Quantcast
Channel: ዘ-ሐበሻ – Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 8745 articles
Browse latest View live

ሰላማዊ ሰልፉ ላይ ከታሰሩት መካከል አብዛኛዎቹ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል * ማዕከላዊ አጠገብ የሚገኝ እስር ቤት ተወስደዋል

$
0
0

(ነገረ ኢትዮጵያ) በሰልፉ ሰልፉ ወቅት ታፍሰው ከታሰሩት መካከል አብዛኛዎቹ እጅና እግራቸውን እንደተሰበረ እማኞች ገልጸዋል፡፡ ታሳዎቹ መጀመሪያ ከነበሩበት ጨርቆስ አካባቢ የሚገኝ እስር ቤት ምሽት ሶስት ሰዓት ላይ ሶስተኛ ወደተባለው እስር ቤት ሲዘዋወሩ እያነከሱና በሌሎች ታሳሪዎች ደግፈዋቸው ታይተዋል፡፡ ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት እጁን እንደተሰበረ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ከዚህም ባሻገር ብርሃኑ ተክለያሬድና ሌሎች በርካታ ታሳሪዎች በሌሎች ታሳሪዎች ተደግፈው ታይተዋል፡፡
semayawi
በሌላ ዜና በሰላማዊ ሰልፉ ወቅት የታፈሱት አመራሮች ማዕከላዊ አጠገብ ወደሚገኘው እስር ቤት ተዛወሩ::

9ኙ ፓርቲዎች በጠሩት ሰላማዊ ሰልፍ የታፈሱትና ጨርቆስ ፖፖላሬ እስር ቤት ታስረው የነበሩት የፓርቲ አመራሮች፣ አባላትና የሰላማዊ ሰልፍ ተሳታፊዎች ማዕካለዊ ጥግ ወደሚገኘውና በተለምዶ ሶስተኛ ተብሎ ወደሚጠራው እስር ቤት መዛወራቸው ታወቀ፡፡

ታሳሪዎቹ ከጨርቆስ ፖሊስ ጣቢያ ወደ ሶስተኛ የተዛወሩት ከምሽቱ አንድ ሰዓት በኋላ ሲሆን ሶስት ሰዓት ተኩል አካባቢ በሶስትትልልቅ አውቶቡሶች የታጨቁ ታሳሪዎች ሶስተኛ ፖሊስ ጣቢያ መድረሳቸውን የአይን እማኞች ገልጸዋል፡፡ በተመሳሳይ በሌላ አውቶቡስ የተጫኑ እስረኞች ወደ ሌላ እስር ቤት መዛወራቸው ታውቋል፡፡ ይህ በዚህ እንዳለ ለታሳሪዎች እራትና ልብስ ሊያድሱ ወደ እስር ቤት ያቀኑት ቤተሰቦችና የትግል አጋሮች ምግብ እንዳያስገቡ መከልከላቸውን ገልጸዋል፡፡ በሌላ ካሳንቺስ አካባቢ የሚገኘውና ስድስኛ ተብሎ በሚጠራው እስር ቤት አካባቢ ሌሎች ታሳሪዎች እንደሚገኙ ታውቋል፡፡ ጨርቆስ እስር ቤት ታስረው የነበሩት ሁሉም አመራሮች፣ አባላትና የሰልፉ ተሳታፊዎች ወደ ሶስተኛ ወይንም ሌላ እስር ቤት ይዛወሩ አይዛወሩ እርግጠኛ መሆን አልተቻለም፡፡

የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች፣ አባላትና ተሳታፊዎች ከታፈሱበት ጊዜ ጀምሮ ሶስት ያህል እስር ቤቶች እንደተዛወሩ ለማወቅ ተችሏል፡፡


የነፃነታችን ዋስትና ከባዕዳን ቁጥጥር ነፃ የሆነ ሕዝብን በማማከል የጋራ ምክክርና መግባባትን መሰረት ያደረገ የተባበረ ሕዝባዊ ትግል ነው መግባባትን መሰረት ያደረገ የተባበረ ሕዝባዊ ትግል ነው

$
0
0

ኅዳር 27፣ 2007 (ዲሴምበር 06፣ 2014)

shengo&ENTCበሀገራችን ውስጥ በአሁኑ ወቅት ምን እየተካሄደ ነው? ብለን ስናጤን በአንድ በኩል ነፃነት የጠማው ሕዝብ የትግል ኃያልነትና በሌላ በኩል ደግሞ ሀገራችን ኢትዮጵያና ሕዝቧ በምን ዓይነት ጨካኝና ዘረኛ ሥርዓት ሥር ወድቀው እንደሚገኙ የሚያሳይ ጉልህ ክስተትን እንገነዘባለን። ምርጫ 97ትን ተከትሎ ህወሓት/ኢህአዴግ በደረሰበት ሽንፈት ተደናግጦ በጥቅምት ወር እጅግ አሳዛኝ ጭፍጨፋ፣ እሥራትና ሽብር በሕዝባችን ላይ ፈጸመ። የሕዝብ ድምፅ መቆጠር ሲጀምር ገና ከጅምሩ ተቃዋሚዎች እንዳሸነፉ የተገነዘበው መለስ ዜናዊ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አውጆ ኮሮጆ ግልበጣውን ተያያዘው። በዚህም የድምፅ ስርቆት ከሕዝብ ድምፅ ገልብጦ በተቃራኒው ኢህአዴግ አሸናፊ ነኝ ብሎ አወጀ።  ____[ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]_____

 

 

 

የኦባንግ ጉዞና ለዲያስፖራው ፖለቲካ ያለው አስተዋጽአ

$
0
0

Gishag70@yahoo.com
Save Ethiopian Meeting with Obang metho in Israelበቅርቡ ብዋሽንግተን ዲሲ ከተማ በአቶ ኦባንግ ሜቶ በተጠራው ስብስባ ላይ የመገኘት እድል አጋጥሞኝ ነበር : በስብሰባው ላይ ከተለያዩ የአለም ክፍሎችና ከአሜሪካ ግዛቶች የተሰባሰቡ
በርካታ ኢትዮጵያውያን ተገኝተዋል::
የስብሰባው መሪ ሀሳብ “ስለ እያንዳንዳችን ከመናገር እያንዳንዳችን እንነጋገር” የሚል ድፍረትን : ግልፅነትን : መከባበርን: መነጋገር መቻልን ሃላፊነት በተሞላበት ስሜት ይቀርቡ በነበሩት አስተያየቶች የሚያረጋግጡ ከመሆናቸውም በላይ የተለየዩ የፖለቲካ አመለካከት : እምነት እንዲሁም የተለየዩ ብሄረሰቦች ዉሁድ ኢትዮጵያውያን በአንድ ጠረጴዛ ዙርያ ተቀምጠው ያነሱዋቸው የነበሩት ሃሳቦች በጥንታዊት ኢትዮጵያና በአዲሲቱ ኢትዮጵያ የፖለቲካ ገመድ ጉተታ ግራ ለተጋቡ ጥሩ አስተማሪ መድረክ ነበር:  —–-[ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]______

በአገዛዙ አረመኔያዊ እርምጃ ትግላችን አይቆምም! –ከትብብሩ የተሰጠ መግለጫ

$
0
0

addis ababa semayawi partyየ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ባለፈው አንድ ወር ‹‹ነጻነት ለፍትሓዊ ምርጫ›› በሚል መርሃ ግብር ቀርጸን ስንቀሳቀስ ዋናው አላማችን የስርዓቱን አረመኔያዊነት ለህዝብ በማጋለጥ የኢትዮጵያ ህዝብ በትግሉ እንዲሳተፍ ማድረግ ነው፡፡ እንደጠበቅነው ገና ከጅምሩ የህወሓት/ኢህአዴግ አገዛዝ ትግላችንን በጭካኔ ለማስቆም ጥሯል፡፡ ህዳር 7/2007 ዓ.ም የመጀመሪውን የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ በጠራንበት ወቅት ስብሰባውን በኃይል በትኗል፡፡

ትብብራችን ከመቸውም ጊዜ በላይ ያሰጋው ህወሓት/ኢህአዴግ በተለይ የህዳር 27/28 2007 ዓ.ም የአደባባይ አዳር ሰልፍን እንዳይካሄድ የትብብሩን አመራሮችና አባላቶቻችን በማዋከብ፣ በመደብደብና በማሰር ተጠምዶ ሰንብቷል፡፡ በተለይ በትናንትናው ዕለት ሰልፍ በወጣንበት ወቅት ስርዓቱ አመራሮችንን፣ አባላቶቻችንን፣ ተሳታፊዎችንን እንዲሁም አልፎ ተርፎ መንገደኛውን ህዝብ በጭካኔ ደብድቧል፡፡ አፍሶ አስሯል፡፡ ሙስሊም እህትና ወንድሞቻችን በየጎዳናው ታፍሰው የአገዛዙ አረመኔያዊ እርምጃ ሰለባዎች ሆነዋል፡፡ በርካቶችም በእ
በየ እስር ቤቶቹ ታጉረዋል፡፡ እስካሁን ባለን መረጃ ከ300 በላይ የትብብሩ አመራሮችና አባላት የታሰሩ ሲሆን የትብብሩና የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበርን ጨምሮ በርካታ አመራሮች ከፍተኛ የአካል ጉዳት ድርሶባቸዋል፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ቋሚ ኮሚቴ አባል የሆነው አቤል ኤፍሬም ራሱን እስኪስት ተደብድቧል፡፡ በሰላማዊ ሰልፉ የተገኙ ሴት አመራርና አባላት አንድ አገርን እየመራሁ ነው ከሚል አካል በማይጠበቅ መንገድ በጭካኔ ተደብድዋል፡፡ እነዚህ በጭካኔ የተደበደቡ አመራሮች፣ አባላትና የሰልፉ ተሳታፊዎች ህክምና እንዳያገኙ ተከልክለዋል፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት በጥበቃ ሰራተኝነት የሚሰሩ የ72 አመቱ አቶ ቀኖ አባጆቢር ከስራ ሲወጡ በደህንነት ኃይሎች ታፍነው የተወሰዱና እስካሁን የት እንደደረሱ ያልታወቀ ሲሆን ይህም አገዛዙ የመጨረሻው የአረመኔነት ደረጃ ላይ እንደደረሰና ይህን የስርዓቱ ውንብድና ለማስቆም ጊዜ የማይሰጠው ተግባር መሆኑን በግልጽ የተገነዘብንበት ነው፡፡

አገዛዙ በትናንትናው ዕለት በፍጹም ሰላማዊ ሰዎች ላይ የወሰደው የውንብድና እና አረመኔያዊ እርምጃ በትግሉ ውስጥ የምንጠብቀውና ስርዓቱ ለኢትዮጵያ የማይበጅ መሆኑን ዳግመኛ ያያ

ረጋገጠበት ነው፡፡ የትናንትናው ትላችን አገዛዙ ለይስሙላ እከተለዋለሁ ከሚለው ‹‹ህጋዊ ሰርዓት›› ይልቅ ስልጣኑን በኃይል ለማስጠበቅ ቆርጦ መነሳቱን እና በህገ መንግስት ስም ህዝብን የሚበድልበትን የአረመኔያዊነት ጭንብል ገልጠን ለዓለም ያሳየንበት የትግላችን ውጤት ነው፡፡

አገዛዙ ላላፉት 24 አመታት ስልጣኑን በኃይል ለማስጠበቅ ሲጥር ቆይቷል፡፡ በትናንትናው ዕለት የፈጸመው ፍጹም አረመኔያዊ እርምጃም እንደተለመደው ሰላማዊ ታጋዮችን ያሸማቅቃል ብሎ አስቦ እንደሆነ እሙን ነው፡፡ ነገር ግን ይህ የአገዛዙ አረመኔያዊነት ከሰላማዊነታችን ፍጹም ወደኋላ ሊያንሸራትተን አይችልም፡፡ ወደ ትግል ስንገባ የስርዓቱን ጭካኔና ለኢትዮጵያ የ

ማይመጥን መሆኑን አውቀንና የሚያስከፍለውን መስዋዕትነት ለመክፈል ተዘጋጅተንም ነው፡፡ አሁንም አገዛዙ የህዝብን ድምጽ በማፈን ስልጣኑን ለማስጠበቅ ተመሳሳይ እርምጃ እንደሚወስድ እንጠብቃለን፡፡ ነገር ግን መጀመሪያውንም ትግሉን ስንቀላቀል አስበን የገባነው እየቆሰልን፣ እየታሰርንም፣ እየሞትንም ድምጽ ለሌላቸው ድምጽ ለመሆን ነውና ከትግላችን ቅንጣት ሊያደናቅፈን አይችልም፡፡ ስለሆነም ወደፊትም ይህን የአገዛዙን አረመኔያዊነት በማጋለጥና ህዝቡን በትግሉ በማሳተፍ ለኢትዮጵያ የሚገባት ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን ለመመስረት በቀጣይነትም ማንኛውንም መስዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ ነን፡፡

በዚህ አጋጣሚ ሰላማዊ ሰልፉን ለማሳካት እንዲሁም የህወሓት/ኢህአዴግ ቡድን የፈጸመውን ጭካኔ በማውገዝ ከጎናችን ለቆማችሁ ሁሉ ምስጋናችን የላቀ ነው፡፡ ከህወሓት/ኢህአዴግ አገዛዝ ጋር የሚደረገው ትግል እልህ አስጨራሽ፣ ከፍተኛ መስዋዕትነት የሚያስከፍልና የእያንንዳንዳችን ትብብር የሚጠይቅ መሆኑን ተገንዝበን ሁላችንም በጋራ እንድንቆም ጥሪያችንን እናቀርባለን

ያለ መስዋዕትነት ድል የለም፡፡

የሲቪል ማኅበራት የመፍረስ አደጋ ተጋርጦባቸዋል

$
0
0

በበጎ አድራጎት ሥራዎች ላይ ለበርካታ ዓመታት ተሰማርተው የቆዩ ማኅበራት ፍቃድ ማደሰ ባለመቻላቸው ሕልውናቸው አደጋ ውስጥ መግባቱ ተገለጸ፡፡

newsየሲቪል ማኅበራትና በጎ አድራጎት ድርጅቶች ኤጀንሲ ማኅበራቱ አዋጁ በሚፈቀድው መሠረት አደራጃጀታቸውን ካላስተካከሉ ፈቃድ እንደማይታደስላቸው አስታውቋል፡፡

በዚህ ሒደት ከመቶ በላይ የሚሆኑ ሲቪል ማኅበራት በድጋሚ መዋቅራዊ ማስተካከያ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል፡፡ መዋቅራዊ ማስተካከያ ቢያደርጉም የመዘጋት ዕጣ ፈንታ የተጋረጠባቸው ግን አሉ፡፡ በርካታ በጎ አድራጎት ድርጅቶች መጀመርያ ፈቃድ የወሰዱት ከፍትሕ ሚኒስቴር እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ለበጎ አድራጎትና ለሲቪል ማኅበራት ፈቃድ የመስጠቱንና የመቆጣጠሩን ኃላፊነት ማኅበራት ኤጀንሲው ከተረከበ በኋላ በርካታ ለውጦች ተደርገዋል፡፡

በዚህ መሠረት የኢትዮጵያ የሥነ ምግባር መኮንኖች ማኅበር፣ ነጋዴ ሴቶች ማኅበር፣ በሌሎች አገሮች የተማሩ ምሑራን ያቋቋማቸው ማኅበራት ለምሳሌ ሩሲያና ጀርመን ተምረው አገራቸው የተመለሱ ምሑራን ያቋቋሟቸው ማኅበራት በሙሉ አደጋው ከተጋረጠባቸው መካከል ይገኙበታል፡፡

የሥነ ምግባር መኮንኖች ማኅበር የተቋቋመው ከተለያዩ መንግሥታዊ ተቋማት በተውጣጡ የሥነ ምግባር መኰንኖች ነው፡፡ ይህ ማኅበር የተቋቋመ ሙስናን ለመዋጋት የተጀመረውን ጥረት ለማገዝና ከሙሰኞች የሚሰነዘረውን ጥቃት በጋራ ለመከላከል መሆኑን የማኅበሩ ፕሬዚዳንት አቶ ጌቱ አለማየሁ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

አቶ ጌቱ ጨምረው እንደገለጹት፣ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ኤጀንሲ ለማኅበራቸው በጻፈው ደብዳቤ፣ የእርሳቸው ድርጅት ቀደም ሲል ፈቃድ የተሰጠው በስህተት መሆኑንና የሥነ ምግባር መኮንን የሚባል ሙያ እንደሌለ በማስታወቅ፣ ማኅበሩ እንዲፈርስ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡ ማኅበሩ ባለፈው ረቡዕ በጠራው ጠቅላላ ጉባዔ ለአባላቱ ይህንን ያስታወቀ ሲሆን፣ አባላቱ አቤቱታቸውን ለመንግሥት እንደሚያቀርቡ ገልጸዋል፡፡ አቶ ጌቱ ግን የማኅበሩ ህልውና ያበቃ መሆኑንን ተናግረው፣ ያለውን ሀብት ለኤጀንሲው ለማስረከብ መዘጋጅቱን ጠቁመዋል፡፡

በውጭ አገር የተማሩ ምሑራንም የአደራጃጀት ለውጥ እንዲያደርጉ ተገልጾላቸዋል፡፡ የሲቪል ማኅበራትና የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ኤጀንሲ ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ኃላፊ አቶ አሰፋ ተስፋዬ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ በማኅበራቱ ያሉ አባላቶች የተለያዩ ትምህርቶች የተማሩ ሰዎች ናቸው፡፡ ይህንን የሙያ ማኅበር ብሎ ለማስተናገድ የማይመች በመሆኑ፣ ምሁራኑ በሠለጠኑበት ሙያ ተለያይተው ሊደራጁ እንደሚችሉ ተናግረዋል፡፡ ‹‹ይህ ካልሆነ ግን ማኅበራቱ ያቀረቡት የፈቃድ እድሳት ጥያቄ አይስተናገድም፤›› ሲሉ አቶ አሰፋ አስርድተዋል፡፡ በሌላ በኩልም ነጋዴ ሴቶች ያቋቋሙት ማኅበር ከንግድ ውጪ የበጎ አድራጎት ባህሪ የሌለው ነው በሚል ምክንያቶች በኤጀንሲው ሊስተናገድ አልቻለም፡፡

አቶ አሰፋ እንደገለጹት፣ ቀደም ሲል የተሰጠው ፈቃድ ድብልቅልቅ ያለ በመሆኑ መጥራት ይኖርበታል፡፡ በአሁኑ ወቅት በኤጀንሲው ፈቃድ በማደሰ በኩል ያለውን ችግርና የተደበላለቀ አሠራር በመለየት ጥርት ያለ መንገድ መፍጠር እንደሚያስፈልግ ባለጉዳዮቹ አሳስበዋል፡፡

Source:: Ethiopian Reporter

የግል አየር መንገዶች በአዲስ አበባ ሁለተኛ ኤርፖርት እንዲገነባ ጠየቁ

$
0
0

የግል አየር መንገዶች የአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት በመጨናነቁ አማራጭ ኤርፖርት እንዲገነባላቸው ጠየቁ፡፡

dad2db1c0821d2a1813caaa03420c061_Lየኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን ከባለድርሻ አካላት ጋር ዓርብ ባካሄደው የምክክር መድረክ የግል አየር መንገዶች ተወካዮች የሚያንቀሳቅሷቸው አነስተኛ አውሮፕላኖች ከግዙፉ አውሮፕላኖች ጋር እየተጋፉ መሥራት እንደተቸገሩ ተናግረዋል፡፡

የአቢሲኒያ የበረራ አገልግሎት ምክትል ማኔጂንግ ዳይሬክተር ካፒቴን አማረ ገብረሃና እንደገለጹት፣ የአዲስ አበባ ኤርፖርት አንድ መንደርደሪያ ያለው ሲሆን የአውሮፕላን እንቅስቃሴ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል፡፡ ‹‹እንደ ቦይንግ 777 እና 787 ያሉ ግዙፍ አውሮፕላኖች የሚጠቀሙበት ኤርፖርት ነው፡፡ እኛ ደግሞ እንደ ሴስና ያሉ አነስተኛ አውሮፕላኖችን ነው የምናንቀሳቅሰው፡፡ ትላልቅ አውሮፕላኖች ሊነሱ ወይም ሊያርፉ ሲሉ ጠብቁ እንባላለን፡፡ በእርግጥም ቅድሚያ መሰጠት ያለበት ለትላልቅ አውሮፕላኖች ነው፡፡ ነገር ግን እኛ በዕቅዳችን መሠረት መሥራትና መብረር አልቻልንም፡፡ ‹‹የአብራሪዎች ትምህርት ቤት ከፍተን በማስተማር ላይ ነን፡፡ 13 ያህል አነስተኛ አውሮፕላኖች አሉን፡፡ ተማሪዎቻችንን በበቂ ሁኔታ በረራ መለማመድ አልቻሉም፤›› ብለዋል፡፡

ካፒቴን አማረ ወደ ክልል ሄደው እንዳይሠሩ ገበያው ያለው አዲስ አበባ መሆኑን ጠቅሰው፣ የአነስተኛ አውሮፕላኖች እንቅስቃሴ እየጨመረ በመምጣቱ አነስተኛ አውሮፕላኖች የሚገለገሉበት አማራጭ ኤርፖርት መሥራት አስፈላጊ መሆኑን በአንክሮ ተናግረዋል፡፡ ሌሎችም የግል አየር መንገዶች ድጋፋቸውን ገልጸዋል፡፡

ከበረራ ፈቃድ ጋር በተያያዘ ለመከላከያ ሚኒስቴር ከ24 ሰዓት በፊት አሳውቁ የሚለው መመርያ አስቸጋሪ እንደሆነባቸውም የግል አየር መንገዶች ተናግረዋል፡፡ ደንበኞች አስቸኳይ የበረራ አገልግሎት እንደሚፈልጉ፣ አንዳንዴም የአየር አምቡላንስ አገልግሎት እንደሚጠየቅ ይህም ለሥራቸው እንቅፋት እንደሆነባቸው የግል አየር መንገድ ተወካዮች ተናግረዋል፡፡ ካፒቴን አማረ በተለይ ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ በረራ ማድረግ አስቸጋሪ እንደሆነና ሠራተኞቻቸውም የታሠሩበት አጋጣሚ እንዳለ ጠቁመዋል፡፡

መንግሥት በማዘጋጀት ላይ ያለው አዲስ የአየር ትራንስፖርት ፖሊሲ የት እንደደረሰ የስብሰባው ተሳታፊዎች ጠይቀዋል፡፡

ሌላው ጠንከር ያለ ጥያቄ የተነሳው የአውሮፕላን መቀመጫ ጥያቄ ነው፡፡ የናሽናል ኤርዌይስ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ካፒቴን አበራ ለሚ የግል አየር መንገዶች ላይ የተጣለው የአውሮፕላን መቀመጫ ገደብ የግል አየር መንገዶች እንዳያድጉ ተፅዕኖ እንዳደረገ ተናግረዋል፡፡

ቀደም ሲል የነበረው መመርያ የግል አየር መንገዶች ከ20 መቀመጫ በላይ ላይ ያለው አውሮፕላን እንዳይጠቀሙ ይከለክል ነበር፡፡ በቅርቡ ይህ መመርያ ተሻሽሎ ገደቡ ወደ 50 መቀመጫ ከፍ ተደርጓል፡፡ የግል አየር መንገድ ባለቤቶች በማሻሻያው ብዙም የተደሰቱ አይመስልም፡፡

ካፒቴን አበራ እንደሚሉት በአሁኑ ወቅት አምራቾች 50 መቀመጫ ያለው አውሮፕላን አያመርቱም፡፡ ‹‹በፊት 50 መቀመጫ ያለው አውሮፕላን የሚያመርተው ኩባንያ ፎከር ነበር፡፡ እሱም ከስሮ ተዘግቷል፡፡ ከራሺያ ያረጁ አውሮፕላኖችን እንዳናመጣ 22 ዓመት በላይ ዕድሜ ያለው አውሮፕላን እንዳናስገባ የሲቪል አቪዬሽን መመርያ ይከለክለናል፡፡ አነስተኛ መቀመጫ ባለው አውሮፕላን ተሠርቶ ትርፋማ መሆን አይቻልም፡፡ አቅም ካለኝ ቦይንግ 737 አውሮፕላን አምጥቼ እንድሠራ ለምን አይፈቀድልኝም?›› ሲሉ ጠይቀዋል፡፡

ለጥያቄዎቹ ምላሽ የሰጡት የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ኮሎኔል ወሰንየለህ ሁነኛው፣ የአማራጭ ኤርፖርት ጥያቄን በተመለከተ ያለው ፍላጐት አስገዳጅ እየሆነ እንደሚመጣ ተናግረዋል፡፡ ትላልቅና አነስተኛ አውሮፕላኖችን በአንድ ኤርፖርት ማስተናገድ አስቸጋሪ መሆኑን ኮሎኔል ወሰንየለህ አምነው የተቀበሉት ጉዳይ ነበር፡፡

‹‹ጥያቄው ተገቢ ነው፡፡ ከተወሰነ ጊዜ በኋላ በአዲስ አበባ ኤርፖርት ትላልቅና ትናንሽ አውሮፕላኖችን ማስተናገድ የማይቻልበት ሁኔታ ላይ ይደረሳል፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የበረራ ሥልጠናውን ወደ ድሬዳዋ ለመውሰድ ተገዷል፤›› ያሉት ኮሎኔል ወሰንየለህ፣ በክልል ከተሞች ብዙ ሚሊዮን ብር ፈሶባቸው የተገነቡ አንዳንድ ኤርፖርቶች ብዙም አገልግሎት እንደማይሰጡ ጠቅሰዋል፡፡ የግል አየር መንገዶች እነዚህን ኤርፖርቶች ይጠቀሙ ወይስ በአዲስ አበባ ሁለተኛ ኤርፖርት ይገንባ የሚለው የመንግሥትን ውሳኔ የሚሻ ጉዳይ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽንና ጉዳዩ በዋነኛነት የሚመለከተው የኢትዮጵያ ኤርፖርቶች ድርጅት ከትራንስፖርት ሚኒስቴር ጋር መክረው በበላይ አካል የሚወሰን ጉዳይ እንደሆነ አስረድተዋል፡፡

ከመከላከያ ጋር ተያይዞ የተነሳውን ጥያቄ አስመልክቶ ዋና ዳይሬክተሩ በሰጡት ምላሽ መከላከያ፣ የአገር ደኅንነት የማስጠበቅ ኃላፊነት ያለበት ተቋም መሆኑን፣ የደኅንነት ሥጋቶች መኖራቸውን፣ ባለሥልጣኑ የበረራ ፈቃዶችን በተመለከተ ከመከላከያና ከመረጃና ደኅንነት መሥሪያ ቤቶች ጋር ተባብሮ እንደሚሠራ አስረድተዋል፡፡

የአገር ደኅንነት የማስጠበቅና አየር መንገዶችን ፍላጐት በሚያስታርቅ መልኩ ወጥ የሆነ አሠራር ለመቅረፅ ከመከላከያ ሚኒስቴር ጋር እየተሠራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ ‹‹በጋራ ያዘጋጀነው ሰነድ አለ፡፡ ያልተመለሱ ጥያቄዎች ስለነበሩ ጊዜ ወስዶብናል፡፡ በቅርቡ ተጠናቆ ግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት በቅርቡ እናዘጋጃለን፤›› ብለዋል፡፡

የአውሮፕላን ዕድሜ ገደብን በተመለከተ ማብራሪያ የሰጡት የአገር በረራ ደኅንነት ፕሮግራም (State Safety Program) ኃላፊ ሻምበል ግርማ ገብሬ፣ አፍሪካ የአሮጌ አውሮፕላኖች መጣያ መሆኗን በዚህም የአፍሪካ የበረራ ደኅንነት አስከፊ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡

‹‹ባለን መረጃ መሠረት ብዙ ጊዜ የሚከሰቱ አደጋዎች በአሮጌ አውሮፕላኖች የሚከሰቱ ናቸው፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ሩሲያ ሠራሽ አሮጌ አውሮፕላኖች አምስት ጊዜ ያህል ተከስክሰዋል፡፡ በናይጄሪያ በተደጋጋሚ የተከሰከሱት አሮጌ ቦይንግ 727 አውሮፕላኖች ናቸው፤›› ብለዋል፡፡

የአውሮፕላን ምዝገባና ፈቃድ ክፍል ተወካይ አቶ ዘውዱ ተክላይ በበኩላቸው 22 ዓመት የሚለው ገደብ እንዲያው ዝም ብሎ የተጣለ ሳይሆን ከዓለም አቀፉ የሲቪል አቪዬሽን ድርጅት ምክረ ሐሳብ የተወሰደ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡

የግል አየር መንገዶች የግራውንድ ሃንድሊንግና ፋስሊቴሽን ሥራዎች ለግል ኩባንያዎች እንዲፈቀድ የጠየቁ ሲሆን፣ እነዚህና ሌሎች ጥያቄዎች በአዲሱ የአየር ትራንስፖርት ፖሊሲ ምላሽ እንደሚያገኙ ኮሎኔል ወሰንየለህ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል፡፡

ዓለም አቀፉ የሲቪል አቪዬሽን ድርጅት የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ድርጅትን በመጪው ሚያዚያ ወር እንደሚመረምረው ከመድረኩ ተነግሯል፡፡ ለዚህም ባለሥልጣኑ ሰፊ ዝግጅት በማድረግ ላይ መሆኑን አየር መንገዶች ከባለሥልጣኑ ጋር ተባብረው እንዲሠሩ ጥሪ ቀርቧል፡፡

ባለሥልጣኑ በየጊዜው ዘመናዊ የበረራ መቆጣጠሪያ መሣሪያዎች በከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ በመግዛት በመትከል ላይ ሲሆን፣ በርካታ የአቪዬሽን ባለሙያዎችን በመቅጠርና በማሠልጠን ላይ ይገኛል፡፡ በ2007 በጀት ዓመትም 102 ሚሊዮን ብር ካፒታል በጀት በመመደብ የተለያዩ መሣሪያዎች ግዥና ተከላ ሥራ እንደሚያካሂድ ለማወቅ ተችሏል፡፡

በአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ለተተከለው ዘመናዊ ራዳር መጠባበቂያ የሚሆን መሣሪያ 30 ሚሊዮን ብር፣ ለኮሙዩኒኬሽን መሣሪያዎች ግዥ 25 ሚሊዮን ብር በጀት መበጀቱን ለማወቅ ተችሏል፡፡

በተያያዘ ዜና ሪፖርት ለማያቀርቡ የግል አየር መንገዶች የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን ማስጠንቀቂያ ሰጠ፡፡ የአየር ትራንስፖርትና ዕቅድ ዳይሬክተር አቶ እንደሻው ይገዙ ከ2006 ዓ.ም. ጀምሮ የኢንቨስትመንት ፈቃድ የወሰዱ የግል አየር መንገዶች ስለ ሥራቸው እንቅስቃሴ በየሦስት ወራት ለባለሥልጣኑ ሪፖርት ማድረግ የሚጠበቅባቸው ቢሆንም፣ ግዴታቸውን እየተወጡ እንዳልሆነ ተናግረዋል፡፡ ‹‹ሪፖርት አለማቅረብ ፈቃድ የመሰረዝ ዕርምጃ ሊያስወስድ ይችላል፡፡ ስለዚህ ይህ ማሳሰቢያ ተወስዶ ግዴታችሁን እንድትወጡ እናሳስባለን፤›› ብለዋል፡፡

ኢትዮጵያ ውስጥ 15 የተመዘገቡ የግል አየር መንገዶች ያሉ ሲሆን፣ ወደ ሥራ የገቡት 10 ያህሉ ብቻ ናቸው፡፡ አየር መንገዶቹ የሚሰጡት የቻርተር በረራ አገልግሎት ሲሆን፣ የሚድሮኩ ትራንስኔሽን ኤርዌይስ ከጥቅምት 22 ጀምሮ መደበኛ የአገር ውስጥ በረራ በመስጠት ብቸኛ የግል አየር መንገድ ለመሆን ችሏል፡፡

Source:: Ethiopian Reporter

መልዕክት ከእስር ቤት

$
0
0

ነገረ ኢትዮጵያ

prison_nationትናንት ሰላማዊ ሰልፉ ላይ ታፍሰው ከታሰሩት አመራሮች መካከል ጥረት አድርገን ነበር፡፡ አዲስ አበባ ፖሊስ ጣቢያ (ሶስተኛ) የታሰሩትን አመራሮችን መጠየቅ አይቻልም በመባሉ ማነጋገር ባንችልም ጨርቆስ ፖፖላሬ የሚገኙትን ሁለት አመራሮች መልዕክት እንደሚከተለው አቅርበነዋል፡፡

‹‹ከጉዟችን አንዲት ሴንቲሜትር ወደኋላ አንመለስም››

አቶ ግርማ በቀለ የዘጠኙ ፓርቲዎች ፀኃፊ

እኛ የታሰርነው ለቆምንለት አላማ ነው፡፡ ዴሞክራሲያዊ መብታችን ለማስከበር የሚቻለንን ሁሉ እናደርጋለን፡፡ ይግደሉን እንጅ እንወጣለን ብለናል፡፡ ይህን ያልነው ዴሞክራሲያዊ መብታችን ለማስጠበቅ መስዋዕትነት መከፍል የግድ ስላሚለን ነው፡፡ ያለ መስዋዕትነት ድል ልናገኝ አንችልም፡፡ ስንወጣ መስዋዕትነት እንደምንከፍል እናውቃለን፡፡ ግን ደግሞ ለአላማችን ታማኝ መሆን፣ ቃላችንም መጠበቅ ነበረብንና አድርገነዋል፡፡

ከታሰርን በኋላም ቢሆን አንዳንድ መረጃዎች ይደርሱናል፡፡ ህዝቡ በሞራል ድጋፍ ከእኛ ጋር እንደሆነ ሰምተናል፡፡ በእውነቱ ይህ የሚያበረታታ ነው፡፡ በዚህ አጋጣሚ ከጎናችን ለቆማችሁ ሁሉ ምስጋና ማድረስ እፈልጋለሁ፡፡ እኛ አላማችን እና ግዴታችን እስከሆነ ድረስ መስዋዕትነቱን ለመክፈል ዝግጁ ነን፡፡ ከጉዟችን አንዲት ሴንቲሞትር ወደኋላ አንልም፡፡ እናንተም አብራችሁን እንደምትሆኑ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ ትብብሩንም አጠናክረን እንደምንቀጥል ተስፋ አለኝ፡፡ በርቱ!

‹‹እኛ እንጸናለን፡፡ እናንተም ወደኋላ እንዳትሉ!››

ጌታነህ ባልቻ (የሰማያዊ ፓርቲ ጥናትና ስትራቴጅ ክፍል ኃላፊ)

ትግሉ ቆራጥነት ያስፈልገዋል፡፡ ለዚህ እኛ የተወሰነም ቢሆን እያደረግን ነው፡፡ እኛ በመታሰራችን ህዝቡ መደናፈጥ የለበትም፡፡ እኛ የተወሰነች ነገር ስናደርግ ህዝቡም ማገዝ ይኖርበታል፡፡ በውጭም አገር ውስጥም የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ከጅምሩ ጀምሮ እገዛ አድርገዋል፡፡ ግን ይህ አሁን ካለው የአገሪቱ ችግር አንጻር በቂ አይደለም፡፡ እኛ የተወሰነ ነገር ስናደርግ ህዝቡም ደጋፍ ማድረግ አለበት፡፡ እኛ ስንታሰር ህዝቡ ወደኋላ ማለት የለበትም፡፡ እኛ ስንታሰር ትግሉ ካቆመ ለስርዓቱ ትልቅ ድል ነው፡፡ ስለሆነም ትግሉ መቀጠል አለበት፡፡ እስካሁን ድጋፋችሁን ላደረጋችሁልን ሁሉ እናመሰግናለን፡፡ የእኛ መታሰር የትግሉ አንድ አካል ነው፡፡ እኛ እንጸናለን፡፡ እናንተም ወደኋላ እንዳትሉ!

ብርሀነ መስቀል ረዳን በጨረፍታ

$
0
0

ጸሐፊ፡ አፈንዲ ሙተቂ
—-
በዩኒቨርሲቲ ቆይታዬ (ከ1989-እስከ 1992 በነበረው ጊዜ) “ሐቄ” የምትባል ልጅ አውቃለሁ፡፡ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽ/ቤት የሴቶች ጉዳይ ሃላፊ የነበረችው (በኋላ በኮትዲቯር የኢትዮጵያ አምባሳደር የሆነችው) ወ/ሮ ታደለች ሀይለሚካኤል የዚያች ልጅ እናት እንደነበረች ይወሳ ነበር፡፡ በዚህም የተነሳ የባለስልጣን ልጅ መሆኗን በመፍራት ብቻ ብዙዎች አይጠጓትም ነበር፡፡ ከልጅቷ ጋር የሚቀራረበው ተወልደ መዝገቡ የሚባል የአዲግራት ልጅ ብቻ እንደነበረ አስታውሳለሁ፡፡

BerhaneMeskael Reda የዩኒቨርሲቲው ትምህርት ከተጠናቀቀ ከጥቂት ወራት በኋላ መጽሔቶችን ሳገላብጥ ያቺ ልጅ ለምልክት ከሞት የተረፈች የፈጣሪ ተአምር እንደሆነች ተረዳሁ፡፡ አባቷ ነፍሲያውን ሊጠነቅ በተቃረበበት ወቅት ታሪኩን ትመሰክር ዘንድ የዘራት ብቸኛ ፍሬው ነበረች፡፡ ብዙዎች በእናቷ ሆድ የነበረችበትን ጊዜ በብዕራቸው ነካክተውታል፡፡ ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማሪያም በበኩላቸው ያቺ ነፍስ በእናቷ ሆድ ውስጥ በመገኘቷ እናቷን ከሞት ያተረፈች መሆኗን መስክረውላታል፡፡ ለዚህም ይመስላል እናቷ “ሐቄ” የሚለውን ስም የሰጠቻት፡፡

ህይወት ተፈራ Tower in the sky የተባለውን መጽሐፍ ስትጽፍ ለዚያች ልጅ መጠነኛ ሽፋን ሰጥታለች፡፡ ከእናቷ ጋር የተነሳችውንም ፎቶግራፍ በመጽሐፉ ውስጥ አካተዋለች፡፡
*****
በፎቶግራፉ ላይ የምትመለከቱት የዚያች ልጅ አባት የነበረውን ሰው ነው፡፡ ይህ ሰው ከታሪካዊው የኢትዮጵያ ተማሪዎች ንቅናቄ መሪዎች መካከል አንዱ የነበረውና የመጀመሪያው የኢህአፓ ዋና ጸሓፊ ሆኖ የተመረጠው ብርሀነ መስቀል ረዳ ነው፡፡ ለብዙሃን ህይወት መለወጥ በብርቱ የታገለ፣ ሁለቱን ጠንካራ ስርዓቶች ፊት ለፊት የተጋፈጠ፣ ላመነበት ዓላማ ትምህርቱን ሰውቶ መታገልን የመረጠ፣ ከሀገር ወጥቶ በሰው ሀገርና በበረሃ የተንከራተተ፣ በመጨረሻ ላይ ግን ከገዛ ጓዶቹ ጋር ተጣልቶ የራሱን መንገድ የመረጠ፣ በዚህም ከፍተኛ የውዝግብ ርዕስ ለመሆን የበቃ የዚያ ዘመን ፋኖ!…

ብርሀነ መስቀል ማን ነው?… በኢትዮጵያ ህዝቦች የፖለቲካ ትግል ውስጥ ምን ሚና ነበረው?… የርሱ ህይወትና የትግል መንገድ እንዴት ይገመገማል?… እነኝህ በኔ አቅም የሚመለሱ ጥያቄዎች አይደሉም፡፡ ታሪኩ እስከ አሁን ድረስ እያወዛገበ ስለሆነ ሐቁን ከግርድፉ ማጣራቱ ከባድ ጥረት ይጠይቃል፡፡ ብርሀነ መስቀል በወዳጆቹም ሆነ በጠላቶቹ የሚከበርና የሚፈራ መሆኑን ግን ማንም አያስተባብልም፡፡ ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለ ማሪያም በእስር ቤት አናዝዘውት ከገደሉት በኋላ “የመርሐቤቴ ገበሬዎች ገደሉት” እያሉ ለመዋሸት ቢሞክሩም በኢትዮጵያ ተማሪዎች ንቅናቄ ውስጥ የነበረውን ሚና በአዎንታዊ መልኩ ነው የገለጹት፡፡ በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው የቅርብ ጓደኛው የነበሩት አንጋፋው ገጣሚና ባለቅኔ ኃይሉ ገብረ-ዮሐንስ (ገሞራው) “ችኩል እና ቁጡ ከመሆኑ በስተቀር ለሀገር መሪነት የሚበቃ ስብዕና ነበረው” በማለት መስክረውለታል፡፡

ከሁሉም በላይ የብርሀነ መስቀልን ቆራጥነትና ልዩ ተሰጥኦ ሰፋ ባለ ሁኔታ የገለጹት የኢህአፓው ክፍሉ ታደሰ ነበሩ፡፡ አቶ ክፍሉ “ያ ትውልድ” በተሰኘውና በከፍተኛ ደረጃ ተነባቢ ለመሆን በበቃው መጽሐፋቸው “ብርሀነ መስቀል በኢህአፓ ውስጥ የራሱን አንጃ ፈጥሯል” የሚል ክስ እያቀረቡበት እንኳ ለትግሉ ያበረከተውን አስተዋጽኦ በተዋቡ ቃላት ገልጸዋል፡፡ ለምሳሌ ያህል የሚከተለውን መጥቀስ ይቻላል፡፡
“በተማሪው እንቅስቃሴ ውስጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከተውና አንደበተ ርቱእ የሆነው ብርሃነ መስቀል፣ በእንቅስቃሴው ውስጥ ሲታሰርና ሲፈታ የኖረ ነው” (ክፍሉ ታደሰ፣ ያ ትውልድ፣ ገጽ- 144)
*****
ብርሀነ መስቀል ለደርግ መርማሪዎች የሰጠው ቃል ሰሞኑን በኢንተርኔት ተበትኖ የብዙዎች መነጋገሪያ ሆኗል፡፡ እኔም ይህ 98 ገጾች ያሉት የምርመራ ቃል ከአንድ የፌስቡክ ጓደኛዬ ደርሶኝ እያነበብኩት ነው (ሙሉውን ዶክመንት www.zehabesha.com ከተሰኘ ዌብሳይት ማግኘት ትችላላችሁ)፡፡ እስከ አሁን ድረስ 1/3ኛ ያህሉን አገባድጄዋለሁ፡፡ ይሁንና ፊት ከማውቀው የብርሀነ መስቀል ታሪክ የተለየ ነገር አላገኘሁበትም፡፡ በሚቀጥሉት ቀናት አትኩሮት የሚስቡ መረጃዎችን ካገኘሁበት ልመለስ እችላለሁ፡፡ እስከዚያው ግን ስለብርሀነ መስቀል በትንሹ ላውጋችሁ፡፡

ብርሃነ መስቀል ረዳ ወልደ-ሩፋኤል በ1930ዎቹ አጋማሽ በትግራይ ገጠር ነው የተወለደው፡፡ ያደገው ግን በደሴ ከተማ የከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኛ በነበሩት አጎቱ ቤት ነው፡፡ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ደሴ በሚገኘው የወይዘሮ ስሒን ት/ቤት ካጠናቀቀ በኋላ በ1955 ወደ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ገብቷል፡፡ በዩኒቨርሲቲ ቆይታው ትምህርቱን ከመከታተል ይልቅ ተማሪዎችን ለተቃውሞ በማንቀሳቀሱ ላይ ነበር ያተኮረው፡፡ በዚህም መሰረት ወደ ዩኒቨርሲቲው እንደገባ ከርሱ ቀደም ብለው “አዞዎቹ” በሚል ቡድን ዙሪያ የተሰባሰቡትን የስር-ነቀል ለውጥ ደጋፊ ተማሪዎችን ለመቀላቀል በቅቷል፡፡ ከዓመት በኋላ በ1956 በዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ተማሪዎች ህብረት ውስጥ የመረጃ ኦፊሰር ሆኖ ተመርጧል፡፡ በአመቱ ደግሞ የብሔራዊ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ህብረት ዋና ጸሓፊ ሆኖ ነበር፡፡

ብርሃነ መስቀል በ1957 የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች “መሬት ላራሹ” የሚል መፈክር አንግበው ድምጻቸውን ለፓርላማ ያሰሙበትን ታሪካዊ ሰልፍ ካደራጁት መካከልም ነበር፡፡ በዚያ ሰልፍ ሳቢያ ከትምህርታቸው ከተባረሩት ዘጠኝ ተማሪዎች መካከልም አንዱ ነው (በወቅቱ ከርሱ ጋር የተባረሩት ገብሩ ገብረወልድ፣ ሀይሉ ገብረዮሐንስ፣ ዮሐንስ ስብሐቱ፣ ታዬ ጉርሙ፣ ዘርዑ ክህሸን፣ ስዩም ወልደ ዮሐንስ፣ ሀብቴ ወልደ ጊዮርጊስና ሚካኤል አበበ ናቸው)፡፡ እነዚያ ተማሪዎች ከአንድ ዓመት በኋላ ወደ ዩኒቨርሲቲው ቢመለሱም በተረጋጋ ሁኔታ ትምህርታቸውን መከታተል አልቻሉም፡፡ በየጊዜው በሚካሄዱት ሰልፎችና የተቃውሞ ስብሰባዎች ግንባር ቀደም ተጠያቂ እየሆኑ ይታሰሩ ነበር፡፡ በስተመጨረሻ ግን የ“አዞዎቹ” ቡድን አባላት ከነአካቴው ከዩኒቨርሲቲው ተባረሩ፡፡ በመሆኑም በተደራጀ ሁኔታ ለመታገል ወሰኑ፡፡

በዚህም መሰረት ብርሃነ መስቀልና አምስት ጓደኞቹ ከባህር ዳር ወደ አዲስ አበባ የሚበር አንድ አውሮፕላን በመጥለፍ ወደ ካርቱም ኮበለሉ፡፡ ከጥቂት ወራት በኋላም ወደ አልጄሪያ ተሻገሩ፡፡ በአልጀርስ ቆይታቸው እጅግ ቀስቃሸ የሆኑ ጽሑፎችን እያዘጋጁ ወደ ሀገር ቤት ይልኩ ጀመር (በዚያ ዘመን “ጥላሁን ታከለ” በሚል የብዕር ስም በመጠቀም አስደናቂ ጽሑፎችን ይጽፍ የነበረው ብርሃነ መስቀል ረዳ እንደሆነ ነው የሚታመነው)፡፡ በአልጄሪያ የነበሩት ስደተኛ አብዮተኞች በውጪው ዓለም ትምህርታቸውን ከሚከታተሉ ኢትዮጵያዊያን ጋር በሚያደርጓቸው ግንኙነቶች በተደራጀ መንገድ የሚታገሉበትን መንገድ ቀየሱ፡፡ እነዚያ ውይይቶች እያደጉ ሄደው በ1964 ኢህአድ (የኢትዮጵያ ህዝብ አርነት ድርጅት) የተሰኘ ህቡዕ ፓርቲ ተወለደ፡፡ ብርሀነ መስቀል ረዳም የድርጅቱ ዋና ጸሐፊ ሆኖ ተመረጠ (የድርጅቱ ስም በ1967 “የኢትዮጵያ ህዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ” በሚል ተለውጧል፤ ይህም በአህጽሮት “ኢህአፓ” የሚባለው ነው)፡፡

ብርሀነ መስቀል የኢህአድ ዋና ጸሓፊ በነበረበት የመጀመሪያ ዓመት በአብዛኛው ፓርቲውን የማስተዋወቅና ድጋፍ የመፈለግ ስራዎችን ነበር የሰራው፡፡ በዚህም ከአውሮፓ እስከ መካከለኛው ምስራቅ ድረስ ተጉዟል፡፡ ከባለቤቱ ታደለች ሀይለሚካኤል ጋር የተዋወቀው በዚያን ጊዜ ነው፡፡ በ1966 ብርሃነ መስቀልና ጥቂት ሰዎች የድርጅቱን የትጥቅ ትግል እንዲጀምሩ ወደ ኤርትራ ተላኩ፡፡ ወታደራዊ ስልጠና ለመውሰድ ለአንድ ዓመት በኤርትራ ከቆዩ በኋላ በ1967 መጀመሪያ ላይ ትግራይ ውስጥ ወደሚገኘው አሲምባ ተራራ ተሻገሩ፡፡ ሆኖም የትጥቅ ትግሉን ሳይጀምሩ በአሲምባ ቤዛቸው ለስድስት ወራት ቆዩ፡፡ በዚህ መሀል ስምንት ያህል የቡድኑ አባላት ከብርሀነ መስቀል ጋር የነበራቸውን ቀየሜታ በማሳበብ ድርጅቱን ጥለው ለደርግ መንግሥት እጃቸውን ሰጡ፡፡ ብርሀነ መስቀል በፋኖዎቹ አድራጎት በመቆጣቱ በሌሉበት የሞት ፍርድ ፈረደባቸው፡፡ ሆኖም ይህ ውሳኔው ከሌሎች የኢህአፓ አባላት ተቃውሞ ገጠመው፡፡ የኢህአፓ ማዕከላዊ ኮሚቴ ጉዳዩን ካጣራ በኋላ በሰዎቹ ላይ የተላለፈው የሞት ፍርድ እንዲነሳ ወሰነ፡፡ ብርሀነ መስቀልም ከሰራዊቱ ተነጥሎ ወደ አዲስ አበባ እንዲሄድ ተወሰነ፡፡ ይህም በብርሀነ መስቀልና በሌሎቹ የኢህአፓ መሪዎች መካከል ንትርክ ፈጠረ፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ በነሐሴ ወር 1967 አህአፓ ራሱን በአዲስ መልክና በአዲስ ስም ሲያደራጅ “ዋና ጸሐፊ” የሚባል የስልጣን እርከን ተሰረዘ፡፡ ድርጅቱ ሊቀመንበርም ሆነ ዋና ጸሐፊ የለውም ተብሎ ታወጀ፡፡ ብርሀነ መስቀል ይህንን እርምጃ እርሱን ከቦታው ለማንሳት የተሸረበ ሴራ አድርጎ ስለወሰደው ከፍተኛ ቅሬታ አደረበት፡፡ ከማዕከላዊ ኮሚቴው ጋር የሚያደርገውንም ግንኙነት ማቀዝቀዝ ጀመረ፡፡ የደርግ መንግሥት በሚያዚያ ወር 1968 በህቡዕ ለተደራጁ ድርጅቶች ሁሉ የግንባር ጥሪ ሲያደርግ ብዙሃኑ የኢህአፓ አመራር ጥሪውን በመሰረቱ እንደሚቀበል ከገለጸ በኋላ መሟላት ያለባቸውን ቅድመ ሁኔታዎች አስቀመጠ፡፡ እነዚያ ሁኔታዎች ካልተሟሉ በስተቀር ከደርግ መንግሥት ጋር እንደማይሰራ ገለጸ፡፡ ብርሀነ መስቀል ግን “ቅድመ- ሁኔታ ማስቀመጡ ልክ አይደለም” በማለት ተከራከረ፡፡ በነሐሴ ወር 1968 የኢህአፓ ማዕከላዊ ኮሚቴ “ራሳችንን ለመከላከል የከተማ ትጥቅ ትግል ማድረግ አለብን” በማለት ሲወስን ብርሀነ መስቀል “ውሳኔው አደገኛ ነው፤ ኢህአፓን ያስመታል፤ ደግሞም ደርግ ማርክሳዊ ነኝ ብሎ ያወጀ መንግሥት ስለሆነ ማርክሳዊ መንግሥትን በትጥቅ አመጽ መቃወም የአብዮታዊያን ጸባይ አይደለም” በማለት በብርቱ ተቃወመው፡፡ ይህም ታቃውሞ ከኢህአፓ አመራር ጋር እስከ ወዲያኛው አቆራረጠው፡፡

የኢህአፓ አመራር ብርሀነ መስቀል ያሳያቸውን የአቋም ልዩነቶች ከገመገመ በኋላ ከማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነቱ ሰረዘው፡፡ ከጥቂት ጊዜ በኋላም “ብርሀነ መስቀል በፓርቲው ውስጥ የራሱን አንጃ ለመመስረት ጥረት እያደረገ ነው” የሚል ክስ አቀረበበት፡፡ በድርጅቱ ጋዜጦች ላይ ግለ-ሂስ እንዲያደርግም አዘዘው፡፡ ብርሀነ መስቀልም ሂሱን ካወረደ በኋላ በድርጅቱ ታጣቂዎች እንዲጠበቅ ተደረገ፡፡ በሚያዚያ 1969 ግን ለማንም ግልጽ ባልሆነ መንገድ ከአዲስ አበባ ከተማ ተሰውሮ ወደ መርሐቤቴ አውራጃ ገባ፡፡ እዚያም ከተወሰኑ ሰዎች ጋር የትጥቅ ትግል ለማድረግ ሞከረ፡፡ ይሁን እንጂ በእርምጃው ከጥቂት ወራት በላይ አልዘለቀም፡፡ የደርግ አዳኝ ሀይሎች በ1970 መጀመሪያ ላይ ይዘውት ወደ አዲስ አበባ አመጡት፡፡ ለአንድ ዓመት ከሰድስት ወራት ያህል በታላቁ ቤተ መንግሥት ከታሰረ በኋላ በሚስጢር ተገደለ፡፡
*****
የብርሀነ መስቀል አንጃ የመፍጠር ሙከራ በራሱም አንደበት የተረጋገጠ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ብርሀነ መስቀል “እኔ ያካሄድኩት የእርማት ንቅናቄ እንጂ ፓርቲውን ለማጥፋት ያለመ አንጃ አልፈጠርኩም” ባይ ነው፡፡ በተጨማሪም ባለቤቱ ወይዘሮ ታደለች ሀይለ ሚካኤል በአንድ ወቅት በሰጡት ቃለ ምልልስ ብርሀነ መስቀል የእርማት ንቅናቄ ለማካሄድ መሞከሩን ተናግረዋል፡፡ በዚያ ዘመን በርሱ ስም የተሰራጩትን ልዩ ልዩ ዶክመንቶች በሙሉ የርሱ ናቸው ለማለት ይከብዳል፡፡ አንደኛው ጽሑፍ ግን በርሱ እጅ ጽሑፍ የተጻፈ መሆኑ ስለሚታወቅ የርሱን እምነት ይገልጻል ተብሎ ይታመናል፡፡ ብርሀነ መስቀል በዚያ ጽሑፉ የኢህፓን አመራር ቢኮንንም ደርግንም በሚገባ ይቃወማል፡፡ እንዲሁም በርሱ ስም ድርጅቱን የበጠበጡ በርካታ ቅጥረኞች እንደነበሩም ያወሳል፡፡ ሆኖም የኢህአፓ አመራር እርሱ ያለውን አምኖ የተቀበለው አይመስልም፡፡ ኢህአፓዎች “ለድርጅቱ ብተና ፈር የቀደደ ከሀዲ ነው” ነው የሚሉት፡፡

ማንም የማይክደው አንድ ሐቅ ግን አለ፡፡ የኢትዮጵያ ተማሪዎች ንቅናቄ ሲነሳ ብርሀነ መስቀልን መርሳት በጭራሽ አይሞከርም፡፡ በርካታ የለውጥ ፈላጊው ትውልድ አባላት የርሱን አርአያ በመከተል ወደ ትግሉ ጎራ መቀላቀላቸውንም ማስተባበል አይቻልም፡፡ ስለዚህ ምሁራን በቅጡ ያልተመረመውን የዚህን ፋኖ ታሪክ ጎልጎለው በትግሉ ውስጥ የነበረውን አዎንታዊም ሆነ አሉታዊ ሚና ሳይሸፋፍኑ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
*****
አፈንዲ ሙተቂ
ህዳር 28/2006


የቅዳሜውን የ24 ሰዓት ሰላማዊ ተቃውሞ ያዘጋጁት የትብብሩ አመራሮች ‹‹ህገ መንግስቱን በኃይል በመናድ›› ወንጀል ተከሰሱ

$
0
0

(ነገረ ኢትዮጵያ) በቅዳሜው የ24 ሰዓት ሰላማዊ ተቃውሞ ታፍሰው አዲስ አበባ ፖሊስ ጣቢያ (ሶስተኛ) ታስረው የሚገኙት የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር አመራሮች፣ አባላትና የሰልፉ ተሳታፊዎች ‹‹ህገ መንግስቱን በኃይል በመናድ›› ወንጀል ተከሰው 14 ቀን ተቀጠረባቸው፡፡ ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት፣ አቶ አርጫፎ ኤርዳሎ፣ አለሳ መንገሻና ሌሎቹም የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር አመራሮች፣ አባላትና በሰልፉ ላይ የታፈሱ ዜጎች አራዳ ምድብ ችሎት ቀርበው ለታህሳስ 13/2007 ዓ.ም ተቀጥሮባቸዋል፡፡
1507105_623118397813822_166123240512263774_n
ችሎቱ በዝግ የታየ ቢሆንም ሶስተኛ ከሚገኙት ሴት ታሳሪዎች ጠይቀን ማረጋገጥ እንደቻልነው ‹‹ሁከት በመፍጠር ህገ መንግስቱንና ህጋዊ ስርዓቱን በኃይል ለመናድ እና መንግስት ያልፈቀደው ሰልፍ በመውጣት›› የሚል ክስ ቀርቦባቸዋል፡፡ ታሳሪዎቹ በበኩላቸው ‹‹እኛ ህጋዊና ሰላማዊ ታጋዮች ነን፡፡ በህጉ መሰረት ሰልፉን እንደምናደርግ አሳውቀናል፡፡ በመሆኑም የዋስ መብታችን ተከብሮ ልንለቀቅ ይገባል›› ሲሉ ተከራክረዋል፡፡ አቃቤ ህግ ‹‹ምርመራዬን አልጨረስኩም፡፡ የምሰበስበው ተጨማሪ መረጃ አለ፡፡ መረጃዎችን ይደብቁብኛል፡፡ ሌሎች ተባባሪዎችም አሉ፡፡›› ሲል የጊዜ ቀጠሮ እንዲፈቀድለት ጠይቋል፡፡ በሌላ በኩል ዳኛው ‹‹ህገ መንግስቱና ሌሎቹም ህጎች ለሰላማዊ ሰልፍ ማሳወቅ እንጅ ማስፈቀድ አይጠበቅም የሚሉ ከሆነ ህገ መንግስቱንና ሌሎቹንም ህጎች ማየት አለብኝ፡፡›› ብለው 14 ቀጥረውባቸዋል፡፡ አቃቤ ህግ ‹‹የምሰበስበው ተጨማሪ መረጃ አለ፡፡›› ባለው መሰረት የአብዛኛዎቹን ታሳሪዎች ቤት ሊፈትሽ እንደሚችልም ከፖሊስ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

ከታሳሪዎቹ መካከል 9ኝ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና ጋዜጠኛ በላይ ማናዬ ለየብቻቸው ቅዝቃዜ የበዛበትና ጨለማ ቤት ውስጥ እንደታሰሩ የታወቀ ሲሆን በምርመራ ወቅት ከፍተኛ ድብደባ እየተፈጸመባቸው እንደሆነም አቤቱታ አቅርበዋል፡፡ ሆኖም ዳኛው የቀረበውን አቤቱታ ትኩረት ሳይሰጡ እንዳለፉት ታሳሪዎቹ ገልጸውልናል፡፡ ታሳሪዎቹ አራዳ ምድብ ችሎት በቀረቡበት ወቅት ችሎቱ በበርካታ የፌደራል ፖሊስ ታጥሮ ታይቷል፡፡ የፍርድ ሂደቱን ለመከታተል በርካታ ህዝብ ተገኝቶ የነበር ቢሆንም እንዳይገባ ተከልክሎ ችሎቱ በዝግ ታይቷል፡፡

Hiber Radio: የፈረንሳይ ባንክ የሕወሃትን አገዛዝ የ1 ቢሊዮን ዶላር የሶቨርኒ ቦንድን አላሻሽጥም አለ * ከ70 በላይ ኢትዮጵያውያን የተሳፈሩባት ጀልባ የመን ባህር ዳርቻ ሰጠመች

$
0
0

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ


የህብር ሬዲዮ ህዳር 28 ቀን 2007 ፕሮግራም !

<... በሁሉም ሕጋዊ መንገድ ሄደናል የተጠየቀው ተራ ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ መብት ነው ። ስርዓቱ በዚህ ትልቅ ፍርሃት ገብቶታል የጭካኔ እርምጃውን ስናየይ ይሄ እንቅስቃሴ እንዲቀጥል አለመፈለግ ነው። ይሄ ከተጠናከረ በእርግጠኝነት ይሄ ሕዝብ ስርዓቱን ለመቀየር ይችላል... ኢ/ር ይልቃልን ጨምሮ ብዙዎቹ አመራሮች ጉዳት ደርሶባቸዋል።አቤልን ራሱን እስኪስት ነው በብረት ዱላ የመቱት አሁን የዲሞክራሲ ጥያቄ ሳይሆን መጀመሪያ ነጻነት ጥያቄ ነው። ሕዝቡ ከጎናችን ይሁን ትግላችንን አጠናክረን እንቀጥላለን...>

ወጣት ዮናታን ተስፋዬ የሰማያዊ ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ሀላፊ በመስቀል አደባባይ የተጠራውን ተቃውሞ ለማክሸፍ በአገዛዙ በኩል የተወሰደውን የሀይል ጥቃት እና ቀጣዩን ትግል የታሰሩ ያሉ አመራሮችን እና ሌሎቹ ተቃዋሚዎችን እና ተያያዥ ወቅታዊ ሁኔታዎችን አስመልክቶ ከህብር ሬዲዮ ጋር ካደረገው ቃለ ምልልስ የተወሰደ (ሙሉውን ያዳምጡ)

<<..መተንፈስ አልቻልኩም...>> የኒዮርክ ነዋሪ የሆነው በፖሊስ የሀይል ድርጊት ሕይወቱ ያለፈው ኤሪክ ጉዳይና በአሜሪካ የተጋረጠው ቀለምን መሰረት ያደረገ የሕግ አስከባሪዎች እርምጃ የት ላይ ይቆማል? (ልዩ ዝግጅት)

የሰማያዊ ፓርቲን ጨምሮ የትብብሩ አመራሮች የወሰዱት እርምጃና ለሕጋዊው መብታቸው የተወሰደባቸው ሕገ ወጥ እርምጃ ስርዓቱን ወዴት ይወስደዋል? እኛስ ምን ማድረግ አለብን? ተቃዋሚዎች ለምን አንድ ላይ አይሆኑም ? የቴዲ አፍሮ ከአገር እንዳይወጣ መታገድ የት ድረስ ይዘልቃል ? ቴዲን ለቃሊቲ እያጩት ወይስ ገፍትረው ሊያስወጡት?(ውይይት ከሰብዓዊ መብት ተሟጋቹና የሕግ ባለሙያው ተክለሚካኤል አበበ ጋር (ሙሉውን ያዳምጡት)

ሌሎችም

ዜናዎቻችን

የፈረንሳይ ባንክ የሕወሃትን አገዛዝ የአንድ ቢሊዮን ዶላር የሶቨርኒ ቦንድን አላሻሽጥም አለ

ከ70 በላይ ኢትዮጵያውያን የተሳፈሩባት ጀልባ የመን ባህር ዳርቻ ሰጠመች

የዘጠኙ ፓርቲዎች ትብብር ትግሉ ይቀጥላል ሲል መግለጫ አወጣ

አሜሪካ በኢትዮጵያ ያሉ ዜጎቿን ለደህነታቸው ሲሉ እንዲጠነቀቁ አሳሰበች

ዋና ዋና አመራሩ የታሰሩበት ሰማያዊ ፓርቲ ትግሉ ወደሁዋላ ሳይል እንዲቀጥል ጥሪ አስተላለፈ

የታሰሩት መሪዎች ጨለማ ቤት ናቸው ሕክምና ተከልክለዋል

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሊጀምር ያሰበውን አዲስ የጃፓን በረራ በኢቦላ ስጋት ሳቢያ አቋረጠ

ቶኒ ብሌዬር ከህወሃት አገዛዝ ጋር የሚያደርጉት ቁርኝት ትችት ገጠመው

የትብብሩ ዋና ጸሐፊ ከእስር ቤት ትግሉ እንዲቀጥልና ከጉዞዋችን ወደ ሁዋላ አንልም ሲሉ ጥሪ አስተላለፉ

<<...እኛ እንጸናለን እናንተም በርቱ...>> የሰማያዊ ፓርቲ የስትራቴጂ ሀላፊ ከእስር ቤት

ሌሎችም ዜናዎች አሉ

የቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ኢትዮጵያ

$
0
0

teddy afro
ከቴዎድሮስ ተ/አረጋይ

ማለዳ ፌስቡክ እንዴት አደረ? ብዬ ስከፍት የተዋናይት ሜሮን ጌትነትን ለወሊድ አሜሪካ ልትሄድ መሆኑን አንብቤ ቴዲ አፍሮ ትዝ አለኝ ። የሜሮን አይገርምም ። አሁን ልጆቻቸው ኢትዮጵያ እንዲወለዱ የሚፈቅዱ ወላጆች ጥቂት ወይም እዚያ የመውለድ እድሉ የሌላቸው ናቸው ። የባለሀብት ፣ የባለስልጣን ፣ የፓይለት ፣ የሆስቴስ ፣ ወዘተ ልጆች አሜሪካ ነው በብዛት የሚወለዱት ። ለብዙዎች ኢትዮጵያ አንደ ቀን አሜሪካ ጠቅለው እስኪሄዱ መሸጋገሪያቸው ናት ። እነዚህ ኢትዮጵያ የልጃቸው መኖሪያ እንድትሆን ያልፈቀዱ ዜጎች “ኢትዮጵያ ሀገሬ እወድሻለሁ ” ሊሉ እንዴት ይችላሉ? ሰው እንዴት በእንግድነት ካለበት ቤት ፍቅር ሊወድቅ ይችላል? ምንድነው ሀገር መውደድ? አጋጣሚ ሆኖ ደግሞ እነዚህ ሀገሪቱን ጊዜያዊ መኖሪያ ያደረጉና በቀጣይ ሀገሪቱ የተሻለች መኖሪያነቷ ላይ ጥያቄ ያላቸው ዜጎች የሚበዙቱ የስርዓቱ ተጠቃሚዎች መሆናቸው ነው ።
Meron Getenet
በዚህ ስርዓት ቅጠቀጣ የበዛበት ድምፃዊ ቴዲ አፍሮ ከሀገር ለመውጣትና እዚያው ለመኖር በቂ ምክንያት አለው ። ድምፃዊው ግን ብልጥ ብቻ ሳይሆን ብልህ ነው ። ከሀገሩ ቢወጣ ከባህር የወጣ አሳ እንደሚሆን ያምናል ። ከነችግሩም ሀገርና ህዝብ እንደሚበልጡ ይረዳል ። ከሀገር ወጥተው ከባህር የወጡትን ያያል ። ከዚህ ሁሉ በላይ ሀገሩን ይወዳል ። ይህች የሚወዳት ሀገሩ ለእሱ ባትመቸው እንኳ ለልጆቹ የመኖሪያ ሀገር መሆኗ ላይ ጥያቄ አላነሳም ። ልጆቹን ለሀገሩ ነው የሰጣቸው ። ስለዚህም ባለቤቱ አምለሰት እርግዝናዋ ገፍቶም እዚያች ለብዙዎች ” የተስፋዪቱ ምድር ” የሆነች ሀገር ስትቆይ እዚያው እንደምትወልድ ነበር የገመቱት ። አምለሰት ግን ብዙዎች ወደዚያ በሚሄዱበት ወቅት ወደዚህ መጣች ። የቴዲ ልጅ ኢትዮጵያዊ ሆኖ ተወለደ ። ይህ ብዙ ማለት ነው ። ትልቅ ውሳኔ ነው ። በሀገር ለመማረርና ሀገርን ” ለመጥላት” ፣ ቢያንስ በሀገርና በስርዓቱ (ብዙዎች ዘላቂዋን ሀገርና ነገ የሚወድቀውን ስርዓት ለይተው አያዪም) እምነት ለማጣት ቴዲ ይቀርባል ። ይህ ሁሉ ግን ልጁን አሜሪካዊ ለማድረግ ውሀ የሚቋጥር ምክንያት አልሆነለትም ። ስለዚህ የቴዲን ሀገሬ እሰማታለሁ ። ሀገሬ ሲል እውነትም ሀገሩን እያሰበ ነው ። ቴዲ ” ሀገሬ ለእኔ የሙዚቃ ግጥም ማድመቂያዬ አይደለችም ፤ ሀገሬ ናት ” ቢለኝ አምነዋለሁ ። ብዙዎች ግን አፋቸው እንጂ ተግባራቸው ይህን አይልም ። የቴዲ አፍሮ ኢትየጵያ በስሟ ግጥም የሚሰራላት ፣ ዜማ የሚንቆረቆርላት ፣ ብር የሚታፈስባት ብቻ አይደለችም ። እንደ ትናንቱ ሁሉ ዜግነቷ የሚወደድ በጭንቅ ውስጥ ያለች የተስፋ ሀገር ናት ። ቴዲ ልጆቹን በጉዲፈቻ ማሳደግ የፈቀደ ክፉ አባት አይደለም ። የሚዘፍንላትና በዘፈኑም ሀብት ያፈራባትን ሀገሩን የንግድ መደብር አላደረጋትም ። መኖሪያውና የልጆቹ ማደጊያ እንድትሆን መርጧታል ። ብዙዊች ግን ፣ የቴዲ ከሳሾችም ጭምር ይህ የሀገርን ሀገሬ የማለትና ባለሀገር የመሆን ሞራላዊ ድፍረት በውስጣቸው የለም ።

ሳዑዲ አረቢያ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ 135 ሰዎችን በሽብርተኝነት ክስ አሰረች

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) ሳዑዲ አረቢያ 135 ሰዎችን በሽብርተኝነት ጠርጥራ ማሰሯን አስታወቀች:: የሳዑዲ መንግስት እንዳስታወቀው በሽብርተኝነት ተጠርጥረው ከታሰሩት 135 ሰዎች ውስጥ 109ኙ የራሷ ዜጎች ሲሆኑ ቀሪዎቹ 26 ሰዎች ከኢትዮጵያ; ከሶሪያ; ከየመን; ከግብጽ; ከሊባኖስ; ከአፍጋኒስታን; ከባህሬን እና ከኢራቅ ዜግነት ካላቸው መሆኑን ዘ-ሐበሻ ከሳዑዲ ሚዲያዎች ካገኘችው መረጃ መረዳት ተችሏል::
news
ከአክራሪዎች; ከአሸባሪ ቡድኖች; ከታገዱ የሽብር ኃይሎች ጋር ግንኙነት በመፍጠር, የነርሱን ዓላማ በማሰራጨት, ድብድብ በማንሳትና በሌሎችም ወንጀሎች የተከሰሱት ወገኖች ምን ዓይነት ፍርድ እንደሚጠብቃቸው ሚድያዎቹ የገመቱት ነገር የለም::

በከተማ ውስጥ በሽብር ከተፈረጁ ድርጅቶች ጋር ግንኙነት በፍጠር የተለያዩ የማቃጠል, የማፈንዳት, ሰዎችን በመግደል አንዳንድ ሽብር ወንጀሎች የተጠቀሰባቸው እነዚሁ ወገኖች ጉዳያቸው በፍርድ ቤት እንደሚታይ ይጠበቃል::

የሳዑዲ ሚዲያዎች ከታሰሩት ውጥ ኢትዮጵያውያን ዜጎች እንዳሉበት ይግለጹ እንጂ ስለቁጥራቸው ብዛት ያሉት ነገር የለም::

ከብሔረሰብ በዓል ወደ ለታላቁ ሩጫ! –በእውቀቱ ስዩም

$
0
0

beweketu
ከአምስት ዓመት በፊት ይመስለኛል፣ በደቡብ የሚገኝ የግብርና ዩንቨርሲቲ የብሔር ብሔረሰቦቸን ቀን ምክንያት በማደረግ የክብር አንግዳ አድርጎ ጠራኝ። ትንሽ ካቅማማሁ በኋላ ማየት አይከፋም ብየ ሚኒባስ ተሣፈርሁ። ካምፓስ እንደ ደረስሁ የምግብ ትርኢት ወደ ሚካሄድበት ትልቅ አዳራሽ መሩኝ። ባዳራሹ ትልቅ የግብር ማብያ ጠረጴዛላይ ብሔሮችን የሚወክሉ መብሎችና መጠጦች ተደርድረዋል። ሁሉንም ብሔር ላለማስከፋት ሰማንያ ጉርሻ መጉረስ ይጠበቅብኝ ይሆን በማለት በልቤ እያጉረመረምሁ ለቅምሻ ተሰናዳሁ። ሥጋና ወተት የሁሉም የኢትዮጵያ ብሔሮች ተወዳጅ ምግቦች መሆናቸውን ለመጀመሪያ ጊዜ አስተዋልሁ። ያም ሆኖ፣ ተማሪ ሁላ የራሱን ብሔር ምግብ ልዩ ግኝት አድርጎ ሊያሳይ ይጥራል። አንዱ በተለጎመ ቅል ያቀረበውን ወተት፣ሌላው በሸክላ ጥዋ ያቀርበዋል። አልተሸወድሁም። ወተቱም የላሚቱ ፣ ቅሉም የተፈጥሮ ግኝት እንደሆነ አውቃለሁ።

ቀጣዩ ፕሮግራም፤የብሔር ብሔረሰቦችን ባህላዊ ትርኢት ማየት ነበር። በዩንቨርሲቲው አነስተኛ ስቴድየም ውስጥ በተዘጋጀልኝ ቦታ ላይ ጉብ አልሁ። ስቴድየሙ የተለያዩ የብሔረሰብ ዩኒፎርሞች በለበሱ ተማሪዎች ተሞልቷል። ተሜ ፣እዚም እዚያም ትንንሽ የሰው ደሴት ሰርታ ፣ ወልመጥ ወልመጥ እያለች ጭፈራውን ታስነካዋለች። ብሔረሰብ ይወክላል ተብሎ የሚታሰብ ጥንታዊ እቃ የቀረ አይመስልም። መንሽ፣ጎፈር፣አጎዛ፣አንቀልባ፣አገልግል፣ ሞፈርና ቀንበር፣ጦርና ጋሻ፣ቆልማማ ጩቤ፣ መውዚር ጠመንጃ በየተማሪው እጅ አለ። እንድያውም፣ትንሽ ብጠብቅ የድሮ መድፍ ከነመንኮራኩሩ ሲገባ ማየቴ አይቀርም ነበር።

ዝግጅቱ ተጀመረ። አራት ጎረምሳ ተማሪዎች ርቃን ሰውነታቸውን እንደ ጥምቀት ሽመል አዝጎርጉረው እንጣጥ እንጣጥ እያሉ ባጠገቤ አለፉ። የያዙት አርማ የኦሞ ሸለቆ ብሄሮች ይላል። አንዱን አተኩሬ ሳየው ሸገር የማውቀው መሰለኝ። መጠራጠሬን የታዘበ አጠገቤ የተቀመጠ ተማሪ ምስጢሩን ተነፈሰልኝ፤‹‹የሰውነታቸውን ቅርጽ ለሴቶች ለማሳየት ብለው፣እንደ ኦሞ ለብሰው ነው እንጂ አራቱም የቦሌ ልጆች ናቸው›› አለኝ ።
በነገሩ የሌሉበት ሌሎች ተማሪዎች በስቴድየሙ ዙርያ ተበትነው፣የባለንጀሮቻቸውን ጫንቃ ተደግፈው ከፊታቸው የሚካሄደውን በጥርጣሬ ይመለከታሉ። እኔም መመልከቴን ቀጠልሁ። ከጥቂት ሰላም በሁዋላ አንድ ችግር ተፈጠረ።የትኛው ብሔር ቀድሞ ይለፍ የሚለው ጥያቄ በሁለት ብሔሮች መሀል ውጥረት ለኮሰ። አንዱ ተማሪ የሌላውን ተማሪ ባህላዊ ኮሌታ ጨምድዶ ይዞ ሲተናነቅ አየሁት። ሌሎች ተማሪዎች ለማገላገል ሙከራ ያደርጉ ጀመር። አቧራው መጠብደል ሲጀምር ስጋት ሰቅዞ ያዘኝ። የግቢውን ውበት የማደንቅ መስየ ድብድቡ ሲጀመር ወጥቼ ማመልጥበትን ቀዳዳ መፈለግ ጀመርሁ። በዚህ ዓይነት፣ ለብሔረሰብ በአል መጥቼ፣ለታላቁ ሩጫ ራሴን ሳሟሙቅ፣ ሽማግሌ ገባና ነገሩን አበረደው።

ሰሞኑን ባንድ ዩንቨርሲቲ ግቢ ብሔር መራሽ አምባጓሮ ተቀሰቀሰ ሲሉኝ ትዝ ያለኝ ይሄ ነው። እንደምታውቁት የብሔርና የእግዚአብሔር ነገር ኢትዮጵያ ውስጥ፣ለወሬ አይመቹም። Taboo ናቸው ለማለት ነው። ለደንበኛ ውይይት ሲቀርቡ ሰዎች ይቆጣሉ። ግን ዝምታ፣ የችግሮቻችንን ጥፍርና ክራንቻ ከማሳደግ በቀር ጥቅም የለውም። ወደድንም ጠላንም አገርን ከሥር የሚነቅል ጠብ የሚያስነሡ ሁለቱ ነገሮች ናቸው።

መድረክ፣ የጠራው የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ እውቅና አገኘ

$
0
0

የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) በአዲስ አበባ ከተማ ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚያደርግ የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ሃላፊው አቶ ጥላሁን እንደሻው ለፍኖተ- ነጻነት ገለጹ፡፡

Photo File

Photo File

ሰልፉ ታህሳስ 5 ቀን 2007 ዓ.ም ከጥዋቱ 3፡00 ጀምሮ እስከ ከቀኑ 7፡00 የሚዘልቅ ሲሆን፤ መነሻውን ግንፍሌ ድልድይ አድርጎ መዳረሻውን በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ታቦት ማደርያ ያደርጋል፡፡ በሰልፉ ከሚነሱት ዋና ዋና አጀንዳዎችም መካከል በ2007 ዓ.ም የብሄራዊ ምርጫ ጉዳይን በተመለከተ ኢህአዴግ የያዘውን ግትር አቋም አለዝቦ፣ ለድርድር ዝግጁ እንዲሆን መጠየቅ፤ የ2007 ብሄራዊ ምርጫ ፍትሃዊ እና ዲሞክራሲያዊ ይሆን ዘንድ በገለልተኛ የምርጫ ቦርድ አስፈፃሚዎች እንዲፈፀም፣ ምርጫ ቦርድ ከገዢው ፓርቲ ተላላኪነት ነፃ እንዲሆን፤ ኢህኣዴግ በምርጫ ዋዜማ የተቃዋሚ ፓርቲ አባላትን ማሳደድና ማሰር እንዲሁም ምርጫውም ማወኩን እንዲያቆም፣ የፖለቲካ እና የህሊና እስረኞች እንዲፈቱ. ኢህአዴግ ነፃ ፕሬስን ማፈንና ጋዜጦኞችንና ጦማርያንን ማሳደድና ማሰር እንዲያቆም፣ ኢህኣዴግ ላፀደቀው ህገ-መንግስት ተገዢ እንዲሆንና እንዲያከብረው እንዲሁም የአዲስ አበባ ከተማ ህዝብ የትራንስፖርት እና የውሃ እጥረት እንዲፈታና የከተማው የቴሌኮሚኒኬሽን እና የመብራት መቆራረጥን የመሳሰሉ ጥያቄዎች እንደሚነሱ መድረክ አስታውቋል፡፡

መላው የአዲስ አበባ ከተማ ህዝብ፤ ፍትህና ነፃነት የጠማቸው ኢትዮጵያውያን፤ በኑሮ ውድነት ተማረው ከሰው በታች የሚኖሩ ዜጎች፤ በመብራትና በውሃ መቆራረጥ የተሰቃየው ነጋዴ፤ በአጠቃላይም መላው የከተማው ነዋሪ ለዚህ ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ ስኬት እንዲረባረብ መድረክ ለፍኖተ ነፃነት በላከው መልዕክት ጥሪውን አስተላልፏል፡፡

ሰላማዊ ሰልፉ በአዲስ አበባ መስተዳድር እውቅና እንዳገኘም ለማወቅ ተችሏል፡፡

ታላቁ እስክንድር

$
0
0

ከኢዮኤል ፍሰሐ

ሀገራችን ኢትዮጵያ የሰው ድሃ አይደለችም። በየጊዜው ሰው ይወጣላታል። በእሷ ፍቅር የከነፉ ልጆችን ሁሌም ቢሆን አታጣም። እማማ እንደዚህ አይነት ልጆቿን አምጣ ትወልዳቸዋለች። በእርግጥ ሁላችንም ተምጠን ብንወለድም ፣ ለእሷ ራሳቸውን አሳልፈው ሊሰጧት የተዘጋጁትን ግን ከሁላችንም በከፋ ምጥ ውስጥ ትወልዳችዋለች። ለዛሬ ከእነዚህ እማማ ኢትዮጲያ በከፋ ምጥ ውስጥ ከወለደቻቸው ጀግኖች መሃል የሚመደበውን እስክንድር እንቃኛለን።
Eskinder-Nega
እስክንድር ነጋ ከራሱ ይልቅ የሀገሩን ጥቅም የሚያስቀድም ፣ በሀገሩ ጉዳይ ባይተዋርነት የማያጠቃው ፣ ለግለሰብ ልዕልና የሚታገል ፣ ነጻነትን አጥብቆ የሚፈልግና ለዛም ዋጋ እየከፈለ የሚገኝ ታጋይ ነው። እስክንድር ፣ ላመነበት ነገር ዋጋ እንደሚከፍል በተግባር ያሳየ ሰው ነው። ‹‹ለውጥ ያለመስዋዕትነት አይገኝም። ነጻነታችንን የምንፈልገው ከሆነ ደግሞ እያንዳንዳችን ዋጋ ልንከፍል ይገባል›› ይላል። ይህ ሰው ለነጻነቱ ሲሟገት ሚስቱና ልጆቹን በስደት ተነጥቆ ስጋውን ደግሞ ቃሊቲ አድርጎ ነው። ቃሊቲ ውስጥ ሆኖም ስጋው እንጂ መንፈሱ እንዳልታሰረ በሚገባ ያስታውቃል። አርቆ አሳቢነቱ ፣ አስተዋይነቱና ከአሉታዊ ነገሮች ውስጥ እንኳ አዎንታዊ ነገሮችን የማውጣት ብቃቱ ልዩ ነው። ሰውንም በሰውነቱ ያስተናግዳል። ሁሉንም ሰው በእኩል አይን ማየት ይችላል። እስክንድር ዘንድ ዶክተር ፣ ኢንጅነር ፣ አርቲስት ፣ ጋዜጠኛ ፣ አትሌት ወዘተ…… ሁሉም እኩል ናቸው። ለራሱ መቼም ቢሆን ከፍተኛ ግምት አይሰጥም። እኔ ምን ሰራሁ? ይህ ሁላ ሙገሳ አይገባኝም የሚል ሰው ነው። የፔን አዋርድ ተሸላሚ የሆነ ጊዜ ከወዳጆቼ ጋር በመሆን «እንኳን ደስ አለህ» ለማለት ቃሊቲ በተገኘንበት ጊዜ እንኳን እንዲህ ማለቱን አስታውሳለሁ፤
‹‹እኔ ምን ሰራሁ? ይህ ሽልማት እኮ የእኔ አይደለም። በኢትዮጵያ ውስጥ ዴሞክራሲያዊ ስርአት እንዲሰፍን እየታገሉ የሚገኙት ውጤት ነው። እኔ ብቻዬን ምንም አላደረኩም። ስለዚህ እንደራሴ ሽልማት አድርጌ አልቆጥረውም።›› ይህን ሲለን እጅግ ተገረምኩ።

እሱ እየከፈለ የሚገኘውን ዋጋ እያየሁ እኔ ምን አደረኩ? ሲልም ተደመምኩ። ይህን ሲለን የታሰረ ሰው እንኳ አይመስልም። የመንፈስ ጥንካሬው አስገራሚ ነው። መንፈሱ ከቃሊቲ ውጪ እንደሚገኝ እስክንድርን ቃሊቲ ተገኝቶ የጠየቀው ሁሉ ይመሰክራል። ስጋውም ቢሆን አልተጎዳም። እስኬው ፤ ከጥሩ ተነጋሪነቱ ባሻገር ጥሩ አድማጭም ጭምር ነው። የሰውን ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ መብትንም ያከብራል።
ትህትናው ደግሞ ልዩ ነው።

‹‹እስክንድር ማለት ቤተ-መጻሕፍት ነው።›› ስትል ባለቤቱ ሠርካለም ፋሲል የተናገረችው እውነት እንደሆነም መመስከር እችላለሁ። አዎ! እስክንድር ቤተ-መጻሕፍት ነው። ምን ያህል እውቀት እንዳለው ጠጋ ብላችሁ ስታናግሩት ታውቃላችሁ። እውቀቱን ለማካፈል ባለመሳሳቱ ደግሞ እውነተኛ ምሁር ብዬ እንድጠራው እገደዳለሁ። በአጭር ደቂቃዎች እንኳ ከእስክንድር አንደበት ብዙ ቁም ነገሮችን ቀስሞ መመለስ ይቻላል። ይህ ደግሞ የእስኬውን የእውቀት መጠን በሚገባ ያሳያል። እስኬው ቃሊቲ መሆኑ ክፉኛ ያበሳጫል። ከቃሊቲ ውጪ ቢሆን ኖሮ ብዙ ነገሮችን መስራት ይችላል። ገዢዎቻችንም ይህን ስለተረዱ ክስ መስርተውበት 18 አመት ፅኑ እስራት በይነውበታል። ይህን በሚመለከት ከአንድ ወዳጄ ጋር ስናወጋ ‹‹የእስክንድርን እስር የአንድ ግለሰብ እስር አድርጌ ለመቀበል ይከብደኛል። እስክንድር እኮ የኢትዮጲያ ሪሶርስ ነው። ኢትዮጲያ አንድ ትልቅ ሪሶርስ አታለች። ይህ ሪሶርስ ቃሊቲ መቀመጥ የለበትም። ከቃሊቲ መውጣት አለበት።›› ነበር ያለኝ፡፡ ስለ እስክንድር ይህን ሁላ ብዬ ስለ ጽናቱ ሳላነሳ ባልፍ የእስክንድርን ትልቁንና ዋናውን ጠንካራ ጎን መሳት ይሆናል። እስክንድር ጽናቱ እጅግ ያስደምማል። ጽናቱ የት ድረስ እንደሆነ የሚገልጹ አንድ ሁለት ነገሮችን ላንሳላችሁ።

እስክንድር ፣ ናፍቆት የሚባል ብቸኛ ልጅ አለው። ናፍቆት የተወለደው ምርጫ 97ትን ተከትሎ እሱና ባለቤቱ ለእስር በተዳረጉበት 1998 ዓ.ም ላይ ነው። የናፍቆት የትውልድ ቦታ ደግሞ ቃሊቲ እስር ቤት ነው። ባለቤቱ ሠርካለም ናፍቆትን የተገላገለችው በቃሊቲ እስር ቤት ውስጥ በሚገኝ ክሊኒክ ነው። እስክንድር ከእስር አስኪፈታ ማለትም እስከ 1999 ዓ.ም ድረስ ልጁን አላየውም። ከዚህ በመነሳትም ልጁን ናፍቆት ሲል ሰየመው። እስክንድር እንዲህ የሚወደውን ልጁን ለስምንተኛ ጊዜ ለእስር በበቃበት ማለትም በ መስከረም 3 ቀን 2004 ዓ.ም ላይ በድጋሚ ተለየው። በወቅቱ ናፍቆትን ከትምህርት ቤት በማውጣት ላይ የነበረው እስክንድር ፣ በፖሊሶች ቁጥጥር ስር ሲውል ልጁ ናፍቆት አብሮት ነበረ። ፖሊሶቹ ናፍቆትን ከአባቱ በመለየት አባቱን ይዘውት ሄዱ። ይህን ሲያስተውል የነበረው ናፍቆት ክፉኛ ተረብሾ ነበር።

እስክንድር በእንዲህ መልኩ ከልጁ ከተነጠለ በኋላ ልጁን የሚያገኘው በቃሊቲ ወህኒ ቤት ውስጥ ነው። ናፍቆት ከጊዜ ወደ ጊዜ ስነልቦናው በጣም እየተጎዳ ሲመጣ እስክንድርና ባለቤቱ ሠርካለም በአንድ ነገር ላይ መከሩ። ይህም ልጃቸው አዲስ ከባቢ እንደሚያስፈልገው ነው። በዚህ መሠረትም ሠርካለምና ናፍቆት እስክንድርን በመሰናበት ወደ አሜሪካ አቀኑ። ይህ ውሳኔያቸው ምንኛ ከባድ እንደነበር ሠርካለም ለስደት በተዳረጉበት ጊዜ ፤ በአንድ መጽሄት ላይ እዚህ ውሳኔ ላይ ለመድረስ ያለፈችባቸውን ውጣ ውረዶች ጽፋ ለንባብ ማብቃቷን አስታውሳለሁ። ይህን ጽሁፍ ካነበብኩ በኋላ ቃሊቲ በማምራት

እስክንድርን አገኘሁት። እሱና ሠርካለም ስላሳለፉት ውሳኔ ስጠይቀውም እንዲህ አለኝ፡-
‹‹ለናፍቆት በማሰብ ያደረግነው ነው። እዚህ ሲመጣ የመረበሽ ስሜት አስተውልበት ነበር። ከዛም በተጨማሪ በትምህርት ቤት ውስጥ ከሌሎች ልጆች የመነጠልና የብቸኝነት ስሜት ይታይበት ስለነበር ከባቢ መቀየር የተሻለ ሆኖ ስላገኘነው በጋራ መክረን የደረስንበት ውሳኔ ነው።››
‹‹ባለቤትህንና ልጅህን አንተ እዚህ ሆነህ በስደት መነጠቅህ አይከብድም ወይ?›› አልኩት

እሱም፡-‹‹ባለቤቴንና ልጆቼን በእጅጉ እናፍቃቸዋለሁ። ከእነሱ መነጠሌ ክፉኛ ጎድቶኛል። ግን ይህ መስዋትነት መከፈል ያለበት መስዋዕትነት ነው። እነ ናፍቆት ዴሞክራሲያዊ ስርአት በተገነባባት ኢትዮጵያ ውስጥ መኖር አለባቸው። ለእዚህ ደግሞ መስዋትነቱን መክፈል ያለብኝ እኔ ነኝ።›› ሲል መለሰልኝ፡፡

የተናገረው ንግግሩ የእስክንድር ጽናት ምን ደረጃ እንደሆነ ፍንትው አድርጎ ያሳያል። እንዲህ አይነቱ ጽናት ያላቸው ሰዎች ፣ እጅግ በጣም ጥቂቶች ናቸው። ከእነዛ ጥቂቶች መሀል ደግሞ አንዱ ታላቁ እስክንድር ነው።

የእስክንድርና ጽናት የሚያሳይ አንድ ሌላ ነገር ጨምሬ ጽሁፌን ልቋጭ። በአንድ ወቅት እስክንድርን እየፈራሁና እየተባሁ እንዲህ የሚል ጥያቄ አነሳሁለት። ‹‹እስክንድር ፣ይቅርታ ጠይቀህ የመውጣት ሀሳብ የለህም ወይ?›› (ይህን ጥያቄ ያነሳሁለት የእስክንድር ምላሽ ጠፍቶኝ ሳይሆን የእስክንድር እዛ መሆን ስለሚያበሳጨኝ ነው።)

እንዲህ በማለት ለጥያቄዬ ምላሹን አስከተለ፡- ‹‹የኢህአዴግን መንግስት አይደለም ይቅርታ ይቅርና አመክሮ አልጠይቀውም። 18 አመት አይደል የፈረደብኝ እሷኑ 18 አመት ጠጥቼያት እወጣለሁ እንጂ እንዲህ አይነት ነገርን በጭራሽ አላስብም።››

ይህ ምላሹ የእስክንድር የአእምሮ ጥንካሬና ጽናት ምን ድረስ እንደሆነ እንድገነዘብ አድርጎኛል። እንዲህ አይነት ጽናት ከየት እንደሚገኝ ግን አላውቅም። እንደ ታላቁ እስክንድር ለመሆን እንዲህ አይነት ጽናትና የአእምሮ ጥንካሬ ግድ ይላል። ኢትዮጵያ ብዙ ታላቁ እስክንድሮችን ትሻለች። እስከዛው ግን በአንዱና ቃሊቲ በሚገኘው ታላቁ እስክንድሯ አንገቷን አትደፋም!


40ኛው የህጋዊው ቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ እና “ልማታዊው ሲኖዶስ”

$
0
0

“የብጹዕ አቡነ ዜና ማርቆስ ቦታ አሁንም ክፍት ስለሆነ በቦታው ተጠባባቂ/ምክትል ፓትርያርክ ቢመረጥ መልካም ነው”

 

ታዬ ብርሀኑ

በስደት ላይ የሚገኘው ህጋዊ ቅዱስ ሲኖዶስ 40ኛውን መደበኛ ጉባኤ ከጥቅምት 26-28/2007 ዓ/ም በኮሎምበስ ኦሀዮ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል የተካሄደው ጉባኤ ስኬታማ ነበር። እንደዚህ ዓይነቱ የተሳካ ስብሰባ በኦሀዮ መደረጉ የራሱ የሆነ ታሪካዊ እሴት አለው። ይህም የቅዱስ ሲኖዶስ ድጋፍ ኮሚቴ ብለው የተሰባሰቡ ግለሰቦች በአባቶቻችን መሃል ከሶስት ዓመታት በፊት የጫሩት የመለያየት እሳት ግብዓተ መሬቱ እዛው ቦታ ላይ መፈጸሙ ነው። በእርግጥ አባቶች የነዚህን ስብስቦች አካሄድ ተረድተው ወደ አንድ ገጽ ከመጡ አንድ ዓመት አስቆጥረዋል ሆኖም ከማወጅ በፊት አንድነቱ ይርጋ በሚል ስንጠባበቅ ቆይተን 40ኛው የሕጋዊው ቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ያንጸባረቀውን መልካም ገጽታ እኛ ምኦመናንን ስላስደሰተ እግዚአብሄርን ለማክበርና ለማመሰገን እንዲሁም ደስታችንን እንገልጽ ዘንድ ለመጻፍ ወደድኩ።
holy sinod excile
የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ በቅዱስ ፓትርያርኩ መልካም ፈቃድ በብጹእ አቡነ መልከጼዴቅ ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊነት ዘመናትን በተሻገረ በጠለቀና በበሳል የአመራር ችሎታ ስብሰባው ተመርቶ ወቅታዊና አበይት በሆኑ ርዕሶች ላይ ተነጋግሮ ጉባኤው በስኬት ተፈጽሟል። ሕጋዊው ቅዱስ ሲኖዶስ ስለ ህገ ቤተክርስቲያን መከበርና ሰለ ስብከተ ወንጌል መስፋፋት በስፋት የተነጋገረበት ሲሆን ይህን አሰመልክቶ ከተለያየ አቅጣጫ የቀረቡት አስተያየቶች በተገቢው መንገድ ሁሉም ተስተናግደው ወደ ውሳኔ ሃሳብ ተደርሷል። ቅዱስ ሲኖዶሱ ከተወያየበት ወቅታዊ ርዕሶች በደማቁ ሊሰመርበት የሚገባው ሀገራችንን ኢትዮጵያ ውስጥ በገዢው ፓርቲ እየተካሄደ ያለውን ከርዕስትና ከጉልት ማፈናቀል፣ የዘር ማጥፋትና ማጽዳት ወንጀል፤ የፍትህ እጦት፤ የሰብዓዊ መብት ጥሰት፤ በሃይማኖት ተቋም ውስጥ የሚያደርግውን ጣልቃ ገብነት አውግዞ በመጨረሻም ቅዱስ ሲኖዶስ ይህን የኢትዮጵያን ህዝብን ሰቆቃ የሚያስቆመው ከህዝብ ትግል ጋር እግዚአብሔር በመሆኑ በያዝነው ጾመ ነቢያት ወቅት መላው ኦርቶዶክሳውያን በአጥቢያው በሚገኘው አብያተ ክርስቲያን እየተገኘ የምህላ ጸሎት እንዲሳተፍ ጥሪ አቅርቧል። በመሆኑም ካለፈው እሁድ ጀምሮ በሕጋዊ ቅዱስ ጥላ ጥር በታቀፉ በመላው አለም በሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ዓብያተ ክርስቲያናት ተጀምሯል።

ቅዱስ ሲኖዶስ «እኔስ የመረጥኩት ጾም ይህን አይደለምን የበደልን ሰንሰለት ትፈቱ ዘንድ የቀንበሩን ማነቆ ታላቅቁ ዘንድ የተጨቆኑትን ነጻ ታወጡ ዘንድ ቀንበሩን ሁሉ ትሰብሩ ዘንድ አይደለምን?» ኢሳ 58፥6 በሚለው አምላካዊ ቃል መሰረት የሰብዓዊ መብት ጥሰት ሰንሰለት ህዝቡ ይ,ፈታ ዘንድ፣የኢፍትሐዊነት ቀንበር በኢትዮጵያ ምድር እንዲሰበርና ዘረኝነት በኢትዮጵያ ምድር እንዲገደብና በጠቅላላው ኢትዮጵያውያን ከጭቆና ነጻ ይወጡ ዘንድ ጌታ የመረጠውን ጾም አውጇል። መንፈስ ቅዱስ የሚመራው ሲኖዶስ ፣ በሐዋርያት ወንበር ላይ የተቀመጡ እውነተኛ አባቶች ስለ ምእመናን ሕይወት ግድ ይላቸዋል በክርስቶስ ደም ዋጋ ተክፍሎባቸዋልና። በስደት ያሉት ብጹዓን አባቶችና ካሕናት ሊቀ ካህናቸው ኢየሱስ ክርስቶስ እንደሚከተለው ያስተማራቸውን በቅጡ አስተውለው የጌታ አመትን እየሰበኩ እየገኛሉ። “የጌታ መንፈስ በእኔ ላይ ነው፥ ለድሆች ወንጌልን እሰብክ ዘንድ ቀብቶኛልና፤ ለታሰሩትም መፈታትን ለዕውሮችም ማየትን እሰብክ ዘንድ፥ የተጠቁትንም ነጻ አወጣ ዘንድ የተወደደችውንም የጌታን ዓመት እሰብክ ዘንድ ልኮኛል” ሉቃስ 4፥18
Holy sinod addis ababa
በአንፃሩ ሀገር ቤት የሚገኙው ህገወጡ ሲኖዶስ ስብሰባቸው ጨርሰው ያወጡትን መገለጫ በዘሀበሻ ድረ ገጽና በሐራ ተዋህዶ ላይ ተለጥፎ እንዳየሁት የመጀመሪያ ጥሪ ለሕብረተሰቡ የቀረበው ልማታዊ ጥሪ ነው በተለይም የአባይን ግድብ አሰመልክቶ። የአባይ ግድብ ጉዳይ መንፈሳዊ አባቶችን ጨምሮ የሁሉም ኢትዮጵያዊ ቢሆንም መንፈሳዊ አባቶች ማስቀደም ያለባችው የተጠሩበት ሰማያዊ ጉዳይ ነው። አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአገልግሎት የጠራችው የሰው ሕይወት እንዲያድኑ እንጁ ለሕንፃ ልማት አይደለም። ለነገሩ መንበሩን የተቆጣጠሩት በጦር መሳሪያ ሃይል እንጂ በመንፈስ ቅዱስ ሃይል ስላልሆነ ሲጀመርም ቅድስና የሌለው ሲኖዶስ ነው። በመሆኑም ቅዱስ ሲኖዶስ የሚለው ስያሜ አይገባውም ይልቁንም “ልማታዊ” ሲኖዶስ የሚለውን ስያሜ ይገባችዋል። በጣም የሚያሳዝነው ጉዳይ በእግዚአብሔር አምሳል የተፈጠረው ወገናቸውን መረገጥ በዓይናችው እያዩ የስላሲዎች ህንጻ የሆነው ሕዝብ ላይ የሚደርሰውን ኢ-ፍትሐዊነት ዓይናቸውን ጨፍነው እያለፉ ክርስቶስ በደሙ የዋጃቸውን የአማራውና አኝዋኩ ሕዝብ ላይ የተፈጸመውን የዘር ማጽዳት ዘመቻ እየሰሙ እንዳልሰሙ አልፈው ያልተጠሩበትን ስለ ግዑዙ አባይ መገደብ ያወጡት መገለጫ ምንም መንፈሳዊ መዓዛ የሌለውና በሞራላዊ መስፈርት ሲመዘን እጅግ የወረደ መግለጫ ነው።

ተመዝንክ ግን ቀለህ ተገኘህ የሚለው የመጽሃፍ ቅዱስ ቃል ለነዚህ የአባቶች ስብስብ ተገቢ ቃል ነው (ዳንኤል 5፡26) ። ፍትህ እንደዚሁም ሰብዓዊ መብት እኮ በእግዚአብሔር አምሳል ለተፈጠረ ሰው ስማያዊ ስጦታ ነው። ሰለሆነም የዜጎች ሰብዓዊ መብት ሲጣስ እንዲከበር መጮህ፣ ጸልዩ ብላ ማዘዝ እንዲሁም ጸሎት ብቻ ማዘዝ ሳይሆን መብቱንና ነጻነቱን ለማስከበር የበኩሉን እንዲያረግ ማዘዝ የቤተክርስቲያን ተልዕኮ ነው። ሩቅ ሳንሄድ ኢትዮጲያዊውያኑ ብጹዕ አቡነ ጴጥሮስና አቡነ ሚካኤል ለዚህ ምግባር ዓይነተኛ ምሳሌዎች ናቸው። ሀገር እየደማ፣ ሀገር እየቆሰለ ህዝቡ ርስቱን እየቀማ በሀገሩ እየተሰደደ፣ በሀስት ክስ እያታሰረና እየሞተ ልክ በኢያሪኮ በወንጀለኞች ተደብድቦ ወድቆ በሕይወትና በሞት መካከል የነበረውን ሰው የአይሁድ ካህናት (ፈሪሳውያን) እንዳላዩ ገለል ብለው እንዳለፉት (ሉቃ 10፥30-35) እንደዚሁ የሀገር ቤቶች አባቶችም የሕዝቡን ሕማማትና ሞት ችላ ብለው አልፈው አባይ ይገደብ ይሉናል ምናለ በነካ አፋችው የሰብዓዊ መብትም ጥሰት ይገደብ፣ ዘረኝነትና ስደት ይገደብ ቢሉ። የሚገርመው ሉቃ 10፥30-35 እንደሚነገረን ካህን ያልሆነው ሳምራዊው ግለሰብ በነገድ ከማይገናኘው ለወደቀው ሰው አዝኖ መደረግ ያለበት እርዳታ ሁሉ አደረገለት። በዘርና በነገድ ከኛ ምንም ግንኙነት ሳይኖራችው ግን ኢትዮጵያ ውስጥ ስለሚደረገው የሰብዓዊ መብት ጥሰት “Amnesty International” ፣ “Human Rights Watch” እና የዓለም ዓቀፉ የጋዜጠኞች ማህበር የሚጮሁት የሳምራዊውን በጎ ምግባር ሲወጡ የአዲስ አበባው ልማታዊ ሲኖዶስ ደግሞ የፈሪሳውያኑን ስራ አንጸባርቀዋል። የአዲስ አባባው ሲኖዶስ የሃይማኖትን ስም ተላብሶ በምግባር ግን በአቶ (ምዕመን) ደረጃ ካሉት ከአርቲስት ታማኝ ና ከአቶ ኦባንግ ያነሰ የሞራል ስብዕና እያሳዩ ናቸው። ዲ/ን ዳንኤል “የማያለቅስ ልጅ” በሚለው ጽሁፉ ይህንን የአዲስ አበባውን ሲኖዶስ ስብሰባ አሰረ ሐዋርያትን (የሐዋርያት ፈለግ) የተከተለ ብሎ አድንቆታል ለማንኛውም የአንባቢ ህሊና የሐዋርያትን ፈለግ የተከተለው የትኛው ጉባኤ እንደሆነ ይፍረድ።

ጭራሽ የአዲስ አበባው ሲኖዶስን ጨምሮ ሌሎችም የሃይማኖት ተቋሟት በትግራይ ነጻ አውጪ መንግስት የሰለላ ድርጅት እዝ ስር ተዋቅረው መንጋውን የሚሰልሉና የሚያስጨንቁ ለመንጋው የማይራሩ ጨካኝና ምንደኛ እረኞች እንደሆኑ ለኢሳት የደረሰውን የገዢው ፓርቲ የስለላው ድርጅትን ሪፖርት የድምጽ መረጃ የሰማ ይገነዘባል። የእግዜሃብሔር ቃል ለእነዚህ የሃይማኖት አባቶች እንዲህ ይላል፥

“እግዚአብሔር ከሕዝቡ ሽማግሌዎችና ከአለቆቻቸው ጋር ይፋረዳል፤የወይኑን ቦታ የጨረሳችሁ እናንተ ናችሁ፤ ከድሆች የበዘበዛችሁት በቤታችሁ አለ፤ሕዝቤንም ለምን ታደቅቁአቸዋላችሁ? የድሆችንስ ፊት ለምን ትፈጫላችሁ? ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር። ኢሳ3፥13

“ስለዚህ፥ እረኞች ሆይ፥ የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ፤ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። እነሆ፥ በእረኞች ላይ ነኝ፥ በጎቼንም ከእጃቸው እፈልጋለሁ፥ በጎቼንም ከማሰማራት አስተዋቸዋለሁ። ከዚያም ወዲያ እረኞች ራሳቸውን አያሰማሩም፤ በጎቼንም ከአፋቸው አድናለሁ፥ መብልም አይሆኑላቸውም። ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና። እነሆ፥ እኔ ራሴ በጎቼን እሻለሁ እፈልግማለሁ።እረኛ በተበተኑት በጎች መካከል ባለ ጊዜ መንጋውን እንደሚፈልግ፥ እንዲሁ በጎቼን እፈልጋለሁ፤ በደመናና በጨለማ ቀን ከተበተኑት ስፍራ ሁሉ አድናቸዋለሁ።” ሕዝቅኤል 34፦9-12

በመጨረሻም ህጋዊ ቅዱስ ሲኖዶስ የሚገኝበት ሁኔታ ደስ የሚያሰኝ ነው። በስደት ከሚገኙት የመምህራንና የጋዜጠኞች ማህበር እንደዚሁም ከተለያዩ በስደት ከሚገኙ የኢትዮጲያውያን ተቋሟት የግንኙነት መሰመር ፈጥረው የህዝባችንን ሰቆቃ የሚያጥርበት ጊዜ አብረው ቢመከሩ መልካም ይመስለኛል። የጠቅላይ ቤተክህነቱ አስተዳደሪ ከሰዎች ጋር በበለጠ እየተግባባ እንዲሰሩ ቢመከሩ እንደዚሁም የህዝብ ግንኙነት ክፍል አንደበተ ርቱዕና ነቃ ያሉ አባቶች ቢካተቱበትና የብጹዕ አቡነ ዜና ማርቆስ ቦታ አሁንም ክፍት ስለሆነ በቦታው ተጠባባቂ/ምክትል ፓትርያርክ ቢመረጥ መልካም ነው።

የአባቶቻችን አምላክ የተመሰገነ ይሁን!
Taye_berhanu@ymail.com

Health: የውጥረት ምንጮችን ማድረቂያ 10 ስልቶች 

$
0
0

ሊሊ ሞገስ

ያለ ልዩነት ሁሉም ሰው በአንድም ሆነ ሌላ ምክንያት ውጥረት ውስጥ ራሱን ሊያገኝ ይችላል፡፡ ታዲያ ረዘም ላለ ጊዜ ውጥረት ውስጥ ስንሆን ለልዩ ልዩ የጤና ችግሮች እንጋለጣለን፡፡ እስከ 70% የሚደርሱ ሰዎች ሐኪማቸው ዘንድ የሚመላለሱበት አቢይ ምክንያት ከውጥረት ጋር በተያያዘ የጤና ችግር ነው፡፡

yelling

ስር የሰደደ ውጥረት ከሞላ ጎደል የሰውነታችንን ስርዓት ይረብሻል፡፡ የደም ግፊትን መጠን ያንራል! በሽታ የመከላከል አቅምን ዝቅ ያደርጋል፣ ለድንገተኛ የልብ ህመም (Heart Atlack) እና ምት (Stroke) የሚኖረንን ተጋላጭነት ይጨምራል፣ እርጅናን ያፋጥናል፡፡ ሌላው ቀርቶ ለረዥም ጊዜ የሚቆይ ውጥረት የአንጎልን አነዋወር እና አሰራር በመቀያየር ጭንቀት እና ድብርት ለመሳሰሉት የአዕምሮ ጤና መቃወስ አጋልጦ ይሰጣል፡፡ በዕለት ተዕለት ህይወታችሁ ውስጥ የሚፈጠሩ የውጥረት ምንጮችን ለማድረቅ 10 ስልቶችን እነሆ፡-

1. ፋታ

በየቀኑ መጠነኛ ፋታ የምታገኙበት ጊዜ ይኑራችሁ፡፡ በዚህ የፋታ ሰዓታችሁ ታዲያ ከየትኛውም አይነት ኃላፊነት እና ተግባር ራሳችሁን ነፃ በማድረግ አዕምሮአችሁንም ሆነ አካላችሁን ለማሳረፍ ሙከራ አድርጉ፡፡ ሌላው ቀርቶ ቴሌቪዥን፣ ራዲዮ፣ አይፖድ፣ ኮምፒዩተር፣ ስልክ የመሳሰሉትን ነገሮች እንኳ በዚህ የፋታ ጊዜያችሁ በመዝጋት ውጥረትን ቢያንስ ቢያንስ ረገብ ማድረግ ትችላላችሁ፡፡

2. እስኪ ይሁና!

አንዳንድ የውጥረት ምንጭ ሊሆኑ የሚችሉ ነገሮችን ልንለውጣቸውም ሆነ ልንወጣቸው አንችል ይሆናል፡፡ ለምሳሌ ከልብዎ የሚወዱት ወዳጅዎ በሞት ከዚህ ዓለም ቢለይ ወዳጅዎን ከሞት የሚመልሱበት መላ አይኖርም፡፡ አልያም ደግሞ በህክምና የማይድን ሕመም ቢያጋጥምዎት ያሉበትን ሁኔታ ሙሉ በሙሉ መቀየር አይችሉ ይሆናል፡፡ ታዲያ፣ እነዚህን የውጥረት ምንጮች ማድረቂያ አንዱ ስልት ነባራዊ ሁኔታውን አገናዝቦ ‹‹እስኪ ይሁና!›› ብሎ መቀበል ነው፡፡ ‹‹ለምን እንዲህ እና እንዲያ ሆነ?››፣ ‹‹እንደው ጌታዬ ምን ብበድልህ ነው?››፣ ‹‹እውነት የለህማ!›› ወዘተ… አይነት ቅሬታዎችና ምሬቶች ውጥረትን ያባብሱ ይሆናል እንጂ አይቀንሱም፡፡ ስለዚህ ልንለውጥ የማንችለውን ነገር ዘወትር ከመጋፋት ይልቅ እስኪ ይሁና! ብሎ መቀበል ውጥረትን ይቀንሳል፡፡ ለምሳሌ፣ የካንሰር ታማሚ ቢሆኑ እና ነጋ ጠባ እንደው አምላኬ ምን ብበድልህ ነው? የሚል ምሬት ውስጥ ቢገቡ፤ በአንድ በኩል ህመሙ የሚፈጥረው ውጥረት አለ፤ በሌላ በኩል ደግሞ ‹‹ለምን?›› የሚለው መልስ አልባ ጥያቄዎ የሚፈጥረው ሌላ ውጥረት አለ፡፡ ስለዚህ መለወጥ የማይችሉትን ይህንን እውነታ መቀበል ቢችሉ ቢያንስ እርሶ የፈጠሩትን፣ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ የሆኑብዎትን ሁለተኛ ተጨማሪ ውጥረት ይቀንሳሉ፡፡

3. ዘና ማለት

በየዕለቱ ዘና ሊያደርገን የሚችል አንድ ነገር ማድረግ መቻል ውጥረትን መቀነሻ ፍቱን መላ ነው፡፡ መጫወት፣ መደነስ፣ ሙዚቃ መስማት ወዘተ… ሊሆን ይችላል፡፡ ብቻ ምንም ይሁን ምን በየዕለቱ አንድ ዘና የሚያደርጋችሁን ነገር ማድረግ ውጥረትን ለመቀነስም ሆነ ለመቆጣጠር በእጅጉ ይረዳል፡፡ የሚያስደስታችሁን ነገር በየጊዜው ባደረጋችሁ ቁጥር ለምትሰሩትም ስራ የሚኖራችሁ ፍቅር እንዲሁ ተያይዞ ይጨምራል፡፡

4. ‹‹ስጡ ይሰጣችሁማል!››

ይህ ጥቅስ ከመፅሐፍ ቅዱስ ወርቃማ ጥቅሶች መካከል አንዱ ነው፡፡ መስጠት ለ‹‹መጽደቅ›› ብቻ ሳይሆን ጤናን ለመጠበቅም ይረዳል፤ በሽታ የመከላከል አቅማችንን ከፍ ያደርጋል፤ ህይወታችን በትርጉም የተሞላና በዓላማ የታጠረ እንዲሆን ያግዛል፡፡ ስለዚህ ያላችሁን ማንኛውንም ነገር ጊዜም ሆነ ገንዘብ እንደየአቅማችሁ እና ነባራዊ ሁኔታችሁ ስጡ፣ በምትኩ ከውጥረት ነፃ የሆነ ህይወት ይሰጣችኋል፡፡ አንዳንዶቻችሁ እዚህ ጋ ‹‹እኔ ራሴ እርዳታ የምፈልግ ሰው ነኝ፡፡ ምን ኖሮኝ ነው የምሰጠው? ራስ ሳይጠና ጉተና›› ነኝ ትሉ ይሆናል፡፡ ጊዜን መስጠት፣ ጉልበትን መለገስ፣ አካባቢን ፅዱና አረንጓዴ ማድረግ ወዘተ… በነፃ ራስ ሳይጠናም በዙሪያችን ለሚገኙ ሰዎች ልናበረክት ከምንችለው ብዙ ነገር መካከል ጥቂቱ ነው፡፡ እና ነገሩ ‹‹ከአንጀት ካለቀሱ›› ነውና እንዲያው ለሌሎች ብቻ ብለን ሳይሆን ለራሳችንም አሰብ አድርገን መስጠትን ባህላችን እናድርግ፡፡

5. ወሲብ

የቨርጂኒያው ሳይኮሎጂ ፕሮፌሰር ዶ/ር ጀምስ ኮን ‹‹ከሚያፈቅሩት ሰው ጋር አዘውትሮ ወሲብ መፈፀም ቢታመሙ ቶሎ ለመዳን፣ በህመም እና በሽታ የመያዝ ዕድላችንን ለማጥበብ እንዲሁም ረዥም ዕድሜ ለመኖር ያስችላል›› ይላሉ፡፡ ሌላው ቀርቶ ከሚወዱት ሰው ጋር እጅ ለእጅ ተያይዞ የእግር ጉዞ ማድረግ እንኳ ውጥረትን እንደሚቀንስ የጥናት ውጤታችን ያሳያል ብለዋል፡፡

6. ‹‹ይቅር ብያለሁ!››

ቂምና በቀልን መቋጠር የሚያስከፍለው ዋጋ የትየለሌ ነው፡፡ ውስጣችን ቂምና ቅሬታ ሲያዝል ሰውነታችን ይዝላል፣ አዕምሮአችን አሰራሩ ይዛነፋል፤ አካላችን ጤንነቱ ይጓደላል፡፡ ሚቺጋን ዩኒቨርሲቲ ውስጥ የተደረገ ጥናት ይቅርታ ማድረግ ከጤናማ አዕምሮና አካል ጋር ቀጥተኛ ቁርኝት እንዳለው አረጋግጧል፡፡ ‹‹ይቅር ብያለሁ!›› የሚሉ ሰዎች ‹‹በመቃብሬ ላይ…!›› ከሚሉ ሰዎች ይልቅ በአካልም ሆነ በአዕምሮ ይበልጥ ጤነኛ ናቸው፡፡ ‹‹በደለን›› የምንለውን ሰው ሳይሆን የገዛ ራሳችንን ለመጥቀም ዛሬ ነገ ሳንል ይቅርታ ማድረግን እንለማመድ፡፡

7. ፅሞና

በበዛት የሩቅ ምስራቃዊያኑ ባህል ነው፡፡ በተለይ የአዕምሮ ጤንነት በመጠበቅ ረገድ አይነተኛ ሚና ይጫወታል፡፡ ፅሞና በእንግሊዝኛ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው፡፡ አንዱ ጠቀሜታው ውጥረትን መቀነስ ነው፡፡ በቀን ለአንድ ወይም ሁለት ጊዜ ለሃያ ደቂቃዎች ያህል ‹‹Meditation›› መስራት በርካታ ጠቀሜታ ያስገኛል፡፡ ፅሞና ማለት አንድ ስዕል ላይ ወይም አንዳች ነገር ላይ ብቻ ትኩረት አድርጎ አእምሮ ውጥረት የፈጠሩበትን ነገሮች እንዲዘነጋና እንዲረጋጋ የማድረግ ስልት ነው፡፡ አስሩን እየፈተለ ውጥርጥር ያለንአዕምሮ ፅሞና ረጋ ያደርገዋል፡፡

8. ኑ ጓደኞቼ…!

ጥናቶች እንደሚጠቁሙት ከወንዶች ይልቅ ሴቶች ስሜታዊ ውጥረትን የመቋቋም ችሎታቸው ላቅ ያለ ነው፡፡ ይህ ሊሆን የቻለበት አንድ ምክንያት ሴቶች ከወንዶች ይልቅ ከጓደኞቻቸው ጋር ጥብቅ ቅርርብ እና ጓደኝነት ስሚመሰርቱ ነው፡፡ ስለዚህ በስራም ሆነ በሌላ ጉዳይ አዕምሮ ውጥር ሲል ባልንጀራን/ጓደኛን አግኝቶ የሆድ የሆድን ማውራት ‹‹እፎይ›› ለማለት ይረዳል፡፡

9. ሙዚቃ

ውጥረት ሲበዛብዎት ሙዚቃ ማዳመጥም ሆነ አብሮ ማንጎራጎር ቀላል የማይባል መረጋጋትን እና መነቃቃትን ይፈጥራል፡፡ የአሜሪካ ሳይኮሎጂ ባለሙያዎች ማህበር ቅርብ ጊዜ በአከናወነው ጥናት መሰረት እጅግ በጣም ብዙ ሰዎች ሙዚቃ ውጥረትን የሚያረግቡበት ቁጥር አንድ መሳሪያቸው እንደሆነ አረጋግጧል፡፡

10. ሺ ዓመት አይኖር!

ህይወትን በሁሉም መስክ ቀለል ሊያደርጉ የሚችሉ ቁም ነገሮችን ማከናወን የዋዛ ውጥረት መቆጣጠሪያ እና መከላከያ ስልት አይደለም፡፡ በተቻለ መጠን ህይወትን ቀልጣፋ እና ቀላል የሚያደርጉ አማራጮችን አፈላልጎ መገልገል ብልህነት ነው፡፡ ሺ ዓመት አይኖር! ለምሳ የሚኖሩበት አካባቢ እምብዛም ከመስሪያ ቤትዎ የማይርቅ ከሆነ ከታክሲ ግፊያ እና ሰልፍ ይሉት ልፊያ ዳኑ ማለት ነው፡፡ ታክሲም ላያስፈልግዎት ይችላል፡፡ ሁለትና ሶስት ኪሎ ሜትር የእግር ጉዞ አድርገው ቤትዎ ቢገቡ ወጪም ውጥረትም ቀነሱ ማለት ነው፡፡ የቪዛ ካርድ ተጠቃሚ ቢሆኑ ገንዘብ ለማውጣት በፈለጉ ቁጥር የስራ ቀንና ሰዓት መጠበቅም ይሁን መሰለፍ አያስፈልግዎትም፡፡ ምግብ ቤትዎ አብስለው ቢመገቡ በመስተንግዶና ምግብ ንፅህና ጉድለት እንዲሁም በዋጋ ንረት መጎዳት ምክንያት ለሚደርስብዎት ቅሬታ መላ ዘየዱ ማለት ነው፡፡ የምግብ ዝግጅት ቢማሩ የምግብ ችሎታዎ እና ዕውቀትዎን ከፍ በማድረግ በጣት ከሚቆጠሩ አማራጮች በመውጣት ጣት የሚያስቆረጥሙ ብዙ ምግቦችን አዘጋጅተው ጊዜ፣ ጤናና ደስታ ያተርፋሉ፡፡ ብቻ በሁሉም መስክ በተቻለ መጠን የዕለት ተዕለት ህይወትን ቀላልና ቀልጣፋ የሚያደርጉ እርምጃዎችን መውሰድ ውጥረትን ቀንሶ ጤናን ለመጨመር ይረዳል፡፡

በመጨረሻ፣ ውጥረትን መቀነስ የሚለውን ሐሳብ ከላይ እስከታች ይዘን መዝለቃችን ውጥረት ጨርሶ አያስፈልግም ለማለት እንዳልሆነ አንባቢ ይገንዘብልን፡፡ ልክ የሌለው ውጥረት እርግጥ ነው አይበጅም፡፡ በልክ የሆነ ውጥረት ግን አስፈላጊ ነው፡፡ ስራ ያሰራል፣ በሽታ መከላከያ ህዋሶቻችን እንኳ ንቁ እንዲሆኑ ያግዛል፡፡ መቆጣጠርም ሆነ መከላከል የሚያስፈልገው ከልክ በላይ ሆኖ እረፍት እና እፎይታ፣ ጤናና ደስታ የነሳን ውጥረት ነው፡፡ 

ዴሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጲያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌይ አቋም  መግለጫ       

$
0
0
DCESON

DCESON

ዴሞክራሲያዊ ውጥ በኢትዮጲያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌይ  ከተቋቋመበት አላማዎች አንዱና ዋነኛው በሃገራችን  በኢትዮጲያ ያለውን ኢፍትሃዊ የአንድ ዘር የበላይነት የሰፈነበትን አምባገነን  ስርሃት በማውገዝ እንዲሁም በመታገል ዴሞክራሲያዊ ኢትዮጲያን ማለትም  የዜጎችን እኩልነት የተረጋገጠባት፣  የህዝብ የስልጣን ባለቤትነት የተረጋገጠባት ፣ የዜጎች ሰብአዊ መብት የተከበረባት ፣  የህግ የበላይነት የሰፈነባት፣ እንዲሁም  ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል በኩል አይን የሚታይባት ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጲያን ለመገንባት የሚደረገውን ህዝባዊ ትግል መደገፍና ብሎም በአጋርነት ሞቆም ነው፡፡

ስለሆነም ባሳለፍነው ሳምንት ማለትም ህዳር 27/28 የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር የሃገሪቱ ህገ- መንግስት በሚፈቅደው መሰረት  ለሃያ አራት ሰአት የሚቆይ ሰላማዊ ሰልፍ ጠርተው እንደነበረ ይታወሳል፡፡ ሆኖም በማን አለብኝ ሃገሪቱን እንዳሻው የሚያደርግ ህውሃት(ኢህአዴግ)አሁን በህብረተሰቡ ዘንድ የተፈጠረውን የለውጥ ስሜት እንዲሁም ለዚህ ክስተት ምክኒያት ናቸው ያላቸውን የ9ኑ ፖርቲዎች ትብብር ከመቼውም በላይ ስላሰጋው ከላይ  በተጠቀሰው ቀን የአደባባይ የ24 ሰአት ሰልፍ እንዳይካሄድ የትብብሩን አምራሮችና አባላትን በማዋከብ ስራ በዝቶበት ሰንብቷል፡፡

በመጨረሻም በሰልፉ ላይ የተገኙ የ9ኙ ፓርቲዎች ከፍተኛ አመራሮችና አባሎችን እንዲሁም የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ፍርሃት ባሸበረው ህውሃት (ኢህአዴግ)በጭካኔ ተደብድበዋል፣ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል፣ ተግዘው ታስረዋል፡፡ ሙስሊሙ ማህበረሰብ  በሰላማዊ ሰልፉ ላይ በመገኝታቸው ብቻ ከጎዳና ታፍሰው የአገዛዙ አረመኔዊ እርምጃ ሰለባ ሆነዋል፡፡ እስካሁንም በዚሁ ዘረኛና አረመኔያዊ አገዛዝ ቁጥራቸው ከ300 የሚበልጡ  ሰላማዊ ታጋዮች በእስር ቤት ታፍነውከፍተኛ ድብደባ ደርሶባቸዋል ፡፡

ዴሞክራሲያዊ ውጥ በኢትዮጲያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌይ  አምባገነኑ ህውሃት(ኢህአዴግ) በሰላማዊ ታጋዮች እንዲሁም በሰላማዊ መንገድ ድምጻቸውን ሊያሰሙ በወጡ ዜጎች ላይ የወሰደውን አረመኔያዊ እርምጃ በጥብቅ እያወገዘ የ9ኙ ፖርቲዎች ትብብር እያደረገ ያለውን እልህ አስጨራሽ ትግል በንቃት የሚከታተልና ከጎናችሁ መቆሙን እየገለጸ ለተጀመረው የነጻነት ትግል አጋርነቱን ይገልጻል፡፡

ድል ለኢትዮጲያ ህዝብ!!!!!

ዴሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጲያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌይ !!

 

 

 

 

 

ተንበርክኮ ከመኖር በዓላማ ፀንቶ መሞት ይሻላል!! –በስደት የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር አባላት አስተባባሪ

$
0
0

ሕዳር 22 ቀን 2007 ዓ.ም

ዝነኛው ገጣሚና መምህር ኃይሉ ገብረዮሐንስ

መምህር ኃይሉ ገብረዮሐንስ

በስደት የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር አባላት አስተባባሪ ኮሚቴ ዝነኛው ገጣሚና መምህር ኃይሉ ገብረዮሐንስ በስደት ከሚኖርበት አገር ስዊድን( ስቶኮልም ከተማ) ጥቅምት መጨረሻ 2007 ዓ.ም ማረፉን የሰማው በከፍተኛ ሀዘን ነው።

ሃይሉ ገብረዮሐንስ በመምህርነት ሙያው እንደ አንድ ሃላፊነት የሚሰማው ዜጋ ሀገር ወዳድ ትውልድ ለመፍጠር የበኩሉን አስተዋፅኦ አድርጓል። የዚያ ትውልድ ግንባር ቀደም የለውጥ ሃዋሪያ ሰለሆነም የአገር ባለውለታ ነው። በተፈጥሮ ባገኘው ተሰጥኦና በትምህርት ባዳበረው ገጣሚነት ቀስቃሽ ፣አነቃቂ፣ ትምህርታዊ፣ ፍልስፍናዊና ሥነ ጥበባዊ የሆኑ ግጥሞችን በማቅረብ ይታወቃል። ገሞራው ከወጣትነት እድሜው ጀምሮ ለጭቁን ህዝቦች አርነት መውጣት በፅናት የታገለና በተግባር ያስመሰከረ ነው። እምቅ መልዕክት በያዙት ግጥሞቹ የተነሳም ስቃይ፣ ግርፋትና እስር ደርሶበታል።—[ሙሉውን መግለጫ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]—

 

Download (PDF, Unknown)

 

ሲሳይ ዘርፉ ተጨማሪ 7 ቀን ተቀጠረበት-

$
0
0
10849854_624972437628418_1785418356513815310_n

ሲሳይ ዘርፉ

ህዳር 24/2007 ዓ.ም ለአዳር ሰላማዊ ሰልፍ ቅስቀሳ ላይ እያለ በፖሊስ ተይዞ የታሰረው የሰማያዊ ፓርቲ አባል አቶ ሲሳይ ዘርፉ ተጨማሪ 7 ቀን ተቀጠረበት፡፡ ጉለሌ ፖሊስ መምሪያ ታስሮ የሚገኘው አቶ ሲሳይ ህዳር 25/2007 ዓ.ም አምስት ኪሎ አካባቢ የሚገኘው መናገሻ ፍርድ ቀርቦ ‹‹ያልተፈቀደ ሰላማዊ ሰልፍ በመቀስቀስ›› በሚል ክስ 8 ቀን ተቀጥሮበት እንደነበር ይታወሳል፡፡ ሲሳይ ለታህሳስ 3 ይቀርባል ተብሎ የነበር ቢሆንም ከተቀጠረበት ቀን 2 ቀን ቀድሞ ዛሬ ፍርድ ቤት ቀርቦ ተጨማሪ 7 ቀን ተቀጥሮበታል፡፡

Viewing all 8745 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>