Quantcast
Channel: ዘ-ሐበሻ – Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 8745 articles
Browse latest View live

አጋቾች በአስገድዶ መድፈር 4 ልጅ ያስወለዷት ኢትዮጵያዊት ወደ ሃገሯ ለመግባት በየመን እስር ቤት ትማቅቃለች

$
0
0

በግሩም ተ/ሃይማኖት (ጋዜጠኛ) – ከየመን

yemen በጤና ችግር ምክንያት ሁሌም መሄድ ባልችልም በሄድኩ ቁጥር ሁሌም አሳዛኝ ነገር ነው እየገጠመኝ ያለው፡፡ የበዓል እለት እስረኞችን ለማየት እና በዓልን ለእነሱ ምሳ ማብላት አስበን ኢሚግሬሸን እስር ቤት ሄድን፡፡ ካጋጠሙኝ አሰቃቂ ነገሮች አንዱ አራት ልጅ ይዛ ብርድ ላይ እያደረች ያለች ሴት አወራኋት፡፡ አማርኛ መናገር የማትቸል በመሆኑ አስተርጓሚ ማግኘትም ችግር ሆኖብናል፡፡ የመን ውስጥ ያሉት ህገ-ወጥ አጓጓዦች ስደተኞችን እያፈኑ አሰቃይተው ከቤተሰቦቻቸው ገንዘብ እንዲያስልኩ ያስደርጋሉ፡፡

እነዚህ አጋቾች ያገቷት አንዲት ኢትዮጵያዊት አንድ ልጅ ይዛ ነው ከሶማሊያ የተሻገረችው፡፡ ሶማሊያም አስገድዶ የመድፈር ሁኔታ ገጥሟት ወልዳ ነው የመን የገባችው፡፡ አሁን ደግሞ አግተው የያዟት ቦታ ሶስት ልጅ ወልዳለች፡፡ አራት በግዳጅ የመጡ ልጆች ይዛ ወደሀገር ልትገባ ነው፡፡
መጀመሪያ ልጆቹን እንዴት እንደያዘቻቸው ስላልገባኝ እና አራት መሆናቸውን አይቼ ስለሁኔታው ግርምት ጭሮብኝ ጠየኳት፡፡

‹‹..ባህሩን ስሻገር የያዘኩት እንዷን ልጅ ነበር፡፡ ሀረድ የሚባለው ቦታ የሚያግቱት አፋኞች ያዙን የደረሰብኝን ተወው፡፡ ለሶስት አመት ተኩል እዛው አፍነው አቆዩኝ፡፡ በዚህን ጊዜ ነው እነዚህን ሶስት ልጆች የወለድኩት፡፡ እንዲያውም ሁለቱ ልጆች በ11 ወር ነው የሚበላለጡት፡፡ አራስ ቤት እያለሁ ምንም እረፍት የለኝም ነበር፡፡…››

አንዷን ልጅ ሶማሊያ አግብተሽ ነው ወለድሻት? የኔ ጥያቄ ነበር፡፡
‹‹ እሷንም ሶማሊያ ውስጥ ተገድጄ በተደረገ ግንኙነት ነው የወለድኳት….›› ከዚህ በላይ መስማት አልቻልኩም፡፡ እንባም ተናነቀኝ….እስኪ የምትለውን ቪዲዮውን እዩት….


Sport: አርሰን ቬንገር እያደኗቸው ያሉት 5 ወጣት ተጫዋቾች

$
0
0

ከይርጋ አበበ

Arsene-wenger (1)አርሴን ቬንገር ቡድናቸው ማራኪ ጨዋታ ማሳየት ከቻለ ወይም የክለባቸው የፋይናንስ እንቅስቃሴ ጤናማ ከሆነ ለዋንጫ ደንታ የላቸውም እየተባሉ ይተቻሉ። ለክለባቸው ውጤታማነት የሚያስፈልጉ ተጫዋቾችን ለመግዛት አይደፍሩም። በተቃራኒው ክለባቸው ውስጥ የሚገኙትንና ደህና ዋጋ እንደሚያስገኙ የሚያስቧቸውን ተጫዋቾች ወደ ገበያ ሲያቀርቡ ዓይናቸውን አያሹም ይባላሉ። «ቬንገር ዘጠኝ ዓመት ከዋንጫ ጋር መለያየቱ የማያስጨንቀው ሰው ነው» እያሉ የስፖርት ተንታኞች ያብጠለጥሏቸዋል።

ሆኖም አርሴን ቬንገር ለሚሰነ ዝርባቸው ትችት መልስ ለመስጠት የሚመስልና እጅግ ውድ ዋጋ የወጣበትን ተጫዋች ዘንድሮ እንዲገዛ አድርገዋል። አሠልጣኙ ዘንድሮ ድንገት ሳይጠበቁ ጀርመናዊውን የኳስ ሊቅ ሜሱት ኦዚልን በ42 ነጥብ 5 ሚሊዮን ፓውንድ ወደ ክለባቸው አዘዋውረ ውታል። ለዚህ ጀርመናዊው ኮከብ ያወጡት ገንዘብ በፕሪሚየር ሊጉ ከተከናወኑ ዝውውሮች ሁሉ በትልቅነቱ ሁለተኛው ነው። ቬንገርም በድርጊታቸው ተኩራርተው «እኔ የክለቤን ደረጃ የሚመጥን ከሆነ ለምን መቶ ሚሊዮንስ አያወጣም» ሲሉ ተናገሩ።
ከኦዚል መፈረም በኋላ መነቃቃት ታይቶበት የነበረው ክለባቸው ግን ቀስ በቀስ መንሸራተት በመጀመሩ ክለባቸውን ይበልጥ ማጠናከር እንዳለባቸው አስበዋል። በተለይ በአንዳንድ ቦታዎች ላይ ያለባቸውን ክፍተት ለመድፈን ትኩረት ሰጥተው እየተንቀሳቀሱ መሆኑን በክለባቸው ኦፊሴላዊ ድረ-ገጽ አስታውቀዋል።

አርሴን ቬንገር በተለይ የግቡን መስመር ለማግኘት የተቸገረውን ኦሊቨር ዥሩን ለማገዝ የሚችል ሁነኛ ፊት አውራሪና ከጀርመናዊው መለሎ ፔር ሜርትሳከር ውጭ የሚተማመኑበት የኋላ መስመር ተጫዋች በቡድናቸው ውስጥ ባለመኖሩ እነዚህን ቦታዎች ለመድፈን እንደሚንቀሳቀሱ ይጠበቃል። ለመሆኑ የቬንገርን ዓይን ያንከራተቱት ከዋክብት እነማን ናቸው?

5. ላርስ ቤንደር

አርሰን ቬንገር በቡድናቸው ውስጥ ማቲው ፍላሚኒ በቦታው ቢኖርም ለተከላካዮቻቸው ተጨማሪ ሽፋን የሚሰጥላቸው የአማካይ መስመር ተጫዋች አስፈልጓቸዋል። ለዚህም ዓይናቸውን ያሳረፉበት በጀርመናዊው የባየር ሊቨርኩሰን ወጣት አማካይ ላርስ ቤንደር ላይ ነው። ቬንገር ለዚህ መስመር የሚሆነው ተጫዋች ምርጫ ላይ ላርስ ቤንደርን የመጀመሪያ ምርጫቸው ባያደርጉትም፤ እርሱንም ቢሆን ለማገኘት እስከመጨረሻው እንደሚታገሉ ይጠበቃል።

4. አሌክሳንደር ፓቶ

ኢማኑኤል አዲባዮርና ሮቢን ቫንፐርሲ አርሴናልን ከለቀቁ በኋላ አርሴን ቬንገር የክለባቸውን ደጋፊዎች አንጀት የሚያርስ አጥቂ በክለባቸው ማየት አልቻሉም። በቅርቡ የቫንፐርሲን ቦታ ይተካሉ ተብለው ወደ ክለቡ የተዘዋወሩት ጀርመናዊው ሉካስ ፖዶሊስኪና ፈረንሳዊው ኦሊቨር ዥሩ የታሰቡትን ያህል መሆን አልቻሉም።

በተለይ ሉካስ ፖዶሊስኪ በተደጋጋሚ ጉዳት የሚያጋጥመው ከመሆኑ አኳያ ኦሊቨር ዥሩን በብቸኝነት እንዲጠቀሙ ተገድደዋል። ሆኖም አርሰን ቬንገር ከሀገራቸው ልጅ የሚፈልጉትን አገልግሎት ማግኘት እንዳልቻሉ ፍንጮች እየተነገረ ይገኛል። ለዚህም ይመስላል ለብራዚላዊው አሌክሳንደር ፓቶ ዝውውር በራቸውን ክፍት አድርገው የልጁን ወደ ለንደን ማምራት በጉጉት የሚጠባበቁት።

የቀድሞው የኤሲ ሚላን አጥቂ በአሁኑ ክለቡ ኮሮንቲያስ እያሳየ ያለውን ብቃት የተመለከቱት የአርሴናል ጎረቤቶች ቶተንሃም ሆትስፐርሶችም የልጁ ፈላጊ ሆነው መቅረባቸው ለአርሰን ቬንገር ዳገት ሳይሆንባቸው አይቀርም እየተባለ ነው።
የተጫዋቹን የአውሮፓ ኑሮ እንደገና ለማስጀመር የጓጉት አርሰን ቬንገር ግን ፈተናውን ተቋቁመው የክለባቸውን ማሊያ ያለብሱታል የሚሉ አስተያየቶችም መነገር ከጀመሩ ቆይተዋል።

3. ጁሊያን ድራክስለር

ወጣቱ የሻልካ 04 አማካይ መስመር ተጫዋች ድራክስለር ወደ እንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ተዘዋውሮ መጫወት ይፈልጋል።። አርሴናል ደግሞ የድራክስለር ፈላጊ መሆኑን ቬንገር ፍንጭ ሰጥተዋል። አስተያየት ሰጭዎች ደግሞ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ስፔናውያንና ፈረንሳውያን ተጫዋቾችን «በቃኝ» ያሉ የሚመስሉት አርሰን ቬንገር ፊታቸውን ወደ ጀርመናውያን ማዞራቸውን ተመልክተው የድራክስለር ማረፊያ የጊዜ ጉዳይ ካልሆነ ፍላይ ኤምሬትስ መሆኑ አይቀርም እያሉ ነው።
የሻልካው መለሎ ተጫዋች ድራክስለር ቬንገር የሚፈልጉት ዓይነት ተጫዋች መሆኑና ወጣትነቱ ወደ ሰሜን ለንደን የሚያደርገው ጉዞ እንደሚሳካ የስፖርት ቤተሰቡ ከፍተኛ ግምት የሰጠው ትኩረት መሆኑን ዘገባው ጨምሮ ገልጿል።

2. አይካይ ጎንዶጋን

የአርሰን ቬንገር የአማካይ መስመር ላይ ተመራጭ ተጫዋች ቢኖር ይህ የ23 ዓመት ጀርመናዊ ወጣት ነው። ቬንገር በአማካይ ተከላካይ ቦታ ከማቲው ፍላሚኒ ውጭ የክለባቸውን ማሊያ ለብሶ ሲጫወት ሊያዩት የሚፈልጉት ይህን የቦሩሲያ ዶርትሞንድ ተጫዋች ነው። ተጫዋቹን ለማግኘትም የሚከፈለውን ሁሉ ለመክፈል ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ጎንዶጋን በማንቸስተር ዩናይትድ ሳይቀር ፈላጊው በዝቷል። ተጫዋቹን በእጃቸው ለማስገባት ከባድ ፈተና እንደሚጠብቃቸው የተረዱት አርሴን ቬንገር ልጁን ለማማለል በክለባቸው ያሉትን ስድስት ጀርመናውያን እንደሚጠቀሙ ሲገለጽ፣ ለእናት ክለቡ ደግሞ አሳማኝ የዝውውር ሂሳብ ለመክፈል የሚያግዳቸው ምንም ምክንያት እንደሌለ በልበ ሙሉነት ይናገራሉ።
አርሰን ቬንገር በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የመጫወት ፍላጎቱ ከፍተኛ የሆነውን ጎንዶጋንን ወደ ክለባቸው አዘዋውረው ከሀገሩ ልጆች ጋር ማጫወት ይችሉ እንደሆነ ወደፊት የምናየው ይሆናል።

Karim-Benzema-Hairstyles-20131. ካሪም ቤንዜማ

ካሪም ቤንዜማ ፈረንሳዊ ነው። ይህ የሪያል ማድሪድ ግብ አነፍናፊ ተጫዋች የማይፈልገው ክለብ በምድረ አውሮፓ የለም። ቬንገርም የሀገራቸውን ልጅ በማድሪድ ያለውን ቆይታ እንዳልወደደው ተረድተዋል። በማድሪድ ያለው ቆይታ ቀስ በቀስ እየተነቃነቀ መምጣቱን ተከትሎ ተጫዋቹ የቤርናባውን መውጫ በሮች እየተመለከተ ይገኛል። አርሰን ቬንገርም ከፍተኛ የዝውውር ሂሳብ መድበው እየተንቀሳቀሱ መሆናቸውን የተለያዩ የመረጃ ምንጮች እየዘገቡት ነው።
የኦሊቨር ዥሩ ግብ የማግባት ችግር እየተባባሰ መሄድ ተስፋ ያስቆረጣቸው ቬንገር ችግራቸውን እንዲያቃልላቸው የሀገራቸውን ልጅ ወደ ኢምሬትስ ማዘዋወር የመጀመሪያ ግባቸው ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።

ስደተኞችን እንደ መንግስት “የገቢ ርዕስ”ከማየት አባዜ ባሻገር –ከሙሼ ሰሙ

$
0
0

ከሙሼ ሰሙ

mushe semu በመጀመርያዎቹ ሃያኛው መቶ ክፍለ ዘመን ማብቂያ ላይ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ መብቶችን አስመልክቶ ባረቀቀው ደንብ አንቀጽ 18 ላይ ስደተኞችን ወይም መጤዎችን ስለማፈናቀል ድንጋጌ አውጥቶ ነበር፡፡ ድንጋጌው እንደሚያትተው ከሆነ መጠነ ሰፊ በሆነ ደረጃ፣ ያለማመዛዘን፣ ልዩነት ሳያደርግ ሃይል በታከለበት ሁኔታ መጤዎችንና ስደተኞችን ማፈናቀል በሰብአዊ ፍጡር ላይ እንደተሰራ ከባድ ወንጀል ተቆጥሮ አባል ሃገራት በድርጊቱ ፈጻሚ መንግስታት ላይ የጋራ አቋም እንዲወስዱ ስምምነታቸውን የሚጠይቅ ነበር፡፡

ይህ የተባበሩት መንግስታት ደንብ የሁሉንም ሃገራት ይሁንታ በተለያየ ምክንያት ማግኝት ባይችልም፤ በዓለማችን ላይ ስደተኛ የሌለው ሃገር ከቶም ሊገኝ ስለማይችል በመርህ ደረጃ ሁሉም መንግስታት የሚስማሙበት ጉዳይ እንደሆነ ጥርጥር የለውም፡፡ የዓለማችን የመጎጎዣ ስርዓት እጅግ በመቀልጠፉና በመዘመኑ፣ የጉዞ ውጣ ውረዳችን ከቀናት ወደ ሰዓታት በመቀነሱ፣ መረጃዎች በስፋትና በጥልቀት በመናኘታቸው ምክንያት ዓለማችን ከመቼውም ጊዜ በላይ ጠባለች፡፡ በዚህም ምክንያት የተሻለ ኢኮኖሚያዊም ሆነ ፖለቲካዊ ሕይወት ፍለጋ ቁጥራቸው ይብዛም ይነስ ዜጎቹ ለስደት የማይዳረጉበት ሃገር የለም፡፡ እንግሊዞች ሁለተኛ ሃገራችን ወደሚሏት አሜሪካ ተሰደው፣ ይሰራሉ፡፡ እስራኤሎች፣ የሳኡዲ አረቢያና የአውሮፓ ዜጎች ሳይቀሩ በየሃገሩ በመኖር ሕይወታቸውን ለማቃናት ብሎም ለሃገራቸው ለመትረፍና ከግፍና መከራ ለመሸሽ ይሰደዳሉ፡፡ ዛሬ ላይ ሲወሳ እውነት ሊመስል ባይችልም፤ አብዛኛዎቹ የመካከለኛው ምስራቅ ሃገራት ነዋሪዎች ሕይወታቸውን የሚገፉት በስደተኛነት እንደነበረ እጅግ ቢርቅ ከአንድ ትውልድ የማይዘል ሃቅ መሆኑን መረዳት ያሻል፡፡
1604714_600436510028405_2111798139_n
መጠነ ሰፊ ማፈናቀል (Mass Deportation) በዓለምችን ላይ አዲስ ክስትት አይደለም፡፡ የሳሳንያው ስረወ መንግስትና የፐርዢያው ንጉስ ኮስራው/ሽራው/ 292,000 ባርያዎችንና ምርኮኞችን በጦርነት ካሸነፋት ሃገር አፈናቅሏል፡፡ አሜሪካኖች በየዓመቱ በአስር ሺህ የሚቆጠሩ የላቲን ዜግነት ያላቸውን ስደተኞች አስገዳጅነት በተቀላቀለበት መንገድ ወደ ትውልድ ሃገራቸው ታባርራለች፡፡ እስራኤሎች ቁጥር ስፍር የሌላቸው ፈለስጢናውያንን ከቤታቸውና ከቀያቸው ሲያፈናቅሉና ሲያሰድዱ ዘመናት ተቆጥሯል፡፡ እስከዛሬም ድረስ ፈለስጢናውያን ሃገር አልባ እንደሆኑ ይታወቃል፡፡
በዓለም ታሪክ ከፈለስጢኖች ቀጥሎ በመጠነ ሰፊነቱና በአሰቃቂነቱ በተለይ ተጠቃሽ የሆነው ማሰደደና ማፈናቀል ቱርኮች በአርመኖች ላይ እ.ኤ.አ ከ1915 ጀምሮ በሶስት ተከታታይ ሂደት የፈጸሙት ማፈናቀል ነበር፡፡ በአንደኛው ዓለም ጦርነት ከጀርመንና ከኦስትሮ ሃንጌሪያውያን ጋር ያበረችው ኦቶማን ቱርክ እ.ኤ.አ በ1922 የደረሰባት አሳፋሪ ሽንፈትና ውድቀት ከአንድ ሚሊያን ለሚበልጡ አርመኖች ከቀያቸውና ከመንደራቸው ለመነቀልና ሃገር አላባ ሆነው የስደተኛ ሕይወት እንዲገፉ ምክንያት ሆኗል፡፡ በሃንጌሪ፣ በሎክስመበርግና በቤልጅየም የተፈጸሙ በርካታ ማሰደዶችና ማፈናቀሎች ሌሎች ተጠቃሽ ምሳሌዎች ናቸው፡፡

ሕጋዊ በሆነ መንገድም ሆነ ሕጋዊ ባልሆነ መንገድ ወደ አንድ ሃገር የሚገቡ መጤዎችንና ስደተኞችን ወደ መጡበት ሃገር ማሳደድ ወይም ማፈናቀል (Mass Deportation) የሉዓላዊ ሃገራት ወይም መንግስታት የማይገሰስ መብት ነው፡፡ ከሞራል ሙግት ውጭ ምክንያት ሊጠየቅበት የሚችል አይደለም፡፡ ይህንን ስንል ግን ዜጎቹ የተሰደዱበት ሃገር መንግስት በዜጎቹ መሳደድና መፈናቀል ምክንያት የተከሰተውንና የሚከሰተውን ኢኮኖሚያና ማህበራዊ ቀውስ አስመልክቶ ሊነሳ የሚገባው ጥያቄ የለም ማለት አይደለም፡፡ አጠቃላይ የካሳ ጥያቄ አንዱ ነው፡፡ በተለይ ትኩረት ከሚሰጣቸው ጉዳዮች ውስጥ ቅድሚ የሚሰጠው ስደተኞቹ ከውርደትና ከመብት ረገጣ ከለላ የሚያገኙበትን ሁኔታ ማምቻቸት አንዱ ሲሆን ሌላው ተሰዳጆቹ ሃብት ንብረታቸውን ሳይነጠቅ እንዲሰናበቱ ሁኔታዎችን ማመቻቸት ነው፡፡ ምክንያታዊ የሆነ መንግስት የዜጎቹ ውርደት የሃገር ውርደት መሆኑ ሊነገረው የሚገባ ጉዳይ አይደለም፡፡ ሃገር ያለ ዜጎቹ የሚዋረድበት ሌላ መገለጫ የለውም፡፡ ከዜጎች ውጭ ሃገር ማለት ድንጋይ፣ ተራራ ወይም መሬትና ወንዝ… ነው፡፡

በኢትዮጵያዊያን ስደተኖች ቁጥር ዙርያ ተጨባጭ መረጃ ማቅረብ ባይቻልም በዓለም ላይ በኢኮኖሚያዊም ሆነ ፖለቲካዊ ምክንያቶች በየሃገሩ የተበተኑ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች ቁጥራቸው በሚሊዮኖች እንደሚቆጠር ይነገራል፡፡ ምናልባትም
ኢትዮጵያዊ ስደተኛ የሌለበት ሃገር ማግኝት አዳጋች እንደሆነም በርካታ ለስራም በግል የሚጓዙ ኢትዮጵያዊያን ይናገራሉ፡፡ በተቃራኒው ግን ስደት እንደዚህ ርካሽ የሆነባት ኢትዮጵያ ደግሞ ለስደት የተዳረጉ ዜጎቿን እውቅና በመንሳት፣ ጥበቃናና ከለላ በመነፈገ አቻ የማይገኛላት ሃገር ነች፡፡ ዜጎቻችን ለስደት የዳረገው ኢኮኖሚያዊም ሆነ ፖለቲካዊ ወይም የሰብአዊ መብት ጥሰት መንስኤ የሆኑ መሪዎቻችን በስደተኛ ዜጎቻችን ላይ የሚደርሱ ግፎችን አይቶተው እንዳለዩ ሰምተው እንዳልሰሙ መሆን መገለጫቸው ነው፡፡ ጫጫታው ገፋ ሲል ደግሞ የእብድ ገላጋይ ይመስል በስደተኞቹ ላይ ስም እየለጠፉ ለጥቃት ማጋለጥ ከአንዴም ሁለቴ የታዘብነው ፈተና ነው፡፡

በገዢዎቻችን ታሪክ ስደተኞች በመካድ፣ ከለላና ድጋፍ በመንፈግ በተለይ ኢህአዴግን የሚደርስበት የለም፡፡ ኢህአዴግ ከሽግግሩ ጊዜ ጀምሮ በኤርትራ መሬት በጦርነቱ ተሸንፈው ወደ የመን፣ ሱዳን ሊቢያና የመሳሰሉት ሃገራት የተሰደዱ ኢትዮጵያዊን ወታደሮችን እውቅና በመንሳት በርካታ ግፍና መከራን እንዲቀበሉ አድርጓል፡፡ ከጦር ቀጠናቸው ውጭ ኤርትራን የማያውቁ በርካታ ወታደሮቻችን በኤርትራ በረሃዎች ላይ ሰብሳቢና ተመልካች ማጣታቸው ሳይንስ ከሰው ፍጠሩ ያልተወለዱ ይመስል የቂም በቀል መወጣጫ ሲሆኑ ኢህአዴግ “ሃይ፣ ጉዳዩ በዓለም አቀፍ ሕግን ስርዓት ይዳኝ” ማለት ስላልፈለገ ዜጎቻችን የትም ባክው ቀርተዋል፡፡ ይበልጥ የሚያስደንቀው ደግሞ ዜጎቻችን “ለወረራ የዘመቱ የደርግ ወታደሮች” ናቸው በማለት የእብድ ገላጋይ ዱላውን በማቀበሉ ወታደሮቹ አይከፍሉ ዋጋ እንዲከፍሉ መንስኤም ሆኖ ነበር፡፡ ዛሬ የተረሳ ቢመስለም በኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ታሪክ በአስከፊነታቸው ከሚብጠለጠሉት አሳዛኝ ግፎች ባልተናነሰ ደረጃ ጠባሳውን ጥሎ ያለፈ ሂደት ነበር፡፡

ደርግ በሽብር እየታገዘ እንደ እርድ ከብት ከእርሻ መሬታቸውና ከየትምህርት ቤቱ ያነዳቸው የድሃ አርሶ አደርና የከተሜ ልጆች በኤርትራ መሬት ላይ ለሽንፈት መዳረጋቸው ሳያንሰቸው ተጨማሪ ግፍና መከራ ይቀበሉ ዘንድ ኢህአዴጎች ከሻቢያ ጋር ሊመሳጠርባቸውም ባልተገባ እንደነበር ዛሬ ላይ ድርጅቱ የሚስተው አይመስለኝም፡፡ ጥርሳቸው እየተነቀለ፣ ንብረታቸውን እያተዘረፉ እርቃናቸውን ወደ መጡበት እንዲመለሱ በመደረጋቸው ቁትር ስፍር የሌላቸው ዜጎች በየበርሃውና ጥሻው ውስጥ ወድቀው ቀርተዋል፡፡ በኮንቴይነር ውስጥ እየታሸጉ በባርነት ጉልበታቸውን የተበዘበዙ ወታደሮች ቁጥር ማንም ሊገምተው ከሚችለው በላይ እንደሆነ የሚዘነጋ አይደለም፡፡
saudi
ጊዜ ማለፉ እንደማቀር የሚውቁ አብው ሲተርቱ “ለሕሊናህ መፈረድ ቢያቅት ለጊዜ ፈረድ ይላሉ፡፡ ዛሬ ላይ ያ ሁሉ አልፎ ለደረሰው ውጥንቅጥ ሁሉ መንስኤ የነበሩት አዝማች የደርግ ባለስልጣናት “ይቅርታን አግኝተው” መጽሐፍ ለመድረስና በኢህአዴግ መድረኮች እያተጋበዙ ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር ለመወያየትና ኢህአዴግን ለማማከር በቅተዋል፡፡ በተቃራኒው ደግሞ እነዚህ ወጣቶች ባልቀሰቀሱትና ባልፈቀዱት ጦርነቱ ውስጥ ተማግደዋል፡፡ ብዙዎቹም ከሞት መንጋጋ ማምለጥ ቢችሉም “የደርግ ሰራዊት” ነበሩ በሚል ሰበብ ብቻ በዓለም አቀፍ ሕግ የተደነገገውንና ለጦር ምርኮኛ የሚገባውን ጥበቃና ከለላ ሳያገኙ በመቅረታቸው የቂም በቀል መወጣጫ ለመሆን ሆነዋል፡፡ ኢህአዴግ በወቅቱ ለሕሊናም ሆነ ለጊዜ ባለመፍረዱ ቢያንስ አዝማቾቻቸው በይቅርታ ሰበብ የተቋዳሱትን የእፎይታ ሕይወት እንኳን ለመቋደስ አልታደሉም፡፡ ከጥፋታቸውም ሆነ ከሕሊና ጸጸት ይድኑ ዘንድ እድል አላገኙም፡፡
ምክንያታቸው ሊዋጥልኝ ባይችልም ኢህአዴግን ለመከላከል ሲባል ብቻ ጉዳዮችን በቀላሉ ከማያጣፉት የኢህአዴግ ካድሬዎች የሚያነሱ ኢህአዴግ መንግስት አልነበረም የሚሉ መከራከርያዎች እንዳሉ እገምታለሁ፡፡ ችግሩ የሚነሳው ኢህአዴግ መንግስት ለመሆን መደላድሉን ያላመቻቸና እርካቡን ያልተቆናጠጠ በመሆኑ ነው አልነበረም፡፡ ችግሩ የርዕዮተ ዓለምና የአመለካከት ነው፡፡ ዛሬም የሳኡዲውን ሌሎችንም ስደተኞችን በሚመለከት ያለው ግንዛቤ ይህው ነው፡፡ ኢህአዴግ ፍላጎቱ ቢኖረው ኖሮ መንግስት መሆን ሆነ አለመሆኑ ሊገድበው ባልተገባ ነበር፡፡ ተደማጭነቱ ቢቀር እንኳ፤ ቢያንስ አቤቱታ በማሰማት ጉዳዩ እንዲታሰብብትና አጀንዳ እንዲሆን ግፊት ለማድረግ ከግለሰብ የላቀ አቅም ነበረው፡፡ ደርግ በትጥቅ ትግል ዘመን በሕዝቦች ላይ በሚያካሂደው ማሳደድ ምክንያት ቀላል የማይባል ህዝብን እየተቀበለና እያገዘ እጅግ አስከፊ ስደቶችንና ውጣ ውረዶችን ከሕዝብ ጋር ያሳለፈ ድርጅት ውሎ ሳይድር በዚህ ዓይነት ድርጊት ውስጥ እጁ ሲገኝ መመልከት ለትንታኔ የሚከብድ መሆኑ አጠራጣሪ አይደለም፡፡

በዚህ ጉዳይ የኢህአዴግ ሁነኛ ባሕሪ ለመደገም ተጨማሪ አስርት ዓመታትን መጠበቅ አላስፈለገም ነበር፡፡ “ያዳቆነ ሰይጣን ሳያቀስ አይለቅም” እንዲሉ በ1990 ዓ.ም ያልተጠበቀው የኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ሲፈነዳ ነገሮች ይበልጥ ፍንትው ብለው ወጡ፡፡ የደርግ ወታደሮች በሚል ስም ገና ከጅምሩ ስደተኞችን ከለላ በመንፈግና እውቅና በመንሳት አዲስ ታሪክ ያሟሸው
ኢህአዴግ፣ በመቀጠል ሚናውን ከተመልካችነት ወደ ስደተኛ አባራሪነት (Mass Deportion) አሳድጎ ብቅ አለ፡፡ ለዝንተ ዓለም ኢትዮጵያ ውስጥ በመኖር ኢትዮጵያዊነታቸውን በሕግ የተቀዳጁ፤ ነገር ግን በደም ኤርትራዊ የነበሩ አባወራ፣ ሴት፣ ሕጻናት ወይም ሽማግሌ ሳይመርጥ በጅምላ በማፈስ እስር ቤት እያጎረ ሃብት ንብረታቸውን ለመሰብሰብ እንኳን በቂ ጊዜ ሳያገኙ ከኢትዮጵያ አባሯል፡፡ ኢህአዴግ በኤርትራዊያን ላይ ኢ-ሰብአዊ ድርጊት ሲፈጸም ሂደቱን ለመቀልበስም ያልቻለው ወይም ያልፈለገው በሌላ ምክንያት ሳይሆን እንደዚህ ዓይነት የማሳደድ ድርጊቶች በሌሎች ላይ ሲፈጸም ዝምታን የመረጠ ድርጅት በመሆኑ ነበር፡፡
ዛሬ ላይ ኢህአዴግ በስደተኞች ላይ የሚያሳየው ፍጹም የሆነ ቸልተኝነት መንስኤው ገጽታ ያበላሻሉ ከሚል ጥቅል ድምዳሜ እንደሚነሳ እገምታለሁ፡፡ በተለይ ደግሞ ወደ አረብ ሃገርት በድህነት ምክንያት ስራ ፍለጋ ለሚሰደዱ ዜጎች እውቅና መስጠት የልማት አጀንዳዬንና ያስመዘገብኩትን ኢኮኖሚያዊ እድገት ያጨልማል፣ በስራ ፈጠራና በልማት ተጠምጄ እያለሁ እነሱ በስደት በመጠመድ የችግሩን ስፋትና ጥልቀት ገሃድ ያወጣሉ የሚል ድብቅ ( የማይነገር) ሰበብ ስላለው እንደሆነ መገመት አያዳግትም፡፡ ኢህአዴግ ከነባራዊ ሁኔታው ተነስቶ ስደተኞቹ ከችግሩ ጥልቀትና ስፋት የተነሳ ከመሰደድ እንደማይቦዝኑ ያውቃል፡፡ በዚህም ምክንያት ድህነትን ከስሩ አድርቄዋለሁ ማለትና በድህንት ሰበብ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ተሰደዋል ማለት ለፕሮፓጋንዳ አያመችም፡፡ ያለው አማራጭ ስደተኞቹ በሚሊየን ቢቆጠሩም በሰላሳ ሺዎች እየገደቡ እንደ ሳኡዲዎቹ ጉዳዩ ገንፍሎ ገሃድ እስኪወጣ ድረስ እውቅና መንሳት ብቻ ነው፡፡

በመካከለኛው ምስራቅ በተለይ በሳኡዲ አረቢያ፣ በኩዌትና በሊባኖስ በሌሎቹም ሃገራት የዜጎቻችን የአካል ክፍሎች (Organs) ባልሰለጠኑ የመንደር ሃኪሞች ስለት እየተሞሸለቀ ለቱጃር አረቦች ሲቸበቸቡ ኢህአዴግን ጨምሮ ሁላችንም ለመታዘብ ችለናል፡፡ ዜጎቻችን ከህንጻ ላይ እየተወረሩ ተነኳኩተው በቃሬዛ አሊያም ከተሸከርካሪ ወንበር ጋር ተቆራኝተው ያለ ካሳ አንደ አሮጌ እቃ ሲወረወሩ ተመልክተናል፡፡ በየመን፣ በሱማሌና በሊቢያ በረሃዎች ዜጎቻችን አይዋረዱ ውርደት ሲዋረዱና መሸሺያና መከለያ አጥተው ጦርነት ላይ እንደተማረኩ የዝሙት ባርያዎች (Sex Selave) በሰንሰለት እየታሰሩ የዝሙት ፍላጎት ማርኪያ ሆነዋል፡፡ ወንዶቹ በባርነት ሲያገለግሉ የተቀረጹ ዶክመንትሪ ፊልሞችን በዓለም ዓቀፍ መገናኛ ብዙሃን አማካኝነት በጋራ ተመልክተናል፡፡ በደርግ ስርዓት ጦርነትና የመልካም አስተዳደር እጦት ፤ የተቃና የኢኮኖሚ ፖሊሲ አለመኖርን የመብት ረገጣ ባደረሱቡን ፈተና ምክንያት ሰቆቃችን፣ እርዛታችንና ልመናችን ዓለምን እንዳላሰለቸ ሁሉ ዛሬ ደግሞ ስደታችንና የስደተኝነት ታሪካችን መንግስታዊ ከለላና ድጋፍ በመነፈጉ የዓለም መገናኛ ብዙሃን መጠቋቆሚያና መዘባበቻ እንድንሆን አድርጎናል፡፡

በዚህ መልኩ በኢትዮጵያውያን ስደተኞች ላይ የሚደርሰው የተናጠል ኢ-ሰብአዊ ድርጊት ተባብሶና ገዝፎ ጭካኔ ወደ ተሞላበት መጠነ ሰፊ ማፈናቀልና ማሰደደ ሲሸጋገር ኢህአዴግ የጉዳዩ ባለቤት መሆኑን መቀበል ባለመፈለጉ እራሱን በታዛቢነት አስቀምጦ መክረሙ ቀጣዩ አሳዛኝ ትዕይንት ነበር፡፡ ኢህአዴግ በተለይ በስደተኛች ጉዳይ ዘንድሮም እንዳልተሻሻለ የሚያረጋግጠው፤ በኤርትራ መሬት ላይ በስደት ሲባክኑ የነበሩ ወታደሮችን “ወራሪ የደርግ ወታደር” ማለቱ ለጥቃት በር የከፈተ መሆኑን ዘንግቶ፤ ዛሬ ላይ ደግሞ ከሳኡዲ በግፍ ለተፈናቀሉ ዜጎቻችንን ሌላ ተቀጻላ ስም ለመስጠት አለመቦዘኑ ነበር፡፡ ኢህአዴግ ግፉ እንደተጀመረ ሰሞን እራሱን ከደሙ ንጹሕ ለማድረግ ያቀደ በመሆኑ “ሕገ ወጥ ስደተኞች” የሚል ተቀጽላ በመስጠት ለመከራቸውና ውጣ ወረዳቸው ጀርባውን መስጠቱ ይታወሳል፡፡

የእስልምና ሃይማኖት ተከታይ ስደተኞችን በመቀበሏ ትልቅ ስፍራ የሚሰጣትን የኢትዮጵያ ሃገራችን ስደተኞች የእስልምና መሰረት በሆነችው በሳኡዲ አረቢያ አምባገንን ፖሊሶች፣ ደህንነትና ሰራዊት አማካኝነት በጠራራ ጸሃይና በዓለም አቀፍ መገናኝ ብዙሃን ካሜራ ፊት አስነዋሪ ድርጊት ፈጽመውብናል፡፡ ሰብአዊ ክባራችንን አዋርደዋል፡፡ ዜጎቻችንን ገድለዋል፡፡ ሴቶቻችንን ደፍረዋል፡፡ ሃገራዊ ክብራችንን ተፈታትነዋል፡፡ ይህ ሁሉ ድርጊት በሳኡዲ አረቢያ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኢምባሲ ደጃፍ ስር መፈጸሙ ሌላ አሳፋሪ ጉዳይ ነው፡፡ ኢምባሲው በሩን ከፍቶ የዜጎቻችንን መከራ ለመቋደስ መድፈር ቢያቅተው አንኳን ብሶታቸወን ለመዳመጥ በሩን ገርበብ አድርጎ መታዘብ አልቻለም፡፡

ይልቁንም የኢምባሲው አባላት በዘመናዊ ፎቴ ላይ ተቀምጠው የዜጎቻችንን ግፉ በዲሽ እንደ ፊልም እየተመለከቱ መመሪያ ከመጠበቅ ያለፈ ሚና አልነበራቸውም፡፡ ኢምባሲው የስደተኞቹን ፓስፖርት ለማደስ የአባይ ቦንድ መዋጮ ካልከፈላችሁ በማለት ቁም ስቅል ሲያሳያቸው ከርሞ ከሰባት ወር ውጣ ውረድ በኃላ ፓስፓርታቸውን ሳያድስና ሕጋዊነታቸውን ሳያረጋግጥ በመቅረቱ ያ ሁሉ መዓት በዜጎቻችን ላይ ሊወርድ ችሏል፡፡ ይህ የተለመደው የኢህአዴግ ችግር መገለጫ በመሆኑ

ለዚህ የዜጎቻችን ፈተና የተጠየቀም ሆነ ኃላፊነት የወሰደ የለም፡፡ ሕዝባዊ ነኝ ለሚል ድርጅት በግብር ከፋይ ሕዝብ ወጭ ለሚያለግሉና ለሕዝብ ለማይቆሙ ጥቂት የኢምባሲ ሰራተኞችን ከላላ መሆኑና ከሕዝብ ቁጣ መሸሸጉ እንቆቅልሽ ከመሆን ሊዘል አይችልም፡፡

እርግጥ ነው የሳዑዲ መንግስት የስራ ፈቃድ የሌላቸውን ቀርቶ ፈቃድ ያላቸውን ስደተኞችም ቢሆኑ ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ተገቢውን ካሳ ከፍሎና ንብረታቸውን እንዲሰበስቡ አደርጎ ባዘጋጀላቸው ትርንስፓርት ግፍና መንገላታት ሳይደርስባቸው ማሰናበት ይችላል፡፡ የሳኡዲ መንግስት ይህንን አድርጎ ቢሆን ኖሮ ጥያቂ ሊነሳበት ባልተገባ ነበር፡፡ ነገር ግን፤ ከላይ ለማንሳት እንደሞከርኩት የተፈጸመው ግፉ መስመሩን የሳተ እንደመሆኑ መጠን ኢህአዴግ ለስደተኞቹ ተቀጸላ ስም እየሰጠና ቁጥራቸውን እያወራረደ ለጥቃት ከማጋለጥና ከደሙ ንጹሕ ለመምስል ከመትጋት ይልቅ፤ በቂ ምክንያት ስለነበረው ቢያንስ ማፈናቀሉንና ማሰደዱን ማስቆም ባይችል እንኳ መፍትሔ ሊያገኙ በሚገባቸው በርካታ የዜጎነት ጉዳዮች ዙርያ ጥላ ከለላ በመሆኑ በሕጋዊ መድረኮች ሁሉ መሟገት ነበረበት የሚል ጽኑ እምነት አለኝ፡፡ ለዚህም ቢያንስ ቢያንስ እነዚህን መሰረታዊ ጉዳዮች ማከናወን ነበረበት፡፡

የመጀመርያውና ወሳኙ ጉዳይ ለዜጎቹ እውቅና መስጠትና ለክብር ዘብ መቆም ነበር፡፡ ሳኡዲዎች በዚህ ደረጃ ዜጎቻችንን ሰብአዊ ክብራቸውን እንዳያዋርዱ ለመከላከል ኢህአዴግ ከሳኡዲ መንግሰት ጋር በማንኛውንም ጉዳይ ጋር ለመነጋገር ዝግጁነቱን ቀድሞ በመግለጽ በዜጎቹ ጉዳይ ሃላፊነት የሚሰማውና የዜጎቹን ክብር ለመታደግ ግዴታውንና ኃላፊነቱን የሚወጣ መንግስት መሆኑን ማረጋገጥ ነበረበት፡፡ ስደተኞቹ ለዚህ ሁሉ ጥቃት ለመጋለጥ የቻለሁትም ይህ ባለመሆኑና ባለቤት፣ ተጠሪም ሆነ ወቃሽ የሌላቸው ተደርገው በመወሰዳቸው እንደሆነ መረዳት ይቻላል፡፡ ስደተኞች ኑሮ ስለደላቸውና ስለተረፋቸው እንዳልተሰደዱ ይታወቃል፡፡ በርካታዎቹ መሬታቸው ምርት መስጠት አቅቶት በማረጡ ምክንያት ሌላ የሕይወት መንገድን የመረጡ ናቸው፡፡ ይህንንም የስደት ሕይወት ለማሳካት ሃብት ንብረታቸውን ሽጠው ወይም ተበድረውና ተለቅተው ጉዞ የጀመሩ ናቸው፡፡ ፊታቸውን ወደ ሃገር ቤት አዙረው ለመመለስም መጀመርያ እዳ መክፈል የሚችሉ መሆናቸውን ማረጋገጥ ነበረባቸው፡፡ ቀጥሎም እዳቸውን መክፈል ቢችሉ ዳግም ወደ ችጋርና ሰቆቃ ሕይወት ላለመመለስ ትንሽም ብትሆን ጥሪት መቋጠር ነነበረባቸው፡፡ አብዛኛዎቹ ስደተኞቹ ይህንን ማቃናት ባለመቻላቸው ተይዘው ከመመለስ ይልቅ እራሳቸውን ከሕግ በመሰወር ለመደበቅና ለመሸሽ መሞከራቸው የግድ ነበር፡፡ ይህንን ውስብስብ ችግር ለሳኡዲ መንግሰት፣ የደህንነትና የፖሊስ ተቋማት ቀድሞ በማስረዳት በሕገ ወጥነት ተፈርጀው ግፍ እንዳይፈጸምባቸው መከላከል ይቻል ነበር ፡፡

ሁለተኛው አነሰም በዛ የጉልበታቸውን ዋጋ የማስከበር ጉዳይ ነው፡፡ በመጀመርያውንም ዜጎቻችን የተሰደዱት ሃብት ለማፋራት አቅደው በመሆኑ ሃብታቸውን የማሰባሰብ ጉዳይ ኢህአዴግ ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ጉዳይ ነበር፡፡ እነዚህ ስደተኞች በሳኡዲ ኢኮኖሚ ውስጥ ርካሽ ጉልበታቸውን በመሸጥ ቀላል የማይባል አስተዋጽኦ እንደሚኖራቸው መገመት ይቻላል፡፡ በተለይ ደግሞ ማሰደዱ ሃይልና ግፍ የተቀላቀለበት በዘመቻ የተደረገ እንደመሆኑ መጠን ብዙዎቹ ያፈሯትን ጥሪት ለመሰብሰብና ደሞዛቸውን ለመቀበል እንኳን ፋታ አላገኙም፡፡ ስደተኞቹ ወደ ሃገር ተመልሰዋል፡፡ ሃብት ንብረታቸው ግን የትም ተዝረክርኮ ይገኛል፡፡ ሃብት ንብረታቸውን የማሰብሰብ ጉዳይ አሁንም ያልተፈታ ጥያቄ በመሆኑ ኢህአዴግ ዛሬም ላይ ሆኖ ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ጉዳይ ነው፡፡ ኢህአዴግ ዓለም አቀፍ ግፊትና ተጽእኖ ፈጣሪ ተቋማትንና መንግስታትን መሰረት በማድረግ የሳኡዲን መንግስት ወደ ድርድር መውሰድ አለበት፡፡ ይህ ካልሆነም ጉዳይን ወደ ዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት በመውሰድ ዜጎቻችን ተገቢውን ካሳ አንዲያገኙ ክስ በመመስረት ለዜጎቹ ጉዳይ ተጠሪና መንግስት መሆኑን በተግባር ማሳየት አለበት፡፡ ይህ እንቅስቃሴ ለስደተኞቹ ከሚያስገኘው ጥቅም በላይ ወደፊት ሌሎች መንግስታት በኢትዮጵያዊያን ላይ እንዲዚህ ዓይነት ድፍረት የተሞላበት ኢ-ሰብአዊ ድርጊት እንዳይፈጽሙ ተመክሮ ይሰጣል የሚል እምነት አለኝ፡፡

የሳኡዲ ስደተኞቹ ወደ ሃገራቸው ከመመለሳቸው ውጭ እዚህ ግባ የሚባል ተጨባጭ ስራ እየተሰራ እንዳልሆነ ለመገመት አያዳግትም፡፡ የሳኡዲ ስደተኞች ሕይወት ምናልባትም ከነበሩበት በባሰ ሁኔታ አስቸጋሪ ነገር ላይ እንደወደቀ የሚያሳዩ በርካታ ጠቋሚ ምልክቶች እያታዩ ነው፡፡ በቁጥር ቀላል የማያባሉት ወደ ቀያቸው ከመመለስ ይልቅ በየመንደሩ በሚገኙ ዝቅተኛ መኝታ ቤቶች አስርና አስራ አምስት እየሆኑ በደቦ መኖር ጀምረዋል፡፡ ሴቶች እህቶቻችን በሂደት ለምን አይነት ሕይወት እያተዘጋጁ እንደሆነ መገመት ይቻላል፡፡ ወንዶቹ ዳግም በተለመደው መንገድ ወደ መጡበት ስደት ለመመለስ ጉልበትና አቅም እስኪፈጠር በመጠባበቅ ላይ ናቸው፡፡ ለመሰንበት ሲባልም ወደ አስከፊ ሕይወት ማዝገማቸው የሚገመት ጉዳይ ነው፡፡

ችግሩ ሁሉንም ዜጋ ያስቆጣና በአንድ ያስተባበረ ጸጸትን የፈጠረ እንደነበር የሚረሳ አይደለም፡፡እንደተለመደው ጸጸቱ ቁጣ ከመቀስቀስ ውጭ ወደ ተግባራዊ እርምጃ መለወጥ አልቻለም፡፡ አጋጣሚው የቁጭትና የዋይታ ከመሆን አልፎ ለምን እንደዚህ ዓይነት ፈተና ላይ ወደቅን የሚል መሰረታዊ ጥያቄም ሊወልድ አልቻለም፡፡ ቀጥሉም በጥሞና ለመነጋገርም ሆነ መፍትሔ ለማመንጨት መንስኤና መንገድ ሊዘረጋ አልቻለም፡፡ የዲያስፖራ ፖለቲከኞችም የፖለቲካ ትኩሳቱን በማጋል ለሰልፍ ከመገባበዝ ውጭ የስደተኞቹን ሕይወት በቀጣይ ከአደጋ ለመታደግ ምን መደረግ አለበት ለማለት አልቻሉም፡፡ ዲያስፖራዎች “ከደማቁ ሰልፋቸው” በኃላ ጥቂት መዋጮ አድርገው፣ ቁጣቸውን አብርደው፤ አጀንዳቸውን በእንጥልጥል እጀመሩት ጉዳና ላይ ጥለውት መደ ጉዳያቸው ተመልሰዋል፡፡ ታዋቂ ሙዚቀኞች፣ ግለሰቦች፣ ባለሃብቶች አርቲስቶች… የኢቲቪን መድረክ ሲያጨናንቁ እንዳልነበረ ሁላ የስደተኞቹን ጉዳይ በቀጣይ ምን መፍትሔ ሊቸሩት እንዳቀዱ ለማሳየት አልደፈሩም፡፡ በእርግጥ መንግስት የጉዳዩ ቀዳሚው ባለቤት ነው፡፡ በዚህ ጉዳይ መንግስት ፈተናውን ሊያልፍ አልቻለም፡፡ መንግሰት ፈተናውን ማለፍ ባለመቻሉ ዜጎቻችን አጋር የሌላቸውና ለዘለቄታው ከንቱና ተንከራታች ሆነው መቀረት አይገባቸውም፡፡
በአጠቃላይ ሂደቱ በአሳዛኝ መልኩ ቢጠናቀቅም፤ ከፍተኛ ትምህርት ሰጥቶ እንዳለፈ መረዳት ይቻላል፡፡ መንግስት የዜጎች ጉዳይ በሃገር ወስጥም ሆነ በወጭ ሃገር ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ነው፡፡ የትኩረት አቅጣጫው በመጀመርያ መሆን ያለበት ዜጎች በሃገራቸው ተጠቃሚ የሚሆኑበትንና መብታቸው የሚከበርበትን የመልካም አስተዳደርና የኢኮኖሚ ስርዓት በመዘርጋት ከስደትትና ከውርደት መታደግ ነው፡፡ በዚህ ሁሉ ሁኔታ አጣብቂኝም ውስጥ ሆነው ልባቸው በሕጋዊም ሆነ በሌላ መንገድ ለመሰደደ የተዘጋጁ ዜጎች መኖራቸው ስለማይቀር የስደተኞች ጉዳይ በአለም አቀፍ ግንኙታችን ላይ የምንመዘንበት አንዱ መገለጫችን በመሆኑ ዜጎቻችን ተገቢው ጥበቃና ከለላ እንዲያገኙ ማድረግ ያሻል፡፡ መንግስት፣ኢምባሲዎችና ቆንስላዎች በስደት ላይ የሚገኙ ዜጎቻችንን የገቢ ርዕስ አድርጎ ከማየት መታቀብ አለባቸው፡፡

Health: የብልት መጠናቸው አነስተኛ ለሆኑ ወንዶች 8 አማራጭ ህክምናዎች

$
0
0

ከማስረሻ አህመድ

ከአኗኗራችን፣ ከአመጋገባችን፣ ከአካባቢያችን እንዲሁም በሌሎች አያሌ ምክንያቶች የጤና እክል ይገጥመናል፡፡ እነዚህን እክሎች ደግሞ ለማስወገድ ወደየህክምና ማዕከሎች ጎራ ማለትና ህክምና ማግኘት የተለመደ ነው፡፡ ይሁን አንዳንድ የጤና እክሎችን አሣልፎ ለዶክተሮች መንገር እንዲሁም ማማከር በሀፍረት አልያም በሌላ ምክንያት ደብቀን መፍትሄ የማናገኘበት ደረጃ ተደርሶ ለአያሌ ጉዳቶች እንዳረጋለን፡፡ በዛሬው ጤና አምዳችን በመላው አለም የሚገኙ የወንዶቻችን ችግር ስለሆነው አነስተኛ የብልት መጠን ችግር ነው፡፡ እንደሚታወቀው ይህችግር ህክምና የሚያስፈልገው በውል የታወቀና ባይስተካከል ችግር የሚያስከትል እንከን ነው፡፡ በመሆኑም የዘረፉ ባለሞያዎች አነስተኛ የብልት መጠን ላላቸው ወንዶች የተለያዩ የመፍትሔ አማራጮችን መጠቀም እንደሚቻል ይመክራሉ፡፡ ከነዚህም ውስጥ የሚከተሉት ተጠቃሽ ናቸው፡፡
men health
1. የሆርሞን ህክምና፡-

ይህ ቴስቴስትሮን የተባለውንና የወንዳወንድነት ባህሪ የሚያላብሰውን ሆርሞን በመርፌ መልክ በመስጠት የሚደረግ ህክምና ሲሆን ብዙውን ጊዜ በህፃንነት ሲሰጥ ውጤታማነቱ የጎላ ነው፡፡ ይሁን እንጂ በጎልማሳነት ዕድሜ ላይ መውሰድ አናሳ ውጤታማነት ያለው ነው፡፡

2. ቀላል ዘዴ፡-

አንዳንድ ወንዶች ሰውነታቸው በመወፈሩ የተነሳ ጉያቸው (የብልታቸው አካባቢም) በትርፍ ስብ የሚሞላ ነው፡፡ ይህ መሆኑ የፍትዎት አካለ መጠኑ አንሶ እንዲታይ ያደርገዋል፡፡ በመሆኑም የሰውነት ክብደትን በመቀነስ ብቻ ከበፊቱ የተሻለ የብልት መጠን እንዲኖራቸው በቀላሉ ማድረግ ይችላሉ፡፡

3. መድሐኒቶች፡-

እነዚህ በሚዋጥና በቅባት መልክ ተዘጋጅተው የሚወሰዱ የህክምና ዘዴዎች ሲሆኑ የሚዘጋጁትም ከአንዳንድ ዕፅዋት ነው፡፡ በእነዚህ ዙሪያ የተደረጉ ጥናቶች እንዳስረገጡት ከሆነ መድሀኒቶቹ ውስጥ አንዳንድ ጎጆ በካይ ነገሮች ተገኝቶባቸዋል፡፡ መድሀኒቶቹን በኢንተርኔት በኩል ለሽያጭ የሚቀርቡ ናቸው፡፡

4. ፓምፕ፡-

ይህ በብልት ላይ የሚገጠም አነስተኛ መሳሪያ ሲሆን ትንሽዬ በእጅ የሚሰራ መዝውር ያለው ነው፡፡ ዋና አላማውም በብልት ውስጥ በ4 ያለ ደም እንዲገባ በማድረግ የብልትን ውጥረት በመጨመር መጠኑን ለመጨመር ላይ ያተኮረ ነው፡፡ ይህ የሚሆነው በብልት ላይ የሚገጠመው መሳሪያ ‹‹ኔጌቲቪ ፕሬዠር›› በመፍጠር የመሳብ ሃይሉም ደምን ከደምስሮች ወደ ብልት ውስጥ በደንብ እንዲገባ ማድረግ ነው፡፡ ልክ ነዳጅን በቱቦ በኩል በአፉ ስቦ እንደማስተላለፉ ይቆጠራል የመዘውሩም ጥቅም ኔጌቲቭ ፕሬዥሩን ለመፍጠር ነው፡፡ ይሁን እንጂ ይህ ሁናቴ ማለትም የመሳብ ሀይሉ ከበዛ ወደ ብልት የሚገባው የደም መጠን በጣም ስለሚጨምር የብልትን ውስጣሚ ለስላሳ አካላት ላይ ጉዳት ሊያስከትልበት ስለሚችል የግፊት አጨማመሩ በፋብሪካው ትዕዛዝ መሰረት ብቻ መሆን ይኖርበታል፡፡ ይህፓምፕ አንዳንዶች ራስን በራስ ለማርካት ዘዴም ይጠቀሙበታል፡፡ በዚህ በኩል ለየት ያለ እውቅና ያተረፈው ደናልድ ቶምስን የተባለው ዳኛ ሲሆን በፍርድ ሂደት ወቅት ማሸኑን በመጠቀም ማስተርቤሽን ሲፈፅም ስለተደረሰበት የአራት አመት እስራት ተፈርዶበት በታሪክ ይዘከራል (እ.ኤ.አ ኦገስት 2006)፡፡ በተለይ በስሜት የመነቃቃት እና የመወጠር ችግር ላለበት ብልት የተዋጣለት ዘዴ ነው፡፡ እንዲሁም ቶሎ የመርካት ችግር ላለባቸው ወንዶችም በሰፊው ጠቀሜታን የሚሰጥ ነው፡፡ መሳሪያው ለረጅም ጊዜ ብልት እንደተወጠረ እንዲቆይ በሰፊው ጠቀሜታን የሚሰጥ ነው፡፡ መሳሪያው ለረጅም ጊዜ ብልት እንደተወጠረ እንዲቆይ የማድረግ ብቃት ያለው ነው፡፡ መሣሪያው በልዩ ስሙ ‹‹ቫኪውም ፓምፕ›› በመባል የሚታወቅ ነው፡፡

5. ተወጣሪ ተቀባሪዎች፡-

እነዚህ የህክምና አማራጮች (Inflatable implards) በመባል የሚጠሩ ሲሆኑ በብልት ውስጥ የሚቀበሩና ከፍተኛ የተለጣጭነት ባህሪ ያላቸው ቀጫጭን ቱቦዎች በቀላሉ በመግባትና እነሱን በመለጠጥ የብልትን የውጥረት መጠን መጨመር ነው፡፡ እንደአስፈላጊነቱ የቱቦዎቹ መጠን ተለቅ ተለቅ ያሉ ማድረግ የሚቻል ሲሆን ለረጅም ጊዜም ብልትን እንደተወጠረ የማቆየት ሀይል አላቸው፡፡ ቱቦዎቹ በብልት ውስጥ የሚቀበሩት በቀዶ ጥገና ሲሆን መጥፎ ነገር የተቀበሩትን ቱቦዎች መልሶ ማውጣት የማይቻል መሆኑ ሲሆን ባይወጡ ግን ጉዳት አያስከትልም፡፡

6. የማለብ ዘዴ፡-

ይህ ዘዴ ዋና ዓላማው በብልት ውስጥ የሚገባውን የደም መጠን በመጨመር የብልትን ውጥረት በሂደት የመጨመር ዘዴ ሲሆን የሚደረገውም በእጅ ጣቶች ነው፡፡ በከፊል የተነሳሳ ብልትን በአውራ ጣትና በሌባ ጣት ጠበቅ አድርጎ በመያዝ ወደ ላይ የመግፋት ሁኔታ ሲሆን አላማውም ደምን ወደ ብልት የማስገባት ሂደት ነው፡፡ ዘዴውም የብለትን ውስጣዊ የደም አቀባበል ውሃ የተነከረን ጨርቅ ከጣቶቹ ስር አብሮ በመጠቀም መከወን የበለጠ ውጤት እንዳለውም ይታወቃል፡፡

7. ክላምፒንግ፡-

ይህ ዘዴ ደግሞ በአንድ የተወጠረ ብልት- ታችኛው ስር አካባቢ ጠበቅ ባለ ቀለበት ወይም የጫማ ማሰሪያ ማሰር ነው፡፡ ብልቱን የሚያስሩት ቀለበት ወይም ክር ዓለማው ወደ ብልት የገባው ደም ወደ ኋላ እንዳይመለስና ብልት በደንብ እንደተወጠረ እንዲቆይ የሚያደርጉ ሲሆን ብልትን በሚገባ ማሸት ዘለቄታዊ ደም የመቀበል አቅሙንና መጠኑን እንዲጨምር ለማድረግም ነው፡፡

8. መለጠጥ፡-

ይህ ዘዴ እንደሚመክረው ከሆነ የብልትን ጫፉ (ክርክሩ አካባቢ) ቀጠን ባለ ገመድ ማሰርና ከዚያም ከገመድ ሌላኛው ጫፍ ከበድ ያለ ነገር በማንጠልጠል ረዘም ላሉ ደቂቃዎች ማቆየት ነው፡፡ ዓለማውም የብለትን የመለጠጥ አቅም ማጎልበት ነው፡፡ ይህም የሚሆነው የብልትን ውስጣዊ ተለጣጭ ክፍል ማለትም (ቱኒካ አልጂኒያን) የተባለውን ክፍል በመለጠጥ ሲሆን ዘዴውም ርዝመትን ብቻ ሳይሆን የውፍረት መጠንንም እንደሚጨምር ይታወቃል፡፡

ውድ አንባቢያን ምንም እንኳን ሁሉም ዘዴዎች መሉ በሙሉ ውጤታማ ናቸው ባይባልም የተወሰነ ለውጥ ግን የሚታይባቸው የህክምና ስልቶች ናቸው፡፡ ይሁን እንጅ ከራስ በራስ ዘዴዎቹ ባሻገር ያሉት የቀዶ ጥገና ህክምናዎችና መድሀኒቶች ብዙም አይመከሩም ፡፡ ምንም ከማድረግ በፊት ግን ሃኪምዎን ማማከርዎን እንዳይረሱ ዘ-ሐበሻ ትመክራለች።

የኢትዮጵያን ታሪክ ጥላሸት የመቀባት አባዜ –ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም

$
0
0

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም
ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ

በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ ያለው ገዥው አካል በ19ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የኢትዮጵያ ንጉስ የነበሩት የዳግማዊ አጼ ምኒልክ መቶኛ የሙት ዓመት በዚህ በያዝነው ዓመት (በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር) እየተከበረ ባለበት ወቅት ሙሉ ጊዜውን በመስጠት ንጉሱ የሰሩትን ታላቅ ስራ ሁሉ በማጣጣል እና ጥላሸት በመቀባት ዘመቻ ላይ በመጠመድ ታሪክ የማጠልሸት ድራማውን በመተወን ላይ ይገኛል፡፡ የታሪክ ማጠልሸት ዘመቻው በዋናነት እየተከናወነ ያለው ለገዥው አካል ቅርበት ባላቸው ታማኝ ሎሌዎች፣ የጥቅም ተጋሪዎች እና የእራሳቸው ስብዕና በሌላቸው አሻንጉሊቶች አማካይነት ነው፡፡ ገዥው አካል ሲያስነጥሰው መሃረብ ይዘው በሚቀርቡ አጎብዳጆቹ አማካይነት የጥላቻ መርዛማ ቃላትን፣ የሚቆጠቁጡ ባዶ ዲስኮሮችን እና እርባናየለሽ ምዕናባዊ ስዕል በአዕምሮው ላይ እየፈጠረ አጼ ምኒልክ የግዛት ማስፋፋት ጥማታቸውን ለማርካት ሲሉ በዜጎች ላይ የጭካኔ ተግባራትን እንደፈጸሙ በማስመሰል ለምንም የማይጠቅሙ እርባናየለሽ እና ተራ አሉባልታዎችን በማሰራጨት ላይ ይገኛል፡፡
582717_198631520276500_222803186_n

የገዥው አካል ድንጉላ አገልጋዮች በማናቸውም የማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎች በመሰማራት ታሪካዊ ቅጥፈቶችን፣ አሳሳች ዘገባዎችን፣ የሀሰት ታሪክ ፈጠራዎችን፣ ሆን ተብሎ በሀሰት ላይ የተመሰረቱ መረጃዎችን እና ነጭ ውሸቶችን እንደ በቀቀን እየደጋገሙ በማሰራጨት ላይ ይገኛሉ፡፡ የዕኩይ ዓላማው አራማጆች በታላቁ የኢትዮጵያ መሪ ላይ ግነታዊ ኩምክና በመስራት፣ በማዋረድ እና እውነተኛውን ስብዕናቸውን ጥላሸት በመቀባት የስሜት ፕሮፓጋንዳ ዘመቻ ውስጥ በመዘፈቅ ጌቶቻቸውን ለማስደሰት በታለመ ዕኩይ ምግባር ላይ ተጠምደው ይገኛሉ፡፡ የታላቁ መሪ ነብስ ከስጋቸው ከተለየች ከአንድ መቶ ዓመታት የጊዜ ቆይታ በኋላ የተቀበረን ጉዳይ በማንሳት ታላቁን መሪ ሰይጣናዊ ስብዕና እንደነበራቸው ለማስመሰል በማሰብ የዕኩይ ምግባር ጎተራዎቹ የቻሉትን ያህል ጥረት ለማድረግ ሞክረዋል፡፡ አቶ መለስ ዜናዊ በህይወት ከተለዩ ሁለት ዓመታት እንኳን ሳይሞላቸው የዕኩይ ምግባራት ቋቶቹ የኢትዮጵያ አዳኝ መልዓክ ሊያደርጓቸው ይፈልጋሉ፡፡

በአሁኑ ጊዜ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ላይ በተከፈተው የገፍ ወይም የኃይል የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ ወይም ደግሞ የአጼ ምኒልክን የሙት መንፈስ ደጋግመው በማንሳት ፍጹም ጥላቻ እና የጥላቻ አመለካከት እንዲንሰራፋ በገዥው አካል ስልታዊ እና የተቀነባበረ ዘመቻ የማካሄድ አመክንዮ ለማንም ቢሆን ሊደንቅ አይገባም፡፡ ሀቁ አንድ እና አንድ ብቻ ነው፡፡ የኸውም የምኒልክን ስም ጥላሸት በመቀባት (ሰይጣናዊ ስብዕና በመስጠት) በሚሽከረከር ጉዳይ ላይ ብቻ የሚቆም ጉዳይ አይደለም፡፡ ነገር ግን በቅርቡ በህይወት የተለዩትን የገዥውን አካል የአለቆች ሁሉ አለቃ (Capo di tutti capi) አቶ መለስ ዜናዊን በመላዕክነት ቀብቶ ለማቅረብ የታቀደ ዕኩይ ምግባር ነው፡፡

ዳግማዊ ምኒልክን ጥላሸት የሚቀቡ ሙትመንፈሶች፣

minilikበዳግማዊ አጼ ምኒልክ ላይ እየተካሄደ ያለው ከፍተኛ ጥላሸት የመቀባት የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ ያነጣጠረው የኢትዮጵያን ታሪክ በመፋቅ በአቶ መለስ ዜናዊ የመላዕክነት የህይወት ታሪክ (የመላዕክነት ትረካ) በመተካት የታላቋን ሀገር ትክክለኛ ታሪክ እንደገና ለመጻፍ፣ አዛብቶ ለመጻፍ፣ ገልብጦ ለመጻፍ፣ አወዛግቦ ለመጻፍ፣ በመቀባባት የሚያምር አስመስሎ ለማቅረብ እና እውነተኛውን ታሪክ ለማስወገድ በመደረግ ላይ ያለ ከንቱ ሙከራ ነው፡፡ የአጼ ምኒልክን ታሪክ በመሰረዝ የዘመናችን የ”አፍሪካ ታላቁ መሪ” በማለት የመለስ ዜናዊን ታሪክ ለመጻፍ ይፈልጋሉ፡፡ በሀሰት እምነት ላይ በመመስረት መለስ “አዲሱ የአፍሪካ መሪ ዝርያ“፣ መለስ “የዴሞክራሲያዊ ልማታዊ መንግስት ቀያሽ”፣ መለስ “በዓለም አቀፋዊ የሙቀት እና የአየር ጸባይ ለውጥ የአፍሪካ ጠበቃ”፣ መለስ “ከጂ-8 እና ጂ-20 መሪዎች ጋር በመሆን ክርናቸውን የሚያሳዩ አፍሪካዊ መሪ”፣ መለስ “የቻይና-አፍሪካ የትብብር መድረክ የቤጂንግ ከፍተኛ ዲፕሎማሲያዊ ጉባኤ ሊቀመንበር”፣ መለስ የሶማሌ ጅሃዲስቶች እና አሸባሪዎች አስወጋጅ”… ተብለው ከእውነተኛ ስብዕናቸው ውጭ በሆነ መልኩ እንዲመለክባቸው ይፍልጋሉ፡:

የታላቁን መሪ የዳግማዊ ምኒልክን ስብዕና ጥላሸት በመቀባት አቶ መለስን ቅብዓ መልዓክ (የተቀባ መልዓክ) ለማድረግ ይፈልጋሉ፡፡ ለመሆኑ አጼ ምኒልክን ጥላሸት የሚቀቧቸው ለምንድን ነው? ምክንያቱም አጼ ምኒልክ በአመራር ጥበባቸው እና በትግላቸው ግጭትን በመፍጠር ሲናቆሩ ከነበሩት ባላባቶች፣ ለስልጣን ብቻ ከሚቋምጡ ከተለያዩ አካባቢያዊ ንጉሶች፣ ከተለያዩ ልዕልቶች የቅምጥል የአገዛዝ ስርዓት፣ እና ከጎጣዊ ምስለኔዎች የተበታተነ አገዛዝ በማላቀቅ ዘመናዊቷን የአፍሪካ ብሄር ታላቋን ኢትዮጵያን በመመስረታቸው ብቻ ነው፡፡ የዕኩይ ምግባር አራማጆች አጼ ምኒልክን ጥላሸት ይቀቧቸዋል፣ ምክንያቱም ምኒልክ ታላቆቹን የአውሮፓ ኢምፔሪያሊስት ኃያላን በጦር ሜዳ ውሎ በማሸነፍ አንጸባራቂ ድል በመቀዳጀት የኢትዮጵያን ዘለቄታዊ ነጻነት ያጎናጸፉ እና የሀገሪቱን ሉዓላዊነት ያስከበሩ ጀግና መሪ በመሆናቸው ነው፡፡ ጥላሸት ይቀቧቸዋል ምክንያቱም ምኒልክ እውነተኛ የአፍሪካ መሪ በመሆናቸው ነው፡፡ የአጼ ምኒልክን ስም በማጥፋት እና ለኢትዮጵያ ህዝብ ያበረከቱትን የውርስ ትሩፋታቸውን በማንቋሸሽ ለአቶ መለስ ክብር ለመስጠት እና ከእርሳቸው የሚገኘውን ውርስ ብጹዕ/ቅዱስ ለማድረግ ይፈልጋሉ፡፡

ገዥው አካል የአጼ ምኒልክን ታሪክ በእራሱ ታሪክ ለመተካት ይፈልጋል፡፡ አጼ ምኒልክ የባቡር ሀዲድ በመዘርጋት የመጀመሪያው አፍሪካዊ መሪ ነበሩ፡፡ ይህንን አንጸባራቂ ታሪክ በመለወጥ አቶ መለስ ረዥም፣ ቆንጆ እና ቀላል የባቡር ሀዲድ ሲስተም በኢትዮጵያ ለማምጣት የመጀመሪያው መሪ ነበሩ በማለት የታሪክ ባለቤትነት ሽሚያን ለማጎናጸፍ ይፈልጋሉ፡፡ አጼ ምኒልክ የስልክ እና የቴሌግራፍ አገልግሎትን በአፍሪካ አህጉር በማስተዋወቅ የመጀመሪያው አፍሪካዊ መሪ ነበሩ፡፡ እ.ኤ.አ በ1889 አሌክሳንደር ግራህም ቤል “የድምጽ መነጋገሪያ መሳሪያ” የፓተንት ዕውቅና ካገኙበት 13 ዓመታት በኋላ እና በአጼ ምኒልክ ቤተመንግስት የመጀመሪያው የስልክ መስመር በተዘረጋበት ጊዜ በቴክኖሎጂው ሁኔታ ጭንቀት ውስጥ ገብተው የነበሩት የቤተክህነት ሰዎች ይህ የሰይጣን ስራ ነው በማለት ንጉሱ እንዲያስወግዱት በጠየቋቸው ጊዜ አጼ ምኒልክ ለቴክኖሎጂው ጠቀሜታ ካላቸው ጽኑ እምነት አኳያ ሳያስወግዱት ቀርተዋል፡፡ በአስርት ዓመታት ጊዜ ውስጥ አጼ ምኒልክ አዲስ አበባን በምስራቅ ኢትዮጵያ ከምትገኘው የሀረር ከተማ ጋር የሚያገናኝ የስልክ መስመር በመዘርጋት መርቀው ከፈቱ፡፡ ያንን አንጸባራቂ ታሪክ ወደ ጎን በማለት የአሁኖቹ ገዥዎች በኢትዮጵያ ዘመናዊ የመገናኛ ቴክኖሎጂ ሲስተምን በኢትዮጵያ ያመጡ አቶ መለስ ዜናዊ እንደሆኑ አድርገው ያቀርባሉ፡፡ እውነታው ግን በተገላቢጦሽ በአፍሪካ የስልክ እና የቴሌግራፍ መስመር በመዘርጋት ግንባርቀደም የነበረችው ኢትዮጵያ በአሁኑ ጊዜ ከአፍሪካ በመጥፎ የተንቀሳቃሽ ስልክ እና የኢንተርኔት አግልግሎት አጠቃቀም ሳቢያ በመጨረሻው እረድፍ ላይ ትገኛለች፡፡ ባለፈው ሳምንት የዎል ስትሪት መጽሄት/Wall Street Journal እንደዘገበው በኢትዮጵያ ውስጥ አርሶ አደሮች የተንቀሳቃሽ ስልኮች ቢይዙም “ችግሩ የግንኙነት መስመር ለማግኘት ብዙ ማይሎችን (ኪሎሜትሮችን)መጓዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡“ በማለት የችግሩን አሳሳቢነት አመላክቷል፡፡ ኢትዮጵያ በመጥፎ የኢንተርኔት አገልግሎት አጠቃቀም ከአፍሪካ ከመጨረሻዎቹ ሀገሮች በሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡

የዘመኑ ገዥዎቻችን አጼ ምኒልክ የሴቶችን ጡት ቆርጠው የሚጥሉ ጨካኝ ንጉስ እንደሆኑ አድርገው ታሪክን አዛብተው ለመጻፍ ይፈልጋሉ፡፡ ጨካኝነት ከተነሳ ዘንድ ከአቶ መለስ ዜናዊ የበለጠ ጨካኝ እና አረመኔ ይኖራልን? አቶ መለስ እራሳቸው እ.ኤ.አ በ2005 በተደረገው ሀገራዊ ምርጫ መጭበርበር ምክንያት ተቃውሟቸውን ለመግለጽ በወጡ ያልታጠቁ ሰላማዊ ዜጎች ላይ ለአነጣጥሮ ተኳሽ ጦራቸው ትዕዛዝ በመስጠት በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች እንዲገደሉ አድርገዋል፡፡ ይህንን እልቂት አስመልክቶ በእራሳቸው በአቶ መለስ ልዩ ትዕዛዝ ጉዳዩን እንዲያጣራ የተሰየመው የአጣሪ ኮሚሽን ምርመራውን አካሂዶ ባቀረበው ዘገባ መሰረት በአቶ መለስ ቀጥታ ትዕዛዝ እና ቁጥጥር አማካይነት የፖሊስ እና የደህንነት ኃይሎች በዕቅድ ተይዞ እና ሆን ተብሎ ታስቦበት 193 ሰላማዊ ሰዎች እንዲገደሉ እና ሌሎች 763 ሰዎች ደግሞ ከባድ ቁስለኛ እንዲሆኑ ተደርጓል፡፡ እ.ኤ.አ በ2004 አቶ መለስ እራሳቸው ለታጣቂዎቻቸው ትዕዛዝ በመስጠት በምዕራብ ኢትዮጵያ በጋምቤላ 400 ሰላማዊ ዜጎች እንዲያልቁ አድርገዋል፡፡ ኦጋዴን እየተባለ በሚጠራው አካባቢ የተካሄደውን የአየር ድብደባ እና መንደሮችን በማቃጠል የጥቃት ሰለባ ያደረገው ወንጀል የተፈጸመው በአቶ መለስ ስልጣን ልዩ ትዕዛዝ ነበር፡፡ በአቶ መለስ ትዕዛዝ በኦጋዴን ታጣቂ ኃይሎች ሴቶችን አስገድደው ደፍረዋል፣ መንደሮችን አቃጥለዋል፣ ህዝቡን በሽብር ቆፍን ውስጥ ለመሸበብ ሲባል “የመቀጣጫ ግድያዎችን” ማለትም በህዝብ ፊት በአደባባይ በስቅላት እንዲሁም ጭንቅላትን ቆርጦ የመጣል ወንጀሎች እንዲፈጸሙ ተደርጓል፡፡ የተባበሩት መንግስታት የሂዩማን ራይትስ ዎች ተሟጋች ዳይሬክተር/United Nations Advocacy Director for Human Rights Watch ስቴቭ ክራውሻው በኦጋዴን አካባቢ በሰላማዊ ዜጎች ላይ የተፈጸመውን ወንጀል “ትንሿ ዳርፉር” በማለት አመሳስለው ገልጸውታል፡፡
ገዥዎቻችን አጼ ምኒልክን የኦሮሞ ህዝቦች ጠላት እንደሆኑ አድርገው ታሪክን በመበረዝ የታሪክ ድሪቶ አቀነባብረው እንደገና የጎደፈ ታሪክ ለመጻፍ ይታትራሉ፡፡ አቶ መለስ በህይወት ቢኖሩ ኖሮ እሳቸው እና የዕኩይ ምግባር አጋሮቻቸው በኦሮሞ ህዝብ ላይ እስከ አሁን ድረስ ያልተነገረውን እና ለመናገር የሚዘገንነውን በሰው ልጆች ላይ የፈጸሙትን ወንጀል ወደ ፍትህ አደባባይ በማቅረብ እንዲታይ ለማድረግ ከበቂ በላይ መረጃዎች አሉ፡፡ እ.ኤ.አ በ2012 ፍሪደም ሀውስ/Freedom House የተባለው ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት ባቀረበው ዘገባ መሰረት አቶ መለስ እና አገዛዛቸው በኦሮሞ ህዝብ ላይ ሰፊ የሆነ የአድልኦ እና የጭቆና መረብ በመዘርጋት ተግባራት ላይ ተጠምደው ቆይተዋል፡፡ አቶ መለስ የኦሮሞ ነጻነት ግንባርን እንቅስቃሴ በመገደብ ብዛት ያላቸው ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ የሚጠረጠሩ የድርጅቱን አባላት እና መሪዎችን ከህግ አግባብ ውጭ በቁጥጥር ስር በማዋል በማጎሪያ እስርቤት አስገብተው ሲያሰቃዩ ቆይተዋል፣ አሁንም በመሰቃየት ላይ ይገኛሉ፡፡ እ.ኤ.አ በ2001 የቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት የነበሩት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ስልጣናቸውን ሲለቁ እንደተናገሩት “ወደ 25,000 የሚሆኑ የኦሮሞ ህዝቦች ከኦሮሞ ህዝቦች ነጻነት ግንባር ጋር በተያያዘ የገዥው አካል ክስ ምክንያት በተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢዎች እና በአዲስ አበባ ከተማ እስር ቤቶች ታስረው በመማቀቅ ላይ ነበሩ፡፡” በማለት ይፋ አድርገዋል፡፡ የመለስ የትግል ጓድ እና የቀድሞው የመከላከያ ሚኒስትር የነበሩት አቶ ስዬ አብርሃ በሚያስገርም ሁኔታ እንደተመለከቱት “ቃሊቲ እስር ቤት ኦሮምኛ ይናገራል፣ በዚሁ ግቢ በአንድ በመቶዎች የሚቆጠሩ እስረኞችን በሚይዝ ካምፕ ውስጥ 99 በመቶ የሚሆኑት እስረኞች ኦሮሞዎች ናቸው፡፡ አብዛኞቹ እስረኞች ደግሞ የታሰሩበት ምክንያት ምን እንደሆነ አያውቁም፣ ሆኖም ግን የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ተጠርጣሪ በመባል ዓመታትን በእስር ቤት በማስቆጠር ላይ ይገኛሉ፡፡“ በማለት ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል፡፡

Adwavictoryእ.ኤ.አ በ2006 ጂሃዲስቶች (አሸባሪዎች) የሶማሌን አገር ወረዋታል እና የሶማሌ መንግስት ጣልቃ ገብቸ ጂሃዲስቶችን እንዳስወጣለት “ጋብዞኛል” በሚል ተንኮልን ያዘለ ሰበብ ምክንያት አቶ መለስ በሶማሌ አገር ላይ ወረራ አካሂደዋል፡፡ አቶ መለስ በቴሌቪዥን ቀርበው እንዲህ ብለዋል፣ “የአገራችንን ሉዓዋላዊነት ለማስከበር እና በእስልምና ፍርድ ቤቶች ህብረት እና በሌሎች ጸረ ኢትዮጵያ ኃይሎች በመታገዝ የሚያደርሷቸውን ተደጋጋሚ አደጋዎች ለመግታት ሲባል የኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት ወዳልፈለገው ጦርነት እንዲገባ ተገድዷል፡፡“ በተመሳሳይ መልኩ በዴሴምበር 27 2006 የአቶ መለስ ሰራዊት እና ታንኮች የሞቃዲሾን ከተማ ወረሩ፡፡ እ.ኤ.አ በኦገስት 2007 የአቶ መለስ ሰራዊት በሶማሌ ውስጥ የሚያደርገው እንቅስቃሴ ተገታ፣ በሰው ህይወት ላይ የደረሰው ኪሳራ አስደንጋጭ ነበር፡፡ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ንጹሃን የሶማሌ ዜጎች ህይወት የተቀጠፈ ሲሆን ከ870,000 በላይ የሚሆኑት ዜጎች ደግሞ ሞቃዲሾን ለቀው ለመሰደድ ተገደዋል፡፡ በ2006 በሞቃዲሾ ከተማ ወደ 1.2 ሚሊዮን ገደማ የሚሆን ህዝብ ነበር፡፡ ከአቶ መለስ የሶማሌ ወረራ በኋላ ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች “ከአፍሪካ በጣም አስቀያሚ አስከፊ የሰብአዊ መብት ሁኔታ ያለበት“ በማለት የሶማሌን የሰብአዊ መብት አያያዝ በተጨባጭ ገልጸውታል፡፡

አጼ ምኒልክ ከአውሮፓውያን ወራሪ ኃይሎች ጋር የመከላከል ጦርነትን በማካሄድ በድል አድራጊነት ተወጥተዋል፡፡ አጼ ሚኒልክ የአውሮፓ ኃያል ከሚባል አገር ጋር ጦርነት በማድረግ በጦር ሜዳ ድል አድርገው ወራሪው ኃይል በመጣበት እግሩ ጓዙን ጠቅልሎ እንደ ውሻ ጅራቱን በእግሮቹ መካከል ወትፎ እንዲመለስ በማድረግ በአፍሪካ ታሪክ የመጀመሪያው መሪ መሆናቸው የሚካድ ጉዳይ አይደለም፡፡ አጼ ምኒልክ ወራሪውን የኢጣልያንን ጦር አምባላጌ እና መቀሌ ላይ ድል አድርገዋል፡፡ እንዲሁም እ.ኤ.አ በ1896 አድዋ ላይ ወሳኙን ፍልሚያ በማድረግ የአድዋን ጦርነት በድል አድራጊነት ተወጥተዋል፡፡ “ኋላቀር አፍሪካውያን ጥቁሮች” ወታደሮች ኃያሉን የአውሮፓ ኢምፔሪያሊስት የጦር ኃይል ያሸንፋል የሚል እምነት በማንም አውሮፓዊ የተገመተ አልነበረም፡፡ አጼ ምኒልክ በዘመናዊ መሳሪያ ትጥቅ፣ በስልት እና በቁሳቁስ አቅርቦት በዘመኑ በጣም የተጎዱ መሪ ቢሆኑም ቅሉ የብሩህ አዕምሮ ባለቤት እና ወታደራዊ ስልት የሚያውቁ በመሆናቸው ውጊያውን በማካሄድ ጦርነቱን አሸንፈው በአንጸባራቂ ድል በመታጀብ የነጮችን የበላይነት እና አይበገሬነት ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ በማስወገድ ለጥቁር ህዝቦች በአጠቃላይ ለአፍሪካውያን ደግሞ በተለይ የኩራት ፈርጥ ለመሆን በቅተዋል፡፡ ብዙ የአውሮፓ ኃያላን አገሮች አጼ ምኒልክን በማታለል እና በማጭበርበር ከኢትዮጵያ ግዛት ቆርሰው በመውሰድ ኢትዮጵያን ቅኝ ተገዥ ለማድረግ ከፍተኛ ጥረት አድርገዋል፡፡ እ.ኤ.አ በ1889 አጼ ምኒልክ በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል የሚገኙ ግዛቶችን አስመልክቶ ከኢጣሊያ መንግስት ጋር የውጫሌ ስምምነትን አጸደቁ፡፡ በውል ስምምነት ሰነዱ የኢጣሊያንኛው ትርጉም ከኢትዮጵያ የአማርኛ ትርጉም ጋር የማይመሳሰል መሆኑን አጼ ምኒልክ እንደተገነዘቡ እና ኢትዮጵያ በኢጣሊያን ጠባቂነት የሚለውን ሀረግ ሲመለከቱ የውል ስምምነቱን በማውገዝ አፈረሱት፡፡

የገዥው አካል አፈቀላጤዎች አቶ መለስ ኢትዮጵያ የአህጉሩ ታላቅ አገር እንድትሆን ጥረት ያደረጉ እና የአህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ መሪ እንደሆኑ በማድነቅ እና ስብዕናቸውን ከፍ ከፍ በማድረግ የአሁኑን የኢትዮጵያ ታሪክ ደልዘው በእርሳቸው ተተክቶ እንዲጻፍ ነው በመዋተት ላይ የሚገኙት፡፡ አቶ መለስ የኢትዮጵያን የግዛት አንድነት እና ሉዓላዊነት ያስከበሩ መሪ እንደሆኑ አድርገው ለማሳየት ይፈልጋሉ፡፡ እውነታው ግን የተገላቢጦሹን ያመላክታል፡፡ እ.ኤ.አ ከ1998-1999 ድረስ የባድሜን የግዛት ወሰን ለማስከበር በተካሄደው የኢትዮጵያ እና የኤርትራ ጦርነት የአቶ መለስ ጦር የ80,000 ኢትዮጵያውያንን ህይወት ያለምንም ወታደራዊ ስልት በጭዳነት ለመስዋዕትነት ዳርጎ ወታደራዊ ድልን ተቀዳጅቶ ነበር፡፡ በወገኖቻችን የህይወት እና ንብረት መስዋዕትነት የተገኘውን ድል ሰራዊቱ ገና አጣጥሞ ሳይጠግብ የኢትዮጵያው መሪ አቶ መለስ ከመቅጽበት በመገለባበጥ ባድሜን በዓለም አቀፋዊ የስምምነት ውል በማስቀየድ ለኤርትራ መንግስት ቡራኬ ብለዋል፡፡ በምንም ዓይነት መልኩ በየትኛውም አገር አንድ ወታደራዊ ኃይል እጅግ ከባድ መስዋዕትነትን ከፍሎ ያገኘውን አንጸባራቂ ድል ለተሸናፊው ጠላቱ በፈቃደኝነት መልሶ የሰጠበት የጦርነት ታሪክ የለም፣ ተመዝግቦም አያውቅም፡፡ እ.ኤ.አ በ1991 ወታደራዊውን አምባገነን ደርግን በትጥቅ ትግል ካስወገዱ በኋላ በአሜሪካ መንግስት አደራዳሪነት የሽግግር ስምምነቱ በሚፈረምበት ወቅት እኒሁ የኢትዮጵያው መሪ አቶ መለስ በኤርትራ የወሰን ግዛት ዳርቻ ላይ የምትገኘውን ከቀይ ባህር ጋር በመግቢያ እና በመውጫነት ለኢትዮጵያ ህዝብ የባህር በር በመሆን አገልግሎት የምትሰጠውን የአሰብን ወደብ ወደ ኢትዮጵያ ግዛት እንድትካለል የቀረበውን ሀሳብ አልቀበልም በማለት አሁንም በድጋሜ ለኤርትራ መንግስት ቡራኬ በመስጠት ይደልዎ ብለዋል፡፡ አቶ መለስ የኢትዮጵያን ግዛት ለባዕድ ኃይል በመስጠት ታላቋን አገር ወደብአልባ በማድረግ በፈጸሙት የአገር ክህደት ወንጀል ብቸኛው ተጠያቂ ናቸው፡፡ አሁንም ተከታታይነት ያለውን የትራጄዲ ድራማ በመቀጠል በሚስጥር በተደረጉ ስምምነቶች የይስሙላው ፓርላማ ለስሙ እንኳ መከረበት ሳይባል ምንም ሳይታሰብበት በጥድፊያ እኒሁ የኢትዮጵያው “መሪ” አሁንም የኢትዮጵያ አንጡራ ግዛት የሆነውን መሬት ለሱዳን መንግስት እንደ የገና ስጦታ የእጅ መንሻ ቡራኬ አድርገውታል፡፡ እኒሁ የኢትዮጵያው መሪ አቶ መለስ በድብቅ እና ታማኝነት በጎደለው መልኩ የአገሪቱን እጅግ በጣም ለም የሆነውን በሚሊዮኖች ሄክታር የሚቆጠር መሬት ዕዳቸውን እንኳ ውል ባለው መልክ ለመክፈል ለማይችሉ የአየር ባየር ጭልፊት ነጋዴዎች አሁንም ለእጅ መንሻ አቅርበዋል፡፡

አጼ ምኒልክ የኢትዮጵያን አንድነት በማጠናከር ዘመናዊ የመንግስት መዋቅር ዘርግተዋል፡፡ አቶ መለስ ግን ምዕናባዊ ዘመናዊነትን አምጥተዋል፡፡ አቶ መለስ ያለሐኪሞች እና መድኃኒት ሆስፒታል ገንብተዋል፡፡ በአንድ ወቅት ሐኪሞች አያስፈልጉንም በማለት በይፋ ተናግረዋል፡፡ ብቃት ያላቸው የዩኒቭርስቲ መምህራን እና ፕሮፌሰሮች፣ መጻህፍት፣ ቤተ መጻህፍት፣ ወይም ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ሳይኖር ዩኒቨርስቲዎችን ገንብተዋል፡፡ የመጸዳጃ ሲስተም የሌላቸውን ህንጻዎች ገንብተዋል፡፡ አጼ ምኒልክ ኢትዮጵያን የምዕራቡ ዓለም ስልጣኔ ትሩፋት ተቋዳሽ እንድትሆን አድርገዋል፡፡ አቶ መለስ “ልማታዊ መንግስት” የሚል እርባናየለሽ ህልዮት ከምስራቅ ኢስያ ሀገራት አምባገነኖች ኮርጀው በማምጣት ኢትዮጵያን ወደ ኋላ መልሰዋታል፡፡ እ.ኤ.አ በ1991 ስልጣን ከያዙ በኋላ አቶ መለስ ዘመናዊውን የኢትዮጵያ መንግስት አወቃቀር በማፈራረስ ወዲያውኑ አገሪቱን ክልል እየተባለ በሚጠራው ወይም የአፓርታይድ አይነት ባንቱስታንስ ወይም ክልሊስታንስ የተባለ የመከፋፈል ተልዕኮውን አጠናቀቀ፡፡ አቶ መለስ በሀሰት ላይ በመመስረት ባለሁለት አሀዝ የኢኮኖሚ ዕድገት አስመዝግበናል፣ እና “ኢትዮጵያ ነዳጅ ወደ ውጭ ከማይልኩ የሰብ ሰሀራ አፍሪካ አገሮች መካከል ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት የምታስመዘግብ አገር ናት” በማለት በሸፍጥ ለማሳመን በመወትወት ላይ ይገኛሉ፡፡ እውነታው ግን ኢትዮጵያ በዓለም ከሚገኙ የመጨረሻዎቹ ደኃ አገሮች ከመጨረሻው በሁለተኛ ደረጃ ላይ የምትገኝ አገር መሆኗን “ኢትዮጵያ ለምንድን ነው ደኃ የሆነችው?” በማለት ቀደም ሲል ባዘጋጀሁት ትችቴ ላይ በግልጽ አስቀምጨዋለሁ፡፡

አጼ ምኒልክ የኢትዮጵያ “ህዳሴ” መሪ ነበሩ፡፡ አገራቸውን ለማጠናከር እና ዘመናዊ ለማድረግ ወሳኝ የሚባሉ እርምጃዎችን ወስደዋል፡፡ ለዘመናዊ ቴክኖሎጂ ልዩ ትኩረት በመስጠት ለአገራቸው አዲስ ዓይነት የግንኙነት ስርዓት እንዲዘረጋ አድርገዋል፡፡ አጼ ምኒልክ አገራቸው ኢትዮጵያ የስልክ እና የቴሌግራፍ እንዲሁም ዘመናዊ የፖስታ አገልግሎት ተጠቃሚ እንደትሆን አድርገዋል፡፡ አጼ ምኒልክ የኤሌክትሪክ አገልግሎት በአዲስ አበባ ከተማ እንዲጀመር አድርገዋል፡፡ የመጀመሪያዋን በሞተር ኃይል የምትንቀሳቀስ አውቶሞቢል ወደ ሀገራቸው ያስገቡ አጼ ምኒልክ ናቸው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የማሪያ ቴሬዛ ገንዘብን የማይመች የገንዘብ መገበያያን በዚያን ዘመን በዓለም ገበያ ላይ በመገበያያነት አገልግሎት ስራ ላይ ይውሉ በነበሩ በመዳብ የወርቅ ቁራጭ የገንዘብ ሳንቲሞች በመተካት ዘመናዊ የገንዘብ ግብይትን በኢትዮጵያ አስጀምረዋል፡፡ አጼ ምኒልክ ከምንም ከማንም በላይ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ቅድሚያ ይሰጡ ነበር፡፡ አጼ ምኒልክ እ.ኤ.አ በ1894 ከጅቡቲ እስከ አዲስ አበባ የሚዘልቅ የባቡ ሀዲድ መስመር ለመዘርጋት ከፈረንሳይ መንግስት ጋር የስምምነት ውል ፈረሙ፡፡ በተመሳሳይ ዓመት የአውሮፓ ኃያላን አገሮች አፍሪካን እንደ ቅርጫ ስጋ የሚከፋፍለውን የአውሮፓ ቅኝገዥዎች የበርሊን ጉባኤን አካሄዱ፡፡ በዚያን ጊዜ ፈረንሳዮች የነበራቸውን ኃይል በመተማመን ከባቡር ሀዲዱ ጋር በተያያዘ መልኩ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ለመዳፈር ሲሞክሩ አገር ወዳዱ መሪ ፈረንሳዮችን ጭጭ እንዲሉ አድርገው በ1906 የአገራቸውን ሉዓላዊነት ካስጠበቁ በኋላ ነው ቀዝቀዝ ማለት የጀመሩት ሐዲዱም መሰራት የቀጠለው ፡፡ እንግዲህ እንዲህ የነበረውን አንጸባራቂ ታሪክ በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ ያለው ገዥው አካል የውሸት የአቶ መለስን ትረካ በማጉላት የህዳሴው መሪ፣ በአፍሪካ ታሪክ እስከ አሁን ድረስ ታይቶ የማይታወቅ የኤሌክትሪክ ኃይል ግድብ ገንቢ፣ የድልድዮች ገንቢ፣ የመንገዶች እና የባቡር ሀዲዶች… በማለት ታሪክን አዛብቶ ሸውራራ ታሪክ ለመጻፍ እየተውተረተረነው ያለው፡፡

አጼ ምኒልክ የፊውዳል መንግስታት የበላይ የነበሩ መሪ ነበሩ፡፡ በወቅቱ በአገር ውስጥ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ በጣም አስቸጋሪ ሁኔታ በነበረበት ጊዜ ማድረግ የሚፈልጉትን ማድረግ የሚችሉ አፍሪካዊ መሪ ነበሩ፡፡ በእግዚአብሄር በአላህ ፈቃድ አንዲት የተባበረች እና የተከበረች ኢትዮጵያን ለተተኪው ትውልድ አውርሰው አልፈዋል፡፡ የአቶ መለስ ጠንካራው የውርሳቸው ትሩፋት በአፍሪካ የመጀመሪያውን ፈላጭ ቆራጭ አምባገነናዊ አገዛዝ ማውረሳቸው ነው፡፡ በሁፊንግተን ፖስት ትችቴ/Huffington Post Commentary በግልጽ እንዳስቀመጥኩት “ዴሞክራሲ የህዝብ፣ በህዝብ፣ ለህዝብ የቆመ የመንግስት አስተዳደር ከሆነ የማፊያ አገዛዝ/thugocracy ደግሞ (የወሮ በላ) የሌቦች፣ ለሌቦች በሌቦች የቆመ የወሮ በላ መንግስት አስተዳደር ነው፡፡“ በግልጽ አባባል የማፊያ አገዛዝ የሚሽከረከረው በወሮበላ ሌቦች እና በዘራፊዎች ነው፡፡ በማፊያ የአገዛዝ ስርዓት የፖለቲካ ስልጣንን ሙዝዝ ብሎ መያዝ እና እንደ መዥገር መጣበቅ ዋናው ተግባሩ ሲሆን ገዥው አካል የህዝብን ገንዘብ በመዝረፍ እና ለብዙሀኑ ህዝብ ህልውና የቆሙትን መሰረታዊ አገልግሎቶች ውሱን ሀብቶች በመቀራመት ግላዊ ሀብትን ለማጋባስ ነው፡፡

የአቶ መለስ የማፊያ (የወሮ በላ) አገዛዝ በሰነድ ብቻ ተመዝግቦ የሚያዝ ሳይሆን በቀድሞው የመከላከያ የትግል ጓደኛቸው ጭምር የአይን ምስክርነት የተሰጠበት ጉዳይ ነው፡፡ ገና ከጫካ ትግል ሲጀምሩ አቶ መለስ እና የትግል ጓዶቻቸው የሌቦች አስተዳደራዊ ስርዓት ነበር የዘረጉት፡፡ እ.ኤ.አ በ1980ዎቹ የመጀመሪያ ዓመታት ለረሀብ ሰለባ ለወደቀው የትግራይ ህዝብ እርዳታ ተብሎ ከእርዳታ ሰጭ ድርጅቶች የተላከውን ከ10 ሚሊዮን ዶላር በላይ የሚሆን ገንዘብ ከተሰጠበት ዓላማ ውጭ አማጺው ቡድን ለጦር መሳሪያ መግዣ እና እራሳቸውን ማበልጸጊያ አድርገውታል፡፡ በቅርብ እየወጡ ያሉ ዘገባዎች እንደሚያመላክቱት ከግማሽ በላይ የሚሆነው የአገሪቱ ኢኮኖሚ በአቶ መለስ ባለስልጣኖች፣ ደጋፊዎች፣ ሎሌዎች፣ ጓደኞች፣ የስራ ባልደረቦች እና ሌሎች ቁጥጥር ስር ተቀፍድዶ ይገኛል፡፡ ሙስናን በሚመለከት የዓለም ባንክ “ሙስናን በኢትዮጵያ መመርመር” በሚል ርዕስ የተወሰኑ አገሮችን ባናሙናነት ወስዶ በማጥናት ባወጣው ባለ500 ገጽ የግኝት ዘገባ መሰረት ሙስና እና የህዝብን ሀብት መዝረፍ በኢትዮጵያ ዋና መገለጫ ሆኗል በማለት ደምድሟል፡፡ ዘራፊነት አና ሙስና የአቶ መለስ የመጨረሻው ውርሳቸው ነው፡፡

አጼ ምኒልክን መጥላት ይወዳሉ፣

ጥላቻ የነብሳችን የመጨረሻው የበሽታ ምልክት ነው፡፡ ጥላቻ ኢምክንያታዊ ነው ወይም አመክንዮ የለውም፡፡ በጥላቻ ላይ የተጻፉ በርካታ ሳይንሳዊ ጽሁፎች እንደሚያመለክቱት በጥላቻ የተመረዙት ምንጊዜም ይጠላሉ ምክንያቱም ይፈራሉ፣ ደህንነት አይሰማቸውም፣ ምቀኞች ናቸው፣ ወይም ደግሞ እራሳቸውን ይጠላሉ ምክንያቱም የጥላቻቸው መነሻ እና መድረሻ እነዚሁ በጥላቻ የተሞሉት ግብዞች ናቸውና፡፡ ከሁሉም በላይ በጥላቻ የተሞሉት ወገኖች እራሳቸውን ይጠላሉ ምክንያቱም ብቁነት የጎደላቸው፣ ኃይልየለሽነት፣ ተስፋቢስነት፣ እና የእረዳትየለሽነት ስሜት የተጠናወታቸው ነው፡፡
ማንዴላ እንዲህ ብለው ነበር፣ “ሰው በቆዳው ቀለም፣ ወይም ደግሞ በማንነቱ፣ ወይም በኃይማኖቱ ምክንያት ብቻ ማንም ማንንም ሊጠላ አልተወለደም፡፡ ሰዎች መጥላትን መማር አለባቸው፣“ በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ በስልጣን ላይ ያሉትን የገዥው አካል ኃላፊዎች ሁኔታ በማስብበት ጊዜ በማንዴላ ፍልስፍናዊ ግምገማ ላይ አምነት ማጣት ይቃጣኛል፡፡ ማንዴላ እንዲህ በማለትም አክለዋል፣ “መጥላትን የሚማሩ ከሆነ ፍቅርን ሊማሩም ይችላሉ፣ ምክንያቱም ፍቅር ከተቃራኒው የበለጠ በሰው ልጅ ልብ ውስጥ የመስረጽ ተፈጥሯዊ ባህሪ አለውና፡፡“ ተቃራኒውን በተጨባጭ የሚያመላክቱ በርካታ መረጃዎች ቢኖሩም የማንዴላ መርሆዎች በስልጣን ላይ ባሉት ባለስልጣኖች ሁሉ ሊተገበሩ እንደሚችሉ ጽኑ እምነት አለኝ፡፡

በመርህ እና በተግባርም እንደሚታየው በጋንዲ መርሆዎች መሰረት ለመኖር ጥረት ማድረግ አለብን፣ “ኃጢያተኛውን ሳይሆን ኃጢያቱን እንጥላ፣“ በጥላቻ የተመረዙትን የምንጠላ ከሆነ የእነርሱ የመስታወት ነጸብራቅ እንሆናለን፣ እራሳችንም የምንጠላቸውን እንሆናለን፣ እንደ ሰው ስብዕና አቶ መለስን እና መሰሎቻቸውን የምንጠላ ከሆነ እነርሱኑ ሆን ማለት ነው፡፡ የምንጠላ ከሆነ ምግባራቸውን እንጅ እንደ ሰው እራሳቸውን መሆን የለበትም፡፡

ጥላቻ ጠንካራ ኃይል ነው፡፡ በናዚዝስቶች የተሰራጨው ጥላቻ አገሮችን በጠቅላላ እንዲጠፉ አድርጓል፡፡ በሩዋንዳ የተከሰተው ጥላቻ የሚሊዮኖችን ሩዋንዳውያን ህይወት ቀጥፏል፡፡ በዳርፉር የተቆሰቆሰው ጥላቻ በሚሊዮን የሚቆጠሩ የሱዳን ዜጎችን ህይወት አጥፍቷል፡፡ በአሁኑ ጊዜ በተከሰተው የኃይማኖት ጥላቻ በናይጄሪያ እና በመካከለኛው አፍሪካ ሬፑብሊክ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች በመሞት ላይ ይገኛሉ፡፡ በምንም ዓይነት መንገድ ወደ ጥላቻ መግባት የለብንም፡፡

በዓለም ላይ ሁለት ዓይነት ህዝቦች እንዳሉ አምናለሁ፡፡ “ጎረቤትህን እንደ እራስህ ውደድ“ የሚለውን ወርቃማ ህግ የሚከተሉ ህዝቦች አሉ፡፡ ሌሎች ደግሞ “የመዳብ ህግ” እያልኩ በምጠራው “ጎረቤትህን እንደ እራስህ ጥላ“ እያሉ የሚኖሩ ህዝቦች አሉ፡፡ በጥላቻ የተሞሉ ሰዎች የእራሳቸውን እረዳትየለሽነት፣ የደህንነት እጦት ስሜት፣ የጥፋተኝነት ስሜት እና በጥላቻቸው መሳሪያነት ድርጊቶችን በመለወጥ አሸናፊነትን የሚጎናጸፉ ይመስላቸዋል፡፡ ሌሎችን በመጥላት የራሳቸውን የበታችነት ስሜት እና የእራስን ዋጋ ዝቅ አድርጎ የማየት ችግራቸውን በማስወገድ እራሳቸውን ከፍ ያደረጉ ይመስላቸዋል፡፡ አጼ ምኒልክን የሚጠሉ ሰዎች በእርግጥ አይጠሏቸውም፣ እራሳቸውን የሚጠሉ እና ምኒልክን ለመሆን የሚያስቡ ምኒልክ የሚያደርጓቸውን ነገሮች ሁሉ ተምሳሌት ለማድረግ የሚጥሩ ናቸው፡፡

በአሁኑ ጌዜ በኢትዮጵያ በስልጣን ላይ ላሉት ሁሉ አዝንላቸዋለሁ፡፡ በእርግጥ በጣም አዝንላቸዋለሁ፡፡ እነዚህ በጥላቻ የተሞሉት ወገኖች የኢትዮጵያን ታላላቅ መሪዎች እና የኢትዮጵያን ታሪክ ጥላሸት በመቀባት በቅርቡ በህይወት የተለዩትን መሪያቸውን እና የሁለት አስርት ዓመታት ኃጢያታቸውን በማስሰረይ ብጹ የሚያደርጓቸው ይመስላቸዋል፡፡ የአጼ ምኒልክን እና የቀዳማዊ ኃይለስላሴን በጎ ተግባራት ጥላሸት በመቀባት የአቶ መለስን ስብዕና የሚገነቡ ይመስላቸዋል፡፡ የአጼ ምኒልክን ሐውልት ከህዝባዊ ቦታዎች በማራቅ እና የአቶ መለስን እርካሽ ወረቀት ፎቶግራፎች በየመንገዶች ላይ በመለጠፍ አቶ መለስን ወደ መልዓክነት ያቀረቧቸው ይመስላቸዋል፡፡ አቶ መለስ የአጼ ኃይለስላሴ ሀውልት ከንክሩማህ ቀጥሎ በአፍሪካ ህብረት ቅጥር ግቢ ውስጥ እንዳይቆም ሽንጣቸውን ገትረው ተከራክረዋል፡፡ ሆኖም ግን ንክሩማህ እራሳቸው የአጼ ኃይለስላሴ ያልተጠቆጠበ ጥረት ባይኖር ኖሮ የአፍሪካ ድርጅት እውን መሆን አይችልም ነበር በማለት ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል፡፡

በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ ያሉት ባለስልጣኖች የጥላቻቸው ባህሪ እና አተገባበር ነጻብራቅ ረዘም ያለ ጊዜ የቆየ ቢሆንም ለዚህ ምክንያታዊ መግለጫ አላገኘሁለትም፡፡ ብዙ ሰዎች በፍርሀት እና በጭንቀት ላይ ያሉ ሰለ ወደፊት ምንይመጣል አያሉ ነው ምክንያቱም በቀጣይነት የሚከሰተው ሁኔታ የማይታወቅ እና ለመተንበይም አስቸጋሪ የሆነበት ሁኔታ ሰለሆነ ነው፡፡ ያለፈውን ጊዜ፣ የጥንት 19ኛውን ክፍለ ዘመን ኢትዮጵያ የሚፈሩትን ሰዎች በትክክል ለመረዳት አልችልም፡፡ በሞያዬ ካለኝ ልምድ አንጻር ያለፈውን ጊዜ የሚፈሩ እና የሚሸበሩ ወንጀለኞ ይሄዉም በፊት በፈፀሙት ወንጀል የሚያዙ ሰለሚመስላቸውና ሰለሚፈሩ ነው:: በስልጣን ላይ ያሉ አምባገነኖች ስልጣናቸውን ከህግ አግባብ ውጭ በመጠቀም የሰላማዊ ዜጎችን መብት የጣሱ እና የደፈጠጡበትን ወንጀል ለመደበቅ ሲሉ ጥላቻን በማራመድ እና ከፋፍሎ መግዛትን አጀንዳቸው አድርገው ይይዙታል ከሚል መደምደሚያ ላይ ደርሻለሁ፡፡ በኢትዮጵያውያን ልዩ ልዩ ጎሳዎች ላይ ጥልቅ ጥላቻና እና ፍርሀትን በመፍጠር ለፈጸሟቸው እኩይ ተግባራት ተጠያቂ እንዳይሆኑ እና ኃላፊነትን እንዳይወስዱ የጥላቻ መንፈስን እንደ መርህ በመያዝ ያራምዳሉ፡፡ በህዝቦች መካከል ጥላቻን በመዝራትም በኢኮኖሚያዊ ችግሮች ምክንያት ተወጥረው ያሉትን ዜጎች ሀሳቦች ለማስቀየሻ ይጠቀሙበታል፡፡

በጥላቻ የተሞላን ሰው እንደ እራስህ ውደድ፣

ወርቃማው ህግ እንዲህ ይላል፣ “ጎረቤትህን እንደ እራስህ ውደድ፡፡“ እኔ ደግሞ እንዲህ እላለሁ፣ “የሚጠላህን እንደ እራስህ ውድ፡፡“ ከመጥላት ይልቅ መውድደ የተሻለ ነገር ነው፡፡ ጥላቻ ወርዋሪውን ተመልሶ እንደሚጎዳ ቦንብ ነው፡፡ መጀመሪያ ከሚወረውረው ሰው እጅ ይወጣል ተመልሶ ግን በጥላቻ የተሞላውን ሰው እራሱን ይጎዳዋል፡፡ የማንዴላን አባባል በመዋስ፣ ጥላቻ የነብስ መርዝ ነው፡፡ በጥላቻ የተሞሉት በሚጠሉበት ጊዜ መርዝን ይጠጣሉ እናም የሚጠሏቸው እንዲሞቱ ይጠብቃሉ፡፡ በስልጣን ላይ ያሉ ሁሉ ጥላቻን ማራመድ እንዳለባቸው ልዩ ምክር የሚሰጥ ለየት ያለ የፍልስፍና ዓይነትም አለ፡፡ ጥላቻ ሁልጊዜ የተጠላውን ሰው የተወደደ እና የተከበረ ስብዕና ያለው እንዲሆን ያደርገዋል፡፡ በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ በስልጣን ላይ ተቆናጥጠው ያሉ ወገኖች በዱሮዋ ደቡብ አፍሪካ ከነበሩት የአፓርታይድ መሰል የመንፈስ ጓዶቻቸው ትምህርቶችን ሊማሩ ይገባል፡፡ የአፓርታይድ ጌቶች የማንዴላን ስብዕና፣ አመራር እና ክብር ለበርካታ አስርት ዓመታት ለማዋረድ ፈለጉ፡፡ ማንዴላ አሸባሪ እና ኮሙኒስት ናቸው በማለት ማንኛውንም ዓይነት የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ ከፈቱባቸው፡፡ ይንንም ምክንያት በማድረግ ማንዴላ በእስር ቤት በቆዩባቸው ጊዚያት ሁሉ ምንም ዓይነት የፎቶግራፍ ምስላቸው እንዳይወጣ አደረጉ፡፡ ሆኖም ግን ያልታሰቡ አጋጣሚዎች ተከሰቱ፡፡ በሂደት ጊዜ እያለፈ እና የጸረ አፓርታይድ ንቅናቄው እየተጠናከረ ሲሄድ ማንዴላን አሳንሶ የማየት አባዚያቸው የማንዴላን የመላዕክነት ደረጃ ከፍ እያደረገ ወደ ዓለም አቀፋዊ ተምሳሌነት እንዲሸጋገሩ እገዛ አደረገላቸው፡፡ ከዚህ ሊወሰድ የሚችለው ታላቅ ቁምነገር የአጼ ምኒልክን እና የአጼ ኃይለስላሴን ስብዕና ዝቅ ለማድረግ ጥረት ባደረጉ ቁጥር እነዚህ መሪዎች በኢትዮጵያ የወጣቶች ትውልድ የአስተሳሰብ አድማስ ዘንድ የበለጠ ክብር እና ሞገስን እየተቀዳጁ ታዋቂ እየሆኑ ይሄዳሉ፡፡ በእነዚህ መሪዎች ላይ የማያቋርጥ እና ዘለቄታዊ ያለው የማዋረድ ዘመቻ ባደረጉ ቁጥር የቀድሞው ትውልድ ጉዳዩን የበለጠ እንዲገመግመው እና አቋሙን እንዲያጠናክር ያደርገዋል፡፡

ፍቅር ከጥላቻ በላይ ዘልቆ መሄድን ይጠይቃል፡፡ ዶ/ር ማርቲን ሉተር ኪንግ እና ማንዴላ በሰዎች እና በህብረተሰብ ክፍሎች ዘንድ ፍቅር ያለውን የማይበገር የአሸናፊነት ኃይል፣ እንዲሁም ፍቅር በዘር፣ በጎሳ እና በኃይማኖት የተዘራን የጥላቻ ካንሰር የመፈወስ ችሎታ እንዳለው በግልጽ አስተምረውናል፡፡ ማንዴላ ለመጥላት እና በቀልን ለመፈጸም ምክንያት አላቸው፡፡ ለ27 ዓመታት የማንዴላ ስም የእስረኛ ቁጥር 46664 ነበር፡፡ እ.ኤ.አ በፌብሯሪ 1990 ጧት ከእስር ቤት ተለቅቀው ከእስር ቤቱ በር ሲወጡ ከሚሊዮን ዶላር ዋጋ በላይ የሚያወጣውን ፈገግታቸውን አሳይተዋል፡፡ ለ27 ዓመታት ከቤተሰቦቻቸው ነጥለው በእስር ቤት ውስጥ ባማቀቋቸው የአፓርታይድ ጌቶች ላይ ምንም ዓይነት የጥላቻ ስሜት አላሳዩም፡፡ ማንዴላ ታላቅ ትምህርት አስተምረውን አልፈዋል፣ እንዲህ በማለት፣ “እየተራመድኩ ወደ በሩ በምቃረብበት ጊዜ ይህ ሁኔታ ወደ ነጻነት እየመራኝ እንደሆነ አስብ ነበር፡፡ የበቀልተኝነት ስሜቴን እና ጥላቻዬን እዚያው እስር ቤት ጥዬው ካልወጣሁ እዚያው እስር ቤት እንዳለሁ እቆጥረዋለሁ፡፡“ በማለት የጥላቻን መጥፎነት በግልጽ ተናግረዋል፡፡ ማንዴላ ፍጹም የጥላቻ እስረኛ አልነበሩም፡፡ እስረኛው የአፓርታይድ ጥላቻ ነበር፣ እናም አስረኞቹ የአፓርታይድ አለቆች እና ጌቶች ነበሩ፡፡ ማንዴላ ከእስር ቤት በመውጣት በጥላቻ ሰንሰለት ከአፓርታይድ ግንብ ጋር የታሰሩትን እውነተኞቹን የአፓርታይድ እስረኞች ከጥላቻ፣ ከፍርሀት፣ እና ከበቀልተኝነት ነጻ ለማውጣት ተንቀሳቅሰዋል፡፡

በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ በስልጣን ላይ ያሉት ገዥዎች በጥላቻቸው የሚቀጥሉ ከሆነ በደቡብ አፍሪካ አፓርታይድ በስልጣን ላይ በነበረበት ጊዜ የደረሰው ዕጣ ፈንታ የሚደርስባቸው መሆኑን መገንዘብ ይኖርባቸዋል፡፡ በአፓርታይድ የአገዛዝ ዘመን ጊዜ “ነጻዎቹ” ነጮች እውነተኛው የማይቀረው የብዙሀን አገዛዝ በሚመጣበት ጊዜ ለብዙ ጊዜ በጭቆና ቀንበር አስረው ሲያማቅቋቸው የነበሩት ጥቁር አፍሪካውያኖች ምን ሊያደርጓቸው እንደሚችሉ ሌት እና ቀን ያሰላስሉ ነበር፡፡ በጥቁር አፍሪካውያን ላይ የነበራቸው ጥላቻ እንቅልፍየለሽ ሌሊቶችን ብቻ እንዲያሳልፉ አላደረጓቸውም፣ ሆኖም ግን ልቦቻቸው፣ አዕምሯቸው እና ነብሳቸው እንዲሁም ስብዕናዎቻቸውም ጭምር እንዲሰበሩ አደረጋቸው እንጅ፡፡ ሙት መንፈሶች አደረጓቸው፣ ነጻ ሆነው ባሏቸው ኃብቶቻቸው ለመደሰት ባለመቻል የቁም ሙት አደረጓቸው፣ እንዲሁም በኤሌክትሪክ እና በእስር ቤት የሽቦ አጥር ታጥረው የእራሳቸው ጎረቤቶች የእስር ቤት በሮች ሆኑባቸው፡፡ በእርግጥ በጦር ካምፕ የሚኖሩ ህዝቦች ሆኑ፡፡
ምንጊዜም የተሻለ መንገድ አለ፡፡ የጥላቻ ትችት ከማቅረባችን በፊት እውነተኛውን ነገር ለማወቅ የበለጠ ጽናት ሊኖረን ይገባል፡፡ ስለዳግማዊ አጼ ምኒልክ፣ ስለ አጼ ኃይለስላሴ፣ ስለ ኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማርያም እና ስለ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ እውነኛውን ነገር ማቅረብ ይኖርብናል፡፡ እነርሱን መጥላት ሳይሆን ከስህተቶቻቸው እንማር፣ እኛ በህይወት ያለነው የእነርሱን ስህተት መድገም የለብንም፡፡ ጥላሸት በመቀባት ላይ ላለመሰማራት ከእነርሱ ስህተት እንማር፣ ነገር ግን የእርቅን መንገድ በመፈለግ የእነርሱን ስህተቶች እናርም፡፡ ከኢትዮጵያ ወጣቱ ትውልድ ጋር ህብረት በመፍጠር ማንም ወንድ ወይም ሴት በማንነቱ/ቷ፣ በዘሩ/ሯ ሳይሆን ሰው በመሆኑ/ኗ፣ አፍሪካዊ/ት እና ኢትዮጵያዊ/ት በመሆናቸው ብቻ በመመልከት አዲሲቷን ፍቅር የነገሰባት ኢትዮጵያ ለመገንባት እንነሳ፡፡ ማንም ወንድ ወይም ሴት ባለው/ላት ስልጣን በመመካት ባልታጠቁ ዜጎች እና በሰላማዊ ሰዎች ላይ የጦር እልቂት ሊያዝዝ/ልታዝዝ የማይችሉበት እና ይህ ዓይነቱ አስተሳሰብም ሊወገድ የሚችልበት ነጻ ህሊናን በመፍጠር አዲሲቷን ፍቅር የነገሰባት ኢትዮጵያ ለመገንባት እንነሳ፡፡ በእያንዳንዱ/ዷ ግለሰብ የጎሳ፣ የእምነት ወይም የቋንቋ ልዩነት ሳንፈጥር በአንድነት በመሆን የእያንዳንዱ/ዷ ዜጋ መብት እና ክብር የሚጠበቅበትን ህብረተሰብ ለመፍጠር እንነሳ፡፡ በዚህ ዓይነት ሁኔታ ነው የወደፊቱን ብሩህ ዘመን ለመፍጠር የምንችለው፡፡ ለብዙ ጊዜ በመቆየት በጊዜ ደመና ተሸፍኖ የደበዘዘውን ነገር ቆፍሮ በማውጣት እና ጥላሸት በመቀባት አይደለም ፍቅር የነገሰበትን የወደፊቱን ትውልድ መገንባት የምንችለው፡፡

በጥላቻ ንግግር አንዘን ወይም ደግሞ አንቆጣ፡፡ ምንም ዓይነት እርባና የለውም፡፡ ይልቁንም ጥላሸት የመቀባት ዘመቻውን በሰከነ መልክ እናጋልጥ፡፡ መላዕክ ለማድረግ የሚደረገው ጥረት ስህተት እና ውሸት መሆኑን እና የኢትዮጵያን ታሪክ ጥላሸት ለመቀበት እና ለመበረዝ የሚደረገውን መዋተት እናጋልጥ፡፡ ከጥላቻ አራማጆች ጋር በማበር እራሳችንን ወደ ጭቃ እና የሚያጣብቅ ቆሻሻ ውስጥ አንጣል፡፡ እንዲህ የሚሉትን የጆርጅ በርናርድ ሻውን ምክሮችን በፍጹም መርሳት የለብንም፣ “ከብዙ ጊዜ በፊት ከአሳማ ጋር ማጥ ዉስጥ ላለመታገል ትምህርት አግኝቻለሁ፣ ለመታገል ከሞከርክ ቆሻሻ ትሆናለህ፣ አሳማው ግን ማጡን የነብሱን ያህል ይወደዋል፡፡“ ጥላቻን ሙያ አርገው ከሚኖሩ ሰዎች ጋር የጥላቻ ቃላትን መለዋወጥ ከአሳማ ጋር በጭቃ ማጥ ውስጥ የነጻ ትግል ውድድርን እንደማድረግ ይቆጠራል፡፡
ጥላቻን ወደ ፍቅር መለወጥ
በጥላቻ መንፈስ የተሞሉት ወገኖች ይጥሉ እና ይዋሹ፡፡ ስለዚያ ጉዳይ የምናደርገው አንዳች ነገር የለም፡፡ በእራሳችን የሀይል ንፍቀ ክበብ ውስጥ ያለን ልዩ ችሎታ እራሳችንን ከጥላቻ ወደ ፍቅር ከመቀየር ላይ ነው፡፡ በእርግጥም አሉታዊ ኃይሎችን ወደ አዎንታዊ ኃይሎች የመቀየር ችሎታ አለን፡፡ ከጥላቻ ወደ ፍቅር ለመቀየር እንችላለን፣ ይህን የምናደርገው ግን ነገሩ ቀላል ስለሆነ አይደለም ይልቁንም የበለጠ ከባድ ስለሆነ እንጅ፡፡ ፍቅር በግለሰብ ደረጃም ይሁን፣ በሌሎችም ይሁን፣ በማህበረሰቡ ወይም በአጠቃላይ በህዝቡ ላይ ይሁን ለተግባራዊነቱ ታላቅ ስራ መስራትን ይጠይቃል፡፡
ከማህተመ ጋንዲ እና “እውነተኛው ኃይል”/Satyagraha ከሚሉት አቀራረባቸው እስቲ ትምህርት እንቅሰም፡፡ ጋንዲ እንዲህ በማለት ገለጻ አድርገዋል፣ “እውነት/satya ፍቅርን በማጎናጸፍ የመንፈስ ጽናትን ይወልዳል፣ እናም ከኃይል ጋር ተመሳሳይ በመሆን ያገለግላል፡፡“ ዓላማው በጥላቻ የተሞላው/ችው እንዳያስገድድ/እንዳታስገድድ በማድረግ ሀሳባቸውን ለማስለውጥ ነው፡፡ በተግባራዊነት ሁኔታው ስንመለከተው ዓላማው በጥላቻ የተሞላውን/ችውን ጥላቻ ማራመድ የእራሱን/ሷን ልብ፣ አዕምሮ እና ነብሳቸውን የሚጎዳቸው መሆኑን በማሳመን እንዲቀየሩ ለማድረግ ነው፡፡ ከማንኛውም ጉዳትን ከሚያመጡ ነገሮች ሁሉ የሚጠብቁን እራስን፣ ማህበረሰቡን እና አገርን መውደድ ነው፡፡ በጥላቻ ከተሞሉት ወገኖች ፍቅር የተሞሉ ወገኖችን ለማፍራት እውነተኛውን ኃይል/Satyagraha በተግባር እናውል፡፡

ከዶ/ር ማርቲን ሉተር ኪንግ የምንማራቸው በርካታ ቁምነገሮች አሉ፣ እንዲህም በማለት ያስተምሩናል፣ “ጨለማን ጨለማ አያስወግደውም፣ ብርሃን ብቻ ነው ያንን ማድረግ የሚችለው፡፡ ጥላቻን ጥላቻ ሊያስወግደው አይችልም፣ ፍቅር ብቻ ነው ያንን ማድረግ የሚችል፡፡“ ብለዋል፡፡ እንዲህ በማለትም አስተምረዋል፣ “ይቅርታ የማድረግ ችሎታችንን ማሳደግና ማጠናከር ይኖርብናል፡፡ ይቅርታ የማያደርግ/የማታደርግ ሰው ለማፍቀር ኃይል የለውም/የላትም፡፡ በመጥፎነታችንም ላይ ጥሩ ነገሮችም አሉ፡፡ በመጥፎ ነገሮቻችን ላይም ጥሩ ነገሮች አሉ፡፡ ይህንን ሁኔታ ባወቅን ጊዜ ጠላቶቻችንን ከመጥላት በመጠኑም ቢሆን እንታቀባለን፡፡“ ይቅርታ አድራጊነት እና እርቅ ብቸኞች የጥላቻ ፈውስ እና መድኃኒቶች ናቸው፡፡

ከዘመናችን ታላቅ ቀልድ አዋቂ ከቻርለስ ቻፕሊን እንኳ ትምህርት መቅሰም ይኖርብናል፡፡ እንዲህም ይለናል፣ “የሰው ልጅ ጥላቻ ያልፋል፣ እና አምባገነኖችም ይሞታሉ፣ እናም ከህዝቦች የነጠቁት ስልጣን ተመልሶ በህዝቡ እጅ ይገባል፡፡ ስለሆነም የሰው ልጅ ሟች እስከሆነ ድረስ ነጻነት ከናካቴው ሊጠፋ አይችልም፡፡“ ነጻነት በጥላቻ ከተሞሉት የሰው ዘሮች ሁሉ የበለጠ እድሜ አለው፡፡ በጎሳ ማንነት መፈረጅን እርግፍ አድርገን እንተው እና ሰው በመሆናችን ብቻ በኢትዮጵያዊነታችን እና በአፍሪካዊነታችን እንኩራ፡፡

በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ በስልጣን ላይ ላሉ የማስተላለፈው መልዕክት፣

በኢትዮጵያ በስልጣን ላይ ሆነው ጥላቻን ለሚያራግቡት አጭር መልዕክት አለኝ፡፡ በአሁኑ ጊዜ የምትቆሰቁሱት የዘር እና የጎሳ ጥላቻ ፍላጻ በአንድ ወቅት ተመልሶ እራሳችሁ ላይ ይሰካል፡፡ በአሁኑ ጊዜ የአጼ ምኒልክን ክብር እና ዝና ለማንቋሸሽ በታለመ ዕኩይ ምግባር ጡት ቆራጭ አረመኔ ነበሩ በማለት በመሳለቅ እና በማፌዝ ላይ ትገኛላችሁ፡፡ በአሁኑ ጊዜ አጼ ምኒልክን እንዲጠሉ የሚሰበክላቸው ሰዎች ነገ ደግሞ አቶ መለስን እንዲጠሉ የማይሰበክበት ምክንያት አይኖርም፡፡ የእናንተ ታላቁ ባለራዕይ መሪ አቶ መለስ በኦጋዴን፣ በጋምቤላ፣ በአዲስ አበባ እና በሌሎችም ቦታዎች በንጹሃን ዜጎች ላይ በፈጸሟቸው የጅምላ እልቂቶች ሳቢያ በድንጋይ እና በእብነበረድ በተቀረጹ ሃውልቶች ላይ ሆነው ሁለተኛው ሮዶልፍ ግራዛኒ በመባል የሚታወሱበት ጊዜ እሩቅ አይሆንም፡፡ ዛሬ ጓደኞች ብላችሁ የያዛችኋቸው ሰዎች ነገ ቀንደኛ ጠላቶቻችሁ ሆነው ይቀርባሉ፡፡ ዛሬ የእናንተ ጠላቶች አድርጋችሁ ጥላሸት የምትቀቧቸው ሰዎች ነገ ጽዋው ሞልቶ እጣ ፈንታችሁ ደርሶ የዘራችሁትን የምታጭዱበት ጊዜ ሲመጣ የእናንተ ጓደኞች ሆነው ይቀርባሉ፡፡

ዳግማዊ አጼ ምኒልክ መልዓክ ወይም ጭራቅ አልነበሩም፡፡ ሰይጣን ወይም ደግሞ እግዚአብሄርም አልነበሩም፡፡ የተቀሩት የአፍሪካ አገሮች በኃአውሮፓ ኢምፔሪያሊስት ኃይሎች ሲቆራረሱ፣ መጫወቻ ሲሆኑ፣ ሲነሱ ሲጣሉ፣ ሲበጠሱ ሲቀጠሉ፣ ሲሸጡ እና ሲለወጡ እንዲሁም ሲጋዙ በነበረበት ጊዜ አጼ ምኒልክ ደግሞ ኢትዮጵያን ሲያጠናክሩ እና ሲያዘምኑ የነበሩ የተከበሩ አፍሪካዊ ንጉስ ነበሩ፡፡ ዳግማዊ አጼ ምኒሊክ በአንድ መለኪያ ብች ይገምገሙ፣ በእውነት! የታሪክ ሰዎች እውነታውን መናገር አለባቸው፣ እና ሁሉንም እውነታዎች፣ ሌላ ምንም ነገር ሳይሆን ስለምኒልክ ያለውን እውነታ ብቻ፡፡ ለአጼ ምኒልክ 100ኛ ሙት ዓመት መታሰቢያ ሲባል እ.ኤ.አ በ1909 በኒዮርክ ታይምስ ባሮን ዲ ጃርልስበርግ የተባለ የቤልጄም አሳሽ ለዳግማዊ አጼ ምኒልክ ምስክርነት ለጋዜጣው ቃል በመስጠት የተዘገበውን በከፊል ምስከርነት እውነታ መረጃ እንደሚከተለው አቅርቤዋለሁ፡፡ ይህ ታሪካዊ የምስክርነት መረጃ ዳግማዊ አጼ ምኒልክን ከሰሯቸው ስራዎች አንጻር በትክክለኛው የታሪክ ሚዛን ላይ በማስቀመጥ እንዲገመገሙ ያስችላል የሚል ጽኑ እምነት አለ፡፡

ዳግማዊ አጼ ምኒልክ የዘውድ ስልጣኑን ለመቆናጠጥ ትግል ማድረግ ከጀመሩበት ከ20 ዓመታት በኋላ አቢሲኒያን ከከፊል የኋላቀርነት አገዛዝ በማውጣት ወደ አውሮፓውያን የንጉሳዊ ህገመንግስት የአገዛዝ ስርዓት ምሳሌነት አሸጋግረዋታል… እራሳቸውን ነጻ እና በእራስ የሚተማመኑ አድርገው የሚቆጥሩት ዘ እምነገደ የይሁዳ አንበሳ ስዩመ እግዚአብሔር የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገስት ዘ ኢትዮጵያ የኢጣሊያንን የቅኝ ግዛትነት ፍላጎት አምባ ጋሪማ ላይ ጦርነት ገጥመው በአሸናፊነት እንዳንኮታኮቱት… አጼ ምኒልክ ከአጼ ዮሀንስ ህልፈተ ህይወት በኋላ እ.ኤ.አ ኖቬምበር 4 1889 የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገስት ሆነው ሲሰየሙ የአቢሲኒያን መንግስት ከመሰረቱት የአካባቢያዊ መንግስታት በሙሉ ቅቡልነት አልነበራቸውም፡፡ ከብዙ ድካም እና ትግል በኋላ ነው እነዚህን የአካባቢ ገዥዎች እና ንጉስነታቸውን አንቀበልም ያሉትን አማጺ ገዥዎች በማሳመን እና በኃይል በማንበርከክ በመጨረሻ ስኬታማ ለመሆን የበቁት… ከዚያ በኋላ የአጼ ምኒልክ ዋና ዓላማ የነበረው የአውሮፓን ስልጣኔ ወደ አገራቸው ማስገባት ነበር፡፡ ንጉሱ የፊውዳሉን ህግ በማፈራረስ በእርግጥም በግዛታቸው እስከ አሁንም ድረስ ጨርሶ እንዳልጠፋ እና ባሮችን ነጻ በማውጣት የባሪያ ንግድን በማጥፋት በግዛታቸው በሙሉ ከክፍያ ነጻ የሆነ የትምህርት ስርዓትን ዘርግተዋል፡፡ በዚህም መሰረት እንደማንኛውም የአውሮፓ ሀገር ሁሉ በቀጣዮቹ ትውልዶች ትምህርት በመላ የአቢሲኒያ ግዛት ውስጥ የሚስፋፋ ይሆናል፡፡

ምኒልክ በመላ አፍሪካ በስልጣን ላይ ካሉ መሪዎች ሁሉ ልዩ ባህሪ ያላቸው ናቸው፡፡ እንደ የዲፕሎማሲ ሰው፣ እንደ ገንዘብ ኃላፊ፣ እንደ ወታደር ከሌሎች ወንድማዊ ንጉሶች የቅርበ መረጃዎችን በመውሰድ በእራሳቸው አካሄድ እንደሚመስላቸው የሚተረጉሙ ንጉስ ናቸው፡፡ እንደ ወታደር እና እንደ የዲፕሎማሲ ሰው የኢጣሊያኖችን በአቢሲኒያ መሸነፍ ለንጉሱ እንደ መልካም አጋጣሚ ምን ያህል ጠቃሚ የሆኑ ንጉስ መሆናቸውን አሳይተዋል፡፡ በቅርብ ዓመታት ደግሞ የገንዘብ ብልህ ጥንቁቅ አያያዝ ምኒልክን ልዩ ያደርጋቸዋል፡፡ ስለገንዘብ እንደ ወጣትም፣ የዙፋን ስልጣናቸውን ከመያዛቸው እና በዙፋኑ ላይ ከተቀመጡም በኋላ በፓሪስ የስቶክ ገበያ ትንበያን/Paris Bourse ላይ ተሳትፎ ማድረጋቸው መልካም ተፈጥሯዊ ችሎታ ያላቸው መሆኑን ያመላክታል፡፡ እነዚህ ጠቃሚ ትንበያዎች የነበሩ ሲሆን ምኒልክ የዙፋን ስልጣኑን ከያዙ በኋላ ለመቋረጥ ችለዋል… የገንዘብ አሰራር ስርዓታቸውን በማስፋት እስከ ዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ ድረስ በማስፋት በአሜሪካ የባቡር ሀዲድ ካምፓኒዎች ላይ ትልቅ የድርሻ ባለቤት ለመሆን በቅተዋል፡፡ ከአሜሪካ የሴኪዩሪቲ ሰርቲፊኬቶች እና ከፈረንሳይ እና ከቤልጄም ባለሀብቶች ጋር ከ25 ሚሊዮን ዶላር ያላነሰ መዋዕለ ንዋይ በስራ ላይ እንዲውል አድርገው ነበር፡፡
በጣም የሚያስገርመው የአቢሲኒያው ደብዛዛ ንጉስ በሁሉም ነገሮች ላይ ያላቸው ሁለገብ እውቀት ነው፡፡ በጣም ምጡቅ የቋንቋ ችሎታ የነበራቸው ሲሆኑ ፈረንሳይኛ፣ እንግሊዝኛ እና ጣሊያንኛ ቋንቋዎችን አቀላጥፈው መናገር ይችላሉ፡፡ አብዛኛውን ጊዜ ለመንግስታዊ ስራቸው ሙሉ ጊዜ ሰጥተው የሚሰሩ ሲሆን በአውሮፓ የሚዘጋጁ ጽሁፎችንም የመከታተል ዕድል ስላላቸው እና በትኩረት ስለሚከታተሉ አዲስ መጽሀፍ በወጣ ቁጥር ስለደራሲው ሲጠየቅ አዲስ አይሆኑም፡፡ ባዲሳባ ቤተመንግስት በሰዎቻቸው በሚታወቁበት መጽሀፍትን በማሰባሰብ ስራቸው እውቅና እንዲሰጣቸው ሲባል በተዘጋጀው ስብሰባ ላይ በተገኙበት ዕለት በቤተ መጻህፍታቸው ከ20 ሺህ ያላነሱ ጥራዞች መገኘታቸው ልዩ ኩራት እንዲሰማቸው አድርጓል፡፡ የምኒልክ መጻህፍትን የማሰባሰብ የትርፍ ጊዜ ስራ በጥንት የአፍሪካ እና የኢስያ ስልጣኔዎች ዘመንም የሚደረግ ነበር፡፡

በአጼ ምኒልክ ላይ የጥላቻ ዘመቻ ከሚያደርጉት ወገኖች ጋር የማቀርበው መደራደርያ ፣

በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ላይ የጥላቻ ዘመቻ ስለማሰራጨት ጉዳይ የማቀርበው መደራደርያ አለኝ ፡
በአጼ ምኒልክ ስብዕና ላይ የምታደርጓቸውን ውሸቶችና ቅጥፈቶች የምታቆሙ ከሆነ እኔም ስለአቶ መለስ የምናገራቸውን እውነቶችመናገር አቆማለሁ!
ጥር 7 ቀን 2006 ዓ.ም

አንድነት በኢትዮ-ሱዳን ድንበር ማካለል ዙሪያ ሕዝባዊ ውይይት ሊያደርግ ነው

$
0
0

ከያሬድ አማረ/ ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ

UDJአንድነት ፓርቲ ጥር 18/2006ዓ.ም በኢትዮ ሱዳን ድንበር ማካለል ዙሪያ ከህዝብ ጋር ውይይት እንደሚያካሂድ አስታወቀ።

አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ በኢትዮ ሱዳን የድንበር ማካለል በሚል በሁለቱ መንግስታት ብቻ በሚስጥር በተያዘው መርሀ ግብር ዙሪያ ከህዝብ ጋር ውይይት እንደሚያደርግ ተገልጧል፡፡

ፓርቲው በመጪው ጥር 18ቀን 2006ዓ.ም የሚያካሂደው ህዝባዊ ውይይት በኢትዮጵያ በመንግስትና በሱዳን መንግስት መካከል ይፋ ባልሆነው የድንበር ማካለሉ ሂደት ግልፅነት የጎደለው የድንበር ማካለል በሚል ሽፋን ሊደረግ የታሰበና በአካቢው የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ዜጎችን ለሰቀቀን የዳረገ ከመሆኑም ባሻገር በጉዳዩ አሳሳቢነት ዙሪያ መወያየት አስፈላጊ በመሆኑ ፓርቲው ከህዝብ ጋር ተወያይቶ ግልፅ አቋሙን የሚያሰቀምጥበት በመሆኑ የኢትዮጵያ ጉዳይ ያገባኛል የሚል ሁሉ በውይይቱ ላይ በመገኘት ሃሳቡን እንዲገልፅ አንድነት ጥሪውን አቅርቧል፡፡

በሌላ ዜና አንድነት ፓርቲ ለአማራ ክልል እና ለጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ የኢትዮ ሱዳን ድንበር ማካለል ጉዳይ በአጭር ግዜ ውስጥ ለህዝብ ግልፅ እንዲሆን በደብዳቤ አሳሰበ።

አንድነት ለአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደርና ለጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ በኢትዮ ሱዳን የድንበር ማካለል ዙሪያ ግልፅ የሆነ ማብራሪያ በአጭር ግዜ ውስጥ ለህዝብ እንዲሰጥ በደብዳቤ ጠይቋል።

የአንድነት ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ አያሌው ለፍኖተ ነፃነት እንደገለፁት ኢህአዴግ በሉአላዊ ግዛት ማስከበር ጉዳይ የግዴለሽ አመለካከት ያለው በመሆኑ ብሔራዊ ጥቅማችንን ሊጎዳ የሚችል እርምጃ ሲወስድ በመቆየቱና የተለማመድው በመሆኑ አሁንም በተለመደው ግብሩ ለህዝብ ግልፅ ባልሆነ ሁኔታ ሊካሄድ የታቀደው የድንበር ማካለል የኢትዮጵያን ጥቅም ባላስጠበቀ መንገድ ሊፈፀም እንደሚችል ፓርቲው ከፍተኛ ስጋት ስላደረበት ጉዳዩን በቅርበት እየተከታተለና በሚስጥር የያዘው የአማራ ክልል ርእሰ መስተዳደርም ሆነ ጠቅላይ ሚንስትሩ ስለ ድንበር ማካለሉ አጠቃላይ ዝርዝር ሁኔታ ለህዝቡ በአጭር ግዜ ውስጥ ግልፅ የሆነ ማብራሪያ እንዲሰጥ በደብዳቤ መጠየቃቸውን ገልፀዋል፡፡

የመረጃና የሃሳብ ነፃነትን ለጋራ ጥቅም እናውለው! –ቃልኪዳን ከኖርዌ

$
0
0

kalkidanቃልኪዳን ካሳሁን /ከኖርዌ

ሀገሪቱ እየገነባች ያለው ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የፈጣን ልማት ባለቤት አላደረጋትም። ባለፉት ሺ ዓመታት በኢትዮጵያ ያልነበረ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እንድንጀምርና በጋራ እንድናሳድግ እድል አልፈጠረም። ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ከመለያየትና ከፀረ እኩልነት አስተሳሰብ ወጥተው መከባበር፣ መደጋገፍና በልዩነት ውስጥ አንድ ሀገር መገንባት እንዲጀምሩ አላገዘም።

Read full Story in PDF

“የአንድነት ፓርቲ የመጪው ጊዜ ፈተና”–የመልስ መልስ ለአቶ ግርማ ካሳ እና ለመሰሎቻቸው –ከፋሲል የኔዓለም (ጋዜጠኛ)

$
0
0

“የአንድነት ፓርቲ የመጪው ጊዜ ፈተና” በሚል ርዕስ ለጻፍኩት ጽሁፍ ስለሰጡት ምላሽ ከልብ አመሰግናለሁ። ሀሳቦችን በጨዋ መንገድ ማንሸራሸር ለእድገት ይጠቅማልና ሁላችንም ይልመድብን እላለሁ። ስለአንድነት ፓርቲ ተቆርቋሪ ሆነው የሰጡት መልስ ብዙም እንዳላረካኝ ስገልጽልዎ በከፍተኛ አክብሮት ነው። ማንም ጤናኛ ሰው በአገር ውስጥ ሰላማዊ በሆነ መንገድ ዴሞክራሲያዊ ለውጥ እንዲመጣ ይፈልጋል። አንድነት ፓርቲ በዚህ እምነት የሚያደርገውን ትግልም አደንቃለሁ። ይሁን እንጅ የትግል ፍሬ መለኪያው ሂደት ሳይሆን ውጤት ነውና አንድነት ፓርቲ፣ ኢ/ር ግዛቸው ሊሄዱበት ባሰቡት መንገድ ከተጓዘ፣ ውጤታማ ይሆናል የሚል እምነት የለኝም። እርስዎ በዚህ አስተያየት አልተስማሙም። አለመስማማትዎን ሁለት ቁምነገሮችን በማንሳት ለማሳየት ሞክረዋል፤ እኔም በእነዚህ ነጥቦች ላይ ተመስርቼ የመልስ መልስ አቀርባለሁ።

አንደኛ፤ አንድነት ፓርቲ፣ የአገሪቱ የህግ አካል የሆነውን ፣ የምርጫ ስነምግባር መመሪያው እስካሁን አለመፈረሙ ስህተት ነበር፣ አሁንም ፈርሞ ከኢህአዴግ ጋር መነጋገር አለበት የሚል መከራከሪያ አቅርበዋል። የስነምግባር መመሪያውን ፈርመው ለድርድር ተቀምጠው የነበሩት የቀድሞው የመኢአድ ሊቀመንበር ኢ/ር ሃይሉ ሻውል በመጽሀፋቸው የተናገሩት ሰነዱን መፈረም ያዋጣል አያዋጣም የሚለውን ለማየት ይረዳናልና ልጥቀስ፤-

Hailu Shwel ” ከኢህአዴግ ጋር ያደረግነውን ድርድር በተመለከተ አንዳንዱ ‘ ወደሰለጠነ ፖለቲካ ልንገባ ይሆን?’ ብሎ በደህና ሁኔታ ያየው ወገን ነበር። ሌላው ወገን ግን ‘እንዴት ያሰረውን ሰው ሄዶ እጅ ይጨብጣል’ የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አሰምቷል። የ2002ቱን የምርጫ ስነምግባር ሰነዱን ስንፈርም ተቃውሞ እንደሚኖር ሳናውቅ ቀርተን አይደለም። ፊርማው ብቻውን ለእኛ ደስታን የሚሰጠንም ሆኖ አልነበረም።ሌላኛው አማራጭና አስተሳሰብ ግን ግብዝነትናን የሚያጠናክርና የሰላም ሂደትን የሚገታ ይሆናል የሚል ግምት መያዛችን አንዱ ምክንያታችን ነው። በወቅቱ እኛ ሰነድ መፈረማችን ለህዝብ ምን ፋይዳ አለው የሚለውንም በአግባቡ አይተነዋል። እኛ ያሰብነው ወረቀት ቢሮ ውስጥ ይፈረማል፣ ያልቃል የሚል ነበር። እነሱ ግን አምባሳደሮች ጋብዘው፣ ሚዲያዎችን ጠርተው የተለየ ዝግጅት አደረጉ። ነገሩን ለዓለም ለማሳወቅ መፈለጋቸው ለሁሉም ግልጽ ሆነ። በዚያን ወቅት እኛ የማናውቀው ውጥረት ነበረባቸው የሚል የዘገየ ግምት ተከሰተልኝ ። እኔ እንደሚመስለኝ የአውሮፓ ህብረት ታዛቢዎች የመታዘብ ይሁንታ የሰጡት ያ ስምምነት ስለተፈረመ ይመስላል። መኢአድ ሰነዱን የፈረምንበት ዋናው ምክንያት ግን የ500 ስቃይ ላይ የነበሩ እስረኞችና የቤተሰቦቻቸው ሰቆቃ አሰቃይቶን ነው። እኔን በተመለከተ ኢህአዴግ ወደ እኛ አስገባነው ብሎ ቢያስወራም አልሰመረለትም።”

(ህይወቴና የፖለቲካ እርምጃየ፣ ሃይሉ ሻውል፣ ገጽ139)።

አቶ ግርማ እዚህ ላይ አራት ነጥቦችን ላንሳ። አንደኛው፣ አቶ ሃይሉ እንዳሉት የስነምግባር መመሪያው ለኢህአዴግ አለማቀፍ ተቀባይነትን ለማሰጠት ጠቅሟል። ቢያንስ የምርጫ ታዛቢ እንዲላክ አድርጓል። የታዛቢው የመጨረሻ ሪፖርት ባያምርም። ሁለተኛ አቶ ሃይሉ 500 ሰዎችን ከእስር ለማስፈታት ብለው እንጅ ሙሉ በሙሉ አምነውበት ሰነዱን አለመፈረማቸውን ገልጸዋል። ልብ ይበሉ አቶ ግርማ! ከ80 ሚሊዮን እስረኞች የተፈቱት 500 ዎቹ ብቻ ናቸው። 80 ሚሊዮኑ ህዝብ ከእስር እንዲፈታ ስንት የምርጫ ስነምግባር ፊርማዎችን መፈረም ይኖርብን ይሆን? ሶስተኛ ፣ መኢአድ ፊርማውን መፈረሙ ህዝቡ እንዲከፋፈል አድርጎታል። አንድነትስ ተመሳሳይ ነገር አይሰራም ብለው ያስባሉ? የሚከፋፈለውን ህዝብ አንድ ለማድረግ እርስዎ የህዝብ ግንኙነት ስራ ለመስራት ተዘጋጅተዋል? አይርሱ ፖለቲካ 50 በመቶው ገጽታ ( image) ነው። አራተኛ፣ ኢህአዴግ የፊርማውን ስነስርአት ለራሱ የፕሮፓጋንዳ ፍጆታ ተጠቅሞበታል። በድብቅ ይፈረማል የተባለውን ፊርማ ለአደባባይ አብቅቶታል። በአንድነት ላይስ እንዲህ እንደማይደረግ ምን ዋስትና አለ? በህዝቡ ላይ የሚፈጥረውን አሉታዊ ስሜትስ እንዴት ነው መቋቋም የሚቻለው?

ኢ/ር ሃይሉ ሻውል አያበቁም፣ ይቀጥላሉ ” በሌላ በኩል ከህዝቡ ወገን ደግሞ ” ሃይሉ ከዳን” የሚልም ነበር። ውጪ አገር ያሉትማ በኢንተርኔት ላይ ፎቶግራፌን እያገላበጡ እኔ ለቀድሞው ጠ/ሚንስትር አቶ መለስ ዜናዊ እጅ እንደምነሳ አስመስለው ሲዘልፉኝ ከርመዋል።… የሰነዱ መፈረም ለ2002 ምርጫ ዝግጅት ለእኛ አባላት ትንሽ ፋታ ሰጥቷል። ገጠር ሲታገሉ የሰነበቱት እሳት ውስጥ ነበሩ፤ ከፊርማው በሁዋላ ለአጭር ቀናት ቢሆንም በመጠኑ ማስፈራራት ጋብ አለ።” ይሄ ፊርማውን በመፈረም የተገኘ ጥሩ ዜና ነው አቶ ግርማ። ግን ይቀጥል ይሆን ? እንመልከተው፦ ” ምርጫው እየተቃረበ ሲመጣ ግን ሁሉም ነገር ተረሳና ኢህአዴግ የተለመደ ጭቆናውን ማስፋፋት ተያያዘው… መኢአድ ከ2002 ምርጫ ጋር ተያይዞ ከኢህአዴግ ጋር የስነምግባር ደንቡን ከፈረመ በሁዋላ በኢህአዴግ በኩል የተገቡ ቃሎች ባለመተግበራቸው ከጋራ መድረኩ ራሱን አግልሏል። ኢህአዴግ ሁሉም ነገር በቁጥጥር ስር እንዲሆን ፈለገ። በመድረኩም እንነጋገር ብለን የምንጠይቀውን አጀንዳ አይቀበሉትም። የሄ ከሆነ የጋራ ስምምነት የምክክር አይደለም ብለን ተውነው። ስንመለከተው ኢህአዴግ ትእዛዝ የሚያስተላልፍበት መድረክ ስለሆነ ለኢትዮጵያ ዲሞክራሲ ግንባታ ጸር እንጂ ጠቃሚ አለመሆኑን በገሀድ ታየ። ገዢው ፓርቲ በዚህ በጋራ መድረክ አባልነት የቀጠሩትን ፓርቲዎች ደመወዝ መሰል ድጎማ እየከፈለ በቁጥጥር ይዟቸው ቀጥሎአል።በ2002 የስነምግባር ደንቡን ብንፈርምም የእኛ አባሎች ላይ የሚደርሰው ወከባና እንግልት ከዚያ በሁዋላ እየቀጠለ መጣ…” ይሉና አቶ ሀይሉ ይቀጥላሉ…
አቶ ግርማ ካሳ እንግዲህ አንድነትንም ወደዚህ የአራዊቶች ጉባኤ ( ፋቡላ) በመክተት ፓርቲውን በኢህአዴግ ቁጥጥር ስር ሊያደርጉት እና ደሞዝ ሊያሰፍሩለት ያስባሉ ማለት ነው። ለአንድነት ፓርቲ ታጋዮች ካለኝ ከበሬታ አንጻር ፓርቲው በኢህአዴግ ቁጥጥር ስር እንዲሆን አልመኝም። ወርሃዊ ደሞዝ እንዲሰፈርለትም አልሻም።ምክንያቱም እንዲህ አይነቱ አካሄድ ለዲሞክራሲ የሚደረገውን ትግል የሚገድል ነውና ።

መድረክም አንድነትም ፊርማውን እስከዛሬ ባለመፈረማቸው የረባ ውጤት አላገኙ ይሆናል፤ ነገር ግን ” No to cheating!” በማለታቸው ከመኢአድ የተሻለ ክብር እና ድጋፍ አግኝተው እንደነበር አንዘነጋውም።

andu_udjሁለተኛው መከራከሪያዎ አቶ አንዱዓለምንና ናትናኤልን በተመለከተ የሰጠሁትን አስተያየት ተንተርሶ የቀረበ ነው። እኔ አንድነቶችን ከመከፋፈል ማዳን እንጅ፣ እነሱን የመከፋፈል አላማ የለኝም፣ በፍጹም!። ይሄን ስጽፍም ፓርቲውን ከመከፋፈል ለማዳን እንጅ ለሌላ አላማ አይደለም። ወ/ት ብርቱካን እስር ቤት ከገባች በሁዋላ ፓርቲዋ ( አመራሩ) ረስቷት ነበር። እንዴያውም አንዳንዶች “እንኳን ታሰረች” ሳይሉ ሁሉ አልቀረም። ያን ጊዜ ማን ነበር ለብርቱካን አብዝቶ የጮኸው? ዲያስፖራው እና በተለይ ኢሳት አልነበሩምን? የካናዳው ልጅ ተክሌ ” ብርቱካኔ ብረሳሽ ቀኜ ይርሳሽ” ብሎ ዜማ ያወጣላት አምስተርዳም የኢሳት ስቱዲዮ ውስጥ ሆኖ ነው። በወቅቱ የነበሩ ባልደረቦቼ ብርቱካንን በተመለከተ ብዙ ዝግጅቶችን ይሰሩ ነበር። ምንም እንኳ ኢሳት እዚህ ውስጥ እንዲገባ ባልሻም፣ “የኢሳቱ ባልደረባ” እያሉ ስለጻፉና በተዘዋዋሪም እኔ የጻፍኩትን የኢሳት አቋም አድርገው ለማሳየት ስለሞከሩ ትንሽም ብትሆን እውነቱን ለመናገር ይጠቅማል ብየ ስላሰብኩ ነው ኢሳትን መጥቀሴ። ( በነገራችን ላይ ኢሳት የግል አስተያየቴን እንዳልጽፍ እያደረገኝ ነው፣ በግሌ የምጽፈውን አንባቢዎች ” የኢሳት አቋም አድርገው ይወስዱብኝ ይሆን” እያልኩ በመስጋት፣ መጻፍ እየፈለኩ አልጽፍም፤ ለሀሳብ ነጻነት በሚታገል ድርጅት ውስጥ የምሰራ ሰው፣ በዚሁ ድርጅት መልሼ መታፈኔ ይገርመኛል፤ ያፈነኝ ግን ድርጅቱ ሳይሆን፣ ሰዎች ከድርጅቱ ጋር ያያይዙብኝ ይሆን የሚለው ፍርሀት ነው።)

አንዱዓለምና ናትናኤል የብርቱካን እጣ እንዲገጥማቸው አልሻም። በፓርቲው ሸውራራ አካሄድ ስነልቦናቸው እንዲጎዳም አልፈልግም፤ የስነምግባር ደንቡን መፈረም አንዱዓለምን እና ናትናኤልን ከእስር እንደያማያስፈታ አስረግጬ መናገር እችላለሁ። እነሱን የማያስፈታ ሰነድ ደግሞ ጥንቅር ብሎ ይቅር። አንዱዓለምና ናትናኤል በመረሳታቸው እጅግ ያንገበግበኛል። የተቃውሞ ሰልፍ ማድረጉና የገንዘብ መዋጮ የመሰብሰቡ ስራ እንኳ ቆሟል። ይሄ አልበቃ ብሎ በደንብ ባልተጠና የፖለቲካ አካሄድ ስነልቦናቸው ሲጎዳ አይቶ በሁዋላ ከመጸጸት አሁን የሚመስለንን መናገሩ ይጠቅማል እንጅ አይጎዳም።
እነ አንዱዓለም ያልመከሩበት ፖሊሲ በምንም ታዕምር ተግባራዊ መሆን የለበትም! አንዱዓለም የታሰረው ሮቢን አይላንድ አይደለም! ማማከር ይችላል። አንዱዓለም ” አይቃወምም ፣ ይስማማል” በሚል የሚቀርበው መከራከሪያ ብዙ መንገድ አይወስድም።

አንዱአያም አራጌ ” ያልተሄደበት መንገድ” በሚለው መጽሀፉ በገጽ 58 ላይ ስለ አምባገነኖች ባህሪ የጠቀሰው ትክክለኛ ነው እላለሁ ” የአለም ታሪክ እንደሚያሳየው አምባገነኖች በገዛ ፈቃዳቸው ስልጣናቸው ለቀው አያውቁም። እንደውም እነርሱ ስልጣን ከለቀቁ ሀገር እንደሚበታተን፣ ህዝብ እንደሚጨራረሽ የማስፈራሪያ ፕሮፓጋንዳ ይነዛሉ። ፈርተው ያስፈራሉ። ይሄ ባህሪያቸው መሆኑን መረዳትና ያለመዘናጋት መታገል ያስፈልጋል… ፍጹም ሰላማዊ በሆነ መንገድ አሁን ያለውን አገዛዝ ለህዝብ ፈቃድ እንዲገዛ የግድ ማለት ያስፍልጋል።”

እኔ ነገ ስለሚሆነው ነገር ነው የምጽፈው፣ ትክክል መሆንና አለመሆኔን ለማየት ትንሽ ጊዜ መጠበቁ የሚሻል ይመስለኛል። ተሳስቼም ከሆነ ያን ጊዜ ሂሳቤን አወራርዳለሁ። ( በነገራችን ላይ አንድ ጊዜም እንዲሁ ሰማያዊ ፓርቲ በአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ላይ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ማቀዱን በመቃወሜና ቀኑን እንዲቀይረው በመጠየቄ ብዙ ትችቶችን አስተናግጃለሁ፤ በሁዋላ ፓርቲው ( የእኔን ምክር ሰምቶ ይሁን አይሁን አላውቅም) ቀኑን ቀየረው፤ ለወረደብኝ ትችት ግን ሂሳቡን ያወራረደልኝ ሰው አልነበረም፤ ሲጽፉብኝ የነበሩ የማውቃቸው ሰዎች ሳይቀር ድምጻቸውን አጠፉ። እኔ ከተሳሳትኩ ሂሳቤን እንደማወራርድ ቃል እገባለሁ፣ ለመመጻደቅ ሳይሆን ለእድገት ይጠቅማል ብየ ስለማምን ነው።)


(ሰበር ዜና) በትግራይ ክልል በአጽቢ ወንበርታ በሕዝብ እና በአስተዳዳሪዎች መካከል ጸብ ተነሳ፤ 37 ጊዜ ጥይት ተተኩሷል

$
0
0

(አብርሃ ደስታ ከመቀሌ)

(አብርሃ ደስታ ከመቀሌ)

አብርሃ ደስታ ከመቀሌ እንደዘገበው ይህ ዜና እየተዘገበ ባለበት ሰዓት (ሓሙስ 08/05/06 ዓም ከቀኑ 11:30 ጀምሮ) በትግራይ ክልል በአፅቢ ወንበርታ ወረዳ (ጣብያ ሩባ ፈለግ ቁሸት ሕኔቶ) በህዝብና አስተዳዳሪዎች መካከል (በውኃ አጠቃቀም ምክንያት) በተፈጠረ አለመግባባት ሃይለኛ አምባጓሮ ተፈጥሯል። ፖሊሶች ተኩስ ከፍተዋል። እንደ አብርሃ ዘገባ ከ11:30 እስከ 11:40 ሰዓት ባለግዜ ለሰላሳ ሰባት (37) ግዜ ተተኩሷል።

“ምልሻዎች በተጠቀቅ ይገኛሉ።” ያለው የአብርሃ ዘገባ “የመንግስት የሚድያ ሰዎች ሂደቱ እየቀረፁት ነው። የቆሰለ ውይም የሞተ ሰው ስለሞኖሩ ወይ አለመኖሩ በግርግሩ ምክንያት ለማወቅ አልተቻለም። ተኩሱ እየቀጠለ ነው።” ብሏል።

አብርሃ በፌስቡክ ገጹ ጨምሮም በአፅቢ ወንበርታ ወረዳ ህዝብና አስተዳዳሪዎች መካከል ባጋጠመ ግጭት ፖሊስ ቢተኩስም ችግሩ ከፖሊስ አቅም በላይ በመሆኑ አሁን አስተዳደሩ የመከላከያ ሰራዊትን እርዳታ ጠርቷል። አሁን የመንግስት ምልሻዎች በአካባቢው እየተሰማሩ ይገኛሉ። በግጭቱ የተሳተፈው ኗሪ ህዝብ ከሺ በላይ ይሆናል። እስካሁን ድረስ የኗሪው ህዝብ ተወካዮች የነበሩ አራት ሰዎች የት እንደገቡ አይታወቅም። ፖሊሶች ህዝቡን ለመበተን ሃይል ቢጠቀሙም ህዝቡ ግን አራቱ ተወካዮቹ ካልተለቀቁ ላለመበተን አድማ መቷል። ህዝብ እየተሰባሰበ ነው። (የተኩስ ድምፅ በስልክ አስደምጠውኛል)።

በዚህ ዜና ዙሪያ ዘ-ሐበሻ ዘርዘር ያለ መረጃ ከደረሳት ለማቅረብ ትሞክራለች።

ዛሬ በትግራይ ትግል አጽቢ ወንበርታ በፖሊስ እና በሕዝብ መካከል ስለተነሳው ግጭት የአብርሃ ደስታ የቀጥታ (Live) ዘገባዎች

$
0
0

የአፅቢ ግጭት

አብርሃ ደስታበአፅቢ ወንበርታ በተከፈተው ግጭት የመንግስት ፖሊሶች ተኩስ መክፈታቸው፣ አርሶአደሮች መደብደባቸው፣ እንዲሁም አራት የኗሪዎቹ ተወካዮች በሃይል አስረው ወዳልታወቀ አከባቢ መውሰዳቸው ታውቋል። ህዝቡም (የአካባቢው ምልሻዎች ሳይቀሩ) አስራ ሁለት ፖሊሶችና አንድ የመንግስት ምልሻ ከበው አግተው ይዟቸው ቆይተዋል። አራቱ የህዝቡ ተወካዮች እስካልተለቀቁ ድረስ ፖሊሶቹ እንደማይለቀቁ የአርሶ አደሮቹ ተወካዮች አሳውቀው ነበር። አሁን በተደረገ ድርድር አራቱ ተወካዮች ይፈታሉ፣ በህዝቡ ታግተው የነበሩ አስራ ሁለት ፖሊሶችም ይለቀቃሉ። ህዝቡ የአራቱ ሰዎች መለቀቅ እየተጠባበቀ ይገኛል። ፖሊሶቹ ተለቀዋል፤ አራቱ ገብሬዎች እስኪፈቱ ድረስ ግን እዛው ይቆያሉ። መከላከያ ሰራዊት ጥሪ ቢቀርብላቸውም እስካሁን ድረስ (እስከ ምሽቱ 1:30) ባካባቢው አልደረሱም።

ድርድሩ አልተሳካም፡ ተኩስ ተከፍቷል ህዝብ እየተደበደበ ነው

ፖሊሶች አራት የኗሪዎቹ ተወካዮች በሃይል ሲወስዱ የአፅቢ ህዝብም አስራ አራት ፖሊሶችና አንድ ምልሻ አግተው ነበር። ህዝቡ ፖሊሶቹ እንዲለቅ አስተዳደሩ ደግሞ አራቱ ተወካዮች እንዲለቅ ድርድር ተጀምሮ ነበር። በድርድሩ መሃል የወረዳው አስተዳደር አዲስ ሃይል በመጥራት (ከሌላ ወረዳና ከክልል አስተዳደር የፀጥታ ሃይሎች በመላክ) ህዝብ በተሰበሰበብት መተኮስ ጀመሩ (ከምሽቱ 2:30-2:56)። ምልሻዎቹና ወታደሮቹ የታገቱትን ፖሊሶች ለማስለቀቅ እስከ ሁለት መቶ (በኗሪዎቹ ግምት መሰረት) የሚደርስ ጥይት በመተኮስ የታገቱት ፖሊሶችን ማስለቀቅ ችለዋል። እስከ ሁለት ሺ የሚጠጋ ህዝብ ተሰብስቦ እየጨኸ ይገኛል። አሁን (ከምሽቱ ሦስት ሰዓት) ብዙ ምልሻዎች የጫኑ ብዙ መኪኖች ወደ አከባቢው እየገቡ ነው። በሌላ አቅጣጫ (በስተ ሰሜን በኩል) ደግሞ ሌሎች ብዙ መኪኖች እየገቡ ነው (ምልሻ ወይ ፖሊስ ወይ ወታደሮች መሆናቸው ግን በትክክል አይታወቁም)። ህዝብ በዱላ መደብደብ ጀምረዋል። ህዝቡ እየጮኸና ፈጣሪው እየለመነ ነው። የህዝቡ ጩኸትና ለቅሶ በስልክ መስማት ችያለሁ። እያናግሩኝ ያሉ ሰዎችም መረጋጋት ተስኗቸዋል። አሁን ከምሽቱ 3:05 ሁነዋል።

ተኩሱ ቆሟል፣ ምልሻዎቹ ለሁለት ተከፍሏል፣ ወታደሮች ገብተዋል

ታግተው የነበሩ የመንግስት ፖሊሶች ሌሎች ፖሊሶችና ምልሻዎች በከፈቱት ተኩስ ተለቀዋል። አሁን ህዝቡና የመንግስት ምልሻዎች በሜትሮች ርቀት ተለያይተው ማዶ ለማዶ ይተያያሉ። የአፅቢ ወንበርታ ተወላጆች የሆኑ የመንግስት ምልሻዎች የመንግስት አካላትን ከድተው ከህዝቡ ጎን ተሰልፈዋል (ከአንድ ምልሻ በስተቀር ሁሉም የአፅቢ ወንበርታ ምልሻዎች ከህዝቡ ጎን ይገኛሉ)። ሁለቱም ምልሻዎች (የአፅቢ ወንበርታና አስተዳደሩ ከሌላ ወረዳ ያስመጣቸው) ተፋጠዋል። አሁን 3: 15 በደራ ጣብያ ገብረኪዳን ልዩ ስሙ “አፅገበት” የሚባል ቦታ የነበሩ ወታደሮች (መከላከያ ሰራዊት) ባከባቢው ደርሰዋል። እስካሁን ምንም ዓይነት እርምጃ አልጀመሩም። ፀጥታ ሰፍነዋል። ህዝቡ ግን እንደተሰበሰበ አለ። “ተወካዮቻችን ፍቱልን” እያለ ይገኛል። አሁን ከምሽቱ 3:24 ነው።

ወታደሮቹ ህዝብ እንዲበተን ጥሪ አቀረቡ

በሰባት መኪኖች ሙሉ ተጭነው ወታደሮች ገብተው አከባቢው ተቆጣጥረውታል። “የዞን አስተዳዳሪዎች ነን” ያሉ ባለስልጣናት ህዝቡ “የአሸባሪነት ተግባር” እያከናወነ መሆኑ በርቀት ተናግረዋል። ህዝቡም “አሸባሪዎች እናንተ ናች ሁ፤ ልጆቻችን ፍቱልን” እያለ ሲጮህ ነበር። በመጨረሻም ወታደሮቹ ህዝቡ እንዲበተን ማስጠንቀቅያ ቢሰጡም አራቱ የአፅቢ ወንበርታ ልጆች ካልተፈቱ እንደማይበተን አስታውቀዋል። መከላከያውና አስተዳዳሪዎቹ ቢያስፈራሩም ህዝቡ ግን ለመበተን ፍቃደኛ አልሆነም። ዘጋቢዎቼ ወደ ቤታቸው እየተንቀሳቀሱ ነው። ነገ እንገናኝ። አሁን ከምሽቱ 3:55 ነው። ቸር ያሰማን።

አቡነ ማቲያስ ቤተ ክርስቲያኒቱን ከብዝበዛ በማዳን ታሪክ እንዲሠሩ ተጠየቁ

$
0
0

ሰንደቅ ጋዜጣ ከአዲስ አበባ እንደዘገበው፦

‹‹ዐይናችን፣ ጆሯችንና ልባችን የቤተ ክርስቲያናችንን ህልውና በሚወስነው የአደረጃጀትና አሠራር ለውጥ ተግባራዊነት ላይ ነው፤ የቤተ ክርስቲያናችን ትንሣኤ ደርሷል ብለን እናምናለን፡፡›› /ምእመናን/

‹‹ከእውነተኛ የቤተ ክርስቲያኒቷ ጥቅም ወዲያና ወዲህ አልልም፤ አትጠራጠሩ! ሕጉ የጠራ ኾኖ በትክክሉ ይወጣል፤ ቤተ ክርስቲያናችን ወደቀደመ ክብሯ ትመለሳለች፡፡›› /ፓትርያርኩ/

‹‹የቤተ ክርስቲያናችን አስተዳደር ከመሠረታዊው ተልእኮው ጋራ ያልተቀናጀ ከመኾኑም በላይ በወገንተኝነትና በሙስና የሚፈጸሙ የተለያዩ የሥነ ምግባር ብልሽቶች በስፋት የሚንጸባረቁበት ኾኖ ይስተዋላል፡፡ ይህን ከቤተ ክርስቲያኒቷ ክብርና ቅድስና ጋራ የማይጣጣም ሒደት ቅዱስ ሲኖዶሱ አስቸኳይ ርምጃ ሊወስድበት ይገባል፡፡ አስፈላጊው እርማት በወቅቱ ሳይደረግ በመቅረቱ፣ ምእመናኑ በቤተ ክርስቲያኒቱ አመራር ላይ እምነት ማጣትን እያሳደረ ኹኔታውም እየተባባሰ ሲሔድ ይታያል፡፡ ስለዚህ ታሪክ እንዳይፈርድብን ካህናቱንና ምእመናኑን በማስተባበር አስቸኳይ የእርምት ርምጃ መውሰድ አስፈላጊ ይኾናል፡፡››

“እንደ አቡነ ጳውሎስ ነጭ ልብስ አልለብስም” – አቡነ ማቲያስ (ሙሉ ቃለ ምልልሱን ያድምጡ)
ይህ ጥቅስ አቡነ ማትያስ ስድስተኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ኾነው ከተሾሙ በኋላ የመጀመሪያቸውን የቅ/ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ሁለተኛ ዓመታዊ ስብሰባ ግንቦት 22 ቀን 2006 ዓ.ም. በንግግር ሲከፍቱ ካሰሙት ቃል የተወሰደ ነው፡፡
ፓትርያርኩ ‹‹የቤተ ክርስቲያኒቱን ስም ለመጠበቅና የቀደመ ክብሯን ለመመለስ›› ሥር ነቀል የለውጥ ርምጃዎች እንደሚወስዱ ባስታወቁበት በዚያ የመክፈቻ ንግግራቸው÷ የቅ/ሲኖዶሱ ምልዓተ ጉባኤ ብልሹ አሠራርን ለማረምና ለማስወገድ፣ አስተዳደሩን በአዲስ መልክ ለማዋቀርና ለፋይናንስ አያያዙ ዘመናዊነት፣ ግልጽነትና ተጠያቂነት ያለው አደረጃጀት ለመዘርጋት የሚያስችሉ ሦስት መሠረታዊ ርምጃዎችን እንደሚወስድ አመልክተው ነበር፡፡

አቡነ ማትያስ የቤተ ክርስቲያኒቱን ጤናማ ሒደት የሚወስኑ ናቸው ባሏቸው ሦስቱ መሠረታዊ ርምጃዎች ጋራ በተለይም ልዩ ሀገረ ስብከታቸው በኾነው በአዲስ አበባ ሀ/ስብከት እየገዘፈና እየተመሰቃቀለ የመጣውን የመልካም አስተዳደር ዕጦትም በአደረጃጀቱና አሠራር ለውጥ ማስተካከል አስፈላጊ መኾኑን አሥምረውበት ነበር፡፡

ሓላፊነትና ተጠያቂነት ያለበት ግልጽ የአስተዳደር ሥርዐት የሚሰፍንበትን የለውጥ መሠረት በአስቸኳይ ማስቀመጥና አቅጣጫውን መቀየስ ‹‹በእግዚአብሔር፣ በታሪክና በመጪው ትውልድ ፊት›› ኹልጊዜ በሚዛን እየተመዘነ እንደሚኖር መዘንጋት እንደሌለበት ፓትርያርኩ ያሳሰቡት ለቅ/ሲኖዶሱ አባላት ጭምር ነበር፡፡

በስብሰባው መጨረሻ ግንቦት 30 ቀን 2006 ዓ.ም. ለብዙኃን መገናኛ ግልጽ የተደረገው የቅዱስ ሲኖዶሱ ምልዓተ ጉባኤ መግለጫ÷ በየቀኑ በለውጥ ጎዳና ከሚራመደው ዓለም በተሻለና በበለጠ መንፈሳዊና አእምሯዊ ጥበብ ሕዝበ ክርስቲያኑን ለመምራት፣ ለማስተማርና ለማገልገል ዕንቅፋት የኾኑ ችግሮችን በመለየት ዓበይት ውሳኔዎች መተላለፋቸው የተነገረበት ነበር፡፡ ከእነርሱም መካከል፣ የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት በመልካም አስተዳደር፣ በፋይናንስ አያያዝና በሰው ኃይል አመዳደብ የሕግ የበላይነትን አክብሮ የሚሠራበት የአደረጃጀትና አሠራር ለውጥ በቋሚ ሲኖዶሱና በፓትርያርኩ ጥብቅ ክትትል እንደሚደረግበት የሚያመለክተው ይገኝበታል፡፡

የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ለሌሎች አህጉረ ስብከት በሞዴልነት የሚጠቀስበት ነው የተባለው የአደረጃጀትና አሠራር ለውጥ ጥናትም በፓትርያርኩ አባታዊ መመሪያ በተሰጠውና በሀ/ስብከቱ የፓትርያርኩ ረዳት ሊቀ ጳጳስ ኾነው በምልዓተ ጉባኤው ውሳኔ በተሾሙት አቡነ እስጢፋኖስ የቅርብ ክትትል በተደረገለት የባለሞያ ቡድን ተካሒዷል፡፡ 13 ጥራዞችና ከአንድ ሺሕ በላይ አጠቃላይ ገጾች ያሉት የአደረጃጀትና አሠራር ለውጥ ጥናቱ፣ በጥቅምት ወር በተካሔደው የቅ/ሲኖዶሱ ምልዓተ ጉባኤ የመጀመሪያ ዓመታዊ ስብሰባ ላይ ሙሉ ይዘቱን በሚወክል ስላይድ ቀርቦ መገምገሙ ተገልጧል፡፡
ምልዓተ ጉባኤው በግምገማው፣ የቤተ ክርስቲያኒቱ መሠረታዊ ተልእኮ ለኾኑት ክህነታዊና የስብከተ ወንጌል ተግባራት ቅድሚያ በመስጠት÷ ሥራና ሠራተኛን እንዲገናኝ፣ ደመወዝና ሞያ በሐቅ እንዲነጻጸር፣ ተቀባይነትና ተአማኒነት ያለው የገንዘብ ፍሰት እንዲኖርና የራስ አገዝ የልማት እንቅስቃሴ እንዲፋጠን ያስችላል ለተባለው የመዋቅርና አሠራር ጥናት ተግባራዊነት አቅጣጫ ሰጥቷል፡፡ ጥናቱ ወደታች ወርዶ በማኅበረ ካህናት፣ በማኅበረ ምእመናንና በሰንበት ት/ቤቶች ወጣቶች ውይይት ዳብሮ፣ በውይይቱ በተገኘው ግብአት ተስተካክሎ ለቋሚ ሲኖዶስ እንዲቀርብና ቋሚ ሲኖዶሱም ዓይቶና ተመልክቶ በሥራ ላይ እንዲያውል ነው ምልዓተ ጉባኤው የሰጠው አቅጣጫ፡፡

ከትላንት በስቲያ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት አዳራሽ ከአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ገዳማትና አድባራት የተውጣጡና ከፓትርያርኩ ጋራ የተነጋገሩ ምእመናን ለአደረጃጀትና አሠራር ለውጥ ጥናቱ ያላቸውን ድጋፍና ለተግባራዊነቱም የሚኖራቸውን አጋርነት ገልጸዋል፡፡ ሀ/ስብከቱ ከኅዳር 14 – ታኅሣሥ 17 ቀን 2006 ዓ.ም. ድረስ ቁጥራቸው ከ2700 በላይ የኾኑ አለቆችን፣ የአስተዳደር ሠራተኞችን፣ ካህናትን፣ ሊቃውንትን፣ የሰንበት ት/ቤቶች ወጣቶችንና ምእመናንን በአደረጃጀትና አሠራር ጥናት ሰነዱ ላይ ማወያየቱን የገለጹት ምእመናኑ፣ የቤተ ክርስቲያኒቱን መልካም ስምና ዝና ወደ ቀደመ የክብር ቦታው ለመመለስ የሚያስችል ነው ያሉት የአደረጃጀትና አሠራር ጥናቱ በቅ/ሲኖዶሱ ውሳኔ መሠረት በውይይቱ በተሰበሰበው ግብአት ተስተካክሎና በቋሚ ሲኖዶሱ ጸድቆ ተግባር ላይ እንዲውል ጠይቀዋል፡፡
ማንኛውም ለውጥ በተለይም የሥራ አመራር ለውጥ የራሱ ተግዳሮቶች እንዳሉት የተናገሩት ከደብረ ሲና እግዚአብሔር አብ ቤተ ክርስቲያን የመጡት የደብሩ ሰበካ ጉባኤ ምክትል ሊቀ መንበር አቶ ዮናስ፣ በአደረጃጀትና አሠራር ጥናቱ ጥቂቶች የሚያሰሙት ተቃውሞ መታየት ያለበት በትግበራ ሒደት በሚቋቋመው የቅሬታ ኮሚቴ መኾኑን አስረድተዋል፡፡ በለውጥ ሥራ አመራር ከተለመደው በተለየ ከትግበራ በፊት በመዋቅር፣ አደረጃጀትና አሠራር ለውጥ ጥናቱ የጎደለው እንዲሟላ፣ የጠመመው እንዲቃና ቤተ ክርስቲያኒቱ ዕድል መስጠቷን ሰበብ አስባብ እየፈለጉና ምክንያት እየለጠፉ ለውጠን ለማሰናከል የሚሞክሩ አካላት መኖራቸውን ገልጸዋል፡፡ ተቃዋሞው ለውጡን ከራስ ጥቅም አንጻር ብቻ ከመመልከት የሚመነጭ መኾኑን ያብራሩት አቶ ዮናስ፣ ‹‹የእኛን ልብስ ለብሰው እኛን መስለው የገቡ ተቃዋሚዎች እኛ ለልጆቻችን ለማስተላለፍ የምንፈልጋትን ቤተ ክርስቲያን አይወክሉም፤›› ብለዋል፤ በተቃዋሚዎቹ ግፊት የአደረጃጀትና አሠራር ጥናቱ በዐዲስ መልክ ለመገምገም የተላለፈው ውሳኔም በጥንቃቄና በጥልቀት እንዲታይ ፓትርያርኩን አደራ ብለዋል፡፡
የአደረጃጀትና አሠራር ለውጥ ጥናቱ ወጣቶችም ሽማግሌዎችም ወይዛዝርትም የሚስማሙበትና በቤተ ክርስቲያኒቱ የተንሰራፋውን የአስተዳደር ብልሽትና የገንዘብ ብዝበዛ እንደሚያስቆም ጽኑ እምነት እንዳላቸው የገለጹት ሌላው አስተያየት ሰጭ አቶ ከበደ ሙላት ከመንበረ መንግሥት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም የመጡ ናቸው፡፡ የቤተ ክርስቲያኒቱ ቃለ ዐዋዲ ለመጀመሪያ ጊዜ በ1965 ዓ.ም. ሲረቀቅ ከአርቃቂዎቹ አንዱ እንደነበሩ የተናገሩት አዛውንቱ ምእመን አቶ ከበደ፣ ‹‹ዛሬ ያ ቃለ ዐዋዲና እኔ አርጅተናል፤ ጊዜው የሚጠይቀው አዲስ መዋቅር ያስፈልገናል፤ አዲስ መዋቅር ባለመኖሩ ምክንያት ቤተ ክርስቲያናችን ላይ ብዙ ጉዳት እየደረሰ ሲያንገበግበን ኖሯል፤›› በማለት የተሰማቸውን ቁጭት ገልጸዋል፡፡

የአደረጃጀትና የአሠራር ለውጥ ጥናቱ የተረቀቀው አዲስ መዋቅር በሚያስፈልግበት ወቅት መኾኑን የጠቀሱት አቶ ከበደ፣ በአስተዳደር ብልሽቱ ራሳቸውን ያበለጸጉ አካላት በለውጡ በሚቋረጥባቸው ሕገ ወጥ ጥቅም ክፉ ወሬ ማስወራታቸው አስገራሚ አይደለም ብለዋል፡፡ አያይዘውም ‹‹እንኳንስ ከቤተ ክህነትና ከቤተ መንግሥትም ቢኾን ለአገርና ለሕዝብ የሚጠቅም ነገር ሲነሣ ኹሉም እልል ብሎ አይቀበልም›› ያሉት አቶ ከበደ፣ ‹‹በኢትዮጵያ ምዕራፍ ውስጥ ለስምዎም ለታሪክዎም ብቅ ብሎ የሚታይ ነው›› ያሉትን የአደረጃጀትና የአሠራር ለውጥ ፓትርያርኩ ደፍረው እንዲያስፈጽሙትና ቤተ ክርስቲያኒቷን ከብዝበዛ በማዳን ታሪክ እንዲሠሩ ተማፅነዋቸዋል፡፡ ‹‹እግዚአብሔር ነው አደራ የጣለብዎት፤ ሕዝቡም አደራ ጥሎብዎታል፤ ያንን ሕዝቡ የጣለብዎትን አደራ ከፍጻሜ ለማድረስ ብርታቱን ይስጥዎት፡፡››
የአደረጃጀትና የአሠራር ለውጥ ጥናቱ በሕይወት ያሉትም የሌሉትም በርካታ ምእመናን የጸሎትና እንባ ውጤት ነው ለማለት እንደሚደፍሩ የተናገሩት ወ/ሮ ቅድስት የተባሉ ምእመንት፣ በመንፈሳዊውም በሥጋዊውም ስለት በተሳሉ ባለሞያዎች የተዘጋጀ ነው ባሉት ጥናት ‹‹የቤተ ክርስቲያናችን ትንሣኤ ደርሷል ብለን እናምናለን፤›› ብለዋል፡፡ በጥናቱ የቤተ ክርስቲያኒቱን ችግር በሚገባ ማወቃቸውን ያስረዱት ወ/ሮ ቅድስት÷ ከመቼውም ጊዜ በበለጠ የምእመኑ ዐይን፣ ጆሮና ልብ ለቤተ ክርስቲያን ህልውናና የቀረው ሕዝቧ እንዳይበተን ወሳኝ ነው ባሉት የጥናቱ ተግባራዊነት ላይ መኾኑን ገልጸዋል፤ ያለአንዳች ተቃውሞም በአስቸኳይ ተግባራዊ እንዲኾንም ፓትርያርኩን ጠይቀዋል፡፡

ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ ምእመናኑ ለአደረጃጀትና አሠራር ለውጥ ጥናቱ ተግባራዊነት ያላቸውን ስጋት በመግለጻቸው ደስ መሰኘታቸውን አስታውቀዋል፡፡ አንድ የተወሰነ ቡድኑ ያጠናው የሕግ ረቂቅ ከቤተ ክርስቲያን ባህልና ቋንቋ አንጻር እንዲታይ መደረጉ ሕጉ የበለጠ እንዲጠራና እንዲጠነክር ያደርገዋል እንጂ እንደማያዳክመው በማረጋገጥ የዘመኑ ምሁራንና ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ያሉበት ኮሚቴ ዳግመኛ እንዲያየው መሠየሙን ለምእመናኑ አስታውቀዋል፡፡ የአደረጃጀትና የአሠራር ለውጥ ጥናቱ ከቀረበው ይዘት ተዳክሞና የቤተ ክርስቲያኒቱን ጥቅም የሚጎዳ ኾኖ ቢመጣ እንደማይቀበሉትም ለምእመናኑ በተደጋጋሚ ቃል ገብተዋል፡፡

‹‹ከዚኽም ከዚያም ይምጣ፤ ኹሉም የሚናገረውን አዳምጣለኹ፤ ኹሉም የሚናገረውን እያስተናገድኹ ከቤተ ክርስቲያኒቱ ጥቅም ግን ወዲያና ወዲህ አልልም፤›› ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ ፍላጎታቸው ቤተ ክርስቲያኒቱ ትክክለኛ መሥመሯን እንድትይዝ፣ ወደ ጥንቱ ቅድስናዋና ንጽሕናዋ እንድትመለስ በመኾኑ የአደረጃጀትና የአሠራር ጥናቱ ከደረሰበት ወደ ኋላ የሚመለስበት ምንም ምክንያት እንደማይኖርና ወደኋላ መመለስ ዘበት ነው ብለዋል፡፡ ‹‹አትጠራጠሩ! ምሁራኑም ይዩት፤ ሊቃውንቱም ይዩት፤ ሕጉ የጠራ ኾኖ በትክክሉ ይወጣል፤ ቤተ ክርስቲያናችን ወደ ቀደመ ክብሯ ትመለሳለች፤›› በማለት ለተግባራዊነቱ የምእመናኑን ድጋፍና እገዛ ጠይቀዋል፡፡

መሬታቸው ለህንድ ሻይ ልማት ኩባንያ መሰጠቱን የተቃወሙ ኢትዮጵያውያን ከመንግስት ዱላ ገጠማቸው

$
0
0

ሰንደቅ ጋዜጣ ከአዲስ አበባ እንደዘገበው፦

በጋምቤላ እና በሸካ አዋሳኝ ክልል ውስጥ ከሚገኙ ህዝቦች መካከል 100 ሺ የሚሆኑ የሸካ ተወላጆች 3012 የሚደርስ ሄክታር መሬት ከአካባቢያችን ጥብቅ ደን ተወስዶ ቨርዳንት ሃርቨስት አግሮ ኢንዱስትሪ ለተሰኘ የህንድ ኩባንያ መሰጠቱን በመቃወማችን ጉዳት እየደረሰብን ነው ሲሉ የብሔሩ ተወላጆች ምሬታቸውን ለሰንደቅ ጋዜጣ ገለጹ። በክልሉ እንደተካተቱት ሌሎች አምስት ብሔሮች ስድስተኛ ሆነን አልተመዘገብንም፤ ልጆቻችን በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው ማስተማር አልቻልንም፤ በክልሉ ተገቢ የሆነ የመሰረተ ልማት ግንባታ ተጠቃሚ አልሆነም፤ ለዚህም አካባቢው የሚካሄደውን ኢንቨስትመንት ተቃዋሚ እንደሆነ ተደርጎ መታሰቡ አግባብ አለመሆኑን የሸካ ህዝቦች ተወካይ በመሆን አቤቱታቸውን ለማሰማት የመጡት አቶ ታምሩ አምበሉ አስረድተዋል።
tea
በጋምቤላ ክልል የመጀንግ ዞን አመራር የሆኑት አቶ ይማም ቃሪስ በበኩላቸው ይህንን አቤቱታ የሚያሰሙት ጥቂት ግለሰቦች የራሳቸውን ፖለቲካዊ ፍላጎት ያላቸውና ተጨፈጨፈ የሚሉትም ጥብቅ ደን ሳይሆን ቁጥቋጦ ነው ብለዋል። አክለውም እንደጋምቤላ ክልላዊ መንግስት ደንብና አሰራር መሰረት የህንዱ ኩባንያ መሬቱን እንዲያለማ መፍቀዳችን ትክክል ነው ይላሉ።

የሸካ ህዝቦች ለዘመናት ጠብቀው ባቆዩት ጥብቅ ደን ውስጥ ማር በማምረት እንደሚተዳደሩ ያስረዱት አቤቱታ አቅራቢዎቹ የአካባቢውን ህዝብ ባላማከለ መልኩ ጥብቅ ደኑን እንዲጨፈጨፍ ማድረግ ከውስጡ የሚመነጩትን ወንዞች መጉዳት ነው ሲሉ ከአካባቢ ጥበቃ አንፃር መፍትሄ ሊበጅለት ይገባል ይላሉ። ይህንንም አስመልክተው በ1999 ዓ.ም የብሔር ብሔረሰቦች መብት ተጠቃሚዎች አይደለንም በሚል ለፌዴሬሽን ምክር ቤት የ1200 ሰዎችን ፊርማ አሰባስበው የመብት ጥያቄ አቅርበው እንደነበር በማስታወስ፤ የመብት ጥያቄያቸው ሳይመለስ እስከ 2002 ዓ.ም መጠበቃቸውንና አልፎም የህዝቡን ዋና መተዳደሪያ የሆነውን ጥብቅ ደን ለማጥፋት ምክንያት ሆኖብናል ይላሉ።

በተለይም የህንዱ ቨርደንት ሃርቨስት አግሮ ኢንዱስትሪ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር በጋምቤላ ህዝቦች ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት መዠንገር ዞን ጎደሬ ወረዳ የጎማሬ ቀበሌ አስተዳደር በሸካ ክልል ውስጥ ከፍተኛ ጥበቃ የሚደረግለትን 3012 ሄክታር ጥብቅ ደን ለሻይ ልማት መፈቀዱ አግባብ አይደለም ሲሉ በተለያዩ መንገዶች አቤቱታቸውን አሰምተዋል። “እኛ ምንም አይነት ኢንቨስትመንትን የመቃወም ኀሳብ እንደሌለን እንዲታወቅልን እንፈልጋለን” የሚሉት የህዝቡ ተወካዮችና አቤቱታ አቅራቢዎች፤ ይህ ቦታ አማራጭ ቢፈለግለት ይሻላል። ደን ከጠፋ ዘራችን የአኗኗር ባህላችን ሁሉ ይጠፋል የሚል እንደሆነም ተናግረዋል። ያም ሆኖ ለኩባንያው ግንባታ ሲባል በ67 ሄክታር ላይ የሚገኝ ደን ተጨፍጭፎ 1640 በላይ ጣውላዎች ወጥተው ተገኝተዋል ሲሉ አስረድተዋል።

ይህን ጉዳይ አስመልክቶ የቀድሞው የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት አቶ ግርማ ወ/ጊዮርጊስ በወቅቱ ለአካባቢ ጥበቃ ኃላፊ በፃፉት ደብዳቤ፤ በጋምቤላ አካባቢ ያለውን የተፈጥሮ ደን ያለበት ሰፊ መሬት ደኑ በጣም ጥቅጥቅ ያለና ለአየር ጥበቃ ሊቆይ የሚገባው ሆኖ ሳለ ለሻይ ልማት ኢንቨስትመንት ተሰጥቶ ሊመነጠር ስለመሆኑ የአካባቢው ህዝብ ይህን ችግር ለማሳወቅ ሰዎች ወክሎ መላኩን በመግለፅ አስቸኳይ እርምጃ እንዲወስድ ማሳሰባቸውን ተናግረዋል።

በበርካታ ባለሙያዎች ጥናት ተደርጎለት የአካባቢው የደን ሀብት እንዲጠበቅ ቢወሰንም አሁንም ድረስ የተሰራ ስራ አለመኖሩንና የአካባቢው ህዝብም ስጋት ላይ መሆኑን በመጥቀስ ህዝብና መንግስት ጉዳያችን ተረድቶ ጥብቁን ደን ከጥፋት ይከላከለው ዘንድ ድምጻችንን እናሰማለን ብለዋል፤ አቤቱታ አቅራቢዎቹ።
የመጀንግ ዞን አመራር በሰጡት ምላሽ ቦታው ጥናት ተደርጎበት ለልማት የተመራ መሆኑን በመግለፅ፤ ኩባንያው የሻይ ልማት ስራውን ከ2003 ዓ.ም ጀምሮ እየሰራ እንደሚገኝና ነገር ግን ጥቂት የግል ፍላጎት ያላቸው ግሰቦች እንቅፋት የሚሆን እንቅስቃሴ አድርገዋል ሲሉ ይወቅሳሉ።

ቴዲ አፍሮ የቅኔ ዕንቡጥ –ለእናቱ ልዩ ዓርማ ነው!

$
0
0

ከሥርጉተ ሥላሴ 16.01.2014 (ሲዊዘርላንድ – ዙሪክ)

“የሰው ልብ መንገዱን ያዘጋጃል እግዚአብሄር፤ ግን አካሄዱን ያቃናለታል“ (ምሳሌ ምዕራፍ 16 ቁጥር 9 )

የሀገሬን ክብር አዝልቀህ – ልታደምቅ
ታጥቀህ ተነስተኃል – አንተ የቅኝት ብርቅ፤
ራዕይ — አብነት።
እማን ከፍ አድርገህ ልታሸልማተኝ ጌጥ
ዕውቅናዋ ፈክቶ ዓለምን ልትመስጥ።
ተግተህ ትሠራለህ – አንተ የቅኔ ዕንቡጥ፤
የነፃነት ቃና – የትውልዳችን – ፈርጥ!

ባልባለቀው መንፈሴ – ቴዴ አፍሮ የተስፋዬ ፀሐይ ነው። ማህተም አለበት!
teddy afro
ዋና በር … ከሳቢያ ጥረት ምክንያታዊ፤ ከሳቢያ ተኮር ድካምም ምክንያታዊ ተግባራት የድል ዋዜማ ናቸው። ምክንያቱም የችግሩን ምንጭ ከሥሩ የሚያደርቀው በምክንያታዊና መሬት በረገጠ ተግባር ብቻ ጨለማው ነግቶ፤ የምሥራች ለነፃነት የመሸለም ስበታቸው ሆነ አስገዳጅነታቸው ጉልበታም ናቸው። የሚያስቀሩት ፍርፋሪ ስለማይኖርም ዘላቂ ድህነት ያስገኛሉ። የመፍትሄ መንገድ ጠራጊ የችግሩን ሳቢያ ማወቁ ሳይሆን ይልቁንም ምክንያቱን በሚገባ በልቶ ያማያዳግም መለስ ከመስጠቱ ላይ ነው። ምክንያት ተኮር የምርምር ተግባር በሸታውን ያገኛል። ህመሙን ከሥሩም ይነቅላል። ሳቢያ ተኮር እርጃዎች አቅመቢስ በመሆናቸው፤ ዋስትና የማይሰጡ ማስታገሻ ናቸው፤ አዘናጊ ልፈስፍስ ዝልቦ መንገዶች ናቸው!

ምልሰት፣ እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2008፤ በኢትዮ – አፍሪካዊው የቅኔው ልዑል በብላቴ ሎሬት ጸጋዬ ሥም በሰዬምኩት ማህበራዊ ድህረ ገጽ፤ እንዲሁም በጸጋዬ ድምጽ ራድዮ ፕሮግራሜ ቃሊቲ ውስጥ ለነበረው ታናሼ „ሥምን መላዕክ ያወጣዋል“ በሚል አንድ መጣጥፍ መጻፌን ብቻ ሳይሆን በድምፄም ማቅረቤን አስታውሳለሁ። ልቤ ውስጥ የገባ የቅኔ ቀንበጥ ነበርና ቴዲ አፍሮ። ስለ ወጣቱ ከያኒ – ገጣሚ – ዜመኛ – ድምጽ ቃና፤ እንዲሁም የአቀራረብ ብቃት- በዛ ጹሑፌ ላይ ሥራዎቹ ተተርጓሚነታቸው (interpretable) እንዲሁም ተዋራራሽነታቸውን በስፋት ነበር የገለጽኩት።

የድርሻዬን ይባልለት – ስለ ይፈልቃል ገና!

ዛሬም ደግሞ ትንሽዬ የግል ዕይታዬን ለማለት ትክሻዬን ለሚወርደው ዱላ አስመችቼ ለመቀበል ቆረጥኩና እንዲህ ልል ነው። በዚህ ፈታኛ ወቅት መቆስቋሻ የሚያስፈልግበት ሳይሆን ገብቶ መርመጥመጥም ይጥማል። ፈተና ተፈልጎ የማይገኝ ከተገኘ ግን አንጥሮ የሚያሳምር ሜሮን ነው። አባቶቻችን ፈተናቸው ሲዘገይ ወይንም ፈተና ቸልም ብሎ ሲረሳቸው ሁለት ሶስት ሱባኤ ይይዛሉ። እኔው የእነሱ ህይውት ኑሮኝ በመንፈሳዊ ዘርፍ ብጣቂ ዘር ባይኖረኝም። በገኃዱ ዓለም ግን እኔም ፈተና ሥልጡን አድርጎ ቀርፆኛል። ተላምጄዋለሁ። ከጋሼ ጸጋዬ ፍቅር መንጭቶ በውሰድኩት የድህረ ገጽ ስያሜ ብርትዬም ታስራ በነበረችበት ውቅት ተግቼ በብዕር ብቻ ሳይሆን በተገኘው አጋጣሜ ሁሉ መፋለሜ፤ እኔን ቢደቁሰኝም፤ ክሱ ሀገር ምድሩን ቢያዳርስም እኔኑ ቢያደቃኝም፤ የወረደው ማዕት …. ግን ኃይልና ብርታት ሰጥቶት ከዛ በኋላ የተከደኑ ብዙ ሲሳዮችን እንድከውን አምላኬ ረዳኝ። ቀን ሲወጣ ታላቋ ኢትዮጵያ ትንቆጠቆጥበታለች። አዎን! እኔ በምኖርበት ሀገር ኢትዮጵያ የምትባል ታላቅ ሀገር ጸጋዬ የሚባል የኢትዮ አፍሪካዊ ፈላስፋ ዕውቅናቸው ሙሉዑ እንዲሆን ሆኗል። የኦነግን ተልዕኮ ለማሳካት ሆነ በቅዱስ ወንጌል ሰባኪ ተብዬ ክስ ተመስርቶብኝ ነበር። ለዛውም ለአንስት ባልተሰጠኝ ጸጋ ብከሰስም አሸነፍኩ። ተመስገን። እድሜ ለሚሹንግ ዩንቨርስቲ ታላቅ ሚዛናዊ ኢትዮጵያዊ ሙሑር። ብዕራቸው ከእሥር አስለቀቀን በጋራ ….. ሰላምም አሰፉን። ምስክርነታቸው አንጀት አርስ ነበርና። አለን ሚዲያዎቼ እና እኔ እንደ አመረብን። ፈቃዱን ለሰጠኝ ለራዲዮ ፕሮግራሙ ቲም የተሰጠው አጥጋቢ ጥሁፍም በእጄ ላይ ይገኛል።

እግዚአብሄር ይመስገን የ21ኛው ምዕተ ዓመት ታላቅ ሥራ የሆነውን የደራሲ አቶ ምስብእክ ወርቁን „ዴርቶ ጋዳን“ ረቂቅ ወጥ ሥራ ጭብጥ ሳስብ፤ የቴዲን በጋሼ ጸጋዬ ዙሪያ የሰራቸውን ድንቅ ጽጌረዳዊ ተግባር በመንፈሴ ደም ሳዘዋውር፤ የመንፈስ ቋሚ ትውፊታችን በዕድሜ ተከታዮቼ እንዲህ ፋፍቶ ሳልሞት ቆሜ በህይወት በማዬቴ እግዜአብሄር ይመስገን። አሜን! የኔ ታናሾችን እግዚአብሄር ያኑልርኝ። ደሜ ቋንቋ ቢኖረው የሚናገረው ቋንቋ ጸጋዬ በሆነ ነበር – ተግባባን?! እኔ ጋሼ ጸጋዬን እማውቀው ኢትዮጵያዊ ሆኖ እናቱን – ሰንደቁ ሲያደርግ ነው። ክብራችንም ነው። ጉልህ የቋንቋ ሊቅም።

አሁን ወደ ተነሳሁበት ወጣቱ የተወቀሰበትን „ጥቁሩን ሰው“ ለእኔ የሰጠኝን ንጹህ ትርጉም ለሌሎች ወገኖቼ ለምን አልሰጣቸውም ብዬ አላዝንም። ውበት እንደ አካባቢው ስለሚተረጎም። እኔ በሚታዬኝ፣ ለእኔ በሚሰማኝ ውስጥ እነሱ ላይኖሩ ይቻላሉ – ለእኔ አርቲስት ቴዲ አፍሮ ሥጦታ ነው። ለትውልዱ በጣምራ ገለጻ አንገት ነው። ባለዜማዎችን ለዘመኑ ሊመራ የሚችል ምልክትም ነው። ይህ ወጣት የከወናቸውን ተግባራት በማስተዋል ሆነን ስናነባቸው አሱም ሆኑ ሥራዎቹም አርማችን ናቸው። ባለመታደል ሆኖ እንጂ። ከዚህ ሌላ እኔ የወጣቶች አደራጅ ስለነበርኩኝ ስሜታቸው በጣም ቅርቤ ነው። „የልጅ ነገር አንዱ ፍሬ አንዱ ጥሬ ሆኖ“ ነው እንጂ በዚህ ዙሪያ መሬት ዬያዘ ሰፊ ጥናት ከወጣቶቹ ጋር ሰርተን ነበር። ከእጄ ቢኖር እንዴት ወርቅ በነበረ። በሌላ በኩልም ወጣትነት ሁላችን ያለፍንበትም ነው።
ለማንኛውም ወጣት አትሁን ማለትም የፈጣሪን ታላቅ ተፈጥሮዊ ዶግማ ሆነ ሥልጣን መጋፋት ይመስለኛል። በዚህ አፍላ ዘመን ስንት ቦታ ይደረሳል። ወጣትነት ሳተናነት ነው ….. በእኔ ስሜት ማዕቀፍ ውስጥ ያለው የነፃነት ትርጉም፤ የማንነቴ ጣዝማ በመሆኑ የውስጤ ፍጹም ገዢ ነው። ነፃነት ማንነት ላለው እኔነቴ አንጎሉም ነውና። ማናቸውም የገኃዱ ዓለምን የኑሮ ስንክሳሮች የማያቸው ሆነ የምመዝናቸው እኔን ከሰጠኝ ብሄራዊ ነፃነት በታች እንጂ በላይ ከቶም ሊሆን አይችልምና። ከዚህ አንጻር ቴዲ አፍሮ ለትውልዱ ጥበብ ነው። አጀንዳዎቹ ኢትዮጵያና ነፃነቷ ስለሆነ – የሥርጉተም።

ስለሆነም „የጥቁሩ ሰው“ ፊልም በሙዚቃ የተቀነባበረ ብቻ ሳይሆን እኔ ሳዬው፤ እውነትም ለመናገር፤ ፊልሙ በዛ ዘመን የተሰራ ነው የመሰለኝ። ማለት ትዕይንቱ ጦርነቱ እዬተካሄደ የተቀረጸ ዓይነት ነው። ጭብጡና የጭብጡ ማዕከላዊ ተልኮዎ በሥርዓተ ተክሊል በፍጹም ሁኔታ በተፈጥሯዊ አኃታዊነት የተጋቡ ናቸው። በጣም የተዋጣለት ታላቅ ተግባር ሆኖ ነው ያዬሁት። ከዚህ ባለፈ ድሉ ሙሴውን – የህዝብ ስለመሆኑም አባወራ ጀግኖቻችን በነቂስ አውጥቶ ነው የተቃኘው ስለሆነ ይህ ወጣት በቀደመው፤ በዛሬው ወይንስ በሚመጣው በዬትኛው ዘመን የተፈጠረ ነው በማለት በልቤ ውስጥ ባለችው ሙዳይ ወስጥ እጅግ መስጥሬ አስቀመጥኩት። መብቴ ነው። እኔ እንደዚህ ላሉ ወጣት ጀግኖቼ አብዝቼ እሳሳላቸዋለሁ፤ ሰብስቤ በማህጸኔ ውስጥ ባስቀምጣቸውም እወዳለሁ፤ ዓለም ቀናተኛ ስለሆነች እንዳትነጠቀኝ ስለምሰጋ

teddy afroየወጣቱን ንጥር ተግባር ብቁ ከሚያደርጉት መሰረታዊ ነገሮች ግጥሞቹ ጥልቅ መሆናቸው ነው። ትናንትን ከዛሬ፤ ዛሬን ከነገ በነብይነት ማያያዣ ፈጥሮ ያወራርሳቸዋል። ጥበብ ማለት ይህ ነው። ግጥምጥሞሽ ያልሆነ። እርግጥ ነው በግልብ ካዬናቸው ጊዜያዊ ደስታ ወይንም የማንደግፈው ከሆነም ጠብ አጫሪነ ስሜትን ቀስቅሶ ሊያበሳጨን ይችላል። አብሶ ከመልዕክቱና ሰብሉ ሊያለማ ከፈለገው ማዕከላዊ ማሳ ካልተነሳን እንደ መደዴ የቃላት ድርደር አድርገን ልንመከተው እንችላለን። የመልዕክቱ ውስጥ ንዑድ መንፈስ ነፃነት ነፃነት ነፃነት፤ ተፈሪነት ተፈሪነት፤ ገናናነት ገናናነት፤ ኢትዮጵያዊነት ኢትዮጵያዊነት – አፍሪካዊነት ነው – የዓለም አብነት ኢትዮጵያ! ይህ ነው ውስጣችነን የወያኔ ሸፍጥ ካላሸፈተው …..
እያንዳንዱን ስንኝ በተን አድርገን በቁሙ ሳናነብ ውስጡን በቅንነትና በአዎንታዊነት ስንፈትሸው ቃሎችን ከስንኙ ሐረግ ነጥለን በመልካቸው ስናይ ደግሞ ቀለማችን አጉልቶ፤ እኛነታችን አብርቶ፤ ፍቅርን እንደ ታቦት ከብክቦ፤ ሩቅ ተጉዞ ሰላምን በናፍቆት ይጠራና ውስጣችን አስተቃቅፎ፤ ነገን በተስፋ ቀይሶ ይመከረናል፤ ያስተምረናል። ይፈትሸናል። ፍላጎታችን ኮትኩቶ የአቅጣጫውን ቅዬሳ ናሙና ከመንፈሳችን ሰርበዬር ውስጥ በሳቢነት ይቀርጸዋል። …..

እንዲሁም „ጥቁሩ ሰው“ በሀገራችን የነበረውን፤ አሁን ያለውን የሥነ ጥብብ እድገት ሥልጣኔም ቁልጭ አድርጎ ያሳዬናል። „ይህ የትውልድ ክፍተት አለበት፤ ወጥ ሥራዎች ተራቆቱ፤ የቀደሙት የሙዚቃ ስንኞች ቃናቸው ከዕውነተኛው ወይንም ከጋህዱ ዓለም ጋር በእጅጉ የተቆራኙ ነበሩ። መሬት ያያዙ ነበሩ፤ ስለሆነም ወስጥን የመግዛት አቅም – ኃይልና – ስበት ነበራቸው። የዛሬዎቹ ግን ቤታቸው እንኳን አይመታም፤ ሥር አልሰደዱም“ … ወዘተ
… ለሚሉት ዕውነት ለመናገር የአርቲስት ቴዲ አፍሮ የመንፈስ ምርት ጥያቄያቸውን ሁሉ በአግባቡ የመለሰ ይመስለኛል። ደግሜም እላለሁ … እኔ አሁን ለተፈጠሩት ወጣቶች እጅግ ታላቅ አክብሮትና አድናቆት አለኝ። በስለው ነው የተወለዱት ማለት እችላለሁ። መድረክ ሲያገኙ የማዬው ብቃት ከቶውንም ሊለካ የማይችል የመንፈስ ሐሴት ይሰጠኛል። ለዛውም በዚህ ሙጃ ሥርዓት፤ በዘመነ ወያኔ ተወልደውና አድገው … ሞት ያልተዋጀበት አንድም የኢትዮጵያዊነት የመንፈስ ተቋም በሌለበት …. ይህን ጥሰው የወጡ የዘመኑ ጥቁር አንበሶች ናቸው – ለእኔ።

ንጽጽር፤
የብዙ ታዋቂ ዓለምዓቀፍ ባንዶችን ኮነሰርትን አብዝቼ እከታተላለሁ። የወጣቱ የፈጠራ ብቃት እኔ ነኝ ካለ ባንድ ጋር ሊመጥን የሚችል በቂ አቅም እንዳለው ነው ያዬሁበት። የቴዴ ሥራዎች መነሻ እሩቅ አይደለሙ። ከእናቱ ጓዳ፤ ከተጨባጩ ጭብጥ ስለሆነ፤ ስሜትን የመሳብ ችሎታው ብቻ ሳይሆን ስሜትን ተቆጣጥሮ የማቆዬት ጉልበቱም አንቱ ነው። ሁሉን ነገር፣ ሁሉን አካባቢ በቅኑና በትሁት መንፈስ ይዳስሳል። አንዱ የግጥም ዜማ በራሱ አንድ መጸሐፍ ይወጣዋል። ይህ ለኢትዮጵያ የሥነ – ግጥም ሆነ ሙዚቃ ነገ አዲስ አቅጣጫ ነው። ለማግሥትም ብቁ እርሾ!

ሌላው ቅኝቱ ራሱ መሰራቱ፤ ፍሬዘሩ ከውስጡ መፍለቁ፤ ከዚህም በላፈ የስንኙን ፍሰት ሳይጎዳ እንደ ራሱ ውስጠት አድርጎ፤ ጤናቸውን ጠብቆ፣ ሴላቸው ሆነ ደም ሥራቸው ሳይጎዳ፤ ኦርጋናቸው ሳይነደል እንደ ተፍጥሯቸው ስለሚቀርበው ይህ ደግሞ የወጣቱ ልዩ መለያ ጸጋው ነው። /ጀርመኖች አውስጌቦልሼ ታለንት/ ከሰው ዘር የተለዬ መክሊት እንደ ማለት። በዬሙያው እንዲህ ያሉ ሁለት አንጎል ያላቸው ይፈጠራሉና። በዚህ ዘመን ኢትዮጵያዊነት በጠላትነት ተፈርጆ፤ በፖሊሲ ደረጃ ወያኔ ተግቶ እዬሰራ፤ በዘመኑ ተፍጠሮ ግን፤ የወያኔን ኢትዮጵያዊነትን የማፍረስ ፖሊሲ የቀደመ፤ የበለጠ ሥራ ነው። አንድ የፖለቲካ ድርጅት ረጅም ዓመት ከደከመበት የቴዲ ስንኞች የበለጠ ያፈሩና አርበኞች ናቸው። ለኢትዮጵያዊነትም ዘብ አደርም ናቸው። ሥነ ጥበብ ወተቱ የአድማጭ የሰላ እርምት ነውና ወጣቱ እርማቶችን በጸጋ ተቀብሎ ማስተናገድ ከቻለ አንድ ትውልድ የመፍጠር አቅሙ አንቱ እንደሚሆንም አልጠራጠርም።

የቅኔው ልዑል ብላቴ ሎሬት ጸጋዬ ገ/መድህን ያን የመሰሉ ሥራዎቹን፤ ትውልድ የማይተካው ያ …. ዕንቁው ጋሼ ወጋዬሁ እሸቱ ነበር የሚተውንለት – የሚያነብለት። መዳህኒተዓለም አባታችን ንጉሥ ዳዊትን „እንደ ልቤ“ አለው ለጋሼ ጸጋዬም እንደ ልቤ ነበረው ጋሼ ወጋዬሁ። ዕድለኛ ነበር። እንደ ውስጡ ሆኖ፣ ከውስጡ የተቀመጠ ለእሱ ጸጋ ብሎ አምላኩ የመረቀለት ጋሼ ወጋዬሁ ነበር። ትውናው እንደ እራሱ ውስጥ አድርጎም ያቀርብለት ነበር። የጋሼ ጸጋዬ ስሜቱ መንትዮሽ በአህትዮሽ እንደ ነበር ይሰማኛል። መቼም እንዲህ ዓይነት አጋጣሚ በሺ ዘመናት አንድ ጊዜ ወይንም ሁለት ጊዜ ነው የሚከሰተው። ከዚህ አንፃር ውስጡን ከእነተፈጥሮው ማቅረብ መቻሉ ለቴዴ ዕድለኛነቱን ድርብ ያደርገዋል። በስሜቱ የፍልጎት ልብ ውስጥ እሱ እራሱ በመንፈስም በአካልም አለና። ተቀድቶ የማያልቀው ውበቱም ይህ ነው። ወጣቱ ከያኒ የጻፈውን እራሱ ያቀርበዋል …. እራሱ አቀናብሮ እራሱ ያስጌጠዋል። አደራጅቶ፤ ውስጡን የሚገልጽለት ሌላ ሰው ቢያስፈልገው ኖሮ ከባድ ነበር። ግን እድሉና ምርቃቱ ወፍ አወጣቸው። ስለሆነም ተ — ጠ – በ – በ – በ – ት።

የሰማይ የላቀ ስጦታ!

እኔ የእግር ኳስ ፍቅረኛ ነኝ። እጅግ በጣም እግር ኳስን እወዳለሁ። አሁን ዬይድነቃቸው ልጆች ለእፍሪካ ዋንጫ በ2013 እ.ኤአ. ሲታደሙ ሰፊ የሆነ አትኩሮት ነበረኝ። ኢሮ ስፖርት ሀገራችን እንዴት ከፍ እዬደረገ ሲገልጸው እንደ ነበረ ማመን እስኪያቅት ድረስ እጅግ እጅግ ድንቅ ነበር። ያን ጊዜ አጋጣሚው ረድቶ ሀገሬ ኢትዮጵያ ከፍ አለች። ታሪኳ፤ የህዝቧ ባህል፤ ወግ ልምዷ፤ የነፃነት ገድሏ ሁሉ ተዘከረ። ኢትዮጵያን የኢሮ ስፖርት ፕሮግራም አቅራቢዎች ሆኑ አዘጋጆች ውስጣችን አሳምረው ነበር ኪናዊ አድርጎ ያነበቡን – ቀለማም አድርገው ነበር የኳሉን። ለእኔ ፈውስ ነበር። ዳንኩኝ!
መቼም ትውልዱ አዲሱ ማለቴ ነው በብዙ ፈታና ውስጥ ሆኖ፤ ግን ድንቅ ነገር ያሳዬናልና ከዓለም ዋንጫ ዝርዝር ውስጥ ዬኛዎቹ ሲገቡ ደስታዬ ወደር አልበረው። ታዲያ የመጨረሻ ማጣሪያው ከናይጀሪያ ጋር ሲሆን ግን አልተመቸኝም ነበር። አሳምሬ ናይጀሪያዎችን አውቃቸዋለሁና። የሆነ ሆኖ የኔዎቹ ማጣሪያ ሳያልፉ ሲቀሩ ዕንባ አውጥቼ ነበር ያለቀስኩት። የእውነት። እናት ሀገሬ፣ የመንፈስ ተክሊሌ፤ እምዬ ኢትዮጵያ – እንጀራዬ የመላ ዓለምን የእግር ኳስ ጨዋታን አለመገኘቷ አስከፋኝ። ልክ እንደ መጻፍ፤ መጸሐፍ ማንበብ ድንቡልቡሏንም ስለምወድ ብራዚል ላይ እመቤት ኢትዮጵያ ስትደምቅ ናፈቆኝ ግን ሳይሆን ሲቀር በጣም ተጎዳሁ። የኢትዮጵያ ጎል ጠበቂ ገና አልተወለደምና።

እግዚአብሄር ይመስገን … ሁልጊዜም የማምናበት ነገር፤ ኢትዮጵያ አምላክ አላትና ዕንቡጡ ቅኔ አህጉርን ወክሎ በ2014 የዓለም ዋንጫ ብራዚል ላይ መገኘት በራሱ ክብር ነው። የሰማይ የላቀ ሥጦታ ነው። ልዩ ምርቃት ነው። የሥነ ጥበብ ቤተኛ ታዳሚዎች ሁሉ ልንደሰትብት የሚገባው መሪ ድል ነው። ቅኔኛው ቴዲ አፍሮ እንደ አባቶቹ እንደነ የቅኔው ልዑል ብላቴ ጸጋዬ ገ/መድህን መንገድ ተከትሎ፤ የአፍሪካ ነገር መስመሩ ነበርና፤ ፈልጎ የተነሳለት ድንቅ ራዕይ ከሀገሩ አልፎ አህጉሩንም ሊወክል ነው። እግዚአብሄር ደግ አምላክ ነው እንሆ አደረገለትም። ጉዞው አቅጣጫው እጅግ አጓጊ ነው።

ፅኑ ዕይታ!

እናት ሀገር ኢትዮጵያ ስትከብር፣ ስትደምቅ፤ ከፍ ስትል፣ ዜግነት ሲያበራ፣ እንደ ትናንቱ ኢትዮጵያ አፍሪካን በሥነ ጥበብ ጎራ ዳግም ልትመራ ስትመረጥ፤ ለመልካም ነገር ስትታጭ፤ ልዩ ፍጹም ልዩ ትርጉም ነው – ዕጹብ ድንቅ። ፍካታዊ ገጸ በረከት ነው። አበባዊ ረድኤት ነው። ለዚህ ተግባር ስኬታማነት እንደ ሰው የተገባን እናድርግ እንጂ፤ ትዕዛዙ ከመዳህኒተዓለም አባቴ ስለሆነ ሳንኩን ሁሉ አሸንፎ ሚሊዮን ፈን ያፈራል። አብሶ ጀርመኖች የሥነ – ጥበብ አክባሪና አፍቃሪ በመሆናቸው ለሽልማት ያጩታል። ጠብቁ። ቴዲን የቆዬ ሰው ይዬው። አፍሪካዊ ቪቫ ይሆናል። ዕውቅናውን አሳምረው ይሰጡታል። ሰፊ የሆነ በር ተክፍቶለታል። በሰውኛ ሥልጣን በሩን መዝጋት አይቻልም። „ልክን ማወቅ ከልክ ያደርሳል“ ይላል ጎንደሬ ኢትዮጵያዊነት ፈተናን አሸንፎ የተፈጠረ ሚስጢር ነውና!
ጀርመን በሥነ ጥበብ ጉዳይ 13ኛው ፕላኔት ነው – ለእኔ። ፍጹም የተለዩ ናቸው። በደንበር – በክልልል – በቀለም በምንም ነገር አይደለም የጥበብን ልዩ ጸጋ የሚለኩት፤ በመንፈስ ቅዱስ ንዑድ ስሜት እንጂ። የሰማይ ጸጋን ለመተርጎም ሆነ ለማመሳጠር ተስጥቷቸዋል። ይህ ቀን እኔ ስመኘው ነበር። አንድ ዝግጅት ለጀርመን ህዝብ ቢኖረው በማለት። የለመኑትን የማይነሳ አምላክ ከጀርመን አልፎ ዓለም ሊታደምበት እንሆ ፈጣሪ አምላክ ወሰነ። ተመስገን!
እኔ በግሌ በፈጣሪዬ ስለማምን፤ ደግሞም የሥነ ጥብብ ሰውነት ሥጦታው የሰማይ ስለሆነ ጥበቃው ሰማያዊ ነው። በድንግልና ውስጡን ሆኖ ስለሚጫወተው ሥነ ጥበብን ያምርበታልና ሰጪው አጥር ቅጥር ይሆንለታል።

አዎን! ቀኑ እስኪደርስ ድረስ በጥንቃቄ፣ በፆም በጸሎት፣ ከብዙ ነገር ታቅቦ፣ ለዚህ ማዕረግ ካበቃው ከአምላኩ ጋር ቴዴ መሆን እንዳለበት እንደ ታላቅ እህታዊ አስተያየቴን አካፍለዋለሁ፤ ህይወቱ ያላችሁ ደግሞ እንደ ዕምነታችሁ በጸሎት ትደግፉት፣ ትረዱት ዘንድ በትሁት መንፈስ እጠይቃችኋለሁ። ከፀሎት በላይ ጠበቂ የለምና። ከጸሎት በላይ ዘበኛ የለምና። ምክንያቱም ያቺ መከራዋና ፍዳዋ የጠናባት ልዕልት ኢትዮጵያ፣ ልጆቿን አብልታ ማሳደር ያቃታት እናት ሀገር፤ ሚሊዮን የነገ ፍሬዎች ጉርሻ አጥተው በጠኔ የሚረግፉባት አምላኳ አረሳትምና እንሆ ከፍ ሊያደርጋት ማቀዱ ዬምልዓት ዕንባ ካሳ ነው። ለአምላካችንም ለቅዱስ እግዚአብሄር ከእኛ የሚፈልገውን ምስጋናችን ሳናቋርጥ እንግለጽለት። በዚህ ዘመን አንድ ታዊቂ፤ ተደማጭ ለዛውም ወጣት ማፍራት ነገን ያበራልና።
የአይቮሪው ዓለምዓቀፍ ታዋቂ የእግር ኳስ ተጫወች ዝሆኑ ድሮግባን፤ የዩክራይን ሁለት ወንድማማቹች የጀርመን ዓለም ዓቀፍ ቦክሰኞች ወስጥ ታናሹ ለዩክሬን ፍትኃዊ አስተዳደር ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ሲገኝ የዓለም ሚዲያ እንዴት ያረብርባል መሰላችሁ፤ የኛ ግን ትዕቢተኛው የሳውዲ መንግሥት የታላቅ ሀገርን ክብር ጠቅጥቆ ልጇቿን እንደ እንሰሳ አስፓልት ላይ እንደዛ ሲያርድ አንድ ለዕንባችን ዕውቅና የሚያሰጥ ታዋቂ፤ ተደማጭ፤ ዓለም ጆሮውን የሰጠው ዋቢ አልነበረንም። ነገ ግን ይኖረናል ….. ለዚህ ፈታናውን ተጋርቶ መረባረብ የግንባር ተልዕኳችን ነው። ጦርነቱ ተክፍቷል በድል ማጠናቀቅ አለብን! ማቄን ጨርቄን የለም! ለተደራጀ መሬት ለያዘ ተግባር እያንዳንዳችን በግል ሁላችንም በጋራ እንትጋ! ኢትዮጵያ ናት ፊት ለፊት ቁማ እሳት ውስጥ እዬተርመጠመጠች ያለችው። በኪነጥበቡ ይህ ዕውቅና ሲመጣ ደግሞ ግንባር መሆን!

በተረፈ ትምክህት ጎርፍ ነው፤ አድማም ጤዛ ነው። በሥነ ጥበብ ላይ ተደራጅቶ ጦርነት መክፈትም ወስጥን መፋቅ ነው። ፍቅር ግን የጸደቀ ፍሬ ነው። ኢትዮጵያዊነት የሚያሳፍር ሳይሆን የሚያኮራ፣ ተለምኖም የማይገኝ ምርጥ ዘርነት ነው። ውስጣችን የነጠረ ወርቅ ነው። ድህነታችን፣ የህዝብ መበደል፣ መንገላታት ደግሞ የሥርዓታት እንጂ እናት አንዱን ልጅ የክት ሌላውን የዘወትር፤ አንዱን አብልታ ሌላውን አስርባ በፍጹም አታውቅም። የወተት ጡት ጋቶቻ ለሁላችንም እኩል ማጥባትን አዘውትረው ይሻሉ …. ህግጋቶቿ ናቸውና። እቅፏም ለሁላችን ሳይዛነፍ በእኩልንት ነው። ማዕዷም እኩል ለሁላችንም ነው። ስለሆነም በእናት ሀገራችን ላይ የሚሰነዘሩ ጥቃቶች ሁሉ መቆስቆሻ ሳንፈልግ ሁላችንም እኩል መማገድ በእጅጉ ያስፈለገናል። ፈተና መጥቷል – ማለፍን ይጠይቃል_! እናት ኢትዮጵያ የበደለችው አንድም ሰው የለም!

ክወና! …

ኢትዮጵያን የፈጠራት አምላኳ ምንጊዜም ስለማይረሳት እሷን ለማጠቃት የተነሱት ሁሉ የዶግ አመድ ይሆናሉ። በእኛ እድሜ እንኳን ሱማሌ፤ ኤርትራ፤ ግብጽ፤ አሁን ደግሞ ሱዳን ይታመሳሉ። አምላኳ ቀናተኛ ነውና። በ2012 እ.ኣ.አ. የአሳ ግማቱ ከአናቱ እንዲሉ እጬጌውን ከመንበራቸው፤ የጎጥ አፄውንም ደግሞ ከአራት ኪሎ ቤተ መንግሥት ለኑዛዜ ሳያበቃ ነበር ያነሳቸው። ይህ ምርታማ መሬት፤ ለምለም አካባቢ፤ ሃብታምነት የሚባለውም ቢሆን አባታችን ከተከፋ ትል ከሰማይ ሊያዘንብበት ይችላል። እናስተዋል! —- ጉዳቱ ደግሞ የጋራ ነው እንደ ሰው ለምናስበው – ለእኛ።
እንኳንስ በተፈጥሮ ኤኪኖሚዋ ጥገኛ ለሆነ፤ ያልጠመጣጠነ ኤኮኖሚዊ ዕድገት ለሚገርፋት ኢትዮጵያ ቀርቶ የሰማይን ቁጣ እንጃፓን፣ ሱናሜም ማስቆም አልቻሉም። ይልቅ እንደ ሰው አስበን በዛ ቦታ ማን ይኖራል? ህፃናትን፣ አቅመ -ደካሞችን፤ ህሙማን፤ ነፍሰጡር ሴቶችን፤ እንሳሰት ሳይቀሩ ሊታስብላቸው ይገባል። ቀይ ቀበሮ እኔን ይገልጸኛል። ሶፍ ኡመር ዋሻ እኔን ያብራራኛል። ልዩ የሚባሉ አብዛኞቹ ሌላ ዓለም የማይገኙ አዕዋፋት ኢትዮጵያ ብቻ ነው የሚገኙት፤ ሁሉንም የሰማዩ ቁጣ ውስጣችን አብሮ እንዳያጭደው አደብ ገዝተን ወደ ፈጣሪያችን እንመለስ!
… ለሰው አይደለም። ወደ ፈጣሪያችን ቀልባችን መልሰን እራሳችን አዋርደን፤ ይቅርታ አምላካችን እንጠይቅ …. ኢትዮጵያ ሶስት አፄዎቿ ዓለም በቃኝ ብለው ገዳምን የመረጡ ንዑዳን የፈጠረች ቅድስት ሀገር ናት። ዘጠኙ ቅዱሳን ከተፈጠሩባት ሀገር አስበልጠው የመረጧት ሀገር ናት። ነብዩም ለጆቻቸው የተመኩባት ተምሳሌት ሀገር ናት።

የማከብራችሁ ወገኖቼ …. እጅግም የምናፍቃችሁ ደሞቼ … መንጠራራት መልካም ባይሆንም፤ ሰው ባላው ነገር ወይንም በቀጣይ ፍላጎቶቹ ዙሪያ አብዝቶ ሊንጠራራ ወይንም ሊመካ ይችላል። በተማመነበት ጉዳይ። በክርስቶ ወይንም በአላህ ሥልጣን መንጣራራት ግን ዕጣው ትውልድን ያሳርራል – ያርሳልም። ቅጣቱን የሚያቆም ምድራዊ ኃይልም አይኖርም፤ አባ ጳውሎስን አተረፈ ተዋህዶ? ወይንስ ቲፒ.ኤል.ኤፍ ሄሮድስ መለስን ታደገ? ገዳማት ታረሱ …. ቁጣውም ነደደ!
ፍቅር ተንበርክኮ እንሆ ይለምናል። አሁንም ህዝባችን በፍቅር ይጋባል፣ ይዋለዳል፣ አብልጅነት ይናሳል፣ ይጎራበታል፣ ጡት ይጣባል፤ ጓደኝነት ይገጥማል፣ ማህበሩን ዝክሩን አብሮ ይጠጣል፤ ሀዘን ተፍሰኃውን ፈቅዶና ደስ ብሎት ይጋራል፤ ይረዳዳል፤ ይህን የደም ግንኙት መበጠስ አይቻልም … ሰውኛ አይደለምና ….. በቁጭት ምክንያት ምላሽ ለመስጠት ፍላታችን ለማስታጋስ ስንል በምንሰነዝራቸው ቃሎች ከእልህና ከግብታዊነት ጸድተን እንስከን። ማስተማር የሚቻለው የሚወረወረውን ናዳ መልሶ በመልቀቅ ሳይሆን፤ ጨዋነታችን በለገሰን አርምሞ፤ በተደሞ፤ በትግሥትና በሆደ ሰፊነት ወያኔ ያዘጋጀውን ሴራ ማክሸፍ ስንችል ብቻ ይሆናል ብጡልነት። የዚህ ሁሉ ትርምስ ተዋናዩ ወያኔ ነው። ይህ አውሬ ያዘጋጀው መርዝ ወገኖቻችን አልተረዱትም። ዕውነተኛውን ነገር ወስጣችን ፈቅዶ ይቀበል ዘንድ እግዚአብሄር ይርዳን። ትጉኃን ቀጥሉ የሃቅ ምስክር መረጃዎችን በሚዛን ቀልቡን። አትናቁ ወይንም አቅልላችሁ አትዩትት። የተደራጀ ፈተና ነው። ፈተናው የሚረታው ደግሞ በበለጠ በተደራጀ ሥልጡንና ብልህ ተግባር ብቻ ነው።
ቀኑ እዬናፈቀኝ – የሰንደቄ ዜማ …
ህብር ስንኞችህ ማንነት ሊያለማ።
አፍሪካዊነቴ ሊደምቅም – ሊያበራ
በፈጠራ ዓውራ! ….
ዛሬ ለትናንቱ፤ ትናንትም ለነገ – አድዮ አጎመራ፤
ሉሲ ከፍ ትላላች በመንፈስ – በማማ
በፍውሰትህ – ጣዝማ …..።
እናት ታጌጣለች ….. በሞገስህ ግርማ፤
ታሪክ ይዘከራል – በወጣቱ ዓርማ!
ዓለም ይታደማል በመረዋ እማማ!
ህበረ – ቀለማቱ፤ — የቁንጅና ዋና!
አማንህ – ሊያዘመር ….
እሙ – ልትቀምር
የታጠቀ ዕውነት ብቃት ሊመሰክር፤
ያ …. የደግ ታሪክ ገር፤ መቅድምን ሊመራ
የዘማናት ሂደት …. ትውፊት ሊያነባብር
ዋዜማን – ሊያዘመር …. ብቃት አጎመራ!

ማሰሰቢያ።
• ግጥሞቹ 13.01.2014 00.17 (እ.ኤ.አ) ተጻፉ።
• ጎልተው የተጻፉት ፊደላት ጠብቀው እንዲነበቡ የሻትኳቸው ናቸው።
• የግጥሞቹ – ዕርእሶቹ ጎልተው የተጻፉት የተሰመረባቸው ቃሎች ናቸው። ነፃነት ታወጀላቸው ከፈለጉት ቦታ ላይ ሆኑ፤
• ፎቶው ከቴዲ አፍሮ የግል ድህረ ገጹ የተወሰደ ነው።
መፍቻ።
ዋና ሁለቱንም ትርጉም ይዞ ነው የታደመው። ለሁለተኛው ግጥሜ እርእስም ነው።
• ላልቶ ሲነበብ አብይ፣ ኣናት፣ አለቃ፣ መሪ፤ አስተዳደሪ፤ ሰብሳቢ፤ አዛዥ፤ ሙሴ፣ እረኛ፣ ተጠሪ፣ እርእሰ ጉዳይ እንደ ማለት … ሁሎችም እንደ አረፍተ- ነገሩ ፍሰት ይተረጉሙታል። ለእኔ ግጥም ሙሴ የሚለው ግጥሙ ነው።
• ሁለተኛው ጠብቆ ሲነበብ ደግሞ የአሳን ተፈጥሮዊ የኑሮ ልማድን የሚከተል ይሆናል። … የሰው ልጅ በእህልና በመጠጥ ብቻ አይኖርም። ህሊናው መስኖ ይፈልጋል። መስኖው ደግሞ ሥነ ጥበብ ነው። ሥነ ጥበብ ጥሩ ዋናተኛ ነው። ዋናው በውጭ ሳይሆን ውስጥን የሚቀድስ የሚፈውስ፤ የሚጠግን፤ የሚያጽናና፤ የሚያጸና፤ የውበት ውበት፤ የጌጥ ጌጥ ነው። ልዩነት በአንድነት አንድነት በልዩነት አኃቲነት በመፈቃቀድ የሚያበቅል – የሚያጸድቅም ነው … በዚህ ሂደት ህልም ህልም ነው ነገሩ የሚመስለው የዓለም ብቸኛ ፍቅረኛ በሆነው የእግር ኳስ ትንሳኤ የኢትዮጵያ ሥነ – ጥበብ በበትሩ አሳላፊ በውስጥነት ሊዋኝ ነው …. ያ … የዓለም ሚዲያ ሰልፉ፤ ያ … የዓለም ዕውቅ ሰዎች ታዳሚነት ውስተት እኛነት መስፍን ሆኖ ሊሰነቅ፤ እሰቡት ….. ውህድነት። በአንድ ለጋ ሊጋባ …. ይህ የምልዓት መንፈስ በሐሤት ኢትዮጵያን በዕዝነ – ህሊናን ሲዳስሳት … የቅዝፈቱን ቅኔ ዘጉባኤን የዳጎሰ ድምር ነው ዋና ያልኩት ….
• ጣዝማ …. ከተለመደው ውጪ የሚገኝ የተፈጥሮ የማይረጋ ማር። ለጤና እጅግ መዳህኒት የሆነ። አብዛኛውን ጊዜ የሚገኘው በቆላማ የሀገራችን ቦታዎች ነው። ቀለሙም ትንሽ ደመቅ ያለ ነው።
• አድዮ ማንም ሀገር ብሄራዊ አበባ የለውም። ኢትዮጵያ ግን አላት። መንገድ ጠራጊዋ የተስፋ አበባ አድዮ የአዲስ ዓመት ዋዜማ! የሰንደቅዓላማችን ማዕከላዊ ቀለም ከዚህ ተፈጥሮ ጋር የተሳሰረ ይመስለኛል – በኪዳን። በ5ኛው መጸሐፌ ላይ „በፊደል“ የልጆች የግጥም መድብል የተሰራበት ነው፤ እንደዚህ ለዬት ያሉ ተፈጥሯችነን ከፊደል ላይ ዘርዘር አድርጌ ጽፌዋለሁ። በነገራችን ላይ የፊደል የፊት ሽፋን ከዓለም የሚለዬን፤ እንደ ውስጣችን የተፈጠረው ድንቁ የፊደል ገበታችን ሲሆን ከሌሎቹ መጸሐፍቶቼ በበለጠ በነጮች ተወዳጅም የሆነው እሱ ነው። ይወዱታል … በጣም። ቋንቋው አማርኛ ግን ተማረኩለት … ሌላ ቀን በዚህ ዙሪያ እመጣላሁ … አሁን ደግሞ የአፈሙዙ አቅጣጫ በእሱ ዙሪያ ስለሆነ ….
መንፈሶቼ – ታዳሚዎቼ! የፍቅር ማዕድ በመከባባር አብሮ አቆዬን ፤ለተሰጠኝ በቂ ጊዜ ምስጋናዬን በቅኑ ውስጠት – እንሆ!
ፈጣሪ አምላካችን የተበተነን ልቦናን ስበስቦ፤ እናታችን ከፍ ትል ዘንድ የጀመረውን ይጨርስ።
ልብ ይስጠን – ለሁላችን! የምንችለበትም ጽናትም! አሜን

ጨረስኩ — ንጹህ አዬርም አገኘሁ – ዱላውን የምችልበት!

እግዚአብሄር ይስጥልኝ።

የአንድነት ተልእኮና የፋሲል የኔአለም ጫፍ የቆመ እይታ

$
0
0

ዳንኤል ተፈራ

Daniel-Tefera አንድነት ፓርቲ በተሳካ ሁኔታ ጠቅላላ ጉባኤውን ፈጽሞ በበርካታ ወጣቶች የተገነባውን ካቢኔ ይፋ ካደረገ በኋላ ጥቂት ሳምንታት አለፉ፡፡ በነዚህ ጥቂት ሳምንታትም ትግሉን በማያዳግም ሁኔታ የህዝብ አድርጎ የሚፈለገውን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እውን ለማድረግ ቀን ከሌሊት መስራት ይገባል የሚል እቅድ አንግቦ ደፋ ቀና በማለት ላይ ነው፡፡ በዚህ ሁኔታ ውስጥ እያለን ግን የግል አስተያየት በማለት የኢሳቱ ጋዜጠኛ ፋሲል የኔአለም “የአንድነት ፓርቲ የመጭው ጊዜ ፈተና›› በሚል የፃፈውን ያልታሰበበት ጽሁፍ አነበብኩ፡፡

በቅድሚያ ጽሁፉን አንብቤ ሳበቃ ለምን መልስ መስጠት አስፈላጊ ሆኖ እንዳገኘሁት መግለጽ ይገባኛል፡፡ ፋሲል ማስተላለፍ የፈለገው ‹‹አንድ ጫፍ ብቻ›› የረገጠ መልእክት የተዛነፉ ሃሳቦች የተላለፈበት፣ ከግለሰብ ጥላቻ በመነሳት ፓርቲውን ፈተና ውስጥ ያለ በማስመሰልና ዋጋ እየከፈሉ ያሉትን ውድ አባሎቻችንን በግብአትነት በመጠቀም ክፍፍል ለመፍጠር የፈለገ በመሆኑ ነው፡፡ ወይም ፀሀፊው ‹‹ሁለት የከረሩ ጫፎች ብቻ ያስፈልጋሉ›› ከሚል አይነት አመለካከት ላይ ቆሞ ከመፃፍ የመነጨ ነው፡፡ ሁለተኛው ምክንያቴ በአምባገነኑ ስርዓት ተጠፍንገው ከተያዙ የብሮድካስት ሚዲያዎች ውጭ አማራጭ አልባ ለሆነው ህዝብ በአማራጭነት ለቀረበው ኢሳት ካለኝ አክብሮት ነው፡፡ ምክንያቱም ጋዜጠኛ ፋሲል የኔዓለም የኢሳት ባልደረባ እና ኃላፊነት ያለበት ሰው በመሆኑ፡፡

ፋሲል በጠቅላላ ጉባኤው በከፍተኛ ድምጽ የአንድነት ፓርቲ ፕሬዚደንት ሆነው የተመረጡት ኢ/ር ግዛቸው ሽፈራው ከሪፖርተር ጋዜጣ ጋር ቃለ-ምልልስ ካደረጉት ውስጥ ‹‹ከኢህአዴግ ጋር ገንቢ ግንኙነት (Contractive engagement) እንዲኖረን እንፈልጋለን. . .›› የሚለው ለሱ ሃሳብ የሚመቸውን ቆንጥሮ በማውጣት ከልደቱ አያሌው ‹‹ሦስተኛ መንገድ›› ካለው ወይም ‹‹ መሀል ላይ መቆም›› ብሎ ከተረጎመው ሃሳብ ጋር ለማያያዝ ሞክሯል፡፡ ስህተቱ እዚህ ላይ ይጀምራል፡፡ አንድነት ሊበራል አስተሳሰብ የሚያራምድ በመሆኑ የግለሰቦች መብት በቅድሚያ መረጋገጥ አለበት ብሎ ያምናል፤ በስትራቴጂው እንዳስቀመጠውም የኢህአዴግ አይነት ብሔር (የቡድን) መብትን ማክረር ወይም የዚህ ተቃራኒ የሆነው የኢትዮጵያ ብሔርተኝነት ላይ ብቻ ቆሞ ሌሎችን አለማዳመጥ ዴሞክራሲያዊ አይደለም ይላል፡፡ ሁሉም ባልተሸራረፈ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ውስጥ ያለምንም ጣልቃ ገብነት የመደራጀት መብታቸው መከበር አለት፡፡ ስለዚህ ጥያቄው ጫፍ የመቆም ሳይሆን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የመፍጠር ነው፡፡
UDJ
ስለዚህ አንድነት እንደ ሊበራል ፓርቲ ከገዢው ፓርቲ ጋር መደራደር ይገባል፡፡ መደራደር፣ ሰጥቶ መቀበል እንደነውር መታየት የለበትም ብሎ አስቀምጧል፡፡ ኢ/ር ግዛቸውም በቃለ ምልልሱ ያስቀመጡት ይህንን ነው፡፡ መደራደር የፖለቲካ ፓርቲዎች አንዱ ሥራ ነው፡፡ መደራደር ዘመናዊ አስተሳሰብም ነው፡፡ አሁንም እየታገልን ያለው ችግራችንን በጠረጴዛ ዙሪያ እንፍታ፣ ሆደ ሰፊ እንሁን፣ ጠርዝ ከያዘና ከፍረጃ ፖለቲካ እንላቀቅ በማለት ነው፡፡ አቶ ፋሲል ‹‹መሀል ላይ መቆም›› ያለው እንደዚህ አይነቱን ሃሳብ ነው፡፡ እንጅ ራሱ ፀሀፊው አንድነትም ሆነ አመራሩ ተንበርክኮ እንዳልሆነ፣ እንደ አንድነት ዋጋ የከፈለና እየከፈለ ያለ ፓርቲ እንደሌለ የሚያውቅ ይመስለኛል፡፡

ጠርዝ ላይ የቆመ ሃሳብ አለማራመድ ወላዋይ አያሰኝም፡፡ አንድነት መሀል መንገድ የሚለው የብሔረሰብ አክራሪነትም ሆነ የህብረ ብሔር አክራሪነት አይጠይቅምም ከሚል ነው፡፡ ሁለቱን የሚያቀራርብ የመሀል መንገድ መኖር አለበት እንደማለት፡፡ እንደዚህ ማሰብም ጤናማ ነው፡፡ መብትም ነው፡፡ ሁላችንም ሃሳብ የምናቀርበው ለሀገር ይጠቅማል የምንለውን ነው፡፡ አሸናፊው ሃሳብም በህዝብ ዘንድ ቅቡል ይሆናል፡፡

ጋዜጠኛ ፋሲል ግን ለኢ/ር ግዛቸው ካለው የግል ጥላቻ ይመስለኛል ጥቂት ነገር ቆንጥሮ ‹‹ፍርሃት ነው›› ለማለት ይሞክራል፡፡ በውጭ ሀገር እየኖሩ መታገል፣ ትግሉን መደገፍ እንደሚችል አምናለሁ፡፡ ለፋሲል ግን አንድ ጥያቄ መጠየቅ እፈልጋለሁ፡፡ የሚፈራ ሰው መቀመጫው የት ነው? እንደሚመስለኝ ወይ የኢኮኖሚ ጥያቄ ካልሆነ በስተቀር ፀሀፊው ከሀገር የወጣው ሀገሩን ስለሚጠላ ሳይሆን ሥርዓቱን ስለፈራ ነው፡፡ ሥርዓቱን ፈርቶ በተሰደደ ሰውና ከሥርዓቱ ጋር ፊት ለፊት ግብግብ እየፈጠረ ያለ ሰው መካከል ትልቅ የሞራል ልዩነት አለ፡፡ ስለዚህ ጋዜጠኛ ፋሲል የኔዓለም ፍርሃትን የተረጎመበት መንገድ ድንጋዩ ተመልሶ ወደ እርሱ እንዲያርፍ የሚያደርግ ነው፡፡ በዚህ ሁኔታ ከሀገር ወጥቶ ትግሉን መደገፍ ትክክል ቢሆንም ፖለቲካውን ለመምራት መሞከርም ሌላ ትልቅ ስህተት ይሆናል፡፡ እንዲህ ሲባል እዚሁ ኢትዮጵያ ውስጥ ለውጥ ለማምጣት የአቅማችንን እያደረግን ያለን ሰዎች መተቸት የለብንም ብዬ አላምንም፡፡ በመሳደበና በመተቸት መካከል ግን ትልቅ ልዩነት እንዳለ ሊሰመርበት ይገባል፡፡
ሌላው ማንሳት የምፈልገው ጋዜጠኛ ፋሲል የአንዱዓለምንና ናትናኤልን ስም በመጥቀስ ጫፍ ላይ የቆመ ሃሳብ የሚያራምዱ አድርጎ መግለፁም ስህተት ነው፡፡ አንዱዓለምም ሆነ ናትናኤል ፋሲል የጠቀሰውን አይነት ሃሳብ የሚያራምዱ አይደሉም፡፡ ሆነውም አያውቁም፡፡ በተለይም የአንዱዓለምን ሃሳብ ለመረዳት መጽሀፉን ማንበብ ተገቢ ነው፡፡ ወጣቱ ፖለቲከኛ በሆደ ሠፊነት ‹‹ ኧረ የመቻቻል ያለህ፣ ኧረ የድርድር ያለህ፣ ኧረ የመደማመጥ ያለህ . . .›› በማለት አንድ ጫፍ ላይ ቆሞ ማክረር እንደማይጠቅም ገልጿል፡፡ ለአዲሱ አመራርም እውቅናና ድጋፍ ሰጥቷል፣ ደስተኛም ነው፡፡ ይሄን የምለው አንዱዓለም ለገና በዓል በአካል አግኝቼ ሃሳቡን ለረዥም የማዳመጥ እድል ስለገጠመኝ ነው፡፡

በመጨረሻ ግን ስለ ኢሳት ማንሳት እፈልጋለሁ፡፡ ኢሳት ለኢትዮጵያውያን በአማራጭነት ብቅ ያለ ትልቅ ሚዲያ ነው፡፡ ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያውያን ያለውን አበርክትቷል ማድነቅ እፈልጋለሁ፡፡ እኔም በተለያየ ጊዜ በዚሁ ሚዲያ ላይ የተለያዩ ሃሳቦችን ሰጥቼ አውቃለሁ፤ ወደ ፊትም እድሉን ባገኘሁ ቁጥር እሰጣለሁ፡፡ የተለያዩ አማራጭ ሃሳቦችን በተደራጀ ነፃ ሚዲያ ማግኘት የተራበው የኢትዮጵያ ሕዝብ እንዳያዝን የኢሳት ጋዜጠኞችን የኢዲቶሪያል ቦርድ አባላት በእጅጉ ሊየስቡበት ይገባል፡፡ ማንኛውም ሚዲያ ከአድሎ አሠራር ነፃ መሆን አለበት፡፡ በዚህ ሚዲያ ላይ የሚሰሩ ጋዜጠኞቹ ግን የግል አመለካከታቸውንና እምነታቸውን በማስቀደም አንድን ድርጅት ለማጥቃት የሚሄዱበትን መንገድ መፈተሽ ጠቃሚ ነው፡፡ ጋዜጠኛ ፋሲል በአንድነትና አመራሩ ላይ የሰነዘረው የተዛባ አስተሳሰብ “በግል አስተያየት ስም” የቀረበ ቢሆንም ግለሰብ አንድ ትልቅ ፓርቲ ላይ ሲጽፍ መውሰድ የሚገባውን ጥንቃቄ አላደረገም፡፡ ስለዚህ ብዙ ተሳሳተ፡፡ ለማንኛውም ሁሌም ከጥላቻ የሚነሳ ሃሳብ ለህዝብም አይጠቅምም በማለት ላጠቃልል፡፡

በትግራይ ክልል የአፅቢ ወንበርታ የተነሳው ህዝባዊ ዓመፅ ቆመ፤ መንግስት ካሳ ሊከፍል ነው

$
0
0

ህዝብ ተበትኗል፣ መንግስት ካሳ ይከፍላል፣ የታሰሩ አይፈቱም

አብርሃ ደስታ

አብርሃ ደስታ

የአፅቢ ወንበርታ ወረዳ (ጣብያ ሩባፈለግ፣ ቁሸት ሕኖይቶ) ህዝብ የከፈተው ዓመፅ ዛሬ (ዓርብ 09/05/06 ዓም ከምሽቱ አስራ ሁለት ሰዓት ከአስር ደቂቃ (12:10) ላይ ቆሟል። ህዝብ ወደየቤቱ ተመልሷል። የፀጥታ ሃይሎች ግን ከአከባቢው አልራቁም።

አስተዳዳሪዎች ህዝቡን በፌደራል ፖሊስ አስከብበው ሲያስፈራሩት የዋሉ ሲሆን የህዝቡን ጥያቄ (ካሳ የመክፈሉ ጉዳይ) ለመመለስ ተስማምተዋል። ስለዚህ ህዝቡ በጠየቀው መሰረት መንግስት ተገቢውን ካሳ ይከፍላል። የታሰሩት የአከባቢው ኗሪዎች ግን አይፈቱም። ህዝቡ “የታሰሩትን ይፈቱልን” ብሎ ሲጠይቅ “እርምጃ እንወስድባችኋለን፣ ማንም መጥቶ አያድናችሁም” የሚል ማስፈራርያ ደርሷቸዋል። ስለዚህ መንግስት ጥያቄ በማንሳታቸው ምክንያት የታሰሩትን ዜጎች ለመልቀቅ ዝግጁ አይደለም።

የመንግስት አካላት ህዝቡን ካሳ ለመክፈል ሲስማሙ የህዝቡን ጥያቄ ትክክለኛነት ተቀብለውና አምነው እንደሆነ አቅርበዋል። ጥያቄው ያነሱት ዜጎች ከእስር ለመፍታት ግን ፍቃደኛ አይደሉም። በትግራይ ዜጎች መብታቸው ሲጠይቁ ለእስር ይዳረጋሉ። የአፅቢ ወንበርታ ጠያቂዎች ምሳሌ ናቸው። ታሳሪዎች የዛሬን ጨምሮ ስምንት ናቸው።

ጥያቄ የጠየቀ ዜጋ ለምን ይታሰራል? ጥያቄ የመጠየቅ መብት የለውም? መንግስት የህዝብን ጥያቄ በአግባቡ ከመመለስ ይልቅ ለምን ወደ ሃይል እርምጃ ይሄዳል? አምባገነኖች በራስ የመተማመን ባህሪ ስለሌላቸው ለሁሉም ሃይል መጠቀም ይወዳሉ።


“ብጥብጥና ሁከት” የህወሃት የተለመደ አባባል: “መንግስት ሆይ ህዝቦችህ ይወዱሃል የምንልህ እኛ ነን እንጂ እነሱስ ሞትህን ይመኛሉ”

$
0
0

ናትናኤል ካብቲመር ኦስሎ ኖርዌይ 5 ጥር 2006

መቼም በኢትዮጲያ ብጥብጥና ሁከት የሚባለውን አባባል የማያቅ አለ ለማለት ያሰቸግራል። ምክንያቱም የመብትና የፍትህ ጥያቄ በተነሳ ቁጥር የህወሃት መንግስት “ ብጥብጥና ሁከት ሊያሰነሱ ሲሉ” ማለቱ የተለመደ ነው። ምንም አይነት መብትን የተመለክቱ ጥያቄዎች በድርጅት ወይም በግለሰብ በተነሱ ቁጥር “ብጥብጥና ሁከት” ሊያስነሱ ሲሉ ይባልና እስር ቤት ይወረወራሉ። እዚህጋ በርካታ ጥያቄዎችን የሚያስነሳ ነገር ይታያል። በኢትዮጲያ መብት ማለት ምንድነው? አንድ ግለሰብ ወይም ቡድን የመብት ጥያቄዎቹን ለመንግስት እንዴት ነው ማቅረብ ያለበት? ግራ የሚያጋባ ነገር ነው። ግን አንድ መራራ እውነት አለ እሱም መብት ማለት በኢትዮጲያ መንግስት መጥኖና ለክቶ ለራሱ በሚስማማ መልኩ ለማህበረሰቡ መብቶች ብሎ የተዋቸው ናቸው። መብት ሲባል በወያኔ ካድሬ አመለካከት ያው ሁሌ ንፅፅሩ ከዛ ከፈረደበት ደርግ ነው “በደርግ ጊዜ ሰአት እላፊ ነበር አሁን ግን የለም” ፣ “በደርግ ጊዜ ብሄራዊ ውትድርና ነበር አሁን ግን የለም” ስለዚህ ወያኔ ዲሞክራሲያዊ መንግስት ነው እንባላለን።
semayawi
ብጥብጥና ሁከት ምን ማለት እንደሆነ ሁላችንም ጠንቅቀን እናውቃለን ነገር ግን በአሁኑ ሰኣት በየእስር ቤቱ እየማቀቁ የሚገኙት ወጣቶች የመብት ጥያቄ በማንሳታቸው ነው እንጂ በጥብጠው እንዳልሆን ለማንም ግልፅ ነው። ደሞ ሌሎች አባባሎች አሉ “የተወሰኑ” ፣ “አንዳንድ” የሚባሉ ለምሳሌ ባለፈው ምስኪኖቹ የኢትዮጲያ መምህራን ደሞዝን አስመልክቶ ላነሱት ጨዋነት የተሞላው የመብት ጥያቄ ሟቹ አቶ መለስ “አንዳንድ ብቃት ያነሳቸው መምህራን ብጥብጥና ሁከት ሊያስነሱ ሲሉ” ብለው በአነስተኛ ገቢ በኑሮ ውድነት የሚሰቃዩትን ምስኪን የኢትዮጲያ መምህራን በሃዘን አንገታቸውን አስደፏቸው። እብሪት ከተሞላው ስድብና ማስፈራሪያ ውጪ ላነሱት ጥያቄ በአግባቡ እንኳን ማብራሪያ አልተሰጣቸውም።

የኢትዮጲያ ሙስሊም ማህበረሰብም ከህፃን እስከ ሽማግሌ እምነታቸውን አስመልክቶ ላነሱት ጨዋ የመብት ጥያቄ “አንዳንድ ብጥብጥና ሁከት ፈጣሪዎች” እየተባለ ይዘገባል። ባለፈው የብራዚል ማህበረሰብ ላነሳው የመብት ጥያቄ ፕሬዝዳንቷ ዲልማ ሩሴፍ የተናገሩት ንግግር እጅግ ያስቀናል “መብታችሁን ለማስከበር በመነሳታቹ ኮራሁባቹ” ነበር ያሏቸው። አንድ ነገር እርግጠኛ ሆኜ የምናገረው በወያኔ አገዛዝ ይህንን በፍፁም አንሰማም። ለምን? የኢትዮጲያ ህዝብ በጥባጭ ስለሆነ? ወይም መንግስትን አጉል ጥያቄ ስለሚጠይቅ? አይደለም። ህወሃት ራሱ የሰራውና እየሰራ ያለው ኢሰባዊ የሆን ግፍና የመብት ረገጣ ስለሚያስበረግገው ሰው ሲሰብሰብ አይወድም። እጅግ በሚያስገርም መልኩ በቅርቡ የሳውዲ መንግስት በኢትዮጲያዊያን ላይ ያደረሰውን አስከፊ ግፍና የመብት ረገጣ ለመቃወም የወጣውን ህዝብ እንኳን “ብጥብጥና ሁከት” ሊያስነሱ ተብሎ እየተደበደቡ ተበተኑ። ኧረ ሌላም ብዙ አይተናል።
ነፃና ዲሞክራሲያዊ መንግስትማ የህዝቡን የመብት ጥያቄ እንዴት እንደሚመልስ እናያለን። እንደውም የኢትዮጲያ ህዝብ ሲበዛ የዋህ ነው ባለፈው ውጥንቅጡ በወጣውና መላቅጡ በጠፋው የኢትዮጲያ ፖለቲካና ኢኮኖሚ የተነሳ ተሰደው በሳውዲ ሲሰቃዩ ቆይተው ወደሃገራቸው ከተመለሱት ስደተኞችጋ አንድ ሁለት ፎቶ ስለተነሱ ብቻ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩን የሚያደንቁም ተነስተው ነበር። ምን ስላደረጉ? ምንም። እንደው ህዝባችን ትንሽ ሲያረጉለት ወዲያው ለምስጋና አንገቱን ስለሚያጎነብስ ነው እንጂ። ይህን የመሰለ የዋህ ምስኪን ህዝብ በዘርፈብዙ ችግር ሲሰቃይ ማየት እጅግ ያበሳጫል።
ለምሳሌ የመብት ጥያቄ ማንሳት “ብጥብጥ” መባሉ ቀርቶ ለማንኛውም ኢትዮጲያዊ ተፈቀደ እንበልና ምስኪኑ የኢትዮጲያ ህዝብም “ኧረ ተው ከዚህ ሀገር ንቀለኝ” እያለ አማልክትን ከማስቸገር መብቱን ለማስከበር ቢነሳ ምን ያህሉ የሃገራችን ህዝብ የመብት ጥያቄ እንደሚያነሳ ሁላችንም መገመት አያቅተንም።
Muslim Etiopia 1
አንዳንዴ ሳስበው መንግስት ዝም ሲባል የተወደደ ይመስለዋል መሰለኝ ምናልባትም አንዳንድ አገልግሎት ሰጪ ቦታ የሚሰሩ ካድሬዎች የህዝቡን ሮሮ ትተው “ህዝቡ ለመንግስት ፍቅር አለው” ብለው ሪፖርት ስለሚያቀርቡ ይሆናል። እውነታው ቢገለፅ ግን ሪፖርታቸው የሚሆነው “መንግስት ሆይ ህዝቦችህ ይወዱሃል የምንልህ እኛ ነን እንጂ እነሱስ ሞትህን ይመኛሉ” ነበር።

ታስታውሱ እንደሆን አቶ መለስ “ይህ ማዕበል” ብለው አለወትሮአቸው ድምፃቸውን ሞቅ አርገው የተናገሩት መንግስታቸው የተወደደ መስሏቸው ነበር ወዲያው በነጋታው መልሱን አገኙት እንጂ። ግን እንዴት እንደዛ አሰቡ? በትክክል ቁጥሩን የማያውቁትን ህዝብ ፣ መንግስት በስርአቱ መዝግቦ ያልያዘውን ህዝብ ፣ በኑሮ ውድነት ፣ በነፃነት እጦት እያሰቃዩት ያለውን ህዝብ እንዴት ይወደኛል ብለው አሰቡ። ያስገርማል።

ወደዋናው ሃሳቤ ስመለስ ማንኛውም የሰው ልጅ መብቱን መጠየቅ ማስከበር አለበት ማንኛውም ኢትዮጲያዊም እንድዚሁ። ይህን ስል ግን የግድ መስቀል አደባባይ መሰብሰብ ላይቻል ይችላል ቢሆን ጥሩ ነበር ነገር ግን ሁሉም ኢትዮጲያዊ በሚኖርበት ፣ በሚሰራበት ፣ በሚማርበት ፣ አገልግሎት በሚያገኝበት ቦታ መብቱን ማስከበር አለበት። ባገኘው አጋጣሚ እምቢ ማለት አለበት።

የማለዳ ወግ ..ኢትዮጵያን ለማየት ፣ ጥምቀትን በጎንደር ማክበር!… (ነብዩ ሲራክ ከሳዑዲ አረቢያ)

$
0
0

የከተራው በአል

ከተራ ምንድን ነው? ከሚለው ትርጓሜ እንነሳ … በየዓመቱ የጥምቀት በዓል በድመቀት ይከበራል፡፡ ከበዓሉ በፊት የከተራ በዓል የሚከበርበትን ታሪካዊና ሃይማኖታዊ ገለጻ ከተራ ከበበ ካለው የግእዝ ግሥ የወጣ ነው፡፡ ፍችው ውኃ መከተር፣ መገደብ ማለት ነው፡፡ የጥምቀት ዋዜማ ታቦተ ሕጉ ከቤተ መቅደስ ወጥቶ ውኃ ባለበት አካባቢ ስለሚያድር የየአጥቢያው ሕዝብ እየተሰበሰበ በወንዝ ዳር ወይም በምንጭ አካባቢ ድንኳን ይተከላል፡፡ ድንኳንም ከሌለ ዳስ ሲጥል ይውላል፡፡ የምንጮች ውኃ ደካማ በመሆኑ እንዲጠራቀም ይከተራል ፣ ጉድጓድ እየተቆፈረ ውኃው እንዳይሄድ ይገደባል፡፡

ከተራ በዓል በየዓመቱ በበዓለ ጥምቀት ዋዜማ ጥር 10 ቀን ይውላል ። የኦርቶዶክስ ክርስትና እምነት ተከታይ ምእመናን ሲወርድ ሲዋረድ ይዘው በመጡት ሃይማኔታዊና ባህላዊ እሴት መሰረት በጥምቀትን በዓል ዋዜማ ወንዝ ምንጭ ውሃው ይገደባል ፣ ይከተራል። ውኃው የሚከተረው በማግሥቱ ጥር 11 ቀን የጥምቀት በዓል ስለሚከበር ለሕዝቡ መጠመቂያ እንዲሆን ነው። ይህ በጥምቀት ዋዜማ የሚደረገው ውኃውን መከተርና መገደብ ስርአትም ” ከተራ ” የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡

405383_3133893752237_1633541756_n

543833_10200420756947440_784368804_a

images-171

images-226

የከተራው በዓል ሲከበር

ታቦተ ሕጉን ተሸክመው ዮርዳኖስን እንደ ተሻገሩት ካህናተ ኦሪት፤ ካህናቱ የማይለወጠውን ታቦተ ሕጉን በራሳቸው ተሸክመው የብሉዩን ሥርዓት ከሐዲስ ኪዳን ጋር አንድ አድርገው የሐዲስ ኪዳን መሠረት ኢየሱስ ክርስቶስን እያሰቡ፤ ካህናተ ሐዲስም ወደ ከተራ (ዮርዳኖስ) ይጓዛሉ፡፡ ሊቃውንቱም እንዲሁ ለበዓሉ የሚስማማውን ቃለ እግዚአብሔር እያደረሱ እንደሚያድሩ የሃይማኖት ልሂቃን አባቶች ያስረዳሉ።

ከተራ ዕለት ጥር 10 ቀን ኢየሱስ ክርስቶስ በዮሐንስ እጅ ለመጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ ወንዝ የሄደበትን ለማዘከር ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን “ኃዳፌ ነፍስ ለጻድቃን” የሚለውን ዋዜማ ይቆማሉ፡፡ የዋዜማው ቀለም ከቀኑ በአራት ሰዓት በመላው አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ይጀመራል ። ከዚያም የዋዜማው ሥርዐት ቅዱስ ተብሎ እስከ ሰላም ያለው ቀለም ይደርሳል፡፡ በዕለቱም ቅዳሴ ይቀደሳል፡፡ ታቦተ ሕጉን የሚያነሡት ሰሞነኛ ካህን ከምግበ ሥጋ ተከልክለው ለዕለቱ የሚገባውን ጸሎት ያደርሳሉ፡፡በከተራው ዕለት ድንኳን ተተክሎ፣ ዳሱ ተጥሎና ውኃው ተከትሮ ሁሉም ነገር ከተስተካከለ በኋላ ታቦተ ሕጉ የሚንቀሳቀስበት ሰዓት ሲደርስ የየቤተ መቅደሱ ታቦታት በወርቅና በብር መጎናጸፊያ እየተሸፈኑ በተለያየ ኅብር በተሸለሙ የክህነት አልባሳት በደመቁ ካህናትና የመጾር መስቀል በያዙ ዲያቆናት ከብረው፣ ከቤተ መቅደስ ወደ አብሕርት /ምጥማቃት/ ለመሄድ ሲነሡ መላው አብያተ ክርስቲያናት የደወል ድምፅ ያሰማሉ፡፡ ምእመናን ከልጅ እስከ ዐዋቂ በዐጸደ ቤተ ክርስቲንና ታቦታቱ በሚያልፉባቸው ህዝበ ክርስትያኑ ያጅቧቸዋል። በአማሩ አልባሳት ተውበውም መንገዶች በእልልታ በሆታና በጭፈራ በማድመቅ ታቦቶችን በክብር ወደ ተዘጋጀው የበዓሉ ቦታ አጅበው ይደርሳሉ!

በዓለ ጥምቀት እና ኢትዮጵያ

ታላቁ የከተራ እና የጥምቀት በዓል ሲነሳ ኢትዮጵያውያን ሩቅ ዘመንን ተሻግረን ቅዱሳን ሰማዕት አባቶችን ሊቃውንት አባቶችን አስተምሮት እናዘክራለን። በቅዱስ ላልይበላ ዘመነ መንግሥት በኢትዮጵያ ምድር እየተመላለሱ በብሕትውና እና በስብከተ ወንጌል ያገለግሉ የነበሩት ጻድቁ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በአክሱም፣ በመቐለና በመርጡለ ማርያም እየተዘዋወሩ ባሕረ ጥምቀቱን ባርከዋል፡፡ በዐፄ ይኩኖ አምላክ ዘመነ መንግሥት (1260-1275 ዓ.ም) በጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት (1203-1204 ዓ.ም) አሳሳቢነት የተጀመረው ሥርዐተ በዓል ተጠናክሮ እንዲቀጥል በዐዋጅ ትእዛዝ አስተላልፈዋል፡፡ ታቦታቱም በሕዝብ ጥበቃና ክብካቤ ተደርጎላቸው በየጥምቀተ ባሕሩ እንዲያድሩ ወስነዋል፡፡ የበዓሉ አከባበር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየሰፋና አድማሱ ብሔራዊነትን እየያዘ መጣ፡፡

ከዐፄ ገብረ መስቀል ጀምሮ የአደባባይ በዓል የሆነው የጥምቀት በዓል በ15ኛው ክ/ዘመን በደገኛው ኢትዮጵያዊው ንጉሠ ነገሥት ዐፄ ዘርዓ ያዕቆብ(1426-1460 ዓ.ም) አማካኝነት ታቦታቱ ወደ ወንዝ ወርደው ዕለቱን እንዳይመለሱ፣ በዚያ ፈንታ በጥምቀት ዋዜማ ጥር 10 ቀን ከሰዓት በኋላ ወደ ባሕረ ጥምቀቱ ወርደው እንዲያድሩ፣ አገሩን በኪደተ እግር ይባርኩም ዘንድ በሄዱበት መንገድ እንዳይመለሱ በዐዋጅ ወሰኑ፡፡ ይህን ታሪክ በመከተል ዐፄ ናዖድ (1486-1500) ዓ.ም) ማንኛውም የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ምእመን ታቦተ ሕጉ ወደ ባሕረ ጥምቀቱ በሚወርድበት እና ከባሕረ ጥምቀቱ ወደ ቤተ መቅደሱ በሚመለስበት ጊዜ አጅቦ አውርዶ፣ አጅቦ መመለስ እንዳለበት በዐዋጅ አስነግረው ነበር፡፡ ሕዝቡም ታቦታተ ሕጉን በሆታና በእልልታ ከቤተ መቅደስ አጅቦ ከአወጣ በኋላ በባሕረ ጥምቀት ከትሞ ማደር ጀመረ ። …

ኢትዮጵያ ዜና ጥምቀተ ክርስቶስን ከሰማችበት ከመጀመሪያው መቶ ክፍለ ዘመን አንሥቶ በተለይም ከአጤ ገብረ መስቀል ዘመነ መንግሥት (6ኛው መ/ክ/ዘ) ወዲህ የጥምቀትን በዓል ዛሬ በሚታየው አኳኋን ስታከበር እንደ ቆየች ይታመናል፡፡ በክብረ በዓሉ ከመንበረ ክብራቸው ወጥተው ወደ ባሕረ ጥምቀት የሚወርዱት ታቦታት በካህናቱ ሃሌታ፣ በምእመናኑ እልልታ እና በየአጥቢያ አብያተ ክርስቲያኑ በተቋቋሙ የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች መዝሙሮች ታጅበው በተመሳሳይ አኳኋን እንደሚመለሱ ይታወቃል፡፡
ኢትዮጵያን ለማየት ፣ ጥምቀት በጎንደር ማክበር …
timket_in_gondar

በአርባ አራቱ ታቦት መናህሪያ በጎንደር ከልጅነት እስከ እውቀት የማውቀው ታላቅ ህዝባዊ በአል ቢኖር የጥምቀት በአል ነው . . . የጎንደር አባቶችና እናቶች ባማረ የባህል ልብሶቻቸው ተውበው ደምቀው ጎንደርና ጥምቀትን ያደምቋታል። ጥምቀት ገና ከጥንት ከጠዋቱ የውጭ ሃገር ጎብኝዎችን ቀልብ ከሚስቡት በአላት ቀዳሚ መሆኑንም አውቃለሁ ። አባቶች ጥንግ ድርብ እና አልፎ አልፎም ቀደምቱን ያማራ በርኖስ የባህል ልብሳቸውን ለብሰው ጥምቀትን ደምቀው ሲያደምቁት ፣ የቀረው ነዋሪም “ለጥምቀት ያልሆነ ልብስ ይበጣጠስ” ሆነና አቅሙ የፈቀደ አዲስ ልብስ አስገቶ ይለብሳል። ያጡ የነጡት ደግሞ ያላቸውን መላብስ አጣጥበውና በወግ በወጉ ጠቅመው በአደባባይ የሚታዩት በጥምቀት ነው፡፡ በጥምቀት የጎንደር ስመ ጥሩ የአርባ አራቱ ታቦት ፣ ሊቃውንት፤ ስመጥር የደብር አለቆችና ካህናት በሚያምረው ልብሰ ተክህኖ አምረውና ደምቀው ይታያሉ . . . በነጭ የባህል ልብሳቸው ላይ ጣል ከሚያደርጉት ጥቁር ካባቸውንና በራሳቸው ጥምጣም የሚታወቁት በጎንደር የቅኔ ፤ የመወድስና የአቋቋም ዝማሬ ሊቃውንት ባማረው አንደበታቸው የውዳሴ መዝሙር ጣዕመ ዜማ፣ ወርብና ሽብሸባውን በአደባባይ የሚያሰሙበት ልዩ አጋጣሚ ቢኖር ይህ የጥምቀት በአል ነው . . . ዘመን በዘመን ሲተካ ጥምቀት በጎንደር እንዲህ እያደመቀ እዚህ ደርሰናል . . . !
ዛሬም ጎንደር በጥምቀት በቱሪስት መናህሪያ ሆና ዘመንን የኢትዮጵያ መገለጫ ሆና አይን እንደሳበች ትገኛለች ! ከዛሬ አራት ከፍለ ዘመን (400 አመት ) በፊት የተሰሩት የጎንደር ቤተ መንግስቶች አስገራሚ ጥበብ ዛሬ ድረስ ውበትና ግርማ ሞገስ ይታይባቸዋል፡፡ የዚያን ዘመን ሰማይ ጠቀስ ቤተ መንግስቶችን አስገንብተው የጎንደርን ከተማ በመቆርቆራቸው የሚታወቁት አጼ ፋሲል ሱስንዮስ ጥምቀት መዋኛ ገንዳንም ከቀሃ ወንዝ ዳረወቻ ገንብተዋል። አጼ ፋሲለደስ ሃገሬው በአሉን የሚያከብርበትን የመዋኛ ቅጽግ ግቢ ከልለው ያሰሩ ብልህ መሪ ነበሩ ! ይህም የያኔው ብልህ መሪ ለጥምቀት የሰጠውን ልዩ ክብር አመልካች ለመሆኑ ጥርጥር የለኝም ፡፡ አጼ ፋሲል በቀሃ ወንዝ ዳርቻ ያሰሩት የመዋኛ ገንዳ ዛሬ ድረስ ለጎንደር ጥምቀት መድመቅ ፈርጥ ሆኖ ዘመን ሲነጉድ የዚያ ዘመን የስልጣኔ አሻራችን ያስቃኘናል፡፡ ከመዋመኛው አንድ ጫፍ ታቦተ ጽላቱ በክብር የሚያርፍበት መቅደስ አሰርተዋል፡፡ በዚያ የጸሎት ቤት ስርአተ ቅዳሴ ፤ ማህሌት ሽብሸባው ጥምቀት በመጣ በሄደ ቁጥር ይከወንበታል፡፡ ግራማ የተላበሰውን ይህን መዋኛ ሶስት ፎቅ ህንጻ በአስገራሚ ጥበብን ይታይበታል።
ጥምቀት በጥንታዊዋ መዲና በጎንደር ሲከበር የጥበብና የስልጣኔ አሻራ ሲከበር ለበአል አክባሪዎቹ ብዙ መልዕክትን ማጫሩ አይቀርም ! የአጼ ፋሲል የቀደመ ስልጣኔ ቅሪት ውብ ህንጻዎች የጥንቱን ማንነታችን እያወሱ ካወቅንበት ከዛሬ የኢሊ ጉዞዋችን እንድንነቃም እያደመቀ እያዋዛ ያዘክሩናል …
ጥምቀትን ታኮ የተመረቀው የመይሳው ካሳ ሃውልት ፣ የማይረሳኝ የመኪና አደጋ … ትዝታ

ዛሬ ዛሬ የጥምቀት በአል በአብዛኛው በወጣቱ ሙሉ ተነሳሽነት በልዩ ስሜትና ዝግጂት በልዩ ስሜት እንደሚከበር በስልክ ያጫወተችኝ እድሜዋ ከ80 የዘለለው የእድሜ ባለጸጋ እማሆይ እናቴ ነበረች ። ዛሬን አያድርገውና ድሮ በልጅነት ካህን አባቴንና እናቴን ተከትየ በፋሲል ውቅር ከተማ በጎንደር በአሉ አከባበር ደምቄ አድጌበታለሁና የጥምቀትና ጎንደር ትዝታ አብረውኝ ይኖራሉ …፡፡

ከሁለት አመት በፊት ጥምቀትን በጎንደር ለማክበር ባደግኩበት ቀየ ተገኝቸ ነበር ። በከተራው በአል በጥምቀት ዋዜማም በጉጉት ይጠበቅ የነበረው የአጼ ቴዎድሮስ ሃውልት ምረቃ ላይ ተገኝቸም ኢትዮጵያን በጎንደር አይቻታለሁ ፡፡ በተወለዱ ባደጉበት ምድር ለአንድ ክፍለ ዘመን ጥርኝ አፈር ለመታሰቢያቸው የተነፈጋቸው የኢትዮጵያ አንድነት ተምሳሌት የአጼ ቴዎድሮስ ሃውልት በጎንደር ከተማ እምብርት በፒያሳ መሃል አደባባይ ተሰርቶ የምረቃውን ስነ ስርአት ሲካሔድም ተመልክቻለሁ ። ካች አምና በተከበረው ጥምቀት በጎንደር ደመና አሳዛኝ ትዕይንት ሲስተናገድም እማኝ ነበርኩ !
394801_3133895432279_2125852827_n
የአባይ በርሃው የመኪና አደጋ : (

የጎንደር ጥምቀት ክብረ በአል ጋር የቴዎድሮስ ሃውልት ምረቃ ሊከበር በዝግጅት ላይ እያለ ከወደ አባይ በርሃ የተሰማው መርዶ የከፋ ነበር። መርዶው በመይሳው ካሳ ሃውልት ምረቃና በጥምቀቱ የደመቀ ዋዜማ ስሜታቸው በደስታ ላይ የነበርነውን በአል አክባሪ ሁሉ ቅስም የሰበረ ነበር። በአሉን ለማክበር አስበው ወደ ጎንደር ሲገሰግሱ በአባይ በርሃ በተከሰተው የመኪና አደጋ ህይዎታቸው ያጡበት ወገኖች ቁጥርም ከፍ ያለ ነበር ። በርሃው ወገኖቹን በልቶታልና ጎንደሬውን አንገቱን በሃዘን ደፍቶ ማቅ ያለበሰው ቀን ቢኖር ይህ ቀን ነበር :( ደስታቸውን ለመግለጽ ሳግ እየተናነቃቸው ለቴዎድሮስና ለሚናፍቋት አንድነቷ የተጠበቀች ኢትዮጵያ ያላቸውን ፍቅር በመግለጽ ላይ የነበረው ኢትዮየጵያዊ ከትንሽ እስከ ትልቅ በርሃው በበላቸው ወገኖቹ በሃዘን ቅስሙ መሰበሩና ስሜቱ መጎዳቱን በእያንዳንዱን ፊት ይነበብ እንደነበር አይረሳኝም …
በአባይ በርሃ ገደል ገብቶ ሰው የጨረሰው አውቶቡስ እኔ ልጆቸና እህቴ በአንድ ሆነን በተሳፈርንበት አውቶቡስ እኩል ከአዲስ አበባ ነበር የተነሳው። ከአዲስ አበባ እስከ አባይ በርሃ ድረስ ከበስተኋላችን ይጓዝ ነበር ። በአባይ በርሃ ደልደል ባለ መንገድ ዳር በአንድነት ለደቂቃዎች እረፍት አድርገንም ነበር ። እኛ ቀድመን አቀበቱን ወጠን ደጅን እንደደረስን የማይታመነውን አደጋ መርዶ ሰማን… ይከተለን የነበረው አውቶቡስ ከሃምሳ በላይ አብዛኛው እንደኛ ጥምቀትን በጎንደር ሊያከብር የተሳፈረው ወገን ገደል ገብቶ ሰው አንዳለቀ በቀትሩ የራዲዮ ዜና እወጃ ሰማን! ያ ቀን. ለእኔ የሚረሳ እና የሚዘነጋ አይደለም ! በአባይ አፋፍ አንድ ጫፍ እረፍት ባደረግንባት ደቂቃ ሰላምታ የተለዋወጥኳቸውን ወገኖች በሰአታት ልዩነት የማለቃቸውን አሰቃቂ ዜና የሰማሁባት እለት ሆዴን ያላወሰኝና ያስደነገጠኝ ስሜት ትዝታው አሁን ድረስ ያውከኛል …ነፍሳቸውን ይማር !
ኢትዮጵያ የምትከብርበት የጎንደር ጥምቀት …

ከአካባቢ የወረዳ የዞንና የገጠር ከተሞች የመጣው ኮበሌ ባለጀንፎ ሽመል ከዘራውን ወልውሎ ለሆታና ጭፈራው ዝግጅታቸውን ጨርሰዋል፡፡ ከሁሉም ቀልብን የሚስቡት የከተማ ጎረምሶች በህብረት ተሰባስበው በዘመነኛና በባህላዊው ዘፈን ጥምቀቱን ሲያደምቁት ፣ ወጣት አርሶ አደሮች በበኩላችው የሚያምር አረንጓዴና ሰማያዊ በቁልፍ የተንቆጠቆጠ ቂምጣና ጨሸሞዞቻቸው በተጨማሪ የሚያምር ገናባሌ አድርገው በአልባሳት ደምቀዋል፡፡ ኮበሌዎች ጠባብቡን ቁምጣ ፣ ሸሚዝና ገንባሌ ለብሰውና ከጎፈሬያቸው ላይ ሚዷቸውን ሻጥ በማድረግ በአሉን ለማድመቅ የበኩላቸው በማድረግ ላይ ናቸው ፡፡ አልፎ አልፎም ቢሆን ኮረዳ ሴቶች ጭምር በቅባት የጠገበ ጸጉራቸውን ቁንዳላ ተሰርተው አረንጓዴ ቀሚስ አሰፍተውና በነጩ ቁልፍ አሽቆጥቁጠው ከመቸውም ጊዜ በላይ ለጎንደር ጥምቀት ህብረ ባህላዊ ድምቀትን ሰጥተው አድማቂዎች ናቸው። ወጣቶች ፣ ሃገር ቤት ከመጣው ቢጤያቸው ጋር ሲላቸው ሰይ ሰይ ተብሎ የሚታወቀውን ባህላዊ የዱላ ጫወታ እየተጫወቱ ባአሉን ያደምቁታል። እንዲያው በአጠቃላይ ከህጻናት ጀምሮ ኮበሌው፣ ኮረዳው ፣ እና እድሜ ጠገብ አባቶችና እናቶች የጎንደር ጥምቀትን በአል ልዩ ውበት ናቸው . . .
አንተ የት መጣህ አይባልም …ማን የማንን ይጫወት አይባልም! ኦሮሞው ፤ከንባታው ፤ ጉራጌው፤ ሃረሪው ፤ትግሬው ፤ አማራው ፤ ሱማሌው ይዘፈናል ፣ የደለቃል ፣ ጃሎ ይባላል! ኢትዮጵያዊ በጎንደር የጥምቀት በአል አንድ ሆኖ ባንድ ክብረ በአሉን ይታደማል ! አገር ጎብኝው ፈርንጅና ጥቁሩ ከሃገረ አሜሪካ ፤ ከአውሮፓን ከሩቅ ምስራቅና ከአውስትራልያና ከተለያዩ አለማት የመጡት ሀገር ጎብኝዎች በካሜራቸው እያጠመዱ ጥምቀትን በጎንደር ሲያከብሩ የኢትዮጵያን በጎንደር እያዩ ነው! የእረፍት ጊዜያችውን በዓለ ጥምቀትን ተጠግተው ጎንደርን ሲጎበኙ በጨዋታው ደምቀው ተውበው፣ የዚያን ዘመን የእነ አጼ ፋሲልን ቤተ መንግስቶች ፣ የቅድመ አያቶቻችን ድንቅና ውብ ባህልና ያለፈ መልካም ስራ እየተደነቁ የሚያልፉበት ትዕይንት በመሆኑ ኢትዮጵያን ለማየት ጎንደርን በጥምቀት ማየት ያሰኝዎታል! በሀገሬው ሆታ ጭፈራ ተደምመው የደስታ የፌስታ ቀንወትን እያሳመሩ ኢትዮጵያን በጎንደር እያዩ ጥምቀትን ያከብራሉ ! . . . የካች አምናው ትዝታ ራሴን ቢያነሆልለው በከተራው በአል በትዝታ ተጉዠ በማለዳ ወጋዎጌ ይህችን ያህል ላስቃኛችሁ ወደድኩ . . .

መልካም የከተራና የጥምቀት በአል !
ነቢዩ ሲራክ

የግርጌ ማስታዎሻ : ስለከተራና ጥምቀት ብዙን መረጃ ያገኘሁት ከሐመር መጽሔት ሲሆን ለወዳጆች እንዲስማማ አድርጌ ማቅረቤን ሳልጠቁም አላልፍም።

ምርጫ እና የስርዓት ለውጥ

$
0
0

ሙሉጌታ አሻግሬ
mulugetaashagre@yahoo.com

አገራት ዘመናዊ የተባለውን የመንግስት አስተዳደር መተግበር ከጀመሩበት ግዜ አንስቶ እስከዚህኛው ዘመን ድረስ የተለያዩ የመንግስት አወቃቀርና ርዕዮተ ዓለም ተስተናግደዋል። ሰዎች መለኮታዊ እምነታቸውን ወደጎን አድርገው ከማኦ እስከ ማርክስ ከሌኒን እስከ ካስትሮ ‘ማርክሲዝም ያነበቡና የተገበሩ ብፁዓን ናቸው’ ብለው የችግርን ጥግ እስኪገነዘቡ ድረስ ነጉደዋል። ዓለማችን በሶሻሊዝም ስትናጥ፤ ኮምኒዝምም የዓለማችንን ህዝቦች ሁሉ እኩል አደርጋለሁ ብሎ በተነሳ ሰባ ምናምን ዕድሜው ተንኮታኩቷል። ምዕራባውያን ምስራቆችን በኢኮኖሚ ብልጫ ማርከዋቸዋል። የምስራቅ አውሮፓ አገራት ከምዕራብያውያኑ በኢኮኖሚ አቅማቸው እጅግ ዘቅጠው ተገኝተዋል።
election
ይሁን እንጂ አሁንም የዚህ ርዕዮተዓለም አራማጆች በአንድ ወይም በሌላ መልኩ እዚህም እዚያም ይታያሉ። የቻይናው ዘመናዊ ‘ልማታዊ መንግስት’ አወቃቀር ለዚህ አባባል አንዱ ማሳያ ነው። አሁን በአገራችን ያለው መንግስት ትላልቆቹ ‘ተሰሚ’ ባለስልጣናት የማሌሊት ደቀመዛሙርት ነበሩ። አሁንም በውስጣቸ እንደዛው ሊሆኑ ይችላሉ…ማን ያውቃል። ለዚህም ይሆናል ኢትዮጵያ የቻይናን ጠረን እየያዘች የመጣችው። የቻይና አካሄድ የአፍሪካ አምባገነን ባለስልጣናትን በወንበራቸው ለማቆየት ፍቱን መንገድ ነው። “ከዳቦ በኋላ ዲሞክራሲ”። አጭር እና ግልጽ አምባገነናዊ አካሄድ። ስለዚህ የመጨረሻው ሰው ዳቦ እስኪያገኝ ድረስ ዴሞክራሲ አላስፈላጊ ትሆናለች። ይህች አካሄድ በአገራችን መንግስት ይፋ ዕውቅና የተሰጣት ግዜ… አዲዮስ መድብለ ፓርቲ ስርዓት በኢትዮጵያ።

በሌላ በኩል ‘ ዲሞክራሲ ዘመናዊነት ነው’ ብለው የተነሱት ምዕራባውያን፤ ሃሳብን የመግለፅና የመንግስትን በህዝቦች በጎ ፍቃድ የመመረጥ ሁኔታን ጠቅልለው ለህዝባቸው በመስጠት ህዝቡ የዚህ ዕድል (መብት) ተጠቃሚ እንዲሆን አድርገውታል። ይሁን እንጂ እንደ ኮሚኒስቶቹ የጎላ የኢኮኖሚ ችግር ባይታይም በዲሞክራቶች በኩልም የኢኮኖሚው ሁኔታ ኮለል ብሎ እየፈሰሰ ነበር ለማለት ያስቸግራል። ዓለማችን ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የተዘፈቀችበት የኢኮኖሚ መውሸልሸል ምክንያትም ሃብት በተወሰኑ ቡድኖች እጅ እየተጠቀለለች መግባቷና የመንግስታት (የመስተዳድሩ) ኢኮኖሚውን የመቆጣጠር አቅም መልፈስፈስ ውጤት ነው የሚሉ ወገኖች አሉ። ይህ አስተያየት ትክክል ሊሆን ይችላል። ምክንያቱም ስርዓቱ ሃብትን ማዕከል በማድረግ ስለተገነባ ኢኮኖሚው ጡንቻ አውጥቶ የመንግስታትን የመወሰን አቅም ሲፈታተነው ታይቷል።

ከዚህ በተቃራኒ ጠንካራ ኢኮኖሚ በራሱ አገራትን እንደ አገር ሊያቆም እንደሚችል በተለያዩ አገራት በተከሰቱ ሁኔታዎች ታዝበናል። ከጥቂት ዓመታት በፊት ቤልጄየም ያለመንግስት ከአንድ ዓመት በላይ ቆይታለች። በዚህ ግዜ ውስጥ ሁሉ ይህ ነው የሚባል ችግር ሳይከሰት ዜጎች በነባር ህጎች ሲተዳደሩና ባለሃብቱም የታክስ ግዴታውን ሲወጣ ተስተውሏል። አንዳንድ ግለሰቦች የዚህ ውጤት ምክንያት የህግ የበላይነት በአገሩ በመስፈኑ ነው ብለው ቢከራከሩም የኢኮኖሚው ጥንካሬ በራሱ ትልቁ የወሳኝነት ድርሻ ነበረው። በእርግጥ የተዘረጋው አስተዳደራዊ ስርዓት(System) ጉልህ ድርሻ ነበረው። በኔዘርላንድም የተከሰተው ተመሳሳይ ሁኔታ ነበር። የመንግስት ካቢኔ አባላት ተኮራርፈው ምክር ቤታቸውን ከአንዴም ሁለቴ ዘግተው ፓርላማውን የልጆች እቃ እቃ ጨዋታ ባስመሰሉበት ግዜ ሁሉ የአገሩ ዜጎች ይህ ትርምስ እና ጫጫታ ትዝ ሳይላቸው የዕለት ተዕለት ድርጊታቸውን ሲያከናውኑ ታይተዋል። ዲሞክራሲና ኢኮኖሚ ከተባበሩ አይቀር እንዲህ ነው።

ስለዚህ በአግባቡ የተገራ ኢኮኖሚ የዜጎችን ሰላምና አኗኗር ለማቃናት ብቻ ሳይሆን ለአገር ህልውናም የራሱ አስተዋፅኦ አለው ማለት ነው።

ወደ አገራችን ይህን ሁኔታ ስንወስደው ያለመታደል ሁኖ ኢትዮጵያ ባዶ እጇን እያጨበጨበች ትገኛለች። ኢኮኖሚው የለ፣ ዲሞክራሲው የለ።

ኢትዮጵያችን ከተገነባችበት የነፃነትና የተጋድሎ ታሪክ ባሻገር ነፃነታችን ዳቦ እንዲሆንና አገራችን ዘመናዊ የመንግስት አወቃቀር እንዲኖራት ሁሉም ቅን አሳቢ ዜጋ ይመኛል። ዘመናዊነት ዘመናዊ ቁሶችን መጠቀምና ዘመን አመጣሽ ሁኔታዎችን መከተል ብቻ አይደለም። ዘመናዊነት ማለት መግባባት፤ ዘመናዊነት ማለት መቻቻል፤ ዘመናዊነት ማለት እርስ በእርስ መቀባበል፤ ዘመናዊነት ማለት ሃሳብን የመግለጽ ሁኔታ መመቻቸት፤ ዘመናዊነት ማለት የሕግ የበላይነት፤ ዘመናዊነት ማለት ህዝቦች በመረጡትና በፈቀዱት አካል መወከልና አገር እንድተዳደር ማድረግ ነው። በዚህ ዓለምአቀፋዊ የኢኮኖሚና ማህበረሰባዊ ትስስር (Globalization) ስርዓት ውስጥ ለመኖር የሌሎችን በጎ ልምድ መውሰዱ ብልህነት ነው። ካልሆነ ግን ያለንበትን ደረጃ አሻሽለን ቁልቁል እናድጋለን። ስለዚህ በአንጻራዊ ሁኔታም ቢሆን የተሻሉ የሚባሉትን አገራት የኢኮኖሚና መንግስት አስተዳደር ስርዓት ከኢትዮጵያ ባህልና አኗኗር ጋር አስታርቆ መተግበሩ እጅግ አስፈላጊ ነው።

አገራችን ንጉሣዊ ስርዓትን በሰፊው አስተናግዳለች። ከዚያም ሶሻሊዝምን ብሎም ያለፈው ስርዓት ዕድሜ ጥንፋፊ ላይ ቅይጥ ኢኮኖሚ ጭልጭል ብላ አልፋለች። በዚህኛውም መንግስት ‘ዲሞክራሲያዊ’ (እንዳትታዘቡኝ) ስርዓት እየተከተለች ነው።

በጄ!!! ዲሞክራሲውን ተቀብለን ስርዓቱን ለመገንባት ሰማይ እየቧጠጥን ይኼው ሃያ ሦስት ዓመት እንደምንም አለፈ። በ1997 አገር ጉድ ብሎ ፤ ህዝብ ተጨንቆ፤ ዲሞክራሲ በኢትዮጵያ ልትወለድ የምጥ ሂደት ውስጥ ገባን። ዲሞክራሲ ለጥቂት እውን ሳትሆን ጨነገፈች። ‘ዲሞክራቶቹ’ መግደል ጀመሩ። ዲሞክራሲ ናፋቂዎች ታሰሩ፤ ተገደሉ። ሌሎች የሚዜ አገልግሎት ለመስጠት ፓርላማ ገቡ። ለአምስት ዓመት በዘለቀው የመሣቂያ መሣለቂያ ድራማ እንደ ችሎታቸው ተውነው፤ ህዝቡ ዲሞክራሲ ይዘውልን ይመጣሉ ብሎ ደጅ ደጁን እያየ ሲጠብቅ ከፓርላማ ተሰናበቱ። አራት ነጥብ።
ቀጠለች አብዮታዊ ዴሞክራሲ። ምረጡ አስመርጡ ። ሃሳባችሁን ስጡ ተናገሩ ተባለ። እጅግ የተሳካ ምርጫ ተደርጎ ታሪካዊዋ አብዮታዊ ዲሞክራሲ 99.96% የፓርላማ ወንበር አግኝታ ኑሮ ቀጠለ።

አሁንም በቅርቡ ምርጫ አለ። ህዝቡ ጥያቄ አለው፤ ነፃነትና ፍትህ። ልማትና ዕድገት። እኩልነትና ሰላም። ይኽን ጥያቄ እንመልሳለን ያሉት ሰላማዊ የትግል ስልት የሚከተሉ የፖለቲካ ድርጅቶች ጓዛቸውን እየሸከፉ ነው። በምርጫ ሊወዳደሩ። መንግስትም የ ’ ይቻላል’ አረንጓዴ መብራት አሳይቷቸዋል። ለእነዚህ ድርጅቶች ጥያቄው የሚጀምረው እዚህ ላይ ነው።

የመጀመርያው ጥያቄ፣ የመጪው ምርጫ ዓላማ ምንድን ነው?

ህዝቡ የአጃቢነት ስራ የሚሰሩ ግለሰቦችን በፓርላማ ማየት አይፈልግም። ፓርላማ ገብቶ የአምስት ዓመት የስራ ኮንትራት የሚፈልግ የሰላማዊ ትግል አራማጅ አባል ካለ፤ በህዝቡ ስም ከመነገድ በየትኛውም የመንግስት ይሁን ሌላ ድርጅት መቀጠር ቢሞክር መልካም ነው። ለፓርላማ የሚደረገው ሩጫ ውጤት ለህዝቡ የሚታይና የሚጨበጥ ለውጥ ማምጣት አለበት። ካለፉት የፓርላማ ኳኳታዎች እንደታዘብነው፤ ድምፀ ተዓቅቦ በማድረግ ይሁን ድጋፍ ባለመስጠት አንዲት ነገር ስትለወጥ አሊያም ስትስተካከል አላየንም። ለውጥ ለማምጣት ደግሞ ፓርላማ ገብቶ በቃላት ጉሽሚያ የነፃ ትግል ማድረግ የትም እንደማያደርስ በደማቁ አይተነዋል።

የመንግስትን ኪሳራነትና ድክመት ዲያስፖራው ሳይቀባባና ሳይፈራ እንደ ጉድ ያጎነዋል። “የተከበሩ” “ክቡርነትዎ” ምናምን ሳይል አካፋን አካፋ ይለዋል። ጉድለትን መናገር ለውጥ የሚያመጣ ቢሆን፤ የህዝቡን ጥያቄ እያሽጎደጎደ በየዕለቱ በሚጮኽው ዲያስፖራ ብቻ ኢትዮጵያ ውስጥ ከዛሬ ስንት ዓመት በፊት ዲሞክራሲ በነገሰች። የመንግስት ተቃዋሚ ነን የሚሉት ፓርላማ ቁጭ ብለው የሚያሽሞነሙኑትን ጥያቄ ገዥው መንግስት እጅግ ቀድሞ ከዲያስፖራው እርቃኑን ይነገረዋል። ስለዚህ ይህ ችግር “በክቡርነትዎ ታጅቦ ሲቀርብ የፓርላማው ስራ እንደተለመደው የፕሮቶኮል አገልግሎት ይሆናል ማለት ነው። የፓርላማ መግባት ዋነኛ ግብ በስማ በለው “የተከበሩ” ለማለት ሳይሆን የህዝቡን ጥያቄ ለመመለስ ብቻ ነው። የህዝቡ ጥያቄ ምላሽ ደግሞ በተግባር መሆን አለበት። ዳቦ እና ነፃነት ከቃላትነት ወርደው የሚዳሰሱ መሆን አለባቸው። የመንግስትን አሰራር አቃቂር በማውጣትና በቃላት መጎንተል ዳቦ አልሆነም። የህሊና እስረኞችንም ነፃ አላወጣም። በዚህ ሂደት ውስጥ አንድም ግዜ ቢሆን ገዥው መንግስት ለማከናወን ያቀደው ተግባር ተከልሶ አሊያም ተሰርዞ አያውቅም።

ስለዚህ። ስለዚህ ህዝቡ ለውጥ ይፈልጋል። ይህ ለውጥ የሚመጣው ደግሞ በ50+ የፓርላማ ጨዋታ ብቻ ነው። ይህን በኢትዮጵያ ፓርላማ ስንተረጉመው በፓርላማው ካሉት 547 መቀመጫዎች ቢያንስ 274 መቀመጫዎች (ሁሉም ተመራጮች አምስቱን ዓመት በሰላም ካጠናቀቁ) ያስፈልጋል። በመሆኑም የሰላማዊ ትግል አቀንቃኞች ይህን ያህል መቀመጫ ማግኘት ግድ ይሆንባቸዋል። የወንበሯ ቁጥር ከዚህ ዝቅ ካለች የተለመደው አጃቢነት በመሳቂያ መሣለቂያነት ይቀጥላል። ስለዚህ አጃቢነት መብቃት አለበት።
ሁለተኛው ጥያቄ፣ የሰላማዊ ትግል ሰልፈኞች ድል ለማድረግ ምን ያህል ዝግጁ ናቸው?

የፓርቲዎቻችንና ድርጅቶች ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ናት። ሁሉም ሰላማውያን የሰፈሩት ከከተሜው ጋር ነው። አገሪቱ ደግሞ 85% ህዝብ አለኝ የምትለው ከከተማው ውጭ ነው። ስለዚህ የፓርላማው ወንበር ያለው ከተማ ላይ አይደለም። ወንበር ከድሃው ገበሬ ጋር ነው ያለችው። ከህዝቡ የወንበር አደራ ለመቀበል መታመን ያስፈልጋል። ህዝባችንስ ደግሞ ለማያውቀው ሰው እንዴት ወንበሩን በአደራ ይሰጣል ? ለዚያውም ለአምስት ዓመት። ስለዚህ እንሂድ ፤ እንውረድ። የደፈረሰውን ጠጥተን፤ ጢስ አይናችንን እየወጋን የድሃውን ወገን ክፉ እና ደግ እንካፈል። የሃዘን እንጉርጉሮውን ቅኔ እንፍታ።
የእኛ ነጭ ሸሚዝ በከረቫት መታነቁ በጠኔ ለሚመታው፤ በበሽታ ለሚማቅቀው፤ ለታረዘው ላልተማረው ወገን ምኑም አይደለም። ምናልባት የበላይነታችንን ለማሳየት ካልተጠቀምንበት በስተቀር። ነገርግን አገሪቷን እንደ አገር ለማቆም ደም እና ላቡን ለማፍሰስ የማይሰለቸው ወገን የእኛ ነጭ መልበስና ማማር መሠረት ነው። አገር ስትወረር ደሙን የሚያፈስ ድሃው ገበሬ ነው። ሃገርህ አይደለም ተብሎ የሚፈናቀለው ይሄው ወገን ነው። ረሃብና ድርቅ ሲመታው የሚረግፈው ይሄው ድሃ ዜጋ ነው። እኛ ነጭ ከሻኛ እያማረጥን እንድንበላ አፈር ምሶ አፈር ሆኖ የሚለፋው ይህ ድሃ ገበሬ ነው። ስለዚህ እሱን ሳንይዝ ሰላማዊ ታጋዮች ሆነን ከተማ ውስጥ ተሞሽረን በአምስት ዓመት ውስጥ ሁለት ቀን ሄደን ምረጠን ስንለው ይታዘበናል። መቼም ቋንቋውን ስለምንናገር፤ ብንወዛም መልኩን ስለምንመስል የአንድ አገር ህዝብ እንደሆንን ከመገመት ውጭ ችግሬን ይገነዘባሉ ፤ መፍትሄ ያመጣሉ ብሎ አያምንም። ህዝባችን እንዲያውቀን አብዛኛው ኑሯችን ከእሱው ጋር ይሁን።

ፓርቲዎችና ድርጅቶች በአገሪቱ የተለያዩ ቦታዎች ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት እንዳላቸው ይናገራሉ። የእነዚህ ጽህፈት ቤቶች ስራ ምን እንደሆነና ምን እንደሰሩ የሚያሳይ ሪፖርት ለህዝብ የቀረበበት ግዜ የለም። አንዳንዶቹ በራቸው በወር አንዴ ይከፈት ይሆናል። የበዙት ደግሞ የሸረሪት ትዕይንት ማሳያ ሆነው ይከርማሉ። የተወሰኑት ደግሞ የፊት በሩ ተቆልፎ በስተጀርባው የግለሰብ መኖሪያም እንደሆኑ የአደባባይ ምስጢር ነው። ምን እየሰራን ነው የህዝቡን ጥያቄ እንመልሳለን የምንለው? በቃ ከታገልን የእውነት እናድርገው። ከተማ ላይ ተከማችተን በፓርላማ ናፍቆት ከምንቆዝም ፤ ህዝቡን ተጠግተን ኑሮውን እንኑር።

ስለዚህ የፓርላማ ወንበር የምታልሙ ድርጅቶች ተባብራችሁም፤ ተዛዝላችሁም ቢያንስ 274 ወንበር ማምጣት አለባችሁ። ሰሞኑን እንደተሰማው ከሆነ አዳዲስ ድርጅቶች ልምድ ለማግኘት እንዲችሉ ፓርላማ ቢገቡ የተሻለ ነው የሚል አንዲት ቀልድ ተለቃለች። የምን ልምድ እንደሆነ ግልፅ አይደለም። የፓርላማ ወንበር ምን ያህል እንደሚመች? አፈጉባዔው ስንት ግዜ እንደሚያስፈራራና መነጋገሪያውን ስንት ግዜ እንደሚያጠፋብን? ወይስ የፓርላማው በር ላይ ጫማ እና ቀበቶ እያወለቁ የሚደረገው ቅጥ አንባሩ የጠፋውን ፍተሻ መለማመድ?
የኢትዮጵያ ህዝብ ሲጀመር ሰው ነው። ከዚያም የአገሩ ዜጋ። መለማመጃ አይደለም። ስለዚህ ለፓርላማ እንሮጣለን የምትሉ ወገኖች የተለመደውን የሚዜ አገልግሎት ላለመስጠት እርግጠኞች መሆን ያስፈልጋችኋል። ከዚህ በዘለለ ፓርላማ በመግባት በገዥው ስርዓት የሚዘጋጀውን ድራማ በአጃቢ ተወናይነት በመተወን የምታተርፉት መሳቂያና መሳለቂያ መሆን ብቻ ሳይሆን የህዝቡንም ችግር ለአምስት ዓመት ማራዘም ነው። በጥልቀት አስቡበት።
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!!

ክህደት ከአናት ሲጀምር:- በቀድሞው የኢትዮጵያ አየር ኃይል ውስጥ

$
0
0

እውነት ቤት ሥትሰራ …
ውሸት ላግዝ ካለች
ሚስማር ካቀበለች
ጭቃ ካራገጠች
ቤቱም አልተሰራ … እውነትም አልኖረች ።
… እንደዚያ ነው በባቢሎን ዘመን ።

የአንዱ ቋንቋ ከአንደኛው ይዘበራረቃል ….. መግባባትና መረዳዳት ብርቅ ይሆናል ። በጠራ አማርኛ የተጣፈውን በጉግማንጉግኛ በመተርጐም ከውስጡ የሚፈልጉትን ብቻ አለፍ አለፍ እያሉ ያነቡታል ። እናም የራሳቸውን ትርጉም ይሰጡታል ። ፍየል ወድያ ….. ቅዝምዝምም ወዲህ ይሆናል ።
ከቀድሞው የኢትዮጵያ አየር ኃይል አባላት መካከል ጥቂት አዛውንቶች ታሪክን ደልዘው በወያኒኛ አዲስ ታሪክ ስለ አየር ኃይሉ እንዲፅፉ በህውሃት እየተጠየቁ ነው ። እነዚህ ባለ ብዙ አኩሪ ታሪክ ባለቤት አዛውንቶች መንታ መንገድ ላይ ቆመዋል ። በዓለም ዙርያ ተበትነው ያሉት የቀድሞው አየር ኃይል አባላት ሃሳባቸውን እንዲደግፉና የእርዳታ እጃቸውንም እንዲዘረጉ ለማግባባት እየሞከሩ ነው ። እኛም የቀድሞው የአየር ኃይል አባላት እንዲህ አልን ……….
ethiopian airforce
“ የአየር ኃይልን ታሪክ ለትውልድ ለማስቀረት የምታደርጉት ጥረት በጐና የሚደገፍ ምግባር ነው በርቱ ፤ ነገር ግን የገዢው ፓርቲ ሞግዚትነት አያስፈልጋችሁም ። በተጨማሪም በተፅዕኖ ስር ሆናችሁ ሚዛናዊነት የሚጐድለውና የተደለዘ ታሪክ ለትውልድ እንዳታቆዩ ሥጋት ቢጤ አለችን ።
(ያም ቢሆን መፅሃፉን ካነበብን በኋላ የምንታዘበው ይሆናል … አያጣላም ።) የአየር ኃይል ቬተራን አሶሴሽንን እናቋቁማለን የምትሉትን በተመለከተ ግን ወራጅ አለ ። እጅግ ከስጋት በላይ የሆኑ ጥያቄዎች አሉን ። “ የቀድሞው አየር ኃይል ቬተራን አሶሴሽን ” እያላችሁን ከሆነ ግን እንግባባለን ።
የሚለውን ጥቅል ሃሳብ በመልዕክታችን ብንሰድላቸው በጉግማንጉግኛ በመተርጐም እኛ ፖለቲካ አንነካካም …. ፖለቲካንና ኰረንቲን በሩቁ ነው ብለናል ይሉናል ከአዲስ አባ ደብዳቤ እየፃፉ ። እነሱ ለካ የአሁኑን የህውሃትን መንደርተኛ አየር ኃይል ነው ቬተራን እያሉ የሚያንቆለጳጵሱት ። በህውሃት ሰማይ ስር ጉድ ሳይሰማ አያድርም አይደል !

እኛ ድፍን የአየር ኃይል ተቋም ላይ ስለተፈፀመ ክህደት ስናወራ …. እነሱ አንድ ግለሰብ አገርንና ህዝብን ለከዳ ስርዓት ስለሚመሰርተው ዕድርና የተዝካር ግርግር ሊያስረዱን ይሞክራሉ ። እኛ እኰ የቆማችሁበት አፈር ሥር ነፍሱ ያልወጣች የምታጣጥር የገዛ ጓደኛችሁ ነፍስ አለች ነው የምንላቸው ።
መጀመሪያ ባለንጀራችሁን ነፃ አውጡት ፤ እናንተም በጐን በሾርኔ ሳይሆን በአደባባይ በህግ ነፃ ውጡ ምክንያቱም እንደ ዶሮዋ ገመዳችሁ ረዘመላችሁ እንጂ ፈፅሞ አልተለቀቃችሁም እያልን ነው ።

ህውሃት እንደሆነ በሰው ተጠቅሞና አዋርዶ እንደሚያባርር የአደባባይ ሚስጢር ነው ። ደግሞም ይህ ይጠፋችኋል ብለን አንሞግትም ፤ ….. የመሰንበት ጉጉት ህሊናን ፈፅሞ ካልተቆጣጠረ በቀር ። አየር ኃይል ለአገር አንድነት የተፋለመ ጀግና እንጂ ጨፍጫፊ ያለመሆኑን በአደባባይ ስትመሰክሩና በህግ
ስታስነግሩ ….. የአየር ኃይል ተቋም እንደ ተቋም ነፃ ሲወጣ …. እርቅ ሲወርድ ፣ አገርን ከጠላት በመከላከላቸው ብቻ የሞትና የእድሜ ልክ ፍርደኞች በአደባባይ ነፃ ሲወጡ …. ያን ጊዜ ሁላችንም በአንድነት ነፃ እንወጣለን ። ያለበለዚያ ግን ትውልድም አገርም ላይ ይቅር የማይባል ክህደት ትፈፅማላችሁ እያልን ነው ያለነው ፤ በጠራ አገርኛ ቋንቋ ።

የቬተራን አሶሴሽንን በመወከል ያገባኛል ብለው ከአዲስ አበባ መልዕክት የሰደዱልን ሰው በፍፁም ሃሳባችንና ሥጋታችንን በትክክል የተገነዘቡ አይመስሉም ወይንም ዛሬ ኢትዮጵያ በምትባለው አገር ውስጥ ያለውን ነባራዊ ሁኔታ የሚከታተሉም መሆናቸውን እንድንጠራጠር እያደረገን ነው ። ድንገት ዘንድሮ ጆሮዋቸውም ዓይናቸውም የተከፈተላቸው ይመስል በቃል ያጠኑትንና ስለ አየር ኃይሉ የሚገምቱትን በጐ ፍላጐት ለመተግበር የተነሱ ይመስላል ።

የህውሃት አስተዳደር አዛውንት የአየር ኃይሉን አባላት በማምሻ እድሜያቸው ታሪክን ደልዘው የእራሱን የተንጋደደና የተንሸዋረረ ታሪክ እንዲፅፉለት እየተጠቀመባቸውና ከጠራ ታሪካቸው አንስቶ ከራሱ ቆሻሻና ስውር ፍላጐት ሥር እያንደባልላቸው ያለ ይመስላል ። አየር ኃይሉ በአዋጅ ሙሉ ለሙሉ ከስራ ውጪ በተደረገበት ዘመን ላይ ፤ ጨፍጫፊ ተብሎም ቅፅል ስም ወጥቶለት ወደ ከርቸሌ መጋዙንና በመንደርተኛ ፓይለቶች እየተተካ መሆነኑን ትንፍሽ እንዳይሉ በዚሁ በምሽት እድሜያቸው እየተደለሉ ናቸው ። እንዲያውም ሙዝየም እስከ መክፈት የዘለቀ ህልምም እንዳላቸው እየጠቀሱ ነው ። አገር ቢኖረንማ ኖሮ ለትውልድ የሚቀር ፣ ታሪክን የሚዘክር ሙዝየም ማቆም እንዴት የተባረከ ህልም ነበር ? ነገር ግን አገርም ዜግነትም በተዋረዱበትና እድሜያቸውን ሙሉ ለአገር አገልግሎት ያበረከቱ አንጋፎች እንደ አሮጌ ቁና በውርደት እንዲኖሩ በአደባባይና በአዋጅ ባይበየን ኖሮ ፣ ትውልድም በበጐ መሰረት ላይ ቀጥሎ ቢሆን ኖሮ …. ሁሉም አላማ በጐና ለአገርም ሆነ ለትውልድ የሚጠቅሙ ይሆኑ ነበር ።

እንግዲያውስ እነዚህ በህውሃት እየተደለሉ ያሉት የአየር ኃይሉ ነባር አዛውንቶች እርማቸውን ያውጡ ። ህውሃት አገሪቷን ከተቆጣጠረ ወዲህ ያለውን አየር ኃይል ተብዬ እንጂ የቀድሞውን ታሪክ ምናምኒት አሻራ እንኳ አያገኙም ። አጠቃላይ ሰፈሩና ቢሮዎቹም ጭምር በአይጥ መንጋ እንደተመታ ባድማ ዶክመንቶች ተፈርፍረው ድምጥማጣቸው መጥፋቱን አይጠራጠሩ ። የአየር ኃይሉን የታሪክ አሻራ ሊያስረዱ የሚችሉ የተለያዩ አውሮፕላኖችን ማናምኒት ሳያስቀር አቧራቸውን እያራገፈ የህውሃቱ አበበ ተ/ኃይማኖት (ጆቤ) እዚህ ግባ በማይባል ዋጋ መቸብቸቡን እንዴት ሳይነግራቸው እንደቀረ ይገርመናል ? ይህ ቀበኛ ሽፍታ ለጌጥና ለታሪክ በአየር ኃይሉ ጠ/መምሪያ ፊት ለፊት እንኳ ተቀምጣ የነበረችውን ገብሬ ቦላሌን ሳይቀር አንጠፍጥፎ መሸጡን ለምን ደበቃቸው ? ታሪክ በመስራት አገራችንን ያስከበረችውን ኤፍ-5 አውሮፕላንንስ አንዲት ሳያስቀር መቸብቸቡንስ ?

በትግራይ ነፃ አውጪ ግንባር የሚመራውን የአሁኑን ሥርዓት አያውቁትም እንበል ወይስ የክፋትና የብቀላ ምግባሩን ሁሉ ትተው በጐ ተክለ ሰውነት ሊገነቡለት እየሞከሩ ይሆን ? ታዲያ ይህንን እየሰሩ እንዴት ፖለቲካ አንነካካም ይሉናል ? በእነርሱው አመራር ስር የተገነባው የአየር ኃይል ሰራዊት እኰ በጅምላ ጨፍጫፊና ወንጀለኛ ተብሎ እድሜውን ሙሉ ከአቀናው መስሪያ ቤት በውርደት ተባሮ ቤተሰቡ ተበትኖ በረሃብና በችጋር እንዲያልቅ ተፈርዶበታል ! እውነተኛዎቹ የአየር ኃይሉ አርበኞች ድፍን 22 ዓመታት ሙሉ ተሸማቀውና አንገታቸውን ደፍተው መሃል ደ/ዘ ውስጥ (በቀለ ሞላ ሆቴል ፊት ለፊት) በጠጠርና በቆርኪ ዳማና ቼዝ ሲጫወቱ የአዛውንቶቻችን መንግስት የት ነበር ? ለዚህ ሁሉ ግፍና በደል ተጠያቂው ማነው ? እነዚህንና ሌሎች በደሎችን እንዴት ነው የሚያስታርቁት ? በምንስ መመዘኛ ቀበኛ ሽፍታ የመሰረት ድንጋይ እንዲያነጥፍላቸው ያደርጋሉ …. ! ከረገጡት ምድር ስር
የባልንጀሮቻቸው የምትቃትት ነፍስ ምን ትላቸው ይሆን ? ፖለቲካ … ፖለቲካ …. ለምን እንደሚሉን አልገባንም ። ፖለቲካ ምንድነው ?

ለዘመነኖቹ የመንግስት ባለስልጣናት ማደር ? ለስብሰባ ሲጠሩ ፈጥኖ ሸገር ላይ መከሰት ? ወይስ ሲመሩት የነበረውን ሰራዊት አስማርኰና ክዶ ለትግራዩ የነፃነት (ተገንጣይ) ግንባር በፈቃደኝነት መገበር ? እኛ ፖለቲከኞች እያሉን የሚያበሻቅጡን ከአገር በግፍ ተገፍታሪ ስደተኞች በሰላም ተከባብረንና ተዛዝነን ድፍን 20 ዓመታትን እንዳሳለፍን በአለፈው የበጋ ወቅት በዋሽንግተን ከተማ ተገኝተው መታዘባቸውን እናውቃለን ። አየር ኃይል ማለት ለኛ መታወቂያችን ፣ ማንነታችንና ዜግነታችንም ጭምር ነው ። በህብረት ተደጋግፈን እንኖራለን ፤ የተቸገረን እንረዳለን ፣ የታመመን እናስታምማለን … እንጠይቃለን ፣ እስከወዲያኛው የሚሰናበተንንም በኃዘን እንሸኛለን ።

ጀግኖቻችንን ከተጣሉበት እያስታወስንና እያነሳን እናከብራቹኋለን እንላለን ። በየዓመቱም የአየር ኃይል ቀን በማለት በህብረት ዩኒፎርማችንን ለብሰን ባንዲራችንን ከፍ አድርገን እያውለበለብን ኢትዮጵያ ሃገሬን እንዘምራለን ….. ። ይህንን ባንዲራና ዝማሬ የአሁኑ መንግስት አይወደውም ። በዘር ከፋፍሎ እኛ እና እነርሱ ፣ የቀድሞውና የአሁኑ ፣ ጨፍጫፊና ዲሞክራቲክ በማለት እየለያየ አጥፍቶናል ። አሁን ደግሞ እዚሁ ያለንበት አገር ድረስ ክንዱን እያረዘመ መካከላችን ሊገባ እየተቅበዘበዘ እንደሆነ ይገባናል ። እባካችሁን አዛውንቶቻችን ለዚህ መንደርተኛ ስርዓት ክርንና ጅማት እየሆናችሁ ህውሃት ጣቱን እቤታችን ድረስ እንዲያረዝም እየረዳችሁ መካከላችን እንዲገባ አታድርጉ ፤ በማህበራችንም በኩል አትምጡ ።

በግል እኰ መፅሃፍ አይደለም ኤግዚቢሽንም መክፈት ትችላላችሁ ። አሁን እየመጣችሁበት ያለው መንገድ ግን የሁሉንም ምክር ፣ የብዙሃንን ይሁኝታ ይጠይቃል ። እናንተ ደግሞ እዚያው አገር ቤት ያሉትን እውነተኞቹን አርበኞች አንድ በአንድ ሲያልቁ ጠብቃችሁ ፣ በህይወት የተረፉትንም ንቃችሁና ገፍትራችሁ ቀበኛ የሃገር ጠላት የሆኑትን ቱባ የህውሃት ባለስልጣናትን በጀርባችሁ አዝለችሁ አትላንቲክን በማቆራረጥ ልታነታርኩን ትሞክራላችሁ። ለምን ድምፃችሁን አጥፍታችሁ ታሪክ መፃፍም ሆነ ዕድር ማቋቋም አልመረጣችሁም ? በማህበራችን በኩል ለመምጣት ለምን መረጣችሁ …. ? በብዙሃን ስደተኛና በውርደት ተባራሪ ስም በየሸራተኑ ከበሮ መደለቁንስ ምን አመጣው ?

እንግዲያውስ ለሁለተኛ ጊዜ ምክር እንለግስ ……….
ሰው ባለቀ እድሜው ላይ ለኑዛዜ ይመቻቻል ….. እውነትን ተናግሬ ካልሞትኩ ብሎ ከህሊናው ጋር ትንቅንቅና እልክ ይጋባል ….. እውነቱን አፍርጦ በመሸበት ያድራል … እንጂ ለዳግም ምርኰ እራሱን አሳልፎ አይሰጥም ። በዚህ እድሜ እኰ ግጥም ብሎ ከሞላ የውስኪ ባንኰኒ ላይ የምንጭ ውሃ ካልሆነ ንክች አላደርግም .. ፣ ከተትረፈረፈ ጮማና ቁርጥ መሃል ቲማቲምና ቅጠላ ቅጠል ካልሆነ ምናምኒት አልቀምስም እየተባለ የሚኖርበት እድሜ ነው ፣ ብዙ የሚያጓጓ ህይወት የለም ። ታዲያ ምንድነው በዚህ በኪኒኒ ተደግፎ በሚኬድበት የምሽት እድሜ ላይ ሆኖ ውሃና ዘይትን ለመቀላቀል መሞከር ? በዚህ ምግባር ትውልድ አይደለም ከአብራክህ የወጣ ልጅ ይጠየፍሃል ።

እግዚአብሄር ኢትዮጵያን ይባርክ
ታዛቢዎች በህብረት !
ከቀድሞው የኢትዮጵያ አየር ኃይል በያሉበት ።

PDF created with pdfFactory trial version www.pdffactory.com

ከ18 በላይ የሙስሊም ተቋማት “ዘወትር ከመፍትሄ አፈላላጊው ኮሚቴ ጎን ነን፤ ትግላችንም ተጠናክሮ ይቀጥላል”አሉ

$
0
0

muslim dim
(ዘ-ሐበሻ) በተለያዩ ቦታዎች የሚገኙ ከ18 በላይ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የቋማት በ እስር ላይ ከሚገኙት መፍትሄ አፈላላጊው ኮሚቴ ጎን እንቆማለን፤ ትግላችንም ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ ለዘ-ሐበሻ በላኩት መግለጫ አስታወቁ።

“በመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴአችን በቅርቡ የተሰጠው መግለጫ ለትግሉ መነቃቃትን የፈጠረና አባላቱም ከረዥም ጊዜ እስራትና ሰቆቃ በኋላ ለተነሱለት ዓላማ በጽናት ለመቆማቸው አድናቆታችን የላቀ ነው፡፡ የህዝብ ልጅነታቸውንና የእምነት ነጻነት አውነተኛ ጠበቆች መሆናቸውን በተግባር አስተምረውናል፡፡” ያሉት ተቋማቱ “ይህም ለትግሉ ቀጣይነት በአንድነት ለመሥራት ቃላችንን የምናድስበት አጋጣሚ የፈጠረልን ሲሆን የፍርድ ቤቱን ውሳኔና ባጠቃላይ መንግስት በተያያዘው ሙስሊሙን የማዋከብ፣ የማሸበር እንዲሁም ንብረቶችን የመቀማት ህገወጥ ድርጊት በሚመለከት የሚከተለውን ባለ ስድስት ነጥብ የአቋም መግለጫ አውጥተናል፤” ብለዋል።

ሙሉውን መግለጫ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

Viewing all 8745 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>