለዋል::

በባሌና በወለጋ አካባቢዎች አሁንም ውጥረቱ እንዳለ የሚጠቁሙት የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች ጉዳዩ አፋጣኝ እልባት ካላገኘ ወደ አስከፊ ደረጃ ሊደርስ እንደሚችል ያላቸውን ስጋት ጨምረው ገልጸዋል:: በተለይም እስከ ትናንት ድረስ በሃሮማያ ዩኒቨርሲቲ የሞቱት ተማሪዎች ቁጥር 3 የነበረ መሆኑና አሁን ደግሞ ወደ 4 ከፍ ማለቱ ጉዳዩን አጡዞት ይገኛል::

ይህ በ እንዲህ እንዳለም ዛሬም በ ም ዕራብ ወለጋ ጉሊሶ አካባቢ ከፍተኛ የሆነ ተቃውሞ ሲካሄድ መዋሉም ተዘግቧል:: አካባቢውን የፌደራል ፖሊስ ቢወረውም ሕዝቡ ተቃውሞውን በአደባባይ እየገለጸ አዲሱን የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን እየተቃወመ ነው::

The post የአዲስ አበባን ማስተር ፕላን በመቃወም የተነሳው ተቃውሞ ወደ ቱሎ ቦሎና ወሊሶ አካባቢ ተዳረሰ appeared first on Zehabesha Amharic.

መንግስት በጎንደር የ17 ሰዎች ሕይወት መጥፋቱን አመነ * አንዱን የገደልኩት እኔ ነኝ ብሏል

$
0
0

gonder

(ዘ-ሐበሻ) በትናንትናው የዘ-ሐበሻ የዜና እወጃ በጎንደር በ እስር ቤት ላይ በደረሰ ቃጠሎ የበርካታ ሰዎች ሕይወት መጥፋቱን ዘግበን ነበር:: መንግስት አንድ ሰው መግደሉን ሲያምን ሌሎቹ 16 ሰዎች ህይወት የጠፋው በቃጠሎው ወቅት ከ እስር ቤቱ ለማምለጥ ሲጋፉ ነው አለ::

የአማራ ክልል ፖሊስ ለመንግስት ሚድያዎች በሰጠው መግለጫው ትናንት ህዳር 21፣ 2008 በጎንደር ማረሚያ ቤት ከቀኑ 7፡30 አካባቢ በተነሳ የእሳት ቃጠሎ ከማረሚያ ቤቱ ለመውጣት በተደረገው ግፊያ የ16 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ አንድ ሰው ሊያመልጥ ሲል ከፖሊስ በተተኮሰ ጥይት መገደሉን ገልጿል::

እንደ አይን እማኞች ገለጻ ከሆነ ሕይወታቸው ያለፈው ሰዎች ቁጥር ከ30 በላይ ቢሆንም መንግስት ቁጥሩን ማሳነሱንና በ እጁ የጠፉትን ቁጥር ወደ አንድ ብቻ ማሳነሱ እንዳሳዘናቸው ገልጸዋል:: እንደ እማኞች ገለጻ አብዛኛው እስረኛ በመንግስት እጅ የተገደለ እንጂ ከ እስር ቤት ከ እሳት ለማምለጥና ለመውጣት ሲጋፉ አይደለም::

The post መንግስት በጎንደር የ17 ሰዎች ሕይወት መጥፋቱን አመነ * አንዱን የገደልኩት እኔ ነኝ ብሏል appeared first on Zehabesha Amharic.

የፕ/ር ብርሃኑ ነጋ በአውሮፓ ህብረት መገኘት ለኢትዮጵያ ዲሞክራሲ ሀይሎች የጋራ ዲፕሎማሲያዊ ድል ነው |ከዚህ ወዲያ አፍ እንዳመጣ “ሽብርተኛ” ማለት የህወሃት መሩ መንግስት እብደት ሆነ!

$
0
0

ቢላል አበጋዝ  ዋሽግተን ዲ ሲ

ረቡዕ ፣ ዲሴምበር 2 ቀን 2015

ዛሬ ኢትዮጵያ ለህወሃት መሩ መንግስት ተንፈራጦ መግዛት የምትመች አለመሆንዋን ማንም ዜና መከታተል ለሚፈልግ ግልጽ ነው።የህወሃት ባለስልጣናትም ከወትሮው በተለየ መልኩ እርስ በርስ እየተናቆሩ ነው።ተስፋ የቆረጡት ደግሞ ንብረት እያሸሹ ይገኛሉ።በቀይ ባህር አካባቢ አፍሪካ ቀንድን ሊያምስ የሚችል ደመናም ጥሏል ማለት ይቻላል።ሀብታም አረቦችም ልክ እንደ ህወሃት በስጋት ተወጥረዋል።ኢትዮጵያን ማተራመስ ቅር ሳይላቸው ማንኛውንም ድርጊት የሚፈጽሙ ለመሆናቸው የቅርብ ጊዜ ታሪካችን ይመሰክራል።

birhanu nega

ከላይ የጠቀስኩት አደጋ ማንጃበቡ ሳያንስ ዛሬ አስራ አምስት ሚሊዮን ወገናችን ለራብ ተዳርጓል።ይህን መከራ በመካድ የጀመረው ህወሃት ህይወት ለማትረፍ የሚጥር አይደለም።በኢትዮጵያ በያለበት እስራትና ግድያው በርትቷል።የፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በአውሮፓ ህብረት ስለ ኢትዮጵያ እንዲናገር መጋበዙ ያቀረብኩትን የኢትዮጵያ ሁኔታ ለመንግስታቱ ተወካዮች መግለጽ ብቻ ሳይሆን አጣዳፊ ሁኔታ መፈጠሩንም የማስስጨበጥ ሁኗል። ኢትዮጵያን የፋሺት ኢጣሊያ መንጋጋ ሲያኝካት የተሰደዱ አርበኞች በዓለም መድረክ ጮሆውላት ነበር። ዛሬም በህወሃት መንጋጋ ስትታኘክ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ከኢትዮጵያውያ ወገኖቹ ጋር ሆኖ ድምጹን ከፍ አድርጎ አሰምቶላታል።ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ይህን የፈጸመው በግንባር ሆነው ህወሃት መሩን መንግስት ብርክ እያስያዙ ያሉትን የኢትዮጵያን ጀግኖች ከበረሃ ተለይቶ ነው።

የኢትዮጵያ ሁኔታ ጊዜ የማይሰጥ ነው።ህወሃት መሩ መንግስት በመለስ ዜናዊና ጀሌዎቹ አማካይነት ያፈላው የጥላቻ ጥንስስ ድንገት ሳይፈነዳ አደጋውን ሊገታ የሚችል ዝግጅት ማድረግን ይጠይቃል።ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ሁሉም የሚወከልበት ጊዜያዊ መንግስት ካልቆመ ወያኔ ፈጽሞ የመግዛት ሀይሉን ሊያጣ የሚችልበት ጊዜ እሩቅ አይሆንም።ህዝቡ በቃኝ ለማለቱ ምልክቶቹ መበራከታቸው ይህን አመላካች ነው።የኢትዮጵያ ኦርቶዶስ ሃይማኖትን ተቋማት ጣልቃ በመግባት አዳክሟል።የእስልምና ሃይማኖት ተቋማትን ደፍሮ መሪዎችን ለእስር ዳርጓል።ነጻነትና ዜግነት በየፈጁ ተደፍሯል።

የዓለም መንግስታት በተለይ ሃያላን የኢትዮጵያን ጉዳይ ወደጎን በመተው ህወሃት መሩን መንግስት መወንጀል ሳይሆን በስመ ሽብርተኝነትን መቋቋም አብረውት እየሰሩ ነው።በታሪካችንም የፋሺት ኢጣሊያውን ሙሶሊኒንም አይዞህ ያሉት ነበሩ።ሁሉም ለየራሱ ጥቅም በዓለም ዲፕሎማሲ ሰልፉን ያስተካክላል።በየጊዜውም ይለውጣል።ኢትዮጵያን የምንል አንድ መሆን የግድ የሚለን ጊዜ አሁን ነው።ህወሃት መሩ መንግስትማ ለሙግት፡ለመልስ እንኳን ያቆመው ቅጥረኛ የውጭ አገር ተላላኪን ነው ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በዋለበት መድረክ።የህወሃት ድንቁርና አንድ መገለጫ ምልክት ነው።የፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በአውሮፓ ህብረት መግለጫ መስጠት ህወሃት መሩን መንግስት ለሚቃወሙና ለተራበው ከተሜ ገጠሬ ወገናችን ትልቅ ግምት የሚሰጠው ዲፕሎማሲያዊ ድል ነው።ኢትዮጵያ በዚህ የመከራ ዘመን ለታደጓትን አላህ ለነሱም ይመስክርላቸው።

 

ድል ለዲሞክራሲያዊ  ሀይሎች ሁሉ!

ኢትዮጵያ በአንድነትዋ በነጻነት ለዘለዓለም ትኑር!

አላህ ኢትዮጵያ ይጠብቃት!

 

 

 

The post የፕ/ር ብርሃኑ ነጋ በአውሮፓ ህብረት መገኘት ለኢትዮጵያ ዲሞክራሲ ሀይሎች የጋራ ዲፕሎማሲያዊ ድል ነው | ከዚህ ወዲያ አፍ እንዳመጣ “ሽብርተኛ” ማለት የህወሃት መሩ መንግስት እብደት ሆነ! appeared first on Zehabesha Amharic.

Viewing all 8745 articles
Browse latest View live