Quantcast
Channel: ዘ-ሐበሻ – Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all articles
Browse latest Browse all 8745

በትግራይ አብይ ዓዲ የአረና አባላት ናችሁ በሚል እየታሰሩ መሆኑ ተሰማ

$
0
0

news
በዓብይ ዓዲ ከተማ ልዩ ስሙ ዓዲ ግዲ በተባለው አካባቢ የሚኖሩ ወገኖቻችን የአረና አባላት በመሆናቸው ብቻ እየታሰሩ መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል ሲል ደህሚት ዘገበ::

ምንጮቹን ጠቅሶ የዘገበው ደህሚት በትግራይ ማዕከላዊ ዞን ዓብይ ዓዲ ከተማ ልዩ ቦታው ዓዲ ግዲ በተባለው አካባቢ የሚኖሩ የአረና ድርጂት አባላት ምንም የሰሩት ወንጀል ሳይኖራቸው ከመኖሪያ ቤታቸው የስርዓቱ ተላላኪ ፖሊሶች ያለምንም ህጋዊ የፍርድ ቤት ትዕዛዝ እያሰሩ እየወሰዷቸው መሆኑን ለማወቅ ተችሏል::

መረጃው ጨምሮም ዮናስ ገብረአምላክ ተላ የተባለ የአረና ድርጅት አባል መጋቢት 18/ 2007 ዓ/ም ከጧቱ 2።30 ከመኖሪያ ቤቱ ፖሊሶች ትፈለጋለህ በማለት እንደወሰዱት የገለፀው መረጃው ይህን ህጋዊነት የሌለው ተግባራቸውን ይታዘቡ የነበሩ ቤተሰቦቹ ለምን ታስሩታላችሁ? ብለው በጠየቁበት ጊዜ ምርመራ ካደርግን በኋላ እንነግራችኃለን በማለት ወስደው በከተማዋ ቀበሌ 03 እንዳባዴራ በተባለው ፖሊስ ጣቢያ አስረውት እንደሚገኙ ለማወቅ ተችሏል፣

The post በትግራይ አብይ ዓዲ የአረና አባላት ናችሁ በሚል እየታሰሩ መሆኑ ተሰማ appeared first on Zehabesha Amharic.


Viewing all articles
Browse latest Browse all 8745

Trending Articles



<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>