Quantcast
Channel: ዘ-ሐበሻ – Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 8745 articles
Browse latest View live

ቋሚ ሲኖዶስ የፓትርያርኩን መመሪያ ተፈጻሚነት አግዷል * ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ ፓትርያርኩን አሳሰቡ

$
0
0

abune-matyas
Source: ሐራ ዘተዋሕዶ

ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ: ፓትርያርኩ ለቤተ ክርስቲያን ሰላም ሲሉ መዋቅራዊ አሠራርን በእጅጉ የሚፃረረውን አካሔዳቸውን እንዲያጤኑ አሳሰቧቸው፤ ቋሚ ሲኖዶስ የፓትርያርኩን መመሪያ ተፈጻሚነት አግዷል::

•የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ፣ ፓትርያርኩ ከሕግ አግባብ ውጭ ለሾሟቸው ዋና እና ምክትል ሥራ አስኪያጆች የምደባ ደብዳቤ እንደማይጽፉ በዛሬው የቋሚ ሲኖዶስ ስብሰባ አስታውቀዋል፡፡ ቋሚ ሲኖዶሱ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ አስተያየታቸውን በጽሑፍ እንዲያቀርቡ አዝዟቸዋል፡፡
•አሠራሩ፣ ምርጫው እና መመሪያው ተቀባይነት የሚኖረው ሥራ አስኪያጆቹ ‹‹በሀገረ ስብከቱ የፓትርያርኩ ረዳት ሊቀ ጳጳስ ተመርጠው ቀርበው ከጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ የጋራ ስምምነት ተደርሶበት በፓትርያርኩ ሲሾሙ ነው፡፡››

* * *

•‹‹ዋና ሥራ አስኪያጅ እና ምክትል ሥራ አስኪያጅ ለፓትርያርክ ተጠሪ ኾኖ አያውቅም፤ ሊኾንም አይችልም፤ የሕግ ድጋፍ ስለሌለው፡፡ ይህ ያልተለመደ የሥራ ሒደት ብቻ ሳይኾን ከሕገ ቤተ ክርስቲያን፣ ከቃለ ዐዋዲው እና ከአገሪቱ የሕግ አሠራር ጭምር ውጭ ኾኖ ተመልክቸዋለኹ፡፡››
•‹‹የሥራ አስኪያጅ ምርጫው እና የተሰጠው መመሪያ ከትዝብት ላይ የሚጥል መኾኑን ተረድተውልን ለቤተ ክርስቲያን ሰላማዊ አሠራርና ለኹላችንም ሰላም ሲባል ውሳኔዎን እንደገና እንዲያጤኑት እያሳሰብኹ በተሰጠው መመሪያ እንዲኹም በሥራ አስኪያጅ ምርጫ የማልስማማና ለማስተናገድ የምቸገር መኾኔን ለቅዱስነትዎ ሳቀርብ በታላቅ ትሕትና ነው፡፡››

/ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ፤ የከምባታ ሐዲያና ጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የፓትርያርኩ ረዳት ሊቀ ጳጳስ በዛሬው ዕለት ለፓትርያርኩ ከጻፉትና ለቅዱስ ሲኖዶስ በግልባጭ ከአሳወቁት ደብዳቤ/

The post ቋሚ ሲኖዶስ የፓትርያርኩን መመሪያ ተፈጻሚነት አግዷል * ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ ፓትርያርኩን አሳሰቡ appeared first on Zehabesha Amharic.


በጎንደር ከተማ አንድ የሚሊሺያ አዛዥ ተገደለ በርካታ ሰዎችም ታሰሩ

$
0
0

ኢሳት ዜና :- የኢሳት ምንጮች እንደገለጹት የጎንደር ከተማ የሚሊያሻዎች ሃላፊ ኮማንደር መጋቢት 11 ቀን 2015 ዓም ቀበሌ 15 ወይም ፋሲለደስ ትምህርት ቤት አካባቢ ከምሽቱ 2 ሰአት አካባቢ ላይ ማንነታቸው ባልታወቁ ታጣቂዎች ተገድሏል። ገዳዮቹም መሳሪያውን ማርከው ከእነ ትጥቃቸው ወደ አርማጭሆ ጫካ መግባታቸው ታውቋል። የጸጥታ ዘርፍ ሃላፊው ግንባሩ አካባቢ በጥይት የተመታ ሲሆን ወዲያውኑ ህይወቱ አልፏል።

ድርጊቱን ተከትሎ የጸጥታ ሃይሎች አከታትለው በመተኮሳቸው ህዝቡ ሁኔታውን ለማየት ወደ አደባባይ ሲወጣ ወደያውኑ መብራት እንዲጠፋ ተድርጓል።
newss
አዣዡ በህዝቡ ላይ የተለያዩ የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን ይፈጽም እንደነበር የከተማዋ ነዋሪዎች ተናግረዋል። የፌደራል ፖሊስ አባላት አሁንም በአካባቢው እያንዣበቡ መሆኑን የአይን ምስክሮች ገልጸዋል።

በሌላ በኩል ደግሞ ሰሞኑን ታጣቂዎች ገብተዋል በሚል መንግስት ከፍተኛ ቁጥር ሰራዊት በአብርሃ ጅራ፣ አብድራፊና አጎራባች ከተሞች አሰማርቶ ፍተሻ እያካሄደ ሲሆን፣ የአካባቢው ባለስልጣናትም ሳይቀር ተቃዋሚዎችን ትደግፋላችሁ ተብለው ተይዘዋል።
በመተማ አካባቢ በቅርቡ ለመከላከያ ሰራዊት ደሞዝ ሊከፍሉ በመንገድ ላይ የነበሩ አንድ ኮሎኔል፣ አንድ መቶ አለቃ፣ አንድ ተራ ወታደርና ሹፎራቸው ተገድለው ገንዘቡ በታጣቂዎች ከተወሰደ በሁዋላ ፣ ድርጊቱን የፈጸሙት ወደ አብርሃ ጅራ የገቡ የአርበኞች
ግንቦት7 አባላት ናቸው በሚል ፍተሻ ሲካሄድ ሰንብቷል። ምንጮች እንደሚሉት ታጣቂዎቹ 3 ክላሽንኮቭ ጠመንጃዎች፣3 ሽጉጦችንና 250 ሺ ብር የያዘ የገንዘብ መያዢያ ቀረጢት ይዘው ተሰውረዋል።

ታጣቂዎቹ ምእራብ አርማጭሆ ገብተው ምሳ መብላታቸውን፣ የአካባቢውን ነዋሪዎች በሬ ግዝተው መጋበዛቸውንና ስለ አለማቸው ማስረዳታቸውን የሚገልጹት የአይን እማኞች፣ የአካባቢው ነዋሪም ድጋፉን እንደሰጣቸው ነዋሪዎች ተናግረዋል።
በአብድራፊና አብርሃጅራ ከተማዎች መምህራን፣ አንድ ሴቶች ጉዳይ ውስጥ በሃላፊነት የሚሰራ የመንግስት ሰራተኛ፣ የአካባቢው የኢህአዴግ ወጣቶች ሊግ ሃላፊ ፣ የመንግስት ታጣቂ ሚሊሺያ ተይዘው ታስረዋል። በአካባቢው የታሰሩት ሰዎች ቁጥር ከ20
በላይ መሆኑን ነዋሪዎች ይናገራሉ።

ወደኤርትራበርሃየሚሻገሩኢትዮጵያውንቁጥርመበራከቱንተከትሎ፣በሱዳንጠረፍዙሪያመከላከያሰራዊትየመውጫበር የተባሉትን ቦታዎች ሁሉ ዘግቶ ጥበቃውን አጠናክሯል።

የአካባቢው ሰዎች እንደሚናገሩት ከተቃዋሚዎች ጋር ግንኙነት አላቸው በሚል በተለያዩ ወራቶች ከተገደሉት መካከል ዓስናቀውታፈረ፣ ሙሉጸሓይ፣ አቡሃይ ተክሌ ፣ ፣ ፈንታ አዛናው ፣ ድግሴ አድየ፣ ታደሰ ድረስ፣ ተስፋው አለሙ፣ ሙሉጌታ ማሞ፣ ደጀን
በይፋ፣ አለነ ተገኘ ፣ ሙላው አለሙ፣ ጋራ ጉርባ፣ ተስፋ፣ ዳርጌ አወቀ፣ ደጉ፣ ጨምር፣ ጥላሁን ፣ ሃብቴ አለምኔና ጸጋው ዘመነ የተባሉት ይገኙበታል።

ምህረት አባይ የተባለው ባለስልጣን ደግሞ እነ ሙላው አለሙን ማስገደሉን ነዋሪዎች ሲናገሩ፣ ሹመት የሚባለው የጎንደር የጸጥታ ሹም ደግሞ ከሳንጃ እስር ቤት በማስወጣት በእነ ደጉ፣ ጨምርና ጥላሁን ላይ እርምጃ ወስዷል።
በጉዳዩ ዙሪያ የወረዳዎችን አመራሮች አስተያየት ለማካተት ያደረግነው ተደጋጋሚ ጥረት አልተሳካም።

The post በጎንደር ከተማ አንድ የሚሊሺያ አዛዥ ተገደለ በርካታ ሰዎችም ታሰሩ appeared first on Zehabesha Amharic.

ኢትዮጵያውያኑ በጄኔቫ ሰላማዊ ሰልፍ አደረጉ

$
0
0

Geneva ethiopia

Geneva
የጀርመን ድምጽ ራድዮ ዘገባ:-
በተለያዩ ሃገራት በስደት የተበተኑ ኢትዮጵያዉያን ስለሚገጥማቸዉ ችግር ለተመ የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን እንደሚያሳዉቁ የገለፁት የሰልፉ አስተባባሪዎች፤ የኢትዮጵያን ወቅታዊ ፖለቲካ እና የሰብዓዊ መብቶች ይዞታ ለዓለም ዓቀፍ ተቋማት ለማሳወቅ መሰብሰባቸዉንም አመልክተዋል። ከሰልፉ አስተባባሪዎች አንዱ መሆናቸዉን የገለፁልትን አቶ ዉሂብ የሺጥላን ስለሰልፉ ዓላማ ለጀርመን ድምጽ ራድዮ እንደሚከተለው አስረድተዋል:: ያድምጡት:-
[jwplayer mediaid=”39896″]

The post ኢትዮጵያውያኑ በጄኔቫ ሰላማዊ ሰልፍ አደረጉ appeared first on Zehabesha Amharic.

(ሰበር ዘገባ) የአፍሪካ ሰብአዊና የህዝቦች መብት ኮሚሽን በሕዝበ ሙስሊሙ ኮሚቴዎች ላይ ለተፈጸሙት ኢሰብአዊ የመብት ጥሰቶች ምላሽ እንዲሰጡ ማሳሰቢያ ደብዳቤ ላከ

$
0
0

Muslim in ethiopia
ሰበር ዜና BBN ሁሉም መስማት ያለበት ሰበር ዘገባ
የአፍሪካ ሰብአዊና የህዝቦች መብት ኮሚሽን የህዝበ ሙስሊሙን ኮሚቴዎች በማስመልከት ለኢትዪጲያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማሪያም ደሳለኝ ለተፈጸሙት ኢሰብአዊ የመብት ጥሰቶች ምላሽ እንዲሰጡ ማሳሰቢያ ደብዳቤ ላከ:: ኮሚሽኑ የጻፈውን ደብዳቤ አስመልክቶ ዶክተር አባድር ኢብራሂምን በማነጋገር ሰበር ዘገባ አሰናድተናል:-

[jwplayer mediaid=”39903″]

The post (ሰበር ዘገባ) የአፍሪካ ሰብአዊና የህዝቦች መብት ኮሚሽን በሕዝበ ሙስሊሙ ኮሚቴዎች ላይ ለተፈጸሙት ኢሰብአዊ የመብት ጥሰቶች ምላሽ እንዲሰጡ ማሳሰቢያ ደብዳቤ ላከ appeared first on Zehabesha Amharic.

ትርትር …. –ከሥርጉተ ሥላሴ

$
0
0

 

ከሥርጉተ ሥላሴ 21.03.2015 /ሲወዘርላንድ – ዙሪክ/

እኔ እላላሁ እንዲህ —- ዓለም „ሰው“ ለሚለው ቃል የሚመጥን፣ አቅም ያለው ድርጊትም ትርጉምም የላትም። ፍቅር ግን አለው።

ጠፋብኝ – መንደሩ

የብትንድር  – ግብሩ፤

ንክንኩ – ዛለእግሩ

ንክንፋስ – ምግባሩ

ትርትር ሆነ – በትሩ።

ከሥርጉተ ሥላሴ 02.023.2014 (ሲዊዘርላንድ - ዙሪክ)

ከሥርጉተ ሥላሴ 02.023.2014 (ሲዊዘርላንድ – ዙሪክ)

እኮ ስለምን ይለፍ እንሰጠዋለን?! እኮ ለምን ይፈቅድለታል? ምን ለማትረፍ? እያዘንኩ ልጀምረው። እኛ በእኛ ላይ ወይነናል። እኛ በእኛ ላይ ሸፍተናል። እኛ በእኛ ላይ ጥቃት እዬፈጸምን – ይመስለኛል። እኮ ለምን? ምን ለማትረፍ? ሃዘኑ እያርመጠመጠኝ ልቀጥለው – እስቲ። ዘሃ ግራው የጠፋበት ዘመን ….

ወያኔ አሸንፎናል ወይንስ አላሸነፈንም? ወያኔ በመንፈሳችን ላይ ጫና መፍጠር ችሏል ወይንስ አልቻለም? እኛስ የመንፈሳችን ስደት ወደ ወያኔያዊ ማንፌስቱ አድርገነዋልን ወይንስ ነፃ ወጥተናል? ዳኛው ህሊናችን ይበይንበት።

አሁን ለእኔ የዲ/ዳንኤል „የአገው ብሄረሰብ አባልነት ወይንም የትዳር አጋሩ ‚ትግሬነት‘“ ምን ይፈይድልኛል ለእኔ ጉዳዬ ነውን?“ በነገራችን ላይ የአገው ማህበረሰብ በኢትዮጵያ ሥልጣኔ ጉልህና ደማቅ ድርሻ የነበረው፤ ግን አቅም ያለው ዕውቅና ያልተሰጠው፤ ብዙም ያልተባለለት ነው። ሌላው የማንዲጎ ጎንደር ተወልዶ ማደግ ምንስ ዕሴት አለው? እራፊ የቀረች መሬት አንድ አረም በቀለባት ተብሎ መከራ ማዬት። የመጣው ሁሉ እንደ ጥንቸል ቤተ – ሙከራ መሆኑ መፈጸሚያ አልበቃ ብሎ ብተውት ምን አለ ጎንደርን ባዕቱ እኮ ህማማት ላይ ነው። ስለምንስ ብሩኩ ቡቃያ የበቀለበት ዬባለቅኔው! ዬቴዲ እትብት የተቀበረበት አልተጠቀሰም። አስፈላጊ ከሆነ ለንጽጽርም ይረዳ ነበር – አረም አብቃዩና ፍሬ ዘለቁ። ይገርም ነው። የአቶ ኤርምያስ ግማሽ ኦሮሞነትና አማራነት ምን ጠቃሚ ጠረን አለው?“ ወይንም የትናንት በሥርዓትና በሀገር ደረጃ የተከወነ ዛሬም ያለ ኢትዮጵያን የማጥቃት የውጭ ዝንቅ – ገብ ሂደት ከእኛ ጋር ተዋልደው፣ ተጋብተው፣ ተዛምድው ያሉ ወገኖች እዬነቀሱ „የዚህኛው የዛኛው ብሄረሰብ ሃይማኖት ነገድ አባል አይሁድ ምንትስ ማለትስ ምን አመጣው?“ ለዛሬ ወይንስ ለነገ በረከት ይሆናልን? ዛሬም እዬተሰደድን፤ ዛሬም ጥገኝነት እዬጠዬቅን፤ ዛሬም እርዳታ እዬጠዬቅን፤ ዛሬም ከውጭ ሀገር ዜጎች ጋር እዬተጋባን፤ ልጆች እዬወለድን ትናንት እንዲህና እንዲህ ነበሩ በስተጀርባ እከሌ የሚባል ሀገር ነበር ማለቱ ይገባልን? ነገም እኮ ኢትዮጵያ ተለይታ ደሴት ሀገር ልትሆን አትችልም። አስፈላጊው የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ከመላው ዓለም ጋር ጠንክሮ ቀጣይ ነው።

ህም! ለነገ ደግሞ ስደተኞችን ለይቶ መተንተኑስ … ክቡሩን የሥጋ – ወደሙ ጋብቻ ከማፈናቀል አንፃርስ ይህ ዝንባሌ  ሃይማኖታዊ ነውን? „ትግሬ“ የትዳር አጋሩ የሆነ ሁሉ በሚፈጽመው የራሱ አሉታዊ ሆነ አዎንታዊ ተግባር ባለቤቱ እያለ ሌላ መንጠላጠያ ሳቢያ መፈለጉ ምን አስፈለገ? ስለምን በምክንያቱ ላይ አናተኩርም? ለዚህም ነው መፍትሄ አመንጭነታችን ታቱ የሚለው። የሚነካካ ነገር ይፈለጋል። የሚወገዝ ነገር ይፈለጋል። ነገ ደግሞ በዚህ ጎሳዊ ማንፌስቶ ተገደው በጠበንጃ ታፍነው የዕለት ኑራቸውን የሚገፉት እዬተነጠሉ ስደት ይታጭላቸዋል። መልካም ነገሮችም አብረው ይናዳሉ – ጥናት አልባ በሆነ ሁኔታ። የሀገር ሃብትነቱ ይዘላል። ለዚህ ከሆነ የነፃነት ራህቡ … ቁርጭምምጭሚቱ ውልቅ ይሆናል። ዛሬም እኮ መስዋዕት የሚከፍሉ ወገኖቻችን አሉበት። በእግር ብረት ሥር ሆነው ስለነፃነት ግንባራቸውን የሚሰጡ – ማገዶዎች አሉበት። በሌላ በኩልም ዬአካላቸውን ካቴና ችለው ኃላፊነት ወስደውም ቤተሰቦቻቸውን የሚያስተዳደሩ፤ ዱላውንም – መፈንከቱንም ግልምጫውንም የወያኔን የቻሉ። ዓይን እያዬ ጆሮም እዬሰማ …. ህ!

ብቻ ለእኔ ዜሮ ሲደምር ዜሮ ወይንም ዜሮ ሲባዛ በዜሮ ሆኖ ነው ያገኘሁት። የሚጠቅመው ለምሳሌ፤  ሥርጉተ በተሰማራችበት፤ ወይንም ኃላፊነት ወስዳ በምታራምደው – እምነት ወይንም የፖለቲካ መስመር፤ ያጠፋቸውን ነገር ነቅሶ በማውጣት፤ በትኖ በመተንተን እሷኑ እራሷን ሞግቶ ማሸነፍ፤ ወይንም እድትታረም ማደረግ ነው እንጂ ሥርጉተ ያደገችበት ማህበረሰብ ወይንም ነገድ አብሮ መወቃት – መታጨድ የተገባ አይደለም። እኔ ላጠፋሁት – ለበደልኩት – ላባከንኩት – ለተሻማሁት ጊዜ ተወቃሿ እኔ ብቻ እንጂ ሌላ ቦታ ስደት መሄድ አያስፈልግም።  „ትግሬነት፤ ኦሮሞነት፤ አገውነት፤ አማራነት፤ ጎጃሜነት፤ ጉራጌነት፤ ሃድያነት፣ እስራኤላዊነት ወዘተ – ወዘተ“ የወል መጠሪያ ነው። በዛ ብሄረሰብ ስንት መልካም ሰዎች፤ ስንት ደጎች፤ ስንት አብነቶች ስንትስ የአደራ ናሙና ዜጎች አሉን? እልፍ ናቸው …

በዛ የማህበረሰብ ማዕቀፍ ስንት አንቱዎች፤ ስንት ሊቀ – ሊቃናት፣ ስንት ቅዱሳን አሉ? እልፎች። …. የተጸዎዖ ስም እኮ የወጣበት ምክንያት እኔን እንዲገልጽ ሆኖ ነው። የወል ሥምም እንዲሁ። ….. የወሉን ሥነ – ሞራል፣ ሥነ – ምግባር ሥነ —- ኑሮ፤ ሥነ – ታሪክ እንዲገልጽ ነው። በአንድ ማሳ አረም ይበቅላል። ፍሬ የሚሰጥም እጽዋትም ይበቅላል። አረሙ ከማደጉ በፊት ዘር እንዳያበላሽ ተነጥሎል ይነቀላል። ፍሬ ዘለቁ ደግሞ እድገቱ እንዳይደናቀፍ ተመጣጣኝ አዬርና ህልው የሚያድርጉ ነገሮች ይሟሉለታል። አሁን እኛ እያደረግን ያለው ግን እንደዛ አይደለም። ሁሉንም አረም እያደረግነው ነው። ትውልድን ለማተካካት ድርሻን በዚህ መልክ መከወን ሰባራ መንገድ ነው። ማንዘርዘሪያ ዬት ይገዛ ይሆን?! ይህ ማለት ግን በዳይም – ተባዳይም፤ የበለጠ እጁን ተጠቃሚ የለም ማለት አይደለም። ከጎሳ ፓሊሲ የሚጠበቁት አሳሮች ሁሉ እስከፈለጋቸው ድረስ፤ በረዶው ሁሉ እስኪበቃው አድቅቆናል ወረራውም – ደቁሶናል። ህልማችን በመሰሉ አይጓዝ ነው ብልሃቱ። ተሽሎ መገኘት የሚባል ብሂል አለ ….

የሆነ ሆኖ „ዛሬ የአማራ ወጣቶች እራሳችን መቻል እንችላለን። ስለዚህ እንገንጠል“ የሚል ጥያቄ እንዳነሱ አንብቤያለሁ። ብዕሯ መከፋቷንም አብራ ጨምራ ግልጻለች። እኔም በተደሞ ነበር ያነበብኩት። እንዲሁም በዚህ ዙሪያ ልንሠራበት የሚገባውን ተግባር እያወጣሁ እያወረድኩ እያለ፤ ቀጣይ ጹሑፍ በተከታታይ ወጣ። ዘር ቆጠራው ቀጠለ። ዝንቅንቅ ያለ- ጭብጡም የተቦጫጨረ – ጉድ። „አይሁድ፣ አገው ወዘተ ወዘተ .. ምንትሶ ቅብጥርሶ“ ምን ያድርጉ እነዚህ ወጣቶች!? ወያኔ በፓሊሲ ደረጃ ጎሳዊ ሶሻሊስትን ንድፈ ሃሳብ ፀንሶ – ወልዶ – አሳድጎ – እዬበተነ እኛ ደግሞ በራሳችን መንፈስ የወያኔ ሃርነት ትግራይን ማንፌስቶ ፍለጋ ስደት ፈቃጅ እንሆንለታለን። እያንዳንዷ የዚህ መሰል ስንጥርና ስንጠቅ ሂደት በኢትዮጵያዊነት ላይ ጫና እዬፈጠረ ስለመሆኑ ከልብ ማሰብ ያስፈልጋል። አንዳንድ ወገኖችን ስታወያዩ ተቆርቋሪነታቸው በሁለመናነት ታያላችሁ። ከዛ – ከዛማ ደስ ብሏችሁ አብራችሁ ስትወያዩ መጨረሻ ላይ መዳራሻቸው ከጎሳቸው ላይ ይሆናል። ስለምን? እኛም አብረን በጎጥ፣ በመንደር ዶክተሪን እንዲህ ብልዩነት መስመር ተመስጠን እዬሠራንበት ስለሆነ። ማርክ ቢሰጥ … ውስጣችን ስለ መውደቁ ማወቅ ቀላል ነው። ለዚህም ነው የወያኔ ሃርነት ትግራይ ማንፌስቶ ጥቃት በሰነዘረባቸው ላይ ተባደግ ዕይታ የሚኖረን፤ አርበኛ በላይነሽን የሚያደንቅ ርዕዮትን አይጨምርም፤ ርዕዮትን የሚል ኦልባና ሊሊሳን አያክልም፤ ኦልባና የሚል አንዱአለምን አያካትም፤ አንዱአለም የሚል አቡበከርን ይዘላል፤ አቡበከር የሚለው አብርሃምን ይተዋል፤ አብርሃም የሚለው አንዳርጋቸውን ይሰርዛል ወዘተ .. ወዘተ ። ቃል የማውጣት አቅም ያንሳል። መርምሩት – ወገኖቼ በትህትህና፤ አቅማችን ዋጥ የሚያደርገውን አሳማውን ዝንባሌ ….

ይህም ብቻ አይደለም በተገኘው አጋጣሚ ክፍተት የሚፈጥሩ ነገሮች መደፈን ሲጋባቸው – ይሰፋሉ።  „ሊቃውንተ ቤተክርስትያን እኔን ሲያስተምሩ „ነብዬ መሃመድ“ ብሎ መጥራት ወንጀል ነው ብለው አልነበረም። ይልቁንም ማዕድ ላይ እያሉ „‘አላህ አክብር‘ ሲታወጅ፤ እኛ ማዕድ ላይ ሆነን አነሱ ግን ፈጣሪያችን ያመሰግናሉ ይሉ ነበር – በአድናቆት፤ ዝናብ ሲኮርፍ እባካችሁ ለእነሱ ንገሩ ድዋ – ያድርጉ፤ እኛም ምህላ ለሁለት ሰባት እናደርጋለን ሲሉ‘ የዓለም ሊቃውንት 100 ድንቅ ካሏቸው የሥነጹሑፍ ምርቶች ውስጥ ነብዬ መሐመድ አንዱ ናቸው ሲሉ ነበር ያነበብነው“ እንዲህ ሁሉም ነገር መጫሪያ ፈላጊ ሆኖ ቋፍ ላይ ባለበት፤ ሆድ በባሳው ወቅት፤ በግልም በጋራ ዕንባን አምጦ፤ አልቅሶ ውሎ በሚያድርበት የጨለመ – ምዕራፍ ላይ ሆነን እንዲህ ባሉ ጠመዝማዛ የአረም ቅንጦቶች መጓዙ ዛሬንም አያበረክትም። ነገንም አያሰመርቅም። የትናንት አደራንም አያሰነበትም። ተከታይም – አያገኝም። አንድ መምህር ለትምህርቱ አጋዢ ማነጻጸሪያ ወይንም መንተራሻ ቢያስፈልገው መንቀሳቀስ እንዳይችል እስር እኮ እዬተበዬነበት ነው – ህም! ሥምም ማዕቀብ – ድንበር ተጣለበት። ወዮ ነፃነት! በለስ ቢቀናሽ ሥንት የቤት ሥራ እንዳለብሽ እስኪ መትሪው —-

እኛም እኮ መሃመድ የሚባሉ ብዙ ደሞች አሉን እኮ። መሃመድ በሚል ሥያሜ የሚጠሩ የነገ ሀገር ተረካቢ ልጆች አሉን። ወገኖቼ „መሃመድ“ የሚባል ጓደኛ፤ የሥራ ባልደረባ፤ ባለ ሱቅ፤ ጎረቤት ወዳጅ ቢኖራችሁ ሥሙን ስትጠሩ በጥቅሻ ሊሆን ይሆን?! ምን አይነት አሲዳዊ ፍሰት እንደሆነ ለእኔ ግራና ወልጋዳ ነው። ግብጽ ላይ እኮ የቅዱስ አባታችን የአቡነ ተ/ሃይማኖት በክብርና በሞገስ መታሰቢያ አለ። http://en.wikipedia.org/wiki/Tekle_Haymanot። በሀገረ ግብጽ በገዳማት ያሉ ደናግል ሆኑ ማህበረ ምዕመናኑ መጠሪያም እንደ ሀገራቸው የአጠራር ዘይቤ ሲሆንም ቋንቋውም እንዲሁ። ዘልቀን ብንገባበት ያነንም እንወነጅል ይሆን? የትኛውም ዓለም ቅዱስ ጊዮርጊስ መታሰቢያ ብቻ ሳይሆን እልፎች ይጠሩበታል። … እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሰምራ ስለምን ሃጢያተኛ በዛ? ለሚለው ዲያቢሎስ ስለሚያስታቸው ነውና ስለምን ከዲያቢሎስ ጋር እርቅ አታደርግም ብላ አምላኳን ፈጣሪያዋን ስለመጠዬቋ ከታምሯ ላይ አለ። የእሷ ጭንቀት ለኢትዮጵውያን ብቻ አልነበረም፤ ለዓለም እንጂ። … ቅዱሳን ሀገር የላቸውም፤ የትም ቦታ በዬትኛውም ሁኔታ ሊፈጠሩ ሊላኩ ይቻላሉ።

እንዲህ መላ ተቋማት ኢትዮጵያዊነትን የሚያውጁ በመንፈስም በአካልም ጦር በተመዘዘባቸው ወቅት „ወደ ማንነት ማዬት“ አምራጭ የለሽ መፍትሄ ሆኖ ሳለ፤ የቁርሾ ጉድፍ መበተን በፍጹም ሁኔታ ከትውልዱ ድርሻ ውጪ ነው – ለእኔ። እርግጥ የበለጠውን ጉዳት የሚያውቁት የዬአካባቢው ተወላጆች ስለሆኑ፤ ለመረጃ ልውውጥ ካልሆነ በስተቀር ለነገ የኢትዮጵያዊነት አቅም መቅኖ ግን የግልሰቡን ጎሳ ወይንም ባዕት እዬነጠሉ ማቅረብ፤ ተጠያቂም ለማደረግ ማስላት እጥፍ ድርብርብርብ ኪሳራ ነው። የዚህን የእኛ ትውልድ ዋንኛ የተልዕኮም ዕጣም ሆነ አቅጣጫም ቅርጭጭታም፤ ቀጫጫም ያደርገዋል – ባይ ናት ሥርጉተ – ሥላሴ።

ሰው በማንነቱ፣ በእሱነቱ፣ ከውስጡ ነፃነት እንዲሰማው ያስፈልጋል። ሲተችም፣ ሲጽፍም ነፃ ሆኖ መፃፍ የሚችለው በዚህ መንፈስ ሲሆን ብቻ እንጂ ገና ከዚህ አካባቢ እትብቴ ስለተቀበረ፤ ወይንም ሃይማኖቴ ይህ ስለሆነ ወይንም ነገዴ ይህ ስለሆነ፤ ወይንም የትዳር አጋሬ እንዲህ ስለሆነች ብሎ ስጋት ሊኖርበት አይገባም። ቀጥ ብሎ ለመቆም በራሱ የተማመነ፤ ማንነት ካለ እራሱን ገልጦ ውስጡን ማሳዬት ይቻላል። ውስጡን ማዬት ከተቻለ የጎሸውን ለማጥራት፤ እንክርዳድና ግርዱን መለዬት ብቻም ሳይሆን ጤናማና አዎንታዊ መንገድ ለመደልደልም ያስችላል። የተጎዳውንም አይዞህ ከጎንህ ነን ለማለት ይረዳል። ይህን እኛው ከነፈግነው ግን የድብብቆሽ ጨዋታ ይሆናል። የድብብቆሽ ጨዋታ ደግሞ ራዕዩን የድቡሽት ቤት ያደርገዋል፤ ርህራሄ – የለውምና። ከሁሉ በላይ ለወያኔ ሃርነት ትግራይ ማንፌስቶ በፈቃድ እጃችን ሰጥተናል ማለት ነው። ተወረናል። አቅምም አይኖርም የጎሳ ማንፌስቶን የመተቸት፤ የማውገዝና የመታገል። ነገም ወጮፎው ያዬለበት ዳመናማ ነው።

በአንድ ሥርዓት ውስጥ እልፎች ሠርቶ በማደር መኖር ግድ ይላቸዋል። ሌላም ሃላፊነት አለባቸው። እኛ ትተነው የመጣነውን ትውልድን የመተካት። ከዚህ ውጪ አማራጭ የለም። ስደቱም ቢሆን የአንድ ሀገር ህዝብ እንዳለ ሊሰደድ ከቶውን አይችልም። ጫካ ልግባ ቢልም እንደዚሁ። እኛ ደግሞ አንድ የነፃነት አርበኛ እስረኛ ቤተሰብ አብልተን ለማሳደር የምንችል አይደለንም። እንኳንስ ለእልፍ አለንልህ በማለት ለኑሮው መደጎም። ቀላሏን በወር አንድ ብር በዓመት በነፍስ ወከፍ 12 ብር እንደዬአለንበት ሀገር ማዋጣት እንኳን የምንፈቅድ አይደለንም። በእጃችን አለን የምንላት ቤሳ ሳንቲም የለንም። አቅም ያለው እራሱን በራሱ የሚያስተዳደር ተቋም ለዘር – የለንም። እንኳንስ ከዚህ የላቁ ነገሮችን ለመከወን። ፕሮጀክቱን ለመዘርጋት ቢታሰብም እንኳን፤ ፕሮጀክቱ ከመፈጠሩ በፊት ለራዕዩ ቀብረ – ሥርዓት ይታወጃል። /እራሴ ሞክሬ አይቸዋለሁ/  10 ሺህ ወገን በወር አንድ ብር ቢያወጣ 10 ሺህ ይሆናል በዓመት ደግሞ 120ሺህ …. ይሆን ነበር። ከሁሉ በላይ መንፈስን ወጥ አድርጎ የመግራት፤ አቅሙም አንቱ ነበር ተጨማሪ የኃይል አምንጭነቱም ጉልላት ይሆን ነበር። ሌሎችም ዕምቅ ትርፎች አሉበት ምህረት እርቅ ተስፋ ፍቅር ወዘተ … ለማንኛውም መድረስ አለመቻል ነው መጠነ ሰፊው ህዝብ ተጎጂ ሆኖ ግን ሰጥ ለጥ ብሎ እዬተገዛ ያለው። መድረስ አንችልማ? ቅልብጭ ያለው እውነት ቁምነገርም ይሄው ነው። ሀገራችን ኢትዮጵያ ላይ ቁልጭ ያለ ባርነት ነው ያለው። ዴሞክራሲ ከባርነት ነፃ ለወጡ ሀገሮች ነው። „ እዬዬም ሲደላ ነው።“ የኛው ግን ከጎጥ አገዛዝ ባርነት ገና አልወጣነም። በዚህ ሁለመናው እራስ ከእግር በሆነ ሁኔታ ላይ ሁነን ተጨማሪ ችግር ለዛውም ጥላቻ- ንቀት – ዘር በጣሽ መስመር ስንቀጣጥል ወይንም ስናመርት ውልን እናድራለን። — ምግለት!

ለመሆኑ አዲስ ሥርዓት ተሳክቶ ቢመሠረት ከሥራአቱ ጋር የሠራህ እዬተባለ ደግሞ ሌላ የስደት መንገድ፣ የመከራ ዘመን ልናጭለት ይሆን – ለዚህ መከረኛ ህዝብ? ህ! ዛሬ ሥልጣን ላይ ያለው የትግራይ ወያኔ ሃርነት ማንፌስቶ ነው። ነገ ይህ ማንፌስቶ አመድ ቢሆን፤ በዚህ ሥያሜ ሥር የነበሩ በሥርዓቱ ውስጥ ሠርተው ለማደር እንደ ሌሎች ይገደዱ የነበሩ የነገዱ አባሎች ወገኖቻችን ከእነሱ ጋር የተገባ፤ የተዋለደ ወገን አብሮ በነቂስ የበቀል መሻሪያ ሊሆን ነውን?! ሃራም ጋብቻ፤ ሃራም ጉርብትና፤ ሃራም አበልጅነት ሊባል ነውን? የጋራችን ልጆች ደግሞ እኮ አሉ። ለማን ነው ድካሙ?! ለቀጣዩ ትውልድ አይደለንም? ልጅነት እኮ የአንድ ነጠላ ቤተሰብ ብቻ አይደለም። ኃላፊነቱ የማህበረስብ ነው። እርክክብ አለ – የትውልድ። እንዲህ ያለ የተጋጋጠ ወይንም ጠረኑ የተነነ – ብዕር ለእኔ አረም የዘራ፣ አረም የሚያመርት፤ አረም የሆነ መንፈስ ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያዊነቱን ወዶ ስደት የላከ ነው። እራሱን አጥቷል በፈቃዱ። „ተቆርቋሪነት“ ትልቅ ተልዕኮ አለው። እጅ – ለእጅ፤ ደም – ለደም፤ ሥጋ – ለሥጋ፤ የሚያያዝባቸው ሊቃናተ – ሁነቶች እረቂቃን ናቸው።

እንጃ! እንዴትና እንዴት ይሆን እምናስበው? ከቱግታ ወጥተን ተግ ላይ እንስከን፤ ኢትዮጵያዊነት በዕውን በውስጣችን ካለ፤ እንዲሁም ያ ክቡር ሰንደቅዓላማ በወያኔ ሃርነት ትግራይ ማንፌስቶ ህግ ስለታሰረበት ወገን፤ — የለበሰው፣ ሰንደቁን ያፈቀረ ምክንያት ተፈልጎ ግዞት መላኩ እያገላበጠ መንፈሳችን – ከቀቀለው። እባካችሁን እራሳችን ‚እራሳችን‘ እንዲቀማው አንፍቀድለት?!!!

ወደ ራሳችን እንመለስ – በአክብሮት። ወደ ክብራችን እንመለስ – በዘንካታ ትህትና፤ ወደ ውስጣችን እንይ – በጀርጋዳ ቅንነት፤ ወደ ሥነ – ትውፊታዊ ህይወታችን እናስተውል – ከልባችን። የውበታችን ረቂቅነት ከልባችን ይግባ፣ ከደማችን ጋር ይመሳጠር – ያውጋም። ግልቢያ – ለፈረስ ነው፤ ስግረትም – ለወንዝ፤ በረራም – ለወፍ፤ የሰው ልጅ አላምጦ መዋጥ አለበት። „አደራ ለዛውም – የሀገር አደራ፤ አደራ ለዛውም – የዜግነት አደራ፤ አደራ ለዛውም የአኩሪ ታሪክ ባላቤትነት መለያነት – የነፃነት አደራ አለብን፤ አደራ ትውልድን ገንብቶ የመተካት ውድ አደራ አለብን። አደራ በመሆን የከበረ የፍቅር ልዑቅ አደራ አለብን“ ለዚህ እንማስን። የጠላትን ጥቃትን የሚቋቋም ሙሉ አኃታዊ ሥነ ምግባርን አምጠን እንውለደው። የጥቃታችን መሠረተ ፍሬ ነገር የጎጥ ዶክተሪን ነውና።

የትም ሀገር የተሰደደ ወይንም ሊሰደድ ያሰበ፤ ወይንም በትምህርት – በጋብቻ፤ ውጪ የሚወጣ ሁሉ መጀመሪያ ፎርሙን የሚሞላው „ኢትዮጵያዊ“ ብሎ ነው። ወያኔ የፈጠረውም ይሁን እኛ እያመጣን ያለው ልጥፍ ልሙጥ ጉድ ለውጭ ሀገር ዜጎች እራሱ ባዕድ ነው። የሚገርመው በዚህ ማንነት ውስጥ ኑሮ ከተደላደለ በኋላ የተገለበጠ እራስን ያልሰጠ መሽሎክ ይታያል። እሱን ህሊና ይዳኘው። ነገም ቢሆን ኢትዮጵያ የሚለው ሥያሜ ይጠፋል ብሎ ማሰብ መሽቶ አይነጋም ማለት ነው። ወይንም አህጉራት ሁሉም ሰባቱ ውቅያኖስ ይሆናሉ ብሎ ማለም ነው። የዕውነት ፍልቀቱ ዳርቻ የለውም። ኢትዮጵያዊነት ዕድሜውን መገደብ አይቻልም። ዘላቂ ነውና … ። የጎሳ ራዕይ በራሱ ጊዜ በመዳህኒዓለም ጥበብ ከስሟል። በዬትም ዓለም ከእንግዲህ እንደበፊቱ ቁልምጫ የለም።

ለማንኛውም መለመድ ያለበት መንገድ ለዛሬም ለነገም፤ የትኛውም ወገኔ እኔ ባጠፋሁት፣ በፈጸምኩት ስህተት ብቻ ሳይሆን፤ ስህተት ነው ብሎ ባሰበው ወይንም በሚመስለው ወይንም ስህተት ነው በሚለው ቢፈልግ ይክተፈኝ፤ ይተርትረኝ፤ ይፍለጠኝ፤ በመዶሻ ይቀጥቅጠኝ። ከቻልኩ ሙግቴን አቀርባለሁ፤ ከናቅሁት ደግሞ እተወዋለሁ፤ ነገር ግን ዕትብቴ የተቀበረበት ክ/ሀገር ሆነ ነገዴ ወይንም የሃይማኖቴን ዶግማ ግን መንካት የለበትም። በፍጹም። ትዳሬና አካሌም። ደግሞ ነፃነት የዘር ሀረግ ቆጠራ ቀመር አይደለም። ነፃነት ያደገና የሰለጠነ – ሰው የመሆን፤ እንደ ሰው ለመኖር ፈቃዱን ሰው የመስጠትም ሆነ የመንሳት መብት እንዴለለው የሚገልጽ ልዩ ክስተታዊ የእኩልነት አምክንዮ ነው። ነፃነት በጭነት አይተረጎምም። ጓዘ ቀላል ነው።  ….

በመጨረሻ እምለው ኢትዮጵያ ሀገራችን የአድምታ ሚስጢር ልዑላን ዲታ ናት – ተርፎም ይናኛል። ንባቡን፣ ትርጉሙን፤ ማመሳጠሩን ዓራት ዓይናማዎች አሉበት። ክህነተ ሥልጣን የመስጠትም የመነሳትም አቅም ያለው ሃይማኖታዊ ዶግማ በማስፈጸም ከአቨው ነው። ለነገሩ ሥልጣነ ክህነት ሰውኛም አይደለም። „ካልተሠራበት እሳት ሆኖ ያቃጥላል“ ይላሉ – አቨው። ጠያቂውም መዳህኒተአለም ነው፤ እንደ ሥራው ይላል መጸሐፉም። ባለቤቱ „ቅብዕ – ሥልጣኑን“ ቢያረክሰው እንኳን „ተመሥጥሮ ክብሩ አለ“ ይላሉ – አቨው። ስለዚህም „አትዳፈሩት!“ ብለው በአፅኽኖት ይመክራሉ። ለነገሩ እኔ „እኔን“ ሳከብረው ሌላውም እኔን ያከብረኛል። እኔ ሌላውን ሳከብረው ከሌላው ጋር ያሉ መንፈሶች ሁሉ እኔን ያከብሩኛል። ስጥለው ክብሬን የትም ደግሞ ሁሉም የክብረት መንፈስ ይሸሸኛል።

እህ! ሌላስ ያደግነበት ማህበረሰብ እኮ ታላቆችን ወንዶች ጋሼ፣ አይዋ፤ እያያ፤ ጥላዬ፣ ጋሻዬ ብለን አክብርን አቆላምጠን አልበረንም የምንጠራው፤ ሴቶችን እትዬ፣ አቫዬ፣ እቴ-ወለላዬ፣ እታታ፣ እታለም፤ እቴዋ፤ እቴ-አባባ፤ እቴ-አንጀቴ፤ እቴ-ማሬ አልነበረም? ብልህ አዋቂዎችን፤ ማር፣ ቀኝ ጌታ፤ የኔታ፣ ብላቴ፣ ጌታ፣ አለቃ አልነበርንም፤ እንኳንስ ዬሥርዓተ – ቤተክርስትያናት ዓዕማዳተ – ሃውልተ – ሚስጢራት ያለበት „ዲቁና“ ወይንም „ነብይነት“። እንደ ወርዳችን እና ቁመታችን ልክ ቢኖረን መልካም ነው። ልቅነት የእኛ አልነበረም። ጎንደሬም ሲተርት „ልክን ማወቅ ከልክ ያደርሳል“ ይላል። ልብ ይስጠን አምላካችን። ከእኛ በመንፈስ በላቀ ጥንካሬና ጽናት ሆነ፤ በማገዶነት የተሻለውን የሚያደርጉት ግን ያልበሉትን ዕዳ እንዲከፍሉ የተገደዱትን አዲስ የትውልዱ – የዘመኑ ባለቤቶች /ግርድ – ድቃቂ – እንክርዳድ/ እዬዛራን አናምሳቸው – እባካችሁን /// //////  መሸቢያ ሳምንት – ለእኔዎቹ። ውዶቼ ዘሃበሻ! እግዚአብሄር ይስጥልኝ።

ለእኔስ ሰው መሆኔ ብቻ ይበቃኛል።

ኢትዮጵያዊነት አሸናፊ ቀለማም ማንነት!

እግዚአብሄር ይስጥልኝ።

The post ትርትር …. – ከሥርጉተ ሥላሴ appeared first on Zehabesha Amharic.

9 ፓርቲዎች በ15 ከተሞች ሰላማዊ ሰልፍ ጠሩ

$
0
0

Photo File

Photo File


9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ለህዝባዊ ሰልፍ የመረጣቸውን 15 ከተሞች ይፋ አደረገ
• ሰልፉ መጋቢት 20/2007 ዓ.ም ይደረጋል

የሰማያዊ ፓርቲ ልሳን የሆነው ነገረ ኢትዮጵያ ጋዜጣ እንደዘገበው የ9ኙ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ትብብር ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍና የምርጫ ቅስቀሳ ለማካሄድ የመረጣቸውን 15 ከተሞች ይፋ አደረገ፡፡ ትብብሩ በተመሳሳይ ሰዓት በ15 ዋና ዋና የሀገሪቱ ከተሞች ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ ለማድረግ ቀደም ብሎ አሳውቆ እንደነበር ይታወሳል፡፡

በዚህ መሰረት የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር መጋቢት 20/2007 ዓ.ም በተመሳሳይ ሰዓት ሰልፉን የሚያካሂድባቸው ከተሞች የሚከተሉት ሆነዋል፡፡ እነዚህም አዳማ፣ ባህር ዳር፣ አርባ ምንጭ፣ ደብረ ታቦር፣ ሐዋሳ፣ ጅማ፣ ደብረ ብርሃን፣ ወልቂጤ፣ አሰበ ተፈሪ (ጭሮ)፣ ወላይታ ሶዶ፣ ደሴ፣ ዱራሜ፣ ደብረ ማርቆስ እና ሆሳዕና ናቸው፡፡

ትብብሩ ‹‹መጋቢት 20 በፍጹም አይቀርም›› በሚል ለህዝቡ የድጋፍ ሰልፍ ጥሪ ያደረገ ሲሆን፣ ከተሞቹ የተመረጡትም ፓርቲዎቹ በየአካባቢዎች ባቀረቡት እጩ ብዛት መሰረት እንደሆነ ገልጹዋል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ ደግሞ በዋና ከተማዋ አዲስ አበባ የሚደረገው የድጋፍ ሰልፍ በተመረጡት ከተሞች የሚደረገው ሰልፍ በተከናወነ በሳምንቱ ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

The post 9 ፓርቲዎች በ15 ከተሞች ሰላማዊ ሰልፍ ጠሩ appeared first on Zehabesha Amharic.

“የህዝብ ወኪሎችን በነጻ ከማሰናበት ያነሰ ብይን አንቀበልም!”–ድምፃችን ይሰማ

$
0
0

muslim dim
ታላቅ የትዊተር ዘመቻ – መጋቢት 21/2007
ቅዳሜ መጋቢት 12/2007

ካሁን ቀደም ስኬታማ መሆን የቻለ እና ለሁለት ሰዓታት የቆየ የትዊተር ዘመቻ ማድረጋችን ይታወሳል፡፡ በወቅቱ የተጠቀምነው ሐሽታግም የዓለም አቀፍ ሚዲያዎችን ትኩረት ማግኘት ችሎ ነበር፡፡ ሁለተኛው የትዊትር ዘመቻችን የሚካሄደው መጋቢት 21/2007 ሲሆን ዋነኛ ጭብጡ ‹‹የህዝብ ወኪሎችን በነጻ ከማሰናበት ያነሰ ብይን አንቀበልም!›› የተሰኘ ነው፡፡

እንደሚታወቀው በድምጻችን መርጠን የላክናቸው ወኪሎቻችን በመንግስት የሐሰት ክስ ሲንገላቱ ቆይተው በያዝነው ወር መጨረሻ መጋቢት 30/2007 ለብይን ተቀጥረዋል፡፡ ዛሬ ላይ በወኪሎቻችን መታሰር የታሰርነውም ሆነ የተከሰስነው እኛው የወከልናቸው ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች መሆናችን ከጅምሩም አንስቶ ሲረጋገጥ የቆየ እውነታ ነው፡፡ ሊካድ በማይችልበት ደረጃ ላይም ደርሷል፡፡ በመጋቢት 30 በወኪሎቻችን ላይ የሚሰጠው ብይንም በእኛ በኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ላይ የሚሰጥ ብይን መሆኑ እርግጥ ነው፡፡ ለዚህ እውነታ ታሪካዊ ምስክር ለመሆን የፊታችን መጋቢት 21/2007 ሁለተኛውን የትዊተር ዘመቻችንን እናደርጋለን።

የዘመቻው ዝርዝር አፈጻጸሞች እና መርሃ ግብሮች ከፊታችን ባሉት ቀናት የሚገለጹ ሲሆን እስከዚያው ግን አስፈላጊውን ዝግጅት ማድረግ እና በቂ የቅስቀሳ ስራ መስራት እጅግ አስፈላጊ ነው፡፡ ዘመቻውን ከወዲሁ ላልሰሙት ሁሉ በማሰማትም የተሳታፊዎችን ቁጥር ማሳደግ ይገባናል፡፡ ለዚህ የቅስቀሳ ስራ እንዲያግዝ የፌስቡክ ፕሮፋይል ፎቶ እና የከቨር ፎቶ ተዘጋጅቶ በገጻችን ጥቅም ላይ የዋለ ሲሆን ሁላችንም የፕሮፋይሉን ፎቶ እንደፕሮፋይል፣ የከቨሩን ፎቶ ደግሞ ለግል የፌስቡክ ግድግዳችን በከቨር ፎቶነት በመጠቀም ላልሰሙት ሁሉ ለማሰማት ጥረት እናደርግ ዘንድ በአላህ ስም እንጠይቃለን!

‹‹የህዝብ ወኪሎችን በነጻ ከማሰናበት ያነሰ ብይን አንቀበልም!››
ትግላችን እስከድል ደጃፎች በአላህ ፈቃድ ይቀጥላል!
ድምጻችን ይሰማ!
አላሁ አክበር

The post “የህዝብ ወኪሎችን በነጻ ከማሰናበት ያነሰ ብይን አንቀበልም!” – ድምፃችን ይሰማ appeared first on Zehabesha Amharic.

በጋሞ ጎፋ በቅስቀሳ ላይ የነበሩ የሰማያዊ አባላት ታሰሩ

$
0
0

ethiopia-blue-party-300x164በጋሞ ጎፋ ዞን ኮንሶ ወረዳ በምርጫ ቅስቀሳ ላይ የነበሩ ስምንት የሰማያዊ ፓርቲ አባላት መታሰራቸውን የዞኑ የፓርቲው አስተባባሪ ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡

አባላቱ ከመጋቢት 9/2007 ዓ.ም ጀምሮ በእስር ላይ እንደሚገኙ ታውቋል፡፡ በእስር ላይ የሚገኙት ስምንቱ ሰዎች የሚከተሉት ናቸው፡-
1. ካርታ ካርኪ
2. ኩንሳ ካፒሊ
3. ታሪኩ አንካሶ
4. ካያና ካላታ
5. ገላዬ ካይድራ
6. ካርታ ሀይቶ
7. ኩንሱ ካምባ
8. ሆዳ ሆልጥሽ

ናቸው፡፡

The post በጋሞ ጎፋ በቅስቀሳ ላይ የነበሩ የሰማያዊ አባላት ታሰሩ appeared first on Zehabesha Amharic.


ቤተክርስቲያናችን ውስጥ የመከፋፈልና የማፍረስ እንቅስቃሴ ለማስቆም)የተጻፈ ግልጽ ደብዳቤ

$
0
0

orth

 

መጋቢት 23 ቀን 567 ዓም/ MARCH 21, 2015 በጋዜጠኛ አቶ አዲሱ አበበ መሪነት በቤተ ክርስቲያናችን ላይ የተነገረው የሐሰት ወሬና ከቤተ ክርስቲያኗ ውጭ የሚካሄዱ ስብሰባዎች)ጉዳይ በዓለም ሁሉ መነዛቱ የታወቀ ነው። ቤተ ክርስቲያናችን ግን ለዚህ አፍራሽ ድርጊት አስተያየት ከመስጠት ተቆጥባ ቆይታለች። አሁን ግን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ አስተያየቷን እንድትሰጥ ተገዳለች። ምክንያቱም ውሸት ሲደጋገም እውነት ይመስላል፣ ሰሚውንም ያደናግራል።

እመሠክርላታልሁ ከሚሉላት ከኦርቶዶክስዊት ተዋኅዶ ቤተ ክርስቲያን እምነት ጋር፤ እውነትን ለመመሥከር እፍጨረጨርለታለሁ ከሚሉለት ጋዜጠኝነት ጋር ሁኔታዎች ሲጋጭቦት እናያለን። እንዲሁም፤ ታማኝንትንና ተቀባይነትን በሰፊው እንዲለግሦት ከሚማጸኑት ሕዝብዎና እውነት እንዲነገርባችው ከተዘረጉት ሕዝባዊ መገናኛዎች ጋር መጋጨትዎንም እናስተውላለን። ስለዚህ የዚህ ግልጽ ደብዳቤ ዓላማ ከዚህ ተግባሮ እንዲቆጠቡ ለማሳሰብና በእርሶ አንደበት የተነገሩትን ስሕተቶች የሰሙ ሁሉ የራሳቸውን ፍርድ እንዲስጡ ለማስገንዘብ ነው። –—[ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]—–

 

 

 

The post ቤተክርስቲያናችን ውስጥ የመከፋፈልና የማፍረስ እንቅስቃሴ ለማስቆም)የተጻፈ ግልጽ ደብዳቤ appeared first on Zehabesha Amharic.

የሳምንቱ አበይት ዜናዎችና ዳሰሳ በዴሲሶን ሬዲዮ ይቀርብላቸዋል

$
0
0

aseac

የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ትግል ‹‹መብቴን ካላከበርክ እኔም….. !›› ወደሚልበት የትግል ምዕራፍ መሸጋገሩ 

ጋዜጠኛ ተመስገን በማረሚያ ቤት ህክምና መከልከሉ 

የተቃዋሚ ፓርቲዎች አመራሮች የእምነት ክህደት ቃላቸውን ‹ሰጡ›

የደቡብ ሱዳን መንግስት የኢትዮጵያ አማጽያንን ይደግፋል ተባለ

……..

አርበኞች ግንቦት 7 ተቀላቀሉን፤ ካልሆነም በያላችሁት ተደራጁ!በሚል ለኢትዮጵያ ህዝብ ጥሪ

አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ፣ ከህወሓት ዘረኛ ፋሽስታዊ አገዛዝ ነፃ ለመውጣት የሚመኝ ኢትዮጵያዊ ሁሉ እንዲደራጅ ጥሪ ያቀረበ ሲሆን! እያንዳንዱ ነፃነት ፈላጊ ኢትዮጵያዊ ከሚያምነውና ከሚመስለው ወዳጁ ጋር ይቧደን፤ ቡድኑንም በሥርዓትና በሚስጢር ያደራጅ ብሏል በመግለጫው አክለውም
ከእንግዲህ “ምን እንሥራ፧ ትግሉን እንዴት እንርዳ?” እያሉ ለሚጠይቁ ወገኖቻችን በሙሉ መልሳችን “ከቻላችሁ ተቀላቀሉን፤ ካልሆነም በያላችሁት ተደራጁ” የሚል ነው ያሉ ሲሆን ድርጅት ኃይል ነው። መደራጀት በራሱ ትልቅ ሥራ ነው። ድርጅት ድርጅት የሚሆነው ደግሞ በሥርዓት ሲዋቀርና በሥነሥርዓት ሲመራ ነው። ስለሆነም ነፃነት ናፋቂ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሌላ አደራጅና አስተባባሪ እንዲመጣለት ሳይጠብቅ በራስ አነሳሽነት እንዲደራጅ ይህ ጥሪ ተላልፏል ብለዋል::

በመጨረሻም
በአርበኞች ግንቦት 7 እምነት የኢትዮጵያ ሕዝብ አስተባባሪና መመሪያ የሚጠብቅበት ጊዜ አልፏል። ህወሓት የዘረጋው የአፈና ሥርዓት የጠበቀ ትስስርና ቁጥጥር ያለው ድርጅት ማቆም እንዳይቻል አድርጓል። ስለሆነም ያለን አማራጭ ያለ በላይ አካል ትክክል ራሳቸውን በራሳቸው ማስተዳደር የሚችሉ ስብስቦችን በመላው የአገራችን ክፍሎች በአፋጣኝ ማደራጀት ነው። ይህንን ደግሞ ማድረግ ይቻላል።

ወቅቱ ህወሓትን ከጫንቃችን ላይ ለማውረድ የምንደራጅበት ነው። ድርጅት ኃይል ነው፤ አደራጅና አስተባባሪ ሳንጠብቅ በራስ ተነሳሽነት ዛሬውን እንደራጅ!የሚል ጥሪ አቅርባል::

የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ትግል ‹‹መብቴን ካላከበርክ እኔም….. !›› ወደሚልበት የትግል ምዕራፍ መሸጋገሩ ተገለፀ!

ለ 3 አመታት በተለያዩ የሰላማዊ ትግል ዘዴዎች መብቴን አክብሩ ሲል የቆየው ህዝበ ሙስሊም የህዝብን ድምፅ ለመስማት ፈቃደኛ ያልሆነው የሃገራችን መንግስት በቀጣይ የህዝብን ድምፅ ይሰማ ዘንድ ወደሚያስገድዱ ህዝባዊ እንቢተኝነት ትግሉ መሸጋገሩን ድምፃችን ይሰማ አስታውቋል፡፡

የአንድ መንግስት ህልውና  ህዝቡ ፍቃደኝነት ላይ የተንጠለጠለ ነው፡፡ያለው የድምፃችን ይሰማ መግለጫ ሕዝብ ሲመረውም ‹‹መብቴ ይከበርልኝ›› ከሚል ጩኸት ‹‹መብቴን ካላከበርክ እኔም….. !›› ወደሚል ዛቻ መሄዱ አይቀሬ ነው ብላል ይህን ጊዜ ሕዝቡ ‹‹ትብብር የመንፈግ ትግል ውስጥ ገባ›› ይባላል፡፡ ይህ ዓይነቱ ትግል ውጤታማ መሆኑ አይቀሬ እንደሆነ የዘርፉ ምሁራን አጽንኦት ሰጥተው ያስተምራሉ፡፡በማለት አክለውም

በጨዋ ደንብ እና በአንጸባራቂ ሰላማዊ ስነ ምግባር ለሶስት ዓመታት መብቱን ሲጠይቅ እና ሲታገል የቆየው ኢትዮጵያዊው ሙስሊም ‹‹መብቴ ይከበርልኝ›› ከሚል ያልተሰማ ጥያቄው ‹‹መብቴን ካላከበርክ እኔም….. !›› ወደሚልበት የትግል ምዕራፍ ላይ እነሆ ደርሰናል! ሰሞኑን ይህንኑ አስመልክቶ የምንለው ይኖራልና ሁላችንም ቃል የገባንበትን ትግል እስከድል ደጃፎች ለማድረስ ወገባችንን እናጥብቅ፤በማለት ጥሪ አቅርባል::

ጋዜጠኛ ተመስገን በማረሚያ ቤት ህክምና መከልከሉ ተነገረ

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ: በእስር በሚገኝበት የዝዋይ ማረሚያ ቤት: በጤና አገልግሎት እጦት እንደተቸገረ ሲፒጄ አስታወቀ. የጋዜጠኞች የመብት ተቆርቋሪው ቡድን ሲፒጄ : ባሳለፍነው ሳምንት ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው ከሆነ: ጋዜጠኛ ተመስገን በማረሚያ ቤት የጤና አገልግሎት እንዳያገኝ ስለተከለከለ: በሆድና በወገብ ህመም እየተሰቃየ እንደሆነ አመልክቷል.

ጥቅምት ላይ የሶስት አመታት እስር ተፈርዶበት: በዝዋይ ማረሚያ ቤት የሚገኘው ተመስገን ደሳለኝ :ከመታሰሩ ቀደም ብሎ በየሳምንቱ የህክምና ክትትል ያደርግ እንደነበረ የተገለጸ ሲሆን: አሁን ግን በእስር ቤቱ ባለስልጣናት: የህክምና አገልግሎት በመከልከሉ የተነሳ :በተለይ የጀርባ ህመሙ በመባባሱ: መሄድ እስከሚያቅተው እንደተቸገረ የሲፒጄ መግለጫ ይዘረዝራል.

የቀድሞው የፍትህ ጋዜጣ ባለቤት የነበረው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ: አመጽን የሚያነሳሱ የሀሰት ወሬዎችን በመጻፍ: እንዲሁም የሰዎችን መልካም ስም በማጉደፍ በሚሉ ወንጀሎች ተከሶ :የሶስት አመታት እስራት እንደተፈረደበት ይታወቃል.

ይሁን እንጂ የክሱን መዝገብ በሚገባ መገምገሙንና :ማጥናቱን የሚናገረው ሲፒጄ :ተመስገን ለእስር የተዳረገው :የተባሉትን ወንጀሎች ሰርቶ ሳይሆን :በሚያወጣቸው ጽሁፎች መንግስትን ደጋግሞ በመተቸቱ ነው ሲል: መንግስትን ይከሳል. እስር ቤት ከገባም በኋላ: የእስረኞችን አያያዝ በተመለከተ: አንድ ጽሁፍ ከዛው ሆኖ በመጻፉና በተለያዩ ሚዲያዎች በመታተሙ የተነሳ :በማረሚያው ባለስልጣናት ማንም ዘመድ ወዳጅና ቤተሰብ እንዳይጎበኘው ለወራት ተከልክሎ መቆየቱን ሲፒጄ :ይናገራል.

ድርጅቱ ማረሚያ ቤቱ በተመስገን ላይ የሚፈጽመውን የመብት ጥሰት ለማስቆም: ለኢፌድሪ ፍትህ ሚኒስቴር እንዲሁም አሜሪካ ላለው የኢትዮጵያ ኤምባሲ :በተደጋጋሚ ጊዜ በስልክና በኢሜል ጥያቄ ማቅረቡን ጠቅሶ :ይሁን እንጂ ከመንግስት በኩል ምንም አይነት ምላሽ እንዳልተሰጠው ተናግሯል.

በሀገሪቱ የጋዜጠኞች ይዞታ ላይ የራሱን ጥናት እንዳደረገ የሚገልጸው ሲፒጄ :መንግስት 17 ጋዜጠኞችን ማሰሩንና: ከ 30 የማያንሱ ደግሞ መሰደዳቸውን ይናገራል. የኢትዮጵያ መንግስት: ተቋሙ የሚያወጣቸውን ሪፖርቶችና ማሳሰቢያዎች ወደጎን በማለት: ይህን ጋዜጠኞችን የማፈን ተግባሩን እንደገፋበት የሚገልጸው ድርጅቱ :በተለይ ከመጪው የግንቦት ምርጫ በፊት : ብዙሀኑን ነጻ ሚዲያና ጋዜጠኞች የማፈን ተግባሩን ቀጥሎበታል ሲል መንግስትን ከሷል.

የተቃዋሚ ፓርቲዎች አመራሮች የእምነት ክህደት ቃላቸውን ‹ሰጡ›

በእነ ዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ :የሽብር ክስ የተመሰረተባቸው የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮችና :ሌሎች በተመሳሳይ መዝገቡ የተካተቱ ተከሳሾች: በተከሰሱበት ድርጊት ላይ የእምነት ክህደት ቃላቸውን ሰጡ፡፡

ሰማያዊ ፓርቲ፣ የአንድነት እና የዓረና ትግራይ አመራሮችን ጨምሮ 10 ተከሳሾች: መጋቢት 10/2007 ዓ.ም በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት  19ኛ ወንጀል ችሎት የቀረቡ ሲሆን : ተከሳሾች በቀረበባቸው ክስ ላይ: የእምነት ክህደት ቃላቸውን ሰጥተዋል፡፡ በዚህ መሰረት: ከአንደኛ ተከሳሽ ዘላለም ወርቃገኘሁ ጀምሮ፣ ‹‹በክሱ ላይ የተመለከተውን ድርጊት ፈጽመዋል ወይስ አልፈጸሙም?›› የሚል ተመሳሳይ ጥያቄ ለእያንዳንዳቸው የቀረበላቸው ሲሆን: ብዙዎቹ ተከሳሾች ምላሻቸውን በቀጥታ ለመስጠት አለመፈለጋቸውን አሳይተዋል፡፡

1ኛ ተከሳሽ ዘላለም ወርቃገኘሁ: ለቀረበለት ጥያቄ፣ ‹‹በአቃቤ ህግ እና በፖሊስ ተቀነባብሮ የቀረበብኝን ክስ በተመለከተ ለክሱ እውቅና ላለመስጠት ምንም አልልም፡፡ በክሱ ላይ አስተያየት በመስጠት: ለጸረ-ሽብር አዋጁ እውቅና መስጠት አልፈልግም›› የሚል መልስ በመስጠቱ: ፍርድ ቤቱ ክሱን ክዶ ቃል እንደሰጠ አድርጎ መዝግቦታል፡፡

2ኛ ተከሳሽ ሀብታሙ አያሌው በበኩሉ: ‹‹በክሱ ላይ የተመለከተውን ድርጊት እንዳልፈጸምኩ : እንኳን እኔ ከሳሾቼም በደንብ ያውቃሉ፡፡ ከሳሾቼ: እኔ ድርጊቱን የመፈጸም ፍላጎቱም ሀሳቡም እንደሌለኝ ያውቃሉ›› ብሏል፡፡

3ኛ ተከሳሽ ዳንኤል ሺበሽ ደግሞ፣ ‹‹እኔ ስለ ሽብር የሰማሁት ከአልቃይዳው መሪ ኦሳማ ቢላደን እና መለስ ዜናዊ ነው፡፡ እኔ አሸባሪ አይደለሁም፤ ሀሳቡም ሆነ ፍላጎቱም የለኝም፡፡ ባህሌና እምነቴም አይፈቅድልኝም›› ሲል ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል፡፡

 

4ኛ ተከሳሽ አብርሃ ደስታ ‹‹አሸባሪ ማለት የፖለቲካም ሆነ ሌላ ዓላማውን: ሰላማዊ ዜጎችን በማሸበር ለማስፈጸም የሚሰራ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ብቸኛው አሸባሪ ድርጅት ህወሓት/ኢህአዴግ ነው፡፡ እኔ ደግሞ የዚህ አሸባሪ ድርጅት ተቃዋሚ ነኝ›› በሚል ምላሽ ሲሰጥ

5ኛ ተከሳሽ የሺዋስ አሰፋ በበኩሉ፣ ‹‹በመጀመሪያ ለመጨረሻ ጊዜ ስለሆነ የምናገረው እንዳታቋርጡኝ አደራ እላለሁ፡፡ ክሱ ቅንብር ነው፡፡ ዳኞችም ህጉ የሰጣቸው ነጻነት አይታይባቸውም፡፡ ይህ 19ኛ ወንጀል ችሎት የጦር ችሎት ነው የሚመስለኝ፡፡ ስለሆነም የጦር ችሎት በሚመስል ችሎት እየተንገላታን ነው›› ሲል ተናግሯል፡፡ የሺዋስ በዳኞች በተደጋጋሚ ንግግሩ እንዲቅረጥ ተደርጓል፡፡ በመጨረሻም ክሱን ክዶ ቃል ሰጥቷል በሚል ተመዝገቦለታል፡፡

በአጠቃላይ ተከሳሾች ክሱ ላይ የተጠቀሰውን ድርጊት ክደው ቃል በመስጠታቸው አቃቤ ህግ ምስክሮችን እንዲያሰማ ለግንቦት 13፣ 14፣ 15/2007 ዓ.ም ለተከታታይ 3 ቀናት ምስክር እንዲሰማ ቀጠሮ ተሰጥቷል፡፡  በተየያያዘ ዜና

የዞን 9 ጦማሪያና ጋዜጠኞች በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት  ቀርበው ተጨማሪ የጊዜ ቀጠሮ እንደተሰጠባቸው ታውቃል

አቃቤ ሕግ በተከሻሾች ላይ ያቀረበው የኦዲዮ ሲዲ ማስረጃ እንዲደርሳቸው ባቀረቡት ጥያቄ ላይ ችሎቱ ብይኑን ስላልጨረሰ ለመጋቢት 15 ቀን 2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ የተሰጠባቸው…….

የደቡብ ሱዳን መንግስት የኢትዮጵያ አማጽያንን ይደግፋል ተባለ

በሳልቫኪር የሚመራው የደቡብ ሱዳን መንግስት ኢትዮጵያን የሚወጉ አማጽያንን እንደሚያደራጅና እንደሚደግፍ ተነገረ፡፡ ሱዳን ትሪብዩን የደቡብ ሱዳን አማጽያንን ጠቅሶ እንዳወራው ከሆነ የደቡብ ሱዳን መንግስት ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በገጠመው ቅያሜ ምላሽ ለመስጠት ሲል ኢትዮጵያን በጋምቤላ በኩል የሚወጉ አማጽያንን እያስታጠቀ ይልካል ሲል አውርቷል፡፡

አስተማማኝ መረጃ ማግኘታቸውን የገለጹት የደበብ ሱዳን አማጺያን መሪ የሪክ ማቻር ቃል አቀባይ ጋትዴት ዳክ ለሱዳን ትሪብዩን ሲናገሩ የደቡብ ሱዳን መንግስት በኢትዮጵያ ላይ አማጽያንን እንደሚመለምል፣ እንደሚያሰለጥንና እያስታጠቀ ወደጋምቤላ ክልል እንደሚልክ ገልጸዋል፡፡

ይህ በደቡብ ሱዳን መንግስት በመደራጀትና ወደኢትዮጵያ ጋምቤላ ገብቶ ጥቃት ለመሰንዘር በመንቀሳቀስ ላይ ያለ ሀይል በደርግ ዘመን የጋምቤላ አካባቢ አስተዳደር በነበሩትና እአአ በ1991 አገዛዙ ሲወድቅ ወደውጪ በሸሹት ሰው በቶዋት ፓል ቻይ መሪነት የሚንቀሳቀስ እንደሆነ አማጺያኑ ለሱዳን ትሪብዩን ተናግረዋል፡፡

ቶዋት ፓል ቻይ በጋምቤላ አገዛዝ ዘመናቸው ያኔ በጆን ጋራንግ ለሚመራውና አሁን ላይ በሳልቫኪር እየተመራ ደቡብ ሱዳንን ለሚያስተዳድረው የደቡብ ሱዳን ነጻ አውጪ ጦር ድጋፍ በመስጠት የሚታወቁ ሰው ሲሆኑ ኋላ ለይ በስደት ዘመናቸውም ሳልቫ የተመቻቸ ሀላፊነትና መጠጊያ ሰጥተዋቸው እንደቆዩ ተወስቷል፡፡

The post የሳምንቱ አበይት ዜናዎችና ዳሰሳ በዴሲሶን ሬዲዮ ይቀርብላቸዋል appeared first on Zehabesha Amharic.

የሕወሓት ሰዎች በትግራይ ክልል ለፓርላማ ከመድረክ ዕጩዎች ጋር ይፎካከራሉ

$
0
0

አርከበ ዕቁባይ አይወዳደሩም

299d05d703691f17d2f061a06bf1f93c_Lዘንድሮ ለአምስተኛ ጊዜ በሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ የሕወሓት/ኢሕአዴግ ከፍተኛ አመራሮች ከሆኑት መካከል አቶ ዓባይ ፀሐዬ፣ ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም፣ ዶ/ር አድኃነ ኃይለ አድኃናና አቶ ጌታቸው ረዳ በትግራይ ክልል በተለያዩ ዞኖች ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከመድረክ ዕጩዎች ጋር እንደሚወዳደሩ ለማወቅ ተችሏል፡፡

ከድርጅቱና ከብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው፣ በዘንድሮ አምስተኛ ዙር ምርጫ አቶ ዓባይ ፀሐዬ በስለኽለኻ (ምዕራብ ዞን)፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም በብዘት (ምሥራቅ ዞን)፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ልዩ አማካሪ አቶ ጌታቸው ረዳ በአላማጣ (ደቡብ ዞን) ሕወሓት/ኢሕአዴግን ወክለው ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከአረና ትግራይ (መድረክ) ተወካዮች ጋር ይፎካከራሉ፡፡

በሽሬ እንዳ ሥላሴ የአረና ትግራይ ለሉዓላዊነት ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ተካልኝ ታደሰ አቶ ዓባይ ፀሐዬን፣ በአዲስ አበባ የአረና ፓርቲ ተጠሪ አቶ ኪዳነ አመነ ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖምን፣ እንዲሁም የአረና የደቡብ ትግራይ አካባቢ ተጠሪ አቶ ንጉሥ አብርሃ ደግሞ አቶ ጌታቸው ረዳን መድረክን ወክለው እንደሚፎካከሩ ለማወቅ ተችሏል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም የቀድሞው የትምህርት ሚኒስትር ዶ/ር አድኃና ኃይለ አድኃና በማይጨው ከተማ ሕወሓት/ኢሕአዴግን ወክለው እንደሚወዳደሩ ለማወቅ ተችሏል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ የአረና ትግራይ (መድረክ) ማዕከላዊ ኮሚቴ አባልና የምሥራቅ ዞን አስተባባሪ የሆኑት መምህር ፍፁም ግርሙ በአዲግራት ከተማ የኢሕአዴግ ዕጩ የሆኑትን ዶ/ር መብራህቱ መለስን ይፎካከራሉ፡፡ እንዲሁም የአረና ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አምዶም ገብረ ሥላሴ በሀገረ ሰላም (ተምቤን አበዓዲ) የምርጫ ጣቢያ የሕወሓት/ኢሕአዴግ ተወካይ የሆኑትን አቶ ብርሃኑ ገብረ ማርያምን ይፎካከራሉ፡፡

በተያያዘ ዜና ከቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሕልፈት በኋላ የሕወሓት ሊቀመንበር የሆኑት የትግራይ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ዓባይ ወልዱ፣ ያለምንም ተቀናቃኝ በአክሱም አካባቢ ለክልል ምክር ቤት ለምርጫ ይቀርባሉ፡፡

መድረክን ወክለው ባለፈው አራተኛ ዙር ምርጫ አቶ ዓባይን የተፎካከሩት ወንድማቸው አቶ አውዓሎም ወልዱ እንደማይወዳደሩ ለማወቅ ተችሏል፡፡ እንዲሁም ባለፈው ምርጫ መድረክን ወክለው በአደዋ ከአቶ መለስ ጋር ተፎካክረው የነበሩት የአረና ትግራይ ፓርቲ መሥራች ወ/ት አረጋሽ አዳነ በመቐለ ከተማ ለክልል ምክር ቤት የሚወዳደሩ ሲሆን፣ በእሳቸው ቦታ አቶ ተክላይ ታደለ ከሕወሓት ምክትል ሊቀመንበር ከዶ/ር ደብረ ጽዮን ጋር እንደሚፎካከሩ ለማወቅ ተችሏል፡፡

ቀደም ሲል ከሕወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴና ከሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ የተሰናበቱት ዶ/ር አርከበ ዕቁባይ፣ በተለያዩ ማኅበራዊ ድረ ገጾችና በተለያዩ ሕዝባዊ ስብሰባዎች ወደ ፓርቲው ከፍተኛ አመራር እንዲመለሱ ጥያቄ ቀርቦላቸው ነበር ቢባልም፣ በዘንድሮ ምርጫ እንደማይወዳደሩ ለማወቅ ተችሏል፡፡

አረና ትግራይ ለሉዓላዊነት ፓርቲ በትግራይ ክልል ከሚገኙት ሕወሓት ሙሉ ለሙሉ ከሚወዳደርባቸው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 38 ወንበሮች መካከል በሃያ ዘጠኙ ይፎካከራል፡፡ እንዲሁም ለክልል ምክር ቤት 74 ተወዳዳሪዎች ማቅረቡ ታውቋል፡፡

ፓርቲው አባል የሆነበት መድረክን በመወከልም በአዲስ አበባ ከተማ ሦስት ተፎካካሪዎችን (አቶ ጎይተኦም ፀጋይ፣ አቶ ካህሳይ ዘገየና አቶ አብረሃ ካሳን) ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በዕጩነት ማቅረቡን ለማወቅ ተችሏል፡፡

Source:: Ethiopian Reporter

The post የሕወሓት ሰዎች በትግራይ ክልል ለፓርላማ ከመድረክ ዕጩዎች ጋር ይፎካከራሉ appeared first on Zehabesha Amharic.

የኢትዮጵያ ተዋጊ ጄቶች፤ የኤርትራን የወርቅ ማዕድን ማውጫ፤ ሚሻን በቦንብ ደበደቡ ሲል የሕወሓት መንግስት ገለጸ

$
0
0

የኤርትራ ወርቅ ማዕድን የአየር ጥቃት ደረሰበት
ከየኤርትራ ኢኮኖሚ ዋልታ እንደሆነ የሚነገርለት፣ በማይ እዳጋ የሚገኘው የሚሻዕ ወርቅ ማዕድን ካምፓኒ በአየር መደብደቡን የሕወሓት መንግስት አስታወቀ::

የሕወሓት መንግስት እንዳለው የአየር ጥቃቱን ያደረሰው በወያኔ የሚመራው ወታደራዊ ኃይል ሲሆን፤ በጥቃቱም የወርቅ ማውጫው ክፉኛ መጎዳቱን ገልጿል:: የኤርትራ መንግስት በዚህ ጉዳይ ያለው ነገር የለም:: ዘ-ሐበሻ ጉዳዩን ተከታትላ ትዘግባለች::

ኤርትራ ከዚህ የማዕድን ማውጫ በአመት እስከ 400 ሚሊዮን ዶላር ታገኛለች። የዚህ ማዕድን ስፍራ መመታት፤ የአገሪቱን የኢኮኖሚ ኃይል በእጅጉ ይጎዳዋል።

The post የኢትዮጵያ ተዋጊ ጄቶች፤ የኤርትራን የወርቅ ማዕድን ማውጫ፤ ሚሻን በቦንብ ደበደቡ ሲል የሕወሓት መንግስት ገለጸ appeared first on Zehabesha Amharic.

ማነው አሸባሪ የትግሪይ ነጻ አውጪ ግንባር? ወይስ ኢትዮጵያዊው ግንቦት ሰባት? –ከሳሙኤል አሊ

$
0
0

samuelየትግራይ ነጻ አውጪ  ኢትዮጵያን መምራት ከጀመረ 24 አመታትን አስቆጥራል። በዚህ የጭለማ ዘመን ኢትዮጵያዊው በወያኔ  ጭፍን ጥላቻ  እንደ ጭቃ እየተረገጠ መገዛት ከጀመረ አመታቶች ተቆጠሩ። እነዚህ ጨለምተኞች በአፋቸው እውነት የማይናገሩ ልቦናቸው ቂም ያረገዘ፣  አእምሮአቸው በክፋት የተመረዘ፣  የአስተሳሰብ ደሃ፣ ዘረኛ እና ዘረኝነትን በሰው ልቦና የሚዘሩ፣ በኢትዮጵያ ሕዝብ የተጠሉ የደደቢት በቆልቶች ናቸው::

ኢትዮጵያን  ከTPLF  አፓርታይድ አገዛዝ ነፃ ለማውጣት የሚታገለው ግንቦት 7 አሸባሪ ነውን? እስቲ በከፊል እንመልከት፡-

ወያኔ ያሰመረው መስመር አለ ያም መስመር ኢትዮጵያን የሚያጠፋ መስመር ነው። ህዝብን ከህዝብ ጋር፣ ዘርን ከ ዘር ጋር፣ ጎሳን ከጎሳ ጋር፣ የሚያጋጭ መስመር ነው። ኢትዮጵያኑ  ሀይማኖታቸውን በነጻነት እንዳያምኑ  የሃይማኖት አባቶችን እንዳይመርጡ በነጻነት ፈጣርያቸውን እንዳያመልኩ  የሚያደርግ መስመር ነው።  ዜጎች ሲኖሩበት ከነበረው ቄያቸው ካለበቂ ካሳ የተወሰኑ አካላትን ለመጥቀም ሲባል ብቻ ለልማት በሚል ሰበብ ማፈናቀል እና የጎዳና ተዳዳሪ ተመጽዋች የሚያደርግ መስመር ነው። ነፍስ ጡር እህቶቻችንን አጥንታቸው እስኪሰበር የሚቀጠቅጥ መስመር …መብታቸውን የጠየቁ የነጻነት ታጋዮችን  ወደ ጭለማ ቤት የሚወረውር መስመር… ኸረ ስንቱ ተጠቅሶ ይቻላል…።’

ይሄን የባርነት እና  የሽብርተኝነት አገዛዝ  አይኑን በጥቁር ጨርቅ ሸፍኖ ምንም እንዳልተፈጠረ እራሱን አሳምኖ የሚቀበል ካለ ወያኔ ከደገሰው ድግስ መመገብ ይችላል ወያኔ ከካበው የእንቧይ ካብ መሰቀል ይችላል።

ከመስመሩ  ውጪ የሆኑትን ሁሉ ተለጣፊ ታርጋ እየተስጣቸው አንተ ግንቦት 7 ነህ፣ አንተ ኦነግ ነህ፣ አንት ኦብነግ፣ እያሉ የፖለቲካ እንቅስቃሲያቸውን ለማጥፋት ይጠቀሙበታል። እውን ግን በዚህ በማፈን ስራ እና  በማጠልሽት ድርጊታቸው የኢትዮጵያን ህዝብ ሊያቆሙት ይችላሉን?

የወያኔው መሪ በአንድ ወቅት  ጠንካራ ተቃዋሚ የለም ብለው በተናገሩ ማግስት መሬት  ያንቀጠቀጠ  ደጋፍ  ያገኙት ቅንጅቶች ኢትዮጵያዊነት ማለት ምን ማለት እንደሆነ  በምርጫ በካርድ አሳያቸው ይሄን ያዩ ጊዜ ወደ ሚኒሊክ ቤተመንግስት በታንክ እንጂ በካርድ መች ገባን በማለት የተሰረቀው ድምጻችን ይመለስል ብለው አደባባይ በወጡ ሰላማዊ ዜጎቻችን ላይ  ግንባራቸው ላይ 11 ቁጥር ታፔላ ባስገጠሙ አጋዚ  ወታደሮች በጠራራ ጸሃይ በጥይት ተቆሉ የንጹሃን ደም በየጎዳናው ፈሰሰ  ያን ጌዜ ነበር የኢትዮጵያ ህዝብ በመረጣቸው አካላት ሊመራ  እንደማይችል በመረዳታቸው   ይህን መሰዋትነት ለመክፈል  የተዘጋጁ በጥቂት ግዜ  ውስጥ  ግንቦት 7፣ አርበኞች ግንባር እንዲሁም ሌሎች  ብረት አንስተው ወደ ጫካ ተመሙ። ይሄም ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ የመጣው የህዝብ ቁጣ  ሲያዩ ውስጣቸው ተሸበረ ስራቸውንም  ስለሚያውቁ  መርዘኛ ተግባራቸውን  ማሰራጨት ጀምረዋል።

ወያኔ በመማር ማስተማር ሂደት ውስጥ ግልጽ እና እውቀት ያለው እንዲሁም  ሰለ አገር አሳቢውን በተሰመረላቸው መስመር  ላይ ይገቡ ዘንድ ግድ ይላቸዋል። በዚህ መስመር ያልገቡትን በሙሉ  ስም ይለጥፍላቸዋል አንተ ከኢሳት እና ከ ግንቦት7 ጋር   ግኑኝነት አለህ  የሻብያ ተላላኪ ነህ  አልያም እነዚህ ድርጅቶች ትረዳለህ በሚል ሰበብ ክስ ይቀርብባቸውና   ወደ እስር ቤት ይወረወራሉ።

ወያኔ በፖለቲካና ፖለቲከኞች ዙርያ በወያኔ አዙሪት ውስጥ እንዲዞሩ ይጠየቃሉ  በዚህ አዙሪት ውስጥ ገብተው አራሳቸውን አዙረው የኢትዮጵያን ህዝብ አዙሪት ውስጥ እንዲከቱ ይደረጋሉ የለም የወያኔ ፖለቲካ አዙሪት ኢትዮጵያን አጥፊ ነው ስርዓቱም የበሰበሰ የዘረኝነት ፖለቲካ የሚከተል ነው ይህ የዘር ፖለቲካ ደግሞ እንደ ርዋንዳ  ከመጨራረስ እና ከመተላለቅ ውጭ ለኢትዮጵያ የሚጠቅማት ነገር የለም። ይህ የዘር ፖለቲካ በአንድ አገር የሁሉንም መብት ባለማክበር እልቂትን የሚያመጣ  እንጂ እድገትና ፍቅርን አይሰጠንም። ይሄ  የዘር ፖለቲካ ለመሰረተውም ለሚከተለውም እንዲሁም ለሁሉም ህብረተሰብ በመጠፋፋት የፀፀት ታሪክ እንጂ የወደፊታን ኢትዮጵያን አይጠቅማትም ብለው የፖለቲካ ፓርቲ መስርተው አቋማቸውን በግልጽ አሳውቀው እየተንቀሳቀሱ ባሉት ፓለቲከኞች ላይ በ 24 አመት ውስጥ ምንም ያልተለወጠውን የወደቀ እና የተናቀ  ስራውን በመስራት የአሸባሪነት ስም ሰጥቶ  እስር ቤቱን የንጹሃን ዜጎች ማሰቃያ ካደረገው አመታቶችን ቆጥሩ።

የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ አንድ ሆነን የምንሳበት ጊዜው አሁን ነው። ከአሁን በኋላ ወያኔ እያሰረን እየገደለን እንዲኖር ለደቂቃም ቢሆን መፍቀድ የለብንም። ዘርን ከዘር፣ ሐይማኖትን ከሐይማኖት፣ አጋጭቶ  እራሱ ጥግ ሆኖ ሊስቅ የፈለገን  በኢትዮጵያን ምድር ላይ የበቀለ ወያኔ የተባለውን ባንዳ  ጠላት በጋራ ሆነን እናሰወግድ።  ለነጻነት  እና  ለፍትህ  ለእኩለነት የሚታገለው የግንቦት7  መሪዎችን የምናውቃቸው አብረውን የነበሩ ሰለ ኢትዮጵያ  መጽአኢ ተስፋ  ቀን ከለሊት የሚተጉ  ሰለ  አንዲቷ ኢትዮጵያ ሲሉ መስዋት ለመሆን የተዘጋጁ መሆናቸውን ሁሉም የሚያውቀው ሃቅ ነው። ስለዚህ   የቻልን ወደዚህ የትግል ጎራ እንቀላል። ሁሉም በያለበት ለነጻነቱ ሲል ይደራጅ።  ገበሬውም ሞፈሩን፣ ተማሪውም ብዕሩን፣ አስተማሪውም ጠሜኔውን፣ ነጋዴውም ብሩን፣ ወታደሩም ብረቱን  ያንሳ።  የሐይማኖት ሰዎችም ጸሎታችሁን  ሰለ   ኢትዮጵያ  ብላቹህ በአንድነት አሰሙ  ኢትዮጵያን እና ህዝቧን የሚታደጋት አምላክ አላትና ። ለ24 አመት ኢትዮጵያን ሲያሸብር   የኖረውን ወያኔን እናጥፋ። ሞት  ለዘረኞች  እና  ለዘርዛሪዎች ይሆናል።

 

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር

 

ከሳሙኤል አሊ (ከኖርዌይ)

22.03.2015

samilost89@yahoo.com

 

The post ማነው አሸባሪ የትግሪይ ነጻ አውጪ ግንባር? ወይስ ኢትዮጵያዊው ግንቦት ሰባት? – ከሳሙኤል አሊ appeared first on Zehabesha Amharic.

ምረጫ ክርክር 2፡ “የፌዴራል ስርዓተ በኢትዮጵያ”-የግል ዕይታ –ግርማ ሠይፉ ማሩ

$
0
0

girmaseifu32@yahoo.com; www.girmaseifu.blogspot.com

ተከራካሪዎች፤

  • ካሳ ተክለብርሃን እና አባዱላ ገመዳ                       ኢህአዴግ
  • በኃይሉ ሸመክት እና ደረጀ ጣሰው                      “ድንኩ አንድነት”
  • ተሾመ ወልደሐዋሪያት እና ሰማቸውን ያልያዝኩት         አዛውንት መኢብን
  • ኤርሚያስ ባልከው እና ሰሙን ያልያዝኩት ወጣት             ኢዴፓ
  • አበባው መሃሪ እና አንድ ሰማቸውን ያልያዝኩት           አዛውንት መኢአድ
(ግርማ ሰይፉ)

(ግርማ ሰይፉ)

የሁለት ሺ ሰባት ምርጫ ክርክር ሁለተኛ ክፍል “የፌዴራል ስርዓተ በኢትዮጵያ” በሚል ነው፡፡ በዚህ ክርክር ዙሪያ ስናወራ አንድ ወዳጄ አንድ ቀልድ ቢጤ ነገረኝ፡፡ በዚሁ ቀልድ ብጀምረው ወደድኩ፡፡ በቅርቡ የእንግሊዝ፣ የአሜሪካ እና የኢትዮጵያ ምርጫ አስፈሚዎች ለልምድ ልውውጥ ተገናኝተው ነበር አሉ፡፡ የአንግሊዙ ተወካይ በቅድሚያ አሁን እኛ ምርጫ በብቃት አካሂደን በዚያው እለት ምርጫ ውጤት መግለፅ ችለናል ብለው የደረሱበትን ደረጃ ሲናገሩ፤ የአሜሪካው ተወካይ ደግሞ እኛ ደግሞ ውጤቱን በቀጥታ ማሰራጨት ችለናል ብለው ይናገራሉ፡፡ የኢትዮጵያ ተወካይ (ፕሮፌሰር መርጊያ በቃና ይሁኑ አቶ ነጋ ዱፊሳ አልተገለፀም) ይህ ምን ያስገርማል ብለው በኩራት በእኛ ሀገር ውጤቱ ከምርጫ በፊት ይታወቃል ብለው አረፉት፡፡ የዘንድሮ ምርጫ የዋንጫው ባለቤት የታወቀበት ውድድር መሆኑ ከግንዛቤ እንዲያዝ እኛም እንደ ህዘብ እንደተረዳን ቀልዱ ያሰረዳል ብዬ አምናለሁ፡፡

በዛሬው ክርክር በእውነቱ ያዘንኩት በክርክሩ ፓርቲያችውን ወክለው ለቀረቡት ለአቶ ካሳ ተክለ ብርሃን እና ለአቶ አባዱላ ገመዳ ነው፡፡ በረጅም ዓመት በትጥቅ ትግል እንዲሁመ 24 ዓመት በመንግሰትነት የፖለቲካ አመራር ሲሰጡ የነበሩ ሰዎች የዚህ ሁሉ “ድካም” እና መስዋዕትነት ውጤት ዛሬ ከጎናቸው ሆነው በደህንነት መስሪያ ቤት ፈቃድ ያገኙ፤ የኢትዮጵያ ህዝብ የደረሰበትን የፖለቲካ ደረጃ የማይመጥኑ የፓርቲ ወኪል ነን የሚሉ ሰዎች ጋር ያደረጉት ክርከር ነው፡፡ ማለት የፈለኩት ኢህአዴግ የዚህን ያህል የፖለቲካ ልምድ አለኝ እያለ ልኩ የዚህን ያህል የወረደ እንዲሆን በአንድነት እና በመኢአድ ፓርቲ ላይ ያደረገው ጣልቃ ገብነት ነው፡፡ እንደ እነርሱ አባባል ለሰማዕታት ክብር ለመስጠት የሚያስችል ደረጃ ዲሞክራሲውን ሊያደርሱት አልተቻላቸውም፡፡ ህወሃት ትግል ከጀመረበት ቢቆጠር ከአርባ ዓመት በላይ ተደክሞ የተደረሰው እዚህ መሆኑ አሳፋሪ ነው የሚል የግል እይታ አለኝ፡፡

ለማነኛውም ወደ ክርክሩ ዝርዝር ስንገባ ካለፈው በተቃራኒ መጥፎውን የክርክር ጀማሪነት የወሰዱት “ድንኩን አንድነት” ወክለው የተገኙት አንድነትን በማፍረስ ቀንደኛ ተዋናይ የነበረው ደረጀ ጣሰው እና በኃይሉ ሽመክት የሚባል አንድነት ውስጥ የማላውቀው ወጣት ነው፡፡ በኃይሉ ሽመክትን በእውነት የት ወረዳ የተደራጃ አባል እንደነበር አላውቅም፡፡ ለማነኛውም ሁሉንም የማወቅ ፍላጎትም ሁኔታም የለኝም፡፡ እርግጡ ግን ለክርክር ካዘጋጀናቸው ሰዎች ውስጥ አልነበረም፡፡ አንድነትን ወክለው እንዲከራከሩ በዝገጅት ላይ የነበሩት የአንድነትን ፕሮግራም ጠንቅቆ ማወቅ የግድ ስለሚል ነው፡፡ ለዚህ ዋነኛው ማሳያ “የኮሚሽነር ጄነራል” ትዕግስቱ አወሉ “ድንኩ አንድነት” ፓርቲ ፕሮግራም ለውጥ ካለደረገ በስተቀር የአንድነት የፌዴራሊዝም አማራጭ “ጂኦግራፊ መሰረት ያደረገ ፌዴራሊዝም” የሚል አይደለም፡፡ በኃይሉ ስለ ፌዴራሊዝም ጎግል ሲያደረግ ስራ በዝቶበት የአንድነትን የፌዴራሊዝም ግልፅ አማራጭ ለማቅረብ አልቻላም፡፡ የበሀይሉን ለአንድነት ፓርቲ እንግዳነት የሚያሳብቀው ሌላው አንድነት “ሀብታሙ ሰዩም” የሚባል እሰረኛ የሌለው መሆኑ ነው፡፡ ደረጀ ጣሰው ከዚህ አንፃር  ጥቁር እንግዳውን በሀይሉ ሸመክትን በመራጃ ማቀበል እንዲረዳው የሚጠበቅ አይመስለኝም፡፡ በክርክር አብሮት ስለተገኘ ምሽት ክለብ ወሰዶ እስክስታ/ዳንስ ሊጋብዘው ይችል ይሆናል፡፡ ሌላው የበሀይሉን እንግዳነት የሚያሳየው “ራዕያችን ዋንጫ ነው” የሚለው የቃላት ግድፈት ዋንጫውን እንደ ምርጫ ምልክት የመረጥን ሰዎች በዋንጫው ዙሪያ ያደረግነውን ዝርዝር ውይይት ስለአላገኙት ዋንጫው ከምርጫ ውድድር ምልክትነት አልፎ “ራዕይ” እሰከመሆን የሚደርስ የቃላት ግድፈት ውስጥ እንዲገባ አድርጎታል፡፡ ለማነኛም በኃይሉ ከፎረም የመጣ፣ በአንድነት ወጣቶች ውስጥ ራሱን የደበቀ የቀበሮ ባሕታዊ መሰለኝ፤ ለማነኛውም በሀይሉ ሊማር የሚችል ወጣት እንደሆነ ለመገንዘብ አልተቸገርኩም፡፡ አንድነትን ወክሎ ለክርክር ይመጥናል የሚባል ተከራካሪ አይደለም፡፡ ለ”ድንኩ አንድነት” ግን ከበቂ በላይ ነው፡፡ በሀይሉ የአንድነት አባል ከሆነ ወረዳውን እና የወርሃዊ ክፍያ የከፈለበትን ፌስ ቡክ ላይ ቢለጥፈው “ከፎረም” የመጣ ከሚለው ጥርጣሬ እተርፋለሁ፡፡

መኢብን በእርግጥ የመሳፍንት/መስፍን መኢብን ነው ወይ? ያስብላል፡፡ እኔ መሳፍንት/መስፍን የሚባል ግለሰብ የሚመራው ፓርቲ በሀገር ውስጥ ነዋሪ የሆኑ የኢትዮጵያን ሁኔታ የሚረዱ አባላት አሉ ብዬ አላምንም ነበር፡፡ ይህን ለማለት የሚያስደፍረኝ በግሉ የፈለገውን ከማለትና ከማድረግ አልፎ ተቃዋሚ ፓርቲዎችን በጠራራ ፀሃይ ከገዢዎች ጎን ተሰልፎ ሲዘልፍ ተው የሚለው አባል በፓርቲው ውስጥ መኖር አለበት ብዬ ስለማምን ነው፡፡ ለማነኛውም የመኢብን ተወካዮች በተደራጀ መልክም ባይሆን በዚህች ሀገር ያለውን ፌዴራሊዝም ዕፀፆች ለማሳየት ሙከራ አድርገዋል፡፡ ተከፋፍሎ የተሰጣቸው 19 ደቂቃ አንሶዋል ቢሉም በሁሉም ክፍሎች ግምሻ ላይ ሃሰብ አጥሮዋቸው ፈተና ውስጥ ሲገቡ ታዝበናል፡፡ ለማነኛውም ኢህአዴግ ከ24 ዓመት ወዲህ ያመጣው ኦሮሞ፣ ትግሬም፣ ሀዲያም፣ ወዘተ የሌለ መሆኑን በመግለፅ ይህ የኢህአዴግ የአፋዊ ፌዴራሊዝም ተቀባይነት የለውም ማለታቸው እውነት ነው፡፡ ይህ ግን በምንም መመዘኛ መኢብን የሚባል ፓርቲ ለምርጫ መቅረብ ያለበት ፓርቲ ነው ማለቴ አይደለም፡፡ ህዝብ ወክሎ ለምርጫ ለመቅረብ የሚያስችል የፓርቲ አቋም ያለው ፓርቲ ነው ብዬ ከምር ልወስደው አልችልም፡፡ የመሳፍንት ዓይነት ሰው የሚመራው ፓርቲ የፈለገ ጠንካራ ሰው ውስጡ ቢኖር የትም ሊደርስ አይችልም፡፡ እነዚህም ለክርክር የመጡ ሰዎች መሳፍንትን ያላስታገሱ እንኳን ሀገር፣ ቀበሌ ማስተዳደር የሚችሉ ሊሆኑ አይችሉም፡፡ መሳፍንት የሚመጥነው ኢህአዴግ ስለሆነ ከተቀበሉት ፎርም ሞልቶ እዚያው ቢገባ የሚል አስተያየት መሰጠት ስህተት አይመሰለኝም፡፡

በዚህ ክርክር እንደ ኢዴፓ ውጤታማ ክርክር ለመከራከር የሚያስችል መረጃ ያለው ፓርቲ በግሌ አልገምትም ነበር፡፡ ለዚህ አስተያየቴ መነሻ  የኢዴፓው ልደቱ አያሌው መፅሃፍ ለማጣቀሸ የሚሆን እንደሆነ ስለማውቅ ነው፡፡ ለክርክሩ የቀረቡት ወጣቶች ግን ከልምድም ሆነ ከዝግጅት ማነስ አዚህ ግባ የሚባል ክርክር ማድረግና ነጥብ ማስቆጠር አልቻሉም፡፡ የልደቱን መፅሃፍ እንደ ማጣቀሻ ሳይሆን እንደ ቅዱስ መፅሃፍ ነው የወዱት፡፡ አሁን በኢዴፓ ውስጥ ፊቱን እየለመድነው የመጣነው ወጣት ኤርሚያስ ባልከው ያባከናቸውን ጊዜዎች ለጓደኛው/ከይቅርታ ጋር ሰሙን አልያዝኩትም/ ቢተውለት የተሻለ ይሆን ነበር ብዬ እገምታለሁ፡፡ ለማነኛውም ኢህአዴጎች ለኢዴፓ ባላቸው ቅን ልቦና እና አሁን ለክርክር የቀረቡት ሰዎች ተናዳፊ ያለመሆን ካልሆነ በስተቀር ኤርሚያስ ባልከው በተደጋጋሚ የኦሮሚያ መገንጠል በሚል በቀጥታ ከልደቱ መፅሃፍ የወሰደውን ሃሰብ እንደወረዳ እያቀረበ ለጥቃት እራሱን ሲያጋልጥ ነበር፡፡ ሰሙን ያልያዝኩት የኢዴፓ ተከራካሪ ህገመንግሰት ለማሻሻል አስቸጋሪ መሆኑ ግልፅ ሆኖ እያለ አሁን ኢዴፓ ባቀረበው ዕጩም ሆነ በሌላ መስመር ሊያሳካው የማይችለውን የህገ መንግሰት ማሻሻል ጉዳይ አንስቶ ጊዜ ሲያባክን ነበር፡፡ የዚህ ክርክር ፋይዳ የሚኖረው ለምርጫ ሳይሆን ለእውቀት በሚደረግ ክርክር ቢሆን ነበር፡፡ የኢዴፓው ተከራካሪ ሊብራል ዲሞክራሲ በሚከተሉ ሀገሮች ያለ ፌዴራሊዝም ተፈትኖ የወደቀ በሚል በኢህአዴግ የቀረበውን መሰረተ ቢስ ክስ ተፈትኖ የወደቀ ሳይሆን ተፈትኖ ያለፈ መሆኑ በደንብ ለማስረዳት ሞክሮዋል፡፡ ፈተና ያላለፈው እንኳን 70 ዓመት 24 ዓመት በቅጡ መቆም ያቃተወ ግራ ዘመም ሀገሮች ውስጥ ያለው ፌዴራሊዝም በተለይም አምሳያ የሌለው አቶ ካሳ ተክለ ብርሃን ለዓለም ያበረከትነው ብለው የተመፃደቁበት ፌዴራሊዝም በእግሩ መቆም ያለመቻሉ ነው፡፡ የኢትዮጵያን ፌዴራሊዝም ልዩ እያሉ የሚያሞካሹ ምሁር ነን የሚሉ ብዙ ሰዎች እንዳሉ ይታወቃል፡፡ አቶ ካሳ ተክለብርሃንም ሆነ ድርጅታቸው ኢሀአዴግ ሁሌም የሚያሰቡትን የሚነግሯቸው ምሁራን ስለሚመርጡ ነው፡፡

በኢዴፓ እምነት አሁን ያሉት ክልሎች ስልጣን ያላቸው ፌዴራል መንግሰት አባላት ሳይሆኑ፣ የሰራ ድልድል የተደረገላቸው ምድብ ሰራተኞች መሆናቸው ትክክለኛ ምልከታ ነው፡፡ በእኔ ዕይታ ለዚህ ማሳያ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ርዕስ መስተዳደር ከነበሩት ከአቶ ያረጋል አይሽሹም የተሻለ ማሳያ የሚገኝ አይመስለኝም፡፡ ከእርሳቸውም ሌላ በተፈለገ ጊዜ ከክልል ርዕሰ መሰተዳደርነት ተነሰቶ መጥቶ ወደ ፌዴራል መንግሰት የሚመጡበት ሁኔታ በተደጋጋሚ የታየ ነው፡፡ የአሁኑ ጠቅላይ ሚኒሰትራችን በብቃት ማነስ በሚል ከደቡብ ክልል መምጣታቸው፣ እርሳቸውን በብቃት ይተካሉ የተባሉት አቶ ሸፈራው ሽጉጤ ከመለስ ዜናው ሞት በኋላ ከክልል ርዕሰ መስተዳድረነት መነሳት፣ የጋምቤላው ርዕስ መስተዳድር ተነስተው ፌዴራል መስሪያ ቤት ቢሾሙም አድብተው ስደት መምረጣቸው፣ የድሬዳዋ የዙር አመራር፣ የሀረሪ ሀደሬዎችን ማዕከል ያደረገው የመንግሰት አሰያየም፤ ወዘተ እየተመለከትን በምን መመዛኛ የአንድ ፌዴራል አካል የሆነ የክልል መንግሰታት ናቸው ብለን ተጨፍነን ልንሞኝ አንችልም፡፡ የኢዴፓዎች መፈክር በተሳሳተ መስመርም ሆነው – “ዛሬም ይቻላል” የሚል ነው፡፡

 

በዚህ ክርክር የመኢህአድ ተወካይ አቶ አበባው መሐሪ አንድ ሀቅ ተናግረዋል፡፡ ህዝቡን በዚህ ምርጫ ምረጡን እና እንዲህ እናደርጋለን ብለው እስከመጨረሻው ለማሳሳት አልሞከሩም፡፡ በስተመጨረሻም ቢሆን በግልፅ ያሉተ “ምረጡን እና ምክር ቤት ከገባን ወክለን እንከራከርላችኋለን” ነው፡፡ ለወጉም ቢሆን መንግሰት እንሆናለን አላሉም፡፡ በዚህ አባባላቸው የኢህአዴግን ቀጣይ መንግሰትነትን አምነው ተቀብለውታል፡፡ በክርክሩ ከአንድ ፖለቲከኛ በማይጠበቅ ደረጃ የሰሩት ስህተት እና አቶ አባዱላንም ያሳሳቱት “ህዝቡ በአሰር ብር እንዳይታለል” በሚል የሰጡት አስተያየት ነው፡፡ አቶ አበባው መሃሪ በምድር ላይ ያለውን ሀቅ ገዢው ፓርቲ በኢኮኖሚ ደካማ የሆኑተን ዜጎች በተለያየ መንገድ እንደሚያማልል ለመግለፅ ነው፡፡ ይህን ሀሳብ በቅጡ መግለፅ ካልቻሉ በዚህ ደረጃ ባይሉት ጥሩ ነበር፤ አቶ አባዱላም ይህን በዚሁ መንፈስ ከህዝብ ጋር ለማጋጨት ባይሞክሩ ጥሩ ነበር፡፡ ይህን የአቶ አበባው መሃሪን ስህተት ተከራካሪው አቶ ሬድዋን ሁሴን ወይም ሽመልስ ከማል ቢሆኑ ኖሮ አንድ ዶክመንተሪ የሚወጣው ስድብ ይገጥማቸው ነበር፡፡ አሁንም ኢህአዴግ በቀጣይ በኢቲቪ በሚያቀርበው ዶክመንተሪ ከህዝብ ጋር በሚያጋጭ መልኩ ቅስቀሳ አይደረግባቸውም የሚል እምነት የለኝም፡፡ ለማነኛውም “ከፍትፍት እና ከእሳት” ምርጫ ቀርቦዋል አሰበህ ምረጥ ብለው ክርክሩን አጠናቀዋል፡፡

አቶ አበባው መሃሪ በአማካሪነት ያመጧቸው አዛውንት አስተያየት ካልሰጡ ለምን እንዳደከሟቸው አይገባኝም፡፡ አሁንም እንዚህ ጎምቶ የሀገር አዛውንቶች በኢትዮጵያ ፖለቲካ ዋነኛ ተዋናይ ለመሆን የሚያደርጉትን ፍላጎት ለመግታት ካልተቻለ በቀጣይ ዋነኛ ተዋናይ የሚሆነው አዲስ ትውልድ እንዴት እድል እንደሚያገኝ ግራ የሚያጋባ ነው፡፡ አቶ አበባው መሀሪም ቢሆን በዚህ ክርክር ደረጃውን የጠበቀ የቀድሞውን መኢህአድ ወክለው ሊቀርቡ አልቻሉም፣ ወደፊትም አይችሉምና በጊዜ ቢያስቡበት ጥሩ ነው የሚል ምክር መለገስ አለብኝ፡፡ አንተን ብሎ መካሪ የሚልም ቢኖር ማለቴ ነው፡፡

ኢህአዴግ ባለፈው እንዳልኩት አዲስ ሀሳብ ሆነ አዲስ ሰው እንደሌለው አሁንም በድጋሚ አሳይቶናል፡፡ ፌዴራሊዝምን በሚመለከት ኢህአዴግ እየደጋገመ ሲናገረው ለራሱም እውነት እየመሰለው የመጣው አሁን የተዘረጋው ፌዴራሊዝም ስርዓት ባይኖር ይህች ሀገር ትበታተን ነበር የሚለው ነው፡፡ መሳሪያ ይዘው ይህችን ሀገር ሲቆጣጠሩ እነርሱ እንደ ፈለጉ ካላደረጓት ይህችን ሀገር ለመበታተን ፍላጎት ነበራቸው የሚባል ከሆነ እውነት ነው፡፡ እነሱ ስልጣን ሲይዙ እኛ በህይወት ያለን ምስክሮች ሀገራችን ቋንቋን በዋነኝነት መሰረት ያደረገ ፌዴራሊዝም ካልመጣ እንበታተናለን ብለን ተማምለን አናውቅም፡፡ ልክ ነው ህውሃት ለመገንጠል ሃሳብ ነበረው፣ ኦነግም እንደዚሁ የነፃ ኦሮሚያ ሀሳብ እሰከ አሁን አልተወም፡፡ ኦነግ እንደ ድርጅት ይህን ሀሳብ ባይተወውም መሪዎቹ እነ ሌንጮ ለታ ለአርባ ዓመት በኦነግ ሰም የተከፈለውን መሰዋዕትነት እንዴት እንደሚያወራርዱት ሳናውቅ፤ የመገንጠል ሀሳቡን ትተውት አዲስ አበባ ገብተዋል የሚል ወሬ ነፍስ ዘርቶዋል፡፡

ኢህአዴግ የሚባል ድርጅት ይህችን ሀገር ካልመራ ሀገር ትበተናለች ሰላም የሚባል ነገር የለም የሚባል ቅጥ ያጣ ሟርት ምንጩ ምን እንደሆነ ባይገባኝም፤ ይህን የሀሰት ፕሮፓጋንዳ ደጋግመው ሲያወሩት ለራሳቸውም እውነት እየመሰላቸው መጥቶዋል፡፡ በኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ ልዩ በሆነ ሁኔታ ብዙ ቋንቋ እንዳለ አድርገው የሚነግሩን ለምን እንደሆነ እሰከ አሁን ለማንም ግልፅ አይደለም፡፡ በሌሎች የዓለም ሀገራት ብዙ ቋንቋ ብዙ ባሕል እያለም ተፋቅሮ መኖር የሚባል ነገር፣ ሀገር የሚባል የጋራ ቤት መስራት እንደተቻለ በፍፁም እንድናውቅ አይፈልጉም፡፡ በአንድ ቋንቋ እየተናገሩም በሰለምና በፍቅ መኖር አቅቷቸው በጎሳ እየተቧደኑ መገዳደል እንደሚቻል በቅርብ ያለች ሀገር ሶማሌ መፍረስ እንዳለም እንደምናውቅ አያውቁም፡፡ ስለዚህ ኢህአዴጎች ተጨፈኑ ላሞኛችሁ እያሉን ነው የሚገኘው፡፡ ይህንኑ መፈክር ነው አሁን ከ24 ዓመት በኋላ ይዘው ለምርጫ ክርክር የቀረቡት፡፡ ለዚህ ነው አዲስ ነገር የላቸውም የምለው፡፡

ለማነኛውም አስገራሚ ሆኖ ያገኘሁት የመከራከሪያ ነጥብ ከአቶ አባዱላ የቀረበው ነው፡፡ የኦሮሞ ህዝብ ወደ ትጥቅ ትግለ የገባው በቋነቋ መናገር ሲከለከል፣ ባህሉን ማሳደግ ሲያቅተው ነው የሚለው ነው፡፡ ይህ ክርክር በተለይ አቶ አባዱላ ገመዳ ላይ የሚያምር ሆኖ አላገኘሁትም፡፡  ልክ እንደ ትግራይ ልጆች ይህን ብለው ከአዲስ አበባ የኦሮሞ ልጆችን አደራጅተው ቢሄዱ ይህን ሃሳብ ልናከብረው እንችል ነበር፡፡ ለደርግ ሰራዊት ለመዋጋት ወታደር ሆነው በጦር ሜዳ ተማርከው፤ በምርኮ ወቅት ባገኙት የብሔርተኝነት ምክር በሰማኒያዎች መጀመሪያ ጀምረው ባደረጉት የጠመንጃ ትግል አማርኛ አስጠልቶኝ ነው ጫካ የገባሁት የሚመስል አሰተያየት ውሃ አልቋጥር ብሎኛል፡፡ ኢህአዴግ ፌዴራሊዝምን የመረጠው ብዝዓነትን ለማስተናገድ የቻለ ስርዓት ባለመኖሩ ነው ይሉናል፡፡ ይህ ባይሆን ልንበተን ነበር ሲሉን እኔ የሚገባኝ ግን ሊበትኑን ጫካ የነበሩት ግን እነርሱ ራሳቸው መሆናቸው ነው፡፡

ለማነኛውም ሁሉም የሚስማሙበት እኛም ቤታችን ሆነን ሰምምነታችንን የምንሰጥበት ጉዳይ ኢትዮጵያ የፌዴራሊዝም ሰርዓት ብቸኛውም አማራጭ የሚለውን ትተን ጥሩ አማራጭ ነው በሚለው ሰምምነት ያለበት መሆኑን ነው፡፡  ሰምምነት የሌለበት እና በህዘብ ይሁንታ ሊታረም የሚገባው ደግሞ ምን ዓይነት ፌዴራሊዝም? የሚለው ነው፡፡ ይህ ደግሞ በአንድ ጊዜ ተሰርቶ የሚያልቅ ሳይሆን ህዝቦች በሂደት እያዳበሩት የሚሄዱት በዓለም ላይ ያለ የአስተዳደር ዘይቤ ነው፡፡ ፌዴራሊዝም በህዘብ ብዛትና በመሬት ሰፋት እኩል የሆኑ የፌዴራል ግዛቶች የሚያዋቅሩትም አይደለም፡፡ አንድ ዓይነት ቋንቋም ሰለሚናገሩ በአንድ የፌዴራል ክልል ውስጥ መሆን አለባቸው የሚል ፎርሙላም አይሰራም፡፡ አሁን በኢትዮጵያ ያሉት ክልሎች መቼም ቢሆን በራሳቸው መንግሰት ሆነው የራሳቸው የተለየ የአስተዳደር ዘይቤ የመሰረቱበት ሁኔታ ሰለአልነበረ፤ በኢትዮጵያ የሚያስፈልገው ምርጥ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም የሚያመጣ እና በተለይ ደግሞ ዜጎች ባልተማከለ አስተዳደር ፍትህና መልካም አስተዳደር የሚያገኙበት፣ በሀገሪቱ ፖለቲካ በቀጥታ ለመሳተፍ የሚያስችል ብቻ ሳይሆን የአካባቢያቸውን ልዮ ሁኔታ ያገናዘበ የእድገትና የፖለቲካ ተሳትፎ ለማደረግ ነፃነት የሚሰጥ ነው፡፡ ይህን ያገናዘበ የፌዴራል ሰርዓት ቢያንስ፤

  • የተለያዩ ህጎች በፌዴራል ክለሎች በሚገኙ መንግሰታት መካከል ሊኖር ይቸላል፡፡ ለምሳሌ የሞት ፍርድን ቀድመው የሚያስቀሩ ክልሎች ሊኖሩ ይችላሉ፤
  • ኦሮሚያን የመሰሉ ትልልቅ ክልሎች ውስጥ ለምሳሌ ቦረና ጅማ የመሳሰሉት አካባቢዎች የገዳ ስርዓት ሞዴል የክልል አስተዳደር እንዲኖር የሚያደርግ አሰራር፤
  • መሬትን ለኤኮኖሚ ጥቅምና ለክልሉ ፈጣን ልማት ሲሉ በነፃ ለኢንቨስትመንት ማቅረብን ጨምሮ ታክስ ክፍያን በተለያየ ምጣኔ ማስከፈል፤
  • የሰለጠነ የሰው ኃይል ወደ ክልላቸው ለመሳብ ሲባል የሚወሰዱ የተለያዩ እርምጃዎች ለምሳሌ የክፍያ ሰርዓት እና የሰራ ቋንቋን ከአንድ በላይ ማድረግ፤ወዘተ

በግልፅ የሚታዩ ልዩነቶች ሊሆኑ ይቸላሉ፡፡

የሁለት ሺ ሰባት ምርጫ አማራጭ ባይኖርም ወጪን ይዞ ገዢውን ፓርቲ ለማንገስ በሁሉም መስክ እየተውተረተረ ይገኛል፡፡ እኔም ሰራ እንዳልፈታ ያለኝን የግል ዕይታ ወርውሪያለሁ፡፡ ሁሉም ላይስማማ ቢችልም ተመዝግቦ እንዲቀመጥ በሚል ያሰፈርኩትን ሀሳብ ተወያዩበት፤ ኢህአዴግ ለውድድር የተዘጋጀበት ዐውድ ግን በእውነት አሰደማሚ እንደሆነ ይቀጥላል፡፡ ይህም ፍርሃቱን ካልሆነ ምን ሊያሳይ እንደሚችል አልገባኝ ብሎ አለሁኝ፡፡

ቸር ይግጠመን!!!

The post ምረጫ ክርክር 2፡ “የፌዴራል ስርዓተ በኢትዮጵያ”-የግል ዕይታ – ግርማ ሠይፉ ማሩ appeared first on Zehabesha Amharic.

ወደ ኢትዮጵያ የሄዱት ሌንጮ ለታ በ72 ሰዓት ወደ አውሮፓ ተመለሱ * መንግስት አባሯቸው ነው ይባላል

$
0
0

Wikileaks on Lencho Leta (TOP Secret) – Must Listen
(ዘ-ሐበሻ) የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግንባርን ይዘው ወደ አዲስ አበባ የገቡት ኦቦ ሌንጮ ለታ ኢትዮጵያ በገቡ በ72 ሰዓታት ውስጥ ወደ አውሮፓ መመለሳቸውን የዘ-ሐበሻ ምንጮች አስታወቁ:: ኦዴፍ ውስጥ ያሉ የዘ-ሐበሻ ምንጮች እንደገለጹት ኦቦ ሌንጮ ለታ በኢትዮጵያ መንግስት ተባረዋል የሚባል ነገር ቢሰሙም ማረጋገጥ ግን አልተቻለም::

ዘ-ሐበሻ የአቶ ሌንጮ ለታን ጉዳይ ለማጣራት ወደ ኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግንባር የሕዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ሌንጮ ባቲ ጋር የደወለች ሲሆን ከ7 ጊዜ በላይ ብንሞክርም ስልካቸው ስለማይነሳ ሌንጮ ለምን እንደተመለሱ ማረጋገጥ አልተቻለም::

The post ወደ ኢትዮጵያ የሄዱት ሌንጮ ለታ በ72 ሰዓት ወደ አውሮፓ ተመለሱ * መንግስት አባሯቸው ነው ይባላል appeared first on Zehabesha Amharic.


ኤርትራ የሚገኙት የኢትዮጵያ ነፃነት ታጋዮች ከዚህ ቀደም በወያኔ ላይ ጥቃት ሲፈጽሙ የሚያሳይ ቭዲዮ

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) ኤርትራ የሚገኙት የኢትዮጵያ የነፃነት ታጋዮች በተለያዩ ጊዜያት ወደ ኢትዮጵያ ድንበር በመግባት በወያኔ ሰራዊት ላይ ጥቃት በመፈጸም ይመለሳሉ:: የኢሳት ጋዜጠኞች ሰሞኑን ወደ ኤርትራ ከተጓዙ በኋላ ከትህዴን, ከአርበኞች ግንቦት 7 እና ከሌሎችም ሃይሎች የተለያዩ ቭዲዮዎች ደርሰዋቸዋል:: ቀጣዩ ቭዲዮ ኤርትራ ያሉ የነፃነት ታጋዮች ከዚህ በፊት በወያኔ ላይ ጥቃት ሲፈጽሙ ያሳያል:: ምንም እንኳ ቭዲዮው አዲስ ባይሆንም ይመልከቱት::

ኤርትራ የሚገኙት የኢትዮጵያ ነፃነት ታጋዮች ከዚህ ቀደም በወያኔ ላይ ጥቃት ሲፈጽሙ የሚያሳይ ቭዲዮ

The post ኤርትራ የሚገኙት የኢትዮጵያ ነፃነት ታጋዮች ከዚህ ቀደም በወያኔ ላይ ጥቃት ሲፈጽሙ የሚያሳይ ቭዲዮ appeared first on Zehabesha Amharic.

የሕወሓት መንግስት በኤርትራ ላይ የአየር ጥቃት ፈጸምኩ የሚለው ቅዠት ነው ተባለ * “እንኳን የአየር ድብደባ ይቅርና ሞቅ ያለ ጭብጨባም አልተሰማም”

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) የሕወሓት መንግስት በኤርትራ በማይ እዳጋ የሚገኘው የሚሻዕ ወርቅ ማዕድን ካምፓኒ ላይ የአየር ጥቃት አደረስኩ ብሎ ከገለጸ በኋላ የኤርትራ መንግስት በኢትዮጵያ ምንም አይነት ጥቃት እንደደረሰበት የገለጸው ነገር አልነበረም:: አስመራ የሚገኙ የዘ-ሐበሻ ምንጮች እንደሚሉት ከሆነ በማይ እደጋ እንኳን የአየር ድብደባ ይቅርና ሞቅ ያለ ጭብጨባም አልተሰማም::
Vandalism
በኤርትራ ይህን የወርቅ ማዕድን የሚያወጣው የካናዳው የማዕድን አውጪ ድርጅት (NEVSUN RESOURCES LTD) ማምሻውን በድረገጹ (www.nevsun.com) ባወጣው መግለጫ የአየር ጥቃት እንደደረሰበት አልገለጸም:: ድርጅቱ ማርች 13 ቀን 2015 ልክ በማንኛውም መስሪያ ቤት እንደሚደርስ አደጋ መጠነኛ መሰባበር የደረሰበት ቢሆንም ጥገና አድርጎ ወደ ስራ እንደሚመለስ ገልጿል:: ይህ ጉዳት የደረሰበት የሕወሓት መንግስት እንደሚለው በአየር ጥቃት እንደሆነ ካምፓኒው ያስቀመጠው ነገር የለም::

የሕወሃት መንግስት ለምን ይህ ዜናን ማሰማት ፈለገ? የሚለውን ዘ-ሐበሻ ወደ አስመራ ምንጮቿ ጋር ደውላ የነበረ ሲሆን ምንጮቹም “የሕወሓት መንግስት ይህን ዜና ማሰራጨት የፈለገው ከፍራቻ የተነሳ ነው:: በዚህ በሚሻዕ የወርቅ ማዕድን ማውጫ በማንኛውም ድርጅት ውስጥ እንደሚፈጠር መጠነኛ የማሽኖች መሰባበር አደጋ መፈጠሩን የወያኔ ደህነንቶች መረጃ አላቸው:: የዚህ ድርጅት አካባቢ ደግሞ የኢትዮጵያ ነፃነት ታጋዮች የሚገኙበት ወታደራዊ ካምፖች አሉ:: አደጋው ከደረሰ ከአንድ ሳምንት በኋላ የሕወሓት መንግስት በኤርትራ ላይ የአየር ጥቃት እንደፈጸመ ማውራቱ ከገባበት ውጥረት የሕዝቡን አመለካከት ለመቀየር ነው” ብለዋል::

በተለይም በጎንደር አካባቢ በሕወሓት ወታደሮች እና በጎንደር ሕዝብ መካከል በተፈጠረው ውጥረት በዛሬው ዕለት 4 ሰዎች መሞታቸውን ተከትሎና ሰሞኑንም ሕዝቡ ጠመንጃ እየያዘ ጫካ እየገባ በመሆኑ ይህን ለማስቀየስ የሕወሓት መንግስት የቀየሰው የፕሮፓጋንዳ ስልት ነው ሲሉ እነዚሁ ወታደራዊ ምንጮች ለዘ-ሐበሻ ገልጸዋል::

The post የሕወሓት መንግስት በኤርትራ ላይ የአየር ጥቃት ፈጸምኩ የሚለው ቅዠት ነው ተባለ * “እንኳን የአየር ድብደባ ይቅርና ሞቅ ያለ ጭብጨባም አልተሰማም” appeared first on Zehabesha Amharic.

Hiber Radio: ኢትዮጵያ 90 ከመቶ የዝሆን ሀብቷን ማጣቷ…አልሸባብ ለኢትዮጵያ የሰልላል ያለውን ወጣት በአደባባይ መግደሉ…የአገዛዙ ጄኔራል ድንበር ተሻግረው ጋዜጠኛውን እገድልሃለው ሲሉ መዛታቸው…የሌንጮ ለታ ከኢትዮጵያ መግባትና መባረር የጋዜጠኛ በፈቃዱ ሞረዳ አስተያየት…ግብፅ በአባይ ውሃ የመጠቀም ታሪካዊ መብቴ አይለወጥም ስትል አቋሟን ዳግም መግለጿ…የመኢአድ 20 አባላት መታሰራቸውና ሌሎችም…

$
0
0

Habitamu
የህብር ሬዲዮ መጋቢት 13 ቀን 2007 ፕሮግራም

<...የአቶ ሌንጮ ለታ አገር ቤት በገቡ በ24 ሰዓት ውስጥ መባረር ጥሩ ነው ። ሰላማዊ ትግል የሚባለው...ሁሉም በመረጠው መንገድ ሰላማዊ የሚለውም የትጥቅ ትግል የሚለውም አንዱ በአንዱ ላይ ድንጋይ አይወርውር...> ጋዜጠኛ በፍቃዱ ሞረዳ በቅርቡ ከኦሮሚያ ሚዲአ ኔትወርክ የለቀቀና ቀድሞ በአገር ቤት ትታተም የነበረችው የጦማር ጋዜጣ አሳታሚና ዋና አዘጋጅ የአቶ ሌንጮን አገር ቤት መግባትና ከአገር ቤት መውታት አስመልክቶ ለህብር ሬዲዮ ከሰጠው ማብራሪያ (ሙሉውን ያዳምጡ)

<...የናይጄሪያ መንግስት በሟቹ የአገሪቱ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ጄ/ል ሳኒ አባቻ ከተዘረፈውን መካከል ከአስራ ስድስት ዓመት በሁዋላ እያስመለሱ ነው ...ከኢትዮጵያ ተዘርፎ የወጣው ሰላሳ ቢሊዮን ዶላር ይደርሳል የተዘረፈውን ግን የማይጠይቁት ሌባ ሌባን ስለማያጋልጠው ...> ዶ/ር አክሎግ ቢራራ ከኢትዮጵያ ተዘርፎ ስለወጣው ገንዘብ ጠያቂ መጥፋቱ ላይ አነጋግረናቸው ከሰጡን ቃለ መጠይቅ (ሙሉውን ያዳምጡ)

ሩሲያንና አሜሪካን ጨምሮ ታላላቅ አገሮች ጋር የምትወዛገብበት የክሪሚያ ሕዝበ ውሳኔና ውህደቱን ተከትሎ የቀረቡ ተቃውሞዎች (ልዩ ዘገባ)

ሌሎችም

ዜናዎቻችን

– አቶ ሌንጮ ለታ በኢትዮጵያው አገዛዝ የደህንነት ሀላፊ ትዕዛዝ ከአገር ተባረሩ

* የድርጅታቸው ሰዎች አቶ ሌንጮ የሚያናግራቸው ባለስልጣን ስለጠፋ ከአገር ወጥተዋል ሲሉ ገልፀዋል

– የኢትዮጵያው አገዛዝ መገናኛ ብዙሃን እንደዘገቡት ወደ ኤርትራ ዘልቆ የአየር ጥቃት አልሰነዘረም

* በጥቃቱ ወደመ የተባለው የካናዳው የወርቅ ማዕድን ኩባንያ ፋብሪካው ስራውን እንዳላቋረጠ ገለጸ

– ግብፅ በአባይ ውሃ የመጠቀም ታሪካዊ መብቴ አይለወጥም ስትል አቋሟን ዳግም ገለፀች

– የግብፅ መግለጫ ኢትዮጵያ ሱዳንና ግብፅ ደርሰንበታል ካሉት ፊርማ ቀረሽ ስምምነት አደጋ ላይ ሳይጥለው አይቀርም

– የሶማሊያው አክራሪ ቡድን አልሸባብ ለኢትዮጵያ የሰልላል ያለውን አንድ ወጣት ሰሞኑን በአደባባይ ገደለ

– ኢትዮጵያ 90 ከመቶ የዝሆን ሀብቷን ማጣቷ ተነገረ

– በጋሞ ጎፋ በቅስቀሳ ላይ የነበሩት የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ታሰሩ

* የባህር ዳር የፓርቲው ቢሮ በወከባና ማስፈራሪያ መዘጋቱ ተገለፀ

– የመኢአድ ከ20 በላይ አባላቱ ማዕከላዊን ጨምሮ በአገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች በእስር ላይ መሆናቸውን ተገለፀ

– የኢትዮጵያው አገዛዝ ጄኔራል ድንበር ተሻግረው እገድለሃለሁ እንዳሉት ጋዜጠኛው ገለጸ

ሌሎችም ዜናዎች አሉ

The post Hiber Radio: ኢትዮጵያ 90 ከመቶ የዝሆን ሀብቷን ማጣቷ… አልሸባብ ለኢትዮጵያ የሰልላል ያለውን ወጣት በአደባባይ መግደሉ… የአገዛዙ ጄኔራል ድንበር ተሻግረው ጋዜጠኛውን እገድልሃለው ሲሉ መዛታቸው… የሌንጮ ለታ ከኢትዮጵያ መግባትና መባረር የጋዜጠኛ በፈቃዱ ሞረዳ አስተያየት… ግብፅ በአባይ ውሃ የመጠቀም ታሪካዊ መብቴ አይለወጥም ስትል አቋሟን ዳግም መግለጿ… የመኢአድ 20 አባላት መታሰራቸውና ሌሎችም… appeared first on Zehabesha Amharic.

ፓትርያርኩ ቋሚ ሲኖዶሱን በመተላለፍ በድጋሚ መመሪያ ሰጡ፤ ዋና ሥራ አስኪያጁ፣ ቤተ ክርስቲያኒቱን ለከፍተኛ ውዝግብ እንደሚዳርግ በመግለጽ ሕገ ቤተ ክርስቲያኑን ያገነዘበ ተለዋጭ መመሪያ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል

$
0
0

ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ፡-

  • ‹‹የአ/አበባ ሀ/ስብከት የፓትርያርኩ ልዩ ሀ/ስብከት ነው›› የሚለውን ድንጋጌ ተገን አድርገዋል
  • የወቅቱ ዋና እና ምክትል ሥራ አስኪያጆች ወደ ጠቅላይ ቤተ ክህነቱ እንዲዛወሩ አዝዘዋል
  • የሀ/ስብከቱ ብልሹ አሠራር የቀጠለው ‹ሥዩማኖቹ› በወቅቱ ሥራ ባለመጀመራቸው ነው ብለዋል

aba-mathias

  • ተጠሪ
    ነታቸው ለቅዱስ ሲኖዶስም ለፓትርያርኩም የኾኑት ረዳት ሊቀ ጳጳሱ አልተስማሙበትም
  • የረዳት ሊቀ ጳጳሱ ድርሻ ከሌሎች ሊቃነ ጳጳሳት ተግባርና ሓላፊነት በተለየ አልተዘረዘረም
  • የአ/አ ሀ/ስብከትን ልዩ ኹኔታዎች ያገናዘበ የሥራ አስኪያጆች አሿሿም ዝርዝር አልወጣም
  • ፓትርያርኩንና የሀ/ስብከቱን ረዳት ሊቀ ጳጳስ የሚያስማማ ተለዋጭ መመሪያ ይሰጠኝ

ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ፣ ከረዳት ሊቀ ጳጳሳቸው ስምምነት ውጭ በራሳቸው ቀጥተኛ ውሳኔ ለሠየሟቸው የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ እና ምክትል ሥራ አስኪያጆች፣ በዛሬው ዕለት የምደባቸው ደብዳቤ እንዲደርሳቸው ለጠቅላይ ቤተ ክህነቱን ዋና ሥራ አስኪያጅ ለኹለተኛ ጊዜ መመሪያ ሰጡ፡፡

‹‹ሕጋዊ አሠራርን በእጅጉ የሚፃረር ነው›› በሚል ከረዳት ሊቀ ጳጳሱ ጠንካራ ተቃውሞ የገጠመውንና ከሕገ ቤተ ክርስቲያን አንጻር በብፁዕ ዋና ሥራ አስኪያጁ የአፈጻጸም ጥያቄዎች የተነሡበትን ያለፈው ሳምንት የመጀመሪያ መመሪያቸውን ያስታወሱት ፓትርያርኩ፣‹‹የተሰጠው አመራር ባለመፈጸሙ በሀገረ ስብከቱ ያለው ብልሹ አሠራር እንዲቀጥል እየተደረገ ነው፤›› በማለት ነው መመሪያውን ለኹለተኛ ጊዜ የጻፉት፡፡

ፓትርያርኩ ከልዩ ጽ/ቤታቸው በቁጥር ል/ጽ/312/10/2007 በቀን 14/7/2007 ዓ.ም. ድጋሚ መመሪያ በሰጡበት በዛሬው ደብዳቤአቸው፣ የወቅቱ የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ አእላፍ ቀሲስ በላይ መኰንን እና ምክትል ሥራ አስኪያጁ መ/ር ኃይለ ማርያም ኣብርሃ ከሓላፊነታቸው መነሣታቸውንም አስታውቀዋል፡፡ ‹‹ደረጃቸውን በጠበቀ ኹኔታ ወደ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ተዛውረው እንዲሠሩ›› እንዲደረግና ይኸው መመሪያም በዛሬው ዕለት ተፈጻሚ እንዲኾን በጥብቅ አስታውቀዋል፡፡

የፓትርያርኩ የሹመት መመሪያ ‹‹በቤተ ክርስቲያኒቱ መዋቅራዊ ሒደት ያልተለመደ ነው›› ያሉት በሀገረ ስብከቱ የፓትርያርኩ ረዳት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ በበኩላቸው፣ የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅም ኾነ ምክትል ሥራ አስኪያጅ ተጠሪነት ለቅዱስ ፓትርያርኩ ኾኖ እንደማያውቅና መኾንም እንደማይችል ለቅዱስነታቸው በአድራሻ በጻፉት ደብዳቤ በማስታወስ አካሔዱ ከሕገ ቤተ ክርስቲያን፣ ከቃለ ዐዋዲ ደንቡ እና ከሀገሪቱ የሕግ አሠራር ጭምር ውጭ ኾኖ እንደተመለከቱት ገልጸዋል፡፡

አሠራሩ የሕግ ድጋፍ የሚኖረው፣ የሀገረ ስብከቱ ረዳት ሊቀ ጳጳስ መርጦ አቅርቦ ከጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ጋር ጭምር የጋራ ስምምነት ሲደረስበት እንደኾነ ብፁዕነታቸው አስገንዝበዋል፡፡ አሠራሩ እንደ አጠቃላይ ሲታይ ከትዝብት ላይ የሚጥል መኾኑን በመጥቀስም‹‹ለቤተ ክርስቲያኒቱ ሰላማዊ አሠራር ለኹላችንም ሰላም›› ሲባል ፓትርያርኩ ውሳኔአቸውን እንደገና እንዲያጤኑ አሳስበዋቸዋል፡፡ የሹመት መመሪያውን እንዲሰሙት የተደረገው በግልባጭ ቢኾንም በተካሔደው የሥራ አስኪያጅ ምርጫ እንደማይስማሙና የመመሪያውን ተፈጻሚነት ለማስተናገድ እንደሚቸገሩም አስታውቀዋቸዋል፡፡

የፓትርያርኩ ተደጋጋሚ የሹመት መመሪያ በአድራሻ ሲጻፍላቸው፣ መመሪያው ከቤተ ክርስቲያን ሕግና ደንብ አኳያ እንዲጤን የሚያሳስበው የረዳት ሊቀ ጳጳሱ ደብዳቤ ደግሞ በግልባጭ የደረሳቸው የጠቅላይ ቤተ ክህነት ብፁዕ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቡነ ማቴዎስም፣ ባለፈው ሳምንት ዐርብ የቋሚ ሲኖዶስ መደበኛ ስብሰባ ወቅት፣ የቅዱስነታቸውን አባታዊ መመሪያ ለማስፈጸም ዝግጁ መኾናቸውን ነገር ግን አፈጻጸሙ አከራካሪ ሐሳቦችን ስለሚያስነሣ የሚያስከትለው ውዝግብና አለመግባባት አስቀድሞ በስፋት እንዲጤን ጠይቀው ነበር፡፡

ቋሚ ሲኖዶሱን በርእሰ መንበርነት የሚመሩት ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ፣ የብፁዕ ዋና ሥራ አስኪያጁ ሐሳብ በአጀንዳ ተይዞ እንዳይደመጥ ለማድረግ ‹‹ውሳኔ ነው፤ መታየት አይችልም›› በማለት ቢቃወሙም ቋሚ ሲኖዶሱ ብፁዕነታቸው አስተያየታቸውን በጽሑፍ እንዲያቀርቡ ትእዛዝ በመስጠት ለቀጣይ ስብሰባ እንዳሳደረው ተዘግቦ ነበር፡፡ በዚኽ ኹኔታ ውስጥ ነው ፓትርያርኩ ሥዩማን ሥራ አስኪያጆቻቸው ሥራ እንዲጀምሩ የሹመት ምደባው በዋና ሥራ አስኪያጁ በኩል በዛሬው ዕለት እንዲጻፍላቸው ለኹለተኛ ጊዜ‹‹በጥብቅ አስታውቃለኹ›› በማለት ያዘዟቸው፡፡

Source:: haratewahido

The post ፓትርያርኩ ቋሚ ሲኖዶሱን በመተላለፍ በድጋሚ መመሪያ ሰጡ፤ ዋና ሥራ አስኪያጁ፣ ቤተ ክርስቲያኒቱን ለከፍተኛ ውዝግብ እንደሚዳርግ በመግለጽ ሕገ ቤተ ክርስቲያኑን ያገነዘበ ተለዋጭ መመሪያ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል appeared first on Zehabesha Amharic.

በሰሜን ጎንደር አካባቢ የታየውን የጸጥታ መደፍረስ ተከትሎ የመከላከያ ሰራዊት አባላት በተጠንቀቅ እንዲቆሙ ታዘዙ

$
0
0

ኢሳት ዜና :-የኢሳት ምንጮች እንደገለጹት ሰሞኑን በሰሜን ጎንደር አካባቢ የታየውን የጸጥታ መደፍረስ ተከትሎ የአገሪቱ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ካለፈው ሃሙስ ቀን ጀምሮ በተጠንቀቅ እንዲቆሙ ታዛዋል።
Ethiopian soldiers ride on an army truck on the road to Afgooye, south of Mogadishu
የኢሳት ምንጮች እንደገለጹት የአየር ሃይል አባላት ካለፈው ሃሙስ ጀምሮ ከግቢ እንዳይወጡ ሲታዘዙ የተወሰኑት ደግሞ ከደብረዘይት እና ድሬዳዋ አየር ሃይል  ወደ መቀሌ አምርተዋል። ብዛት ያለው የእግረኛ ሰራዊትም ወደ ኤርትራና ሱዳን ድንበሮች አቅንቷል።

ወታደራዊ ልምምዶችና አዳዳስ ምልመላዎችም እየተካሄዱ መሆኑንም ምንጮች ገልጸዋል።

ማንነታቸው በውል ያልታወቀ የተቃዋሚ ሃይሎች ጎንደር ከተማ ውስጥ የሚሊሺያ አዛዥ የሆነውን ኮማንደር ተፈራን ገድለው  ካመለጡ በሁዋላ፣ እነሱን ለመያዝ መጋቢት 12 አርማጭ ልዩ ቦታው እንኮይ ተራራ ላይ በተደረገ ጦርነት ፣ ከተቃዋሚዎች በኩል ሻምበል ይርዳውና

አዲሱ የተባሉ  ሲገደሉ፣ ከመንግስት ታጣቂዎች በኩል ደግሞ  የልዩ ሃይል አባል የሆነው  እባበይ እንዲሁም አንድ ስሙ በውል ያልታወቀና ሁለት የሚሊሺያ አባላት ተገድለዋል። ከቀኑ ዘጠኝ ሰአት ጀምሮ እስከ ምሽት በቀጠለው የተኩስ ልውውጥ፣ አንድ ተማሪ በመንግስት

ሃይሎች ተገድሏል። የመንግስት የጸጥታ ሃይሎች ምሽት ላይ አካባቢውን ጥለው መውጣታቸውን የአይን እማኞች ገልጸዋል።

በጉዳዩ ዙሪያ የመንግስትን አስተያየት ለማካተት የተደረገው ጥረት አልተሳካም።

The post በሰሜን ጎንደር አካባቢ የታየውን የጸጥታ መደፍረስ ተከትሎ የመከላከያ ሰራዊት አባላት በተጠንቀቅ እንዲቆሙ ታዘዙ appeared first on Zehabesha Amharic.

Viewing all 8745 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>