Quantcast
Channel: ዘ-ሐበሻ – Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 8745 articles
Browse latest View live

መኢአድ ፕሬዝደንት አቶ ማሙሸት አማረ የፍርድ ቤት ውሎ

$
0
0

ለገሰ ወ / ሃና

መኢአድ ፕሬዝደንት አቶ ማሙሸት አማረ ዛሬ ሰኔ 27 /2007 ዓም ፍርድ ቤት ቀጠሮ እንዳለው ገልጬ ነበር በቀጠሮው መሠረት ዛሬ አቅርበውታል

Mamushetሰኔ 15 / 2007 ዓም በቀረበበት ወቅት ምስክሮቹ አልቀረቡም ተብሎ ለዛሬ ምስክሮቹ ታስረው እንዲቀርቡ ነበር ታዞ የነበረው
ዛሬ ሰኔ 27/2007 ዓም 4 :00 አካባቢ የተሠየመው ችሎት ምስክሮቹ ዛሬም እንዳልቀረቡ በመግለጽ ሰኔ 15/2007 ዓም ቀርበው እንደነበረ ምስክርነቱን ያልሰጡት ተደራራቢ መዝገብ ስለነበረ እንደሆነ ተገልጿል በእለቱ ማለትም ሰኔ 15/2007 ተሰጥቶ የነበረው ምክንያት ምስክሮች አልቀረቡም በሚል ነበር ለዛሬ ታስረው ይቅረቡም የተባለው በዚህ ምክንያት ነበር ዛሬየተገለፀው ሀምሌ 15/2007 ዓም ቀርበው እንደነበረ ከዳኛ ተገልጿል
በዛሬው እለትም ምስክሮቹ ፍርድ ቤት መቅረባቸው ምስክሮቹን የሚያውቃቸው አረጋግጦልኛል ችሎት ከመሠየሙ በፊት አቃቤ ህግ አነጋግሯቸው እንደነበረ ከዛ እውጭ ቆይተው የማሙሸት ጉዳይ ቀጠሮ ከተሰጠበት በኇላ አለን ማለታቸው አይተናል
አቃቤ ህግ በማሙሸት ላይ ያዘጋጃቸውን የሀሰት ምስክሮች ቀርበው እያለ እንዳልቀረቡ አድርገው ምስክሮቹ ታሰረው ይቅረቡ የሚል መልስ ከችሎት ተሰጥቷል በእውነቱ የኢትዮጵያን ውስጥ ያለውን እውነት ያልተገለጠለት ወይም ያልተገነዘበ ሰው ይህንን አላምንም ማለቱ አቀርም እንዲያምን አይገደድም እውነቱ ግን ይህ ነው ማመን ይገባዋል
ምንም እፍረት ያልፈጠረባቸው የዘመናችን ክፉ እና አረመኔዎች ውንብድና ያስገርማል አቃቤ ህግ በማሙሸት ላይ ያዘጋጃቸውን የሀሰት ምስክሮች ቀርበው እያለ እንዳልቀረቡ አድርገው ምስክሮቹ ታሰረው ይቅረቡ የሚል መልስ ከችሎት ተሰጥቷል አቃቤ ህግ በማሙሸት ላይ ለምስክርት የመለመላቸውን ሰዎች ለምን ሊያስመሠክር እንዳልቻለ በይታወቅም ማሙሸትን በእስር ለማቆየት ይመስላል
የተከሰሰበት አንቀጽ እስከ 6 ወር የሚደርስ ቀላል እስራት እና በብር አስከ 500 ብር የሚያስቀጣ ነው ማሙሸት ከታሰረ በህግ ያስቀጣል የተባለውን ጊዜ ከግማሽ ላይ ታስሮል
ይህም ሆኖ የቦሌ ምድብ ችሎት በነጻ አሁን የሚቀርብበት አራዳ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት 5000 አስይዞ ይዉጣ ቢባልም ገንዘቡ ተይዟል እሱም ተስሮ እዚሁ ፍርድ ቤት ካላይ የተገለፀውን ምክንያት እየደረደሩ ያሰቃዩታል የፍርድ ቤቱን እና የፓሊስን አካሄድ ስንመለከት ማሙሸትን አስሮ ለማሰቃየት እንደሆነ መገንዘብ ይቻላል
ዛሬም እንቀደሙት ጊዜያት ቀጠሮ ሰጥቷል ምስክሮቹ ታስረው ነሐሴ 5/2007 ዓም 5:00 ሰአት እንዲቀርቡ ታዟል ያኔ ደግሞ ምን እንደሚባል ጊዜው ሲደርስ የምናው ይሆናል የሀገራችን የፍርድ ሂደት ይህንን ይመስላል ::
በሌላ በኩል
አብርሃም ጌጡ ያለበት ሁኔታ እጅግ አሳስቦናል
የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ ) የውጭ ግንኙነት ሀላፌ አቶ አብርሃም ጌጡ ታስሮ ከነበረበት አዲስ አበባ ፓሊስ ኮሚሽን (3ኛ ) ከሀምሌ 15/2007 ዓም ጀምሮ ወደ ማዕከላዊ ተወስዷል
ቀደም ሲል ቀርቦበት የነበረው ሚያዝያ 13/2007 በሊቢያ የታረዱ ወገኖቻችንን በተመለከተ መንግስት የጠራውን ሰልፍ የልደታ ክፍለ ከተማ ወጣቶችን አደራጅተህ ሚያዝያ 14/2007ዓም የተጠራውን ሰልፍ እንዲበጠበጥ አድርገሃል የሚል ነበር
ይህንን ክስ በተመለከተ በልደታ ፍርድ ቤት እና በአራዳ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ፓሊስ እያቀረበ የጊዜ ቀጠሮ እየጠየቀበት ቆይቷል ይቀርባል ባልተባለበት በበአል ቀን (የኢድ በአል እለት )ሀምሌ 10 2007 ዓም አራዳ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አቅርበው ዳኛ ለመጨረሻ ጊዜ በማለት ለፓሊስ 7 ቀን ሰጥቶት ነበር ፓሊስ በተሰጠው ቀን ሀምሌ 17 /2007 ዓም መቅረብ ሲገባው አላቀረቡትም ፍርድ ቤት ይቅረብ ከተባለበት 2 ቀን ቀደም ብሎ ወደ ማዕከላዊ አዛውረውታል በቀጠሮው መሠረት ፍርድ ቤት ሄደን ስንጠይቅ አልቀረበም በምን ምክንያት እንዳልቀረበ ስንጠይቅ ክሱ መቋረጡን ነግረውናል ጠበቃው በተደጋጋሚ አብርሃምን ለማነጋገር ወደ ማዕከላዊ ቢሄድም አብርሃምን ማናገር እንደማይችል ተነግሮታል
በአሁኑ ሰአት አብርሃም በምን ሁኔታ ላይ እንዳለ አልታወቀም በዚህ ምክንያት ቤተሰቡና የትግል አጋሮቹን ስጋት ላይ ጥሏል ይህንን ስጋታችንን
በሰብአዊ መብት ዙሪያ የምትሰሩ ድርጅቶችና የሚዲያ ተቋማት የወንድማችን የአብርሃም ጌጡን ሁኔታ እጽንኦት በመስጠት የሚቻላችሁን እንድታደርጉ እናሳስባለን ።


ከፕሬዝዳንት ኦባማ ጉብኝት ማግስት ….. ግርማ ሠይፉ ማሩ

$
0
0

 

girmaseifu32@yahoo.com , girmaseifu.blogspot.com

Girma  Seifuኦባማ ኢትዮጵያን መጎብኘት አለበት? የለበትም? የሚለው አጀንዳ ማከራከሩ መቆም ያለበት ጉዳይ ይመስለኛል፡፡ ፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማ መጥተዋል በቃ!! በእኔ እምነት ኦባማ ኢትዮጵያ የመጡት ኢትዮጵያ ባሳየችው ፈጣን ዕድገት ተመስጠው፣ ይህ ዕድገት ካፈራው ፍሬ የአሜሪካን ህዝብ እንዲቃመስ (ብዙዎቹ እንደሚሉት ቦይንግን እየገዛንም ቢሆን) ብለው አይደለም፡፡ በእኔ እምነት ኦባማ ከስልጣን ከመልቀቃቸው በፊት የአባታቸውን ሀገር ኬኒያን መጎብኘታቸው በብዙ መመዛኛ የግድ አስፈላጊ ነገር ነበር፡፡ ለዚህ አንድ መናጆ በቅርብ ያለች ኢትዮጵያ እንድትሆን የግድ የሚሉ ነጥቦች ተገኝተዋል፡፡ በዋነኝነት ደግሞ ሁሉቱ ሀገሮች በግንባር ቀደምትነት እየተፋለሙት የሚገኘው አልሸባብ የሚባለው የሽብር ቡድን ነው፡፡ በአሜሪካ መንግሰት ዘንድ ይህ ጉዳይ ትኩረት ተሰጥቶት የኦባማ ጉብኝት ፈቃድ እንዲያገኝ ይሁንታ ሊያስገኝ የሚችል ነጥብ ነው፡፡ ኢትዮጵያ በተጨማሪ የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ በመሆኗ ኦባማ በፀረ ሽብር ህጉ ህብረት አፍሪካዊያን በጋራ እንዲቆሙ በአፍሪካ ህብረት ፅ/ቤት በኩል ማስተላለፍ አንዱ መንገድ ነው፡፡ ይህ ደግሞ የሚቻለው የሁሉም አፍሪካ ተወካዮች የሚገኙባት ሀገር ኢትዮጵያ እንደሆነች የሚስት የለም፣ ይህ ኢትዮጵያ ሀገራችን በዓለም ቁንጮ በሆነች ሀገር መሪ እንድትጎበኝ ዕድል ሰጥቷታል፡፡ እንዲህም ሆኖ ኢትዮጵያ ውስጥ ምንም በጎ ነገር የለም የሚለው ነገር በፍፁም የለኝም፡፡

በእኔ እምነት ኦባማ አፍሪካን መጎብኘት ካለባቸው እና አምስት ሀገር መመርጥ ካለባቸው ኢትዮጵያ አንድ መሆን እንዳለባት አምናለሁ፡፡ ይህ ደግሞ ለኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት ካለኝ ግምት እንጂ ሀገሪቱን የሚመራው መንግሰት ኢህአዲግ ስለሆነ አይደለም፡፡ ለማንኛውም ፕሬዝዳንት ኦባማ ኢትዮጵያ የምትባል የሰው ዘር መገኛ የሆነች ድንቅ ሀገር ጎብኝተው ተመልሰዋል፡፡ ከዚህ ጉብኝት ምን ጠበቀን? ምን አገኘን? የሚለው ነገር በቅጡ መታወቅ አለበት፡፡ ይህ ጉዳይ ወደፊት በደንብ የሚፈተሸ ሲሆን አሁን ግን ካለብኝ ስጋት አንፃር አሳቤን ላጋራችሁ፡፡

እጅግ ብዙ የሚባሉ ምን አልባትም በፖለቲካ ውስጥ ንቁ ተሳትፎ አለን የሚሉ ሰዎች ፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማ መጥተው ይህን አንባገነን መንግሰት በአደባባይ እንዲያውግዙ እና ይህን የመሰለ ድርጊታቸውን የማያቆሙ ከሆነ ዲፕሎማሲያዊም ሆነ ከዚያ የዘለለ እርምጃ ሊወስዱ እንዲሚችሉ ማስጠንቀቂያ እንዲሰጡላቸው ነበር፡፡ ከዚያ በመነሳት ኦባማ በጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት “በዲሞክራሲያዊ አግባብ የተመረጠን መንግሰት በሀይል ማውረድ ተገቢ አይደለም” የሚለውን ቁንፅል ሃሳብ ይዘው ለምን አሉ በሚል ቡራ ከረዩ ሲባል ታዝቢያለሁ፡፡ ፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማ እንኳን ሰው ሀገር ለጉብኝት ሄደው አይደለም በሀገራቸው ቤተ መንግሰት (ኋይት ሀውስ) ተቀምጠው እንዲህ ዓይነት ከዲፕሎማሲ መስመር የወጣ የአንድን ሀገር መንግሰት ለማዘዝም ሆነ ለማስጠንቀቅ አይችሉም፡፡ በተለይ ኦባማ ከሚከተሉት የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ አንፃር ይህ በፍፁም የሚያስኬድ አይደለም፡፡ ለምሳሌ በሪፐብሊካን ዘመን ወዮልሽ ስትባል ከነበረችው ኢራን ጋር የተሻለ የሚሉትን መቀራረብ እና መነጋገር እንጂ ማስፈራራት ተገቢ አይደለም ብለው ይስራሉ፡፡ ኦባማ አሁንም ኢትየጵያ መጥተው ያስተላለፉት መልዕክት የኢትየጵያ መንግሰት አንባገነን ነው ብሎ በመራቅ ሳይሆን ቀርቦ በማነጋገር ማለዘብ ይቻላል ነው፡፡ ከቻይና ጋርም እንስራለን ሲሉን መልዕክቱ ግልፅ ነው፡፡ ኦባማ “በርማ” የሄዱት መንግሰቱ ዲሞክራሲያዊ ስለሆነ አይደለም፡፡ ኢትየጵያም የመጡት እንደዚሁ፡፡

የኦባማ ጉብኝት የአባታቸውን ትውልድ ሀገር ለመጎብኘት ካላቸው ቁርጥ አቋም ጋር መናጆ ተደርገን ነው የምንል ሰዎችም ብንሆን የፕሬዝዳንቱ ጉብኝት ምንም የሚያመጣው ፋይዳ የለም የሚል እምነት የለንም፡፡ ይህን ፋይዳ ግን ገዢው ፓርቲ እና መንግሰት እንዴት ይጠቀሙበታል የሚለው ነው፡፡ በሚያሳዝን ሁኔታ ገዢው ፓርቲ በዋነኝነት ይህን ጉብኝት መጠቀም የጀመረው ለፕሮፓጋንዳ ፍጆታ እና ይህን ጉብኝት የተቃወሙትን በተለይ ግልፅ ተቃዎሞ ሲያሰሙ የነበሩትን በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊና ትውልደ ኢትዮጵያዊያንን ለማውገዝ እና ለማሸማቀቅ ነው፡፡ ይህ ትርፍ ከአስገኘም የአጭር ጊዜ እንጂ ዘላቂ ትርፍ ሊያመጣ የሚችል ሳይሆን መቃቃርን የሚያፋፋ አካሄድ ነው፡፡ ለዚህ ደግሞ የኦባማ ጉብኝት ትርፍ በአፍንጫችን ቢወጣ ይሻለን ነበር፡፡ ከዚህ መንግሰት ባህሪ አንፃር ከኦባማ ጋር በሚስጥር በተደረገ ውይይት መነሻ የሚደረጉ ፈጣን የፖሊሲም ሆነ የአስራር ለውጥ በግሌ አልጠብቅም፡፡ ምክንያቱም “ኦባማ እንዲህ አድርጉ ብሎ አደረጉ” መባል አይፈልጉም፡፡ በሌላ ፅንፍ ያሉትም ቢሆኑ “ኦባማ አዟቸው አደረጉ” ማለታቸው አይቀርም፡፡ ይህ በኢትዮጵያዊ ስነ ልቦና ሲታይ ፊት ለፊት ያለው ሲሆን ይህ ደግሞ ለለውጥ እጅግ ደንቃራ የሆነ አስተሳሰብ እንደሆነ ሳይታለም የተፈታ ነው፡፡ ይህን ሊሰብር የሚችል መሪ ያለን አልመሰለኝም፡፡ አግኝተን ግምቴ ልክ ባይሆን ደስ ይለኛል፡፡

ሌላው ከፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማ ጉብኝት ከፍተኛ ጥቅም ይገኛል ተብሎ የሚጠበቀው በገፅታ ግንባታ እና እርሱን ተከትሎ የሚመጣው የግል ባለ ንዋዮች የሚያደርጉት ኢንቨስትመንት ነው፡፡ ከፕሬዝዳንቱ ጋር እጅግ ብዙ ጋዜጠኞች ትክክለኛውን የኢትዮጵያ ገፅታ በሚችሉት መስመር ሁሉ ለማግኘት እንደሞክሩ ይታመናል፡፡ እነርሱን መሰረት አድረገው መረጃ የሚተነትኑ እና የሚያወጡ አካላት የሚሰጡት ግመገማ ውጤት ለኢንቨስተሮች ውሳኔ መሰረት ሆኖ ያገለግላል፡፡ የአሜሪካና የቻይና መሪዎች በሀገሮች ጉብኝት ሲያደርጉ ጉልዕ ልዩነት አለ፡፡ የቻይና ፕሬዝዳንት መጥተው ጉብኝት አድርገው ቢሄዱ አንድ ቃል ሊገቡ የሚችሉት ነገር ይኖራል፡፡ መንግሰታቸው ከሚመሯቸው ተቋማት የተወሰኑትን በኢትዮጵያ ውስጥ ኢንቨስት አድርጉ ብለው ትዕዛዝ ሊስጡ ይችላሉ፡፡ ነገር ግን ፕሬዝዳን ባራክ ኦባማ ይህን ለማድረግ እድልም መብትም የላቸውም፡፡ የአሜሪካ ባለሀብቶች ከመንግሰታቸው ጥበቃን እንጂ የት ኢንቨሰት እንደሚያደርጉ መመሪያ አይሰጣቸውም፤ አይቀበሉም፡፡ የሚገርመው በራሳቸው ውሳኔ ባደረጉት የኢንቨስትምንት ውሳኔ ግን መንግስታቸውን በቂ ጥበቃ እንዲያደርግላቸው ያስገድዱታል፡፡ ይህ ነው የአሜሪካ ስርዓት፡፡

የኢትዮጵያ መንግሰት ከኦባማ ጉብኝት ውጤት ይጠብቅ ከሆነ ያለ ምንም ይሉኝታ በሀገራችን የግል ኢንቨስትመን (በተለይ የውጭ) እንዳይመጣ ማነቆ የሆነውን የውስጥ ሰላምን (ፀጥታ አላልኩም) ማምጣት አለበት፡፡ ይህ ማለት በጠምንጃ ታፍኖ ዝም ያለ ህዝብን መፍጠር ሳይሆን በዲሞክራሲያዊ ሰርዓት ውስጥ የሚገኝ ስላምን መፍጠር ይጠበቅበታል፡፡ ለዚህም ዋነኛ ግብዓት ሆነው የሚያገለግሉትን ነፃ ሚዲያ፣ የመድበለ ፓርቲ ስርዓት ግንባታን፣ በህገ መንግሰት ላይ የተደነገጉትን የስብዓዊ መብት ድንጋጌዎች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ መፍታት፣ ልዩነቶች በህጋዊ አግባብ መፍታት የሚቻልበት የፍትሕ ሰርዓት መዘርጋት፣ ወዘተ እጅግ በጣም አስፈላጊ ናቸው፡፡ እነዚህ ሲሟሉ የአውሮፓና አሜሪካ ባለሀብቶች ይመጣሉ፣ ኦባማም ኢትዮጵያን ባይጎበኙም፡፡

ኦባማ በአፍሪካ የስልጣን ገደብ ማጣት፣ ሙስና፣ የነፃው ፕሬስ እመቃ ወዘተ ለዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ካንሰር መሁኑን አበክረው ገልፀዋል፡፡ የሚገርመው መሪዎቻችን ያጨበጭቡ ነበር፡፡ ታመሃል ሲባል የሚያጨበጭብ ታማሚ አንባቢ ልብ ሊለው ይገባል፡፡ በአኔ እምነት በካንሰር የተያዘ የፖለቲካ ስርዓት ውስጥ በሚገኝ ኢኮኖሚ ውስጥ መዋለ ንዋይ ለማፍሰስ የሚመጣ ይኖራል ማለት የሚታሰብ አይደለም፡፡ ከኦባማ ጋር የመጡት የልዑካን ቡድኖች ውስጥ የሚገኙት የንግድ ማህበረሰብ ተወካዮች በኢትዮጵያ ውስጥ የአንድ ፓርቲ አንባገነን ስርዓት እንዳለ አይሰሙም፣ በሲቪክ ማህበረስብ ውስጥ እየተደረገ ስለ አለው እመቃ አይረዱም፣ ከሲቪል ማህበራት ጋር የተደረገው ውይይት በሚዲያ ሳይገለፅ በሚስጥር ውይይት ይደረግበት ማለቱ ምን ማለት እንደሆነ አይገባቸውም ማለት እነዚህ ባለ ሀብቶች በሚወስዱት ውሳኔ ሳይሆን በድንገት ባለሀብት የሆኑ ያስመስላል፡፡ ኢቲቪ ማታለል የሚችለው በኢቲቪ መረጃ መሰረት አድርገው ውሳኔ ለሚያሳልፉ ብቻ ነው፡፡

በኦባማ ጉብኝት ምክንያት አንድ የተገኘ ውጤት አለ፡፡ ይህ ውጤት ለአሜሪካም ለኢትዮጵያም እኩል ነው ብለን አናምንም፡፡ የኢትዮጵያ እና የአሜሪካ መንግስታት ባስማማቸው ጉዳይ ላይ ቃል ኪዳናቸውን አድሰዋል፡፡ ከዚህ በፊት በሚስጥር ተይዞ የነበረው የኢትዮጵያ የምስራቅ አፍሪካ የፀረ ሽብር (በተለይ አልሻባባም በሚመለከት) ኃይል ግንባር መሪ መሆን አሁን በይፋ ታውጇል፡፡ ለዚህም የሚያስፈልገውን ሁለቱም መንግሰታት ለማዋጣት አቅሙ አላቸው፡፡ እኛ ደምና ነብሳችንን እነርሱ ደግሞ ዶላር ሊሰጡን ተሰማምተናል፡፡ በዚህ አጀንዳ ዙሪያ በሁለቱ መንግሰታት ዘንድ ልዮነት የለም፡፡ ይልቁንም ሁለቱ ሀገራት በዚህ አጀንዳ ዙሪያ ባላቸው የጫጉላ ጊዜ ሌሎች አጀንዳዎች እንዲገፉ እና በተለይ የኢትዮጵያን የግፍ ቀን እንዲረዝም በር ከፍተዋል፡፡ የኢትዮጵያ መንግሰት አልሻባብና መሰሎችን ብቻ ሳይሆን ለዲሞክራሲ የምጮሁ ኢትዮጵያዊያንንም ከእነዚህ ጋር ቀላቅሎ ለመውቀጥ አስፍስፎ ይገኛል፡፡ እሰከ ዛሬ የበላቸውን እነ አንዱዓም አራጌን፣ ናትናኤል መኮንን፣ ሀብታሙ አያሌው፣ ዳንኤል ሺበሽን፣ ጋዜጠኞች፣ ብሎገሮች ወዘተ ጨምሮ ማለት ነው፡፡

የዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንበታን በሚመለከት አሜሪካኖች ምክር የሚሰጡ ሲሆን የወዳጅ ምክርን መስማት ያለመስማት ደግሞ በኢትዮጵያ መንግሰት እጅ የሚገኝ ነው፡፡ በኢትዮጵያ መንግሰት አተያየ በተለይ በጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም አገላለፅ “እንቁላል በአንድ ቅርጫት” አይቀመጥም፡፡ የፖለቲካም ሆነ የኢኮኖሚ ወዳጅ አንድ አይበቃም፡፡ ከቻይናም ከአሜሪካም ያስፈልጋል፡፡ አንዱ ቢያኮርፍ በአንዱ የሚል ዘይቤ ተጀምሮዋል፡፡ ኦባማ ማኩረፍና መራቅ አይጠቅምም- መነጋገር ነው የሚያዋጣው ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ መንግሰት ምንም ግልፅ የሆነ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ቢፈፅም፣ ከዓለም ሁለተኛ ሚዲያ አፋኝ መንግሰት ቢሆኑም ኢትዮጵያን ከሚመስል ትልቅ ሀገር ጋር ጠብ አያስፈልግም፡፡ የኢትዮጵያ መንግሰትም ቢሆን አሜሪካ ምንም እንኳን ኒዎሊብራል የሆነች ሀገር ብትሆን እና በሀገሯ ኢኮኖሚያዊ ፍትህ የሚያሰፍን መንግሰት ሳይሆን ገበያ የሚመራት ቢሆንም፣ አይንሽን ላፈር ብሎ መሳደብ ጥቅም የለውም፡፡ ሰለዚህ ሁለቱ መንግሰታት የጫጉላ ጊዚያቸውን በሚያስማማቸው ጉዳይ ላይ ያደርጋሉ፡፡ የእኛ ደምና ነብስ እንዲሁም ዲሞክራሲያዊና ስብዓዊ መብታችን አሳልፎ መስጠት፣ የአሜሪካኖች የታክስ ከፋይ ገንዘብ ለጊዜውም ቢሆን ጋብቻ ፈፅመዋል፡፡

ቸር ይግጠመን

 

 

 

 

“ገንዘብ አላችሁ” ምንጩን ለሌላ ልቀቁ –ከ ፕ/ር ጌታቸው ኃይሌ

$
0
0
Getachew Haile

ፕ/ር ጌታቸው ኃይሌ

“ገንዘብ አላችሁ” ምንጩን ለሌላ ልቀቁ ከጌታቸው ኃይሌ ፕሬዚዴንት ኦባማ አዲስ አበባ ላይ ለተሰበሰቡት የአፍሪካ መሪዎች ሰኞ ዕለት ሐምሌ 20 ቀን 2007 ዓመተ ምሕረት ንግግር እንዳደረገላቸው እናስታውሳለን። በንግግሩ ውስጥ ሥልጣን ለባለተራ የሚተው እንጅ እስከ ዕለተ ሞት የሚስገበገቡለት እንዳይደለ ለመሪዎቹ ሲያስታውሳቸው ገንዘብ እንደሆን አከማችታችኋል አላቸው። አፍሪካውያንን በሥልጣን ኮርቻ ላይ ለመንጠላጠል፥ ከተንጠላጠሉ በኋላም እዚያው ተጣብቆ ለመኖር የሚያጓጓቸው ገንዘብ ለመግፈፍ ብቻ ሊሆን አይችልም። ይህ አንዱ ነው እንጂ፥ ሁሉም አይደለም። ለምሳሌ፥ የደርግ ባለሥልጣኖች ለሥልጣኑ የተስገበገቡት ገንዘብ ለማካበት አይመስለኝም። ባለሥልጣን መሆን ስም ያስጠራል። አልባሌ ሆኖ ከመቅረት ያድናል። ሥልጣን ለኀይለ ማርያም ደሳለኝ የጠቀመው ይኸ ብቻ ይመስለኛል። በችሎታቸውና በሕዝብ ምርጫ የታላላቅ አገሮች መሪዎች ከሆኑ ጋር እኩል ይቆማል፤ አብሮ ይበላል። ከሰው ዓይንና ከሰው አፍ ላለመጥፋት ብዙ ሰዎች የቱን ያህል እንደሚጓጉለት በርሊን ከተማ ሄዶ ለሰፊ ሕዝብ በመታየት ራሱ መስክሯል። —-[ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]–

 

በአርበኞች ግንቦት 7 ሕዝባዊ ትግል ላይ ከየአቅጣጫው እየተሰነዘሩ ያሉ ፈተናዎችና ማርከሻ መድኃኒታቸው!

$
0
0

Birhanu nega photo

እግዚአብሔር ይመስገንና አሁን የነገዋን ነጻይቱን ኢትዮጵያ ለማየት መንገዱ ላይ ቆመን መራመድ የቻልንበት ሰዓት ላይ ደርሰናል፡፡ ይሄ ትልቅ ትልቅ እመርታ ነው፡፡ አሁን ባለንበት ሁኔታ ራሱ ወያኔ ተሸንፎ እንደወደቀ መቁጠር ይቻላል፡፡ የቀረው የባለሥልጣኑ የጊዜ ጉዳይ ነው፡፡ ነገ የሚሆነው ነገ እንጅ ዛሬ ስለማይሆን ብቻ ነው፡፡ ነገ ግን ዛሬ መሆኑ አይቀርምና ነገ የምንጨብጠውን ዛሬ እንደጨበጥነው መቁጠር ይቻላል፡፡

ይህ ታላቅ እመርታ እንዳይመዘገብ ወያኔ የሀገር ክህደት በመፈጸም ለጎረቤት ሀገራት ሉዓላዊ የሀገሪቱን መሬት እየቆራረሰ ከመስጠት ጀምሮ በተለያየ ጥቅም በመያዝ መሸሻ መሸፈቻ መደራጃ መንቀሳቀሻ መንደርደሪያ እሱ ሱዳንን ይጠቀምባት እንደነበረውና ከሱዳን ያገኝ የነበረውን ድጋፍና ምቹ ሁኔታዎች የሚሰጠን ጎረቤት ሀገር እንዳይኖርና እንዳናገኝ ለማድረግ ያላደረገው ነገር ያላስቀመጠው መሰናክል ያልቆፈረው ጉድጓድ አልነበረም፡፡ ይሄንን ዕድል ልናገኝ የምንችልበት አንድ ቦታ ከተገኘ የኢትዮጵያ ሕዝብ ብሶተኛ ከመሆኑና ይሄንን አጋጣሚ የሚጠባበቅ ከመሆኑ የተነሣ አርፎ ተቀምጦ የነበረውም አማራጭ ስላጣ ብቻ እንደሆነ ይሄንን ዕድሉን ባገኘ ጊዜ ግን ወያኔ ዕድሜ እንደማይኖረው በአጭር ጊዜ ውስጥ እንደሚያልቅለት ጠንቅቆ ያውቀዋልና፡፡ መሸሻ መሸፈቻ ለማሳጣት ይሄንን ያህል ርቀት የተጓዘው ወያኔ ይህ አሁን ከባሕረ ምድር (ኤርትራ) ላይ ያገኘነውንም ለማሳጣት ለማበላሸት ይሄም አልሆን ሲለው ሐሰተኛ የፈጠራ ወሬና ሴራ በመጠንሰስ እንድንሸሽና እንዳንጠቀምበት ለማድረግ በከፍተኛ ደረጃ ሲጥር ነበር እየጣረም ይገኛል፡፡ እውነቱን መለየት ማወቅ መረዳት እስኪያቅተን ድረስ ባሕረ ምድር የመሸጉትን የነጻነት ታጋዮችን ትግል ሊያደናቅፍ ሊያሰናክል ሊያጨናግፍ የሚችሉ የሆኑና ያልሆኑ ነገሮችን መሠረት ያደረጉ ስሞታዎችን ስም ማጥፋቶችን ድምዳሜዎችን የያዙ መጣጥፎች አሁን ማንነታቸው ይበልጥ ግልጽ እየሆኑ እየታወቁ በመጡ ግለሰቦች ቀደም ሲል ግን በጣም ተአማኒነት በነበራቸው ግለሰቦችና ቡድኖች ድረ ገጾች ላይ እየተለቀቁ እየቀረቡ ትግሉን እንድንጠራጠር እንዳናምን እንድንሸሽ ከዚያም አልፎ በጠላትነት እንድንፈርጅ ለማድረግ ከባድ ከባድ ጥረቶች ሲደረጉ ቆይተዋል፡፡

ከዚህ በኋላም ወያኔ እስካለ ድረስና የዕጣ ፈንታው የመጨረሻ መጨረሻ ሰዓት የደረሰ መስሎ እስከታየው ድረስ አያደርገውም የሚባል ነገር ሳይኖረው ሊያደርገው የማይችለው ምንም ዓይነት ነገር ሳይኖር እስከ የመጨረሻ ህቅታው ድረስ የጣረሞቱን በመንፈራገጥ አቅሙን አሟጦ በመጠቀም የተቻለውን ሁሉንም ዓይነት ጥረቶች በማድረግ ይቀጥላል እንጅ ይቆማል ብላቹህ አታስቡ፡፡ አሁን አሁን ከእነዚያ ስም ማጥፋቶች የተጋነኑ ስሞታዎችና የፈጠራ ውንጀላዎች ትክክለኛ የተፈጸሙ ከሆኑትም ጀርባ የወያኔ እጅ እንዳለ ግልጽ እየሆነ መጥቷል፡፡ እኔ በእርግጥ ጥርጣሬው የነበረኝ ቢሆንም አብዛኞቻችን ይሄንን አለመገመታችን አለመጠርጠራችን ምን ያህል የዋሆች ብንሆን ነው እያሰኘኝም ነው፡፡

እነኝህን ጽሑፎች ይጽፉና በድረ ገጻቸው ይለጥፉ የነበሩ ግለሰቦችና ድረ ገጾች አንዳንዶቹ አስቀድሞ በነበረው ማንነታቸው በወያኔነት የምንጠረጥራቸው አልነበሩም፡፡ አንዳንዶቹ ግን ወያኔ በስውር ለዚሁ ዓላማው አስቀድመው ተአማኒነትን አግኝተው እንዲቆዩ አድርጎ ያዘጋጃቸው ናቸው፡፡ ቀደም ሲል በወያኔነት የማንጠረጥራቸው ወይም ወያኔ ያልነበሩትም ቢሆኑ ትናንት አልነበሩም ማለት ዛሬ አይሆኑም ማለት አይደለም፡፡ ወያኔ የመጨረሻው መጨረሻ የደረሰ መስሎ ከታየው እራሱን ለማዳን የሚቆጥበውና የሚሰስተው ምንም ነገር የለም፡፡ እንዳልኳቹህ የሀገርን ካዝና አራቁቶም ቢሆን ገንዘብ ይረጫል፣ ፍላጎታቸው ገንዘብ ሳይሆን ጉዳዮች እንዲፈጸምላቸው ለፈለጉት ጉዳዮቻቸውን ይፈጽምላቸዋል፣ ፍላጎታቸው እነዚህ ሁቱም ያልሆነና ሥልጣን ለሚፈልጉትም ከሚንስትርነት እስከ ዲፕሎማትነት (አቅናኤ ግንኙነት) ድረስ ሥልጣን እየሰጠ ይደልላል፡፡ ሌላው ቀርቶ አያገኝም እንጅ እንዲህ አድርገሀል እንዲህ ብሎ ለፍርድ ላቅርብህ ሳይለው ከሀገር ክህደት እስከ የዘር ማጥፋት ለፈጸመው ወንጀል ላይጠይቀው አስተማማኝ ዋስትና የሚሰጠው አካል ቢያገኝ የመንግሥት ሥልጣንን ሁሉ አሳልፎ በመስጠት እራሱን ለማዳን ዝግጁ ነው፡፡

photo file

photo file

አሁን በዚህ ዘመን በእነዚህ ወያኔ ያንዣበበበትን አደጋ ለማስቀረት ሳይሰስት በሚያቀርባቸው መደለያወች የማይለወጥ የማይደለል ሰው ማግኘት በጣም ከባድ እየሆነ ከመምጣቱ የተነሣ ብዙዎች ያውም በቀላል በቀላል ነገር እየተደለሉ ሕዝብን እንደካዱ ስናይ ቆይተናል፡፡ አብሶ ደግሞ ሀገርና ሕዝብ ነጻ ሆነው ማየት ቁርጠኛ ዓላማ ይዞ ሳይሆን ከግል ጥቅሙ ከዝናና እውቅና ፍለጋ አኳያ እንዲሁም ወያኔ ተወግዶ እሱም ሥልጣን ይዞ በተራው ባለ ሥልጣን ለመባል፣ ለመኮፈስ፣ ሕዝብን ከጫማው ስር ለመርገጥ፣ በግል ጉዳዩ ለገጠመው ችግር የተጣላውን ለመበቀል፣ ለማዘዝ ለመናዘዝ ወይም ደግሞ ለመብላት ምኞትና ፍላጎት ይዞ በተለያዩ የሕዝባዊ ትግል ዘርፎች ተሰማርቶ ወያኔን እየተገዳደረ እየተሯሯጠ ያለ ሰው ከሆነ እንዲህ ዓይነቱን ሰው የያዘውን ሕዝባዊ ትግል በማስካድ ወያኔ የሚፈልገውን ነገር አቅርቦለት አድርጎለት ደልሎ መጠቀሚያው አገልጋዩ እንዲሆን ለማድረግ አይቸግረውም፡፡ አሁን እያስቸገሩ ያሉ ግለሰቦች የተደለሉበት ገንዘብ ወይም ሌላ የመደለያ ነገር መጠንና ዓይነት ይለያይ እንደሆነ ነው እንጅ ከላይ የጠቀስኩትን ዓይነት ፍላጎቶች ይዘው በተለያየ መስክ ሕዝባዊ ትግል ያደርጉ የነበሩ ግለሰቦች እንደነበሩ አሁን ላይ እርግጠኛ መሆን ይቻላል፡፡

በዚህ ጽሑፍ ላይ እኛ ሳናውቃቸው ቀርተን እራሳቸውን ሰውረው ወያኔ ደልሎ ለራሱ ጥቅም እንዲያድሩ ያደረጋቸው ግለሰቦች አሳቢ መስለው የተለያየ ነገር በማውራት የትጥቅ ትግሉ እንዳይታመን እንዳይጠነክር ከግብ እንዳይደርስ ለማድረግ ይጠቀሙባቸው በነበሩ ሐሳቦች ላይ አተኩረን ዕናያለን፡፡ ወደ መሀሉም ወያኔ ገዝቷቸው ካልሆነ በስተቀር ሌላ አሳማኝ ምክንያት ስላላቸው እየተደረገ ያለውን ሕዝባዊ ትግል የሸሹ እንዳልሆኑና ምንም ዓይነት አሳማኝ ምክንያት አቅርበው ሊሸሹ ሊቃወሙ የማይችሉበትን አመክንዮም ዕናያለን፡፡

የትጥቅ ትግሉን የሚቃወሙ ወገኖች የትጥቅ ትግሉን ተአማኒነት ለማሳጣት የሚያነሡዋቸው ነጥቦች ምን ምን ናቸው? የሚለውን ቀድመን ዕንይ በአምስት ዋና ዋና ሐሳቦች ይጠቀለላሉ፡-

  1. ሸአቢያ ራሱ ስላልቻለ አቅም ስለሌለው በእኛ ተጠቅሞ ወያኔን ለመበቀል ለማስወገድ ነው እንጅ በፍጹም በፍጹም ሸአቢያ ለኢትዮጵያ በማሰብ ይሄንን ድጋፍ ሊያደርግ አይችልም፡፡ ሸአቢያ በዚህ ዓላማው ምክንያት በሚያደርግልን ድጋፍ ውጤት ቢመጣ እሱ እንጅ ኢትዮጵያ ተጠቃሚ አትሆንም፡፡
  2. የወያኔና የሸአቢያ ፀብ የውሸት እንጅ እውነተኛ አይደለም እዛ ብንሔድ መልሶ ነው አሳልፎ ለወያኔ የሚሰጠን ወይም የሚፈጀን፣ ፀባቸው የእውነት ቢሆንም ወያኔና ሸአቢያ ቀደም ሲል ከነበራቸው ጥምረት ቁርኝትና ዝምድና አንጻር ለሸአቢያ ከወያኔ ይልቅ እኛ ቀርበነው ይሄንን ያህል ውለታ ሊውልልን አይችልም፣ ሊታመንልን አይችልም፣ ሸአቢያ ለኢትዮጵያ ከወያኔ የባሰ ሸረኛ ጠንቀኛ ጠላት ነው ብሎ ከመጠራጠር፡፡
  3. የታጠቀ ኃይል የምንፈልገውን ዓይነት ለውጥ ሊያመጣ አይችልም፣ በአፈሙዝ የሚገኝ ዲሞክራሲ (መስፍነ ሕዝብ) የለም፣ የታጠቀ ኃይል የራሱን እንጅ የሕዝብን ፍላጎት አያሟላም፡፡ ከሚል ዓለም አቀፋዊውን ነባራዊ ሁኔታ ካልተገነዘበ አስተሳሰብ፡፡
  4. በዘመነ ደርግ ወያኔና ሸአቢያ ደርግን ሲታገሉ በነበረበት ወቅት የስንቅና ትጥቅ (logistics) ሌላም ድጋፍ ያደርጉላቸው እንደነበሩ ሀገራትና አንዳንድ አካላት በዚህ ዘመን ለእኛ ሊያደርግልን የሚችል ባለመኖሩ በቂ ስንቅና ትጥቅ ሊገኝ ስለማይችል ከንቱ ድካምና ከንቱ መሥዋዕትነት ነው ከሚል፡፡
  5. ሸአቢያ እኛን ይዞ ወያኔን ለማስፈራራትና ከወያኔ የሚፈልገውን ለማግኘት እንጅ የምናደርገው ትግል ፍሬ እንዲያፈራ ለስኬት እንዲበቃም በፍጹም አይፈልግም፡፡ የሚሉ ምክንያቶችን ያቀርባሉ፡፡

እነኝህ ሥጋቶች ጥርጣሬዎችና ስሞታዎች ተጨባጭና ትክክለኛ ስለመሆናቸው መፈተሽ ይኖርብናልና እንደ ቅደም ተከተላቸው እንፈትሻቸው፡-

  1. “ሸአቢያ ራሱ ስላልቻለ አቅም ስለሌለው በእኛ ተጠቅሞ ወያኔን ለመበቀል ለማስወገድ ነው እንጅ በፍጹም በፍጹም ሸአቢያ ለኢትዮጵያ በማሰብ ይሄንን ድጋፍ ሊያደርግ አይችልም፡፡ ሸአቢያ በዚህ ዓላማው ምክንያት በሚያደርግልን ድጋፍ ውጤት ቢመጣ እሱ እንጅ ኢትዮጵያ ተጠቃሚ አትሆንም” የሚባለው ነገር ሸአቢያ እንዲህ ዓይነት ሐሳብ ሊኖረው ቢችልም እንኳን የእኛ ጠላት የሆነው ለሸአቢያም ጠላት መሆኑ ጥሩ ዕድል መፍጠሩን በመረዳት የጋራ ጠላትን አንድ ግንባር ፈጥሮ ወይም ተረዳድቶ ማጥቃቱ ማጥፋቱ ስልታዊ አኪያሔድ እንጅ ጉዳቱ ምኑ ላይ ነው? ይሄንን ሥጋት የሚያነሡ ወገኖች ይሄንን ያላቸውን ሥጋት በደፈናው ከመናገር በስተቀር ወያኔ በዚህ ጥምረትና መረዳዳት ቢጠፋ ኢትዮጵያ ተጠቃሚ የማትሆንበትን ምክንያት በግልጽ እንዲህ እንዲህ ነው በማለት አያስረዱም፡፡ በደፈናው ከመጠራጠር በስተቀር የሚሉት ነገር የላቸውም፡፡ ስገምት ግን የእነሡ ሥጋት “ወያኔ ሲወድቅ በወያኔ ቦታ ሸአቢያ ይቀመጥና ውጤቱ ጉልቻ መለዋወጥ ነው የሚሆነው” የሚሉ ይመስላል፡፡ ይሄም ቢሆን ግን ሥጋቱ ተጨባጭ አይደለም፡፡ ከኢትዮጵያ ተገንጥላለች የተባለችው ባሕረ ምድር (ኤርትራ) ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ እንደ አንድ ሀገር አውቄሻለሁ ብሏታል ከተባለ በኋላ ሸአቢያ አዲስ አበባ ገብቶ ሥልጣን ሊይዝ የሚችልበት ምንም ዓይነት ሁኔታ አጋጣሚ አሠራር የሌለና ሊታሰብም የሚችል ባለመሆኑ ተደርጎ ቢገኝም በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ሕግ መሠረት “ወረራ” ተብሎ የሚወገዝና ወረራው በአባል ሀገራት የትብብር ጥቃት እንዲቀለበስ የሚደረግ በመሆኑ ሥጋቱ ተጨባጭ ያልሆነና ሊገመትም የሚገባ አይደለም፡፡
  2. “የወያኔና የሸአቢያ ፀብ የውሸት እንጅ እውነተኛ አይደለም እዛ ብንሔድ መልሶ ነው አሳልፎ ለወያኔ የሚሰጠን ወይም የሚፈጀን፣ ፀባቸው የእውነት ቢሆንም ወያኔና ሸአቢያ ቀደም ሲል ከነበራቸው ጥምረት ቁርኝትና ዝምድና አንጻር ለሸአቢያ ከወያኔ ይልቅ እኛ ቀርበነው ይሄንን ያህል ውለታ ሊውልልን አይችልም፣ ሊታመንልን አይችልም፣ ሸአቢያ ለኢትዮጵያ ከወያኔ የባሰ ሸረኛ ጠንቀኛ ጠላት ነው ብሎ ከመጠራጠር” ይሄ ደግሞ በጣም አስቂኝ ነው፡፡ ሰው አይጠርጥር አይጠንቀቅ አይባልም በተለይ በእኛ ሁኔታ መጠራጠርና መጠንቀቅ ተገቢና አስፈላጊም ነው፡፡ ነገር ግን የጠረጠርነውን ነገር ሊያስወግዱ ሊቀርፉ የሚችሉ ያሉና የሚታዩ ተጨባጭ ኩነቶች ባሉበት ሁኔታ አንድ ሰው በዚህ ደረጃ ተጠራጥሮ የማይመስል ነገርን ሲያስብ ብታገኙት ይሄ ሰው በጤነኛና ትክክለኛ የአእምሮ ጤና ውስጥ እንዳልሆነ እርግጠኛ ልትሆኑ ትችላላቹህ፡፡ ለእንደዚህ ዓይነት መስመር የሳተ አስተሳሰብ የሚዳረጉ ሰዎች እንዲህ ሊሆኑ የሚችሉበት ምክንያት ሲመረመር እንዲህ ብለው በሚጠረጥሯቸው በሚያስቧቸው አካላት ከባድ የሥነልቡና ጫና መታወክና መረበሽ የደረሰባቸው ሆነው ይገኛሉ፡፡ ከዚህም የተነሣ እነዚያን የሚጠረጥሯቸውን አካላት በተመለከተ ሊያደርጉትና ላያደርጉት ሊችሉትና ላይችሉት ሊሠሩትና ላይሠሩት ይችላሉ ብለው የሚያስቡት የሚገምቱት ሲመረመር ከሞላ ጎደል ትክክለኛ ሆኖ አይገኝም፡፡ ሥጋቶቻቸውና ጥርጣሬዎቻቸው ከታወከ ሥነልቡናቸው የሚመነጩና ከገሀዱ ዓለም ተጨባጭ እውነታዎች የራቁ ሆነው ይገኛሉ፡፡ ያሉ ነገሮችንም በተጨባጭ ካሉ ከተፈጸሙ መሬት ላይ ከሚታዩ ነገሮች አንጻር መመዘን መለካት የሚፈልጉ አይደሉም፡፡

ይሁንና ምናልባት ያሉበትን ተጨባጭ ያልሆነ ምናባዊ አስተሳሰብ ማሰብ ማገናዘብ መረዳት ያስችላቸው እንደሆነ ከሚል እንዲህ ለሚሉ ሰዎች ላነሣቸው የምፈልጋቸው ጥያቄዎች አሉኝ፡- ሀ. የሸአቢያና የወያኔ ጸብ የውሸት ከሆነ የዚህ የውሸት ጸባቸው ምክንያት ዓላማና ግብ ምንድን ነው? ለ. ጸባቸው የውሸት ከሆነ ወያኔና ሸአቢያ ለ17 እና ለ30 ዓመታት ደርግን ሲታገሉ ከእያንዳንዳቸው ወገን ካለቀባቸው ሠራዊት በላይ በዚያች በአጭር ጊዜ ጦርነት ባደረጉት ጦርነት ብቻ ከእያንዳንዳቸው ወገን ሰባ ሰባ ሽህ የሚገመት ሠራዊት ላለቀበት አስከፊ ጦርነትስ እንዴት ሊዳረጉ ቻሉ? ሐ. ከዚያ አሰቃቂ ጦርነት በኋላስ ባሕረ ምድር (ኤርትራ) ከዓለም ዓቀፉ ማኅበረሰብ ተነጥላ በማዕቀብ ስር ሆና ሕዝቧም ለአስቸጋሪ የድህነት ኑሮ ተዳርጎ እስከ አሁንም ድረስ በከባድ ችግር ለማለፍ እንዴት ልትገደድ ቻለች? የሚሉ ጥያቄዎችን ለራሳቸው ለመመለስ ቢሞክሩ ጭንቅላታቸውን ወደ ትክክለኛውና ጤነኛው አስተሳሰብ ለመመለስ ይረዳቸው ይሆናል ብየ አስባለሁ፡፡ አንዱ እንዲህ ዓይነት ችግር ያለበት “ጋዜጠኛ” እማ ጭራሽ ምን አለ? “ጸባቸው የውሸት ነው” ካለ በኋላ “የውሸት መሆኑንም የሚያረጋግጠው ኢትዮጵያ ለኤርትራ በየዓመቱ 250 ሚሊዮን (አእላፋት) ዶላር ትረዳለች” በማለት ያለበትን የሥነልቡናና የሥነ አእምሮ የጤና መታወክ ደረጃ ቁልጭ አድርጎ ሊያሳየን ቻለ፡፡ ወይም ደግሞ የትጥቅ ጥግሉን ለማክሸፍ ለስውር ተልእኮ ወያኔ ከቀጠራቸው ቅጥረኞች አንዱ መሆኑን እንዲህ በል ተብሎ ሊሆንም ይችላል፡፡ ምክንያቱም ይህ ያለው ነገር የፈጠራ መሆኑን የሚያረጋግጠው አስቀድመን ከጠቀስናቸው የሸአቢያና የወያኔ ፀብ የውሸት አለመሆኑን ከሚያረጋግጡት ነጥቦች አኳያ የማይመስል ነገር መሆኑና ለወሬው መረጃውን ወይም ምንጩን መጥቀስ ያልቻለ መሆኑ ነው፡፡

ሌላው “ሸአቢያ ታማኝ አይደለም ሸአቢያ ለኢትዮጵያ ከወያኔ የባሰ ሴረኛ ሸረኛ ጠንቀኛ ጠላት ነው” ለሚለውን የዋሀን ወገኖቻችንም ይሄንን አጥብቀው ያነሣሉ፡፡ ለነገሩ እነሱን ጨምሮ የወያኔ ካድሬዎችም ጭምር ሸአቢያ ከወያኔ የባሰ ጠላት ለመሆኑ የሚጠቃቅሷቸው ነገሮች አሉ፡፡ በሸአቢያ በኩል ደግሞ እነኝህ የሚጠቀሱ ነገሮች ሐሜቶችና የወያኔ የፈጠራ ወሬዎች መሆናቸውንና እሱ ግን ከድሮ ጀምሮ ለኢትዮጵያ በማሰብ ቀና ቀና ነገሮችን ሲያደርግ እንደቆየ ቢናገርም እንዲያው አንዳችም የፈጸመብን ክፉ ተግባር የለም ማለት የሚቻል አይመስለኝም፡፡ ምንስ ቢሆን ሲዋጋ የኖረው ከእኛ ጋር መሆኑ ቀረ እንዴ! ጠላቱ አድርጎ የሚያስበንን ለመጉዳት ለማጥቃት ለማዳከም የማይመኘን የማይጥርብን ምን ያህል ታጋሽ አርቆ አሳቢ በሳል ይቅር ባይ ቢሆን ነው? እንኳንና የሚጠቀሱ ነገሮች እያሉ የቱንም ያህል ደግ አሳቢ ቅኖች የነበሩ ቢሆኑም እንኳ የዚህን ያህል ሊያመጻድቅ የሚችል ሥራ ሊኖራቸው እንደማይችል መገመት የሚቻል ይመስለኛል፡፡

ነገር ግን ይህ የሸአቢያ መልካም ሥራ እውነት መሆኑን ማጣቀሻዎችን እያነሡ የመሰከሩ የአንዳንድ ወገኖች ምስክርነትንም ሰምተናል፡፡ እንደኔ እንደኔ ሠራው የተባለው ክፋት እውነት ቢሆንም እንኳን ሊያስደንቀን የሚገባ አይደለም፡፡ በጠላትነት ተፈራርጀን ስንተላለቅ የኖርን ሰዎች ሆነን እያለ አንዳችም ክፉ ነገር እንዲያደርግብን መጠበቅ የኛን የዋህነት ሊያስይ ቢችል እንጅ ሊሆን የባይገባው ነገር መደረጉን የሚያሳይ አይመስለኝም፡፡ ምን ነካቹህ? በቀንደኛ ጠላትነት ተፈራርጀን ለ30 ዓመታት እኮ ነው ጦርነት ስናደርግ የኖርነው! እኛ እነሱን ልናጠፋ እነሱም እኛን ሊያጠፉ፡፡ ዛሬ ላይ ግን ያ ትግላቸው ለስኬት አብቅቷቸው የትግላቸውን ፍሬ እየለቀሙ ያሉበት ደረጃ ላይ በመሆናቸውና ትግላቸው “ያተረፉበት ወይስ የከሰሩበት? መሆን መደረግ የነበረበት ወይስ ያልነበረበት?” የሚል ጥያቄን ለራሳቸው እንዲያነሡ የተገደዱበት ወቅት ላይ ያሉ በመሆኑና ለትግል ያስወጣቸው ችግሮች የነበሩ ከሆነም እንኳን እነዚያን ችግሮች በሌላ መንገድ መፍታት ይቻል የነበረበትን አማራጭ መፈለግ የተሻለ እንደነበር የተረዱበት ወቅት ላይ ያሉ በመሆናቸው እድሜ የማያስተምረው የማያበስለውም የለምና ከዕድሜና ከተሞክሮም በመማራቸው ከዚህ አንጻር በዚያ ወቅት በኢትዮጵያ ላይ የሠሩት የፈጸሙት ሸር ሴራ ወንጀል ተንኮል ክፋት ቢኖርም እንኳን የሚጸጸቱበት እንጅ የሚኮሩበት ባለመሆኑ እንደቀድሟቸው ሁሉ አሁንም እንደዚያው ያደርጋሉ ያስባሉ በማለት ፍጹም አትጠራጠሩ ባልልም ድምዳሜ ላይ መድረሱ ግን የሚገባ ነው ብየ አላስብም፡፡

የወያኔ ካድሬዎች ተቀጣሪዎችና የዋሀን ወገኖች የፈለጉትን ሲያወሩ ለሸአቢያ የነበረን ሥዕል ከድሮው መጥፎ መሆኑ ስለ ሸአቢያ መጥፎነት ምንም ነገር ቢባል በቀላሉ እንድናምን እያደረገን ወደ እውነቱ እንዳንደርስ የተጫነን መስሎ ይሰማኛል፡፡ እኔ እንዲያውም አሁን አሁን እየተረዳሁት የመጣሁት ነገር ቢኖር በሸረኝነት በክፋተኝነት በጠንቀኝነት በሴረኝነት በጠላትነት ወያኔ ሸአቢያን እጥፍ አስከንድቶ የሚበልጠው መሆኑን እንጅ የሚያንሰው አለመሆኑን ነው፡፡ በግልጽ አማርኛ ከመጀመሪያውም ጀምሮ ከሸአቢያ ይልቅ ወያኔ እጅግ በጣም የከፋ ሸረኛ ሴረኛ ክፉ ጠላት ነው፡፡

ይሄንን ልታረጋግጡ የምትችሉበትን አንድ ሁለት ነገሮችን ላንሣላቹህ፡፡ ከ1990ዓ.ም. የወያኔ ሸአቢያ ጦርነት በኋላ እነ አቶ ኢሳይያስ ከዓለሙ ማኅበረሰብ የተነጠሉ መሆናቸውን ታውቃላቹህ፡፡ ለምዕራባዊያን ከኢትዮጵያ ይልቅ ባሕረ ምድር (ኤርትራ) ስልታዊ (strategic) ጠቀሜታ ያላት ነች፡፡ የወያኔ ሸረኝነት ሴረኝነትና ዋሽቶ የማሳመን ችሎታ ከሸአቢያ እጅግ የላቀ መሆኑ ባሕረ ምድር እንዲህ ዓይነት ስልታዊ ጠቀሜታ ያላት መሆኗ በቀላሉ ምዕራባዊያንን ከጎኗ ማሰለፍ የሚያስችላት ሆኖ ሳለ በጠቀስነው ችሎታ ወያኔን ስላልቻሉትና በዲፕሎማሲው (በአቅንኦተ ግንኙነቱ) ላይ የበላይነቱን በመያዙ ከጨዋታ ውጪ እንዳደረጋቸው ዓይተናል፡፡ ይሄው እስከዛሬም በአሳዛኝ ተሸናፊነት ተገልለው እንዲቀሩ አድርጓቸው ቀርቷል፡፡ ከሸአቢያ ያየነው ብቃት ቢኖር የዘመኑን የፖለቲካ ጨዋታ ባለመረዳት ከሁኔታዎች ጋር እንደወያኔ እየተጣጠፈ በብልጠት ጥቅሙን ማስከበር ሳይችል በግትርነት በድርቅና መጽናቱን ብቻ ነው፡፡

ይሄ ሽንፈት በድንበር ዳኝነቱ (ኮሚሽኑ) ውሳኔ ጊዜም ተደግሟል የዳኝነቱ ውሳኔ ትክክል ባይሆንም የድንበር ኮሚሽኑ (ዳኝነቱ) ይግባኝ በሌለው ውሳኔ ባድመን ለባሕረ ምድር የወሰነ ሆኖ እያለ ከሸአቢያ ችሎታ ማነስና ደካማነት ከወያኔ መሠሪነት ሸረኝነት የተነሣ ውሳኔው ተፈጻሚ መሆን እንዳይችል አድርጎታል፡፡ እንግዲህ ሸአቢያ ሊጠቀምባቸው መብቴ ነው የሚለውን ሊያስጠብቅበት የሚያስችለው ዕድሎችና አንዳንድ ነገሮች ቢኖሩትም ከደካማነቱ የተነሣ ጥቅሙን ማስጠበቅ ያልቻለ አካል ነው፡፡ ከእነዚህ ሁለት ሁኔታዎች የምንረዳው የወያኔንና የሸአቢያን በጣም የተራራቀና የማይመጣጠን የብቃትና የችሎታን አቅም ነው፡፡ እንደምናስበውና ከየዋሀን ወገኖቻችን ከወያኔ ቅጥረኞችና ካድሬዎች በሰፊው እንደሚወራልን ሸአቢያ ከወያኔ የላቀ የበለጠ መሠሪ ሸረኛ ብቃትና ችሎታ ያለው ቢሆን ኖሮ አይደለም ከወያኔ በበለጠ በተሸለ በምዕራባዊያኑ ተመራጭ ተፈላጊ ሊያደርገው የሚችሉ ነገሮች እያሉት ቀርቶ ባይኖረውም እንኳ የበላይነቱን ይዞ ልናየው በቻልን ነበር፡፡ የሆነው ግን የተገላቢጦሹ ነው ስልታዊ ጠቀሜታ እንደሌለውና በድንበር ኮሚሽኑ እንደተሸነፈ ሆኖ ከዓለም ዓቀፉም ኅብረተሰብ ተነጥሎ ተገልሎ ይሄ ሳያንሰው ማዕቀብ ተጥሎበት በማዕቀብ እየታሸ ለመኖር የተገደደ መሆኑ ነው፡፡

እዚህ ላይ አንዳንድ ሰዎች ምናልባት ሸአቢያ ምዕራባዊያኑን ከጎኑ ሊያሰልፍ የሚችልበት ጥቅም እያለው ምዕራባዊያኑ ከሸአቢያ ጎን ሊቆሙ ያልቻሉበትና ከወያኔ ጎን ሊቆሙ የቻሉበት ምክንያት “ወያኔ አልሸባብን አጥፍቶ ሱማሌን የተረጋጋችና መንግሥት ያላት ሀገር እንዲያደርግላቸው ስለሚፈልጉ እዚያ ላላቸው ጥቅም ወያኔን ስለሚፈልጉት ነው” የሚሉ ሊኖሩ ይችሉ ይሆናል፡፡ ነገር ግን እውነት እንነጋገር ከተባለ የምዕራባዊያኑ ፍላጎትና ጥቅም እውን ሶማሊያ የተረጋጋች ሀገር እንድትሆን ነው ወይ? እንዳልሆነ ሊቢያ ላይ ምን ብለው ምን አድርገዋቸው እንደቀሩ የታየውና የምናውቀው ነው፡፡ አፈራርሰዋት የአሸባሪዎች መፈንጫ አድርገዋት ቀሩ እንጅ ቃል የገቡትን የመልሶ ማቋቋሚያ ገንዘብ ሰጥተው መስፍነ ሕዝባዊ (ዲሞክራሲያዊ) መንግሥት እንዲመሠርቱ ሲረዷቸው ፈጽሞ አልታዩም፡፡ በመሆኑም የምእራባዊያኑ ጥቅምና ፍላጎት ሶማልያን ማረጋጋትና ባለመንግሥት ማድረግ ሆኖ ባሕረ ምድር ካላት ስልታዊ ጠቀሜታነት አንጻር ከሷ ሊያገኙት የሚችሉት ጥቅም ወያኔ ሱማሌ ላይ ከሚሰጣቸው ጥቅም በልጦባቸው አይደለም ከሸአቢያ ይልቅ ወያኔ በልጦባቸው ከወያኔ ጋር ሊቆሙ የቻሉት፡፡

እናም አትጠራጠሩ የከፋው የባሰው የላቀው መሠሪ ሸረኛና ሴረኛ ወያኔ እንጅ ሸአቢያ አይደለም፡፡ ሸአቢያ እንኳንና ፈጥሮ ፈልስፎ አሲሮ ጥቅሙን ሊያስጠብቅ ይቅርና በያዘው ጥቅሙን ሊያስጠብቅ የሚያስችሉትን ዕድሎች በመጠቀም ሌላው ቀርቶ ያንተ ነው የተባለለትን ውሳኔ ጥቅሙን ማስጠበቅ ያልቻለ ምስኪን ተሸናፊ ነው፡፡ ይህ ነገር ስለ ሸአቢያ መጥፎነት የመሠሪነት ብቃትና ችሎታ ሲወሩ ሲነገሩን የነበሩ ነገሮች ሁሉ እውነትነታቸውን እንደገና መለስ ብለን እንድናይ እንድንፈትሽ የሚያስገድደን ይመስለኛል ይገባልም፡፡ ቢያንስ የተባለው ሁሉ እውነት እንዳልሆነ የሚያረጋግጥ ይመስለኛል፡፡ ጥቂቱ እንኳ እውነት ሊሆን ቢችል አስቀድሜ እንደገለጽኩት ለምን እንዴት ብሎ መጠየቅ ድርጊቱንም ማውገዝ ተገቢ ቢሆንም ከነበሩ የጦርነት ነባራዊ ሁኔታዎች አንጻር በምንም ተአምር መፈጸም አልነበረበትም ማለቱና በዚህም ላይ ተመሥርቶ የመጨረሻ ድምዳሜ ላይ መድረሱ ግን እጅግ እጅግ የዋህነትና እጅግም አለመብሰል ነው፡፡ በቤተሰብ መሀከል በጥቅም ምክንያት ወንድም በወንድሙ እኅት በእኅቷ ወንድም በእኅቱ ልጆች በወላጆቻቸው ወላጅ በልጆቹ ክህደት እየፈጸመ በሚባላበት ዘመን ጠላት ተደራርገው አንዱ ሌላውን ለማጥፋት በሚታገል በታጠቀ ሠራዊት መሀከል አንዳንድ ነገሮች መፈጸማቸው አይቀርምና ይሄና ያ እንዴት ለምን ማለትና ምንም ነገር እንዲፈጸም አለመጠበቅ ያንን የተፈጸመውን ጉዳይም የነገሮች መጨረሻ አድርጎ መቁጠር አሁንም እላቹሀለሁ እጅግ የዋህነትና አለመብሰል ነው፡፡ ምን ነካቹህ እቃቃ ስናጫወት እኮ አይደለም የኖርነው በጦርነት እሳት ስንለባለብ እንጅ፡፡ በፖለቲካ ጨዋታ ውስጥ የሚታየው ዛሬ እንጅ ትላንት አይደለም በዓለማችን ትላንት ሲባሉ ሲቧጨቁ ሲጠፋፉ የነበሩ ዛሬ ላይ ግን እፍ ያለ ፍቅር ውስጥ የገቡ በርካታ ሀገራትንና ቡድኖችን መጥቀስ ይቻላል፡፡

የሆነ ሆኖ ይሄንን ሁሉ እንዳለ ተውትና ያልገባቸው ወገኖችም ሆኑ ወያኔ የገዛቸው ቅጥረኞች የሚናገሩት ክስ አንድም ሳይቀር ሁሉም እውነት እንደሆነ እንቁጠረውና ለወያኔ ከተገዙትና ከወያኔ ካድሬዎች በስተቀር የኢትዮጵያ ሕዝብ ለወያኔ የተገዙና የወያኔ ካድሬዎች የሚያወሩትን ሳይሰማ ትግሉን ተቀላቅሎ ለድል የሚበቃበትን መንገድ ስናገር የሚከተለውን ይመስላል፡- የነጻነት ትግል ማለት ምንም ዓይነት መሰናክልና የፈተና ዓይነት እንቅፋት የሚያግደው የሚያደናቅፈው የሚገታው እንዲያግደው እንዲገታው እንዲያደናቅፈውም የማይፈቅድ ሁልጊዜም በተመቻቸ ሁኔታ ውስጥ ሳይሆን ባልተመቻቸና እንቅፋት መሰናክሎች ፈተናዎች በበዙበት ሁኔታ የሚደረግ የማይመቹ ሁኔታዎች ስላሉ በፍጹም ከመደረግ የማይቆም የማይቀር፤ ያለው ዕድል ከጠጉር የቀጠነ ዕድልም እንኳ ቢሆን በከፍተኛ ጽናት ትዕግሥትና ብልጠት እሱን ተጠቅሞ ዓላማውን ለማሳካት ከፍተኛ ትግልና ትንቅንቅ የሚደረግበት ሌላው ቀርቶ ምንም ዓይነት ዕድልም እንኳ ባይኖር ራሱን ዕድሉን ፈጥሮ ግቡን ለማሳካት የሚደረግ መራራ ትግል እንጅ እንደ ሽርሽር ምቹ ሁኔታዎች የሚጠበቁበት የትግል ዓይነት አይደለም፡፡

እናም አኔ የምላቹህ የወያኔ ቅጥረኞችና ካድሬዎች እንደሚያወሩት ሸአቢያ ከወያኔ የከፋና የኢትዮጵያ ቀንደኛ ጠላት ቢሆንም እንኳ ትግላችን የነጻነት ትግል በመሆኑና በምንም የሚመለስ ሊመለስም የሚገባ ባለመሆኑ እንኳንና ይሄንን ያህል ዕድል ተፈጥሮ ቀርቶ ምንም ዓይነት ዕድል ባይኖርም ራሱ ዋሽተን ወስልተን ቀጥፈን ሌሎች የብልጠት መንገዶችን ተጠቅመንም ቢሆን ዕድሉን ፈጥረን ግባችንን የማሳካት ግዴታ ያለብን በመሆኑ ሸአቢያ እንዳሉት ቢሆንም እንኳ ባለፈው ጊዜ እንዳልኳቹህ የልባችንን በልብ አድርገን መዋሸት ካለብን እየዋሸን “ቃል ግቡልኝ ፈርሙልኝ ማሉልኝ እንዲህ እንዲህ ታደርጉላኛላቹህ” ቢልም በፍጹም እንደማታደርጉት ልባቹህ እያወቀም አንኳ “እሽ ምን ችግር አለው! የፈለከውን እናደርጋለን! እኛ ሎሌህ ደጋፊዎችህ አጋሮችን ነን! ላንተ የማንሆነው የማናደርገው ነገር የለም!” እያልን ግጥም አድርገን በዐሥር ጣታችን በመፈረም እርኩስ ክፉ መሠሪ መሆኑን ብናውቅም “ደግ ቅንና ቅዱስ ነህ!” እያልን “ሸአቢያ ሽህ ዓመት ይንገሥ በሉ!” ቢል “ለምን ሽህ ዓመት ብቻ ለዘለዓለም ኑርልን!” እያልን ሥራችንን በመሥራት ይሄንን ክፉ ቀናችንን ዛሬን ተሻግረን ግባችንን አሳክተን ከነጻነቱ ቀን ነገ ላይ መድረስ ግድ ይለናል፡፡ ዕድል ባይኖርም ዕድል መፍጠር ይሉሀል ይሄ ነው፡፡ እንዲህ የምናደርገው ለምንድን ነው? እውነት ከሆነ ሸአቢያ የማይወደውን አቋም በመያዛችን በሸአቢያ እንዲጠፉ ተደርገዋል እንደተባሉት ወገኖች ከመጠቃት ለመዳን ነው፡፡ በዚህ የትግል ዘመን እውነት ብቻ ተናግረን ፈተናዎቻችንን ማለፍ መሻገር በፍጹም በፍጹም አንችልም፡፡ የልብን በልብ አድርገን ማስመሰልን መዋሸትን መቅጠፍን በሚገባ ልንካንበት ይገባናል ለምን ሲባል? ለዚህች ውድ ሀገራችንና ለውዱ ሕዝባችን ህልውናና ነጻነት ስንል፡፡ ተስፋ አደርጋለሁ አሁን ነገሩ የሚገባቹህ የሚገለጥላቹህ ይመስለኛል፡፡ በመሆኑም ወያኔ ወይም የወያኔ ቅጥረኛ ካልሆንን በስተቀር ሀገራችንን የምንወድ የሀገራችንንና የሕዝባችንን ነጻነት ፈላጊ ሆነን ከዚህ ሕዝባዊ ትግል ልንሸሽ ጭራሽም ትግሉት ልንቃወም የምንችልበት ምንም ዓይነት ምክንያት እንደሌለ በሚገባ በመረዳት እያንዳንዳችን እንደየችሎታችን ትግሉን በመደገፍ የትግሉ አካል መሆን አማራጭ የሌለው መሆኑን አውቀን መንቀሳቀስ ይኖርብናል፡፡

  1. “የታጠቀ ኃይል የምንፈልገውን ዓይነት ለውጥ ሊያመጣ አይችልም፣ በአፈሙዝ የሚገኝ ዲሞክራሲ (መስፍነ ሕዝብ) የለም፣ የታጠቀ ኃይል የራሱን እንጅ የሕዝብን ፍላጎት አያሟላም፡፡ ከሚል ዓለም አቀፋዊውን ነባራዊ ሁኔታ ካልተገነዘበ አስተሳሰብ” ይህ የሥጋት ሐሳብ ላይ ላዩን ሲያዩት እውነት ይመስላል፡፡ በተለይ ደግሞ ምሳሌ ይሉና ደርግንና ወያኔን ምሳሌ አድርገው ሲያቀርቡ እውነት ይመስላቹሀል፡፡ ትንሽ ልትጠረጥሩ የምትችሉት “ታዲያ ምን ይሻላል?” ብላቹህ ስትጠይቋቸው መልስ ሲያጡ ወይም የሚሰጡት መልስ አጥጋቢ ያልሆነና ወያኔን የሚጠቅም ሆኖ ስታገኙት ነው፡፡ ምናልባት እነኝህ ቅጥረኞች የሚያነሡትን ይሄንን የሥጋት ሐሳብ የሚያነሡ ሌሎች የዋሀን የሕዝብ ወገኖች ካሉ ለነሱ ላነሣው የምፈልገው ጥያቄ ቢኖር፡- ይሄንን የሚሉ ሰዎች ለሀገርና ለሕዝብ ታማኝ ከሆኑና ይሄንን ቅን ዓላማቸውን ይዘው የሚታገሉ ከሆነ ወያኔን አባራሪዎቹና እንደተመኙት ሁሉ ሕዝብን የሥልጣን ባለቤት የሚያደርጉት እነሱው አይደሉም ወይ? ሌላ ከማርስ የሚመጣ አብሯቸው የሚገባና አንባገነን ካልሆናቹህ ብሎ የሚያስገድዳቸው አካል አለ ወይ? ዋናው የዓላማ ጽናትና ታማኝነት ነው እንጅ መሣሪያው አይደለም፡፡ ታማኝ ያልሆነ ግለሰብ ወይም አካል ካለ ሲቪል (ሕዝባዊ) ሆኖም ከሀገርና ከሕዝብ ጥቅም በተጻራሪ በመቆም ሕዝብን የሚጨቁን የራሱን ወይም የቡድኑን ጥቅም የሚያስጠብቅ ለራሱና ለቡድኑ ጥቅም ቅድሚያ የሚሰጥ ከመሆን እንደማይድን የብዙ ሀገራት ተሞክሮ በሚገባ ያሳየናል፡፡

በዓለማችን በጦር ኃይል የተመሠረቱ መንግሥታት አንባገነን የሆኑ እንዳሉ ሁሉ የተደላደለ ሕዝባዊና ዲሞክራሲያዊ (መስፍነ ሕዝባዊ) መንግሥት እንዲመሠረት እንዲፈጠር ያደረጉም አሉ፡፡ ዋናው የዓላማ ጽናትና ታማኝነቱ ነው፡፡ በዚህ ላይ አርበኞች ግንት 7 ዓላማው ምን እንደሆነ በግልጽ አስታውቋል “የምታገለው ሕዝብ የፈለገውን የወደደውን መሾም ያልፈለገውን ያልወደደውን መሻር የሚችልበት ሥልጣን እንዲኖረው የሥልጣን ባለቤት እንዲሆን ማድረግ ነው እንጅ ወያኔን አውርጀ ሥልጣን ለመያዝ አይደለም፡፡ ወያኔን ደምስሰን የኢትዮጵያ ሕዝብ የፈለገውን የወደደውን መርጦ መንግሥት ያቋቋመ የመሠተረ ጊዜ የኛ ትግል ይጠናቀቃል” በማለት፡፡ ስለሆነም እንግዲህ እውነተኛ የሕዝብ ልጅ ካለ ለግል ጥቅም ለሥልጣን ሳይሆን ለዚህች ሀገርና ለሕዝቧ ነጻነት ለፍትሕ ለእኩልነት እታገላለሁ የሚል ካለ ቦታው አርበኞች ግንቦት 7 ነው ሔደህ ግባ፡፡

እንዲያው ነገሩን አልን እንጅ እውነተኛና ትክክለኛ ለራሱ ቡድናዊና ግላዊ ጥቅምና ፍላጎት ሳይሆን ለሕዝብ የታመነ ኃይል ታግሎ መጥቶ ይሄንን ማድረግ ቢችልና ሕዝብ የወደድከውን የፈለከውን ምረጥ ተብሎ ሙሉ መብት ቢሰጠው ከባድ መሥዋዕትነት ከፍሎ ለዚህ ክብር ያበቃውን፣ ነጻነት ያቀዳጀውን፣ የሥልጣን ባለቤት ያደረገውን፣ ለሀገሩና ለወገኑ እስከ ሞት ድረስ ራሱን የሰጠለትን ትቶ እዚህ ከሞቀ ቤቱ ቁጭ ብሎ ሲያበግነው የኖረውን፣ እንቅፋት እንኳን እንዳይመታው እራሱን ሲጠብቅ የኖረውን፣ ከሕሕብና ከሀገር ይልቅ ራሱን የሚወደውን እራሱን የሚያስቀድመውን፣ ለሕዝብና ለሀገር ሲል ምንም ዓይነት ዋጋ ለመክፈል የማይፈቅደውን፣ ድፍረት ቁርጠኝነት ጽናት የሌለውን፣ ታማኝነቱን ሀገር ወዳድነቱን ከወሬ ባለፈ በተግባር መሥዋዕትነትን እስከመክፈል ድረስ ታምኖ ዋጋ ከፍሎ ማሳየት የማይችለውን፣ የጭርታ የሰላም ጊዜ አርበኛ ተሽታሻ ተሸታሻውን የሚመርጥ ይመስላቹሀል? በፍጹም!

ወያኔ እኮ መሥዋዕትነትን እንደመክፈሉ እስከዛሬ ድረስ በተደረጉት 5 “ምርጫዎች” በኢትዮጵያ ሕዝብ ሊመረጥ ያልቻለው እኮ ወያኔ ካፈጣጠሩ ኢትዮጵያዊ ባለመሆኑ፣ ዓላማና አስተሳሰቡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ለሽዎች ዓመታት የገነባው የታሪኩ የአንድነቱ የማንነቱ የሥልጣኔው የእሴቶቹ ጠላት ሆኖ ከሚያውቀውና ከሚያምንበት በተጻራሪ ቆሞ ታሪኩን በማጉደፉ፣ ለማፈራረስ ጥረት በማድረጉ፣ በስንት ድካም የገነባውን አንድነቱን ጨርሶ ለማጥፋት በዘር በሃይማኖት እየከፋፈለ ለማባላት በመጣጣሩ በኢትዮጵያ ሕዝብ ዘንድ ተናቀ ተጠላ፤ ከትግሬና ከትግራይ ውጪ ኢትዮጵያን ለማየት ለማሰብ የሚችልበት አቅም አልባ በመሆኑ፣ አስተሳሰቡ ዓላማው ሩጫው ሁሉ ጎጠኛ በመሆኑ ኢትዮጵያ የምትባልን ሀገር ሥዕል በጭንቅላቱ የሌለች ከሌሎቻችን ልቦናም እንድትጠፋ የሚፈልግ በመሆኑ፣ ጭራሽም ሊያፈራርሳት ነገር የሚያሴር ክፋት የሚሸርብ በመሆኑ፣ ባጠቃላይ ለታሪኳ ለማንነቷ ለሥልጣኔዋ ለእሴቶቿ ሁሉ ጠላት በመሆኑ የሀገር ክህደት በመፈጸም ከመሬቷ ጀምሮ ሌሎች ብሔራዊ ጥቅሞቿን አሳልፎ የሚሰጥ የጠላት ቅጥረኛና ባንዳ በመሆኑ ለመንግሥትነት አይደለም ለዕድር አሥተዳዳሪነት እንኳን የሚበቃ አቅም ብቃት ችሎታ ቅንነት የኃላፊነት ታማኝነት ተጠያቂነት ግልጽነት ዕውቀት ተወዳጅነት የሌለው የወንበዴ ጥርቅም ስለሆነበት እንጅ መሥዋዕትነትን ለመክፈል ቆርጠው እንደመታገላቸውማ ቢሆን ማጭበርበር ማስገደድ ማስጨነቅ ማወናበድ ሳያስፈልጋቸው ዕድሜ ልኩን ያለ እነሱ የሚመርጠው ባልነበረ ነበር፡፡ ምክንያቱም ሕዝብ የሚወደውን እስከ ሞት ድረስ የሚታመንለትን ዋጋ የሚከፍልለትን የሚያከብረውን ይወዳልና፡፡ እሱም በተራው የመጨረሻውን ክብር ሰጥቶ ያከብራልና፡፡ የዛኑ ያሕል ደግሞ እስከ ሞት ድረስ መሥዋዕትነትን ለመክፈል የታመነ ቢሆንም እንኳ እንደወያኔ ሁሉ ለጥፋትና ለወረደ ለጠባብ የጥፋት ዓላማ መሥዋዕትነትን የከፈለ ሲያጋጥመው እጅግ ይንቃል ይጠላል ያወግዛል ይረግማል ያገላል ያዋርዳል ይጸየፋል ያንቋሽሻል ያበሻቅጣል እንደ መርገም ጨርቅ ይመለከታል፡፡

  1. “በዘመነ ደርግ ወያኔና ሸአቢያ ደርግን ሲታገሉ በነበረበት ወቅት የስንቅና ትጥቅ (logistics) ሌላም ድጋፍ ያደርጉላቸው እንደነበሩ ሀገራትና አንዳንድ አካላት በዚህ ዘመን ለእኛ ሊያደርግልን የሚችል ባለመኖሩ በቂ ስንቅና ትጥቅ ሊገኝ ስለማይችል ከንቱ ድካምና ከንቱ መሥዋዕትነት ነው” ለሚለው፡- እርግጥ ነው በዚያን ዘመን ወያኔና ሸአቢያ ሲያገኙት የነበረውን ዓይነት ድጋፍ ከእነኛው ሀገራት ማግኘት አንችል ይሆናል፡፡ ይሁንና በዚህ በኩል ያለውን ክፍተት ሸአቢያ ጦርነቱ የእኛ ብቻ ሳይሆን የራሱም መሆኑን በሚገባ ስለሚያውቅ ከምንም በላይ የኢትዮጵያን ሕዝብ ከወያኔ ነጥለው አርቀው ብቻውን ማስቀረት የሚችሉና የኢትዮጵያን ሕዝብ ድጋፍ ማግኘት ከጎናቸው ማሰለፍ የሚችሉ እንዲህ ዓይነት አጋዥ ኃይል ማግኘቱን ቢሳልም የማያገኘው ወርቃማ ዕድል መሆኑን ጠንቅቆ ስለሚያውቅ በስንቅና ትጥቅ በኩል ያለውን ክፍተት ሸአቢያ ለእኛ ብሎ ሳይሆን ለራሱ ብሎ የሚያደርገው የሚያቀርበው በመሆኑ ይሄ የሚያሳስብ ጉዳይ አይደለም፡፡ እነ አቶ ኢሳይያስ በግልጽ እንዳስታወቁት “ላደረኩላቹህና ለማደርግላቹህ ድጋፍ ምንም ዓይነት ምላሽ አልፈልግም የተረጋጋች የበለጸገች እኩልነትና ፍትሕ የሰፈነባት ሰላማዊት ኢትዮጵያን ብሎብ የተረጋጋና ሰላማዊ የቀጠናው ሀገራት እንዲኖሩ ካለኝ ጽኑ ዓላማ ያደረኩትና የማደርገውም በመሆኑ” በማለት ያስታወቁና ለመካስም ካላቸው በጎና ቁርጠኛ አቋም በመነሣት የተዋሐደችና ጠንካራ ምሥራቅ አፍሪካን ለመፍጠር ካላቸው የተቀደሰና ታላቅ ርእይ አንጻር ይሄንን ለማሳካት ያስችል ዘንድ መሠራት ያለባቸውን ሥራዎች እየሠሩ እንደሆነ አምነው ታሪክ ሠርቶ ለማለፍ እየተንቀሳቀሱ እንደሆነ ዓላማቸውን ከረጅም ጊዜና ከአጭር ጊዜ አቅድ አኳያ ግልጽ ያደረጉ በመሆኑ “እነ አቶ ኢሳይያስ ለዚህ ሁሉ ውለታ ምላሽ ሳይፈልጉ ይሄንን ሁሉ ነገር ሊያደርጉልን አይችሉም ላደረጉትና ለሚያደርጉት ምን ልንመልስ ምን ልንከፍል ነው?” የሚያስብልና የሚያሳስብ ጉዳይ አይደለም፡፡ ሁላችንም መወጣት ያለብንን ግዴታና ኃላፊነት የሚጠበቅብንንና ማድረግ ያለብንን ሥራ ነው እየሠራን ያለነው፡፡

ይሁን እንጅ ለሀገራችንና ለሕዝባችን በማሰብ ታጋይ ወገኖቻችን የማይሆን ውለታ (commitment) ውስጥ እንዳይገቡ የምንሠጋና እንዲገቡም የማንፈልግ ከሆነ ለእኛ ነጻነትና ጥቅም ሲሉ ሁለንተናቸውን አሳልፈው የሰጡ እነሱ እንኳን እንዳሉ በማሰብ እያንዳንዳችን ከተረፈን ሳይሆን ምቾታችንን ቆጠብ በማድረግ “ለእኛ ይቅርብን! እኛን ይቸግረን!” ብለንም ቢሆን ትርጉም ያለው ድጋፍ ማድረግ ይጠበቅብናል፡፡ በወሬና ከንፈር በመምጠጥ ወይም በማጨብጨብ ብቻ የሚገነባ የሚሠራ ምንም ነገር የለም፡፡ ተግባር ያስፈልጋል ሀገርን መውደድ በተግባር ከምናደርገው አንዳች ነገር ውጭ በምንም ሊገለጽ አይችልም፡፡ ይሄንን ማድረግ ሳይችል ወሬ ብቻ የሚያወራ ካለን ሊያመጣው የሚችለው ለውጥ ካለመኖሩም በላይ ለወያኔ ዕድሜ መርዘም የራሱን እገዛ በማበርከቱ በሀገር ላይ የሚደርሰው ጉዳትና ኪሳራ ከወያኔ በማይተናነስ መልኩ በታሪክ ተጠያቂ እንደሆንን ልንገነዘብ ይገባል፡፡

በተለይ በተለይ ሀገር ብዙ ወጪ አውጥታባቹህ ሳይማር አስተምሮ ተቸግሮ አሳድጎ ነገር ግን በተለያዩ ገፊ ምክንያቶች (push factors) ከሀገራቹህ ተሰዳቹህ እናንተ እዚህ እንድትደርሱ ሽራፊ ሳንቲም ያላወጣባቹህን የባዕድ ሕዝብና የባዕድ ሀገር በማገልገላቹህ ሀገራቹህን ሕዝባቹህን ባለማገልገላቹህ ውለታውን ለመክፈል ባለመቻላቹህ ቁጭት የሚያንገበግባቹህ የሚቆጫቹህ የሚከነክናቹህ ዕረፍት የነሳቹህ ወገኖች ካላቹህ በተለያየ ምክንያት በረሀ ወርዳቹህ ትግሉን በአካል መቀላቀን ባትችሉም ለዚህ ሕዝባዊ ትግል ትርጉም ያለው ድጋፍ በማድረግ ሀገርራቹህን ልታገለግሉ ባለመቻላቹህ የተሰማቹህን ቁጭት ጸጸት በዚህ መወጣትና ሀገር ወገናቹህን መካስ እንደምትችሉ እንዲሁም ደግሞ  ጉልበታቹህን ዕውቀታቹህን ችሎታቹህን በባዕድ ሀገራት በማፍሰስ ዕድሜያቹህን የፈጃቹህና በዕድሜ መግፋት ምክንያት ከዚህ በኋላ በዕውቀታቹህ በጉልበታቹህ በችሎታቹህ ሀገራቹህንና ሕዝባቹህን ማገልገል የማትችሉ ጡረተኛ ወገኖች ሁሉ ካፈራቹህት ካላቹህ ገንዘብና ንብረት ቁጭታቹህን ጸጸታቹህን ሊያስወግድላቹህ ሊያስወጣላቹህ የሚችል መጠን ያለውን ገንዘብ ለትግሉ በማበርከት መንፈሳዊ እርካታን እንድታገኙ ይንን አጋጣሚ እንድትጠቀሙበት ላመለክታቹህ እወዳለሁ፡፡

የሞቀ ቤታቸውን ቅንጡ ኑሯቸውን ከፍ ያለ ደረጃቸውን ሁለነገራቸውን ጥለው ለእኔና ለእናንተ ለሚወዷት ሀገራቸው ሲሉ ነፍሳቸውን እስከመስጠት ታምነውና ቆርጠው በረሀ የገቡ ፕሮፌሰር ዶክተር ኢንጂኒየር… ወገኖቻችን ግንባር በግንባር ተፋጠው ዕላያቸው ላይ የሚወርድባቸውን ዝናብና ፀሐይ ሳይማረሩ ከሞት ጋር ተፋጠው ለማሸለብ ፋታ አጥተው ያገኟትን ተቃምሰው በረሀብ እየተፈተኑ እነኝህንና ሌሎችንም ሁሉ ዋጋ እየከፈሉ ያሉ መሆናቸውን እያወቃቹህ ከሞቀ ቤታቹህ ሆናቹህ ይህንን ማድረግ ይከብዳቹሀል ለማለት እጅግ ይከብደኛል፡፡

  1. “ሸአቢያ እኛን ይዞ ወያኔን ለማስፈራራትና ከወያኔ የሚፈልገውን ለማግኘት እንጅ የምናደርገው ትግል ፍሬ እንዲያፈራ ለስኬት እንዲበቃም በፍጹም አይፈልግም” ይሄንን የሚሉ ሰዎች ምን ይጠቅሳሉ ለምሳሌ ይሉና “የአርበኞች ግንባር ትግል ከጀመረ 16 ዓመታት ሆኖታል፡፡ ይሄንን ሁሉ ዓመታት ሲቆይ አንድም የሚጠቀስ ተግባር ለመፈጸም አልቻለም እንዲዋጋ አልተፈቀደለትም ዝም ብለው ነው እንዲቀመጡ ያደረጋቸው” ይላሉ፡፡ ይመስለኛል እንዲህ እንዲሉ ያደረጋቸው ስለትግል ስለጦርነት በቂ ግንዛቤ አለመያዛቸው ነው፡፡ ምክንያቱም አሁን ባለው ሁኔታ ውጤት ያለው ጦርነትም ሆነ ሽምቅ ውጊያ በቂ ኃይል ሳይያዝ፣ በቅጡ ሳይደራጁ፣ ሕዝባዊ ዕውቅናና ድጋፍ በበቂ ደረጃ ሳይገኝ ማድረግ ታይቶ ለመጥፋት ካሆነ በስተቀር ዘለቄታ ያለው እንቅስቃሴ ለማድረግ አይቻልም፡፡ ይሄንን ቅሬታ እንደሚያነሡ ሰዎች አስተሳሰብ ቢሆን ኖሮ የአርበኞች ግንባር ባለው አነስተኛ ኃይል እንደተመሠረተ ተንቀሳቅሶ ቢሆን ኖሮ ገና ድሮ ጠፍቶ ነበር፡፡ እንደሚመስለኝ ሸአቢያም ይሄንን እንዳያደርጉ የከለከለበት ምክንያት የተጠናከረ ኃይል እስኪኖራቸው እስኪይዙ መኖራቸው መደራጀታቸው በኢትዮጵያ ሕዝብ ዘንድ በቂ ግንዛቤ እስኪያዝበት ድረስ መጠበቅ አስፈላጊ ስለሆነ ነው፡፡ በመሆኑም ይሄንን ቅሬታ የሚያቀርቡ የትግሉ አካል የነበሩ አሁን ላይ በዚህ ቅሬታቸው ምክንያት ከዓመታት በፊት ትግሉን ጥለው የወጡ ግለሰቦች በወቅቱ ሸአቢያ ይሄንን ባለመፍቀዱ ያነሡበት ቅሬታ ተገቢ አይመስለኝም፡፡ ሸአቢያን በጣም በጥርጣሬ ዓይን ስለምናይ ብቻ እያንዳንዷን ነገር በክፋት እየተረጎምን ለተሳሳተ ድምዳሜዎች እየተዳረግን እንደሆነ ልብ ብንል መልካም ነው፡፡ ይህ ችግር በሥራችን ላይ የራሱ የሆነ እንቅፋት ሊፈጥር ይችላልና በማስተዋል ብንራመድ መልካም ነው፡፡

አሳቢ የመሰሉ ወገኖች የሚሰጡትን ምክር ሐሳብና ተቃውሞ አሳቢ ሆነው ሳይሆን ወያኔ ገዝቷቸው ቅጥረኞች ስለሆኑ እንደሆነ በምን ልናውቅ እንችላለን?

ይሄን ለመለየት በተለይ በአሁኑ ጊዜ ብዙም የሚያስቸግር አይመስለኝም ለማንኛውም እነኝህ ነጥቦች ይጠቅማሉ ብየ አስባለሁ፡-

  1. የሚናገሩትና የሚጽፉት ነገር ከረጅም ጊዜና ከአጭር ጊዜ አኳያ በአንድም ሆነ በሌላ መንገድ ሀገርንና ሕዝብን ሳይሆን ወያኔን የሚጠቅም ከሆነ፡፡
  2. የሚናገሩትና የሚጽፉት ነገር ትግሉን ወደኋላ ለመሳብ ለማሰናከል የሚያሴር ከሆነ፡፡
  3. አሳቢ መስለው እኩይ ሥራቸው የሚከውኑት ወሳኝና አንገብጋቢ ወቅትን (timing) እያዩ ከሆነ ማለትም ወያኔ ሥጋት በተጋረጠበት ሰዓትና አጋጣሚዎች ላይ ከሆነ፡፡ ለምሳሌ ባለፈው አርበኞችና ግንቦት ሰባት ውሕደት በፈጸሙ ወቅት፣ ሰሞኑን ማጥቃት በመጀመሩ ትግሉን ሊያጠናክሩ የሚችሉ ወሳኝ ወሳኝ ምእራፎች በሚመዘገብበት ወቅቶች ላይ ማለት ነው እነኝህ ቅጥረኞችም ይሄንን እመርታ ሊቀለብስ የሚችል ሥራን በመሥራት እራሳቸውን ጠምደው ታይተዋል፡፡
  4. እነዚህ አሳቢ መስለው የቀርቡ ግለሰቦች ሕዝባችን ነጻ እንዲወጣ የሚያቀርቡት ተጨባጭና ጠቃሚ አማራጭ የሌለ መሆኑና “ዝም ብለን አርፈን በወያኔ መገዛት ነው የሚሻለን” የሚል ዓይነት ከሆነ፡፡

እነዚህ እነዚህ ነጥቦች ቅጥረኞችን ለመለየት ይጠቅማሉ የሚል እምነት አለኝ፡፡ እነዚህ ኅሊናቸውን ብቻ ሳይሆን ሁለንተናቸውን ለሆዳቸው የሸጡ ምንደኛ ግለሰቦች ለወያኔ ያደሩ ሳይመስሉ መርዘኛ ሐሳቦቻቸውን ሳይፈሩና ሳያፍሩ በነጻነት ለመናገር ለመጻፍ የሚጠቀሙበት አንድ ሽፋን አለ “ሐሳብን በነጻነት የመግለጽን መብት ከመጠቀምና ተግባራዊ ከማድረግ አኳያ” በሚል ሽፋን ነው፡፡ እንዳሉትም በትክክል ሐሳብን በነጻነት ከመግለጽና ይሄንን ዲሞክራሲያዊ መብት ለመጠበቅና ለማስጠበቅ ከሚል አንጻር ያደረጉት ከሆነ ሚዛናዊነትን ሲጠብቁ ከሁለቱም አቅጣጫዎች ጠንካራ ጠንካራ ሐሳቦችን ሲያስተናግዱ ታገኟቸዋላቹህ፡፡ ነገር ግን ከሁለቱም አቅጣጫዎች ያሉ ጠንካራ ጠንካራ የመከራከሪያ ሐሳቦችንና ተሟጋቾችን የማያስተናግዱና ሚዛናዊነትንም የማይጠብቁ ወያኔን ተጠቃሚ ወደሚያደርግ ወገን የማድላት ዝንባሌ የሚታይባቸው ከሆነ ይሄንን “ሐሳብን በነጻነት የመግለጽ መብትን ተግባራዊ ከማድረግ” የሚለውን መብት ሥውር ተልእኮዋቸውን ለማሳካት ለሽፋን እየተጠቀሙበት ነውና ቅጥረኞች መሆናቸውን ልታረጋግጡ ትችላላቹህ፡፡

ለምሳሌ የቪኦኤው “ጋዜጠኛ” ሔኖክ ሰማእግዜር አቶ ኃይለማርያም ከተማሩበት ዩኒቨርስቲ ሊያገኙት ስለነበረውና በተቃውሞ ምክንያት እንዳያገኙ የተደረገውን ሽልማትና እውቅና ዘገባ በሠራበት ጊዜ ዘገባውን የሠራበት መንገድ ግልጽ በመሆኑ ማንነቱን ለመለየት አስቸጋሪ አልነበረም፡፡ ምክንያቱም ሆን ብሎ የጋዜጠኝነትን መርሖዎች ግልጽነትንና ሚዛናዊነትን ባለመጠበቅ ወያኔን ለመጥቀም በማሰብ ትክክለኛ መረጃወች እንዳይካተቱ በማድረግ ዕውነትን ያዛባ ዘገባ ሠርቷል፡፡

ይህ ሰው ይሄንን ዐይን ያወጣ ስሕተት ረዳት አብራሪ ኃይለመድኅን አበራ ቦይንግ 767 የመንገደኞች አውሮፕላንን (በረርትን) በመጥለፍ አውሮፓ ጥገኝነት የጠየቀበትን ዘገባም በተከታታይ በሠራበት ወቅት ወያኔ “አብራሪው ለረጅም ጊዜ የአእምሮ ጭንቀት ላይ ነበረ ይሄንን ያደረገው ሕመሙ ተባብሶበት ከዚህ ችግሩ የተነሣ ነው” ብሎ የደረሰበትን የፖለቲካ ኪሳራ ለመሸፋፈን ጥረት በማድረግ የሰጠውን ሐሰተኛ ስም አጥፊ መግለጫ እውነት ወይም ትክክለኛ ለማስመሰል በማሰብ አሁንም ሚዛናዊነትን ያልጠበቀና የወያኔን ጥቅም ለማስጠበቅ የጣሩ ዝግጅቶችን አቅርቦ ነበር፡፡ እናም ማንም ጋዜጠኞችም ሆኑ የብዙኃን መገናኛዎች ግልጽ የሆኑ የሞያዊ አሠራር ግድፈቶችን ሲፈጽሙ ስታዩ ያ ሰው ወያም ያ አካል ለሚከላከልለት ሀቁን ለደበቀለት (ለወያኔ) ያደረ የተገዛ የሱን ጥቅም ለማስጠበቅ የሚጥር እንደሆነ ልታረጋግጡ ትችላላቹህ፡፡ እንዲህ መሆኑ በግልጽ የታወቀ ሰው በዚያ የጥፋት ዲርጊቱ ቢገለልና ቢወገዝ ተወገዝኩ ተገለልኩ ጥቃት ደረሰብኝ ብሎ ሊከስ ሊያማርር ሊወቅስ አይችልም መብትም የለውም፡፡

ምክንያቱም ጉዳይ ከሞያዊ ግድፈት አልፎ ሞያውን በማርከስ ኃላፊነትና ግዴታውንም ለግል ዓላማውና ጉዳዩ በመተላለፍ ሞያው የጣለበትን ኃላፊነት አላግባብ ሕገ ወጥ በሆነ መንገድ በመጠቀም ማለትም ወያኔ ወይም የወያኔ አባል በመሆኑ ሆን ብሎ የወያኔን ጥቅም ለማስጠበቅ በመሞከር ጉዳዩን ወደ የመደብ ትግል ፍትጊያ አሻግሮታልና ወይም እንዲለወጥ ያደረገ በመሆኑና የኢትዮጵያ ሕዝብ ደግሞ በወያኔ ላይ ተስፋ ቆርጦ ትጥቅ ያነሣበት ሁኔታ ላይ ያለ በመሆኑ ይህ ሰው ከመወገዝም አልፎ ቦታና ሁኔታዎች ቢፈቅዱና እርምጃ ቢወሰድበትም እንኳ ድርጊቱ ሕገ ወጥ ሊሆን የሚችልበት ሁኔታ የለም፡፡ ምክንያቱም በጋዜጠኝነቱ ያለውን ከለላ በሠራው ወንጀል አጥቶታልና፤ እራሱን ከጋዜጠኝነት አውጥቶ እንደ አንድ የወያኔ ታጋይ ሁሉ የወያኔ ጥቅም አስከባሪ አድርጓልና፡፡

ይህ እርምጃ ቢወሰድበት “ሐሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት ይከበር! እያሉ እነሱ ራሳቸው ይሄንን የሚያደርግን ሰው ያጠቃሉ” ተብሎ ሊገለጽ በፍጹም በፍጹም አይደባም፡፡ ይሄ ብየና አለመብሰልና አለማገናዘብም ነው፡፡ ምክንያቱም የሰውየው ሥራ ሆን ብሎ ከሞያዊ ሥነምግባሩ ውጭ በፈጸመው ስሕተት ምክንያት ሐሳብን በነጻ ከመግለጽ ጋራ ምንም የሚያገናኘው ነገር የሌለ በመሆኑና ይህ የፈጸመው ስሕተትም እራሱን እንደ አንድ የወያኔ ወታደር አድርጎ ስላቆመ ያለውን የጋዜጠኝነትም ሆነ የሌላ መብት ከለላውን ስለሚያሳጣው፡፡ ይህ ሰው ሚዛናዊነትንና ከሁለቱም ወገኖች ጠንካራ የሆኑትን ሐሳቦች ለማስተናገድ የፈቀደ ባለመሆኑ ይልቁንም ትክክለኛ መረጃዎችን ሆን ብሎ የሰወረ በመሆኑ ሐሳብን በነጻ የመግልጽ መብትን ለቅጥፈቱ ሽፋን ሊያደርግ ስለማይችል፡፡

ይሄ “ጋዜጠኛ” ሆነ ሌላ ማንነቱ የታወቀ ሰው ኢትዮጵያዊያን በሚያደርጉት ማንኛውም ኩነት ተገኝቶ ልዘግብ ቢልና ሕዝብ የሚያውቀው በወያኔነቱ በመሆኑ ከወያኔ ጋርም ልዩነታችንን በውይይትና በሌሎች ዲሞክራሲያዊ (መስፍነ ሕዝባዊ) መንገዶች ልንፈታ የምንችልበት መንደግ ዕድል ተጠርቆሞ የተዘጋ በመሆኑና በቀረልን ብቸኛ አማራጭ በኃይል እርምጃ ለመፍታት መብታችንን ለማስከበር የተገደድንበት ሁኔታ ውስጥ ያለን በመሆኑ እንዲህ ዓይነቱን ሰው ሕዝቡ በራሱ ዝግጅቶች እንዳይገኝ የመከልከል የማስወገድ መብት አለው፡፡

“እነዚህ የሚከለከሉ (ከዚህ ዞር በሉልን አንያቹህ!) የተባሉ ጋዜጠኛም ሆኑ ሌሎች ግለሰቦች የወያኔ ደጋፊ ወይም ወያኔ እንኳን ቢሆኑ በመነጋገር ነው እንጅ ልዩነቱ መፈታት ያለበት ለምን በኃይል ይሆናል?” ከተባለ በመነጋገር ልዩነትን ለመፍታት 24 ዓመታት ለምነን ተማጽነን አይሆንም አይቻልም ተብለን መብታችንን ተነጥቀን ተነጋግሮ ልዩነትን የመፍቻው ዘመን አልፎ ሳንወድ በግድ ተገፍተን ወደ ሌላኛው የተተወልን ብቸኛ አማራጭ ማለትም በትጥቅ ትግል የኢትዮጵያን ሕዝብ ነጻነትና መብት የማስከበር አማራጭ የገባንበት ወቅት ውስጥ በመሆናችን እንደዚህ ዓይነት ሰዎችን ካጠገባችን እንዳይደርሱ መከልከል ማራቅ እንችላለን መብታችንም ነው፡፡ ሌላ እርምጃ በእነሱ ላይ ለመውሰድ ያሉበት ሀገር ሕግና ሁኔታዎች አይፈቅዱም እንጅ እንደጠላትነታቸው ሁሉ ሁሉንም ዓይነት እርምጃ በእነሱ ላይ ለመውሰድ የያዝነውና የገባንበት ሕዝባዊ ትግል ያስገድደናል፡፡

ሌሎችም ድረ ገጾችና የብዙኃን መገናኛዎችም ቢሆኑ የመጻፍ፣ የመናገር፣ ሐሳብን የመግለጽ ነጻነት ሲባል የሕዝብን የጋራ ጥቅም የሀገር ደኅንነትንና ህልውናን ለመጠበቅ ለመንከባከብ የተለየ ሐሳብ ካለ እሱን ለማስተናገድ የተሰጠ መብት እንጅ ሀገርንና ወገንን የሚጎዳ ወይም ሀገርንና ወገንን የሚጎዳን አካል ጥቅም ለመጠበቅ የሚነገር የሚጻፍ ሐሳብን ለማስተናገድ የተሰጠ መብት አይደለም፡፡ በግልጽ አማርኛ ወያኔ የዚህች ሀገርና የሕዝቧ ቀንደኛ ጠላት እንደመሆኑ ማንም ሰው የወያኔ ቅጥረኛ ሆኖ የወያኔን ጥቅም ለማስጠበቅ ማለትም ከድሮ ጀምሮ የራሱን ቡድናዊ ጥቅም ለማስጠበቅ ሲል የሀገርን ሕልውናንና የሕዝብን ደኅንነትና ጥቅሞች ለመጉዳት ለማጥቃት ለአደጋ ለመዳረግ የሚያሴረውን የወያኔን ጥቅሞች ለማስጠበቅ የተሰጠ መብት አይደለምና በዚህ ሽፋን ይሄንን ሊያደርጉ እንደማይችሉ ጠንቅቀው ሊያውቁት ይገባል፡፡ የትም ሀገር ቢሆን ያለው አሠራር ይህ ነው፡፡ አሜሪካም ብትሆን ዜጋዋ የሀገሪቱን ብሔራዊ ጥቅም የሚጎዳ ሥራ ሠርቶ “ሐሳብን የመግለጽ ነጻነት ነው” ቢል አትሰማውም “ብሔራዊ ጥቅሜን ለአደጋ ዳርጓል የሀገርንና የሕዝብት ደኅንነት ለአደጋ አጋልጧል ወይም ለጠላት ተቀጥሮ በመሥራት” ወንጂላ እንደ ስኖውደን ታሳድደዋለች እንጅ ሐሳብን የመግለጽ ነጻነት ነው ብላ አትምረውም፡፡

እነኝህ አካላት ሞያዊ ሥነምግባራቸውን በመጣስ የሀገራችንን ጠላት የወያኔን ጥቅም ለማስጠበቅ ከወያኔ ጋር በማበር የወያኔ ቅጥረኛ በመሆን መረጃን በማዛባት እንደሚንቀሳቀሱ ባወቅን ጊዜ ይሄንን መብት አጥተዋልና ይሄንን መብት ለሽፋን መጠቀም አይችሉም፡፡ አሜሪካ ጥቅሟን የሚጎዳባትን ሰውና ዘገባ የሀገርና የሕዝብ ጠላት አድርጋ እንደፈረጀችና እንደምታሳድድ ሁሉ እኛ ኢትዮጵያዊያንም የሀገራችንንና የሕዝባችንን ብሔራዊ ጥቅሞች የሕልውናችንና የደኅንነታችን ጠላት የሆነው ወያኔን ያገለገለ ወይም የደገፈ ጋዜጠኛንም ሆነ ማንኛውንም ሌላ አካል ሁሉ የሀገራችንና የሕዝባችን ጠላት እንፈርጃለን እናሳድዳለንም፡፡ በግልጽ አማርኛ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሁሉም ዕድሎች ተዘግተውበት መብቶቹን ለማስከበር ተገዶ የትጥቅ ትግል ውስጥ የገባበት ሁኔታ ውስጥ ያለ በመሆኑ ማንኛውም ሰው ወዶና ፈቅዶ የወያኔ አባልና ደጋፊ የሆነ ካለ ይህ ሰው ሊሸሸግበትና ሊታደገው የሚችል ምንም ዓይነት ዋስትና እንደሌለው ጠንቅቆ ሊያውቅ ይገባል፡፡

ይመስለኛል በሌላም በኩል ወይ ድፍረት ቁርጠኝነት አጥተው ይሁን ወይ ደግሞ ቅድሚያ የሚሰጡት ቤተሰባዊም ሆነ ሌላ ጉዳይ ኖሮባቸው ብቻ በአንድም በሌላም ምክንያት በትጥቅ ትግሉ መሳተፍ የማይችሉ ከመሆናቸውና የትግሉ አካል ካለመሆናቸው የተነሣም “የሚመጣው ለውጥ በግል እኔን አያካትተኝም በተዋናይነት ቦታ ሰጥቶ አያሳትፈኝም” ከሚል ሥጋትና “እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል” ከሚል ለራሳቸውም ለወለዷቸው ልጆችም ለሀገር ለወገንም ፈጽሞ የማይጠቅም የደነቆረና በሽተኛ የሆነ የራስወዳድነትና የምቀኝነት ጠንቀኛ አስተሳሰብ ወያኔ ወይም የወያኔ ደጋፊም ሳይሆኑ እየተደረገ ያለውን የትጥቅ ትግል የሚቃወሙ ወይም የማይደግፉ ያሉ ይመስለኛል፡፡ እንዲህ የሚያስቡ ግለሰቦች የማሰብና የማገናዘብ ችሎታ በጣም የወረደ ነው፡፡ ከተቆጣጠራቸው ክፉ የምቀኝነት መንፈስ የተነሣ እንደ ዜጋ እራሳቸውን ጨምሮ ተጠቃሚ የሚያደርጋቸው አስመስጋኝና አስከባሪ ሥራ በሌሎች ሲደረግ ሲያዩ ዐይናቸው ደም ይለብሳል፡፡ ዜጋ እንደመሆናቸው የዜግነት ግዴታ እንዳለባቸው ተረድተው እንደ ዜጋ ለሀገሬ ምን ማበርከት ይጠበቅብኛል? ሀገሬ ወገኔ ከኔ ምን ይጠብቃሉ? ብለው ራሳቸውን በመጠየቅ የዜግነት ግዴታቸውን ለመወጣት አስበው በቅንነት ተንቀሳቅሰው የሚያውቁ አይደሉም፡፡ ከተንቀሳቀሱም ለዝና ወይም ድብቅ የሆነ ሌላ የግል ጥቅማቸውን ለማስከበር ለማግኘት እንጅ ለሀገርና ለወገን በማሰብ አንዳች ነገር አድርገው አያውቁም፡፡

እነኝህ ግለሰቦች በሚቃወሙበት ጊዜ ለመቃወማቸው ምክንያት ሲጠየቁ ብዙ ጊዜ ሊያቀርቡት የሚችሉት ምንም ዐይነት ምክንያት የላቸውም፡፡ ካቀረቡም የረባ አይሆንም፡፡ ወይ እራሳቸው አይሠሩትም ወይ ደግሞ ሌላው እንዲሠራው አይፈልጉም አይፈቅዱም፡፡ ሌላው ሠርቶት ሲደነቅ ሲከበር ሲያዩ በሰይጣናዊ የቅናትና የምቀኝነት መንፈስ ቆሽታቸው ይደብናል፡፡ እንኳንና ለልጆቻቸው፣ ለሀገር፣ ለወገን ለራሳቸውም እንኳን ቢሆን ምን ቢሆን እንደሚበጅ በቅጡ የሚያውቁ ሰዎች አይደሉም፡፡ የሚገርመው ለምን እንዲህ እንደሚሆኑ ራሳቸውም እንኳን አያውቁትም፡፡ የሚያደርጉት ነገር ከግል ሕይዎታቸው ጀምሮ እስከ ሀገር ድረስ እንደሚጎዳ እንደማይጠቅም እንኳንና እራሳቸው ሊያስቡት ተነግሯቸውም እንኳ አይገባቸውም እንዲገባቸውም አይፈልጉም፡፡ በጣም የሚገርመው እንዲህ ዓይነት ክፉ የቅናትና የምቀኝነት መንፈስ ተማሩ በሚባሉት የሚብስ መሆኑ ነው፡፡ ችግሩ ግን የተማረ ከሚባለው ጀምሮ መሀይም እስከሚባለው ዜጋ ድረስ በየቦታው አለ፡፡ ሥራ እንዳይሠራ ብዙ ያውካሉ፡፡ በተለይ የተማሩ የተባሉቱ ተቃውሟቸውን የትም ሲያቀርቡ ተቃውሟቸው በቂና አሳማኝ ምክንያት ይኖረው ይሆናል በሚል ግምት ብዙ ጊዜ ሕዝብ ይሰናከልና ድጋፍ መስጠት ላለበት አካል ድጋፍ ይነፍጋል፡፡ በእንደዚህ ዓይነት ችግር ምክንያት የተቀደሰ ዓላማ ተይዞ ስንት ሊሠሩ የሚሞከሩ በርካታ ሥራዎች ከንቱ ሆነው ይቀራሉ፡፡ የእነዚህን ችግር ያለባቸው ግለሰቦች ፈተና ተቋቁሞ ሥራ መሥራት የተቀደሰን ዓላማ ከግብ ማድረስ እንደ ዕድል አልፎ አልፎ የሚገኝ እንጅ በብዛት የሚታይ አይደለም፡፡ እናም ከዚህ ችግራቸው የተነሣ ሕዝባዊ ትግሉን የሚቃወሙ ወገኖች ሊኖሩ እንደሚችሉ እገምታለሁ፡፡ የሆነ ሆኖ የሚያቀርቡት ተቃውሞ ከወያኔነት አንጻር ባይሆንም ቅሉ በሕዝባዊ ትግሉ ላይ የሚያደርሱት ጉዳት ከቅጥረኞች የማይተናነስ እንዲያውም የባሰ በመሆኑ እነሱንም እንደ ወያኔ ሁሉ የሀገርና የሕዝብ ጠላት አድርጎ መቁጠርና የሚፈጽሙትንም ጥቃት መከላከል ግዴታ መሆኑን መዘንጋት የለብንም፡፡

የተያያዝነው ትግል የሞት ሽረት ትግል ነው፡፡ ጨዋታ አይደለም የተያዘው ሀገርንና ሕዝብን ከጠባብ ጨካኝ ደንቆሮ አንባገነን አገዛዝ መዳፍ ፈልቅቀን ነጻ ለማውጣት ነው እየታገልን ያለነው፡፡ የግድ የሚወሰዱ ቆራጥ አቋሞች ይኖራሉ፡፡ የመረጥነውን የማውረድ መብቱ እያለን የመረጥነውን መንግሥት በኃይል ለማውረድ መሥዋዕትነት የምንከፍልበት ምንም ምክንያት የለንም መርጠን ያስቀመጥነውን መንግሥት ማንም በኃይል እንዲያስወግደው አንፈልግም አንፈቅድምም፡፡ አገዛዙ ያልመረጥነው በመሆኑና በኃይል የተጫነን ይህንን አገዛዝ በምርጫ ልናወርደው ልናስወግደው የሚያስችለን ሥርዓት በፍጹም የሌለ ስለሆነ እንጅ፡፡ ከተረባረብን በእርግጠኝነት ተሳክቶልን በቅርብ ጊዜ ሀገርንና ሕዝብን ነጻ እናወጣለን፡፡ ባለመብሰላችን እየሆነና ሊሆን ያለውን በማስተዋል አቅቶን አርቀንና ግራ ቀኝ መመልከት ተስኖን እያንዳንዳችን መወጣት ያለብንን ግዴታና ኃላፊነት መወጣት ቸግሮን መረባረብ መተባበር ካልቻልን ደግሞ ወያኔ እንደሚለው ለ60 ዓመታት ብቻ አይደለም ለዘለዓለሙ ባልመረጥከውና በኃይል ጫንቃህ ላይ ተጭኖ በነፍስ በሥጋህ እየተጫወተብህ ባለው አገዛዝ በወያኔ የጭቆና ቀንበር ስር ተጠፍንገህ ሰብዓዊ ክብርህን አተህ እየተዋረድክ የባርነት ኑሮህን እየኖርክ ይንንም የውርደት ኑሮ ለልጅህ እያወረስክ ፍዳህን ትቆጥራታለህ! በእርግጠኝነት ይህ እንዲሆን የሚወድና የሚደቅድ ኢትዮጵያዊ አይኖርምና ያለን ብቸኛ አማራጭ መረባረብ ነው እንረባረብ ወገን!!!

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!!!

ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው

amsalugkidan@gmail.com

 

22 አመት እስራት ያስፈረደብን ኢስላማዊ መንግስት ወይስ ኢስላማዊ መጅሊስ እንዲቋቋም መጠየቃችን??

$
0
0

muslim addis
አቡ ዳውድ ኡስማን

የኢትዬጲያ ህዝበ ሙስሊም በኮሚቴዎቻችን አማካኝነት ለመንግስት ያቀረብነው ጥያቄ ኢስላማዊ መጅሊስ ይመስረት እንጂ ኢስላማዊ መንግስት ይቋቋምል የሚል ጥያቄ አልነበረም፡፡ ኮሚቴዎቻችንን እስከ 22 አመት የሚደርስ እስራት ያስቀጣቸው ወንጀል ኢስላማዊ መንግስት ለመመስረት ህዝብን ለሽብር በማነሳሳት የሚል አሳፋሪ የሃሰት ክስ ነበር፡፡ አንዳንድ የሌላ እምነት ተከታዬች አውቀውም ይሁን ሳያውቁ ወይም የሚከፈላቸው ካድሬዎች ኮሚቴዎቻችን እንደተባለው ኢስላማዊ መንግስት ለመመስረት ሲንቀሳቀሱ መንግስት ያሰራቸው እንደሆነ አስመስለው ሲያቀርቡ እና አስተያየት ሲሰጡ ታዝቤያለው፡፡

እስቲ ለማንኛውም እዚህ ጋር ቆም እንበልናል ኢስላማዊ መጅሊስ ይመስረት ማለታችን ከቶውንስ በምን ስሌት ኢስላማዊ መንግስት ለመስረት መንቀሳቀስ በሚል ሊተረጎም እንደሚችል አብረን እንመልከተው

ቅድሚያ የመጅሊስ እና የመንግስትን ልዩነት ይህን ይመስላል

1. መጅሊስ የሙስሊሞች ተቋም ሲሆን መንግስት ግን የአንድን ሃገር ህዝብ በበላይነት በምርጫ ተመርጦ የሚያስተዳደር አካል ነው፡፡

2. መጅሊስ በሙስሊሞች በሚመረጡ የሃይማኖት አባቶች የሚመራ ሲሆን መንግስት ግን በሁሉም የሃገሪቱ ዜጎች ሃይማኖት፣ዘር፣ቀለም ሳይለያቸው በጋራ ያስተዳድረናል የሚሉትን በምርጫ ወስነው የሚሰርቱት አካል ነው፡፡

3. መጅሊስ በህዝበ ሙስሊሙ በየመስጂዱ በሚመረጡ የሃይማኖት አባቶች የሚመራ ሲሆን መንግስት ግን በቀበሌ ወይም በየምርጫ ጣብያ ተምርጦ በአብላጫ ድምፅ የፓርላማ ወንበር ባገኘ ፓርቲ የሚመራ አካል ነው፡፡

4. ኢስላማዊ መጅሊስ ማለት በኢትዬጲያ ውስጥ የሚገኙ ሙስሊሞችን ወኪል በመሆን ከየትኛውም የፖለቲካዊ አስተሳሰብ ፀድቶ በሃይማኖታዊ ጉዳዬች ላይ ሙስሊሙን ወከሎ የሚሰራ፣ ሃይማኖቱን ምዕመናን የሚማሩበትን እና የሚተገብሩበትን ሁኔታ የሚያመቻች፣ አማኙ ማህበረሰብ ከመንፈሳዊ ሂወቱ በተጨማሪም በሃገሪቱ ሰላም እና ልማት ላይ ተሳታፊ እንዲሆን የሚያግዝ ተቋም ማለት ነው፡፡ መንግስት ማለት ግን ከሃይማኖታዊ ጉዳዬች በጸዳ መልኩ በሁሉም የማህበራዊ፣ኢኮኖሚያዊ፣ፖለቲካዊ እና ሌሎች ተግባራቶች ላይ ሀዝብን ተጠቃሚ እንዲሆን እና ዜጎች በሃገራችን በሰላም፣በአንድነት፣በነፃነት እና በሃገራቸው ፍትሃዊ በሆነ ልማት ተጠቃሚ የሚሆኑበትን ተግባር የሚያከናውን ግዙፍ አካል ነው፡፡

5. በተጨማሪም መጅሊስ እና መንግስት አንድ አለመሆናቸውን፣አንድ ሊሆኑም እንደማይችሉ በህገመንግስቱ አንቀፅ 11 ላይ ሰፍሮ ይገኛል፡፡

ይህ የሰማይ እና የምድር ልዩነት እያለ ከቶውንስ እንዴት ኢስላማዊ መጅሊስ እና ኢስላማዊ መንግስትን ገዢው ፓርቲ መለየት ተሳነው??

በትግራይ ክልል የውቅሮ ከተማ ህዝበ ሙስሊም ወኪል የነበሩት ኡስታዝ ቡሽራ ያህያ ፍርድ ቤት መጅሊስን ተቃውማቹሃል በሚል በሽብር ወንጀል በተከሰሱበት ወቅት የመከላከያ ቃላቸውን ሲሰጡ እንዲህ ብለው ነበር

“እኛ እኮ መጅሊስ እና መንግስት የተለያዩ መስሎን ነበር፡፡ በህዝበ ሙስሊሙ ያልተመረጡ ህገ ወጥ አመራሮችን ህዝበ በመረጣቸው ይተኩ ብለን የመጅሊሱን አመራሮች መቃወማችን መንግስትን እየተቃወምን መሆኑን አላወቅንም ነበር ፡፡ መጅሊስ ማለት መንግስት መሆኑን አሁን ነው ያወቅነው” በማለት ቃላቸውን ሰጥተው ነበር፡፡

በትክክልም የሙስሊሞች ተቋም የሆነው ኢስላማዊ መጅሊስ ይቋቋም ብሎ መጠየቅ ኢስላማዊ መንግስት ይመስረት ብሎ ከመጠቅ ጋር አንድ ሊሆን የሚችለው መንግስት እና መጅሊሱ አንድ ሲሆኑ ብቻ ነው፡፡

መንግስትም በሃምሌ 27 የፍርድ ውሳኔ በአደባባይ ያረጋገጠልን ነገር ቢኖር ይህንን ነው፡፡ የህዝበ ጥያቄ አንግበው መንግስት ጋር የቀረቡ ወኪሎችን እንዴት የመጅሊሱ አመራሮች ይቀየር ትሉኛላችሁ ? ምርጫው ቀበሌ ሳይሆን መስጂድ ውስጥ እንዴት ይካሄድ ትሉኛላቹ? ምርጫውንስ እንዴት ሙስሊሙ ነፃ ሆኖ እራሱ በሚያምንባቸው ህዝባዊ የምርጫ አስፈፃሚዎች ይካሄድ እንዴት ትላላችሁ?. መጅሊሱን መንካት እኔን መንካት ነው በመሆኑም ጥያቄያችሁ መጅሊሱን እንቀይር ማለታችሁ አንዱን የኔን ተቋም ኢስላማዊ ይሁን ማለታችሁ ነውና በማለት የ 22 አመት እስር ቅጣት በይኖባቸዋል፡፡

ሃገራችን ኢትዬጲያ ይህን ፍትህ የሚያሰፍን መሪ አልሰጣትም ፡፡ ጥቁሩን በነጭ ቀየረው.አሸባሪውን በንፁሃን መነዘረው፣ ህገ አክብሩ በሃይማኖት ጣልቃ አትግቡ ብሎ በአደባባይ ህገ መንግስቱን የሰበከውን ህገ መንግስቱን አፍራሽ ተብሎ በ22 አመት እስራት በግፍ እንዲቀጣ አደረገው፣ ሰላም የሰበከውን ሰላም አደፍራሽ አለው፣ ወዘተ…..

ሃይማኖት እና መንግስትን ለመደባለቅ የሚሞከር በፀረ ሽብር ክሱ 22 አመት እስራት የሚቀጣ ከሆነ ሐይማኖት እና መንግስት ይለያዩ፣ መንግስት በሃይማኖት ውስጥ እጁን ጣልቃ አያግባ ፣የህገ መንግስቱ አንቀፅ 11 ይከበር ያለ አካልስ ምን መሸለም ይኖርበታል?? ይህ ያደረጉት ወኪሎቻችንስ አሁን እጣ ፈንታቸው ምን ሆነ??

መጅሊሱን እና መንግስትን አንድ ተቋም ያደረጋቸው፣ የሃይማኖት ተቋሙን በፖለቲካ መሪ ካድሬዎች እንዲመሩ ያደረገ፣ የእምነት ቦታዎችን የፖለቲካ አጀንዳ ማስፈፀሚያ ያደረገ ባጭሩ አብዬታዊ መጅሊስ የመሰረተው አካልስ በፀር ሽብር ህጉ በስንት አመት ይቀጣ???

‘አብዬታዊ መጅሊስ “በኢስላማዊ መጅሊስ ይተካ በማለታችን ነው ኢስላማዊ መንግስት ለመመስረት በማሴር በሚል የሃሰት ዲሪቶ ክስ የወከልናቸው ኮሚቴዎቻችን በግፍ እስራት የተበየነባቸው፡፡

አብዬታዊ መጅሊስን ወይም መንግስታዊ መጅሊስን መቃወም ኢስላማዊ መንግስት ለመመስረት መጣር መሆኑን ገዢዎቻችን እስቲ ከህገ መንግስቱም ሆነ ምናልባትም እነሱ ብቻ ከሚመሩበት ህግ ካላቸው በገባቸው ቋንቋ ያስረዱን??

muslim dim

በየትኛው የአለማችን ክፍል ይሆን የሃገሪቱ መተዳደሪያ ደንብ የሆነውን ህገ መንግስት ይከበር ብሎ የሚጠይቅ አሸባሪ ያለው??የትኛው አሸባሪ ይሆን ህግ መንግስቱን በእጁ ይዞ በአደባባይ ህጉን አክብሩ እያለ የሚሰብክ?? የትኛው አሸባሪ ይሆን ሲደበድቧችሁ፣ሲመቷቹህ፣ሲገድሏቹም በሰላማዊ መንገድ ችላቹህ ዝም በሉዋቸው የሚል አሸባሪ ያለው?? በየትኛው የአለማችን ክፍል ይሆን የሰው ሰራሽ ህግ የሆነውን ህገ መንግስት ይከበር እያለ ኢስላማዊ መንግስት ለመመስረት የሚንቀሳቀስ አሸባሪ ያለው?? የትኛው አሸባሪ ነው በአደባባይ የሌሎች እምነት ተከታዬችን አክብሩ፣በሰላም ተኗኗሩ እያለ የሚሰብከው??የትኛው አሸባሪ ነው በሚሊዬን የሚቆጠር ደጋፊ ኖሮት ህግ እና ስርአት አክብሮ እንዲከበር የሚንቀሳቀሰው??በየትኛው ሃገር ነው ለሃገሪቷ ልማት እና ሰላም ሁሌም የበኩሉን አስተዋፅኦ የሚወጣ አሸባሪ ያለው?? የትኛው አሸባሪ ነው ሰላምን፣ ፍቅርን፣መቻቻልን፣አንድነትን የሚሰብክ ?? የዚህ መሰሉ አሸባሪ ያለው እምዬ ሃገሬ ኢትዬጲያ ውስጥ ብቻ ነው፡፡ይህን ተግባር በፈፀም የተወነጀሉት እነዚህ ብርቅዬ የሃገር ሃብት የሆኑ ኮሚቴዎቻችን ናቸው!!!

ውሸት ለጊዜው ፎቅ ገንብታ ብትቀመጠም በደሳሳ ጎጆ ያለችው እውነት አንድ ቀን ፈንቅላ መውጣቷ አይቀርም!

ውድ ወኪሎቻችን የሃቅ ፈራጁ ጌታ ነፃ ያወጣቹሃል ኢን ሻ አላህ

መስዋት እየሆኑ ለሚገኙት ኮሚቴዎቻን አላህ ብርታቱን፣ ቅዋውን፣ ሰብሩን፣ ኢስቲቃማውን፣ ደስታውን፣ ሰኪናውን ፣ ኢህላሱን ይወፍቃቸው!

አሚን

በቀለ ገርባ ሚኒሶታ ገቡ * የፊታችን ቅዳሜ ሕዝባዊ ስብሰባ አላቸው

$
0
0

bekele gerba 1

(ዘ-ሐበሻ) የኦሮሞ ፌዴራሊስት ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር ኦቦ በቀለ ገርባ ሚኒሶታ ገብተዋል:: በሚኒያፖሊስ ሴንት ፖል ኤርፖርት ሞቅ ያለ አቀባበል የተደረገላቸው ኦቦ በቀለ የፊታችን ቅዳሜ ሕዝባዊ ስብሰባ እንዳላቸው ለዘ-ሐበሻ የደረሰው መረጃ ጠቁሟል::

እንደደረሰን መረጃ ከሆነ የፊታችን ቅዳሜ ኦገስት 8, 2015 በኦሮሞ ኮምዩኒቲ ሴንተር ከ3 ሰዓት ጀምሮ ስብሰባው ይካሄዳል::

ስብሰባው የሚካሄድበት አድራሻ
465 Mackubin St, St Paul, MN 55103 ነው::

በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች ድርቅ መግባቱ ታወቀ

$
0
0

ካሁን በኋላ በኢትዮጵያ ውስጥ ሰላማዊ ትግል ያስኬዳል የሚል አመለካከት ለማስቀየር በቂ ምክንያት እና ምሳሌ አግኝቻለሁ

$
0
0

ከአካደር ኢበራህም ( አኩ አፋር )
ሓምሌ 28/2007 ዓ.ም

የዛሬ ሶስት አመት ገደማ በአወሊያ ትምህርት ቤት የሙስሊም ተማሪዎች ባነሱት ቀላል፣ ህጋዊና ህግ-መንግስታዊው ጥያቄን ተከትሎ የኢትዮጲያ ሙስሊሞች እስከ ዛሬ በሰላም እና በትዕግሰት የተጓዝነውን የትግል መንገድ ምንም እንኳን መንግስት ለሰላም ያለው አመለካከትና ለህዝብ ያለው ንቀት ገና ከጅምሩ ያሳየበት ቢሆንም የህዝበ ሙስሊሙ አርቆ አሳቢነት እና በበሳል አመራር የድምፃችን ይሰማ መሪነት እሰከዛሬ በሰላም ድምፃችን ይሰማ!!፣ መብቴን ይከበር!!፣ ህገ መንግስቱ ይከበር!! ብንልም ወያኔ «ህዝብን የሚሰማበት ጆሮ የለኝም» ብሎ ትናንት በራሱ ሚዲያዎች ሳይቀር ሲደራደራቸው የነበረው የህዝበ ሙስሊሙ መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴዎች ለሶስት አመታት በእስር ቤት ? ( በማሰቃያው ) በዚህ ባለንበት ክፍለ ዘመን የሰው ልጅ በሰው ልጅ ላይ ይፈፅማል ተብሎ የማይታሰበው በደሎች ሲፈፅምባቸው እና በመንግስት መገናኛ ብዙኃኖች ድራማ ሲሰራባቸው እና ከፍርድ ቤት በፊት በሚዲያ ሲፈርድባቸው ከቆየ በኋላ ዛሬ የድራማው የመጨረሻው ክፍል በተጻፈላቸው መሰረት በካንጋሮ ፍርድ ቤት ተነቧል።
Muslim in ethiopia
ዛሬ በካንጋሮ ፍርድ ቤት የተፈረደው በ18 ሰዎች ወይም 20 ሰዎች ላይ ብቻ አይደለም። በግማሹ የኢትዮጲያ ህዝብ ላይ የተፈረደ እና በማንኛውም ህልም ያለው ኢትዮጲያዊ ተቀባይነት የሌለው፣ ወያኔ ለውድቅት የተቃረበ ሽብር እና አመፅን የናፈቀ በቤተመንግስት የሚኖር የሽብር ቡዱን መሆኑን በራሱ አንደበት ለመላው የኢትዮጲያ ሙስሊሞች ያሳወቀበት ፖለቲካዊ ፍርድ ነው። በሌላ አነጋገር ዛሬ እነ አቡባከርን በ22 አመት ፅኑ እስራት ቀጥቻለሁ የሚለው የወያኔ ቡድን ለራሱ ይህን ያህል አመታት በህዝብ ላይ እንደፈለገ እየፈረደ ለመቆየት ዋስትናው ምንድነው? የሚል ጥያቄ ያስነሳል… በነገራችን ላይ ዛሬ ይህን ፖለቲካዊ ፍርድን ለማውገዝ ሙስሊም መሆን ግዴታ አይደለም!የሰው ልጅ መሆን ብቻ በቂ ነው። በኢትዮጲያ ሙስሊምም ክርስቲያኑም ጭቆና ውስጥ ይገኛል። የሚገርሞው ግን ሰዎች የፈለጉትን ኃይማኖት የመከተል፣ የመደራጀት፣ ሃሳባቸውን በነፃነት የመግልፅ ወዘተ… መብቶች እያላቸው መንግስት እራሱ ህገ-መንግስትን በመጣስ፣ በሃይማኖት ጣልቃ በመግባት ስልጣኑን በመጠቀም ለሚያስራቸው ሁሉ አሸባሪዎች በማለት ሲፈሪጃቸው እና ሲፈርድባቸው ይታያል።

ለመሆኑ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጲያ በመላው ህዝብ የሚደገፈው ሽብር ምን ዓይነት ሽብር ቢሆን ነው? የአገሪቷን የበላይ ህገ-መንግስትን በመጣስ የህዝብን መብት በአደባባይ ከመርገጥ በላይስ ምን ሽብር አለ? የተከበራችሁ የአገሬ ጉዳይ ያገባኛል ብላችሁ በኢትዮጲያ በሰላማዊ ትግል ለውጥ እናመጣለን ብላችሁ የምትታገሉ በሙሉ ሰላም ለሁሉም ቀዳሚ ምርጫ ቢሆንም አለመታደል ሆኖ እኛ ሰላም ብንፈልግም ወያኔ ሰላም እየነሳን አንድ ባንድ እስኪጨረሰን ድረስ መጠበቅ ያለብን አይመስለኝም። እኔ በበኩሌ ካሁን በኋላ ከህይወቴ በላይ ለአትዮጲያ የምሰጠው ነገር ባይኖረኝም ህይወቴን ለውድ ሃይማኖቴና ለውዲቷ ሀገሬ ኢትዮጵያ ለመስጠጥ ተዘጋጅቻለው።


የህወሓት ሁለቱ ኣንጃዎች ፍጥጫ! የኣዲስ ኣበባና የትግራይ ኣንጃዎች የየራሳቸው ቅስቀሳዎች እያካሄዱ ይገኛሉ –ከአምዶም ገብረሥላሴ

$
0
0

ህወሓት የሚመራው መንግስት በትግራይ ህዝብ፣ ሙሁራን፣ ተማሪዎች፣ የፖለቲካ ኣክቲቪስቶች፣ የህወሓት ኣባሎች ሳይቀሩ ከፍተኛ ተቃውሞ እየደረሰው ይገኛል።

ከኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት በሗላ ህወሓት የነበረት ግርማ ሞገስ ያጥች ስትሆን በጦርነቱ ምክንያት ለሁለት የተከፈለችው ህወሓት ጠበንጃዋ ኣንግባ ሁሉንም የተለየ ሃሳብ የያዘ ሰው የተለያዩ ቅጥያ እያሰጠች ድራሹን ስታጠፋው ነበር።
dawit
የትግራይ ህዝብ ከህወሓት ጋር የነበረው ቁርኝት ከፍተኛ ከመኖሩና ሙሉ ድጋፍ እንደሰጣት ዋና ማሳያው “ውድብና”( ድርጅታችን ) ሲላት ለታጋዮችም “ደቅና”(ልጆቻችን) በሚል የማቆላመጥ ስም ይጠራት ነበር።

የህወሓት ጥፋቶች በስራ የሚከሰቱ ስህተቶች በመቁጠር ይቅር እያለ እያለፈ ከነ ችግሮቿ ተሸክሞ ዓመታት ቢጠብቅም በረኻ እያለች የገባችለት ቃል ክዳ ለጥቂት ባለ ስልጣኖች ብቻ የቆመች መኻንና የህዝቡን ችግር፣ ፍላጎትና መስዋእትነት የማይታያት ዓይነ ስውር መሆንዋ ማረጋገጥ ከጀመረ በሗላ የትግራይ ህዝብ “ውድብና” ሲላት የነበርችው በስሟ “ሕወሓት” ብሎ መጥራት “ደቅና” (ልጆቻችን ) የሚለውን “ንሳቶም”(እነሱ)ብሎ መጥራት ከጀመረ ዓመታት ኣልፈዋል።

ህወሓት የህዝብ ጥያቄ፣ ችግር፣ እሮሮ፣ ስቃይ፣ እርዛት፣ ዲሞክራሲያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ጥያቄዎች መስማት የማትችል ዱዳ ሁና ኣልፈዋለች።
የትግራይ ህዝብ የህወሓት ስም መጥራት ተጠይፎ “እነሱ” እያለ ቢጠራቸውም ኣመራሮቹም ሰሚ ጆሮ ኣልነበረባቸውም።

የትግራይ ህዝብ ህወሓት “ጠላቶችህ ሊውጡህ ኣሰፍስፈው እየመጡ ነው፣ እኔ ከሌለው ኣንተ መጥፋትህ ነው” የሚል ፕሮፖጋንዳ ብቸኛው የድጋፍ ምንጭ ኣድርጋ ስትጠቀምበት የነበረችው ከንቱ መቅረት የጀመረውና ህዝቡ የራስ መተማመኑ መመለስ የጀመረው ዓረና ትግራይ ከተመሰረተና በመላ ትግራይ ተንቀሳቅሶ ህወሓትን የሚያስንቅ ፖለቲካዊ ኣቋምና ከሌሎች ኢትዮዽያውያን ለትግራይ ህዝብ ሊያጠፋ የሚያስብም የሚችልም እንደሌለ በማረጋገጡ፣ ለዘመናት ድህነት፣ ሙስና፣ የመልካም ኣስተዳደር እጦት፣ በኣገሩ እኩል የመጠቀም መበትና ሌሎች ዲሞክራሲያዊና ሰብኣዊ መብቶች ሊከበሩለት የሚያስችል የተሻለ ኣማራጭ ይዞ ሲመጣ ከፍተኛ ድጋፉን ሰጥተዋል።

ህወሓት በኣጭር ግዜ ዓረና ያገኘው ህዝባዊ ቅቡልነት መርምሮ ለማስተካከልና ያጣውን ከፍተኛ የህዝብ ድጋፍ ከማስመለስ ይልቅ ዓረና ድርጅት ለማፍረስ ሰርጎ ገቦች ማሰማራትና በዓረና ኣባላት ላይ እስከ ግድያ የደረሰ ጥቃቶች ስትፈፅም ግዜዋን ኣሳልፋዋለች።
እነዚህ ፀረ ዲሞክራሲያዊ ተግባሮች በዓረና ኣባላትና በትግራይ ህዝብ ዘንድ የታዩት ህወሓት በሌላ ዲሞክራሲያዊ ድርጅት መቀያር ያለባት መሆንዋ ራስዋ ያቀረበቻቸው ማስረጃዎች ሁነው ጠቅመዋል።

የዘንድሮ 2007 ምርጫ የህወሓት ህዝባዊ መሰረት ከስሩ የተነቀለበትና በስልጣን የመቆየትዋ ምክንያት የትግራይ ህዝብ ድጋፍ ሳይሆን ጠበንጃዋና ዓፈናዋ ብቻ መሆኑ ፍንትው ኣድርጎ ኣሳይቶን ኣልፈዋል።

የ”100 ፐርሰንት” ድምፅ ልፈፋ በመሬት የሌለ መሆኑ የኢትዮዽያና የትግራይ ህዝብ፣ የተቃዋሞ ድርጅቶችና ኣባሎቻቸው፣ የተቀዋሚ ደጋፊዎች፣ የገዢው ፓርቲ ኣመራሮች(ምርጫው ካለፈ ኣቶ ቴድሮስ ሓጎስ የትግራይ ካድሬ ሰብስበው ኣዋርዳቹናል በሚል ዘለፋና ስድብ ኣዝንቦባቸው ነበር) ፣ ኣባላትና ደጋፊዎች ሳያወላውሉ ያረጋገጡበት ዕድል ፈጥሮ ኣልፈዋል።

የምርጫው ምጤትም
—————-

፩) የዓረና ኣባላትና ደጋፊዎች የዘንድሮ ምርጫ የትግራይ ህዝብ ተሳትፎና ለዓረና የነበረው ድጋፍ በጣም ኣስገራሚ ነበር። ህዝቡ የህወሓት ያማጥላላት ፕሮፖጋንዳ ሳያደናግረው በልበሙሉነት ዓረናን መርጠዋል። የዓረና ኣባላትና ደጋፊዎች በኣሁኑ ሰዓት የኣሸናፊነት መንፈስ የድል ኣድራጊነት ወኔ ተላብሰው የገኛሉ።

፪) የገዢው ፓርቲ ከፍተኛ ኣመራሮች፣ ኣባላት፣ ሙሁራንና ወጣት ኣባሎች ከፍተኛ የሽንፈት ስሜት አያንፀባረቁ ይገኛሉ። እነዚህ የህወሓት ኣባሎች በሁት የሚከፈሉ ሲሆኑ የኣዲስ ኣበባና የትግራይ ኣንጃዎች ተብለው ተባዱነዋል።

፫) የ”ልማታዊ ባለሃብቶች” ተብለው በህወሓት የተመደቡትና ህወሓት ፈጠርኳቸው ብሎ ዘወትር የሚዘምርላቸው ባለሃብቶችም በህወሓት ህልውናና የመቧደን ስራ ተጠምደው ይገኛሉ። እነዚህም የኣዲስ ኣበባና የትግራይ የሚል ስም ይዘዋል።

፬) ወጣትና ፊደል ቀመስ የህወሓት ኣባላትም እንደዚሁ የትግራይና የኣዲስ ኣበባ የሚል ቡዱን ሰርተው በየፊናቸው እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ።

፭) የትግራይ ወጣቶችም የህወሓት ኣቅመቢስነትና እንደ ህዝባዊ ድርጅት የመቀጠል እድሏ ኣጠራጣሪና እርባና ቢስ መሆኑ በመረዳት የተልያዩ መሰባሰቦችና ኣዲስ ፖለቲካዊ ድርጅት የመመስረት እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ ሙከራዎች እያደረጉ ይገኛሉ።

እነዚህ እንቅስቃሴዎች ህወሓት ኣሁን ባለችበት ደረጃ ሁና መቀጠል እንደማትችል ድምዳሜ የደረሱ ናቸው።

“በኣሁኑ ሰዓት ህወሓት በጥሩ ኣቋም ላይ ትገኛለች” የሚል ኣቋም ይዘው የሚንቀሳቀሱ የትግራይ ክልል ቡድን ኣቶ ኣባይ ወልዱና ቴድሮስ ሓጎስ የሚመሩት ሲሆን የነዚህ ደጋፊ የሆነው የወጣቶች ቡድን “ስልጣኑ ለኛ ወጣቶች መሸጋገር ኣለበት” የሚል የኣዳሽ ኣቋም ይዞ የሚደግፋቸው ነው።

የነሓሴ ወር ጉባኤና የሁለቱ ኣንጃዎች ቅስቀሳ
————————————-

ህወሓት 12ኛው ጉባኤዋ በመቐለ ከተማ ነሓሴ 14/ 2007 ትጀምራለች።
በዚህ ጉባኤ ኣሸንፎ ለመውጣት የኣዲስ ኣበባና የትግራይ ኣንጃዎች የየራሳቸው ቅስቀሳዎች እያካሄዱ ይገኛሉ።

A) የትግራይ ቡዱን = ይህ ቡዱን “ትግራይ በጣም ኣድጋለች፣ ህዝባችን ከድህነት ተላቀዋል፣ 11 ፐርሰንት ኣድገናል፣ ሙስናና መልካም ኣስተዳደርም ጠላቶች(ዓረናና የኣዲስ ኣበባ ኣንጃ በኣንድነት የሚከስ ነው) እንደሚያወሩት ኣይደለም። መለስ የተወልን ራኢ ይዘን ለ50 ዓመት ኢትዮዽያን እንገዛለን” የሚል ሆኖ እንደ ዋነኛው ሃይል ኣድርጎ የሚንቀስቀሰውም

1) ከክልል እስከ ቀበሌ የተደራጀው ኣባልና ኣቶ ኣባይ ወልዱን ሊቀ መንበር ኣድርጎ ያስመረጠው ኣንድ ለ ኣምስት ኔትወርክ(1ለ5) ኣደረጃጀት ተጠቅሞ የኣዲሳበባው ኣንጃ በጉባኤው ካድሬውን ተጠቅሞ ኣሽቀንጥሮ ለመጣል ነው። የዚህ ማሳያም በመላ ትግራይ ያሉት ኣደረጃጀቶች የጉባኤው ተሳታፊ ካደሬ መልምሎ “.የመለስ ራኢ እንዳትክዱ ድርጅታችንን እንዳትወድቅ ኣደራ” እያለ እያስማለቸው ይገኛል።

2) በትግራይ ክልል ያሉት ባለሃብቶች በተለይም ከባለስልጣኖች ተባብረው ሃብት ያጠራቀሙ ደጋፊዎቻቸው ኣደራጅተው የኣዲስ ኣበባው ኣንጃ ለማሸነፍ እየተዘጋጁ ይገኛሉ።

፫) የመከላከያ ሰራዊት ኣባላት ሁነው ከፍተኛ ሃብት መሰብሰብ የቻሉትን ጭምር ድጋፍ ለማግኘት እየሰሩ ናቸው።

B ) የኣዲስ ኣበባው ኣንጃ= ይህ ቡድን “የመለስ ራኢ” የሚል ሽፋን ተከናንበን ትግራይ ውስጥ እየሰራን ያለነው ለድርጅታችን ህልውና ኣደጋ ላይ የሚጥል ነው” የሚል ኣቋም ያንፀባርቃል።
በትግራይ ክልል ድህነት ኣንሰራፍተዋል፣ ረሃብ፣ የመልካም ኣስተዳደር ችግር፣ የሙስና መስፋፋት፣ በኣጠቃላይ “የመለስ ራኢ” በሚል ሽፋን ተሽፍነን በዳታ ክምር ብቻ ድርጅታችን መቀጠል ኣትችልም።
ተቃዊሚዎች እያግኙት ያሉት የህዝብ ድጋፍም በያዙት ጠቃሚ ኣማራጭ ሳይሆን በኛ ድክመት ነው” የሚል ኣቋም ይዘው እየተታገሉ ነው።

ሀ) የነ ዶክተር ደብረፅዮንና ዶክተር ኣርከበ ዕቑባይ የሚመሩት ኣንጃ ሲሆን “ህወሓት ኣሁን ባለችበት መንገድ ከቀጠለች ለህልውናዋ ኣደጋ ነው።” የሚሉትና “ኣሁን ከቀበሌ እስከ ፖሊት ቢሮ ያለው ኣመራር ኣቅመ ቢስና በሙስና የተዘፈቀ መሰረታዊ የኣመራር ለውጥ ማምጣት ግድ የሚል ነው” ብሎ የሚያምን ነው።

ለ) የዚህ ኣንጃ ደጋፊዎች በትግራይ ክልል እንዳይሰሩ የተለያዩ እንቅፋቶች የደረሰባቸው ባለ ሃብቶች እና በተለያዩ ጫናዎች ተሰላችተው ከትግራይ የተሰደዱ ልማታዊ ባለሃብቶች ሲሆኑ እነዚህም የትግራዩ ኣንጃ ከተሸነፈ በትግራይ መስራት የሚፈልጉ ናቸው።(ኣቶ ኣባይ ወልዱ ወደ ኣስተዳዳሪነት በመጡበት ወቅት ከኣለማጣ እስከ ሑመራ እነ ገዛገርላሰና ኣርጋዊ ሃይሉ ጨምረው ከ110 በላይ ባለሃብቶች ማሰራቸው የሚታወስ ነው።)

ሰሞኑን ኣቶ ዳዊት ገብረእግዚኣብሄር በዓይጋ ፎረም በኩል የትግራይ ሁኔታና ያሉት ችግሮች ኣፍረጥርጠው የተናገሩትም የዚሁ ዘመቻ ኣካል ነው።

ሐ) የፌደራል ድህንነት መስራቤት= ለትግራዩ ኣንጃ ደግፈው ይንቀሳቀሳሉ የተባሉት የወረዳ ካቢኔ ኣመራሮች በሙስና ማስያዝና ማሳሰር ጀምረዋል። ለምሳሌ የምስራቃዊ ዞን የኣፅቢ ወንበርታ ወረዳ ሃላፊዎች ከፈዴራል የመጡ የደህንነት ሰዎች እየታሰሩ ይገኛሉ። በትግራይ ሙሰኛ ታሰረ ከተባለ በፈጠረው ፖለቲካዊ ልዩነት እንጂ ከክልል እስከ ቀበሌ ያለው የሙሰኛ መዓት ከማሰር ህወሓት ማሰር ይቀላል።

መ) በትግራይ ክልል ያሉ ልማታዊ ባለሃብቶች የዘረፉትን የህዝብ ሃብት ከነሙሉ ሰነዱ በማሳየት ለኣዲስ ኣበባው ኣንጃ ለመቃወም ከሞከሩ ዘብጥያ እንደሚገቡ እያሳይዋቸውና በድንጋጤ ሽባ የሆኑ ይገኛሉ።
ሰሞኑን ኣንድ ሚልዮን ብር ለልጁ ጥሎሽ የሰጠ የክልል ምክር ቤት ኣባል “ልማታዊ ባለሃብት” በመቐለ ከተማ በጣም ኣነጋጋሪ ሆኖ ከማለፉም በላይ የትግራይ ክልል ኣንጃ ደጋፊነት ተፈርጀዋል።

በመቐለ ከተማ በመጪው የህወሓት ጉባኤ ኣቶ ኣባይ ወልዱ ከሚስታቸው ወይዘሮ ትርፉ ኪዳነማርያም ከስልጣናቸው እንደሚነሱ የተረጋገጠ መሆኑ እየተወራ ይገኛል።

የህወሓት ወደ ሁለት ኣንጃዎች የተከፈለችው ባለፈው ጉባኤ ሲሆን በወቅቱ የትግራይ ክልል ኣንጃ የነ ኣቶ በረከት ስምኦን ብኣዴን ድጋፍ ተብጅቶለት ባሸናፊነት ማጠናቀቁ ይታወቃል።

በኣሁነ ሰዓት የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ በኣዲስ ኣበባ እየተካሄደ ይገኛል።

* ከታች ያለው ፎቶ የኣቶ ዳዊት ገብረእግዚኣብሄር ሲሆን ሰሞኑን በዓይጋ ፎሮም በትግርኛ ቃለ መጠይቅ ያካሄዱ ሲሆኑ በትግራይ ያለው ኣስከፊ የህወሓት ድክመት፣ ፀረ ልማት፣ ፀረ ዲሞክራሲና ፀረ ሰላም ተግባና ባህሪ ፍንትው ኣድርገው በማሳየት በዓረና ኣባላት፣ የፌስቡክ ኣክቲቪስቶችና ባጠቃላይ በትግራይ ህዝብ ሲነገለት የበሩት ተግባራት በርሳቸው የደረሱ በደሎች ጭምር በማቅረብ በተለይ ህወሓት በጭፍን ሲደግፉ ለነበሩት ወገኖች ኣስደንጋጭ ምግ ግር ኣድርገዋል።

የነዚህ ሁለት የህወሓት ኣንጃዎች ኣሸናፊ ሁኖ የሚወጣው ቡዱን በትግራይና በትግራይ ህዝብ እንዲሁም በኢትዮዽያ ህዝብ የሚያመጣው ወይም የሚፈጥረው ተኣምር የለም። የኣቶ ኣባይ ወልዱ ኣንጃ ካሸነፈ የኣሁንዋ ትግራይና ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ ይቀጥላል ማለት ነው።

የኣዲስ ኣበባ ኣንጃ ካሸነፈ ደሞ በኣቶ ፀጋይ በርሀ የነበረችው ትግራይ ተመልሳ ትመጣለች እንደማለት ነው። ማንኝዓውም ኣንጃ ካሸነፈ ወደ ስልጣን የሚመጡ ሰዎች ይቀያየሩ እንደሆነ እንጂ መሰረታዊ የሚባል ለውጥ ኣይኖርም።

ያው ወጮ ተገልበጥካዮ ወጮ ወይም ጉልቻ ቢለዋወጥ ወጥ ኣያጣፍጥም እንደሚባለው ነው። የትግራይ ወጣቶች የጀመራቹት ኣዲስ ዲሞክርሳሲያዊ ድርጀት የመመስረት ስራቹ ጥንክራቹ ግፉበት። ከዓረና ትግራይ ጎን ተሰልፈን ያለነውም ከሌሎች ኢትዮዽያውያን ጓዶቻችን ሁነን ዲሞክራሲያዊት ትግራይና ኢትዮዽያ በትላችን እውን እንደርጋለን።

ነፃነታችን በእጃችን ነው።

IT IS SO…!

የተፈረደበት ህገ ሃይማኖቱ እስልማና ነው! የታሠረውም እስልምና ሃይማኖት ነው –በትዕቢተኛው ወያኔ

$
0
0

ከሥርጉተ ሥላሴ 04.08.2015 /ሲዊዘርላንድ ዙሪክ/

እኔ ሥርጉተ ሥላሴ የድምጻችን ይሰማ አባል ነኝ። „ድማፃችን ይሰማ!“

Dimtsachin Yisemaጥያቄዎች ፍጹም ዬሰላማዊ መብት ጥያቄዎች ነበሩ። በምድር ሆኖ የማያውቅ የሰላማዊ ተጋድሎ ታሪክ ያሳዬው ብልሁና ሥልጡኑ „የድምጻችን ይሰማ“ የትግል ሂደት አብነት ነው።„መሪዎቻችን እኛ እንመርጥ መንግሥት በሃይማኖታችን ጣልቃ አይገባም።“ ነበረ። በዚህ አያያዝ ይህ ጥያቄ መቼውንም – አይፈታም።  በዘመነ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ማንፌስቶ – ታሥሯል። ጀግኖቻችን  ከ7 ዓመት እስከ 22 ዓመት ታሥረው እንኳን ቢፈቱ የከፈሉት መስዋዕትንት፤ የሞቱት፤ የተሰደዱት፤ የተደበደቡት ሁሉ ጥያቄያቸው ምላሽ የለውም። ይህ ነው እንግዲህ ፍርደ ገምድልነቱ – በዘረኝነት።

ሌላው ትልቁ ስላቅ ደግሞ እነሱን ተከትሎ ይህን ጥያቄ ዬሚያነሳ የሚጠብቅህ ይህ ነው በማለት ለመቀጣጫ የተወሰደ እርምጃ ነው።

ስለዚህ እጅናህ እግርህን አጣማረህ ዕምነትህን ሳይቀር ቀምቼህ ተንበርክከህ ተገዛ ነው። እዬዳህ ኑር። መሠረታዊው ጥያቄ እስከ 22 ዓመት ተፈርዶበታል፤ ከፍርዱ ከውሳኔው ተፈጻሚነት በኋላም ቢሆን ተቀብለህ ጸጥ እረጭ ብለህ መቀመጥ ነው ዕጣ ፈንታህ! ሌሎችም ጠብቁ ተራችሁን ነው። ትዕቢትም ነው።

ፍርዱ ለእስልማና ህገ – ሃይማኖት ብቻ ሳይሆን በአብሮነቱ ተምሳሌት የሆነው የ90 ሚሊዮንም የኢትዮጵያዊ ህዝብ ላይ የተፈረደ ነው። የወያኔ ሃርነት ትግራይ ዕድሜ መራዘም መሠረታዊ የቀጣይነት ባህሬ ከእኔ እስኪ ደርስ ድረስ ተመቻችቼ መጠበቄ ብቻ ነው። ዬወያኔ ሃርነት ትግሬ ማንፌስቶ ለማንም ለምንም የማይሆን ጠፍ ስለሆነ፤ ከሥሩ ለመንቀል መታገል ነው – አማራጩ። መስመሩ አንድ ብቻ ነው። ስለዚህ የትግሉ ስልት ወደ ዘላቂ እኩልነት ሊያመራ ወደሚችል የነፃነት መንፈስ ዝውውር ወይንም ሽግግር ማድረግ አለበት። ይህን መርኃችን እስካላደረግን ድረስ ወያኔ ሃርነት ትግራይ በራሱ የትግሉን ሂደት ጠንከር ብሎ እንዲሄድ ጉልበት እዬሰጠው ነው። ሞት ሁልጊዜ አዲስ ነው ይባላል። ይህ መሰል ፍርደ ገምደልነት ሌሎች አርበኞቻችን – ያለፉበት ታሪክ ነው። እኛ ሁልጊዜ አዲስ እንሆናለን እንጂ ከመለሲዝም ፋሺዘም ብጣቂ በጎ ነገር መጠበቅ እራስን መርሳት ወይንም እንደ ሰው መፈጠርን መሸሸት ነው።

አቅልሙት በቃኝን – ይሁን መሻገሪያ።

የፍጥረት መገኛ – አንቺ የጥቁር መሬት፤ አፈርሽን ወድጂ፤ ወትትሽን ጠጥቼ – ጡትሽን ጠብቼ

አንዲህ ተገፍቼ እንዲህ ተገፍትሬ —————–ሰብዕና አጥቼ

እትብቴ መንደሬ አንች ነሽ – ባዕቴ

መራር ሆነብኝ ———————– ባይታዋርነቴ።

ገለማኝ – ገለማኝ – ሠራኝ እንደ ገና

ዜጋዋ መሆኔ እንዲህ – ተዘነጋ።

መከራዬ መራኝ  —– ገነነ – ፍዳዬ

ተግባርን አዝርቼ ሰብሌንም – አምርቼ

ዕምነቴን ተቀማሁ ሰማሁኝ – ሰንብቼ።

የቋሳ ማምረቻ ጉትቻ ————- መሆኔ

ሱባኤ ላይ አለሁ ከሁሉ  ————–መንኜ።

አለቀዘቀዘኝም ደልቶኛል – ኑሬዬ

ትውልድ ይዳኘው ዘንድ ይሄው ነው —–ፍሬዬ።

ወርቅነው ፍዳዬ ያባራል————–ዓርማዬ!

እኔን–ስ ፈርቶኛል – አንተ ምን ትላለህ?!

እኔነ —ስ ፈርቶኛል – አንችስ ምን ትያለሽ?!

መናቅ ኮሶ ሆኖሏ ሥሩለት —- መሻሪያ

አቅልሙት በቃኝን ይሁን ———-መሻገሪያ!

ሥጦታ – ለድምጻችን ይሰማ ጀግኖች። 04.08.2015 ሲዊዘርላንድ

 

አባቱ የእኔ ጀግና ናትናኤልሻ  እሺ –  እኔ ታዘዛዥህ ነኝ። በጹሑፎቼ ሁሉ መልእክትህን እለጥፋለሁ። በራዲዮ ፕሮግራሜም በድምጽ መልእክትህን ሙሉውን – አስተላልፋለሁ። http://www.zehabesha.com/amharic/archives/45527

ቀደም ሲል በሠራሁት አጭር ፊልም አንተም ሆንክ አርበኞቻችን – አሉበት። እጅግ ቁልፍ ለሆኑ የሀገር መሪዎች ዓለምአቀፍ ዬሰብዕዊ መብት አስጠባቂ ድርጅቶች ከታህሳስ 10 2014 እስከ 2015 የካቲት 8 ድረስ ድረስ በተለያዬ ሁኔታዎች – ተልዕኳል። አይዛችሁ የእኛ አንበሶች።  https://www.youtube.com/watch?v=FmeGfeOaM_I&list=PLBwFEncxyNfuRqJSALv9zTCXJTUf0nOHd

ድማጻችን ይሰማ!

ኢትዮጵያዊነት ፈተናን አሸንፎ የተፈጠረ ሚስጢር!

እግዚአብሄር ይስጥልኝ።

 

 

ኦቦ ሌንጮ ለታ ተመላሽ ዲያስፖራ የመሆን መብቱ ለምን ተከለከለ?

$
0
0

lencho leta
ከአብሼ ገርባ

የዛሬ ስድስት ወር ገደማ ኦቦ ሌንጮ ያለኝ የፖለቲካ ሀሳብ ኢንቨስት ማድረግ እፈልጋለሁ ብሎ ጏዙን ጠቅልሎ ሀገር ቤት መግባቱ ይታወቃል:: ሆኖም በፍጥነት በመጣበት እግር ሀገሩን ለቆ እንዲወጣ ተደረገ::

የሌንጮ ለታን መባረርና አሁን ያለውን የዲያስፖራ ጥሪ ስንመለከት የተለየ የፖለቲካ ሀሳብ ኢንቨስት ማድረግ እንደማይፈቀድና ዶላርና ቦዶ ሀሳብ ብቻ ይዞ መምጣት እንደሚቻል ነው::

አንድ የኦሮሞ ዲያስፖራ በቴሌቪዥን መስኮት ቀርቦ በዚህ ሀገር ውስጥ አንድም የሰብዓዊ መብት ጥሰት የለም ብሎ በአንድ ቀን አዳር የሰብዓዊ መብት ጥሰት አለመኖሩን ገምግሞ ምስክርነት መስጠት የሚችል ጭንቅላት ያለው ዲያስፖራንም ለማየት ችለናል::

ኢህአዴግ ፖለቲካውን መቶ በመቶ ዝግ በማድረግ ዶላሩን ብቻ አምጡ እያላቸው ነው::

ዋናው ቁልፉ ግን ሀገሪቱን አንቆ የያዘው የዶላር ችግር ሳይሆን ፖለቲካው ስለተቆለፈበት ነው::

በኔ ግምት የዲያስፖራ ዶላር አይደለም የአሜሪካ ዶላር ጠቅላላ ተሰብስቦ ቢመጣ የሀገራችን የፖለቲካ ችግር እስካልተፈታ መፍትሄ ሊሆን አይችልም:

ፍቃዱ በቀለ ዛሬ ከእስር ተፈታ * አበበ ቁምላቸውም በዋስ እንዲወጣ ታዟል

$
0
0

elias 1

elias

ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ እንደዘገበው:- የቀድሞ አንድነት ለፍትህና ለዴሞክራሲ ፓርቲ፣ የአዲስ አበባ ወጣቶች ም/ሰብሳቢ የነበረው እና የዛሬ 20 ቀን በሽብር ወንጀል ተርጥሮ፣ ‹‹ሰዎችን ለግንቦት ሰባት በመመልመል ወደኤርትራ ትልክ ነበር›› የተባለው ፍቃዱ በቀለ ዛሬ ከቀኑ 9፡00 ሰዓት ገደማ በዋስ ከታሰረበት ካሳንችስ ስድስተኛ ፖሊስ ጣቢያ ተፈታ፡፡ በተጨማሪም በተመሳሳይ ክስ ተጠርጥሮ ከ25 ቀናት በላይ በዚሁ ፖሊስ ጣቢያ ታስሮ የነበረው የቀድሞ አንድነት እና በአሁን ወቅት የሰማያዊ ፓርቲ አባል የሆነው አበበ ቁምልቸውም በዋስ እንዲወጣ መታዘዙን ለማወቅ ተችሏል፡፡

በተመሳሳይ ዜናም፣ ‹‹የአልሸባብ ህዋስ ነህ፤ ባራክ ኦማባ በሚገኙበት ስብሰባ ወቅት የሽብር ወንጀል ልትፈጽም አሲረሃል›› ተብሎ ለ28 ቀናት፣ መገናኛ አሚቼ አካባቢ በሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ ታስሮ የነበረው የ‹‹ቀዳሚ ገጽ›› ጋዜጣ ሥራ አስኪያጅና የቀድሞ የ‹‹ሚሊየኖች ድምጽ›› ጋዜጣ ሪፖርተር ሀብታሙ ምናለ ከትናንት በስትያ ምሽት 2፡30 ገደማ ከእስር መውጣቱ ይታወሳል፡፡

ከሳሽ ሲከሰስ –ኢትዮጵያ ውስጥ ፍትሕ ቢኖር ነበር እኛ ኢትዮጵያን ሙስሊሞች እንዲህ ብለን እንከስ ነበር

$
0
0

muslim addis
ተዘጋጀ በመአኮ

የፀረ-ሽብርተኝነት አዋጅ ቁጥር 652/2001

የተመለከተውን በመተላለፍ የተከፈተ ክስ

የቀ/ቁ/      001/2006

የወ/መ/ቁ.    01/0001/06

ለኢትዮጵያ ህዝብ በሙሉ

በመላው ዓለም

ከሳሽ ….. ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች (የህዝበ ሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ)

ተከሳሾች… 1/ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ መንግስት

የሽብር ቡድኑ አጠቃላይ አስፈጻሚ

2/ የህውኃት/ኢህአዴግ ማዕከላዊ ኮሚቴ

የሽብር ቡድኑ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ

3/ የቀድሞው ጠ/ሚኒስትር መለስ ዜናዊ (በሌሉበት)

የሽብር ቡድኑ የቀድሞ አመራር

4/ ጠ/ሚኒስትር ኃ/ማርያም ደሳለኝ

የሽብር ቡድኑ አመራር

5/ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን

የሽብር ቡድኑ ወታደራዊ ክንፍ

6/ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት ቢሮ

የሽብር ቡድኑ መረጃ ክፍል

7/ የኢ.ፌዲ.ሪ የፌዴራል ጉዳዮች ሚነስቴር

የሽብር ቡድኑ የስልጠናና ምልመላ ክንፍ

8/የኢ.ፌዲሪ. የፍትህ ሚኒስቴር

የሽብር ቡድኑ የህግ ሽፋን ሰጭ ክፍል

9/ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር

የሽብር ቡድኑ ተባባሪ

10/ የኢ/እ/ጉ/ጉባኤ (መጅሊስ

የሽብር ቡድኑ ተቀዳሚ ተባባሪና ኃይማኖታዊ ሽፋን ሰጭ ተቋም

11/የፌዴራል ወንጀል ምርመራ (ማዕከላዊ)

የሽብር ቡድኑ ቶርቸርና ማወጣጫ (inquisition) ክፍል

12/ አቶ ጌታቸው አሰፋ

የሽብር ቡድኑ መረጃ ክፍል ሃላፊና አመራር

13/ ዶ/ር ሽፈራው ተ/ማርያም

የሽብር ቡድኑ የስልጠናና ምልመላ ክፍል ሃላፊና አመራር

14/ አቶ ጸጋዬ በርሄ

የሽብር ቡድኑ የፀጥታ ክፍል ሃላፊና አመራር

15/ አቶ ሬድዋን ሁሴን

የሽብር ቡድኑ ቃል-አቀባይ

16/ አቶ አህመዲን አብዱላሂ ጨሎ

የሽብር ቡድኑ ተቀዳሚ ተባባሪና የኃይማኖታዊ ሽፋን ሰጭ ተቋሙ አመራር

17/ ፕሮፌሰር ሃጋይ ኤርሊኽ (በሌሉበት)

የሽብር ቡድኑ ዋና አማካሪ

18/ ዶ/ር ሰሚር አል-ሪፋዒ (በሌሉበት)

የሽብር ቡድኑ አማካሪና የአይዲዮሎጂ ክፍል ተጠሪ

19/ ፔትራም ኃ/የተወ/የግል ማህበር

የሽብር ቡድኑ የፋይናንስ ድጋፍ ሰጭ ክንፍ

20/ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት (አዲስ ዘመን ጋዜጣ)

21/ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንና ሬዲዮ ድርጅት (ኢ.ቲ.ቪ)

የሽብር ቡድኑ የድምጽ-ከምስል ስርጭት ክፍል

1ኛ ክስ

(ከ1ኛ እስከ 21ኛ ተከሳሾችን ይመለከታል

ወንጀሉ

በ1996 የወጣውን የኢ/ፊ/ዲ/ሪ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 32/(1)(ሀ)(ለ)፣ 38(1) እነ የፀረ-ሽብርተኝነት አዋጅ ቁጥር 652/2001 አንቀጽ 3፣4፣5፣6፣7፣8፣10፣እና 11 የተመለከተውን በመተላለፍ ወንጀል ተከሰዋል፡፡

የወንጀሉ ዝርዝር

ተከሳሾች በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋ በመሆን እና የወንጀል አድማ ስምምነት በማድረግ በመላ ሃሳባቸው እና አድራጎታቸው የወንጀል ድርጊቱን እና ወንጀሉ የሚሰጠውን ውጤት ሙሉ በሙሉ በመቀበል እነ የራሳቸው በማድረግ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ-መንግስት አንቀጽ——— ከተረጋገጠው የእመነት ነጻነት በመቃረን ከራሳቸው “አህባሽ” የተሰኘ አክራሪ አስተሳሰብና አስተምህሮት ውጭ በኢትዮጵያ ውስጥ ሌላ የእስልምና አስተሳሰብና አስተምህሮት መኖር የለበትም የሚል ፖለቲካዊ ዓላማ በማንገብ እና የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጉባዔን (መጅሊስን ) ፖለቲካዊ ዓላማን ለማስፈፀም የተቋቋመ ኃይማኖታዊ ተቋም እንዲሆን እቅድና ግብ በማስቀመጥ መንግስት በሃይማኖት ጣልቃ አይገባም የሚለውን የህገ-መንግስቱን አንቀጽ 11ን በመቃረን ቀኑና ወሩ በውል ባልታወቀ 1987 ጀምሮ ህውኃት /ኢህአዴግ በተሰኘው የሽብር ቡድን በመሠባሰብ የረጅም፣ የመካከለኛ እና የአጭር ጊዜ እቅድ በማውጣት እና ስትራቴጂዎችን በመንደፍ ተንቀሳቅሰዋል፡፡

ተከሳሾች “አህባሽ” የተሰኘው አንጃ በእርስ በርስ ጦርነት በምትታመሰዋ ሊባኖስ ውስ የሚንቀሳቀስ ፖለቲካዊ ዓላማ ያለው የኃይማኖት ሴክት መሆኑን እያወቁ፣ እንዲሁም የቀድሞውን የሊባኖስ ጠቅላይ ሚኒስትር ረፊቀስ ሀሪሪን ግድያ የሚያጣራው የተባበሩት መንግስት የወንጀል አጣሪ ቡድን “አህባሽ” የተሰኘው አንጃ ግድያውን እንደፈፀመ ሪፖርት ያወጣ መሆኑን እያወቁ፤ የአህባሽ አንጃ መስራች የሆኑት ሽህ ዐብደላህ አልሃረሪ ሀረር የሶማሊ አካል ነች የሚል ፀረ-ኢትዮጵያ አቋም ያላቸው መሆኑን እያወቁና ይህንን አቋም የሚገልፀውን መጽሀፍ በመጅሊስ በኩል እያሰራጩ፤ ይህንን በሀገር ሰላም ላ አሉታዊ ተጽዕኖ ሊያሳድር የሚችልን አንጃ ህዝብ የሰጣቸውን ስልጣን በመጠቀም ወደ ኢትዮጵያ አስመጥተዋል፣ በዚህም ከህዝብና ከሀገር ደህንነት ይልቅ ጊዜያዊ ፖለቲካዊ ጥቅምን በመምረጥ ስልጣናቸውን ለሽብር ዕቅዳቸው ማስፈፃሚያነት ተጠቅመዋል፡፡

(ፎቶ ፋይል)

(ፎቶ ፋይል)

ይህን አክራሪ አስተሳሰብ የተጠናወተው “አህባሽ” የተሰኘውን አንጃ ከ1996 ጀምሮ በጦር-ኃይሎች ሦስት ቁጥር ማዞሪያ በሚገኘው ተቋሙ አክራሪ አስተሳሰቡን እንዲያስፋፋ በህቡዕ ድጋፍ ሲያደርጉ ቆይተዋል፡፡ ከዚህም አልፎ ዕለቱና ወሩ ባልታወቀ 2003 ላይ በቀድሞው ጠ/ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ፊርማ በቦሌ ክ/ከተማ የሚገኝ አንድ መቶ ሺህ (100000) ካሬ ሜትር ቦታ እንዲሰጣቸውና ለአንጃው ማሰልጠኛ ተቋ ግንባታ ይሆን ዘንድ የፔትራም ኩባንያ ስራ አስኪያጅ አቶ ዐብዱልከሪም በድሪ እንዲከታተለው ትዕዛዝ ሰጥተዋልል፡ በዚህም ተግባራቸው ህዝብ የሰጣቸው ስልጣን ለሽብር ዕቅዳቸው ማስፈፀሚያ ተጠቅመዋል፡፡

የሽብር ቡድኑ ከሐምሌ ወር 2003 ጀምሮ ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች ይህንኑ “አህባሽ” የተሰኘ አክራሪ አስተሳሰብ እንዲቀበሉ በማስገደድ፣ ማንኛውም ሙስሊም እነርሱ ከሊባኖስ ካስመጡት የአስተሳሰብ መስመር ውጭ መከተል የማይቻል መሆኑን በአደባባይ በመግለፅ እና የእምነት ነፃነታቸውን ለማስከበር የተንቀሳቀሱ የኃይማኖት መምህራን፣ ዑለማዎችና ምሁራንን ለሥነ-ልቦና እነ ለአካል ጉዳት በመዳረግ እስር ውስጥ በማዋል፣ የህገ-መንግስት ጥሰታቸውን በተቃወመው ህዝበ-ሙስሊም ላይ የህይወት፣ የአካልና የንብረት ጉዳት አድርሰዋል፡፡

ቀደም ሲል ባቀዱት መሰረትም መጅሊስ (የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጉባኤ) ውስጥ ከእነርሱ አክራሪ አስተሳሰብ ውጭ የሆነ ወይም የሽብር ቡድኑ የፖለቲካ ፓርቲ አባል ያልሆነ ግለሰብ በየትኛውም የመጅሊሱ አስተዳደራዊ እርከን እንዳይሳተፍ አግደዋል፡፡ ህዝብ የማያውቃቸውና የኃይማኖትም ይሁን የአካዳ ዕውቀት የሌላቸው ግለሰቦችን የመጅሊሱ አመራር አድርጎ በመሾም ተቋሙ ህዝበ-ሙስሊሙ ላይ ለሚፈፀመው የሽብር ድርጊት ኃይማኖታዊ ሽፋን እንዲሆን ለማድረግ ተንቀሳቅሰዋል፡፡ ይህንንም ለማሳካት የመንግስት መዋቅርን በመጠቀም በትጋት ሰርተዋል፡፡ በተለይም የብሔራዊ መረጃና ደህንነት ቢሮው ሙሉ ኃይሉን ለዚህ እኩይ ጉዳይ በማዋል በንፁሃን ዜጎች ላይ የእስር፣ የእገታ፣ የድብደባና የግድ ወንጀል ፈፅሟል፡፡ መጅሊሱን ለሽብር ዓላማቸው ማስፈፀሚያነት ለማመቻቸት ይችሉ ዘንድ ህዝበ-ሙስሊሙ ባልተሳተፈበትና የህዝበ-ሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ በፌ/ወ/ምርመራ (ማዕከላዊ) ኢ-ሰብዓዊ ግፍ እየተፈፀመባቸው (እፈፀሙባቸው) ባሉበት ሁኔት ህገ-ወጥ ምርጫ- የመንግስት ተቋም በሆነው ቀበሌ ውስጥ-አካሂደዋል፡፡ በሂደቱም ህገ-ወጥ የመጅሊስ አመራሮችን በሌላ ህገ-ወጥ አመራሮች ተክተዋል፡፡ በዚህም የሽብር ቡድኑ ተሳታፊዎች በኃይማኖት ጉዳይ ቀጥተኛ ጣልቃ ገብነታቸውን አሳይተዋል፡፡

የሽብር ቡድኑ የሀገሪቱን መንግስታዊ ተቋማት በመጠቀምና የሀገሪቱን የፀጥታ ኃይል ሙሉ በሙሉ ለህገ- ወጥ ዓላማቸው በማዋል በ “ህገ-መንግስት ማስተማር” ስም አዲሱን አክራሪ አስተሳሰብ በኃይል ጭነዋልል፡ የግዳጅ ስልጠና ሰጥተዋል፡፡ ስልጠናቸውን ለመሳተፍ ፈቃደኛ ያልሆኑና የፀጥታ ኃይላት ማስፈራሪያና ዛቻ ያልበገራቸው የመስጅድ ኢማሞች ከኢማምነታቸው (ከስግደት መሪነታቸው አባርረዋል፡፡ በኃይማኖት ጉዳይ በቀጥታ ጣልቃ በመግባት የመስጅድ ኢማሞችን ሾመዋል፤ እነርሱ የሾመዋቸውን ኢማሞች “ተከትለን አንሰግድም” ያሉ በርካታ ሙስሊሞችን ዘብጥያ ወርውረዋል፣ ለህገ-ወጥ ድርጊታቸው ማስፈፀሚያ ያቋቋሟቸውን ፍ/ቤቶች በመጠቀም በ “ዋስትና” ስም በርካታ ሚሊዬን ብር ከህዝበ-ሙስሊሙ መዝብረዋል፡፡ ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች በሀገራቸው ሙስሊም ሆነው የመኖር ነፃነታቸውን ነፍገዋል፡፡

የሽብር ቡድኑን ህገ-ወጥ ድርጊት በመቃወም ህገ-መንግስት ይከበር! የሚል ድምፃቸውን ለማሰማት አደባባይ የወጡ በመቶ ሺህዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞችን “ጥቂቶች” ሲሉ አሸማቀዋል፤ የነፃነት ጩኸታቸውን ለሚመለከተው የመንግስት አካል ያደረሱላቸውና ለመብት ጥያቄያቸው መፍትሄ ያፈላልጉላቸው ዘንድ በፊርማቸው አረጋግጠው ውክልናቸውን የቸሯቸውን የህዝብ ልጆች የሽብር ቡድኑ ራሱ በሚፈፅመውና ግዙፍ የወንጀል ድርጊት በሆነው በሽብር በመወንጀል አሰቃቂ ግፍ ፈፅመዋል፡፡ ይህንኑ የሽብር ዕቅዳቸው አካል የሆነውን ህገ-ወጥ ተግባር የህግ ሽፋን ለመስጠት የኢ/ፌ/ዲ/ሪ ፍትህ ሚኒስቴር የተሰኘ ክፍላቸውን በመጠቀም የህዝብ ወኪሎችን ከሃያ ወራት ያላነሰ በእስር ቤት አጉረዋል፡፡ በተጨማሪም በሺህዎች የሚቆጠሩ ሙስሊሞችን “በሁከትና በብጥበጥ” በመወንጀል ተመሳሳይ ወንጀል ፈፅመዋል፡፡ መረጃ ለህዝብ እንዳይደርስ ለማገድ በማሰብ በሙስሊሙ ህ/ሰብ ጉዳይ ላይ በማጠንጠን የሚዘግቡ ሃይማኖታዊና ማህበራዊ ጋዜጦችንና መጽሔቶችን አግደዋል፤ አዝዘግተዋል፡፡

የሽብር ቡድኑ አባስት ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞችን በተለያ ስያሚዎች በመከፋፈል፣ አክራሪ አስተሳሰባቸውን በኃይል በመጫን፣ ይህንን ህገ-ወጥ ተግባራቸውን በተቃውሙ ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሰዋል፤ በርካታ የኃይማኖት መምህራንና ምሁራን ሀገራቸውን ጥለው እንዲሰደዱ አድርገዋል፡፡ ህዝብ የሰጣቸውን ስልጣን ህዝብን ለማሸበር ተጠቅመዋል፡፡

የሽብር ቡድኑ በኮፈሌ፣ በአሳሳ፣ በሀረር፣ በሀርጉ፣ በደጋን፣ በአዲስ አበባ አወሊያ መስጂድ፣ በአንዋር መስጅድና በአዲስ አበባ ስቴድዮም በህዝበ-ሙስሊሙ ላይ የህይወት፣ የአካልና የንብረት ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል፡ጰ፡

ተከሳሾች የሽብር ቡድኑን ዓላማ ለማስፈፀም በማሰብ አክራሪ አስተሳሰባቸውን የማቃባሉ ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞችን በኢኮኖሚ ለማዳከም የተለያዩ እቅዶችን ነድፈው ተንቀሳቅሰዋል፡፡ ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች በሀገር የኢኮኖሚ ዕድገት ብልጽግና የሚጨበጥ ተሳትፎ ማድረግ የሚያስችላቸውን ከወለድ ነፃ ባንክ ማቋቋም እንዳይችሉ ከልክለዋል፡፡ ከወለድ ነፃ ባንክ ማቋቋም የሚፈቅድ አዋጅ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፀደቀ ቢሆንም የሽብር ቡድኑ አመራሮች በሰጡት ቀጭን ትዕዛዝ ከ6800 (ስድስት ሺህ ስምንት መቶ) አባላት በላይ ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞችን ያቀፈውን ዘምዘም ባንክ በብሔራዊ ባንክ ፕሬዝዳንት ፊርማ አዋጁን በመጣስ በኃይል በትነዋል፡፡ በተጨማሪም ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ያላቸውን የትምህርት ተሳትፎ ለማቀጨጭ በማቀድ ሆን ብለው ከህገ-መንግስቱ ጋር የሚቃረንና የእምነት ነፃነትን የሚጋፋ አግላይ ደንብ በትምህርት ሚኒስቴር በኩል በማውጣት ከፍተኛ ጫና አሳድረዋል፡፡ ይህንኑ ህገ-ወጥ ደንብ የተቃወሙ ሙስሊም የዩኒቨርስቲ ተማሪዎችን አንድም ለእስራት አሊያም ከትምህርት ገበታ ለመገለል እንዲደረጉ አድርገዋል፡፡

የሽብር ቡድኑ ዓላማውን ለማስፈፀም ባቋቋማቸው የመገና ብዙሃን የሽብር ቅስቀሳ አድርጓል፡፡ አባላቱ መረጃን አዛብቶ በማቅረብ የጠወሰነን የህበረተሰብ ክፍል በተወሰነው ላይ የማነሳሳት ወንጀል ፈፅመዋል፡፡ ህዝበ-ሙስሊሙ ያነሳቸውን የእምነት ነፃነት ጥያቄዎች በመቀልበስ ሙስም ላልሆኑ ወገኖቹ ስጋት እንደሆነ አድርገው በመሳል ለርካሽ የፖለቲካ ትርፍ ተንቀሳቅሰዋል፡፡ በዚህም ድርጊታቸው ለዘመናት ተከባብሮ የኖረውን የኢትዮጵያ ህዝብ ወደ እርስ በርስ ጦርነት ለማስገባት በማስብ ያልተሳካ ሙከራ አድርገዋል፡፡ ቀስቃሽ የመገናኛ ብዙሃናቸውን በመጠቀም በእስር ላይ ያሉ ንፁሃን የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎችን እና የኃይማኖት መምህራንን በ “ሽብር” በመፈረጅ “ጅሃዳዊ ሀረካት” የተሰኘ ከእውነት የራቀና የተቀነባበረ ዘጋቢ ፊልም በማሰራቸት ህዝብን በህዝብ ላይ አነሳስተዋል፡፡ የሽብር ቡድኑ አባላት በደሴ ከተማ በሸህ ኑሩ ኢማም ላይ ግድያ በመፈፀም የመገናኛ ብዙሃናቸውን በመጠቀም የህዝበ-ሙስሊሙን የመብት ጥያቄ እንቅስቃሴ ለማጠልሸት ተንቀሳቅሰዋል፡፡ የተዛባ መረጃ በመስጠትና በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ ያደራጇቸውን ዜጎች በጥቅም በመደለል አሊያም በማስፈራራት በመላ ሀገሪቱ የሀሰት የድጋፍ ሰልፍ እንዲወጣ በማድረግ ህዝብን ለማታለል ሞክረዋል፡፡ በግድያው ማግስትም በርካታ ንፁሃን ሙስሊሞችን ለእስር በመዳረግ በሽብር ወንጅለዋል፡፡

በአጠቃላይ ተከሳሾች የሽብር ቡድኑን ዓላማ ለማስፈፀም በማቀድ በኃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ በመግባት እነርሱ ከመረጡት አክራሪ አስተሳሰብና አይዲዮሎጂ ውች ያለን ለማጥፋት በመንቀሳቀሳቸው፣ የተወሰነን የህብረተሰብ ክፍል በማስፈራራታቸው በህይወት፣ በአካልና በንብረት ላይ ጉዳት በማድረሳቸው፣ እገታ በመፈጸማቸው፣ የሽብር ድርጊት ለመፈፀም በማቀዳቸው፣ በመዘጋጀታቸው፣ በማሴራቸው፣ በማነሳሳታቸው እና በመፈፀማቸው በግዙፍ የወንጀል ድርጊት ተከሰዋል፡፡

የሽብር ቡድኑ አባላት የወንጀል ተሳትፎ እንደሚከተለው ተዘርዝሯል፡-

1ኛ. ተከሳሽ – የኢ.ፌ.ዲ.ሪ መንግስት

የሽብር ቡድኑን እቅድና ዓላማ ለማስፈፀም በመዋቅሩ ተዋረድ ያሉ መስሪያ ቤቶች እንዲንቀሳቀሱ መመሪያ ሰጥቷል፡፡ የሚፈፅማቸውን የሽብር ድርጊቶች ህጋዊና ትክክለኛ ለማስመሰል የሀገሪቱን የፍትህ ስርዓት እንደ ሽፋን ተጠቅሟል፡፡ ለዚህም ከ8ኛ ተከሳሽ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፍትህ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ንፁሃንን ለእስርና ለኢ-ሰብዓዊ ግፍ ከመዳረጉም በተጨማሪ በሺዎች ከሚቆጠሩ ሙስሊሞች በዋስትና ማስጠበቂያ ስም በሚሊዮኖች የሚቆጠር ብር መዝብሯል፡፡ ለሽብር ዓላማው መደለያ ይሆን ዘንድ በአነስተኛና ጥቃቅን ኢንተርፕራይዝ በማደራጀት ለ2005 የበጀት ዓት ብቻ 350,000,000.00 (ሦስት መቶ ሃምሳ ሚሊዮን ብር) በመመደብ ተንቀሳቅሷል፡፡ ለሽብር ዓላማው የሚገለገልባቸውን የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንና ሬዲዮ ድርጅት (ኢቲቪ) እና የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅትን (አዲስ ዘመን ጋዜጣን) በመጠቀም የሀሰት መረጃ ለህብረተሰቡ በማሰራጨት ህዝበ-ሙስሊሙን ሙስሊም ካልሆነው ወገኑ ጋር ለማጋጨት ተንቀሳቅሷል፡፡ በአጠቃላይ በኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች ላይ የተፈፀመውን የሽብር ድርጊት በፊታውራሪነት የመራና ያስፈፀመ በመሆኑ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ መንግስት በፈፀመው የሽብር ድርጊትን ማቀድ፣ ማሴርና መፈፀም ወንጀል በፀረ-ሽብርተኝነት አዋጅ ቁጥር 652/2001 አንቀጽ 3 እና 4 የተመለከተውን በመተላለፍ ተከሷል፡፡

2ኛ. ተከሳሽ የህውኃት/ ኢህአዴግ ማዕከላዊ ኮሚቴ

የሽብር ቡድኑ ስራ-አስፈፃሚ በመሆን ሰርቷል፡፡ የሽብር ድርጊቱን በማቀድ፣ በማሴር እና አመራር በመስጠት ተሳትፏል፡፡ ቀኑና ወሩ በውል ባልታወቀ 1996 ዓ.ል ጀምሮ በሽብር ድርጊቱ ዙሪያ በህቡዕ በመወያትና የአጭር፣ የመካከለኛ እና የረጅም  ጊዜ እቅድ በማውጣት የኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞችን መሪ ድርጅት የኢ/እ/ጉ/ጉባኤ (መጅሊስን) የፖለቲካዊ ግባቸው ማስፈፀሚያ ኃይማኖታዊ ተቋም እንዲሆን ተንቀሳቅሰዋል፡፡ በህገ-መንግስት አንቀጽ 11 እና አንቀጽ 27 የተደነገገውን የእምነት ነፃነት በመቃረን በእምነት ተቋና በኃይማኖት ጉዳይ በቀጥታ ጣልቃ ገብተዋል፡፡ ይህን ህገ-ወጥ ድርጊት በተቃወሙ ንፁሃን ላይ የኃይል እርምጃ በመውሰድ የሽብር ድርጊት እንዲፈፀም ትዕዛዝ ሰጥተዋል፡፡ ስለሆነም ለሽብር ድርጊት በማሴር፣ በማቀድና አመራር በመስጠት ወንጀል በፀረ-ሽብርተኝነት አዋጅ ቁጥር 652/2001 አንቀጽ 4 እና አንቀጽ 7(2) የተመለከተውን በመተላለፋቸው ተከሰዋል፡፡

3ኛ. ተከሳሽ የቀድሞው ጠ/ሚኒስትር መለስ ዜናዊ (በሌሉበት)

የሽብር ቡድኑ የቀድሞ አመራር በመሆን ሰርተዋል፡፡ የሽብር ድርጊቱን በማሴር፣ በማቀድና አመራር በመስጠት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርገዋል፡፡ ከ17ኛ ተከሳሽ ሃጋይ ኤርሊኽ የተሰጣቸውን ምክር ከልብ በመቀበል ያላቸውን የግል ክህሎት በማከል የሽብር ቡድኑን ዓላማ በመቅረፅ የቡድኑን ጥንስስ ጥለዋል፡፡ በሚያዚያ 9/2004 ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ባደረጉት ንግግር በኃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ በመግባት ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞችን ለመከፋፈል ሞክረዋል፡፡ የሽብር ዘመቻው ለመጀመር የነበራቸውን እቅድ የመብት ጥያቄ ያነሳውን ህዝበ-ሙስሊም “ጥቂቶች” በማለት ከማሸማቀቅ አልፈው “በእንጩጩ ማስቀረት” ሲሉ ዝተዋል፤ አስፈራርተዋል፡፡ ይህንኑ የፓርላማ ንግግራቸውን ተከትሎ 5ኛ ተከሳሽ የፌ/ፖሊስ ኮሚሽን በሚያዚያ 2004 በአሳሳ ከተማ በንፁሃን ሙስሊሞች ላይ የህይወትና የአካል ጉዳት አድርሷል፡፡ ምንም እንኳን የሽብር ድርጊቱን ከመፈፀማቸው በፊት እርሳቸው ራሳቸው በእንጩጩ የቀሩ ቢሆንም የሽብር ቡድኑ በእርሳቸው የተዘረጋለትን የአፈፃፀም እቅድ በመከተል ከፍተኛ የህይወት፣ የአካልና የንብረት ጉዳት አድርሷል፡፡ ግለሰቡ በአዋጅ የፀደቀውን የወለድ ነፃ ባንክ የመመስረት መብትን በመንጠቅ በኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞችና በክርስቲያን ወንድሞቻቸውም ተሳትፎ የተቋቋመውን “ዘምዘም ባንክ” እንዲበተን ቀጥተኛ ትዕዛዝ በመስጠት በትነዋል፡፡ በዚህም የሽብር ቡድኑ ዓላማ አንዱ የሆነውን የኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞችን የኢኮኖሚ ተሳትፎ ማኮሰስን ለማሳካት በማሰብ አዋጅን በመመሪያ ጥሰዋል፡፡ ግለሰቡ በ2004 ለአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት በተፃፈ ደብዳቤ ለአህባሽ ማሰልጠኛ ተቋም ግንባታ የሚውል በቦሌ ክ/ከተማ የሚገኝ 100ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ እንዲሰጥ በፊርማቸው አዘዋል፡፡ በዚህም የህዝብ ስልጣንን ለራሳቸው የሽብር ዓላማ ማሳኪያ ተጠቅመዋል፡፡ ስለሆነም ግለሰቡ የሽብር ድርጊትን በማቀድ፣ በማሴር፣ በማነሳሳትና በመፈፀም ወንጀል በፀረ-ሽብርተኝነት አዋጅ ቁጥር 652/2001 አንቀጽ 4 እና 7(2) የተመለከተውን በመተላለፍ ወንጀል በሌሉበት ተከሰዋል፡፡

4ኛ ተከሳሽ -ጠ/ሚኒስቴር ኃ/ማርያም ደሳለኝ

ተከሳሽ የቀድሞውን ጠ/ሚኒስትር መለስ ዜናዊን (3ኛ ተከሳሽን) የእግር ኮቴ ያለምንም መጨመርና መቀነስ በመከተል የሽብር ቡድኑን መርተዋል፡፡ የሽብር ድርጊቱን የተቃውሙ ሙስሊሞች ላይ እርምጃ እንዲወሰድ ትዕዛዝ ሰጥተዋል፡፡ በሀገሪቱ የቴሌቪዥን ጣቢያ- 21ኛ ተከሳሽ እና በአልጀዚራ የቴሌቪዥን ጣቢያ ህዝበ-ሙስሊሙን “ጥቂቶች” ሲሉ አሸማቀዋል፡፡ ለሚፈፀሙ የሽብር ድርጊቶች ሁሉ አመራር ሰጥተዋል ባባልም የሀገሪቱ የበላይ አመራር ከመሆናቸው አንፃር በይሁንታ በማለፍ በቀጥታ አመራር የመስጠት ያህል ተሳትፎ አድርገዋል፡፡ ስለሆነም ሀገሪቱ ውስጥ የተፈፀሙ የሽብር ድርጊቶችን በሙሉ በማቀድ፣ በመፈፀምና አመራር በመስጠት ወንጀል የፀረ-ሽብርተኝነት አዋጅ ቁጥር 652/2001 አንቀጽ 2 እና 7(2)ን በመተላለፍ ወንጀል ተከሰዋል፡፡

5ኛ. ተከሳሽ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን

የሽብር ቡድኑ ወታደራዊ ክንፍ በመሆን በዜጎች ላይ ከፍተኛ የአካል ጉዳት አድርሷል፡፡ በሚያዚያ 2004 በአሳሳ፣ በሀምሌ 2005 በኮፈሌ፣ ቀኑና ወሩ ባልታወቀ በ2005 በሀርቡ፣ በ2004 በሀረር፣ በሀምሌ 06/2004 በአወሊያ መስጅድ፣ በሐምሌ 14/2004 በአንዋር መስጅድ እና በሐምሌ 2005 በአዲስ አበባ ስቴዲዮም ዙሪያ በኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች ላይ የህይወት፣ የአካልና የንብረት አሰቃቂ ጉዳት አድርሷል፡፡ በሐምሌ 06/2004 በሌሊት አወሊያ መስጅድ ውስጥ ለምፅዋት የሚሆን ምግብ ሲያዘጋጁ የነበሩ ሙስሊሞች ላ እገታ በማድረግ፣ በተዘጋ መስጅድ ውስጥ ባሉ ሙስሊሞች ላይ አስለቃሽ ጥይት ወደ ውስጥ በመተኮስ በህዝብ ጤና ላይ ጉዳት አድርሷል፡፡ በሐምሌ 2005 የዒድ አልፊጥር ባዕልን ለማክበር በአዲስ አበባ ስቴዲዮም በመገኘት የ1ኛ ተከሳሽን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ መንግስትን በኃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ ገብነት በመቃወማቸው በሺህዎች በሚቆጠሩ ሙስሊሞች ላይ አሰቃቂ ድብደባ እና እስር ፈፅሟል፡፡ በዕለቱ ከአስር ሺህ በላይ ሙስሊሞችን ለእስርና እንግልት ዳርጓል፡፡ በመሆኑም ከ2ኛ ተከሳሽ ህውኃት/ኢህአዴግ በተሰጠው አመራር የሽብር ድርጊቱን በቀጥታ የፈፀመ በመሆኑ በፀረ-ሽብርተኝነት አዋጅ ቁጥር 652/2001 አንቀጽ 3(1)(2)(4) የተመለከተውን በመተላለፍ ተከሷል፡፡

6ኛ. ተከሳሽ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት ቢሮ

የሽብር ቡድኑ መረጃ ክፍል በመሆን ለቡድኑ አመራሮች ሀሰተኛ መረጃን በመስጠት የሽብር ድርጊቱን አቀጣጥሏል፡፡ የሽብር ቡድኑ አመራሮችን ከጀርባ ሆኖ በመምራት ሆን ብሎ በኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች ላይ ሽብር እንዲፈፀም አበረታቷል፡፡ የተለያዩ በህቡዕ የተፈፀሙ ግድያዎችን አሲሯል፣ አቀነባብሯል፣ ፈፅሟ፡፡ በ2005 በደሴው ሸህ ኑሩ ኢማም ላይ የተቀነባበረ ግድያ ፈፅሟል፡፡ ይህን በማድረግም የህዝበ-ሙስሊሙን የመብት ጥያቄ እንቅስቃሴ ለማኮላሸት ንፁሃንን አስሯል፤ በሀሰት የከሰሳቸውን ዜጎች ከኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች “ህገ-መንግስት ይከበር” እንቅስቃሴ ጋር ለማዛመድ ጥረት አድርጓል፡፡ ቢሮው ከ5ኛ ተከሳሽ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ጋር በመተባበር ዜጎችን የማገት፣ የማሰር፣ ቶርች የማድረግና የመግደል ወንጀል ቀጥተኛ ተሳታፊ ሆነዋል፡፡ በተጨማሪም ቢሮው በሐምሌ 08/2004 በተወሰኑ የህዝበ-ሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት ላይ የመኪና እገታና ጠለፋ ሙከራ አድርገዋል፡፡ በሀሰት በተወነጀሉት የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴና በተለያዩ ምድብ ችሎት በቀረቡ ንፁሃን ሙስሊሞች ላይ ከ11ኛ ተከሳሽ የፌዴራል ወንጀል ምርመራ ጋር በመሆን ለሽብር ድርጊታቸው የሚሆኑ የሀሰት ምስክሮችን በማባበል አሊያም በማስፈራራት አዘጋጅተዋል፡፡ ስለሆነም የሽብር ድርጊት ቀጥተኛ ተሳታፊ በመሆን እና ምስክር በማባባል ወይም በማስፈራራት ወይም ማስረጃ በማጥፋት ወንጀል በፀረ-ሽብርተኝነት አዋጅ ቁጥር 652/2001 አንቀጽ 3(1)(2)(3)(4) እና 10(1) የተመለከተውን በመተላለፍ ተከሷል፡፡

7ኛ. ተከሳሽ የኢ.ፌዲ.ሪ የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር

የሽብር ቡድኑ የስልጠናና የምልመላ ክፍል በመሆን ሰርቷል፡፡ የህዝብን ሃብትና ጊዜ ለእኩይ ዓላማው በመጠቀም የሽብር ቡድኑን ዓላማ ለማስፈፀም በሙሉ ልቡ ተንቀሳቅሷል፡፡ 10ኛ ተከሳሽን (መጅሊስን) እንደ ኃይማኖታዊ ሽፋን በመጠቀም አክራሪ ስልጠናዎችን አዘጋጅቷል፤ አካሂዷል፡፡ “ህገ-መንግስት ማስተማር” በሚል ስም በኃይማኖታዊ ጉዳዮች በቀጥታ ጣልቃ በመግባት ኢትዮጵያዊያን ለዘመናት የሚያምኑባቸውን ጉዳዮች በአዲሱ አክራሪ አስተሳሰብ መተካት እንዳለባቸው በ2003 ሐምሌ ወር በሃሮማያ ዩኒቨርስቲ ከ10ኛ ተከሳሽ የኢ/እ/ጉ/ጉባኤ (መጅሊስ) ጋር በመተባበር ባዘጋጀው የአህባሽ ስልጠና ላይ የ1ኛ ተከሳሽን (የመንግስትን) አቋም አንፀባርቋል የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የአክራሪ አስተሳሰቡን ማስፋፋትና በሙስሊሙ ኃይማኖታዊ ጉዳይ ላይ ጣልቃ እየገባ ቀጥተኛ ትዕዛዝና መመሪያ መስጠት የዕለት ከዕለት ተግባሩ በማድረግ ህገ-መንግስታዊ ጥሰት ፈፅሟል፡፡ የሽብር ቡድኑ ለመፈፀም ላቀደውና ለፈፀመው የሽብር ድርጊት የአስተሳሰብ መደላድል በመፍጠር ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርጓል፡፡ ስለሆነም የሽብርተኝነት ድርጊት እንዲፈፀም ስልጠና በመስጠት ወንጀል በፀረ-ሽብርተኝነት አዋጅ ቁጥር 652/2001 አንቀጽ 5(1)(2) የተመለከተውን በመተላለፍ ተከሷል፡፡

8ኛ. ተከሳሽ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፍትህ ሚኒስቴር

የሽብር ቡድኑ ለሚፈፅማቸው ህገ-ወጥ ድርጊቶች የህግ ሽፋን በመስጠት ተንቀሳቅሷል፡፡ በስሩ በሚገኘው የፌዴራል ዓቃቢ ህግ በኩል ከ11ኛ ተከሳስ የፌዴራል ወንጀል ምርመራ (ማዕከላዊ) ጋር በመተባበር የሽብር ቡድኑ የሚፈፅማቸውን የህገ-መንግስት ጥሰቶችና የሽብርተኝነት ተግባራት የሚቃወሙና ለህዝብ የሚያጋልጡ የነፃነት ታጋዮችን፣ ጋዜጠኞችንና የፖለቲካ ሰዎችን በሀሰት ውንጀላ በመክሰስ እና የሀሰት የምስክርና ሰነድ በማዘጋጀት ወንጀል ፈፅመዋል፡፡ በተለይም የህዝበ-ሙስሊሙን ህጋዊ ወኮሎች የሽብር ቡድኑ በፈፀመው በሽብር ወንጀል በመክሰስ ለሽብርተኝነት ከለላና ጥበቃ ሰጥቷል፡፡ በመሆኑም የህዝበ-ሙስሊሙን የመብት ጥያቄ የዓለም ማህበረሰብን ባስደመመ ሰላማዊና ህጋዊ መንገድ የመሩና ያስተባበሩ የህዝብ ልጆችን ያለምንም ሀፍረት ወይም ርህራሄ ለእስርና እንግልት ዳርገዋል፤ የንፁሃንን ቤተሰብ አባወራ አልባ አድርገዋል፡፡ ህፃናቶቻቸውን ያለ አባት እንክብካቤ እንዲያድኑ አድርገዋል፡፡ በአጠቃላይ ሚኒስቴር መ/ቤቱ የሽብር ቡድኑ የዜጎች ዋስትና የሆነውን የፍትህ ስርዓት ለጊዜያዊና ለርካሽ የፖለቲካ ጥቅም እንዲያውል ተባብሯል፡፡ በዚህም የሚ/መ/ቤቱ የህዝብን ደህንት አደጋ ላይ በመጣል የፍትህ ስርዓቱን ለጥቂት የሽብር ቡድኑ አባላት ፖለቲካዊ ጥቅም በማዋሉ እና ለሽብር ድርጊት ከለላና ሽፋን በመስጠቱ በሽብር ድርጊት ተባባሪነት የፀረ-ሽብርተኝነት አዋጅ ቁጥር 652/2001 አንቀጽ 5(2) እና 7(1) የተመለከተውን በመተላለፍ ተከሷል፡፡

9ኛ. ተከሳሽ የኢ.ፌዲ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር

የሽብር ቡድ በረጅም ጊዜ እቅዱ የኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞችን የከፍተኛ ትምህርት ተሳትፎ ለማኮሰስ በሚያደርገው ህገ-ወጥ እንቅስቃሴ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴርን ሲጠቀም የሚስቴር መስሪያ ቤቱ ለሽብር እቅዱ ስኬት በፈቃደኝነት ተባብሯል፡፡ ተከሳሹ የእምነት ነፃነትን የሚቃረን የተማሪዎች ደንብ በማርቀቅ ተማሪዎች የመማር ማስተማር ሂደቱን በማያደናቅፍ ሁኔታ የሚተገብሯቸውን ኃይማኖታዊ ስርዓቶች ለማገድ ተንቀሳቅሷል፡፡ በዚህም የእስልምናም ይሁን የክርስትና እምነት ተከታዮችን ከኃይማኖተኝነት በማራቅ ለሽብር ቡድኑ አጎብዳጅ ትውልድ የመፍጠር የረጅም ጊዜ የጎድንዮሽ ዓላማ መሆኑን እያወቀ ወይም ማወቅ ሲገባው ሆን ብሎ የሽብር ቡድኑ ተባባሪ ሆኗል፡፡ ስለሆነም ሽብርተኝነትን በመርዳት ወንጀል የፀረ-ሽብርተኝነት አዋጅ ቁጥር 652/2001 አንቀጽ 7(1) የተመለከተውን በመተላለፍ ተከሷል፡፡

10ኛ. ተከሳሽ የኢ/እ/ጉ/ጉባኤ (መጅሊስ)

የሽብር ቡድኑ ኃይማኖታዊ ሽፋን ሰጭ ተቋም በመሆን ከ1992 ጀምሮ ህገ-ወጥ እንቅስቃሴዎችን ሲያደርግና የሽብርተኝነት ድርጊትን ሲረዱና ሲተባበር ቆይቷል፡፡ በህገ-ወጥ መንገድ ስልጣን የተቆናጠጡ አባላቶቹ ህገ-ወጥ ምርቻ በማድረግ ህዝበ-ሙስሊሙ ባስሰጣቸው ውክልና ያለፈቃዱ ሲመሩት ቆይተዋል፡፡ ተቋሙ የ1ኛ ተከሳሽ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ መንግስት አንድ ቢሮ በመሆን የመንግስት ባለስልጣናት በተለይም 13ኛ ተከሳሽ ዶ/ር ሽፈራው ተ/ማርያም በቀጥታ የሚያዙት በኃይማኖት ሽፋን የፖለቲካ ዓላማ የሚራመድበት ተቋም እንዲሆን ፈቅዷል፡፡ የህዝብን አደራ ወደ ጎን በመተው የመጅሊሱ አመራሮች በከፍተኛ ምዝበራ በመዘፈቅ ከሐጅና ዑምራ ጉዞ የሚገኘውን በሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ ለግል ጥቅማቸውና አክራሪ አስተሳሰባቸውን ለማስፋፋት ተጠቅመዋል፡፡ በተጨማሪም በምዝበራ የተገኘውን ገንዘብም ለ6ኛ ተከሳሽ ለብሔራዊ መረጃና ደህንነት ቢሮ ከፍተኛ ባለስልጣናት በማካፈል የህዝብን ንብረት ህገ-ወጥ ዓላማን ለማስፈፀም አውለዋል፡፡ ያስመጣውን አህባሽ የተሰኘ አስተሳሰብ በኃይል በመጫን የእምነት ነፃነትን ተቃርነዋል፡፡ ተቋሙ ከ7ኛ ተከሳሽ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ጋር በመሆን የግዳጅ ስልጠናዎችን አዘጋጅቷል፡፡ በ8ኛ ተከሳሽ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፍትህ ሚኒስቴር ስር ከሚገኙ የፍትህ ቢሮዎች ጋር በመተባበር በግዳጅ ስልጠናዎች ለመሳተፍ ፈቃደኛ ያልሆኑና ከአክራሪ አስተሳሰባቸው ውጭ የሆኑ የመስጅድ ኢማሞችን አባርረዋል፤ በምትካቸውም ምዕመናኑ የማፈልጓቸውን ኢማሞች ሾመዋል፤ በህዝብ በተመረጡ የመስጅድ ኮሚቴዎች የሚተዳደሩ መስጅዶችን ከ6ኛ ተከሳሽ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት ቢሮ ጋር በመተባበር ከህዝብ በኃይል ነጥቀዋል፡፡ “መንግስት የሾማቸውን ኢማሞች ተከትለን አንሰግድም” በማለት ስግደታቸውን ለብቻቸው የከወኑ ምዕመናን ለእስርና እንግልት እንዲዳረጉ ምክንያት ሆነዋልል፡ በአጠቃላይ ተቋሙ የሽብር ቡድኑ (ህውኃት/ኢህአዴግ) በህዝበ-ሙስሊሙ ላይ የፈፀማቸውን የሽብር እንቅስቃሲዎች ኃይማኖታዊ ቡራኬ የሰቱ በመሆኑ በፀረ-ሽብርተኝነት አዋጅ ቁጥር 652/2001 አንቀጽ 7(1) የተመለከተውን በመተላለፍ ተከሷል፡፡

11ኛ. ተከሳሽ የፌ/ወንጀል ምርመራ (ማዕከላዊ)

የሽብር ቡድኑ ቶርቸር እና ማውጣጫ (Inquisition) ክፍል ሆኖ አገልግሏል፡፡ ዜጎች ያልፈፀሙትን ወንጀል እንዲናዘዙ የአዕምሮ፣ የስነ-ልቦና የአካል ቶርቸር በማካሄድ የሀሰት ሰነድና ማስረጃ በማቀነባበር ከ8ኛ ተከሳሽ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፍትህ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር የሀሰት ክስ በመመስረት ንፁሃንን ወንጅሏል፡፡ ያልተፈፀመ ወንጀልን በማውጣጣት ሂደትም እጅግ ኢ-ሰብአዊ የምርመራ መንገዶችን በመጠቀም በከሳሾች ላይ ከፍተኛ የአካልና የስነ-ልቦና ጉዳት አድርሰዋል፡፡ የክፍሉ አባላት የሽብር ቡድኑ የሚፈፅማቸውን የሽብር ድርጊቶች ለመደበቅና ከለላ ለመስጠት ሆን ብለው ንፁሃን ላይ አሰቃቂ ድብደባና የማሰቃያ መንገዶችን በመጠቀም ሽብር የተፈፀመው በእነኝህ ንፁሃን መሆኑን ለማስመሠል ከሞራል ህግጋትም ሆነ ከህገ-መንግስት የሰብዓዊ መብት ድንጋጌ የተቃረኑ ዘግናኝ ወንጀሎችን ፈፅመዋል፡፡ ተቋሙ በሀሰት በሚወንጅላቸው ንፁሃን ላይም የሀሰት ምስክሮችን በማዘጋጀት፣ በማባባል፣ አሊያም በማስፈራራት የሽብር ድርጊቱ ተሳታፊ እንዲሆኑ በማድረጉ በፀረ-ሽብርተኝነት አዋጅ ቁጥር 652/2001 አንቀጽ 5(1)(ሀ)፣5(2) እና 10(1)(2) የተመለከተውን በመተላለፍ ወንጀል ተከሷል፡፡

12ኛ. ተከሳሽ አቶ ጌታቸው አሰፋ

የሽብር ቡድኑ የመረጃ ክንፍ የሆነውን 6ኛ ተከሳሽ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት ቢሮን በበላይነት መርተዋል፡፡ ፍፁም በሆነ አምባገነናዊ አመራራቸው ንፁሃን ዜጎች እንዲታሰሩ፣ እንዲሰቃዩ እንዲታገቱና እንዲገደሉ ቀጥተኛ ትዕዛዝ ሰጥተዋል፡፡ የኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች የመብት ጥያቄ ህጋዊና ሰላማዊ እነቅስቃሴ ለማኮላሸት አቅደዋል፣ አሲረዋል፣ ተንቀሳቅሰዋል፡፡ የሽብር ቡድኑ ለሚፈፅማቸው የሽብር ድርጊቶች የሚውሉ ግለሰቦችን መልምለዋል ወይም እንዲመለመሉ አድርገዋል፡፡ ስልጣናችውን በመጠቀም በእጅ አዙር እና በቀጥታ የሽብርተኝነት ድርጊት እንዲፈፀም አመራር በመስጠት በወንጀሉ ተሳትፈዋል፡፡ ለሽብር ቡድኑ የተሳሳተ መረጃ በመስጠት የሽብር ድርጊቱን አፋፍመዋል፡፡ ስለሆነም በሽብር ድርጊቱ ቀጥተኛ ተሳታፊና አመራር ሰጭነት በፀረ-ሽብርተኝነት አዋጅ ቁጥር 652/2001 አንቀጽ 3(1)(3) እና 7(2) የተመለከተውን በመተላለፍ ተከሰዋል፡፡

13ኛ. ተከሳሽ ዶ/ር ሽፈራው ተ/ማርያም

የሽብር ቡድኑን የስልጠናና የምልመላ ክፍል የሆነውን 7ኛ ተከሳሽ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴርን በበላይነት መርተዋል፡፡ የሽብር ቡድኑ ከሊባኖስ ያስመጣውን አህባሽ የተሰኘ አክራሪ አስተሳሰብን በግዳጅ ለማሰልጠን 10ኛ ተከሳሽን (መጅሊስን) እንደሽፋን በመጠቀም ተንቀሳቅሰዋል፡፡ አክራሪ አስተሳሰቡን የማስፋፋት ጥረታቸውን ዋነኛ የቢሮ ስራቸው በማድረግ የህዝብን ስልጣን ያለ አግባብ ተጠቅመዋል፡፡ በግዳጅ ስልጠናውም በተለያዩ ዙር እና በተለያዩ የሀገሪቱ ከተሞች 80000 (ሰማንያ ሺህ) ሙስሊሞችን ለማሰልጠን ሞክረዋል፡፡ በተለያዩ የስልጠና መድረኮች በተለይም በሐምሌ ወር 2003 በሐሮሚያ ዩኒቨርስቲ በተካሄደው የግዳጅ ስልጠና በመገኘት ህገ-መንግስቱን በተቃረነ መልኩ በኃይማኖታዊ ጉዳይ በቀጥታ ጣልቃ ገብተዋል፡፡ ህዝብ የሰጣቸውን ስልጣን በመጠቀም የእርሳቸውን አስተሳሰብ ያልተቀበሉ ወገኖችን አስፈራርተዋል፣ ዝተዋል፣ ሙስሊሙን ህ/ሰብ የተለያዩ ስያሜ በመስጠት ለመከፋፈል ጥረዋል፤ 20ኛ ተከሳሽን (አዲስ ዘመን ጋዜጣን) እና 20ኛ ተከሳሽን (ኢ.ሬ.ቴ.ድ፣ ቲቲቪን) በመጠቀም ንፁሃን የመብት ጠያቂ ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞችን በሽብር ፈርጀዋል፡፡ በአጠቃላይ የሽብር ቡድኑ ስራ-አስፈፃሚ አባል እንደመሆናቸው የሽብር ድርጊት እንዲፈፀም አመራር ሰጥተዋል፡፡ ስለሆነም በፈፀሙት ግዙፍ የወንጀል ድርጊት በፀረ-ሽብርተኝነት አዋጅ ቁጥር 652/2001 አንቀጽ 5(1)(ረ) እና 7(2) የተመለከተውን በመተላለፋቸው ተከሰዋል፡፡

14ኛ. ተከሳሽ አቶ ፀጋዬ ኃ/ማርያም

የሽብር ቡድኑ የፀጥታ ክንፍ በመሆን አገልግለዋል፡፡ የቡድኑን ፀጥታ ለማስከበር በማቀድ የህዝብን ፀጥታ አደፍረሰዋል፡፡ በተለያ የአክራሪነት ስልጠናዎች በአካል በመገኘት ንግግር በማድረግ ለሽብር ቀስቅሰዋል፣ የአክራሪ አህባሽ አስተሳሰብን አበረታተዋል፣ የህዝብን ስልጣን በመጠቀም ዜጎችን አስፈራርተዋል፡፡ ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች የግዳጅ ስልጠናዎችን እንዲወስዱ አስገድደዋል፡፡ ሙስሊሙን ህ/ሰብ ለመከፋፈል በማሰብና አክራሪ አስተሳሰባቸውን ለማስፋፋት ከ7ኛ ተከሳሽ የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ጋር በመሆን በርካታ የግዳጅ ስልጠናዎችን አዘጋጅተዋል፡፡ በተለይም በኢትዮ ቻይና ካምፓስ በመስከረም 2004 የተለያ ስያሜ በመስጠት ሙስሊሙን ለመከፋፈል ሞክረዋል፡፡ በተለይም ከ5ኛ ተከሳሽ የፌ/ፖሊስ ኮሚሽን ጋር በመተባበር በኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች ላ የሽብር ድርጊት እንዲፈፀም አቅደዋል፤ ለአፈፃፀሙም ተንቀሳቅሰዋል፡፡ በዚህም በፀረ-ሽብርተኝነት አዋጅ ቁጥር 652/2001 አንቀጽ 3(1)(2)(4) እና 5(1)(ረ) የተመለከተውን በመተላለፍ ተከሰዋል፡፡

15ኛ. ተከሳሽ አቶ ሪድዋን ሁሴን

የሽብር ቡድኑ ቃል አቀባይ በመሆን ለህዝብ የተዛባ መረጃ አስተላልፈዋል፡፡ በተለይም በሰንደቅ ጋዜጣ 2004 እትም ላይ በሰጡት ቃለ-ምልልስ ህዝበ-ሙስሊሙን በሽብርተኝነት ፈርጀዋል፡፡ ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞችን አደጋ አድርጎ በመሳል ህዝብን በህዝብ ላይ አነሳስተዋል፡፡ ቀደም ሲል የህውኃት /ኢህአዴግ የሽብር ቡድን ፀሀፊ በመሆን ለቡድኑ የሙያ፣ የልምድ እና የሞራል ድጋፍ ሰጥተዋል፡፡ ስለሆነም በፀረ-ሽብርተኝነት አዋጅ ቁጥር 652/2001 አንቀጽ 5(1)(ለ) እና 7(1) የተመለከተውን በመተላለፍ ተከሰዋል፡፡

16ኛ. ተከሳሽ አቶ አህመዲን አብዱላሂ ጨሎ

የሽብር ቡድኑ ኃይማኖታዊ ሽፋን በመሆን በኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች ላይ ከፍተኛ ዓለማዊና መንፈሳዊ ክህደት ፈፅመዋል፡፡ ከግብረ አበሮቻቸው ህገ-ወጥ የመጅሊስ አመራሮች ጋር በመሆን የህዝበ-ሙስሊሙ መሪ ድርጅት የሆነውን የኢ/እ/ጉ/ጉባኤ (መጅሊስ ለ2ኛ ተከሳሽ ህውኃት/ኢህአዴግ ፖለቲካዊ ግብ ማስፈፀሚያ ኃይማኖታዊ ሽፋን ይሆን ዘንድ ተንቀሳቅሰዋል፡፤ የህዝበ-ሙስሊሙ ብቸኛ ሚሲዮናዊ ተቋ የሆነውን የአወሊያን ተቋም “ለማፈራረስ” ተንቀሳቅሰዋል፡፡ የሽብር ቡድኑ ለሚያደርጋቸው ህገ-ወጥ እንቅስቃሴዎች መሣሪያ በመሆን ህዝበ-ሙስሊሙን ለሽብር ጥቃት ዳርገዋል፡፡ ስሆነም ለሽብር ቡድ በሰጡት ከለላና ለሽብር ድርጊቱ ተቀዳሚ ረዳት በመሆናቸው በፀረ-ሽብርተኝነት አዋጅ ቁጥር 652/2001 አንቀጽ 5(2) እና 7(1) የተመለከተውን በመተላለፍ ተከሰዋል፡፡

17ኛ. ተከሳሽ ፕሮፌሰር ሃገሮ ኤርሊኽ (በሌሉበት)

የእስራኤል ቴልአቢብ ዩኒቨርስቲ ፕሮፌሰር የሆኑት ይሁዳዊው ሃጋይ ኤርሊኽ የሽብር ቡድን አስተሳሰብ በመቅረፅና የአፍሪካ ቀንድ ከባቢያዊ ፖለቲካ ለሀገራቸው እስራኤል ጥቅም አንፃር እንዲቃኝ በማድረግ ከአይሁዶች ጋር ጥብቅ የስራና የዓላማ ትስስር እንዳለው የሚነገርለትን የ “አህባሽ” አስተሳሰብ ማስፋፋት አስፈላጊ መሆኑን ለሽብር ቡድኑ እኩይ ምክር ሰጥተዋ፡፡ በተለይም ከ3ኛ ተከሳሽ የቀድው ጠ/ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ጋር በነበራቸው የግል ቀረቤታ የሽብር ቡድኑ እኩይ ዓላማቸውን እንዲያራምዱ አድርገዋል፡፡ በመስከረም ወር 2004 በ20ኛ ተከሳሽ (ኢቲቪ)  “Meet ETV” የእንግዝ ፕሮግራም ላይ በመቅረብ የአህባሽ አስተሳሰብ ለኢትዮጵያ አስፈላጊ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ስለሆነም ለሽብር ቡድኑ ለፈጠሩት የአስተሳሰብ መደላደልና ባደረጉት የልምድ፣ የሞራል ድጋፍና ምክር በፀረ-ሽብርተኝነት አዋጅ ቁጥር 652/2001 5(1)(ለ) የተመለከተውን በመተላለፍ ተከሰዋል፡፡

18ኛ ተከሳሽ ዶ/ር ሰሚር አልሪፋዒ

በሽብር ቡድኑ አመራሮች ጋባዥነትና በ21ኛ ተከሳሽ ፔትራም ኃ/የተወ./የግል ኩባንያ ተባባሪነትና አስተባባሪነት ከሊባኖስ ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት የተደራጀ የአክራሪዎች ቡድን በማዘጋጀት ተንቀሳቅሰዋል፡፡ ያደራጃቸው ሊባኖሳዊያን የአህባሽ ግዳጅ ስልጣና ላይ በአሰልጣኝነት እንዲሰሩ አድርገዋል፡፡ ቀኑና ወሩ ባልታወቀ በ2004 በጊዮን ሆቴል ከ13ኛ ተከሳሽ ዶ/ር ሽፈራው ተ/ማርያም ጋር በመሆን ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እርሳቸው ከሚያራምዱት አክራሪ አስተሳሰብ ውጭ ያውን ኢስላማዊ አስተሳሰብ በሽብር ፈርጀዋል፡፡ የኢትዮጵያ መንግስትም ሊታገለው እንደሚገባ በመግለፅ ለህገ-ወጥ እርምጃ አነሳስተዋል፤ ቀስቅሰዋል፡፡ ስለሆነም ለሽብር ቡድኑ የሙያ፣ የልምድና የሞራል ምክርና ድጋፍ በመስጠታቸውና ለሽብር ድርጊት በመስጠታቸው በፀረ-ሽብርተኝነት አዋጅ ቁጥር 652/2001 አንቀጽ 4 እና 5(1)(ለ) የተመለከተውን በመተላለፍ ተከሰዋል፡፡

19ኛ. ተከሳሽ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት (አዲስ ዘመን ጋዜጣ)

የሽብር ቡድኑን ዓላማ ለማሳካት የሚያገለግል የህትመትና ስርጭት ክፍል ነው፡፡ የክፍሉ ጋዜጣ የሆነው አዲስ ዘመን ጋዜጣ መረጃን አዛብቶ በማቅረብ የሽብር ድርጊት እንዲፈፀም አስተዋፅኦ አድርጓል፡፡ በርዕስ አንቀፁና በገጽ 3 የፖለቲካ አምዱ ተከታታይ እትሙ ህዝበ-ሙስሊሙ አዲሱን የአህባሽ አክራሪ አስተሳሰብ መቀበል እንዳለበት ዛቻ አዞል ሀተታዎችን አሰራጭቷል፤ የመብት ጥያቄ እንቅስቃሴውን በሽብር ፈርጇል፤ በሀሰት የሽብርተኝነት ድርጊት አስፈራርቷል፡፡ የሽብር ቡድኑን አመራሮች በተለያዩ ጊዜ ቃለ-መጠይቅ በማድረግ  ለሽብር ቡድኑ የሚዲያ ድጋፍ ሰጥቷል፡፡ ስለሆነም በፀረ-ሽብረተኝነት አዋጅ ቁጥር 652/2001 አንቀፅ 6 እና 11 የተመለከተውን በመተላለፍ ተከሷል፡፡

20ኛ. ተከሳሽ  የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት (ኢ.ሬ.ድ- ኢቲቪ)

ከህዝብ መገናኛ ብዙሃን አንዱ የሆነው ኢ.ቲ.ቪ. የተቋቋመበትን ዓላማ ወደ ጎን በመተው የሽብር ቡድኑን ዓላማ ለማሳካት የታሰቡና የታቀዱ የተዛቡ መረጃዎችን ለህዝብ በማድረስ ህዝብን በህዝብ ላይ አነሳስቷል፤ የህዝበ-ወኪሎችን በሽብር የፈረጀና በሀሰት ቅንብር ተሞላ “ጅሃዳዊ ሀረካት” የተሰኘ ገዛቢ ፊልም በተደጋጋሚ አሰራጭቷል፡፡ የሽብር ቡድኑ የሚፈፅማቸውን ህገ-ወጥ ድርጊቶች በማስመሰል ህዝብን ለማሳሳት ሙከራ አድርጓል፡፡ የሽብር ቡድኑ አመራሮችና ረዳቶች በተለያዩ ጊዜ ያደረጓቸውን የሽብር ቅስቀሳዎች አሰራችቷል፡፡ በዚህም የሽብርተኝነት ድርጊቱ ተባባሪ ሆኗል፡፡ ንፁሃንንና የሽብር ሰለባዎችን ሽብርተኛ በማስመሰል በሀሰት የሽብርተኝነት ድርጊት ህዝብን አስፈራርቷል፡፡ በተለይም የክርስትና እምነት ተከታዮች በእስልምና ተከታይ ወንድቻቸው ላይ ጥርጣሬ እንዲያድርባቸው በማድረግ የእርስ በርስ ጦርነት ለማስነሳት ያልተሣካ ሙከራ አድርጓል፡፡ ስለሆነም በፀረ-ሽብርተኝነት አዋጅ ቁጥር 652/2001 አንቀጽ 6 እና 11 የተመለከተውን በመተላለፍ ተከሷል፡፡

21ኛ. ተከሳሽ ፔትራም ኃ/የተወ/የግል ማህበር

የሽብር ቡድኑ የፋይናንስ ድጋፍ ሰጭ በመሆን በህግ ከተቋቋመበት የንግድ ተቋም ውጭ የአህባሽን አክራሪ አስተሳሰብ ወደ ኢትዮጵያ በማስመጣት ሂደት ላይ የሎጀስቲክ ድጋፍ ሰጥተዋል፡፡ በዚህም 18ኛ ተከሳሽ ዶ/ር ሰሚር አልሪፋዒይ የተባሉ ሊባኖስዊያንና እርሳቸው ያደራጁዋቸው ሊባኖሳዊያን አሰልጣኞች ወደ ኢትዮጵያ በማስመጣት ሂደት ላይ አስተዋጽኦ አድርገዋል፡፡ ተከሳሹ በ3ኛ ተከሳስ የቀድሞው ጠ/ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ፊማ የታዘዘውን በቦሌ ክ/ከተማ የሚገኝ 100000 ካሬ ሜትር (አንድ መቶ ሽህ ካሬ ሜትር) ቦታ ለአህባሽ ማሰልጠኛ ተቋም ግንባታ ይውል ዘንድ ኃላፊነት ወስዶ ተንቀሳቅሷ፡፡ በአጠቃላይ ከፍተኛ የገንዘብ ወጭ በማድረግ ለአህባስ አስተሳሰብ መስፋፋት ከፍተኛ አስተዋፅኦ በማድረግ የሽብር ቡድኑን ረድተዋል፡፡ ስለሆነም በፀረ-ሽብርተኝነት አዋጅ ቁጥር 652/2001 አንቀፅ 5(1) (ሐ)(መ) እና 7(1) የተመለከተውን በመተላለፍ ተከሷል፡፡

2ኛ ክስ

(16 እና 21ኛ ተከሳሾችን በተመለከተ)

ወንጀሉ

በወንጀል ድርጊት የተገኘ ገንዘብ ወይም ንብረት ህጋዊ አስመስሎ ማቅረብን እና ሽብርተኝነት በገንዘብ መርዳትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣ አዋጅ ቁጥር 780/2005 አንቀፅ 31(1)(ሀ)(1) የተመለከተውን በመተላለፍ፡-

የወንጀሉ ዝርዝር

16ኛ ተከሳሽ አቶ አህመዲን አብዱላሂ ጨሎ

ተከሳሽ አህባሽ የተሰኘውን አክራሪ አስተሳሰብ ለማስፋፋት በማቀድ መጠኑ 203000000.00 (ሁለት መቶ ሦስት ሚለዮን ብር) የሆነ ምንጩ ያልታወቀ ገንዘብ በርሳቸው ፊርማ ብቻ እንዲንቀሳቀስ በማድረግ በሽብር ቡድኑ የሚያዘጋጃቸውን የግዳጅ ሥልጠናዎች ወጭ ሸፍነዋል፤ ለ5ኛ ተከሳሽ ለፌ/ፖሊስ ኮሚሽን አባላት የሽብር እንቅስቃሴ የውሎ አበል ክፍያ በመስተት፣ የህዝበ-ሙስሙን እንቅስቃሴ ለማኮላሸት ለተመደቡ ግለሰቦችና የደህንነት አባላት የው አበል በመክፈል፤ በግፍ ለሚወነጀሉ ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች የሀሰት ምስክር ለሚሆኑ የአህባሽ አስተሳሰብ አራማጆች አበል በመክፈል የሽብር ድርጊቱ ቀጥተኛ ረዳት በመሆንና ሽብርተኝነትን በገንዘብ በመርዳታቸው በአዋጅ ቁጥር 780/2005 አንቀፅ 31(1)(ሀ)(1) የተመለከተውን በመተላለፍ ተከሰዋል፡፡

21ኛ. ተከሳስ ፔትራም ኃ/የተወ/የግል/ማህበር

የሽብር ቡድኑ የፋይናንስ ድጋፍ ሰጭ ክንፍ በመሆን በህግ ከተቋቋመበት የንግድ ተቋነት ውጭ አክራሪ አስተሳሰብን ከፍተኛ በጀት በመመደብ ረድቷል፡፡ ተከሳሹ ምንቹ ያስታወቀ ግምቱ $30,000,000.00 (ሰላሳ ሚሊዮን) ዶላር ገንዘብ ህጋዊ በማስመሰል ወደ ኢትዮጵያ በማስገባት የንግድ ተቋሙ ራሱን ከማጠናከር ጎን ለጎን አህባሽን ለማስፋፋት ተጠቅሞበታል፡፡ ከ1996 ጀምሮ በህቡዕ ሲንቀሳቅስ የነበረውንና በጦር ሃይሎች 3 ቁጥር ማዞሪያ የሚገኘውን የአህባሽ ማሰልጠኛ ተቋም ሙሉ በሙሉ ዓመታዊ በጀቱን በመሸፈን ሲረጁ ቆይቷል፡፡ የተከሳሹ ስራ አስኪያጅና ባለቤት አቶ አብዱልከሪም በድሪ ያላቸውን የገንዘብ አቅም በመጠቀም ከመንግስት ባለስልጣናት ጋር ትስስር በመፍጠር አህባሽን ከሊባስ ወደ ኢትዮጵያ በማስመጣት ሂደት ላ የአምባሳደርነት ሚና ተጫውተዋል፡፡ በዚህም ፔትራም ሃ/የተወ/የግል ማህበር በኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች ላይ ለደረሰው የህገ-መንግስት ጥሰትና የሽብር ድርጊት የገንዘብ እርዳታ ያደረገ በመሆኑ ተከሳሽ በአዋጅ ቁጥር 780/2005 አንቀፅ 31(1)(ሀ)(1) የተመለከተውን በመተላለፍ ተከሷል፡፡

 

የማስረጃ ዝርዝር

ሀ/ የሰው ምስክር

  1. መላው የኢትዮጵያ ህዝብ

ለ/ የሰነድ ማስረጃ

  1. 10000 ገጽ የተለያ አስረጂ ሰነዶች

ሐ/ የድምፅ ከምስል ማስረጃ

  1. 15 ቴራ ባይት ማስረጃ

መ/ የፎቶ ግራፍ ገላጭ ማስረጃዎች

  1. 2000 ፎቶዎች (በቁጥር)

ሠ/ በፍ/ቤት ትዕዛዝ የሚቀርቡ

1. በብሔራዊ መረጃና ደህንነት ቢሮ የሚገኙ ሚስጥራዊ ሰነዶች ከብሔራዊ መ/ደህንነት

2. የሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎች በማዕከላዊ የደረሰባቸውን ስቃይና የግዳጅ ቃል እንዲሰጡ የደረሰባቸውን ጫና የሚያሳይ የድምፅ ከምስል ማስረጃ፣ ከፌዴራል ወንጀል ምርመራ (ማዕከላዊ)

3. ኢቲቪ በጅሃዳዊ ሀረካት የተሰኘ የሀሰት ዘጋቢ ፊልም ባስተላለፈበት ፊልም ላይ የተጠቀማቸው ፊልሞች ሙሉ ይዘት ከኢቲቪ

4. የህውኃት/ኢህአዴግ የሽብር ቡድን በተለያዩ ጊዜ ያደረጋቸው ህቡዕ ውይይቶች፣ እቅዶች፣ ሴራዎችና ቃለ-ጉባዔዎች፣ ከድርጅቱ ጽ/ቤት

5. የጠ/ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ አማካሪዎች የሚያቀርቧቸው ጥናታዊ ጽሑፎች ከጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ

6. የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የግል ማስታወሻ ደብተር ከባለቤታቸው ወ/ሮ አዜብ መስፍን

7. የኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞችን የመብት ጥያቄ ለመቀልበስ፣ ለማኮላሸትና ለማምከን የተደረጉ ሚስጥራዊ ውይይቶች ቃለ-ጉባዔዎች ከሁሉም የሚኒስቴር መ/ቤቶችና ከመጅሊስ፡፡

 

©መአኮ

የዋሺንግተን ዲሲ የጋራ ግብረሃይል “በሙስሊም ወንድሞቻችን ላይ የተፈረደው ፍርድ በ90 ሚሊዮን ሕዝብ ላይ የተፈረደ ፍርድ ነው”ሲል አወገዘ

$
0
0

abubeker

ጋዜጣዊ መግለጫ

የፍትሕ ያለህ

ፍትሕ የትንሽ የትልቁ የስላሙም የክርስቲያኑም የንግግር አልፋና ኦሜጋ ከሆነ ሰነበተ አብያተ ክርስቲያናት ጸሎታቸውን ፣መስኪዶች ሶላታቸውን የሚያሳርጉት ስለ ፍትሕ እየጮሁ ነው።የጥንቱን ታሪክ እንዳለ ብናቆየው እንኳ ባሳለፍነው ከሬት የመረረ ወያነያዊ ስርዓት ፍትሕ በውን ተከስታ ልትትታይ ቀርቶ በዳሰሳና በሽታ እንኳ ደብዛዋ ጥፍቶ የ፺ ሚሊዮን ህዝብ የምኞት መዝሙር ሆና ፪፭ አመታትን አስቆጠረች። ዛሬም የፍትሕ ያለህ የህዝብ መዝሙር ሆኖ ቀጥሏል።

የፍትሕ ያለህ በሚል ርዕስ መግለጫ ስናውጣ ባለፈው ፪፭ አመታት የተደሰኮረልን ፍትሃዊ ስርዓት፣ሰፈነ የተባለው ሰላማዊና ልማታዊ አገዛዝ፣ጮቤ የተረገጠለት ዲሞክራሲ ቢከፍቱት ተልባ ስለሆነብን ነው።

በርካቶች በእንበለ ፍርድ በወያኔ ተከሰው በወያኔ ተመስክሮባቸው በወያኔ ዳኛ በወያኔ አቃቤ ህግ በወያኔ የግፍ ሰንሰለት አሳራቸውን የበሉ በዚያውም ያሸለቡ ደብዛቸው የጠፋ ለዛሬ ቤቱ ይቁጠራቸው ለማለት ተገደናል። ላሁኑ ግን በኢትዮጵያ ሙስሊሞች ላይ ሰሞኑን የተጠበቀ ግና አስደንጋጭ ስለሆነው በንጹሃን የሙስሊም መፍትሄ አፈላላጊዎች ላይ የተበየነው ብይን ለተበየነባቸው ጀግኖች ሳይሆን ሃዘናችንን የምንገልጸው በራሱ ላይ ስለፈረደው የፍትሕን ገመድ ገምዶ አንገቱ ላይ ስላጠለቀው የወያኔ ስርዓት ነው።
ከ፱፯ ዓመተ ምህረት ምርጫ ህዝባዊ እንቅስቃሴ በሗላ በሃይል ተጨፍልቆ ብልጭብልጭ ሲል የከረመው ህዝባዊና ኢትዮጵያዊ ወኔ ድንገት ሰሜን ምዕራብ አዲስ አበባ ከዓወሊያ ተቋም ገንፍሎ ምድሪቷን ያጥለቀለቀው የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ትግል ስንቃኘው እንደዜጋ አድናቆት ስንቸረው በመብት ትግሉ ሂወት ያስከፈላቸውን አሳሳ፣ገርባ፣ኮፈሌዎችን፣እንዲሁም በፈሪ በትር የተቀጠቀጡትን አካል የጎደለባቸውን፣ ባኑዋር መስኪድ የጥቁር ሽብር ሰለባ የሆኑትን፣ለፍትሐዊ ትግሉ ቀንዲል ሆነው ዛሬ ለጠየቁት ጥያቄ ከ፯ እስከ ፪፪ አመት በሚል የቀልድ ቲያትር መጋረጃ የተዘጋባቸውን ወንድም እህቶች ታላቅ ወገናዊ አክብሮት እንሰጣለን።

ትግሉ የጋራ ነው ድሉም እንደዚሁ>>> እኛ በዋሺንግተን ዲሲ አካባቢ የምንገኝ የጋራ ግብረሃይል በዚህ ሳምንት የሰማነው እምበለ ፍርድ የጠበቅነው ነውና ባንደነቅም ሆኖም ግን እንዲህ አይነት በ፺ ሚሊዮን ህዝብ ላይ የተቀለደ ቀልድን አንስቅለትም። እንዲያውም ትንታጎቹን ፈጣሪ ያበርታቸው፣ቤተሰቦቻቸውን አምላክ ያጽናናቸው ስንል ለኢትዮጵያ ሙስሊሞች ባጠቃላይ አብሽሩ የሚል መልዕክት እናስተላልፋለን።

ፍትሕ የተዘነበለችው ባጠቃላይ በኢትዮጵያውያኖች ላይ ነውና ለዚህ ሁሉ አብነቱ የፍትሕ ያለህ የሚል ጩኸታችን የሚቆመው ይህ ጸረ እስላም፣ጸረ ክርስቲያን ጸረ ሃገር የሆነው ሰይጣናዊ ስርዓት በጸሎትም በሁለገብ ትግልም በተባበረ ህዝባዊ እምቢታም ተመንግሎ ነጻነታችንን ስንጎናጸፍ ብቻ ነው ብለን እናምናለን።ለዚህም በኛ በኩል ሰላም ላጠጠበት ህዝባችን፣ፍትሕ ለጠፋበት ወገናችን፣በኩልነት ለምታኖረን ኢትዮጵያችን ባስገባን ቀዳዳ ሁሉ ገብተን የመጨረሻዋ እስትንፋሳችን እስክትቆም ድረስ አብረን ተባብረን ለመታገል ስለፍትሕ በሚጮህ ህዝባችን ስም ቃል እንገባለን።

እግዚዓብሄር ትልቅ ነው
አላህ ወኩበር

አዱሊስ ጋዜጣ –በPDF ያንብቡ


Health: መጾም ከመንፈሳዊው ጥቅም ውጭ ለጤና ያለው 7 በረከቶች

$
0
0

Fiftit

በሙለታ መንገሻ

ለተወሰነ ስዓት ከምግብና ከመጠጥ ዘሮች መራቅ ወይም መጾም ከሀይማኖታዊ ጥቅሙ በዘለለ በርካታ የጤና ጠቀሜታዎች እንዳሉት ጥናቶች ያመለክታሉ።

በሳምንት ውስጥ ቢያንስ ለሁለት ቀናት መጾም ከጉዳቱ ጥቅሙ ያመዝናል ይላል ጥናቱ።

መጾም የሚያስገኛቸውን የጤና ጠቀሜታዎች 

 1.የምግብ መፈጨት ስርዓታችን እንዲስተካከል ይረዳል

ጾመ የምግብ መፈጨት ስርዓታችን እረፍት እንዲኖረው በማደረግ የተረጋጋ እና ጤነኛ የምግብ ዝውውር እንዲኖር ያደርጋል። የምግብ መፈጨት ስርዓታችን መስተካከልም በሰውነታችን ውስጥ ያለን የስብ መጠን ለማቃጠል ይረዳናል።

  2.ትክክለኛው የረሃብ ስሜት እንድንለይ ያግዛል

መጾም የሰውነታችን ሆርሞኖች የተስተካከሉ እንዲሆኑ በማድረግ ትክክለኛውን የረሃብ ስሜት እንድንለይ ያደርገናል።

  3.የጠራ የሰውነት ቆዳ እንዲኖረን ያደርጋል

ጾም ሰውነታችንን ከምግብ መፍጨት ስራው ነጻ ስለሚያደረግ ሆርሞኖቻችን ወደ ሌሎች ስራዎች ይገባሉ።

ለአንድ ቀን ምግብ አለመመገብ ሰውነታችን በውስጡ ያሉትን መርዛማ ንጥረ ነገሮችን እንዲያጸዳ እድል የሚሰጥ ሲሆን፥ በዚህ ጊዜም ኩላሊታችን፣ ጉበታችን፣ ቆዳችን እንዲሁም ሌሎች የሰውነታችን ክፍሎች ተግባራቸውን በአግባቡ እንዲከውኑ ያግዛል።

   4.የአዕምሯችን የማሰብ አቅም ይጨምራል

ጾም አእምሯችን ብሬይን ድራይቭድ ኔውሮትሮፊክ ፋክተር የሚባል ፕሮቲን እንዲያመርት ይረዳዋል። ይህም አእምሯችን ጤነኛ እንዲሆን ያደርጋል።

በተጨማሪም ፕሮቲኑ ከአእምሮ ጋር ተያያዥነት ያላቸው እንደ አልዛይመር እና ፓረኪሰንሰ በሽታዎችን ይከላከላል።

    5. የሰውነት ክብደትን ለመቀነስ ይረዳል
አልፎ አልፎ መጾም የሰውነታችንን ክብደት ለመቀነስ እንደሚረዳ ጥናቶች ያመለክታሉ።

ለተወሰነ ስአት ከምግብ መራቅ ሰውነታችን ውስጥ ያለው የስብ መጠን እንዲቃጠል በማድረግ ክብደት ለመቀነስ ይረዳል።

  6. ጥንካሬ እንዲኖረን ያደርጋል

መጾም የሰውነታችንን ጥንካሬ እንደሚቀንስ ነው በዙዎቻችን የምናስበው። ይሁን እንጂ ጥናቶች የሚያሳዩት የዚህን ተቃራኒ ነው።

ትንሽ መብላት የመኖር እድሜያችንን ለመጨመር ፋይዳው ትልቅ መሆኑም ነው የሚነገረው።
 7. በሽታ የመከላከል አቅምን ይጨምራል

መጾም ሰውነታችን በሽታ የመከላከል አቅሙን እንዲጨምር ይረዳል። ይህም በሽታ አምጪ ነገሮችን እንዲሁም ካንሰር አምጬ ሴሎች በውስጣችን እንዳያድጉ ያደርጋል።

ጥናቱ ላይ እንደተገለጸው እንስሳት በተፈጥሮ በሚያማቸው ጊዜ ምግብ ከመፈለግ ይልቅ ራሳቸውን ከምግብ በማራቅ እረፍት ይወስዳሉ።

ይህም ሰውነታቸው በቀላሉ በሽታን ለመከላከል ይረዳቸዋል።

በተቃራኒው በህመም ወቀት ምግብ ለማግኘት የምንሯሯጠው ብቸኞቹ ፍጡሮች የሰው ልጆች ነን ይላል ጥናቱ።

ምንጭ፦ ideadigezt.com

 

አራቱ የበረከት ስምዖን እንግዶች (ጥብቅ ምስጢር –ያንብቡ)

$
0
0

simon
ከሐና ሙሉጌታ

ጥር 6 ቀን 2002 ዓም በተለምዶ ጉበት ከለር እየተባለ የሚጠራውን ቀለም የተቀባች ኮድ ሁለት የታርጋ ቁጥሯ 63795 የሆነች ‹‹ ወያኔ›› ዲኤክስ የቤት አውቶሞቢል ሾፌሩን ጨምሮ አራት ሰዎችን ይዛ ወደ ኢህአዴግ ፅ/ቤት እየከነፈች ነው ሾፌሯ የመኪናዋ ባለቤት ነው ፡፡ሶስት እንግዶችን ባስቸኳይ አቶ በረከት ቢሮ እንዲያደርስ ነው የታዘዘው ሁለት ወጣቶችንና አንድ ሰውነቷ ሞላ ያለች ሴትይዟል ፤የካቴድራል ሥላሴ ቤ/ክርስቲያን በር ሊደርሱ ጥቂት ሲቀር የግንብ አጥሩ ከቤተክርስቲያኑ ግምብ ጋር የተያያዘው ግዙፉ የኢህአዴግ ፅ/ቤት በር ላይ ቆሙ እጆቻቸውን ከመሳሪያቸው ምላጭ ላይ ከማይነቅሉት ላብ አደር የመከላከያ ሠራዊት መካከል አንዱ ጠጋ አለና ‹‹አቤት ›› አለ ከሾፌሩ አጠገብ የተቀመጠችው ሴት ወ/ሮ ‹‹ አቶ በረከት ጋር ቀጠሮ አለን ›› አለችው ወታደሩም ‹‹ሁላችሁም›› አለ ‹‹ አዎ ›› አለች ራመድ አለና ከአንድ ሌላ የእሱ ቢጤ ጋር ተነጋግሮ በሩ ስር ካለች አነስተኛ ቤት ወረቀት ይዞ ወጣና አነበበ ወደ መኪናዋም ተጠጋና የአራቱንም መታወቂያ ጠየቀ ተሰጠው በስማቸው ትክክል ከመታወቂያቸው ላይ ካመሳከረ በኋላ በባለ ዘንግ ክብ መስተዋት የመኪናዋ ሆድ እቃ ሳይቀር ተፈትሽው ወደ ውስጥ እንዲገቡ ተፈቀደላቸው ወታደሩ ይዟት መጥቶ የነበረው ወረቀት ‹‹ ወ/ሮ ሙሉ ከነመኪናቸው ይግቡ›› የሚል ከበረከት ስምዖን ቢሮ የተላከች የመግቢያ ፈቃድ ነበረች ፡፡

አራቱም ሰዎች ከበረከት ፀሐፊ ከዓለም ጠረቤዛ ደረሱ በሃይላንድ ውሃ ጉዳይ ከህላዌ ዮሴፍ ጋር እየተጨቃጨቀች ነበር ቀልደኛውና ሲፈጥረው ባለስልጣን መሆን ያልነበረበት ህላዌ አይቷቸው የማያውቀውን አንግዶች ሲያይ ደንገጥ አለና ወደ ኋላው ሁለት ርምጃ ተሳበ አንግዶቹ አለምን እየጨበጡ መግባት ይችሉ እንደሆነ ጠየቁ በወቅቱ የስምዖን ልጅ በረከት ከአዲሱ ለገሰ ጋር ውይይት ላይ ስለነበር ‹‹ ቁጭ በሉ ከሰዓታችሁ 20 ደቂቃ ቀድማችኋል አለቻቸው›› ተቀመጡ ከጥቂት ደቂቃ በኋላ አዲሱ እየሳቀ ከበረከት ቢሮ ሲወጣ እሱም አንግዶቹን አየና አልፏቸው ሊሄድ ብሎ መለስ አለና እጁን ለሰላምታ ዘረጋላቸው በአክብሮት ጨበጡት ወ/ሮዋን ሲጨብጥ ጠበቅ አድርጎ ያዛትና ‹‹የት ነው የማውቅሽ ሦስተኛ ጉባኤ ላይ ነው አራተኛ ነው … እዚህ ቦታ እዚያ ቦታ ››እያለ ሲያስጨንቃት ወ/ሮዋ ፈገግ በማለት ብቻ ዝም አለችው አዲሱ ግን ተሸውዷል በወቅት ወ/ሮ ሙሉን የትም ቦታ አያውቃትም ነበር፡፡

በረከት ከመቀመጫው ተነስቶ ተቀበላቸው ትንሽ ሰላምታ ከተለዋወጡ በኋላ ሾፌሩ ወደ ውጪ ወጣና ፀሐፊዋ ዓለም ጋር የመጣለትን ወፍራም ቡና እየጠጣ ከፊት ለፊቱ ‹‹ልማታዊውን ባለሀብት አትንኩት›› የሚል ትዕዛዝ ይሁን ልመና ፁሁፍ ያለበትን የሼክ አላሙዲንን ፎቶ እያየ በሀሳብ ሄዷል ሶስቱ ሰዎች ረዘም ላለ ሰዓት ቆዩ ድንገት ያልታሰበ ነገር ተከሰተ የታላቁ ባለስልጣን የአቶ በረከት ቢሮ በኃይል ተበረገደና ወ/ሮዋ ስትቀር ሁለቱ ወጣቶች በቁጣ መንፈስ ወጡ በዚህ ጊዜ ጸሀፊዋ ዓለም በፍጥነት ተነስታ የበረከትን ቢሮ እንደመዝጋት ደህንቱን እንደማረጋገጥም ወደ ውስጥ አየት አድረጋ መልሳ ዘጋችው ሁለቱ በፍጥነት ደረጃውን እየወረዱ ነበር ከጥቂት ቆይታ በኋላም ወ/ሮዋ ወጣች በር ላይ ቆሟ ግን አንዲት ቃል ወረወረች ‹‹በረከት ግን ጊዜ ወስደህ አስብበት ይህ ለሁላችንም (ለማንም) አይበጅም አለችው ተጨማሪ ንግግር ልታደረግ ያሰበች ትመስል ነበር ግን ከአፍንጫው ከፍ ብሎ ባለው ቦታ ላይ ንቅሳት ያለው የበረከት ስምዖን የግል ጠባቂ ከዚህ መጣ ሳይባል ድንገት ከተፍ ብሎ ወ/ሮዋን እንደ ማባበልም እንደ መግፋትም አድርጎ ቢሮውን ከጀርባው እየዘጋ ደጋግፎ ሸኛት ፡፡

በወቅቱ በረከት ቢሮ የመጡት እነዛ ሰዎች እነማን ናቸው ? የተነጋገሩትስ ሰለምንድን ነው? ያልተግባቡትስ በምንድን ነው ? ይህን ጉዳይ ከእኔ ከፀሐፊዋ ይልቅ የአንድነት ፓርቲ የአመራር አባል የነበረው ኢ/ር ዘለቀ ረዲ አሳምሮ ያውቀዋል:: ፁሁፌን ከማጠቃለሌ በፊት እነዛ አራት ሰዎች አሁን የት ናቸው? ለሚለው ጥያቄ መልስ ልስጥ የመኪናዋ ባለቤትና ሾፌር የነበረው በአሁን ወቅት ከኢ/ር ዘለቀ ረዲ ጋር በገጠር መንገድ ሥራና በታላላቅ የውሃ ቁፋሮ ሥራ ተሰማርቶ ሚሊየነር ሆኗል:: አንደኛው ገጣሚ ሙሉ ሰሎሞን ራት ጋብዛው ከምሽቱ አራት ሰዓት ላይ ከካዛንቺስ ወደ መገናኛ መኪናውን እያሽከረከረ ሲሄድ በተሳሳተ መንገድ ከሌላ አቅጣጫ በሚመጣ መኪና ይገጭና ይቆማል:: ድንጋጤው አልፎለት ከመኪናው ሊወርድ ሲል በገጪው መኪና ውስጥ ከነበሩ ሰዎች በተተኮስ ሽጉጥ ተገደለ:: ሶስተኛው ሰው በአሁን ወቅት ወሊሶ ወህኒ ቤት የማያውቀው ወንጀል ተለጥፎለት የሰባት ዓመት ፍርደኛ ሆኖ ተኝቷል:: አራተኛዋና ወ/ሮ ሙሉ ኃይሌ ገብረስላሴን ጨምሮ በሚሊየን የሚቆጥር ገንዘብ አጭበርብራለች ተብላ የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ከሆነችና ነነዊት አፈወርቅ ከተባለች ልጇ ጋር 28 (ሃያ ስምንት) ዓመታት ተፈርዶባት ቃሊቲ ተጥላለች፡

እስኪ የሀገር ውስጥ ሚዲያዎች ወ/ሮ ሙሉ ኃይለማርያም በምን እንደተሳረች የዘገቡትን አድምጡና ፍርድ ስጡ ምን ያህሉ ተዓማኒ ነበር ?እኚህ ስማቸውን መግለፅ አንፈልግም የተባሉና የተጠየቁትን ሚሊዮኖች እያወጡ የሚሰጡ ሰው ማናቸው? ሊንኩን ተጭነው ዜናውን ያድምጡ

በሞስሊሙ ማኅበረሰብ መሪዎች ላይ የተወሰነውን እስራት ሸንጎ ያወግዛል።

$
0
0

ሐምሌ 29፣ 2007 (ኦገስት 5፣ 2015)

shengoሰኞ  ሐምሌ 27፣ 20017  (ኦገስት 3፣ 2015) በሞስሊሙ ማኅበረሰብ መሪዎች ላይ የህወሓት/ኢህአዴግን ፍላጎት በማስፈም የሚታወቀው ፍርድ ቤት ከሰባት ዓመት እስከ 22 ዓመት የሚደርስ እስራት እንደበየነባቸው ይፋ ሆኗል።

የሞስሊሙ ኅብረተሰብን የተቃውሞ ድምጽ መረት በማድረግ በሰላማዊ መንገድ መፍትሄ በማፈላለግ ተግባር ላይ ተሰማርተው የነበሩት እነአቡበከር አህመድ የታሰሩት ከሁለት ዓመት በፊት የህወሓት/ኢህአዴግ መንግሥት በሙስሊሙ ማኅበረሰብ እምነት ውስጥ ጣልቃ በመግባት አመራሩን ለመቆጣጠርና እሱ የሚፈልገውን የእምነት ፈርጅ ኢትዮጵያውያን  ሞሰሊሞች በግዴታ እንዲቀበሉ ያውጠነጠነውን ሃላፊነት የጎደለው ተግባር እምቢ ማለታቸውን ተከትሎ እንደነበር ይታወሳል።

ሸንጎና ሌሎችም እጅግ በርካታ ኢትዮጵያውያን በሀገራችን ውስጥ የሞስሊሙ ማኅበረሰብ መንግሥት በሃይማኖቱ ውስጥ እንዳይገባ ያቀረበውን ጥያቄ በማክበር እጁን እንዲያነሳ በተደጋጋሚ ሲያሳስብ ቆይቷል።  ሆኖም እንደተለመደው ሁሉ ከራሱ ሌላ ማንንም ማዳመጥ ያልለመደው  የህወሓት/ኢህአዴግ ጆሮ ዳባ ልበስ በማለት ሃላፊነት የጎደለው እርምጃ በሚቆጣጠረው ፍርድ ቤት በኩል ተግባራዊ እንዲሆን አድርጓል።

ይህ እርምጃ የሞስሊሙን ኅብረተሰብ የሃይማኖት ነፃነት ጥያቄ ይበልጥ ያጠናክረዋል እንጂ  አያዳክመውም። እንዲያውም የሞስሊሙ ብረተሰብ አባላትና ሌሎችንም በህጋዊና ሰላማዊ መንገድ ጥያቄን አቅርቦ በሕግ መብትን ማስከበር አይቻልም ወደሚል መደምደሚያ እንዲደርሱና አላስፈላጊ በሆነ ጎዳና እንዲጓዙ የሚገፋፋ ነው። ይህ ለሀገራችን ሰላምና መረጋጋት የሚረዳ ሳይሆን አደጋን የሚጋብዝ እጅግ ሃላፊነት የጎደለው እርምጃ ነው።

ሸንጎው በሞስሊሙ ኅብረተሰብ በመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት ላይ የህወሓት/ኢህአዴግ መንግሥት የፖለቲካ መሳሪያ የሆነው ፍርድ ቤት የወሰደውን እርምጃ አጥብቆ ያወግዛል። የሞስሊሙ ኅብረተሰብም መሰረታዊ መብቱን በሰላማዊ መንገድ ለማስከበር በሚያደርገው እንቅስቃሴ የትግል አጋርነቱን ያረጋግጣል።

ኢትዮጵያውያን ሁሉ ህወሓት/ኢህአዴግ የሚያካሂደውን በሃይማኖት ነፃነት ላይ ያነጣጠረውን ጥቃት እንዲያወግዝ  ሸንጎ  ጥሪውን ያቀርባል። የህወሓት/ኢህአዴግ ደጋፊዎችም አገዛዙ ከቀን ወደቀን ሀገራችንንና ሕዝባችንን ወደተባባሰ አደገኛ ጎዳና መውሰዱን እንደቀጠለ መሆኑን እንዲገነዘቡ እያሳሰበ፡ በዚህም ምክንያት ለሚከተል አለመረጋጋት ተጠያቂው ህወሓት/ኢህአዴግ እንደሆነ ሁሉም እንዲገነዘበው እናሳስባለን።

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!

የአርበኞች ግንቦት 7 አመራር ኤፍሬም ማዴቦ አስመራ ወርደው የትጥቅ ትግሉን ተቀላቀሉ

$
0
0

የአርበኞች ግንቦት 7 አመራር ኤፍሬም ማዴቦ አስመራ ወርደው የትጥቅ ትግሉን ተቀላቀሉ
(ዘ-ሐበሻ) ከአርበኞች ግንቦት 7 ከፍተኛ አመራሮች መካከል አንዱ የሆኑት አቶ ኤፍሬም ማዴቦ አስመራ ሄደው የትጥቅ ትግሉን መቀላቀላቸው ተሰማ::

የአርበኞች ግንቦት 7 መሪ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እንዲሁም አቶ ነአምን ዘለቀ አስመራ ወርደው ትግሉን ከተቀላቀሉ ሳምንታት የተቆጠረ ሲሆን አቶ ኤፍሬም ማዴቦም ከትናንት በስቲያ ትግሉን ተቀላቅለዋል::

አርበኞች ግንቦት 7 በሕወሓት መንግስት ሠራዊት ላይ በሰሜን በኩል ጥቃት መሰንዘሩን ተከትሎ አፍቃሬ ወያኔ ሚዲያዎች በሰሜን በኩል ትግል የለም ለማለት “የኢትዮጵያ መንግስት ሰራዊቱን ወደ ሱማሊያ አሰማራ” የሚሉ ዜናዎችን በማስተጋባት ላይ ይገኛሉ::

ለዘ-ሐበሻ የደረሰው መረጃ እንደሚያመለክተው ከአቶ ኤፍሬም በተጨማሪ ሌሎች ስማቸው ያልጠቀሰ የድርጅቱ አመራሮች ትልቅ ገቢ የሚያስገኝላቸው ሥራቸውን እና ቤተሰቦቻቸውን በመተው የትጥቅ ትግሉን ተቀላቅለዋል::

የዛሬ 25 ዓመት ወደ ስደት ገብተው በሰሜን አሜሪካ የተለያዩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የተማሩት አቶ ኤፍሬም ከጆርጅ ሜሰን ዩኒቨርሲቲ በማዕረግ የተመረቁ ታዋቂ የፖለቲካ ሰው ናቸው::

Health: ባለትዳር መሆን የተሻለ ጤንነት እንዲኖረን ያደርጋል?

$
0
0

wedding copy

ባህላዊ ዕውቀትም ይሁን ዘመናዊ ሳይንስ ያገቡ ሰዎች ከወንደላጤዎች የተሻለ ረጅም ዕድሜ እና ጤንነት እንዳላቸው ይገልፃሉ፡፡

“ከላጤዎች ጋር ሲነፃፀር ባለትዳሮች ጤናማዎችና እና ለረጅም ዘመን ለመኖር የታደሉ ናቸው” ይላሉ በካሊፎርነያ ዩኒቨርስቲ ሳይኮሎጂስት የሆኑት ዶክተር ቴዎዶር ሮቤልስ፡፡ “ጥናቶች እንደሚያሳዩት ባለትዳሮች በተለይ ወንዶች ረዘም ላለ ዕድሜ ይኖራሉ፡፡ በልብ በሽታዎች የተነሳ የመሞት ዕድላቸው ከላጤዎች ሲተያይ ያነሰ ነው፡፡ ጤናማ ሰዎች ትዳር የመመስረት ፍላጎት አላቸው” በማለት ትዳር ጤናማ የማድረግ አቅም እንዳለው ይገልጻሉ፡፡
“የሚረዳዱና የሚተጋገዙ ጥንዶች ጤናማነታቸው ከግንኙነታቸው ጋር ተያያዥነት አለው” ይላሉ የኦሃዮ ስቴት ዩኒቨርሲቲ ባልደረባዋ ዶክተር ጃኒስ ኪኮልት ግላሰር፡፡
ትዳር ለጤና በምክንያት
የጥሩ ባህርይ ባለቤት ያደርጋል

ጥንዶች በትዳር ሲጣመሩ በአደንዛዥ ዕፅ፣ በሲጋራ፣ እና በሌሎች ለጤና ጎጂ በሆኑ ነገሮች የሚደርሰባቸው ጉዳት እየቀነሰ ይሄዳል፡፡
“አብረው ለመኖር ሲስማው በፈቃደኝነትም ይሁን በትዳር አጣማሪያቸው ጉትጎታ ከነዚህ ሱሶች ስለሚታቀቡ ወይንም አወሳሰዳቸውን ስለሚቀንሱ የሚከሰት ነው” ይላሉ በኦሃዮ ስቴት ዩኒቨርሲቲ ሳይኮሎጂስት እና ተመራማሪ የሆኑት ዶክተር ክርስቶፈር ፍገንደስ፡፡

ማህበራዊ ግንኙነት

“ባለትዳር ከሆንክ/ሽ እስከ አሁን ከፈጠርካቸው/ ሻቸው ግንኙነቶች በጣም መቀራረብ የሠፈነበት እንደሆነ ትረዳለህ/ሽ፡፡ ይህ ማለት በማንኛውም ወቅት የምትፈልገውን/ጊውን እገዛ እና ድጋፍ ሊያደርግልህ/ ሽ የሚችል ሰው አለህ/ሽ ማለት ነው፡፡” ይላሉ ዶ/ር ጃኒስ፡፡
“በሌላ በኩል ደስተኛ ያልሆኑ ሰዎች ከማህበራዊ ኑሮ የተገለሉ ይሆናሉ፡፡ ይህም ወደ ድብርት ይመራቸዋል፡፡ የጤንነታቸውን ሁኔታም አይከታተሉም” ሲሉ በኒው ዮርክ ዩኒቨርሲቲ ሳይኪያትሪስት የሆኑት ዶክትር ሱዴፕታ ቫርማ ይናገራሉ፡፡

ጤናማ ልምዶችን ያዳብራሉ
ባለቤትዎ ጤናማ ልምዶችን እንዲያዳብሩ ሊረዱዎ ይችላሉ፡፡ “ባለቤትዎ በእርስዎ ባህርይ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ ያሳድራሉ፡፡ ይህን መመገብ የለብህም/ሽም፤ አልኮል ቀንስ/ሺ ወዘተ የሚሉት ከዚህ በጎ ተፅዕኖ የሚመነጩ ናቸው” ይላሉ ዶክተር ቴዎዶር ሮቤልስ፡፡

ከዚህ በተጨማሪም በትዳራቸው ደስተኛ የሆኑ ሰዎች የዶክተሮቻቸውን ትዕዛዝ እንደሚያከብሩ አንድ ጥናት ይገልፃል፡፡
ከሚወዱት ሰው ጋር ለረጅም ጊዜ መኖርዎ ሌሎች የጤና ጠቀሜታዎችም አሉት፡፡ “አብዛኞቻችን ከፍቅረኞቻችን ጋር ለመዝናናት መኖራችን በጎ ጎን አለው፡፡ በትዳር ተጣምሮ መኖር ከሚያስገኘው ጋር ሲወዳደር ግን አነስተኛ ነው” ዶክተር ክርስቶፍር “ከትዳር የምናገኘው ፍቅርና መተጋገዝ ለራሳችን የምንሰጠውን እንክብካቤ እንዲጨምር ያደርጋል፡፡ ይህ የሚሆነው የትዳር ተጣማሪያችን በኛ ደስተኝነት ላይ የማይተካ ሚና ስላለው ነው” በማለት ዶክተር ቫርማ የትዳር ጥቅም ከፍተኛ እንደሆነ ይገልፃሉ፡፡
ቀለበት ማጥለቅ ብቻውን በቂ አይደለም፡፡ የተሻለ ትዳር ማለት የተሻለ ጤና ማለት ነው፡፡ የልብ ቀዶ ጥገና ከተደረገላቸው በሽተኞች ውስጥ በጥሩ ትዳር ውስጥ ያሉት የመዳን ዕድላቸው ከሌሎቹ የተሻለ እንደሆነ ከ15 ዓመታት በላይ የተካሄደ አንድ ጥናት ያስረዳል፡፡ ፍቅርና ደስታ በራቀው ትዳር ውስጥ የሚኖሩ በሽተኞች የመዳን እና በቶሎ የማገገም ዕድላቸው ዝቅተኛ እንደሆነም ጥናቱ ሳይጠቅስ አላለፈም፡፡

ለዚህ የተሰጠው ዋነኛ ምክንያት መጥፎ ትዳር ለከፍተኛ ጭንቀት የሚዳርግ በመሆኑ ነው፡፡ ይህ ደግሞ የበሽታ መከላከል አቅምን ክፉኛ ያዳክማል፡፡ በተለየ ሴቶች ለዚህ ዓይነቱ ጭንቀት ተጋላጭ ናቸው፡፡ በትዳር ላይ በሚጋጥም ጥላቻ (ያለ መወደድ ስሜት) ሴቶቹ ስሜተ ስስ መሆናቸው ለችግር አጋልጧቸዋል
ይላሉ ዶክተር ጃኒስ፡፡

ዶክተር ጃኒስ እና የጥናት ቡድናቸው በምርመራክፍሎች ውስጥ ጥንዶች ባስቀመጡት ስውር ካሜራ ሲጨቃጨቁ ሁኔታውን በመቅረፅ ለማጥናት ሞክረዋል፡፡ “በክርክርና ባለመስማማት ወቅት ጥላቻን የሚያሳዩ ጥንዶች ጭንቀትን የሚያባብሱ ሆርሞኖች መጨመር ታይቶባቸዋል፡፡ የቃላት መቋሰሉ ከፈጠረው ህመም ለመዳንም ብዙ ጊዜ ይወስድባቸዋል” ብለዋል፡፡
ጠቅለል ተደርጐ ሲቀመጥ ከባድ የትዳር ችግር ያለባቸው ሰዎች የበሽታ መከላከል አቅም ሊዳከም ይችላል፡፡ የትዳር የጤናማነት ሁኔታ ወንዶችንም የጤና ችግር ሊያስከትልባቸው ይችላል፡፡

“በጥናታችን እንደደረስንበት ከሆነ ድብርት፣ አለቅጥ ክብደት መጨመር እና ከፍተኛ የደም ግፊት ደስተኛ ባልሆነ ትዳር ውስጥ በሚኖሩ ሴቶች ላይ ይታያሉ፡፡ ነገር ግን ወንዶች ትዳራቸው በሚፈጥርባቸው ብስጭት የአደንዛዥ ዕጾች ሱሰኛ ከሆኑ ተመሳሳይ የጤና ጉድለት ሊያገጥማቸው ይችላል” ሲሉ ዶክተር ቫርማ የችግሩን ስፋት ያስረዳሉ፡፡ እንደሳቸው እምነት ሁለቱም ፆታዎች ደስታ የራቀው ትዳር በሚያስከትላቸው አለመመቸቶች ይጠቃሉ፡፡ ይሁንና የሚያሳዩት የጉዳት መጠን ግን የተለያየ ነው፡፡
ብቸኞች

አንድ ሰው ብቸኛ (single) ነው ሲባል ከሌሎች ጋር የቅርብ ወዳጅነት መመስረት አይችልም ማለት አይደለም፡፡ ሌሎች ደግሞ ለፍቅር የሚሆናቸውን ሰው ባለማግኘታቸው ብቸኛ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ለዚህ ዋነኛው መፍትሔ ጥሩ ጓደኞችን ማፍራት ነው፡፡ እነዚህ ሰዎች ሊያስቡልዎና ሊጠነቀቁልዎ እርስዎም ተመሳሳዩን ሊያደርጉላቸው ይችላሉ፡፡ ይህ ዓይነቱ ራስን በጥሩ ሰዎች መሃከል ማኖር ትዳራቸውን በፍቺ ለበተኑ ሰዎችም ይሠራል፡፡

ፍቺ ካለዕድሜ ከመሞት ጋር ተያያዥነት እንዳለውና በተለይ በወንዶች ላይ በስፋት እንደሚታይ የአሪዞና ዩኒቨርሲቲ ባልደረባ የሆኑት ዶክተር ዴቪድ ስባራ ይናገራሉ፡፡ “በዕድሜ በሰል ካሉ ሰዎች ውስጥ ከፍቺ በኋላ በደስታ የተሞላ ህይወት ሲመሩ የሚታዩ ይኖራሉ፡፡ ደስታ በራቀው ትዳር ውስጥ ካሉና ትዳርዎ እንዲሠራ የሚችሉትን ያህል ከለፉ በኋላ ተስፋ እንደሌለው ካወቁ ፍቺ ምክንያታዊና አምነን መቀበል ያለብን አማራጭ ይሆናል፡፡ ተፋትተው ደስተኛ ሆነው መኖር ከቻሉ ፍቺ የሚያመጣቸው ጐጂ ጐኖች ሊያሳስብዎ አይገቡም” ይላሉ ዶክተር ዴቪድ፡፡

ከፍቺ በኋላ ሴቶች ከወንዶች በተሻለ መልኩ ጥሩ ስሜት ሊሰማቸው ይችላል፡፡ “ላጤዎችን እና የጤናቸውን ሁኔታ ስናይ ሴቶቹ ከወንዶቹ በተሻለ ጤንነት ላይ ይገኛሉ፡፡” የሚሉት ዶክተር ክርስቶፈር ባለትዳሮች ወይንም አብረው የሚኖሩ ፍቅረኞች ለመስማማት በማይችሉበት ወቅት በአክብሮት ያለ ዘለፋ እንዲነጋገሩ ይመከራል፡፡ ጥላቻ በከፍተኛ ሁኔታ የሚንፀባረቅበት ክርክርና ጭቅጭቅ ለጤና ጉዳት ያጋልጣል፡፡ በተገቢው ሁኔታ መነጋገር ሲባል ማዳመጥ፣ መስጠት፣ ቅድሚያ መስጠት እና የተናጋሪውን ስሜት መረዳትን ያጠቃልላል፡፡ በሰው ልጆች ውስጥ ያለው ትልቁ ፍላጐት ለመወደድ መንሰፍሰፍ ሲሆን እውቅና ማግኘት ደግሞ ሌላው ነው፡፡ ይህን ካደረጉ “እያዳመጥኩህ/ሽ ነው” የሚል መልዕክት ያስተላልፋሉ፡፡ ይህ አይነቱ መተሳሰብ የትዳር ችግሮቻችሁን በቀላሉ ለመፍታት እና ለመስማማት ያስችላችኋል፡፡

ይህ ጽሑፍ በአዲስ ጉዳይ መጽሔት ላይ ታትሞ ወጥቶ ነበር

Viewing all 8745 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>