Quantcast
Channel: ዘ-ሐበሻ – Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 8745 articles
Browse latest View live

ተደናቁሮ ለማደናቆር የመረጠ ሰርአት ማነው? – ሊቁ እጅጉ

$
0
0

በ 21ኛ ክፍለ ዘመንሰ ድንቁርና የተፈረደባት አገር ማነች ? (ሎሚ-ተራ ተራ)

በ እርግጠኝነት በቅርቡ በዚህ በአሜሪካን አገር ተወዳጀ በሆነው  ጀፐርዲ (Jeopardy!, ) ተብሎ በሚታወቀው እርሦም ይሞክሩት የጥያቄና መልሰ ውድድር  በጥያቄነት መቀረቡ አይቀሬ ነው ተብሎ የሚገመተውን የጥያቄ አርእሰት ነው ይዤላችሁ የቀረብኩት፡፡

አዎ በ እርግጥ ይዞታው አሰቂኝ ቢመሰልም እውነታውን በአንክሮ ለተመለከተው ማንኛውም ዜጋ ግን ከልብ ያሳዝናል ያሰቆጫልም። ተደናቁሮ ለማደናቆር የመረጠው የወያኔ ሰርአት ግን  ማንም ከልካይ በሌለው ሁኔታ ትውልዱን ለ24 አመት በማፈንና  አዕምሮውን እንኳን በእወቀት እንዳየሰፋ ታዋቂና አዋቂ ናቸው ትውልዱን ሀብት ባይሰጡትም እውቀት ያሰገበዩታል ተብለው የሚታመንባቸውን የ ዩንቨርሲቲ አሰተማሪ ፐሮፌሰሮችን ያለምንም አፈረት እውቀትን ለምን አሰፋፋችሁ ? አደናቁሩ አልናችሁ እንጂ ህዘቡ አይኑ ተገልጦ  የእኛን አፍራሽነትና የዘረኝነት ፖሎቲካ አራማጅነት እንዲረዳ በእውቀት አጥምቁ መች አልናችሁ ? የሚሉ ይመሰል ባደባባይ አይናቸውን በጨው አጥበው ማባረሩን ተያይዘውታል ። ይሔ ታዲያ ምን ሰም ሊሰጠው እና ምን ሊባል እንደሚችል በ እውነቱ አሰቸጋሪ ነው ? እርግማን አይመሰላችሁም ? አሁን ዶ/ር ጌታቸውን ማባረር ምን ይባላል?

“እርሳቸው ግን አሁን ገና ኢትዮጵያዊ ሆንኩ ፣ምከንያቱም ኢትዮጵያዊ  መሆን ማለት መብቴ የሚረገጥ ማለት ነውና ” በሚል  የወያኔ ሰርአት ኢትዬጲያዊነትን ምን አክል እንደሚጠላና አላማውና እቅዱ ሁሉ አገር ማፈረሰና ማጥፋት እንደሆነ እንደፍልሰፍና መሁርነታችው በፍልሰፍና ቃል  በጥሩ ሁኔታ ገልጸውታል። ጥያቄው ግን  ያፈጠጠ ሰርአት አልበኝነት እሰከመቼ በዚህ እብሪተኝነት መቀጠል ይችላል ተብሎ ይታመናል ነው ? ሕዝብሰ ይኸንን አይነት አይን ያፈጠጠ ማን አለብኝነት  ሰርአት እሰከመቼ ተሸክሞ ይዘልቃል ? በቃኝ ! በቃኝ አሁንሰ መረረኝ ብሎ አሸቀንጥሮ ለመጣል አቅም ያጣበት ምክነያት  ምን ይሆን ? በእርግጥ ወያኔ በጥናቱ ባሰላው የማደናቆር እቅድ ሕዝቡ ተደናቁሯል ማለት ነው?  ከሆነሰ የእኛ በ ውጭ የምንኖረው አልተደናቆርንም የምንለው ወያኔ አደናቁሮታል ያልነውን ሕዘባችንን የመታደግ ግዴታችንን እንዴት መወጣት እንችላለን ትላላችሁ ? እር ይታሰብበት ጎበዝ እኛንም አደናቆሩን እንበል እንዴ ? አይገባም እንንቃ ሕዘባችንንም እንታደገው ።

አልታይህ አለኝ አይኔን ጉም ሸፍኖት
አልገለጥ አለኝ እሰትራፖ ይዞት
አይን የሚሸፍን አይን የሚጋርድ
አዲሰ በሸታ ነው “ወያኔ” መሆኑን ሕዘቤ ሆይ ተረዱት
*
ምንድነው ብላችሁ ጥያቄም አቅርቡ
ምላሹን የሚሰጥ ባይኖርም በቅርቡ
ጥያቄም ጠይቁ ለ አቦይ ሰብሀት
ፊት መሪ ለሆነው ለድንቁርና እሳት
ጥያቄም አቅርቡ ለ አቦይ ጸሀይ
ጮቤ ለሚረግጠው በ ሕዘቡ ሰቃይ

*
ዳይሰፖራም ጠይቅ አንተም ተጋርደሀል መደናቆር ይብቃ
በ አንደነት እንቁም የወያኔ ጭፍራ ሴራው እንዲያበቃ።
እንቢኝ በይ ሴቲቱ እንቢኝ በል ወጣቱ እንቢኝ በል ወገኔ
በርቀት መልሰው አጠገብህ ሳይደርሰ የወያኔን ኩነኔ።

በቸር ይግተምን ። አሰተያየት ቢኖሮት በዚህ መላክ ይችላሉ ኢሜል ፤- mwl200825@yahoo.com
ኢትዮጲያ ለዘላለም ትኖራለች !!

 

comment_stage_5

The post ተደናቁሮ ለማደናቆር የመረጠ ሰርአት ማነው? – ሊቁ እጅጉ appeared first on Zehabesha Amharic.


የሕዝበ ሙስሊሙ ትግል ወደ ሕዝባዊ እምቢተኝነት ማደጉን ድምጻችን ይሰማ አስታወቀ

$
0
0

Muslim in ethiopia
ለ 3 አመታት በተለያዩ የሰላማዊ ትግል ዘዴዎች መብቴን አክብሩ ሲል የቆየው ህዝበ ሙስሊም የህዝብን ድምፅ ለመስማት ፈቃደኛ ያልሆነው የሃገራችን መንግስት በቀጣይ የህዝብን ድምፅ ይሰማ ዘንድ ወደሚያስገድዱ ህዝባዊ እንቢተኝነት ትግሉ መሸጋገሩን ድምፃችን ይሰማ አስታውቋል፡፡

የመግለጫው ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ይቀርባል፡-

ሕዝብ የአንድ አገር መሠረት ነው፡፡ የአገር ምሰሶዎች የሚተከሉትም በህዝብ ላይ ነው፡፡ ስለዚህ ‹‹ሕዝብ ለአንድ አገር ሕልውና ዋነኛው ምንጭ ነው›› ብንል በእርግጥም አንሳሳትም፡፡ የመንግስት ተቋማትም ሆነ መንግስት ራሱ የመቋቋሚያ ዓላማው ህዝብን ማገልገል፣ የህዝብን ፍላጎት ማስፈጸም ነው፡፡ ይህ ሳይሆንለት ሲቀር ህዝብ ይቀየማል፤ ይቆጣልም፡፡ መብቱን በተለያዩ መንገዶች መጠየቅ ይጀምራል፡፡ ኢትዮጵያዊው ሙስሊምም ላለፉት ሶስት ዓመታት ሲያደርግ የቆየው ይህንኑ ነው
ትግል የራሱ ደረጃዎች ያሉት ሂደት ነው፡፡ በለዘብተኛ አቤቱታ ይጀምራል፡፡ ድርድሮችን ያልፋል፡፡ ጠንከር ያሉ የመብት ጥየቃ ሂደቶችን ያሳልፋል፡፡ ጥያቄውም ወደትግል ይቀየራል፡፡ መስዋእትነቶች ይከፈሉበታል፡፡ እያዳንዷ መስዋእትነት በራሷ ለትግሉ የሚኖረውን ቁርጠኝነት እና ወኔ እየጨመረች ትሄዳለች፡፡ አሁንም ችግሩ ካልተፈታ ህዝብ ያገለግለው ዘንድ ራሱ በሾመው አካል ላይ ተስፋ መቁረጥ ይጀምራል፡፡ የአገሪቱ ተቋማት ዋነኛ ባህሪያቸውን ለውጠው በደልን የማገልገል ሚና መወጣት በቀጠሉ ቁጥር የህዝቡም ቁርጠኝነት በዚያው ልክ እያደገ ይመጣል፡፡
የአንድ መንግስት ህልውና በእሺተኛ ህዝብ ፍቃደኝነት ላይ የተንጠለጠለ ነው፡፡ ሕዝብ ሲመረውም ‹‹መብቴ ይከበርልኝ›› ከሚል ጩኸት ‹‹መብቴን ካላከበርክ እኔም….. !›› ወደሚል ዛቻ መሄዱ አይቀሬ ነው፡፡ ይህን ጊዜ ሕዝቡ ‹‹ትብብር የመንፈግ ትግል ውስጥ ገባ›› ይባላል፡፡ ይህ ዓይነቱ ትግል ውጤታማ መሆኑ አይቀሬ እንደሆነ የዘርፉ ምሁራን አጽንኦት ሰጥተው ያስተምራሉ፡፡

አዎን! በጨዋ ደንብ እና በአንጸባራቂ ሰላማዊ ስነ ምግባር ለሶስት ዓመታት መብቱን ሲጠይቅ እና ሲታገል የቆየው ኢትዮጵያዊው ሙስሊም ‹‹መብቴ ይከበርልኝ›› ከሚል ያልተሰማ ጥያቄው ‹‹መብቴን ካላከበርክ እኔም….. !›› ወደሚልበት የትግል ምዕራፍ ላይ እነሆ ደርሰናል! ሰሞኑን ይህንኑ አስመልክቶ የምንለው ይኖራልና ሁላችንም ቃል የገባንበትን ትግል እስከድል ደጃፎች ለማድረስ ወገባችንን እናጥብቅ፤ ድልም ከአላህ እንጂ ከሌላ አይደለምና!
ትግላችን እስከድል ደጃፎች በአላህ ፈቃድ ይቀጥላል!

ድምጻችን ይሰማ!
አላሁ አክበር!

The post የሕዝበ ሙስሊሙ ትግል ወደ ሕዝባዊ እምቢተኝነት ማደጉን ድምጻችን ይሰማ አስታወቀ appeared first on Zehabesha Amharic.

Health: የአረንጓዴ ሻይ የጤና ጥቅሞች

$
0
0

Green Tea

(በዶ/ር ሆነሊያት ኤፍሬም ቱፈር)

የሰዉነት ክብደትን ለመቀነስ
አረንጓዴ ሻይ የሰዉነት ክብደትን እና የተከማቸ ስብን የማስወገድ አቅም አለው።

ለስኳር ህመም
የስኳር መጠንን ባለበት ለመቆጣጠር ይረዳል።

ለልብ ህመም
ተመራማሪዎች እንደሚያስረዱት ከሆነ የደም ስር ግድግዳን እንደተፍታታ እንዲቆይ እና የተከማቸ ደም እንዳይኖር በማድረግ ከድንገተኛ ልብ ህመም ይከላከላል።

ለኮሌስቴሮል
ጠቃሚ ያልሆነውን የስብ አይነት ከደም ውስጥ በመቀነስ ጠቃሚው ስብ እንዲበዛ ይረዳል።

ለደም ግፊት
በመደበኛ ሁኔታ አረንጓዴ ሻይን መውሰድ የደም ግፊት መጨመርን ይከላከላል።

ፀረ ባክቴሪያ እና ፀረ ቫይረስ
ይህ የሻይ አይነት ባክቴሪያ እና ቫይረሶችን ማጥፋት እንደሚችል ተመራማሪዎች ይናገራሉ። ለጉሮሮ ህመም፣ ለጥርስ እና የአፍ ውስጥ ኢንፌክሽኖች ፍቱን መሆኑንም አሳውቋል።

ለቆዳ ጤንነት
የቆዳ መሸብሸብን ይከላከላል በፀሃይ እንዳይጎዳም ይረዳል።

ጤና ይስጥልኝ

The post Health: የአረንጓዴ ሻይ የጤና ጥቅሞች appeared first on Zehabesha Amharic.

ዘ-ሐበሻ –መጋቢት 2007 ቅጽ VI ቁጥር. 72

በኢትዮጵያ ሰላም የሚያመጣ የአማራ የተራድኦና የዕርቅ ድርጅት ያስፈልጋል- (ፕ/ር ጌታቸው ኃይሌ)

$
0
0

Getachew Haileመነሻዬ የሻለቃ ዮሴፍን ትግል ይቀጥላል የሚል ርእስ የሰጠው ዘንድሮ አዲስ አበባ ላይ የታተመው መጽሐፍ ነው። ያነበብኩት ቁጭትና ንዴት እየተሰማኝ ነበር። ለዚህ ሰውነት የሚጎዳ ስሜቴ ዋናው ምክንያት የመጽሐፉ ደራሲ እንደገለጸው፥ ጀኔራል አማን አንዶም የተሻለ ለውጥ ለማምጣት ዕድሉ እጃቸው ላይ ወድቆ ሳለ፥ የተሳለ ቢላዎ የያዙ አራጆች ወደቄራ እንደሚነዱት የደለበ በሬ ወደሚገደሉበት ሁኔታ ሲመሯቸው፥ ዓይናቸው እያየ እጃቸውን ሰብስበው በጥሞና መሄዳቸው ነው። ደራሲው እንደሚለው ራሳቸው ጀኔራሉ የመረጧቸው ረዳቶቻቸው ወጣት የጦር መኳንንት (አንዱም ደራሲው ነበር) የደረሳቸውን መረጃ እየጠቀሱ ሲያስጠነቅቋቸው ሰልችቷቸው ኖሮ፥ “ስሙ፣ እኔ የምሰራውን አውቃለሁ፡ ዝም ብየ ባልተጣራ መረጃ አልጓዝም፡ እንድታውቁ የምፈልገው፣ አማን ማለት ደርግ ነው፣ ደርግ ማለት አማን ነው፡ ወደፊት በዚህ ጉዳይ ላይ ምንም ዓይነት ነገር እንድታነሱብኝ አልፈልግም፡ እዚያም ያሉት እኮ ከማንም የሚያንሱ አይደሉም” አሏቸው። እንደ ሰንጠረዥ፥ እንደ ኳስ ጨዋታ፥ በአንድ ስሕተት የተመኘነው ለውጥ ገደል ገባ።

የዚህ ግራ የገባው የጀኔራሉ አቋም ምክንያቱ ምን እንደሆነ ወጣቶቹ ረዳቶቻቸው በደረሳቸው መረጃ ዐውቀውታል፤ ዶክተር በረከተ አብ ሀብተ ሥላሴ ረዳቶቻቸውን ትተው ከደርግ ጋር እንዲተባበሩ ስለመከራቸው ነው። በበረከት አስተያየት ጊዜው ሲደርስና ሲያመች ደርጎችን ማስወገድ ይቻላል፤ እነዚህን ግን አይቻልም። (ባይቻልና ለውጡን እነዚህ የአካዴሚ ምሩቆች ቢመሩት ምን ይሆን ነበር?)

ልጽፍ ያሰብኩት እንኳን በጀኔራል አማን ስሕተት ስለባከነው ዕድል ሳይሆን፥ ጀኔራሉ ለእርዳታ የመለመሏቸው ወጣት የጦር መኳንንት ማንነት ስለሰጠኝ ትዝብት ነው። እነዚህ የጦር መኳንንት የጀኔራል አማንን ችሎታና በጦር ሠራዊቱ ዘንድ ያላቸውን ተወዳጅነት በመተማመን እሳቸውን መሪ አድርገው ንቅናቄ ለማካሄድ ሞክረው ነበረ። የነዚህ ወጣት ሹማምንት ማንነት ሁለት ቁም ነገሮችን አሳይቶኛል። መጀመሪያ ስማቸውን፥ ገጽ 38 ላይ እንደተዘረዘረው ልቅዳው፤ የዚያን ጊዜ ማዕርጋቸው የሁሉም ሻለቅነት ነበር።

አብዱላሂ ዑመር
ሽመልስ መታፈሪያ
አበራ ባንቲዋሉ
ሁሴን አሕመድ
ዮሴ ያዘው
ካህሣ ወልደአብ
ጎሹ ወልዴ
እምቢበል አየለ

እነዚህ ወጣት የጦር መኳንንት ከተለያየ ጎሳ መምጣታቸውን ስማቸው ይመሰክራል። ፍጹም የአማራ ስም ያላቸው በቍጥር በዛ ይላል። ግን ሁሉም አማሮች ናቸው ለማለት ፈጽሞ አይቻልም። ሌላው ቢቀር ጎሹ ወልዴ አማራ እንዳይደለ እናውቃለን። የነዚህ ወጣቶች በአንድ ቡድን ተስማምቶ መሰለፍ ሁለት ቁም ነገሮችን ያስገነዝበናል፤ አንደኛ፥ የአፄ ኃይለ ሥላሴ መንግሥት ጎሰኝነት አልነበረበትም፤ ሁሉንም ለሀገራዊ ቁም ነገር በአንድ ዓይነት ሙያ እኩል አሰልጥኖ ለግዳጅ እኩል አስሰልፏቸዋል። ሁለተኛ፥ ወጣቶቹም ለውጥ ለማምጣት አብረው ሲዶልቱ፥ ጎሰኝነት ኢትዮጵያውያንነታቸውን አላሰናከለባቸውም፤ ለአንድ ዓላማ በመተማመን በአንድነት ቆመዋል። ለአንደኛውም ሆነ ለሁለተኛው ቁም ነገር አለቃቸውና መሪያቸው ሊያደርጉት ያሰቡት አማን አንዶም ከማን ጎሳ እነደነበረ እናስታውስ።

ሕዝብ የተመኘውን ለውጥ (ዲሞክራሲን) ትተው የጎሰኝነትን መርዝ የረጩብንና አሁን ደግሞ ሀገሪቷን የወረሷት ጉደኞች እስኪጨፍሩብን ድረስ፥ እኛ የምናውቃት ኢትዮጵያና መንግሥቷ ከጥንት ጀምሮ እንደዚህ ነበሩ። የወረስናት ኢትዮጵያ ይኸን ትመስል ነበር፤ ነበር፡ ነበር!

የጉደኞቹ መርዝ መጀመሪያ ጊዜ የተረጨው በተማሪዎቹ ንቅናቄ ውስጥ እንደነበረ እናስታውሳለን። ደርግ ድጋፍ ያገኘ መስሎት በኋላ እስኪያፈገፍግ ድረስ ኮሚኒዝም የሚባል የማባባሻ ዘዴ ከሶቬት ዩኒየን እያመጣ አፋፋመው። በፍልስፍናው ላይ ያሰበበትም ያላሰበበትም ሁሉም እኩል ሆይ አለለት። የሚያዳላን እንጂ ሁሉን እኩል የሚያይ አስተዳደርን ማን ይጠላል? ግን ፍልስፍናው “ኢትዮጵያ የጎሳዎች እስር ቤት ናት፤ አሳሪዎቹም አማሮች ናቸው” የሚል መሆኑ ቀደም ብሎ በፍልስፍና ደረጃ ቢታወቅም አሁን ሥር እየሰደደና በሥራ ላይ ሲውል አሠጋ። ይኸን ያነሣሁት ያልተሰማ አዲስ ታሪክ ለማሰማት ሳይሆን፥ ቀጥሎ ወደማነሣው ትዝብት እንዲያሸጋግረኝ ነው።

ወጣቶቹ የጦር መኳንንት የጀኔራል አማንን መሪነት ካጡ በኋላ፥ የለውጡን አመራር ከደርግ ቀምቶ ቀና አቅጣጫ ለማስያዝ ምን ማድረግ እንዳለባቸው ብዙ ጊዜ በሰዋራ ቦታ ላይ እየተገናኙ ተወያይተዋል። በአንዱ ስብሰባቸው ላይ አብዱላሂ (ዑመር) እንዲህ አለ፤

ይህንን በሀገራችን ላይ የተፈጠረውን አሰቃቂ ሁኔታ፣ እኛ አሁን ባለንበት ደረጃ፣ ልንለውጠው እንደማንችል አምናለሁ፡ ሆኖም ደግሞ፣ ይቅርታ አድርጉልኝና፣ እኔ በአደሬነቴ ሳየው፣ በሀገራችን ውስጥ ጭቆና አልነበረም ለማለት አልደፍርም፡ ይኽንንም ስል፣ ለውጡ አሁን በተያዘው መንገድ ፣ በእስራትና በጭፍጨፋ፣ ይቀጥል ማለቴ አይደለም፡ ነገር ግን፣ እኛ ምንም ማድረግ ካልቻልን፣ ምናለበት ለአንድ አመት ያህል፣ አብረን እየሠራን ብናየው፡ ደርግም እኰ፣ ሲረጋጋ፣ ምናልባት፣ ሕዝብ የሚቀበለውን ለውጥ፣ [ሊ]ያመጣ ይችል ይሆናል፡ ያ ካልሆነ ደግሞ፣ የዚያን ጊዜ እንደገና እንሞክራለን፣

ልብ እንበል፤ የጀኔራል መንግሥቱ ንዋይ አመፅ ለውጥ ለማምጣት ነበር። የ“ትግል አይቆምም” ጸሐፊና ጓደኞቹም ያድሙ የነበረውና ትግሉን የቀጠሉት ለውጥ ለማምጣት ነበር። በሀገራችን የፖለቲካ ለውጥ ማስፈለጉን ማንም አይክደውም። ሕልማችን ጥንታዊት አገራችን ዘመናዊ ዲሞክራሲ እንዲሰፍንባትና ሁላችንም በነፃነትና በእኩልነት እንድንኖር ነው። በአጭሩ ዲሚክራሲን እንደምንፈልገው አድርገን እንቀርጸዋለን እንጂ በአሁኑ ዘመን ተወዳዳሪ አይቀርብለትም።

አብዱላሂ ዑመር ግን የለውጡን አስፈላጊነት ያየው ከዲሞክራሲና ከጠቅላላው የኢትዮጵያ ሕዝብ አንጻር ሳይሆን፥ ከጎሰኝነት ነው። በእሱ አእምሮ ለውጥ የሚያስፈልጋቸውና የማያስፈልጋቸው ኢትዮጵያውያን አሉ። የኢትዮጵያን ሕዝብ በአእምሮው ውስጥ ለውጥ ከሚያስፈልገውና ከማያስፈልገው ከፍሎታል። ይህ እምነት የአንድ አደሬ ነው ወይስ እንደዚህ የሚያምኑ ሌሎችም አሉ? አጭሩ መልስ የወያኔዎችን የጥርቃሞ ፓርቲ (ኢሕአዴግን) ዘርዝሮ ማየት ነው። “እነዚህ ወያኔ የፈጠራቸው ተቀጽሎዎች ናቸው” ብንልም፥ በፖለቲካው ደስተኞች የሉባቸውም ለማለት አንደፍርም። አሉባቸው። በሕዝብና በመንግሥት ዘንድ ሥር ሰድዶ የነበረው ኢትዮጵያዊነት እንዳይፋፋ፥ መጀመሪያ የተማሪዎቹ ንቅናቄ፥ ቀጥሎ ደርግ፥ አሁን ደግሞ ወያኔዎች ወኻ ከልክለው አጠውልገውታል። በምትኩ ጎሰኝነትን ስለተከሉበት፥ የትግሉ መልክ ተለውጧል። ለዚህ ነው የሀገር ወዳዱ የትግል ሰይፍ ሁለት ስለት ያለው መሆን ያለበት፤ አንዱ ጎሰኝነትን መጒመጃ ሲሆን ሁለተኛው ለጥንቱ (ለዲሞክራሲ) ትግል መንገዱን መጥረጊያ ይሆናል።

በጎሰኞቹ እምነት መሠረት፥ ለውጥ የያስፈልጋቸው (“” አጥብቀን እንያዝ) የተባሉት እነማናቸው? “ኢትዮጵያ የጎሳዎች እስር ቤት ናት፤ አሳሪዎቹም አማሮች ናቸው” ከተባለ፥ ለውጥ የማያስፈልጋቸው አማሮቹ መሆናቸው ነው። ጉዳዩ ለውጥ የማያስፈልጋቸውን ኢትዮጵያውያን ለይቶ ከማወቅ ላይ አላቆመም። የችግሩ ምክንያት (የኢትዮጵያን ጎሳዎች አሳሪዎችና ጨቋኞች) እነሱ ስለሆኑ፥ ለውጥ

ለማምጣት መፍትሔው “ለውጥ የማያስፈልጋቸውን” መምታት ነው ከሚለው ውሳኔ ተደርሷል። ይኼ እኮ ያንን ሁሉ የኢትዮጵያ ጎሳ በአማራው ሕዝብ ላይ በጠላትነት ማስነሣት፥ የአማራው ሕዝብ ሠላሳ ሚሊዮን ከሆነ ሕዝብን እርስ በርስ ማጫረስ ነው!!
መፍትሔው ምንድን ነው? አማራውን ታጠቅ ማለት የባሰውን ማፋጀት ይሆናል። በዘር መደራጀት ደግሞ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን የታሪክ ተቺዎች ርእስ አድርጎ መቅረት ይሆናል፤ በተለይ በአማራው ላይ አያምርበትም። ግን በዘር፥ በሃይማኖት፣ በጾታ፥ በቀየ፣ በሙያ መደራጀት ፍጹም አስከፊ ርምጃ ነው ወይ? መልሱ እንደ ድርጅቱ ዓላማ ነው፤ ሰዎች ድርጅት የሚያቋቁሙት ወይ ራሳቸውን ለመጠበቅና ባህላቸውን ለማዳበር፥ ወይም ሌላውን ለማጥቃት፥ የፖለቲካ ፓርቲ ለመሆንና በመንግሥት ንብረት የራስን ወገን ብቻ ለመጥቀም፥ ወይም የሌላውን ዘር፥ የሌላውን ሃይማኖት፣ ባለሌላውን ጾታ፥ የሌላውን ቀየ ነዋሪዎች፥ የሌላውን ሙያ አባላት ለማጥቃት ይሆናል። ይኼኛው ዓይነት ድርጅት በሕግ መከልከል፥ መኰነንም አለበት። ለመረዳዳት፥ ከዚያም አልፎ ሌሎችን ለመርዳት ከሆነ ግን በሕግ መፈቀድ፥ መደገፍም አለበት።

እንዲያውም እኮ፥ የአንድ ሀገር የዲሞክራሲ መሠረት እንደዚህ ያሉ የተራድኦ ሕዝባዊ ድርጅቶች መብዛትና መጠናከር ነው። በአሜሪካን አገር የጥቁሮች ሰብአዊ መብት ሊከበር የቻለው ጥቁሮች ለመብታቸው ማስጠበቂያ ባዘጋጁት ድርጅት ጥረትና መሪነት ነው። የሴቶች ማኅበር የሴቶችን መብት ከማስከበር አልፎ፥ ሴቶች በፖለቲካ እንዲሳተፉ ቀን ከሌት እየሠራ ነው። በምርጫ ጊዜ፥ “የእስፓንኛ ተናጋሪዎች ድምፅ ወዴት ይሄድ ይሆን?” የሚለው ጥያቄና መልሱ የጋዜጦቹን የመጀመሪያ ገጽ ይይዛሉ።

የተጠናከረ የአማርኛ ተናጋሪዎች (የአማሮች) የተራድኦና የዕርቅ ድርጅት ቢኖር፥ ለሀገሪቱ የሚሰጠው ጥቅም ወሰን አይኖረውም። እግረ-መንገዱንም በአማራነታቸው በየቦታው በተናጠል ስለሚጠቁት ድምፃቸውን ማስተጋባትና ለመርዳትም ፈጥኖ ለመድረስ ይችላል። ዋና ዓላማው ግን፥ ዕርቀ ሰላም ማውረድና ለዲሞክራሲ መዳበር አመርቂ አገልግሎት መስጠት ነው። የአማሮች ቊጥር ብዙ ነው ብለናል፤ በዚያ ላይ በደጉም በክፉውም ምክንያት ከሌሎቹ ጎሳዎች ጋር በደም የተሳሰረ ስለሆነ፥ ለአንድነት፥ ለነፃነት፥ ለእኩልነት የቆመን የፖለቲካ ተወዳዳሪ ዘርና ሃይማኖት ሳይለይ ለመደገፍ ዝግጁ ነው። ለቍጥረ-ትንሽ ጎሳዎችም መከታ ይሆናል። ኢትዮጵያን ከዘራፊዎች ነፃ የሚያወጣት ፓርቲ የአማራው የተራድኦና የዕርቅ ድርጅት የሚደግፈው ፓርቲ መሆኑን ወያኔዎች ስለሚያውቁ፥ አማራ እንዲደራጅ አይፈልጉም። በአንድ በኩል፥ “አማራ በዘር አይደራጅም” እያሉ አማራውን የሚያደናግሩትን፥ በሌላው በኩል፥ “አማራ እንደገና ሊገዛችሁ ነው” እያሉ ጎሳዎችን ከሥጋት ላይ የሚጥሉትን የሚሽረው የአማራ የተራድኦና የዕርቅ ድርጅት ነው።

አማርኛ ተናጋሪው እንዳይደራጅ የተጣለበትን የውጪ ተጽእኖና የውስጥ የሕሊና ደንቃራ አንሥቶ ለሦስት ግዴታ መደራጀት አለበት፤

አንደኛ፣ ከጎሳዎችና ከድርጅቶቻቸው ጋር ውይይት (dialogue) ለመክፈት። በውይይቱ ብዙ ነገሮች ይነሣሉ። አለመግባባት ካለ፥ ምክንያቱ ምንድንነው? መቸም ወያኔዎቹ ጎሳዎችን በአማራው ላይ ለማስነሣት የቀናቸው፥ ሻለቃ አብዱላሂ ዑመርም፥ “እኔ በአደሬነቴ ሳየው፣ በሀገራችን ውስጥ ጭቆና አልነበረም ለማለት አልደፍርም” ያለው ያለምክንያት ነው ለማለት አልደፍርም። ምክንያቱ ምንድንነው? መሰማት አለበት። አማራውም ላለበት ክስ ሕዝባዊ ፍርድ ቤት አቋቁመን በሰባት ወይም ዘጠኝ ገለልተኛ ዳኖች ፊት መልስ መስጠት አለበት። ከሳሾችም ተከሳሾቹም የምሁራን ምስክሮች እየጠሩ ስለሚሟገቱ፥ ፍርድ ቤቱ ሕዝብ የሚታዘብብበር ትልቅ የምሁራን ጉባኤ ይሆናል። የተረታ ይክሳል፤ የረታ ይካሳል።

ሁለተኛ፣ በምርጫ ጊዜ ኢትዮጵያ-አቀፍና ለኢትዮጵያውያን ሁሉ የሚጠቅም የኢኮኖሚ እድገት አጀንዳ ያለው ፓርቲ የሚያቀርበውን ተወዳዳሪ ለመደገፍ። ተወዳዳሪው የየትኛውም ጎሳ አባል፥ የማንኛውም ሃይማኖት ተከታይ ሊሆን ይችለል። እንዲህ ያለ ድጋፍ ለመስጠት የድርጅቱ ቃል ኪዳን ይሆናል።

ሦስተኛ፣ ማንም ኢትዮጵያዊ በቋንቋው፥ በጾታው፥ በሃይማኖቱ ምክንያት መንግሥት ሲያጠቃው ፈጥኖ ለመድረስ። ድርጅቱ ሲቋቋም፥ ለምሳሌ ለተፈናቀሉት አማሮችና መሬታቸውን ለከበርቴ ተነጥቀው ለተባረሩት አኝዋኮች አለኝታ ይኖራቸዋል።

አማርኛ ተናጋሪው ኢትዮጵያን ለማዳን ከአባቶቹ የወረሰው የታሪክ ግዴታ አለበት። ግዴታውን ለመወጣት ብዛቱና ታሪኩ ይረዳዋል። ታሪካችንን ስንመረምረው፥ ከአክሱም ዘመነ መንግሥት ጀምሮ የኢትዮጵያን መንግሥታዊ ሥልጣኔ የመሠረተውና ያዳበረው፥ እንደ ግዕዝ ሴማዊ ቋንቋ ከሚናገረው ክፍል የሆነው የአማራው ሕዝብ ነው። ዛጔዎች ሥልጣኑን ለጥቂት ዓመታት ቢወስዱትም ያንኑ የአማራ ሥልጣኔ እያዳበሩ ተጓዙ እንጂ ሌላ ሥልጣኔ አላመጡም። አፄ ይኩኖ አምላክና ወራሲዎቹ ሥልጣኑን አስመልሰው፥ የጥንቱን ሥልጣኔ መጀመሪያ በሸዋ-አምሐራ፥ በኋላ በጎንደር አስፋፉት። አፄ ዮሐንስም የሥልጣኑን ማእከል ወደትግራይ አመጡት እንጂ፥ አክሱም ላይ የተመሠረተውን ሥልጣኔ አልለወጡትም። የዳኝነት ችሎታቸውን የሚያካሂዱት በአማርኛ ነበር። ንጉሡና በሳቸው ዘመን የነበሩ ሌሎቹ የትግራይ ባለሥልጣኖች ከውጭ አገር ጋር ይጻጻፉ የነበረው በአማርኛ ነበር። ደብዳቤዎቹ አሁንም በውጪ ሀገር መዛግብት ተከትተው ይገኛሉ።

አማራው ግዴታውን ለመወጣት የመጀመሪያ እርምጃው የተራድኦና የዕርቅ ድርጅት ማቋቋም ነው። የድርጅቱ መቋቋም ኢትዮጵያውያንን ሁሉ የሚያስደስትና ተስፋ የሚያበሥር (የወያኔን ቡድን ብቻ የሚያሠጋ) መሆኑ በግልጽ ቃላት መቅረብ አለበት። አሁን አገራችን ባለችበት የፖለቲካ ሁኔታ ስናየው፥ “አማራ መጣብህ” የሚለውን የወያኔ ማስፈራሪያ ከአማራ የተራድኦና የዕርቅ ድርጅት ሌላ ሊያሳፍርና ውድቅ አድርጎ ሰላም ሊያወርድ የሚችል ኀይል የለም።

ለዚህ ደርሰት አስፈላጊነቱ ስላልታየኝ፥ “አማራ ማነው?” ከሚል፥ መልሱ ብዙ ገጽ ከሚፈጅ ጥያቄ ውስጥ አልገባሁም። ሁሉም ራሱን ስለሚያውቅ፥ “አማራ ነን” የሚል ሁሉ በሙሉ አባልነት፥ በድርጅቱ የዕርቅና የሰላም ዓላማ የሚያምን ግን “አማራ ነኝ” የማይል ኢትዮጵያዊ ደግሞ በደጋፊ አባልነት መመዝገብ ይችላል።

ሳልረሳው፤ ለዚህ ጽሑፍ መነሻ የሆኑት ወጣት የጦር መኳንንት ጀኔራል አማን አንዶምን መሪ አድርገው ደርግን ለመጣል ሳይችሉ ሲቀሩ፥ ከአማን ሞት በኋላ ሌላ ሰፋ ያለ ሙከራ አድርገው ነበር። መሪዎቹ ያድሙ ከነበረብረት ቦታዎች አንዱ ኢንጂኔር ሞገስ ቡሩክ ቤት ሲሆን፥ ባለቤቱ ወይዘሮ ደረጃሽ ወርቅ ቅጣው ብትያዝ የሚደርስባትን እያወቀች ምንም ቅሬታ አላሳየችም። ያም ሲከሽፍ፥ ሞገስ ቡሩክ፥ ተፈሪ ተ/ሃይማኖት፥ ጸሐፊው ዮሴፍ ያዘው ቤተ ሰቦቻቸውን የትም በትነው፥ ኬላ ሰብረው ወጥተው ትግላቸውን እስከመጨረሻው በትጥቅ ትግል ቀጠሉ። የሻለቃ ዮሴፍ ያዘው ባለቤት ወይዘሮ ወይንሸት መኰንን ባሏን የሸኘችው፥” ብቻ እግዚአብሔርን የምለምነውና አንተንም አደራ የምልህ፣ ተይዘህ በዚህ ሳጥን (ጣቷን ወደቲቪው እየጠቆመች) ውስጥ እንዳላይህ ነው” በሚል መሪ ቃል ነበረ፤ የጀግና ሚስቶች!! ተፈሪ ወደቀ፤ ሁለቱ ከዓሥራ ሰባት ዓመት በኋላ ከሚስቶቻቸው ጋር ሊገናኙ ቻሉ። ታሪካቸው የሚያስገርምና የሚመዘገብ የኢትዮጵያ ታሪክ ነው።

የዚህ ጽሑፍ ትኩረት ግን አማራውን ለዕርቅና ለሰላማዊ ለውጥ የማደራጀት ጥሪ ነው። ሞረሽ ወገኔ የሚባል ድርጅት እንዳለ አውቃለሁ። ማሳሰቢያየ በሐሳብ ደረጃ ተደንቆና ተኰንኖ እንዳይቀር፥ አስኳሉ ካለ አስኳሉን ማጎልበት ይቻላል።

– See more at: http://satenaw.com/amharic/archives/5335#sthash.jbZxJjIE.dpuf

The post በኢትዮጵያ ሰላም የሚያመጣ የአማራ የተራድኦና የዕርቅ ድርጅት ያስፈልጋል- (ፕ/ር ጌታቸው ኃይሌ) appeared first on Zehabesha Amharic.

ምን ታቅዶ ምን ተፈፀመ?፣ …የቀጣይ የትግል አቅጣጫ ምን ይሁን? (ኤርሚያስ ለገሰ)

$
0
0

( ክፍል አንድ)

daniel ermiasምርጫ 2007 አስመልክቶ ገዥው መደብ “ምን አስቦ ምን ይፈጵማል ” የሚለውን መነጋገር ከጀመርን ግማሽ አመት አለፈው። ባለፋት ወራት በርካታ የተጠበቁም ያልተጠበቁም ድርጊቶች ተፈጵመዋል። ከእነዚህ ድርጊቶች ወሳኝ የሚባሉትን ነቅሶ በማውጣት መመልከት ያስፈልጋል። በመሆኑም ባለፋት ጊዜያቶች ይፈፀማሉ ብለን የገመትናቸውን ግምገማ እና በቀጣይ ወራት ሊፈፀሙ የሚችሉ እቅዶችን ትንበያ አስተሳስሮ ማየት ተገቢ ይሆናል። ባለፋትም ሆነ በቀጣይ ጊዜያት የሚኖሩ ተግባራት በመለየት መከራከር፣ መወያየትና በመሰረታዊ ጉዳዬች ላይ የጋራ መግባባት ፈጥሮ መንቀሳቀስ ወሳኝ ይሆናል።

እያንዳንዱ ባለድርሻ አካል በአጀንዳው ዙሪያ መነጋገር መቻሉ የተለያዩ ጠቀሜታዎች ይኖሩታል። በአንድ በኩል በኢትዬጲያ የዲሞክራሲ ስርአት ግንባታ ትግል የደረሰበትን ደረጃ ለመመልከት ያስችላል። በሌላ በኩል እንደ ግለሰብ ” የእኔ አስተዋጵኦ ምን ነበር? ፣ ከዚህ በኃላስ ከእኔ ምን ይጠበቃል?” የሚለውን ወደ ራሱ ውስጥ እንዲመለከት እድል ይከፍትለታል። በመሆኑም እነዚህን ከላይ የተጠቀሱ ጠቀሜታዎች ታሳቢ በመውሰድ እንደ አንድ ኢትዬጲያ ውስጥ የዲሞክራሲ ስርአት እንዲመጣ የሚመኝ ግለሰብ ያለፋትን ለመገምገምና ቀጣዩን ለመተንበይ የሚከተሉትን የመነሻ ሀሳቦች ለማንሳት ወደድኩ። እነዚህ አስተያየቶች የየትኛውንም የፓለቲካ ፓርቲ ሆነ የሚዲያ ተቋም ( “የእኔ የሆነውን ” ኢሳት ጨምሮ) አቋም የሚመለከት አይደለም። ከዚህ በተጨማሪም ግምገማውም ሆነ ትንቢቱ እንደመነሻ ለውይይት የቀረበ በመሆኑ ያገባኛል ባዬች በተሻለ ሁኔታ እንደሚያዳብሩት ታሳቢ ተወስዷል።

በዚህ ክፍል አንድና በቀጣዩ ክፍል ሁለት ” ምን ታቅዶ ምን ተፈፀመ?” የሚለው ላይ ብቻ ለማተኮር እሞክራለሁ። በሶስተኛው ክፍል “በቀጣይ ገዥው መደብ ምን ያስባል፣ የቀጣይ የትግል አቅጣጫው ምን ይሁን?” የሚለው ላይ የመነሻ ሀሳብ ይቀርባል። ” ምን ታቅዶ ምን ተፈፀመ?” በሚለው ክፍል ገዥው መደብ የምርጫው ሂደት ትኩረት እንዲነፈገው ያደረገበት ምክንያት፣ ህብረተሰቡን የሚያነቁ አካላት ላይ የተወሰደ እርምጃ፣ ምርጫ ቦርድን የኢህአዴግ ክንፍ ለማድረግ የተወሰዱ እርምጃዎችን፣ የፓርቲ በአላትን እንደ ቅስቀሳ ስልት የመጠቀም ስትራቴጂን፣ የሀይማኖት ተቋማት እና አመራሮች ላይ ገዥው መደብ አቅዶ የፈፀማቸውን እንመለከታለን።

ሀ• ምን ታቅዶ ምን ተፈፀመ?
1• ለምርጫው ሂደት ትኩረት የመንፈግ ስትራቴጂ

በኢትዬጲያ አዲሱ አመት መጀመሪያ ወር ላይ ከሲሳይ አጌና ጋር በነበረን ቆይታ ቅድሚያ ትኩረት ሰጥተን የተነጋገርነው ህውሀት/ ኢህአዴግ ቀጣዩ ምርጫ በሀገሬው ህዝብና የአለም አቀፍ ተቋማት እንዳይነገር ትኩረት መንፈግ ስትራቴጂ እንደሚከተል ነበር። የዚህ ስትራቴጂ መነሻ በምርጫ ዘጠና ሰባት ኢህአዴግ ለምን ተሸነፍን የሚለውን ሲገመግም የተቀመጠ አቅጣጫ እንደሆነ ለማመላከት ተሞክሯል። በ1997 አ• ም• የምርጫው ሂደት በመስከረም ላይ በይፋ ተጀምሮ ነበር። ካልተሳሳትኩ በትምህርት ፓሊሲው ላይ በፓለቲካ ፓርቲዎች መካከል ክርክር የተደረገው በመስከረም ወር ላይ ነበር። በተከታታይ ወራትም የተጋጋለ የምርጫ ክርክር በመካሄዱ ህዝቡ የፓለቲካ ፓርቲዎችን አላማ መገንዘብ ቻለ። እንደ እኔም ሆነ ኢህአዴግ እምነት የምርጫ 97 የፓለቲካ ድባብ ከግራ ወደ ቀኝ የገለበጠው በወቅቱ የተካሄዱት የምርጫ ክርክሮች ናቸው። ይህን አስመልክቶ የመለስ ትሩፋት ገጵ 301 ላይ የሚከተለውን ድምዳሜ ኢህአዴግ ማስቀመጡን ታመለክታለች፣

” … በምርጫ ክርክር ወቅት ኢህአዴግ ባልተዘጋጀበት ሁኔታ በሩን መበርገድ አልነበረበትም። ግንቦት ለሚካሄድ ምርጫ መስከረም ጀምሮ የሚዲያ ክርክር መካሄዱ ጥፋት ነበር።”
በመሆኑም የምርጫውን ሂደት ትኩረት መንፈግ የማይታለፍ ሆነ። አሁንም ሆነ ህውሀት በስልጣን ላይ እስከቆየ ድረስ ይህ ስትራቴጂ ተጠናክሮ ይቀጥላል። በምርጫ 2007 እያየነው ያለነው ይህንኑ ነው። እስከ ታህሳስ መጨረሻ ድረስ ስለምርጫ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ የሚወራ ነገር በመንግስት ሚዲያም ሆነ በገዥው መደብ ካድሬዎች አልነበረም። የምርጫ ክርክሩ የተጀመረው በዚህ ሳምንት ምርጫው ሊካሄድ ከሁለት ዲጅት በታች ቀናት ሲቀረው ነው። ይህም ቢሆን በሰአት ድልድሉ ገዥው መደብና ተላላኪዎቹ የአንበሳውን ድርሻ ወስደው ” አይኔን ግንባር ያድረገው” ቅስቀሳና ማስፈራሪያ ያደረጉበት ነበር። እንደዛም ሆኖ ከእነእጥረቱም ቢሆን የተቃዋሚ አመራሮች የተሻለ ነጥብ አስመዝግበው የወጡበት ነበር። ለዚህ እማኝ የሚሆነው በማህበራዊ ድረገጶች የተፈጠረውን መነቃቃት መመልከት በቂ ይሆናል። ከማህበራዊ ድረገጶች ወጥቶ በህብረተሰብ ደረጃ መነሳሳት ፈጥሯል ወይ? የሚለው ላይ የተሟላ መረጃ ስለሌለኝ ብዙ ማለት የሚቻል አይደለም። ይሁን እንጂ በምርጫ ለውጥ አይመጣም፣ መድብለ ፓርቲ ወደ መቃብር ከወረደ ቆይቷል ፣ ምርጫ ቦርድ የኢህአዴግ አንድ ክንፍ ነው፣… ወዘተ የሚለው አመለካከት በኢትዬጲያ ህዝብ ገዥ አመለካከት በሆነበት ሁኔታ የተለወጠ ነገር አለ ብሎ መገመት ማሞ ቂሎ ከመሆን የሚዘል አይደለም።

2• ህብረተሰቡን የሚያነቁ አካላትን ልክ የማስገባት ስትራቴጂ

ለዚህ ስትራቴጂ መነሻ የሆነውም የምርጫ 97 ውጤት ግምገማ ነው። በግምገማው የተደረሰበት ድምዳሜ የኢትዬጲያን ህዝብ ለመብቱና ነጳነቱ ለማታገል ወስነው የሚንቀሳቀሱ አካላትና ግለሰቦችን ” ዲሞክራሲያዊ ኢንስትሩመንት” በሚል አቅጣጫ “አብዬታዊና ዲሞክራሲያዊ እርምጃ ” መውሰድ የሚል ነበር። ይህ አብዬታዊ እርምጃ ባለፋት አመታት በሚያስደነግጥ ሁኔታ ተጠናክሮ ቀጥሏል። ይህ አይን ያወጣ የጭካኔ እርምጃ በኢትዬጲያ ህዝብ እየተለመደ ከመሄዱ የተነሳ ” ቀጣዩ ተረኛ እከሌ ፓርቲ፣ እከሌ ግለሰብ ነው!” የሚል ትንበያ የሚያሰጥበት አስፈሪ ደረጃ ደርሷል። እንደተባለውም ፓርቲዎችና ግለሰቦች እርምጃ ሲወሰድባቸው ” ምን አዲስ ነገር መጣ? ” የሚሉ አባባሎች ህብረተሰባችን ፀረ ዲሞክራሲን የመሸከም መጥፎ አዝማሚያ አሳይቷል። ይህ አስተሳሰብ ከገባንበት ፍጱም የድህነት አረንቋ ጋር መጃመሉ ስለማይቀር በሂደት እንደ ሀገር ብቻ ሳይሆን እንደ ሙሉ ሰው መቀጠላችንን ጥያቄ ውስጥ የሚከት ወደ መሆን መሸጋገሩ አይቀርም።
ወደ ስትራቴጂው ስንመለስ ከአጭር ጊዜ አኳያ እንደ ቡድን የመጀመሪያ ሰለባ የሆኑት ራሳቸውን ” የዞን ዘጠኝ ጦማሪያን” የሚል ስያሜ የሰጡት ወጣቶች ናቸው። እነዚህ ወጣቶች ላይ ገዥው መደብ ለምን ልዩ ትኩረት ሰጠ? የሚለውን መልሶ ማለፍ ተገቢ ይሆናል። የመጀመሪያው የቡድኑ አባላት ወጣት መሆናቸው ከሚፈጥርላቸው ጉልበት ባሻገር የተለያየ ፕሮፌሽን ባለቤቶች መሆናቸው ነው። የተለያየ ሙያ ባለቤት በመሆናቸው በሁሉም አቅጣጫ የገዥው መደብ ውሳኔዎች፣ እርምጃዎች፣ ፓሊሲዎችና ኩነቶችን ተከታትለው የመንቀፍ እድል ፈጥሮላቸዋል። በተለይ ራሱ ገዥው መደብ የሚፈጥራቸውን ኩነቶች ተገን አድርገው ( የህገመንግስት ቀን፣ የብሔረሰብ ቀን) የማስተማሪያ ስልት ቀይሰው መንቀሳቀሳቸው የሚያበሳጭ እንደሆነ ይጠበቃል። ይህም የኢትዬጲያ ህዝብ ( በተለይ ወጣቱ) ከድርጊቶቹ በስተጀርባ ያሉትን እውነታ እንዲገነዘብ እድል ፈጥረዋል።

ገዥው መደብ በሁለተኛ ደረጃ ልዩ ትኩረት ሊሰጥ ያስገደደበት ምክንያት ባልተጠበቀ ሁኔታ የምሁርነት ሚናን በመዘንጋትና በምናገባኝነት በመሸፈን ራሳቸውን ከሀገራቸው ጉዳይ ያገለሉ ምሁራንን የማነቃቃት ድርሻ በመጫወታቸው እንደሆነ ይገመታል። ይህ ደግሞ ለደቂቃ በትእግስት ሊታለፍ የሚችል አይደለም። የገዥው መደብ ፍላጐት ምሁራንና ተሰሚነት ያላቸው ግለሰቦች በሀገራቸው ጉዳይ ላይ ባይተዋር እንዲሆኖ፣ አልፎ ተርፎም በተሰማሩበት ቦታ ወጣቱን ” ዲ -ፓለቲሳይዝ” እንዲሆን አድርገው እንዲያፈሩ ነው ( በቅርብ ጊዜ ፓለቲካ ምን ያደርግላችኃል የሚሉ የሀይማኖት ሰባኪያን በአደባባይ መውጣታቸውን ልብ ይሏል)። በመሆኑም ገዥው መደብ “ምሁራን በሁለቱም ወገን የተሳለ ቢላዋ” ብሎ የፈረጃቸው ከመሆኑ አንጳር ጦማሪያኑ በሚያነሱት አጀንዳ ተጐትተው ወደ አብዬቱ በመግባት ግንባራቸውን ለጥይት የሚሰጡበት ሁኔታ እንዳይፈጠር ማድረግ ጊዜ የሚሰጠው አይደለም።

ሶስተኛው ምክንያት እነዚህ ጦማሪያን በኢትዬጲያ ውስጥ ያልተጠበቀና አዲስ ሁኔታ መፍጠር መቻላቸው ነው። ይህም በአንድ በኩል ወጪ ቆጣቢና እያደር እየሰፋ የሚሄድ ስልት መከተላቸው ሲሆን፣ በሌላ በኩል ገዥው መደብ ባወጣቸው አፋኝ ህጐች ማእቀፍ ውጭ መንቀሳቀሳቸው ነው። ከዚህ አንጳር ጦማሪያኑ በግብር የመንግስታዊ ያልሆኑ ሲቪክ ድርጅቶችና የሚዲያ ሚና እየተጫወቱ በህግ ደግሞ በአዲሱ NGO LOW ሆነ በሚዲያ ህጉ መታቀፍ አለመቻላቸው ትልቅ ራስ ምታት ይሆናል። እስከማውቀው ድረስ በሁለቱም አዋጆች ጦማሪያኑን ለመመዝገብም ሆነ ቁጥጥር ለማድረግ የሚያስችል ምእራፍም ሆነ የአንቀጵ ማእቀፍ የለም። በዚህም ምክንያት ይመስላል ገዥው መደብ በህልሙም አስቦት የማያውቀውን አዲስ የሚዲያ አዋጅ ወደ ማውጣት የተሸጋገረው።

በመሆኑም የገዥው መደብ የቅድሚያ እርምጃ እነዚህ የየትኛውም የፓለቲካ ፓርቲ አባላት ያልሆኑ ወጣቶችን የሽብርተኝነት ካባ በማልበስ ከጨዋታ ውጭ ማውጣት ነበር። ይህም ከሞላ ጐደል የተሳካ እርምጃ ቢሆንም በተቃራኒው የወጣቶቹን ፈለግ የሚከተሉ፣ የቀደምት ተግባራቸውን የሚዘክሩ፣ ከልደት በአላቸው አንስቶ በተለያዪ አጋጣሚዎች የወጣቶቹን ቀንዲልነት የሚዘክሩ አእላፍ ሀይሎች ከመፈጠር ሊያግዱት አልቻሉም።

ህብረተሰቡን እንዳያነቁ ልክ ከማስገባት አንጳር የገዥው መደብ ጡንቻ ቀጥሎ ያረፈው ተጵእኖ የሚያሳርፋ የፓለቲካ ፓርቲዎችና አመራሮች ላይ ነበር። ( ይቀጥላል)

The post ምን ታቅዶ ምን ተፈፀመ?፣ …የቀጣይ የትግል አቅጣጫ ምን ይሁን? (ኤርሚያስ ለገሰ) appeared first on Zehabesha Amharic.

(የሳውዲ ጉዳይ …) ህገ ወጦችን የማጥራት ዘመቻ ከተጀመረ 50,254 ተይዘዋል –ነቢዩ ሲራክ

$
0
0
* የሳውዲ መንግስት ህገ ወጥ ያላቸውን የውጭ ዜጎች የማጥራቱንና የመያዙን ዘመቻ አጠናክሮ የቀጠለበት ሲሆን በእስካሁኑ አሰሳ 50,254 በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታውቋል
Nebiyu Sirak* መረጃውን ያስተላለፉት የመዲና ፖሊስ አዛዥ ጀኔራል አብዱል ሃዲ አል ሸሃራኒ መሆናቸውን የጠቆሙት የሳውዲ ጋዜጦች ህገ ወጦች የተያዙት በዋና ከተማዋ በሪያድ በጅዳ ፣ በመካ ፣ በመዲና በተቡክ መሆኑን ጠቁመዋል። ባለስልጣኑ በማከልም የተያዙት ህገ ወጦች ማጣራት እየተደረገ እንደ ተጠረጠሩበት ወንጀል እንደሚከሰሱና ወደ ሃገራቸው እንደሚሸኙ አስታውቀዋል።
* ዘመቻው ከተጀመረ ወዲህ ሁከትና ግርግር ብዙም ባይስተዋልም በርካታ በውጭ ዜጎች የሚተዳደሩ ሱቆች የተዘጉ ሲሆን ሞቅ ደመቅ ያለውን የጅዳና የተለያዩ ከተሞች የገበያ እንቅስቃሴ ላይ ተጽዕኖ መፍጠሩ ይጠቀሳል። ምሽት ላይም የተለመደው የሞቀ እንቅስቃሴ የተገታ መሆኑ መስተዋሉ ይጠቀሳል ።
* በተለያዩ ምክንያቶች የመኖሪያ ፈቃዳቸው ጊዜ ሳይታደስ ስለወደቀባቸው የውጭ ዜጎች ጉዳይ የተናገሩት ጀዋዛት ተብሎ የሚታወቀው የሳውዲ የፓስፖርት እና ኢሚግሬሽን ዋና ኃላፊ መ.ጀኔራል ሱሌማን የህያ ፖስፖርታቸው በጊዜ ያላደሱት ፣ ስላላሳደሱበት በቂ ምክንያት እስካላቀረቡ ድረስ ከተያዙ ወደ ሀገራቸው እንደሚሸኙ ባሳለፍነው አርብ ማስታወቃቸው አይዘነጋም ።
* ይህ በእንዲህ እንዳለ በአሰሳው ስጋት ያደረባቸው ኢትዮጵያውያን እጃቸውን በሰላማዊ መንገድ እየሰጡ የሚሄዱበት መንገድ እንዲያመቻቹላቸው የጅዳን ቆንስልና በሪያድ የኢትዮጵያ ኢንባሲ ከሳውዲ መንግስት ጋር በመነጋገር መንገዱን ያስተከሰክሉ ዘንድ ተማጽኗቸውን እንዳሰማ በተለያየ መንገድ ጠይቀውኛል።
እነሆ መልዕክቱን አድርሻለሁ!
እስኪ ቸር ያሰማን !
ነቢዩ ሲራክ
መጋቢት 7 ቀን 2007 ዓም

The post (የሳውዲ ጉዳይ …) ህገ ወጦችን የማጥራት ዘመቻ ከተጀመረ 50,254 ተይዘዋል – ነቢዩ ሲራክ appeared first on Zehabesha Amharic.

ከምርጫው በፊት ልናደርገው የሚገባ ሌላ ምርጫ (ገዛኸኝ አበበ ከኖርዌይ ሌና)

$
0
0

Gezahegn Abebeበኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ስርዓት በማስመልከት በተለያዩ ድረገጽ እና የዜና አውታሮች ላይ የህዝብን ንቃተ ህሊና ሊይጎለብቱ የሚችሉ የተለያዩ ዘገባዎች ይቀርባሉ። በተለይም ደግሞ ፍትህ፣ነጻነት፣እኩልነትን አስመልክቶ እንዲሁም ሊጀመር ጥቂት ጊዜያት የቀረውንና የኢትዮጵያዊያንን አዕምሮ በያዘው የሀገራችን ምርጫ ዙሪያ መነጋገሩ፣ መከራከሩ እና  ከምርጫው በፊት  መስተካከል የሚገባችውን ነገር ማውሳቱ የሰሞኑ ዓቢይ ጉዳይ ሆኗል። በርግጥ የ1997ቱ ምርጫ የህዝብ ቅስም የተሰበረበት እና እስከአሁንም ድረስ የኢትጵያ ህዝብ ስብራት ያላገገመበት ሁኔታ በስፋት ይታያል። በመሆኑም እንደ እኔ እምነት ፍትህ ከሌለበት ሀገር ከፊታችን ካለው ምርጫ ምንም ይፈጠራል ብዬ የምጠብቀው ነገር ባይኖርም ግን ጥቂት የሚባሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች  ምርጫውን አስመልክቱ እየሰሩት ያለው ቅስቀሳ እና ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ የወያኔን መንግስት ከስልጣኑ በማውረድ፣ ለኢትዮጵያ ህዝብ ነጻነት እየከፈሉት ያለው መስዋትነትና ሊያስመሰግናቸው ይገባል ባይ ነኝ ።  እርግጥ ነው ከሁሉም አቅጣጫ የሚስተጋባው የኢትዮጵያዊ ድምጽ ሀገርን ከመውደድ እና ለሀገር ነጻነት እንዲሁም ሉአላዊነት የሚከፈል መስዋዕትነት እስከሆነ ድረስ ትግሉ ይፋፋም ይቀጥል ያስብላል።

ፍትህ የሰፈነበት ምርጫ ሊካሄድ የተገባ መሆኑን ሁላችንም እንስማማበታለን። የሁላችንም የኢትዮጵያ ልጆች ናፍቆት ሰላም የሰፈነባት ሀገር ላይ ምርጫው የህዝብ እንዲሆን ነው። ይህም ህልም በምድራችን ላይ ተጨባጭ ይዞታ ኖሮት  ተግባራዊ ቢሆን ሀገራችን ምን አይነት ቅርጽ ሊኖራት እንደሚችል ማሰብ ከባድ አይደለም። ስለሆነም በአሁን ወቅት   በምድሪቷ ላይ እየገነነ የመጣው ግፋዊ  አገዛዝ ወደበለጠ ደረጃ ደርሶ እጅግ ከመክፋቱ በፊት የትውልድ ሁሉ ናፍቆት የሆነውን እኩልነት እና  ህዝብ ለብዙ ጥፋት ታልፎ በተሰጠበት እንዲሁም ከሀገሪቷ ፊት ለፊት ታላቅ የሆነ ክስረት ተጋርጦ ባለበት የአምባገነን ስርዐት ዘመን የሰከነና የተረጋጋ ህይወትን በኢትዮጵያ ላይ ለማምጣት ታላቅ የሆነ ርብርቦሽ ያስፈልጋል።

ይህንን በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የዘቀጠ የፓለቲካ ስርዐት ወደኋላ ከተጎተተበት ኢፍትሐዊ አሰራሩ ተናጥቆ ለማውጣት እና የሰለጠኑ ሀገራት ወደደረሱበት የነጻነትና እና የእኩልነት ክልል ለማድረስ ከጨዋታ ውጪ የተደረጉት የኢትዮጵያ ምሁራን እና ከማንኛውም የእድገት  እንቅፋቶች የጸዳ አላማ ያላቸው ሀገር ወዳዶች የተዘጋባቸው በር ክፍት ሆኖ  በሁሉም ሀገራዊ አቅጣጫ ጉዳይ ላይ ለምድራቸው የሚቻላቸውን አስተዋጾ እንዲያደርጉ በተለይም ደግሞ ከፊት ለፊታችን በወያኔ ቁጥጥር ስር ያለው ምርጫ በህዝብ ፈቃድ ላይ የተመሰረተ እንዲሆን የኢትዮጵያ ሊሂቃን እድሉ ያለምንም ተጽእኖ በነጻነት ተሰጥቷቸው እንዲሳተፉ ማድረግ ተመራጭነት አለው። ይህን መሰሉ ተግባር በምድሪቷ ላይ የጸና እስከሚሆን ድረስ  እንዲሁም የገዥውን ቡድን እድሜ መቀጠል ፣ የተመዘበሩ ኮሮጆዎች እና የምርጫ ዕቃ ዕቃ ጨዋታ ወቅታቸውን እየጠበቁ ያለፈውን ልማዳቸውን ለመድገም የሚደረጉት እንቅስቃሴዎች ተፈጻሚ ከመሆናቸው በፊት በሁሉም አቅጣጫ መታገል እንደሚገባን እና ከምርጫው በፊት ህዝባዊ አመጽ እንደ አማራጭ ከመውሰድ  በስተቀር በሌላ መንገድ ወያኔን ማክሸፍ እንደማይቻል ሊታወቅ ይገባል።

እውነታውን በመሸፋፈን  ወያኔ በምግብ ራሳችንን ችለናል እያለ  በሚቀልድበት በዚህ የረሀብ ዘመን ዘወትር ሽቅብ እየወጣ ሰማይ ለመንካት እየተመነጠቀ ስላለው የኑሮ ውድነት ህዝቡም ሲያወራ ወያኔም ስለ ‹‹11%›› እድገት ሲደሰኩር፣ ህዝብ ስለ ስራ-አጥነት እና  እርዛት ሲያወራ ወያኔ ‹‹ስለኢንቨስትመንት መስፋፋት›› ሲያብራራ፣ ህዝብ ስለረሃብ ሲያወራ መንግስት ‹‹ስለጥጋብ›› መፈክሩን ሲያሰማ ፤ ህዝብ ስለዳቦ ሲጮህ የወያኔ መንግስት ‹‹ስለመሰረተ ልማት›› እያወሩ እርስ በርስ መግባባት ተስኗ ቸው 23ኛ አመት ዐመት አልፎ ተጋምሷል ። ይህ ያላቻ ጋብቻ ይባላል። በድግሳቸው ቀን  አንዱ የደስታ ሌላኛው የሃዘን ሻማ በማብራት አክብረው አሳልፈዋል፡፡ ከእንደዚህ አይነት ስርዓት አልባ ገዢ ጋር ፍቺ ብቸኛ አማራጭ ነው። ምርጫውም ፍትሀዊ እና የህዝብ ካልሆነ በስተቀር ለኢትዮጵያዊያን የሚያመጣው ምንም አይነት ፈውስ እንደሌለው የታወቀ ይሁን። ይልቁኑም የከዚህ በፊቱን ውሸት እና ማስመሰል ረቀቅ ባለ ማደናገሪያው ለመድገም እየተሯሯጠ መሆኑ ግልጽ በሆነበት በዚህ ወቅት አምባገነኑን ወያኔን ከምርጫው ውጭ ለማድረግ በየትኛው ጎዳና ብንሔድ በትግላችን ግቡን እንደምንመታ  እና የተለያዩ የትግል ልምድ ስልቶች ልውውጥ አድርገን ሀይላችንን በማጠናከር በአንድ የተባበረ ኢትዮጵያዊ ክንድ ከምርጫው በፊት ህዝባዊ አመጽን  የሁላችን ምርጫ ይሁን በማለት መነሳት አለብን።

የኔ የግል ምልከታዬ በአሁን ሰአት ሀገራችን ባለችበት ደረጃ የትግላችን ኢላማ እና መድረሻው መሆን የተገባው አስቀድሞ በሐስት የወያኔ ነቢያቶች ለተነበዩለት   ምርጫ ተባባሪ ሆኖ በመሰለፍ አምባገነኑ አገዛዝ እንዲቀጥል አስተውጽኦ ማበርከት ሳይሆን የኢትዮጵያ ህዝብ የሚወስነውሀገር የምትተዳደርበት ልማታዊ የሆነ ህግ በምድሪቷ ላይ የበላይ እንዲሆን የዜጎች እኩልነት እና ሰብዓዊነት የሚከበሩባቸው ስርዓት በማስፈን ወያኔ በጭቆና የተቆጣጠርውን ስልጣን በመቀማት የህዝብ የስልጣኑ ባለቤት ሆኖ  ፍጹም የሆነ ብሩህ ተስፋ የሚታየባትን ኢትዮጵያን መፍጠር  ነው።

መቼውንም ቢሆን ወያኔ ለነጻ ፍትሀዊ ምርጫ እና ለኢትዮጵያ ህዝብ የበላይነት ለምን አልቆመም ተብሎ አይጠየቅም። ምክንያቱም ይህ ቡድን “ከጅብ ጅማት የተሰራ ክራር ምንጊዜም ቅኝቱ እንብላ እንብላ ነው” እንዲሉ ከፅንሰቱም ፀረ ኢትዮጵያዊ መሆኑ የታወቀ ነው። ከዚህ አስከፊ ስርዓት መልካም የሆነ አስተዳደር መጠበቅ የሚታሰብ አይደለምና እንደገና ሌላ ምዝበራ በሀገርችን ላይ ከመፈፀሙ በፊት ምርጫው ጋር ሳንደርስ በፊት የህዝባዊ አመፅ ትግልን በመምረጥ ወደ ውጤት እንጓዝ።  ምርጫው የኢትዮጵያ ህዝብ የሚመርጠው እና የሚወዳደረው እንጂ ለተሳትፎ ብቻ ብቅ ብሎ በወያኔ ሻጥር የሚሸነፍበት ሊሆን አይገባም።
ለውጥ የግድ አስፈላጊ ነገር ነው፡፡ ሁሉንም የማይጠቅም ቢሆን እንኳን ለብዙኃኑ ሲባል የግድ መምጣት አለበት፡፡ የለውጥ ፍርሐትን አስወግደን በቂ ዝግጅት በማድረግ በተገቢው መንገድ ወያኔን ማስወገድ  ይቻላል፡፡ ለውጥ የሚመጠበትን መንገድ ፈርቶ እና ህዝባዊ አምፅን  ተቃውሞ  ለውጥን መጨበጥ ዘበት ነው፡፡ ‹‹መፍራት ያለብን ፍርሐትን ራሱን ነው›› እንዲሉ ፍራንክሊን ሩዝቬልት፡ የትኛውንም ወደኋላ የሚጎትተንን ፍርሀት ትተን ድጋሚ በምርጫው ከመጭበርበራችን በፊት አስቀድመን በህዝባዊ አመጽ መታገንልን እንምረጥ። ከምርጫው በፊት የኢትዮጵያውያን ምርጫ  በህዝባዊ አመጽ ትግል ለዘመናት በአንባገነንነት በስልጣን ላይ ተቀምጦ ህዝብን በማሰር ፣ በመግደል ላይ ያለውን አረመናዊ መንግስት ከስልጣን ላይ ማውረድ ይሆን ነው  መልዕክቴ ።
gezapower@gmail.com

የሕዝብ ትግል ያቸንፋል !!!

The post ከምርጫው በፊት ልናደርገው የሚገባ ሌላ ምርጫ (ገዛኸኝ አበበ ከኖርዌይ ሌና) appeared first on Zehabesha Amharic.


የታንዛንያ ፖሊስ ሐገሬ ውስጥ በሕገወጥ መንገድ ገብተው ሲንቀሳቀሱ አገኘኋቸው ያላቸውን 63 ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን መያዙን ገለጸ

$
0
0

77024212ፖሊስ ከአካባቢው ነዋሪዎች ጋር በትብብር ባደረገው ዘመቻ ስደተኞቹን ለመያዝ እንደቻለና በሂደቱም አንድ ኢትዮጵያዊ ስደተኛ ሕይወቱ እንዳለፈ ተገልጿል. ስደተኞቹ ሊያዙ የበቁት የአካባቢው ማሕበረሰብ ለፖሊስ ባደረሰው ጥቆማ መሆኑም ተዘግቧል.

ዘገባው አክሎም ስደተኞቹ ይጓጓዙበት የነበረው መኪና ተበላሽቶ እንደቆመ. በዚህም ወቅት የመኪናው አሽከርካሪ ስደተኞቹን ጫካ ውስጥ ተጠልለው እንዲጠብቁት ማድረጉና ከዚያም ጥሏቸው መጥፋቱ ተጠቅሷል.

ኢትዮጵያውያኑ ስደተኞች በተያዙበት ወቅት በረሀብ እና በጤና ችግር ተጎሳቁለው እንደነበር; ረሀብ የጠናባቸው አንዳንዶቹም ማሳ ውስጥ በመግባት ረሃባቸውን ለማስታገስ መሞከራቸውን, ሌሎቹም የአካባቢውን ሕዝብ ምግብ ሲለምኑ እንደነበር የዴይሊ ኒውስ ዘገባ ያስረዳል.

source –.diretube

The post የታንዛንያ ፖሊስ ሐገሬ ውስጥ በሕገወጥ መንገድ ገብተው ሲንቀሳቀሱ አገኘኋቸው ያላቸውን 63 ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን መያዙን ገለጸ appeared first on Zehabesha Amharic.

አንድነት ራስ ምታቱ ነበር ፣ አሁን ደግሞ ሰማያዊ ሆድ ቁርጠቱ ሆነ –ግርማ ካሳ

$
0
0

“የአንድነት አመራር በብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ከተለዬ በኃላ በተሰጠው የሰባት ቀን እጩ የማስመዝገቢያ ጊዜ ውስጥ ለተወካዮች ምክር ቤትና ለክልል ምክር ቤቶች በ80 ምርጫ ክልሎች ተደራሽ በማድረግ 230 እጩዎችን ለማስመዝገብ ችለናል፡፡”
በምርጫ ቦርድ አሰራር፣ ለምርጫ የሚሰጡ የገንዘብ ድጎማዎች ፣ በኢቢሲ/ኢቲቪ የሚቀርቡ የቅስቀሳ ጊዜያቶችን ፣ ፓርቲዎች ባቀረቡት ተመራጮች ቁጥርና አሁን በፓርላማ ባላቸው መቀመጫ ቁጥር እንዲሆን ነው የተደረገው። ይህ አሰራር በእጅጉ ሕወሃትን እንደሚጠቅም የታወቀ ነው።
semayawi
በዚህ መሰረት የሰማያዊ ፓርቲ በሚደረገው ምርጫ 7 ጊዜ ለአሥራ አምስት ደቂቃ መቀስቀስ እንደሚችል ተገልጾለታል። «በቂ ባይሆንም ያን ያህል ኢቢሲ/ኢቲቪ መፍቀዱ ጥሩ ነው» ሊያስብል ይችላል። ሆኖም ሕወሃት በአንድ በኩል ሲከፍት በሌል በኩል እንዴት ለመዘጋት እንደሚሞከር እናሳይ፡:

1) ሰማያዊ የሚያቀርባቸው የቅስቀሳ መልእክቶች ሳንሱር የሚደረጉ ናቸው። ከስድስት ጊዜ በላይ ኢቢሲ « ይሄን ካላስተካከላችሁ አናስተላልፍም» ብሎ መልሷል። እንድ ጊዜ እንደዉም አረንጓዴ፣ ቢጫ ቀይ ሰንደቅ ለም አደረጋችሁ በሚል ነው።
2) ሰማያዊ እንዲያቀርባቸው ከተፈቀደለት ሰባት ፕሮግራሞች አምስቱ እንዲተላለፉ የተወሰኑት ከጠዋቱ አንድ ሰዓት ( በፈረንጆች ነው። ወላጆች ልጆቻቸዉን ትምህርት ቤት ለመላክ ፣ ወደ እስራም ለመሄድ ደፋ ቀን በሚሉበት፣ ብዙዎች ከእንቅልፋቸው ሊነሱ በማይችሉበት ሰዓት ነው ።
የሕወሃቱ ኢቢሲ/ኢቲቪ ሆን ብሎ ሕዝቡ የሰማያዊ ፓርቲን መልእክት ለማዳመጥ እንዳይችል፣ ሲስተማቲክ በሆነ መንገድ ለማከላከል ለምን ፈለገ ? መልሱ አጭር ነው። ሕወሃት ከመቼዉም ጊዜ በላይ የፈራበትና በራሱ መተማመን ያልቻለበት ጊዜ ነው።
በነገራችን ላይ ለፓርላማ ወደ 480 ፣ ለክልሎች ደግሞ 1200 በላይ እጩዎችን አንድነት ፓርቲ ሊያስመዘግብ ተዘጋጅቶ እንደነበረ ሁላችንም እናዉቃለን። በሶማሌ ክልል በስተቀር ከአምስት መቶ በላይ በሆኑ የምርጫ ወረዳዎች ነበር አንድነት የሚወዳደረው። መረቡን ዘርግቶ በስፋት እየተንቀስቀስ ነበር። ሆኖም ባፈጠጠና ባገጠጠ መልኩ ህወሃት የኃይል እርምጃ ወስዶ፣ የአንድነትን ፓርቲ ጠፍጥፎ ለሰራው የትግስቱ ቡድን ሰጧል። አንድነት ማሸነፍ ብቻ ስይሂኦን ድምጽን የማስከበር አቅም እንዳለው ስላወቀ፣ ለምርጫ ቦርድ ቀጥታ ት እዛዝ በመስጠት አንድነት አገደ።

የአንድነት አባላት ሰማያዊን ተቀላቀሉ። ሰማይዊ የበለጠ ተጠናከረ። ከ400 በላይ የፓርላማ እጩዎች አስመዝገበ። ከ200 በላይ የሚሆኑትን ያለ ምንም ምክንያት ምጫ ቦርድ ሰረዘ።
አይ የወያኔ/ሓወህት አስቂኝ ምርጫ ! ከዚህ በፊት በምርጫው ቀን ነበር የሚያወናብዱት። በዚህ አመትማ ለይቶላቸዋል። ምርጫዉ ከመድረሱ ሶስት ወር በፊት ሰዎቺ እየተደናበሩ ነው !!!!
በከዚህበፊት ምርጫ ሕዝብ መርጦ ፣ ድምጹ ነበር የሚሰረቀው። ሕወሃት የድምጽ ሌባ ሰራቂና አጭበርባሪ ነበር። አሁን ግን ሕወሃት መራጭ የሆነበት ምርጫ ነው። አንዱን ፓርቲ እንዲወዳደር፣ ሌላውም እንዳይወዳደር ያደረገ፣ እጩዎች እየሰረዘ አትወዳደሩም በማለት መራጭ የሆነበት ምርጫ ነው! ሕወሃት ድሮ ያደርግ የነበረዉን ማስመሰል እንኳ ትቶ ፍጹም አምባገነን መሆኑን ያሳየበት ምርጫ ነው።

The post አንድነት ራስ ምታቱ ነበር ፣ አሁን ደግሞ ሰማያዊ ሆድ ቁርጠቱ ሆነ – ግርማ ካሳ appeared first on Zehabesha Amharic.

“ኢንተርኔትና ሚድያውን አጨናንቀዋለሁ ”ጥበቡ ወርቅዬ የቀድሞ ድምፃዊ፣ የአሁኑ ዘማሪና ሰባኪ

$
0
0

አቤንኤዘር ጀምበሩ

ጥበቡ ወርቅዬ አገልግሎት ለመታደም ወደ ቤዛ ቤተ/ክ በ06/07/07 ዓም ተገኝቼ ነበር። ምንም እንኳ ዝግጅቱ 8:00 ይጀመራል ተብሎ የነበረ ቢሆንም ጥበቡ ቦታው የደረሰው ከዘጠኝ ሰዐት በኃላ ነበር። ጥቤ የቀድሞ አስታይለኛ አለባበሷ አና ፍሪዟ እንዳለች ነው፣ ፊቱ ላይም ላቅ ያለ የደስ ደስ ስሜት እና መመቸት ይታይበታል። ለአድምተኛው ምንም አይነት ቀረፃ ማድረግ አንደማይፈቀድ ከተላለፈ በኋላ ፣ ጥሪ ተደርጎለት ወደ መድረክ ሲወጣ የነበረው ህዝብ ቆሞ እያጨበጨበ እና እየጮኸ ሲቀበለው “አለማዊ” መድረክ ስራዎቹን ሳያስታውሱት የቀሩ አይመስለኝም።

በኋላ ላይ እራሱ እንደገለፀው “እዛ በታለንትና በድፍረት፣ እዚህ ግን በቅባት” ብሏል። ዝማሬን በሚያቀርብበት ወቅት በሙዚቃ ህይወቱ የሚታወቅበት መልካም ቃና ያለውን ድምፁን ወደ መዝሙር ቀይሮታል፣ ምንም እንኳን አልፎ አልፎ ያሉ መሸጋገሪያዎች ላይ የለመዳቸው የሙዚቃ መግቢያዎች ሲጐትቱት ታዝቤያለሁ። ለምሳሌ አንድ ጊዜ “ነይ ነይ” ብሎ ወዲያው “ሃሌሉያ” አድርግዋታል። የመዝሙር አገልግሎቱን ጨርሶ ወደ ቃል ማካፈል ሲያልፍ፣ የትምህርቱን መነሻ ያደረገው ሐዋሪያት ስራ ምእራፍ 2 ላይ ስላለው የበአለ ሀምሳ ክብረ በአል ላይ ነበር። ጥበቡ መጽሐፍ ቅዱሳዊ እውቀቱ ከፍተኛ ደረጃ መድረሱን መገንዘብ አያዳግትም፣ እንዲሁም ለእምነቱ ከፍተኛ ቅንአት እንዳለውም ጭምር። ይህም የሚያመለክተው ከፍተኛ ጊዜውም በመፅሐፍ ንባብ ላይ እንደሚያሳልፍ ነው። እራሱም እንደገለፀው ለሶስት አመት ተኩል በር ዘግቼ ጨለማ ቤት ጭምር በንባብና በመፅሐፍ ቅዱስ ጥናት ላይ አሳልፌያለሁ ብሏል ።
tibebu workiye

“አንዳንዶች ይመለሳል ይሉኛል፣ ግን ወዴት ነው የምመለሰው” ሲልም አፅእኖት ሰጥቷል። ምንም እንኳን ጥቤ ጥሩ አንዳነበበ አና መረዳት አንዳለው መገንዘብ ቢቻልም፣ በማስተማሩ ረገድ ግን የአቅም ውስንነትና ድፍረት እንደሚስተዋልበት ደፍሮ መናገር ይቻላል። በተለይ ባሁኑ ጊዜ መጽሐፍ ቅዱሳዊ እይታን ፣ ከተጨባጭ ገሃዳዊ ሁኔታዎች እና ከስነ ልቦናዊ ዝግጅት ጋር አያያዙ የሚስቡ ትምህርቶችን ማዘጋጀት በአለም ሁሉ ላይ ባሉ የፕሮቴስታንት ቤተ/ኖች የሚንፀባረቅ ነገር ነው። እንዳየሁት የቃሉ መረዳት ቢኖረውም ከላይ የተጠቀሱት ክህሎቶች ጐድለውት ተመልክቻለሁ። ትምህርቱ ባብዛኛው ረድፍ ያልጠበቀ እና መጽሐፍ ቅዱስ ላይ የተጠቀሱ ነገሮችን መልሶ የመናገር፣ ወይም ትንታኔያዊ አስተምሮ ያለማቅረብ ሁኔታዎች ታዝቤያለሁ። ዘማሪው በትምህርቱ ወቅት የተለያዩ ነገሮችን አንስቷል፣ በአለማዊ ህይወቱ በተለይ በጫት ሱስ እጅጉን እስረኛ አንደነበረ ፣ቄማ ላይ እያሉ ከአርቲስቶች ጋር አብዝቶ ይጋጭ እንደነበር “አይወደኝም፣ ሌላ ሰው ባጠፋው ጭምር እኔ ነበርኩ የምሰደበው፣ ሰይጣን የሱ አንዳልሆንኩ ያውቅ ስለነበር ነው። ” ብሏል።

አርቲስቱ ድሮ በመቃብር አካባቢ እንኳን ሲያልፍ እጅጉን ይሸበር እንደነበርና አሁን ግን በራሱ አገላለፅ “በኮንፊደንስ ነው” ሲል ተደምጧል። ለሱ ከአለም ለመውጣት ምን ያህል አስቸጋሪ እንደነበርና ብዙ የሚይዙ ነገሮች እንደነበሩ ጠቅሰዋል። “የሙዚቃ ዝና፣ ሙዚቃቤት፣ ቁጥሩ የበዛ የሙዚቃ መሳሪያና ሌሎችም ነበሩ” ብሏል። ወደ ጌታ ከመጣ በኋላ መንፈሳዊ ክንውኖቹን ሲናገር፣ 1900 በላይ ሰዎችን ወደ ጌታ አንደመለሰ (የመገናኛ ብዙሃን የተጠቀሙትን ሳይጨምር) ፣ ትልልቅ አርቲስቶችን ሰብስቦ አንደመሰከረ፣ ወደ ጌታ አንደመለሰ እንዲሁም ብዙዎች በመንገድ ላይ እንደሆኑ ገልፅዋል። ሌላው አሁን አሁን በአንዳንድ ድህረ ገፆች ላይም እንደሚታየው ተአምራዊ አገልግሎቱ ነው።

ከንግግሩ መረዳት የሚቻለው እነዚህ እነዚህ አገልግሎቶች ሁሉም ቤት እንዲገቡ ይፈልጋል ፣ በቃሉም “ካሁን በኃላ ኢንተርኔትንና ሚድያውን አጨናንቀዋለሁ” ብሏል። በቅዳሜው አገልግሎት በስራ ማጣት የተፀለየላት ወጣት ፣ ስራ ማጣቷ መንፈሳዊ ተግዳሮት እንደነበር እና በፀሎት ወቅት ጮሆ ሲወጣ በዛው ቅፅበት አቤቷ ስልክ ተደውሎ ለስራ መጠራትዋን እሱ ሲናገር አሷ እጇን በማውለብለብ በእሁዱ ፕሮግራም አረጋግጣለች። እንዲሁም እሱ ፀሎት ያደረገላቸው ሰዎች በእንቅልፍ ወደ መንግሥት ሰማያት ደርሰው እንደተመለሱ ጠቅሷል፣ በስልክ ልውውጥ አጋነንትን እንዳስወጣም ጭምር። ትላልቅ አርቲስቶች ላይ ያለ መሪ መንፈስ ሲመታ መንጋው ይበተናል የሚለው አርቲስቱ፣አሁን ላይ ብዙ አርቲስቶች አንደሚደውሉለት እርሱም አንደሚፀልይላቸው መስክሯል። ሌላው የገረመኝ ነገር በትልልቅ ዘፋኞች ስም የተሰየሙ አርኩሳን መናፍስቶች መኖራቸውን መግለፁ ነው፣ ምድራዊ ህግ ስለማይፈቅድ እንጂ ቢጠራቸው እየጮሁ ወደ አርሱ እንደሚመጡ ገልፅዋል። ድምፃውያኑ አንደ ኮካ በስማቸው የተሰየሙ መናፍስት መኖራቸው አያስገረመኝ፣ ይህችን አረፍተ ነገር በሚናገርበት አፍታ ሁለት አርቲስቶች ወደ አእምሮዬ መጡ።ታደለ አና ሰማኸኝ። በእነዚህ ሙዚቀኞች የተሰየሙ መናፍስት ይኑሩ አይኑሩ ባላውቅም፣ ኖረው ቢጠራቸው ብዬ አሰብኩት። የታደለ “አጋቡዮ” እያለ የሰሜ “አላበድኩም ፣ ጤነኛ ነኝ፣ ያዥኝ” እያሉ ወደ ፊት ሲሮጡ በምናቤ ታየኝ።

ጥቤ ጌታ ይባርክህ። ቸር!

The post “ኢንተርኔትና ሚድያውን አጨናንቀዋለሁ ” ጥበቡ ወርቅዬ የቀድሞ ድምፃዊ፣ የአሁኑ ዘማሪና ሰባኪ appeared first on Zehabesha Amharic.

የብሄር ብሄረሰብ ፖለቲካና የአድዋ ድል –ሚንጋ ነጋሽ

$
0
0

የካቲት 23 2007 (ማርች 2, 2015) የ119ኘዉ የአድዋ ድልና የሰማዕታት መታሰቢያ ቀን ነዉ። አከባበሩ በሃገር ዉስጥ ቢቀዘቀዝም፤ በተዘዋዋሪዉ በአሉን የሚያከብረዉ በዉጭ ሃገር የሚኖረዉ ኢትዮጵያዊ ቁጥር እየጨመረ ይገኛል። በሰሜን አሜሪካ የድል በአሉ ቀን ከአፍሪካ አሜሪካዉያን ታሪክ መዘከሪያ ወር ጋር መያያዙና የየካቲት 12 ሰማእታትን መታሰቢያ ቀን ደግሞ ከሰላሳ በላይ በሆኑ ያለም ከተሞች መዘከሩ፤ በዉጭ  የሚኖሩ ኢትዮጰያዉያን ትኩረት የሰጡት ስለሀገር አቀፍ ድልና ስለአፍሪካዊነት (Pan Africanism) መሆኑ ራሱን የቻለ መልዕክት አለዉ።

በዚህች አጭር ጽሁፍ ለማስገነዘብ የምሞክረዉ አድዋንና መሰል የሃገራችንን እሴቶች በብሄር-ብሄረስብና ወይም በሃይማኖት ዘመም  የፖለቲካ  መነፅር (ethnocentric paradigm) መመልከትና በብዙሃን ዘመም (diverse, multi-ethnic) መነፅር መመልከት የሚየስከትሉትን እደምታዎች ለማሳየት ነዉ። ሁለቱም አመለካከቶች የሚያዩት አንድ ነገር ቢሆንም የሚሰጡት ትርጉም ግን የተለያየ ነዉ። ሃገር አቀፍ ፖሊሲ ሲነደፍ ሁለቱ መነፅሮች የሚያሳዩትን ልዩነትና አንድነትን በቅጡ መረዳት ይጠይቃል። እኔ የታሪክ ወይም የፖለቲካ ስነልቦና ሳይንስ ተማሪ አይደለሁም። ሰለአድዋ ድልም የማዉቀዉ በጣም ዉሱን ነዉ። ቢስማርክ ከጠራዉ እ.ኤአ 1884/85 የበርሊን የአፍሪካ ቅርጫ ኮንፍረንስ (the conference for the scramble of Africa) ጀምሮ እንዴት ኢትዮጵያ እንደሌላዉ የአፍሪካ ክፍል የዚህ ቅርጫ ሰለባ አለመሆንዋ ብዙ የታሪክ ምሁራንን አስረገርሞዋቸዋል። ይህንን ታሪክ አፈወርቅ ገብረየሱስ፡ ገብረ ህይወት ባይከዳኝ፡ ራይመንድ ጆናስ፡ ሪቻርድ ፓንክረስት፡ ዶናልድ ሌቢን፡ ኤድዋርድ ክሬሚ፡ ሃሮልድ ማርከስ፡ ጆን ሰፔንሰር፤ ታደስ ታምራት፡ መርእድ ወልደአረጋይ፤ ብርሃኑ አበበ፤ አለሜ እሽቴ፤ ባህሩ ዘውዴ፡ ሽፍራዉ በቀለ፡ ሹመት ሲሻኝ፡ ዘዉዴ ገብረስላሴ፤ ጌታችዉ ሃይሌ፤ጳዉሎስ ሚለኪያስ፤ ጳዉሎስ ኞኞ መስፍን አርአያ፤ ጌታቸዉ መታፈሪያ በቀጥታና በተዘዋዋሪ የጻፉትንና የተናገሩትን የማንበብ እድል ነበረኝ፡፡

ከፊልም፤ሙዚቃና ግጥም ስራዎች ደግሞ እነ ቦብ ማርሌና ራሰ ተፈሪያኒዝም፤ የሃይሌ ገሪማን፤ የአለምፅሃይ ወዳጆን፤ የፀጋዮ ገብር መደህን፤አዲሰ አለማየሁ እጅጋይሁ ሽባባዉና የቴዎድሮስ ካሳሁንን ስራዎች መስማትና ማየቱ ተጨማሪ ሰሜት  ፈጠሮልኛል።። ከታላላቅ የፖለቲካ መሪዎች ጽሁፎችና ንግግሮች መካከል ደግሞ፡ እነ ማርከስ ጋቢ፡ ማርቲን ሉተር ኪንግን (የኢትዮጵያ ኤምባሲ ግብዣ ጨምሮ)፤ የአፍሪካ የነፃነት መሪዎች ማለትም እነ ሙዋሊሙ ኔሬሬ፡ ኬኔዝ ካዉንዳ፤ጆሞ ኬንያታ፤ ኔልስን ማንዴላ፡ ታቦ እምቤኬ፡ ክዋሚ ንክሩማ፤ በደቡባዊ አፍሪካ በ1880ዎቹ የተፈጠሩትና እስከዛሬ ያሉትን በኢትዮጵያ ስም የሚጠሩትን ቤተ ክርስቲያኖች ታሪክን በተመለክተ የፐ/ር ማሞ ሙጬን የቅርብ ጊዜ ፅሁፎች ሳነብ፤ አሜሪካም በተለይ በሁለተኛዉ እ..ኤ.አ የ1933 የጣሊያን ወረራ ጊዜ ስለነበረዉና ስለአነ መላኩ በያን ሥራና ስለአፍሪካ አሜሪካዉያን ወዶ ዘማቾች ምልመላ ሳነብ፤ የተረዳሁት አድዋ የአድዋዉያንና የኢትዮጵያዉያን የድል ታሪክ ብቻ አለመሆኑን ነዉ። የሃይቲን የነፃነት ትግልና በልጅነቴ እሰማ የነበረዉን የአፄ ምኒልክን የደስታ የተኩስ ሩምታ ምክንያት ያስታዉሰኛል። እነዚህ ምሁራን የነፃነት መሪዎችና አርቲስቶች የተከተሉት በአብዛኛዉ የብሄረሰብና የብሄር መነፅር የታሪክ ትርጉም አልነበረም ብሎ መደምደም ይቻላል።

በአንፃሩ አዲስ ህይወት (የብዕር ሰም): ቦኒ ሆልኮምብና ሲሳይ ኢብሳ፤ ማሩ ቡልቻ፤ በ 1990ዎቹ በ Red Sea Printers ና ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ በኩራዝ አሳታሚ የታተሙ መጻህፍትና ገድል መሰል ጽሁፎች የፖለቲካ ትንታኔያቸዉ በአንዳንንድ የአሜሪካ ዩኒቨርሲቲዎች የሚታየዉን ብሄረ ተኮር ጥናቶች (ethnography and ethnic studies) ተደግፈዉ ማርክሳዊ መሰል ትንታኔና ትርጉም ሊሰጡ ይሞክራሉ። ጎልቶ የሚወጣዉ መልዕክታቸዉ ኢትዮጵያ የሚለዉን የፖለቲካና የሶሺያል መሰረቶች የሚንድ (de-legitimize) ነዉ። የሀገር ዉስጥ ግጭቶችን በብሄር መነጽር ያይዋቸዋል። የአድዋ ጦርነትን ዋና መሪዎችን ከሌሎች ግጭቶች ጋር እያጣቀሱ ሲወቅሱ ይሰማሉ። ብሄር ተኮር ድርጅቶችም ግጭቶቹን የአንድ ወገን በማስመሰል ከዛሬ ፖለቲካ አገናኝተዉ ቢቻል አዲስ ነፃ ሀገር ባይቻል ደግም አሁን ካለዉ የተሻለ የፌዴራል አስተዳደር እንመሰርታለን እያሉ ቃል ይገባሉ። የድሮዋ ኢትዮጵያም ልዩ የብሄረሰቦች እስር ቤት ነበረች የሚል ትረካም አላቸዉ። አዲሲትዋ ኢትዮጵያም የብሄረስቦች (nations, nationalities, peoples, volks) ድምር ነች ወይም ትሆናለች ይላሉ። በዚህም የተነሳ የፖለቲካ የአስተዳደርና የትምህርት ወዋቅሩ ይህንኑ ተከትሎዋል። ይህ አካሄድም ሀገሪቱዋን ከመበተን አድኖዋት በኢኮኖሚም እየተራመደች ነዉ ብለዉ ይከራከራሉ።

የፖለቲካ መሪዎች ይመጣሉ-ይለወጣሉ። ስርአቶቹን የሚመራዉም ርአዮተ አለም እንዲሁ ይቀያየራል። ይህ ደግሞ በብዛት የሚታየዉ አፍሪካ ዉስጥ ባሉ ከቀኝ ግዛት በሁዋላ በተፈጠሩ ሀገሮች (post colony states) ነዉ። አንድ ቲዎሪም ሁሉን ነገር (phenomenon) ሊያብራራ አይችልም። ይህ እንኩዋን በኩዋሊቴቲቭና በፊኖሚኖሎጂ የምርምር መንገድ የሚጠኑ ስራዎችን ቀርቶ በኢምፒሪካል  የምርምር መንገድ ላይም በየጊዜዉ የሚታይ ሁኔታ ነዉ። ታሪክንም በተለያዩ መነፀሮች መመርመር በራሱ ችግር የለዉም። እንዴዉም ይህ አካሄድ በተ;ለይ በፖሊሲ ንድፊያ ጊዜ የተሻለ አካሄድ ሊሆን ይችላል። በእኔ እድሜ ኢትዮጵያ ዉስጥ ሶስተ ያስተዳደር መርሆዎችን አይቻለሁ። ባለፉት 40 አመታት ዉስጥ ብሄር ዘመምና የግራ ዘመም የታሪክ ትርጉዋሜዎች የመንግስትን ዋና ዋና ፖሊሲዎች ሲመሩ አይተናል። ሁለቱም ህብረተስብን በመደብ በብሄርና ወይም በሃይማኖትና በጾታ መክፈልና ልዩነቶች ላይ ማተኮርን ይወዳሉ። አንድን ህብረተሰብ በዴሞግራፊ መርሆዎች ከፍሎ ማጥናቱ ችግር የለዉም። ልዩነታቸዉ ብዙሃንነት (diversity) እንዴት እንደሚስተናገድ ነዉ። ሰለ ከአንድ በላይ ማንነት (dual & multiple identities) በሃገራችን ብዙ አይነገርም።

ብዙዎቹ የዛሬ የብሄር ንቅናቄ መሪዎች በአንድ ወቅት የማርክሲስት ርአዮተ አለም ተከታዮች እንደነበሩ ይታወቃል። አስተዳደር ላይ የሁለቱ ልዩነት ማርክሲሰቶች ሀገር አቀፍ፡ አህጉር አቀፍ፤ከዚያ አልፎ ኢንተርናሽናሊዘምን ሲያወድሱ፤ በተቃራኒዉ ብሄር ተኮር አካሄድን የሚመርጡ ደግሞ ጭንቀታችዉ ቆመንልሃል ለሚሉት የህብረተሰብ ክፍል ሲሆን ግራ ዘመምነታችዉ ስታሊን በስራ ላይ ያላዋለዉን የመገንጠል መንገድ እንዲያቀነቅኑ አድርጎዋቸዋል። ግራ ዘመም ያልሆኑት ብሄር ተኮር ድርጅቶች ደግሞ ተግባራቸዉ ወደ ፋሽዝምና አፓርታይድ፤በማወቅም ሆነ ባለማወቅ፤ ሲያቀርባቸዉ ይታያል። የሶቪየት ህብረትና የይጎዘላቪያን አፈጣጠር፤ አፈራረስና ዉጤቱን ማጤን ይረሳሉ። ስለሆነም አንድ ብሄር ተኮር የፖለተካ ሃይል የተለያዩ ብሄሮች ባሉበት ሀገር ላይ የበላይነት በያዘበት ቦታ ገዢዉን ብሄር ለመጥቀምና ለማሞገስ ተብለዉ የሚደረጉ ሙከራዎች ትክክለኝነታቸዉና ትረጉዋሜያች በቅጡ ሳይፈተሹ በህገ መንግስት ላይ ይሰፍራሉ። የመንግስትም ስራዎች በብሄር ተኮር ፖሊሲዎች ይመራሉ። የብሄር ድርጅቱ ካናሳ ወግን ከመጣ የአናሳዎችን  ህብረት በመፍጠር የብዙሃኖችን ግፊት ለመቁዋቁም ይሞክራል። ማንነት (identity) የምርጫ አጀንዳ ሆኖ ዜሮና አንድ ወይም እድገትና ድህነት፤ባርነትና ነፃነት፤ እኛና እነሱ፤ ሰይጣንና መልአክ፤ወዘተ ተብሎ ይቀርባል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ ይህ አካሄድ በሃይማኖት (bigotry) በመታጅብ ላይ ይገኛል።  ከዚህ ባሻገር ደግሞ ሊበሪቴሪያኒዘምን ማለትም ግለሰብ መብት ላይ የሚያተኩር  የፖለቲካ አስተሳሰብን የሚያራምዱ አሉ። ሁሉም ማለትም የግራዉም ብሄር ተኮሩም ሆነ ሊበሪቴሪያኑ “ዲሞክራሲያዊ” የሚል ታፔላ አላቸዉ።

ሰለዚህ ኤትኖሼንትሪዝም በሃገራች ሲታይ ልዩነትን (diversity) ለማስተናገድ እ.ኤ.እ በ1993 የሰራዉ ህገ መንግስት መፍትሄ እንዳልሆነና ሀገር አቀፍ መግባባት ለመፍጠር አለመቻሉ በቅጡ ተፈትሾአል። የ1991 ዱም ቻርተር ማለትም የህገ መንግሰቱ አዋላጅ የተፃፈዉ ከግጭት በሁዋላ ስለነበር ያመለከተዉ የጊዜዉን የሃይል አሰላለፍ ነበር። ጸሃፊዎቹም እርስ በርሳቸዉ ይጣሉ እንጂ በጽንሰ ሃሳብ ደረጃ ከ25 አመታት በሁዋላም ቢሆን መሰረታዊ ልዩነት አይታይባችዉም። በትምህርት ቤቶችም የሚሰጡ ትምህርቶች የብሄር ተኮር መሰረት ስላላቸዉ ከፍተኘ ትምህርትም በብሄር በመዋቀሩና በክልል አሰተዳደር ስር መሆናቸዉ፤ በምሁሩም ቅን ልቦናዊነት (bona fide, honesty and integrity) ላይ ለመተማመን አስቸጋሪ እየሆነ መጥቶዋል። ሃገሪቱ የተማረ ህዝቡዋን በተለያዩ ምክንያቶች ስታጣና፤ አብዛኛዉ ወጣት የሆነዉ ህዝብ የስራ አጥነት፤የኢኮኖሚና የፖለቲካ ስደት ሰለባ ሲሆን፤ በባህር ላይ ሲሰምጥና በየስደተኛ ካምፖችና እስር ቤቶች ሲታጎር፤ የምርምር ተቁዋሞች መሰረታዊ ምርምር ማደረግ አለመቻላቸዉ፤ ዮኒቨርሲቲዎችም ከጥራት ይልቅ ወደ ብዛት አተኩረዉ በየክልሉ ሲረጩ፤ በብሄር ተኮር ሹማምንት ሲመሩ፤ ዉጥረቶቹንም በፍትሃዊ ምርጫዎች ለማስተንፈስ አለመቻሉ፤ ብሄርና ሃይማኖት የፖለቲካ ማማ (platform) ሆነዉ መቀጠላቸዉ፤ በግጭት ቀጠና ዉስጥ ያለችዉን የሀገራችንን ችግሮች እጅግ ዉስብስብ አድርገዉታል።

ስለዚህም በሀገራችን ዛሬ በስልጣን ላይ ያለዉ ብሄር ተኮር መንግስት እንደ ቀድሞዎቹ የማርክሲሰትና የንጉሳዊ መንግስታት ሁለት ችግሮች ገጥመዉታል። በአንድ በኩል ሌሎች ብሄር ተኮር ተፎካካሪዎቹ የማዕከላዊ መንግስት ስልጣኑን ሊወስዱብትና ለራሳችዉ ብሄር ሊተኩ ይፈልጋሉ፡፡ ይህ ካልሆነላቸዉ ደግም ሃብት ወደ አሽናፊዉ ብሄር ብሄረሰብ እንዳይፈስስ ሲሰተሙን ለማፍረስ ይጥራሉ። ይሀ ጥረት በራሱ በመንግስትና ፓርቲ ዉስጥ፡ በምርጫና በጠመንጃም እየተሞከረ ይገኛል። የብሄር ድርጅቶች መሪዎችም ለሁለተኛ ድል (second breakthrough) እየተዘጋጀን ነዉ ይላሉ። ሁኔታዉ በሶቪየት ህብረትና በዩጎዝላቪያ የኮሚኒስት ፓረቲዎች ዉሰጥ የብሬዥኔቭና የቲቶን ሞት ተከትሎ የተፈጠረዉን ክስተት በገዥዉ የብሄሮች ግምባር ዉስጥ አይከሰትም ብሎ መናገር አይቻልም። እሰከ አሁን በድርጅቱ ዉስጥ የነበረዉ  የሃይል አሰላለፍ ለማስቀጠል ርብርቦሽ ያለም ይመስላል። በሌላ በኩል ደግሞ ከብዙሃኖችና ከዲሞክራሲ ሃይላት ክፉኛ ዉድድር ገጥሞታል። በነፃና ፍትሃዊ ሀገር አቀፍ ምርጫ እንደማያሸንፍ ተረድቶታል። ስለሆነም ተፎካካሪዎቹን ስልጣን ከማካፈል ይልቅ ማፍረስንና አሽባሪዎች ብሉ መሰየሙን መርጦዋል። በ2005ቱ ምርጫ ያኮረፉም ጠመንጃ አንሰተዉ ከቆዩት ጋር የታክቲክ ወዳጅነት የፈጠሩ ይመስላሉ። የሰላም መንገድ መጥበብና መዘጋት አመፅ ተቀባይነት እንዲያገጘ እያደረገ ይገኛል። ከዚህም አልፎ ሰለሰላማዊና የመሳሪያ ትግሎች (armed & peaceful resistance) ተጉዋዳኝነት የሚያሳዩ ፍልስፍናዎች እየቀረቡ ይገኛሉ። ይህንንም ሁኔታ ጎረቤት ሀገሮች ለራሳቸዉ በሚጠቅም መንገድ ሂደቱን ሊቃኙት እንደሚፈልጉ ሳይታለም የተፈታ ጉዳይ ነዉ። በቀጠናዉ ያለዉን አጠቀላይ በሃገሮች መሃል ያሉትን ዉጥረቶችን ወደጎን አድርገን የሃገሪቱን የዉስጥ ዉጥረት ብናይ የመጪዉ ግንቦት ምርጫ ወይም አንዳንድ ሰዎች እንደሚሉት ጥገናዊ የህገ መንግስት መሻሻል እዚህ ግባ የሚባል ፋይዳ እንደማይኖራችዉ ግልፅ ነዉ።

ሰለዚህ በሀገራችን ያሉትንና እየተፈጠሩ ያሉትን ዉጥረቶች ለመፍታት ወሳኝ እርምጃዎች መዉሰድ ያስፈልጋታል። ለዚህም  ቁልፉዋ የምትገኘዉ በአብዛኛዉ የማእከላዊ መንግስትን ስልጣን በሚቆጣጠረዉ ብሄር ተኮር ድርጅት እጅ ቢሆንም   ድርጅቱ ይህንን ሊሰራ የሚችል መሪ ከዉስጡ ለማዉጣጥ እስካሁን አልቻለም። ብሄራዊ አንድነትንና እኩልነትን የሚገነባ፤እሸናፊና ተሸናፊ የሌለበት የፖለቲካ አስተሳሰብና አስተዳደር መመስረት የዛሬዉ የሃገሪቱ ፈተናዎችዋ ሲሆኑ፤ እነዚህ ፈተናዎች ግን የዛሬ 119 እመት በፊት እነ አፄ ምኒልክን፡ እቴጌ ጣይቱን፡ ራሰ አሉላን፤ ፊታዉራሪ ሃብተ ጊዎርጊስን፤ ራስ ጎበናንና ሌሎቹን በሺህ የሚቆጠሩትን የአድዋን አርበኞች ገጥመዋችዉ ከነበሩት ፈተናዎች ጋር የሚወዳደሩ አይደሉም። እ.ኤ.አ ከ1937ቱ ፈተናዎች ጋርም የሚወዳደሩ አይደሉም። በእነዛ ከባድ ፈተናዎች ጊዜ ብዙ መስዋእትነት ተከፍሎዋል።  እነዛን ፈተናዎችን ስንመረምር የእኛ ትዉልድ ፈተና የኤትኖሴንሪክ የታሪክ መነጽር ወዴት እየወሰደን መሆኑን መገንዘብና በቅን ልቦና ላይ የተመሰረተ ብሄራዊ መግባባት የሚፈጠርበትን መንገዶች መሻት ነዉ። ችግሮችን መካድ ወይም መደበቅ ሳይሆን፤ በእዉቀት በዉይይት በዲሞክራሲና በፍትሃዊ ካሳ (restorative justice) የሚፈቱትን የታሪክ ጠባሳዎች እያጎሉ ጣት መቀስሩ ለማንም ጠቃሚ እንደማይሆን ማወቅ ነዉ። የዛሬ ተሽናፊዎች ነገ አሸናፊዎች ለመሆን እንዳይሰሩ፤ ይህንንም በር በጊዜዉና በቅጡ በብሄራዊ እርቅና መካካስ መዝጋት እንጂ፤ እንዴዉ በደረቁ የርስ በርስ ጦርነት ሂደቶችን እንደ ገድል እየቆጠሩ፤ ከበሮ መምታቱ፤ በግብር ከፋዩ ገንዘብ ስርግና ምላሽ መደገሱ፤ ለአንድነትና ለብሄራዊ መግባባት ጠቀሚ ርምጃዎች ሊሆኑ እንደማይችሉ፤ ከድግሱ በሁዋላ ቢሆንም፤ ግንዛቤ መዉሰድ ያስፈልጋል።

ከዚህም በላይ ኤትኖሴንትሪዝም የማእከላዊ መንግስትን ስልጣን ቢይዝም ሆነ ባይዝ የሚያልመዉ ስለ አንድ ንፁህ የጠራ የተቀባ፤ወርቃማና እግዚአብሄር ስለመረጠዉ ጭቁንና ስለተጎዳ ወዘተ ማህበረሰብ ስለሚኖርባት ቅኖናዊት ሀገር  (utopian state) መሆኑ መረሳት የለበትም። በዚህም የተነሳ የተረጋጋ የብዙሀን ብሄር ብሄረሰቦች ሀገርን ማስተዳደር ከባድ ፈተና ይሆንበታል። በብዙ ክልሎችም በነፃ ምርጫ ማሽነፍ ያስቸግረዋል። ቀልፍ የአስተዳደር የማከላከያ የኢኮኖሚ አዎታሮችን ቃል እንደሚገባዉ ማስተዳደር ይሳነዋል። አዲሲቱ ኢትዮጵያ መሆን ያለባት ከብሄርና ብሄረስቦች (nations, nationalities, ethnic groups, volks) የተዉጣጡ ስብስቦች (የህገ መንግስቱን መግቢያ ይመልከቱ) ተስማምተዉ የሚፈጥሩት ሀገር ናት የሚለዉም ምርጫ መር ከሆነ ዲሞክራሲ ጋር ማጣጣም አስቸግሮታል። ስምምነቱም ካልሰራ ደግሞ አንቀፅ 39ን ተጠቅሞ መሄድ ይቻላል የሚለዉን መፈፅም ቀላል አለመሆኑን ተረድቶታል። የሚሄደዉም ክልል ምንም እንኩዋን በአፍሪካም ሆነ በአወሮፓ ለጊዜዉ የሚታየዉ ብሄረሰብና ሃይማኖት ተኮር የሆነዉ የፖሊቲካ ምህንድስና ዉጤት አሉታዊ ቢሆንም፤ የተሻለ/ች አባት/እናት ሀገር መመስረት ይቻላል የሚሉ አሁንም አልጠፍም። ይህንን አካሄድ መፋትሄ ነዉ ብሎ ሀገሪቱ ባለችበት ሁኔታ ለህዝብ በሬፈርነደም ማቅረብ ግን ሃላፊነት የጎደለዉ አካሄድ ነዉ። የጋራ እሴቶችን፤ ክፉም ይሁኑ ደግ መኖራቸዉን መርሳት፤ ሰዎች ከአንድ በላይ ማንነት (dual or multiple identity) እንደሚኖራቸዉ፤ የሀገራት አመሰራረት ሁል ጌዜ ያለችግር አለመሆኑን በቅጡ አለመመርመርና የወዲፊቱን ጉዞ በቅጡ ማለም አለመቻልን ያመለክታል።

በመጨረሻም በዉጭ የምንኖር ኢትዮጰያዎያን ባንፃራዊ ነፃነት ስለምንገኝና ከጊዜ ወደጊዜ ቀጥራችንም እየበዛ ስለሄደ፤ እንደ አድዋ አይነት ሃገር አቀፍ የሆኑ እሴቶች ከማክበር የሚከለክለን ነገር መኖር የለበትም። በሃገራችንም የሰላም ድምፅ ከፍ ብሎ እንዲሰማ መሞከር ይኖርብናል። በመሬትና በአንዳንድ ጥቅሞች መደለልና የገዛ ጥላችንን ሳይቀር መፍራት የለብንም። ራሳችንን ከፍርሃት ነፃ ማዉጣት ይገባናል። ስለ አሀጉራዊ ስለአፍሪካ ዲየስፖራ፤ ስለአፍሪካ አሜሪካዉያን ሰለሃገር አቀፍ እሴቶች ዉርስና ቅርሶች መናገር መጻፍ፤ ማክበርና መዘክር ይኖርብናል። በተለያዩ ቦታዎች ያሉትን የታሪክ አሻራዎች (historical footprints) በምንችለዉ ዘዴ መረዳት፤ማሰባሰብና የተዘረፉት ቅርሳ ቅርሶች እንዲመለሱ መሞከር ይገባናል። የአክሱም ሃዉልት መመለስ የመጀመሪያ እንጂ የመጨረሻ መሆን የለበትም። ከበስተሁዋላም ሆነ ከፊት ሆነዉ የሚሰሩትንና የሚረዱትን ማመስገን ይገባል። ዶ/ር አበራ ሞላና አቶ ኪዳኔ አለማየሁ በመካከላችን መገኘታቸዉና እየሰሩ ያሉትንም ልናዉቅላቸዉና ልናበረታታቸዉ ይገባል። በብሄር ተኮር ፖለቲካ ዉስጥ ራሳችንን አጥረን፤ ታሪካችን የግጭት፤የረሃብ፡ የቸነፈርና የስደት ብቻ እንዳይሆን፤ዛሬ አፍሪካ አሜሪካዉያን የገቡበትን ራስን ያለማወቅ ቀዉስ (identity crisis)፤ ሌሎች አፍሪካዉያን ወገኖቻችን ያለባቸዉን የራስ መተማመን ችግር፤ ልጆቻችን በአዉሮፓ እንዳሉት አናሳ ኮሚኒቲዎች፤ የኢኮኖሚዉ፤የፖለቲካዎና የዕዉቀት ጭራ፤በሁዋላም የአሀገሮቹ ባዐዳን እንዳይሆኑ፤ ከወዲሁ ማስብና ዘዴ ማግኘት የእኛ የመጀመሪያ ትዉልድ ፈላሾች (immigrants) ፈተና ነዉ።

 

[1] አ.ኤ.አ በማርች 15, 2015 በዴንቨር ኮሎራዶ የአድዋ ድል መታሰቢያ በዓል ላይ የተደረገ ንግግር;;

comment pic

The post የብሄር ብሄረሰብ ፖለቲካና የአድዋ ድል – ሚንጋ ነጋሽ appeared first on Zehabesha Amharic.

በረከት ስምዖን “የትግራይ ተወላጅ የሆነ መለስን የሚተካ መሪ አይፈጠርም”ካሉ በኋላ ሕወሓቶች በብስጭት “ብአዴን”የሚለውን ቃል እንደ ስድብ እየተጠቀሙበት ነው

$
0
0

Bereket simon
“..አንተ ብኣዴን ….! …” አዲሱ ስድብ – አምዶም ገብረ ስላሴ

በመቐለ ከተማ ኣዲስ ስድብ ተፈጥሯለች። እቺ ስድብ ለማንኛውም በህወሓት መሪዎች ላይ የብቃት ጥያቄ ያነሳ ሰው እየተሰጠች ያለች ቃል ናት።

በትግራይ የተለየ ሃሳብ ያንፀባረቀ፣ ከባድ የህዝብ ጥያቄ አንስቶ ተቀባይነት ያገኘ፣ የልማት ይሁን የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ያነሳ ሰው ዓረና እየተባለ እንዲሸማቀቅ ይደረግ ነበር።

ሕወሓት ኣርባዋኛዉን አመት ባሳለፈችበት ወቅት፣ ኣቶ በረከት ስሞን የአቶ መለስን የትግል ድርሻ አስመልክተው ባቀረቡት “..የብኣዴን ኣቋም የሚያንፀባርቅ ..” (እሳቸው ጥናታዊ ፅሁፍ ያሉት) ፅሁፍ ካቀረቡ በኋላ ግን ነገሮች ተቀያይረዋል።
ኣቶ በረከት በፅሑፋቸው ኣቶ መለስ ከእንግዲህ በትግራይ መሬት ከመቶ ኣመት በሗላ ካልሆነ በስተቀር እሳቸው የመሰለ (የሚተካ) መሪ ዳግም የማይፈጠር መሆኑ ተነበዩ። ይቺ ኣገላለፅ ለህወሓት ካሁን በሗላ ኣገሪቱ የመምራት ብቃት ያለው ሰው የላቹምና ለኛ ተውልን የሚል መልእክት ያዘለች ነበረች።

በመድረኩ ነበሩ ያተባሉት ኣቦይ ስብሓት “..በረከት ያለውን ሙሉ በሙሉ ኣልቀበለውም፣ ከፈልግሁ ሺዎች ከመልስ የበለጡ እኔ የማውቃቸው ወጣቶች ማቅረብ እችላለው።..” በማለት በእጃቸው እያቃለሉ የኣት ስሙት መልእክታቸው ኣስተላለፉ።
ኣቶ ኣርከበ ዕቑባይም “..እኛ እዚህ ያደረሰን ህዝብ ነው። ትግሉ የመራን የትግራይ ህዝብ ነው። በግለ ሰው ወይም በቡድን ተመርቶ ለድል የበቃ ትግል ኣላውቅም..” የሚል መልእክት በማስተላለፍ ኣቶ በረከትን “..የት ነበርሽ እኛ ኣይደለም ወይ መንገድ መሪ እንድትሆኚ ያደራጀንሽ ..” ኣይነት መልእክት ኣስተላለፉላቸው።

የመለስ ራእይ የሚል መፎክር የያዙት ግን ብኣዴኖች ብቻ ኣይደሉም። በትግራይም ጭፍራ ያላቸው መሆኑን ይታወቃል።
ወደ ዋናው ሃሳቤ ልመልሳቹና ኣንተ ባዴን …! የሚል ቃል በመቐለ ስድብ ኣድርገው የሚጠቀሙበት ሰዎች እየበረከቱ ናቸው። ለነገሩ በፌስቡክም “…ብኣዴን ሲፏቁ ጉንበት 7 ናቸው..” የሚል ዘመቻ እንደተጀመረ እያነበብን ነው።
የኣማራ “..እንገንጠል..” የሚል ጥያቄም የብኣዴንና ህወሓት ልዩነት የወለደውና “..ብኣዴን ትግሉ የተለየ ኣቅጣጫ ሊያስይዘው ፈልጎ ያነሳው ሃሳብ ነው..” የሚሉ ሰዎች ኣሉ።

በወልቃይት ያለው ኣለመረጋጋትም የብኣዴን እጅ ኣለበት እየተባለ ይወራል። ለማንኛውም በመቐለ ከተማ የህወሓት ኣመራሮች ኣቅመ ቢስነት ያወራ ሰው “…ኣንተ ብኣዴን…” የሚል ስድብ እየወረደበት ያለበት ሁኔታ ነው ያለው።

ብኣዴን የህወሓት የቦክር ልጅ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን በትጥቅ ትግል ከነበረው ሚና በላይ እነ ስየና እነ መለስ ልዩነት በፈጠሩበት ወቅት የመለስ መቺ ሃይል መሳርያ በመሆን የተጫወቱት ተራ ይልቃል።

ለብኣዴኖች የምለግሰው ምክር የነብር ጭራ ኣይያዙ ከያዙም ኣይልቀቁ ነው። ብኣዴኖች በኣቋማቸው ከፀኑ ህወሓት ኣፍርሶ በቦታቸው ሌላ ድርጅት ይተክልላቸዋል ተብሎ ይጠበቃል።
‘…ኣንተ ባዴን …!”
ነፃነታችን በእጃችን ነው..!

The post በረከት ስምዖን “የትግራይ ተወላጅ የሆነ መለስን የሚተካ መሪ አይፈጠርም” ካሉ በኋላ ሕወሓቶች በብስጭት “ብአዴን” የሚለውን ቃል እንደ ስድብ እየተጠቀሙበት ነው appeared first on Zehabesha Amharic.

Health: 10 ትልልቅ የፊት አስተጣጠብ ስህተቶች

$
0
0

face wash wrong

ይህ ጽሁፍ በዘ-ሐበሻ ጋዜጣ ቁጥር 72 ላይ ታትሞ ወጥቷል

  1. የተሳሳተ ምርት መምረጥ

ፊትን መታጠብ በጣም ቀላል እና የተለመደ የዕለት ተዕለት ተግባር ይመስላል፡፡ ይሁን እንጂ ፊታችንን በምንታጠበብት ወቅት የምንጠቀማቸው አንዳንድ ምረቶች የፊት ቆዳችን ላይ የትየለሌ ችግር ሊያስከትሉ ይችላሉ፡፡ ከእነዚህ የቆዳችግሮች ውስጥ ድርቀት፣ የማቃጠል ስሜት፣ የወዝ መብዛት እና የቆዳ መሰነጣጠቅ በቀዳሚነት ስማቸው ይነሳል፡፡ እነዚህን ችግሮች ለመከላከል በዋናነት ስልምንጠቀማቸው የፊት ቆዳ ማፅጃዎች ምንነት እና አዘገጃጀት ማወቅ ጠቃሚ ነው፡፡ በተለይ በተለይ የማፅጃዎቹን ይዘት አውቆ መምረጥ መቻል ያለምንም የጎንዮሽ ጉዳት የምርቶቹ ተጠቃሚ ለመሆን ይረዳል፡፡

 

  1. ከልክ በላይ መታጠብ

አንዳንድ ሰዎች ፊታቸውን አያምኑትም፡፡ በቀን አስሬ መታጠብ ይቀናቸዋል፡፡ በወጡ በገቡ ቁጥር ውሃ ፊታቸውን ማስነካት የዘወትር ተግባራቸው ነው፡፡ የፊት ቆዳን በቀን አንድ ጊዜ አልያም ሁለት ጊዜ መታጠብ ይመከራል፡፡ ከሁለት ጊዜ በላይ ፊትን ሙልጭ አድርጎ መታጠብ በአንፃሩ የተለያየ የፊት ቆ ችግር የስከትላል፡፡ ችግሩ የሚከሰትበት አንዱ ምክንያት በተደጋጋሚ እጥበት ምክንያት የሚከሰትን ድርቀት ለመከላከል ቆዳችን ከልክ በላይ ዘይት መሰል ነገር ለማምረት ግዴታ ውስጥ ስለሚገባ ነው፡፡ ሜክአፕ፣ ሰንስክሪን እና መሰል መዋቢያዎችን የማትጠቀሙ ከሆነ እና ያን ያህል ላብ ፊታችሁ ላይ ከሌለ ምንም አይነት ማፅጃ ሳትጠቀሙ ለብ ባለ ውሃ ብቻ ፊታችሁን ማታ ማታ ታጠቡ፡፡ ከጊዜ ወደ ጊዜ ቆዳችሁ ምንም አይነት መዋቢያ የማይጠቀምበት እረፍት መስጠትም መልካም ነው፡፡

 

  1. ከልክ በላይ የጋለ ውሃ መጠቀም

ሞቃት ውሃ የፊታችንን ቆዳ ቀዳዳ ክፍት ያደርጋል፣ ቀዝቃዛ በሌላ በኩል ይዘጋል የሚል የተሳሳተ አመለካከት አለ፡፡ እውነታው ግን ፊታችን ላይ የሚገኙ ቆዳዎች ራሳቸውን የመክፈትም ሆነ የመዝጋት አቅም የላቸውም፡፡ እንደውም በሞቃት ውሃ ከልክ በላይ ቆዳችሁን በማጠብ ከፍተኛ ድርቀት ወይም አላስፈላጊ የሆነ ከፍተኛ የ‹ሴበም› ምርትን ሊያስከትል ይችላል፡፡ የሚመከረው ለብ ያለ ውሃ መጠቀም ነው፡፡

 

  1. ከልክ በላይ ‹ስክራብ› ማድረግ

የፊት ቆዳ ላይ የሚገኙ የሞቱ ህዋሶችን ቀርፎ በተለያየ መንገድ ማንሳት (ስክራብ) ተገቢ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ይሄም በልኩ መሆን መቻል አለበት፡፡ እነዚህን ህይወት የሌላቸው ህዋሶች ለማስወገድ ተፈጥሯዊ የሆኑ ነገሮችን መጠቀም ይመከራል፡፡ ከስኳር እና ከፍራፍሬዎች የሚገኝ አሲድ ተመራጭ ቆዳን ‹‹ስክራብ›› ማድረጊያ ናቸው፡፡ ቢበዛ ቢበዛ በሳምንት ሁለት እና ሶስት ጊዜ ብቻ ስክራብ አድርጉ፡፡ ስክራብ በምታደርጉበት ወቅት ቆዳችሁ ላይ ምንም አይነት ጉዳት እንዳይደርስ ከመታጠቢያ ፎጣ ይልቅ ጣታችሁን ተጠቀሙ፡፡

 

  1. በበቂ ሁኔታ አለመታጠብ

የፊት ቆዳን በአግባቡ አለመታጠብ የፊት ቆዳ ቀዳዳዎች እንዲደፈኑ እና ድርቀት እንዲከሰት ያደርጋል፡፡ ጠዋት ከእንቅልፋችሁ ተነስታችሁ ስራ ለመጀመር ጥድፊያ ውስጥ ሆናችሁም ይሁን ማታ ድቅቅ ብላችሁ ቤታችሁ ገብታችሁ ከመተኛታችሁ በፊት ፊታችሁን በሚገባ መታጠባችሁን አትዘንጉ፡፡

 

  1. የፊት ቆዳን የሚያቃጥሉ ምርቶች መጠቀም

ፓራቢንን የመሳሰሉ አርቴፊሻል ማቆያዎችን፣ መአዛቸው ደስ የሚያሰኙ ማቅለሚያዎችን ወዘተ በአለመጠቀም ለቆዳችሁ ውለታ ዋሉ፡፡ ሶዲየም ሎውሪል ሰልፌት ሌላኛው ልናስወግደው የሚገባ ንጥረ ነገር ነው፡፡ ምንም እንኳ የፈራረሱ ነገሮችን ለማፅዳት ጠቃሚ ቢሆንም በአመዛኙ ቆዳ እንዲቃጠል ያደርጋል፡፡ ይህ ብቻ ሳይሆን ለአንዳንድ ሰዎች አለርጂም ጭምር ነው፡፡ ሁልጊዜም ቢሆን የምትጠቀሙት ምርት ውስጥ ምን ምን አይነት ነገር በምን ያህል መጠን እንደሚገኝ ለመረዳት ሙከራ አድርጉ፡፡

 

  1. በፎጣ ፊትን መወልወል

ፊታችሁን በእጃችሁ አሻሹ እንጂ በፎጣ አትወልውሉ፡፡ በፎጣ ፊትን መወልወል ደስ የሚያሰኝ ነገር ቢሆንም በሌላ መልኩ ግን ቆዳን ሊልጥ እና ጉዳት ላይ ሊጥል ይችላል፡፡ ይህ ብቻ ሳይሆን በአቅራቢያችሁ የሚገኝ አገልግሎት ላይ የዋለም ይሁን ያልዋለ ፎጣ ዝም ብላችሁ አንስታችሁ አትጠቀሙ፡፡ አንድ ሰው የሚጠቀምበትን ፎጣ ሌላ ባይጠቀምም መልካም ነው፡፡ ንፁህ እና ለስላሳ ፎጣ መርጣችሁ ፊታችሁን ጠራርጉ፡፡

 

  1. ፊት እስከሚደርቅ መጠበቅ

ፊታችሁን ከታጠባችሁ በኋላ ወዲያውኑ እርጥበቱ ሳይጠ ፋፊታችሁን ለማለስለስ የምትጠቀሟቸውን መዋቢያዎች ተቀቡ፡፡ ፊታችሁ ከደረቀ በኋላ መዋቢያዎችን መቀባት የተቀባችሁት ማንኛውም ነገር የቆዳ ቀዳዳዎች ዝግ ስለሚሆኑ ወደ ውስጥ ለመግባት ይቸገራል፡፡ በዚህ ምክንያት ፊታችሁ እንደ አብለጨለጨ ሁሉ ትውሉ ይሆናል፡፡

 

  1. ብዙ ገንዘብ ማውጣት

ለፊት ቆዳ ጤንነት አጠባበቅ አቅም እስካለ ድረስ ምንም ገንዘብ አለማውጣት ትክክለኛ ውሳኔ ላይሆን ይችላል፡፡ ቀላል እና ተፈጥሯዊ የሆኑ ንጥረ ነገሮችን የያዙ የፊት ቆዳ ማፅጃዎችን ተጠቀሙ፡፡ ከዚህ ውጪ ውድ የሆኑ በአናቱም ተፈጥሯዊ ያልሆኑ የፊት ቆዳ ማፅጃዎችን መጠቀም አይመከርም፡፡ ይህ ተግባር ኪስንም የፊት ቆዳንም አንድ ላይ ይጎዳል፡፡

 

  1. ዘይት ነክ ማፅጃዎችን መፍራት

ረዘም ላለ ጊዜ ዘይት ነክ ማፅዎች እና ቅባቶች የቆዳ ቀዳዳዎችን ይደፍናሉ የሚል የተሳሳተ እምነት ነበር፡፡ ይህ እምነት ግን አሁን እየተቀየረ ነው፡፡ አጥኚዎች አሁን ቆዳን በዘይት ማፅዳት ጠቀሜታ ሊኖረው እንደሚችል በመግለፅ ላይ ይገኛሉ፡፡ ሌላው ቀርቶ ወዝ የሚበዛባቸው የፊት ቆዎች እንኳ በዚህ ተጠቃሚ ይሆናሉ፡፡ ዘይት ዘይትን ያሟሟል፡፡ ጥሩ ጥሩ የቆዳ ማፅጃ ዘይቶች ቆዳ ቀዳዳ ውስጥ የሚገኙ ቆሻሻዎችን እንዲሁም ባክቴሪዎችን ያፀዳሉ፡፡ የተጎዳ ቆዳን ለማከም ይረዳሉ፡፡ በመሆኑም ተፈጥሯዊ የሆኑ የአትክልት ዘይት ይዘት ያላቸውን ማፅጃዎች ተጠቀሙ፡፡

እንደዚህ አይነት ማፅጃዎችን በቀላሉ ማግኘት የማትችሉ ከሆነ እንኳ ጥራት ያላቸውን የአልሞንድ እና ሱፍ ዘይቶችን እንድትጠቀሙ ይመከራል፡፡ ኮኮናት እና ወይራ ዘይት ለአንዳንዶች በጥሩ ሁኔታ እንደሚሰሩ ቢታወቅም ለአንዳንዶች ግን ራሱን የቻለ ችግር ያስከትላሉ፡፡ በቀስታ ዘይቱን ፊታችሁ ላይ በጣታችሁ ከቀባችሁ በኋላ ለብ ያለ ውሃ ውስጥ በተነከረ ለስላሳ ጨርቅ መልሳችሁ ጥረጉ፡፡ የፊት ቆዳችሁ ቀዳዳዎች በየጊዜው ፊታችሁ ላይ ቀርቶ በሚጠራም ዘይት እንዳይደፈን ሙልጭ አድርጋችሁ በጥንቃቄ የፊት ቆዳችሁን አፅዱ፡፡

The post Health: 10 ትልልቅ የፊት አስተጣጠብ ስህተቶች appeared first on Zehabesha Amharic.

የወያኔ በሬ ላም ወለደ። ከ-ከተማ ዋቅጅራ

$
0
0

Ketemaበተለያዩ ጽሑፎቼ ለመዳሰስ በተወሰኑ ነጥቦች ሲሆኑ የማብራራት እና ሃሳብን በማሳደግ ዙሪያ እንዲሁም አስተያየትን በመስጠቱ ጉዳይ እንዲሁም የምታውቁትን የማሳወቁ ጉዳይ የአንባቢያን ይሆናል።

አፈ ዲሞክራሲ አፍነህ ግዛሲ የሆነው በኢሕአዲግ ስም የሚንቀሳቀሰው TPLF አውራ አውራ የሚባሉትን የኦሮሞ ህዝብን የሚወክሉ የአማራን ህዝብ የሚወክሉ የደቡብን ህዝብ የሚወክሉ እና የትግራይን ህዝብ  የሚወክሉ ጥምር ስም እንደሆነ እላይ እላዩን ሁሉም ህዝብ የሚያውቀው ጉዳይ ነው። እላይ እላዩን ያልኩበት ምክንያት ከላይ በጠቀስኳቸው ስም ምክንያት ማሊያ ለብሰው የሚጫወቱ የTPLF ሰዎች ስለሆኑ ኢሕአዲግ የሚለው ስም ከስምነት ያለፈ  እንደሌለው ለማደናገሪያነት ከመዋል ውጪ ምንም ፋይዳ እንደሌለው ስለሚታወቅ የላይ የላዩን የውጪ መንግስታትን እና ህዝብን ለማደናገር በጭቃ ቤት ላይ የአሸዋ ግርፍ ተገርፎ የድንጋይ ቤት ነው ብሎ እንደመዋሸት ያህል ወያኔ ኢሕአዲግ የሁሉ ብሔር ብሔረሰቦች የእኩልነት ድርጅት ነው ብሎ መደስኮር ከጀመረ ሃያ አራት አመት አስቆጠረ።

ልብ በሉ ወያኔ ሃያ አራት አመት ሙሉ የጭቃ ቤትን በአሸዋ ስለተገረፈ ብቻ የድንጋይ ቤት ነው ብሎ እየዋሸ እና እየሰበከን ያለው። አንዱ ነው አሉ ከሚስቱ ጋር ወደ ውጪ ለስራ ጉዳይ ይሄዳሉ ከዛም ይሄ ፓስታ ፒዛ የሰለቸው ባል  እንጀራ አማረኝ ጋግሪና  እንብላ ይላታል። ሚስትም እሺ ትልና ብዙ አመት ውጪ የኖሩትን ጎረቤታቸውን እንዴት እንደሚጋገር ጠይቃ ሁሉን ነገር ገዛዝታ ትመጣለች በኃላም ዛሬ እራት እንጀራ ነው ስትለው ደስ ብሎት የናፈቀውን እንጀራ ለመብላት የራት ሰአትን ይጠባበቅ ጀመረ። እናም እንጀራው ተጋግሮ የራት ሰአትም ደርሶ እራት ይቀርባል። እንጎቻ እንጎቻ የምታክል ነገር ከጠረጴዛው ላይ ተቀምጧል ዝም ብሎ ሲመለከተው ብላ የውጪ አገር እንጀራ እንደዚ ነው ብላ ኮስተር ስትልበት ባልም ሚስቱን በጣም ይፈራት ስለነበረ ከማነሷ አይን የሚባል የለውም እናም ትኩር ብሎ እያየው ቂጣ ነው ይሄ ነገር ብሎ ሚስቱን ሲጠይቃት አይደለም እንጀራ ነው ብላ ኮስተር አለች አጋገሩን ስላልቻለችበት አይን የሌለው ቂጣ የመሰለ ነገር ነበረ የጋገረችው። እሱም ሁለቱን ሳብ አድርጎ ሰሃኑ ላይ ካስቀመጠ እና ወጥ ካረገበት በኋላ ትኩር ብሎ የምግብ ሰሃኑን  እያየው እንጀራ ነህ እንጀራ ነህ ተብለሃል ብሎ መመገብ ጀመረ ይባላል። ወያኔም እያደረገ ያለው እንዲህ ነው። አሸዋ ግርፍ ቤት የድንጋይ ቤት ነው ብሎ ይናገራል ህዝቡም የድንጋይ ቤት ነህ ድንጋይ ነህ ብሎ መኖር ከጀመረ አመታቶች ነጉደዋል።

እውነትን እንጂ ውሸትን የማይቀበሉ ለህሊናቸው እንጂ ለሆዳቸው ያላደሩ የአሸዋን ግርፍ ቤት የአሸዋ ግርፍ ነው እንጂ  የድንጋይ ቤት አይደለም ብለው የሚናገሩ በእውቀትም በእውነትም የሚሄዱትን ወይ ከአገር በግድ እንዲወጡ ይደረጋሉ አልያም የእውቀት ሃብታም የገንዘብ ደሃ ሆነው ይኖራሉ፣ ወይም ደግሞ ምክንያት ተፈልጎባቸው ወደ እስር ቤት ይወርዳሉ። እነዚህ ሶስት መንገዶች ሲጠቃለሉ ስለእውነት ብለው ባላቸው እውቀት ትክክለኛ ነገር ስለሚናገሩ የሚታሰሩ ናቸው። ዛሬ ይሄ ሰውዬ ይሄ ሰውዬ ይህቺ ሴትዮ ይህቺ ሴትዮ ተብለው በሃብት ሚዛን ላይ የተቀመጡት የኧሸዋን ግርፍ የድንጋይ ቤት ነው ብለው የተቀበሉት እንደሆኑ ይታወቃል ከጥቂት ባለሃብቶች በስተቀር ያለው ሃቅ ይሄው ነው።ስር ሳይኖራቸው መሰረት ሳይጥሉ በአጭር ግዜ እንደ ሸንበቆ ተመዘው የሃብት  አናት ላይ ደርሰው የምናያቸው የኢሕአዴግ ካባ ለብሰው የTPLF ፖሊሲ የሚያራምዱ ናቸው።

ወያኔ ባለእውቀቶችን እና ባለእውነተኞችን የማይፈልግበት ዋናው ምክንያት የወያኔ አሰራርን የአሸዋ ግርፉን ፈልፈል ፈልፈል ቆፈር ቆፈር አድርገው ይሄ እኮ የጭቃ ቤት ነው ከስር መሰረትም የለውም ምሶሶዎችንም ምስጥ በልቶአቸው በስብሰዋል ስለዚህ ይሄ የግርፉን ቤት አፍርሰን በትክክለኛው መሰረት በጠበቀ ብረት ሁሉም ያለስጋት የሚኖርበት የድንጋይ ቤት እንሰራለን ለዚህም ብቃትም እውቀትን እውነትም አገር ወዳድነትም አለን ህዝብን የሚጠቅም አገርን የሚለውጥ እና የሚያሳድግ ችሎታ እንዳላቸው  እና ህዝቡም እንደሚከተላቸው ስለሚያውቁ ባለ  እውቀተኞችን እና ባለ እውነቶችን አየፈልጉም ወይ ያስራሉ ወይ ከአገር እንዲሰደዱ ያደርጋሉ።

ወደፊት አገር ነጻ በምትሆንበት ሰአት ብቁ መምህራን የሚገኙት ከዩንቨርስቲ ሳይሆን ከእስር ቤት ነው። እስር ቤት ስንል አንድም ከነእውቀታጨው ወይኒ የገቡት አንድም እውቀት ኖሯቸው እንዳያስተምሩ የታገዱት አንድም እውቀት ኖሯቸው ከአገር የተሰደዱት ነው። ህዝቡም በእውቀትም በእውነትም በሰላም እጦትም ታስሮ እንዳይኖር የእስር ቤትን ኑሮ አሸንፈው እንዲወጡ ግፈኝነትን ሰብረው ነጻነትን ለብሰው እውቀትና እውነትን ያስተምራሉ። እዚህ ጋር ግን ከዩንቨርስቲ መምህራን አይወጡም እያልኩኝ አይደለም። እውቀት እና እውነት ያላቸው የድንጋይ መሰረቶች እየተባረሩ እና እየታሰሩ የአሸዋ ግርፎች የሆኑት ግን በማስተማሩም በማደናበሩም ለወያኔ ተመራጭ ሆነው የወያኔ ስራ አስፈጻሚ ሆነው ይሾማሉ የሚለውን ሃረግ እንድትመዙልኝ እፈልጋለው።

ስለዚህ የተማረን የሚጠላ እና የሚፈራ እውነትን የማይቀበል እና የማያውቅ ለህዝብና ለአገር ይጠቅማል ተብሎ መጠበቅ በጠራራ ጸሐይ ዝናብ ይዘንባል ብሎ  እንደመጠበቅ ነው። ወያኔን የኢትዮጵያን ህዝብ ንቀውታል ጠልተውታል፣ ገፍተውታል ጥለውታል፣ ዘርፈውታል በልጽገውበታል፣ ሰልጥነውብናል ሰይጥነውብናል፣ ቂም በቀል አብቅለው  ቂም በቀል ዘርተውብናል። የሃያ አራት አመት ፍሬአቸውን የአሸዋ ግርፍ የማስመሰል ስራዎችን አስቃኝተውናል። ታዲያ ዛሬ ግዜው የሰሩትን የክፋት እና የግፍ ስራ ይቀበላሉ። የዘሩትን ማጨጃቸው የሰበሰቡትን መውቂያቸው የወቁትን ማከማቻቸው ግዜው ደርሷል። የአሸዋ ግርፍ ስራችሁ ተገልጦ ሲታይ መሰረት የሌለው ውስጡ ምስጥ የበላው የበሰበሰ ምሶሶዎች ተገልጠው የሚታዩበት የእውነት ግዜው ደርሷል አስመስሎ እና አስፈራርቶ መኖር ከአሁን በኋላ ተቀባይነት የለውም በአሸዋ ገርፋችሁ የውስጥ ማንነታችሁን ደብቃችሁ የተንኮል ስራችሁን ህዝብ ስለተረዳው የበሰበሱት ምሶሶዎችን መሰረት የሌሌው የአሸዋ ግርፍ ቤታችሁን ገፍቶ የሚጥልበት ግዜ እና እውነትን ከባለ እውቀቶች የምንሰማበት ግዜ ቅርብ ነው።

ሃሰት የእውነት ጠላት ነው። አላዋቂ የባለ እውቀት ጠላት ነው። ወንጀለኛ እውነትን ይፈራል። እውቀት የሌለለውም ባለ እውቀቶችን ይሸሻል። ወንጀለኛ ቢደበቅ ለጥቂት ግዜ መሃይምም ቢያዝ ለተወሰነ ግዜ ነውና ፡- እውነት እና እውቀት አሸናፊነታቸው ለሁል ግዜ ነው ነዋሪነታቸው ለዘለቄታ ስለሆነ ይሄንን እንከተላለን ።

ከ-ከተማ ዋቅጅራ

19.03.2015

Email-waqjirak@yahoo.com

 

The post የወያኔ በሬ ላም ወለደ። ከ-ከተማ ዋቅጅራ appeared first on Zehabesha Amharic.


ለብአዴን አባላት ……ከሰማችሁ …….ከሞግዚት አስተዳደር ተፋቱ! –አንበርብር ከአማራ ሳይንት

$
0
0

tplfአፄ ዮሃንስ ንጉስ ተከለ ጊዮርጊስን ድል ነስተዉ ጎጃም ሲገቡ ራስ አዳል አልተደሰቱባቸዉም ነበርና ራስ አዳል ሸሽተዉ በርሃ ገቡ፡፡ አፄዉ ለራስ ደስታ ተድላ ዘመዳቸዉን ድረዉ በጎጃም ላይ ይሾሟቸዋል፡፡ ሆኖም ግን አፄ ዮሃንስ በራስ ደስታ ተድላ ላይ ሙሉ እምነት አልነበራቸዉምና በስራቸዉ ሐጎስ የሚባል አስተዳዳሪ ሾመዋል፡፡ ራስ አዳል ግብር በዛብን ያለዉን ህዝብ አስተባብረዉ የአፄ ዮሃንስ ሰራዊት ሲያጠቁ በዉጊያዉ አፄዉ የሾሟቸዉ ራስ ደስታ እና ሞግዚቱ ሐጎስ ይገደላሉ፡፡

የሟቾችን አስክሬን ወደቀብር ሲወጣ የራስ ደስታን በእንጨት አልጋ፤ የሐጎስን በአጎበር በተከለለ አልጋ ሲወሰዱ ባለቅኔዉ የጎጃም ህዝብ

“እኔስ ምን ቸገረኝ ካንተ አልዋጋ
እስራኤሉን በእንጨት ወታደሩን ባልጋ”

እያለ ሲቀኝ እንደነበር እና የሞግዚት አስተዳደር መጨረሻዉ ዉርድት እንደሆነ ታሪክ ይነግረናል፡፡(ምንጭ፡- የንግስና ሥርዓት እና የነገስታት የዘር ሃረግ፤በጥላሁን ብርሃነ ስላሴ)

የሞግዚትነት አስተዳደር ሙሉ አስተዳደር አይደለም፡፡ የይስሙላ አስተዳደር ነዉ፡፡ ሲፈለግ የሚፀና ሳይፈለግ የሚነሳ፣ ያልፀና እና መልካም ፈቃድን ያልተከተለ አሰራር ነዉ፡፡ የሞግዚትነት አስተዳደር ህዝብን ካለማመን የሚነሳ ቢሆንም ዋና ዓላማዉ የራስን የበላይነት ጠብቆ ማቆያ ነዉ፡፡

አፄ ዮሃንስ ጎጃሜዉንና ሆነ ራስ ደስታን ስላላመኗቸዉ፣ የሐጎስ ሞግዚትነት አስፈልጓቸዋል፡፡ የሞግዚት አስተዳዳሪነት ህዝብን ካለማመን እና ከመጠራጠር መጥቶ በመጨረሻዉ ሰዓት ክብር የሚሰጠዉ ለሞግዚቱ ነዉ፡፡

ሕወሓት-ኢህአዴግ በየቦታዉ ከሚሾማቸዉ አስተዳደሪዎች ጀርባ አንድ ሞግዚት እንደሚያስቀምጥ ትንሽ እልፍ ወይም ገባ ብሎ ለመመረመረ ከነደስታ ጀርባ ሺህ ሐጎሶችን መመልከት ይችላል፡፡ በሞግዚት አስተዳደር ስር መዉደቅ ሁለት ጊዜ መሞት ነዉ፡፡ አንድ ጊዜ ተንቆ እየተደገፉ መኖር እና ነፃነትን ማጣት ሲሆን ሁለተኛዉ በህዝቡም ሆነ በገዥወቻችሁ ፊት ታማኝነት ማጣት እና በስተመጨረሻ የራስ ደስታን ዕጣ መጋራት ነዉ፡፡

የብአዴን ሰዎች እኔ ከማዉቃችሁ ሰዎች ጨምሮ ኑሯችሁ የቀንድ አዉጣ፣ አስተዳደራችሁ የሞግዚት አስተዳደር እና ከሁለት ያጣ ወገን የሆናችሁ ናችሁ፡፡ በቅርብ እየሰማነዉ እንዳለሁ ጀርባችሁ ሲፋቅ ግንቦት 7 እየተባላችሁ፣ ታማኝነታችሁን አጥታችኋል፡፡ በእነ ሓዱሽ እየገፋችሁት ያለዉ የሞግዚት አስተዳደራችሁ ወደ ሞት የሚወስዳችሁ ከመሆኑ በላይ እናንተን በእንጨት ሞግዚታችሁን በወርቅ ሲጭኗችሁ ሁለተኘዉ ሞት ነዉ፡፡

ጊዜዉ ወደ ወገን የመጠቅለያ ነዉ፡፡ ያረጁትን የብአዴን መሪዎቻችሁን እርሷቸዉ እና ከአዲሱ የአማራዉ ክልል ትዉልድ ጋር ስለህዝባችሁ ተነጋሩ፡፡ በመንግስት ላይ አሻጥር እየሰሩ ስልጣን የያዘዉን አካል ማንኮታኮት እና ማዉረድ ከእናንተ ይጠበቃል፡፡ እኔ የማምናቸዉ ብአዴን ዉስጥ ሰርገዉ የገቡ የቅርብ ሰዎች አሉኝ፡፡ ድርጅቱን በብዙ ነገር እየበከሉት ቀፎዉን ሲያስቀሩትእያየሁ ብዙ ጊዜ አብረን የድርጅቱን መፍረሻ ቀን ቆጥረናል፡፡ አሁንም አስተሳሰብ ለዉጥ ላይ እያተኮርን በየመስሪያ ቤቱ ብአዴን በሚያካሂደዉ አደረጃጀት እና ስብሰባ እየገባን ሌሎችን በአስተሳሰብ ነፃ እያወጣን ጎድጓዱን አርቀን መቆፈር እንችላለን፡፡

እንደ መዉጫ የሞግዚት አስተዳደርነት መነሻዉ ህዝብን መናቅ እና አለማመን ስለሆነ እንደ ራስ ደስታ ሁለተኛ ሞት ሳንሞት ራሳችን ከሞግዚትና ከአሳዳሪዎቻችን ነፃ እናድርግ፡፡ የብአዴን አባሎች ሕወሓት በተደጋጋሚ ጀርባቸዉን ሲፍቀዉ ግንቦት 7 ናቸዉ እያላችሁ ሳትታመኑ አብራችሁ ልትኖሩ አይገባም፡፡ ከድርጅቱ በአስተሳሰብ በልጣችሁ ሄዳችሁም አልሄዳችሁም ከመጠርጠር እና ካለመታመን ስለማትድኑ ዛሬዉን ከሞግዚት አስተዳደር ራሳችሁን አላቃችሁ ተከተሉን፡፡

 

The post ለብአዴን አባላት ……ከሰማችሁ …….ከሞግዚት አስተዳደር ተፋቱ! – አንበርብር ከአማራ ሳይንት appeared first on Zehabesha Amharic.

በመስሊሙ ማህበረሰብ ላይ ህወሃት የዘረጋውን የጥላቻና የበቀል ዘመቻ ለመከላከል የወጣ የአቋም መግለጫ

$
0
0

MUslimHኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች የተጣሰውን ህገመንግስታዊ መብት በህግ ለማስከበር የጀመሩት ሰላማዊ ትግል ድፍን ሶስት ዓመታትን አስቆጥሯል፡፡ ይህ ትግል በመላው አለም ሰላማዊ ትግልን መታገል ለሚሹ አርአያ ከመሆኑም ባሻገር በተለያዩ አለም አቀፍ ተቋማት እውቅናን ያገኘም ነው፡፡ በነዚህ መራራ ሶስት የትግል አመታት ህዝቡ በፊርማው የመረጣቸው የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎች የእስር ብቻ ሳይሆን የድብደባ፣ የግርፋት፣ የማዋረድ፣ የሰብዓዊ መብትም መገፈፍ ሰለባ ሆነዋል፤ በሺዎች የሚቆጠሩ ሲታሰሩ፣ ሲገረፉ፣ ቁጥራቸው በውል የማይታወቅ ደግሞ ለመሰደድ በቅተዋል፡፡ሰላማዊ ዜጎች በግፍ ጥይት እየተደበደቡ ለሞት መዳረጋቸው ሊካድ የማይችል የአደባባይ ሚስጥር ነው፡፡[ሙሉውን መግለጫ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]—–

The post በመስሊሙ ማህበረሰብ ላይ ህወሃት የዘረጋውን የጥላቻና የበቀል ዘመቻ ለመከላከል የወጣ የአቋም መግለጫ appeared first on Zehabesha Amharic.

ማርች 8’ትን ስናስታውስ –በላይ ገሠሠ

$
0
0

Birtu & Aregashበሕብረተሰባዊ የዕድገት ታሪክ ውስጥ ሴቶች ለነፃነት፣ እኩልነት፣ ለሰብኣዊ መብትና ፍትሕ መረጋገጥ የከፈሉትን መስዋእትነት ትልቅ ስፍራ ይዞ ይገኛል:: ይህ በመሆኑም ዘንድሮም እንደ ተለመደው በዓለም አቀፍ ደረጃም ሆነ በሀገራችን መከበሩ የሚያሳየን የማርች 8 በዓል ታላቅነት ነው:: በሀገራችን የትግል ታሪክም በተመሳሳይ መልኩ ሴቶች ያልተሳተፉበት የነፃነት ትግል አልነበረም ቢባል የተጋነነ አይደለም:: የባዕዳን ሐይሎች ሀገራችንን በወረሩበት ጊዜም እቴጌ ጣይቱን ጨምሮ ቁጥራቸው ቀላል ያልሆኑ ሴቶች ዘማችና አዝማች በመሆንና ከወንዶች እኩል በመሰለፍ ለኢትዮያችን ህልውና ኩቡር መስዋእትነትን ከፈለው አልፏል:: በዘመናችንም የስርዓት ለውጥ ለማምጣት የተካሄደው ሁለ ገብ መራራ ትግልም የሴቶች ተሳትፎ ወሳኝ ሚና ተጫውቷል:: በዚሁ መራራ ትግልም እነ ማርታን ጨምሮ በሽዎች የሚቆጠሩ ጀግኖች ሴቶች አኩሪ መስዋእትነትን ከፍለው አልፏል:: —[ሙሉውን መግለጫ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]—

 

Download (PDF, 1.22MB)

 

The post ማርች 8’ትን ስናስታውስ – በላይ ገሠሠ appeared first on Zehabesha Amharic.

የሃገሪቱን ሃብት የወያኔ ባለስልጣናት ከጉምሩክ መጋዘኖች ሲዘርፉ አደሩ

$
0
0

Samora (2)
በሃገሪቱ አንጡረ ሃብት ላይ ከፍተኛ ዘረፋ እና በሕዝብ ላይ ከፍተኛ ጭቆና በማድረግ ላይ የሚገኙት የወያኔ ከፍተኛ ባለስልጣናት በጄኔራሎች እና በደህንነት ባለስልጣናት እየተመሩ ለሊቱት ከጉምሩክ መጋዘኖች በውርስ የገቡ እቃዎችን ሲጭኑ ያደሩ መሆኑን ምንጮች ከአዲስ አበባ ገልጸዋል::

ለሊቱን በአዲስ አበባ ውስጥ በሚገኙ የጉምሩክ መጋዘኖች የተወረሱ የመኪና መለዋወጫዎች የኤሌክትሮኒስ እቃዎች የሞባይል ቀፎዎች ውድ ጌጣጌጦች የቤት እቃዎች የመሳሰሉት በባለተሳቢ መኪናዎች አስጭነው መውሰዳቸው ሲታውቅ እቃዎቹ በሃገሪት በተለያየ አከባቢ ተበትነው እንደሚሸጡ ምንጮቹ ገልጸው ለሊቱ የጄነራል ሳሞራ የኑስ የሜ/ጄነራል ተክለብርሃን እና የአርከበ እቁባይ መኪኖች እና ጠባቂዎቻቸው እና ተላላኪዎቻቸው በየመጋዘኖቹ ሲዘዋወሩ እንደነበር እና ለዚህ ዘረፋ ተሳታፊዎቹ እነማን እንደሆኑ በግልጽ ያሳያል ሲሉ ምንጮቹ ገልጸዋል::

የወያኔ ባለስልጣናት ሕዝብን እየጨቆኑ እየዘረፉ እስከመቼ እንደሚቀጥሉ የሚያሳስብ ጉዳይ መሆንን አውቀን ህዝብን እና ሃገርን ከዘረፋ እና ከጭቆና ለማዳን ከለውጥ ሃዮች ጎን በመቆም በሃገር ውስጥ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችን በአስተባበር እና ሕዝብን በመቀሰቀስ ከአስከፊው ስርአት ነጻ ለመውጣት በጋራ መንቀሳቀስ አለብን:: ነጻነታችንን ማራጋገጥ የምንችለው እኛው ታግለን መሆኑን ማውቅ ያለብን ወስኝ ወቅት ላይ ስለሆንን በአንድነት በመቆም ይህንን የሌቦች መንግስት ስርአተ ቀብር እናጣድፈው ዘንድ ጠንክረን መስራት አለብን::

Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)

The post የሃገሪቱን ሃብት የወያኔ ባለስልጣናት ከጉምሩክ መጋዘኖች ሲዘርፉ አደሩ appeared first on Zehabesha Amharic.

ኦቦ ሌንጮና ያልተወራረደው ሂሳብ

$
0
0

lencho leta
By Dawit Solomon

የኦነግ ከፍተኛ አመራር የነበሩት ሌንጮ ለታ የስደት ህይወታቸውን ቋጭተው አገር ቤት ስለመግባታቸው እያደመጥን ነው፡፡በዚህ መቼም ደስ የማይሰኝ የአገሬ ልጅ ይኖራል ብዬ አላስብም፡፡ደስታውን ሙሉ የማያደርገው በፖለቲካ አመለካከታቸው የተነሳ ብዙዎች አሁንም ከቀያቸው ተፈናቅለው፣አልያም ለእስር ተዳርገው በመገኘታቸው ብቻ ነው፡፡
በዚህች አገር ሁሉም አመለካከቱን እያራመደ መኖር የሚችልበት የፖለቲካ ሰርዓት ባለመፈጠሩ የሌንጮን ወደ አገር ቤት መመለስ እንደ ትንግርት እየቆጠርነው ነው፡፡
ምናልባት የሌንጮ የፖለቲካ ቁመና እንደ ቀድሞው ላይሆን ይችላል፣ጦር መዝዞ የነበረው ኦነግም የተቃዋሚዎች ዕጣ ደርሶት ተሰነጣጥቆ ይሆናል፡፡ሌንጮ ግን ድርጅቱን ለረዥም አመታት በመምራት ትልቅ ስም ገንብቷል፡፡እናም ኦነግ ሲባል ሌንጮ ሌንጮ ሲሰኝ ኦነግ ብቅ ይልብናል፡፡

የሌንጮ ኦነግ በዘመነ የሽግግር መንግስት በአሩሲ፣በአርባ ጉጉና በበደኖ ዘር ተኮር የሆነ ጥቃት በማድረስ ብዙዎችን ለህልፈተ ህይወት ስለመዳረጉ በህወሓት ቁጥጥር ስር የሚገኘው የቀድሞው ኢቴቪ መዘገቡ አይዘነጋም፡፡የኦነግ አመራር በበኩሉ ከአገር ከወጣ በኋላ ባወጣቸው መግለጫዎች ለጭፍጨፋው ተጠያቂ መሆን የሚገባው የህወሓት ኦህዴድ ስለ መሆኑ ተናግሯል፡፡

የተፈጸመው ጭፍጨፋ አለም አቀፍ ወንጀል በመሆኑና በጊዜ ይርጋ ስለማይታገድ ዛሬም ለመናገር አልረፈደም፡፡በጭፍጨፋው ወላጆቻቸውን፣የትዳር አጋሮቸቸውን፣ልጆቻቸውን በግፍ የተነጠቁ ዜጎች በመኖራቸው ሌንጮ የሚሰጡት የእምነት ክህደት ቃል ትርጉም እንደሚኖረው ይሰማኛል፡፡

ምናልባት ከመስኮት በስተጀርባ በተደረገ ድርድር ይህ ጉዳይ እንደማይነሳ ስምምነት ተደርሶ ወደ አገር እንዲገቡ መደረጋቸውን መጠርጠር ባይከፋም ክቡር የሆነውን የሰውን ህይወት ስላጠፋ ክስተት አለመነጋገር የዜጎችን ፍትህ የማግኘት መብት ከመርገጥ አይተናነስም ፡፡

ሌንጮ ይመሩት የነበረው ድርጅት ድርጊቱን አለመፈጸሙን እንደ ቀድሞው መመስከር ቢችሉ ይህንን የማስረዳት ሸክም በህወሓትና ኦህዴድ ላይ ይወድቃል፡፡ኦነግ በእርግጥ ድርጊቱን ፈጽሞ ከነበረም የድርጅቱ ሊቀ መንበር ኦቦ ሌንጮ የእጁን ማግኘት ይኖርበታል፡፡

The post ኦቦ ሌንጮና ያልተወራረደው ሂሳብ appeared first on Zehabesha Amharic.

Viewing all 8745 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>