Quantcast
Channel: ዘ-ሐበሻ – Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all articles
Browse latest Browse all 8745

“ሞላ በስርዓቱ ተገዶ 700 ሰራዊት ይዤ መጣሁ ይበል እንጂ በትክክል የሄዱት 115 ናቸው ከነርሱም ውስጥ 48ቱ ተመልሰዋል”–ታጋይ መኮንን ተስፋዬ

$
0
0

የትህዴን ድርጅት በወያኔ ሃይሎች ሊሰለል የማይችል ጠንካራ የስለያና የፀረ ስልያ ማዕከል የገነባ ታላቅ ድርጂት ነው ሲል የድርጂቱ ምክትል ሊቀመንበር ታጋይ መኮነን ተስፋይ በየካቲት ውለታ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ባደረገው ቃለ መጠየቅ ገለፀ::

mekonen
የደህሚት ድምጽ እንደዘገበው ታጋይ መኮነን ተስፋይ ሞላ ከወያኔ የደህንነት ሃይሎች ጋር ለአንድ አመት ያህል ስሰራ ቆይቻለሁ ይላል የሚል ጥያቄ ቀርቦለት ሲመልስ ሞላ ይህን የማድረግ አቅም እንደሌለውና የትህዴንም ትልቅ ድርጂት እንደመሆኑ መጠን ጠላቱንና ወዳጁን ለይቶ የሚያውቅ ጠንካራ ድርጂታዊ የስልያና የፀረ ስለያ ማዕከል የገነባ ስለሆነ የወያኔ የደህንነት ሃይሎች ይህን የማድረግ አቅም የላቸውም ሲል አረጋግጧል::

ታጋይ መኮነን ተስፋይ ጨምሮም ሞላ ከተጠያቂነት ለማምለጥ ድርጂታዊ ጉባኤ እንደሚካሄድ ፈርቶ አመለጠ እንጂ ከወያኔ ጋር አልነበረምየመሆን ሃቅምም የለውም ካለ በኋላ ይህ ለአንድ አመት ግንኙነት ነበረኝ ያለው መግለጫም ሃይለኛ መስሎ ለመታየትና የወያኔ የስለላ ማዕከል ጠንካራ እንደሆነ ለማስመሰል ህዝቡን ለማደናገር የተጠቀመበት የሃሰት ፕሮፖጋንዳ ነው ሲል ገልጿል::

ሞላ 700 የሚሆኑ ታጋዮችን ይዠ የሚለውም ቢሆን በስርኣቱ በል ተብሎ ስለተገደደ እንጂ ከዚያ ባለፈም የነበረውን ድክመት ለመሸፈን ሃይለኛ መስሎ ለመታየት ካልሆነ በስተቀር ሞላ የወሰደው ታጋይ መጠኑ ከ115 የማይበልጡ ሲሆን ከእነዚህ መካከልም 48ቱ ታጋዮች ተደናገረው ስለነበር ወደ ድርጂታቸው መመለሳቸውን አስታውቋል::

በተጨማሪም በሱዳን መሬት አካባቢ በርከት ያሉ ታጋዮች ሞላን በመቃወም ተበታትነው የሚገኙ ሲሆን ትህዴንም ወደ ድርጂታቸው ለመመለስ ሁኔታዎችን እያመቻቸ እንደሚገኝ ጨምሮ አስረድቷል::


Viewing all articles
Browse latest Browse all 8745

Trending Articles



<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>