Quantcast
Channel: ዘ-ሐበሻ – Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 8745 articles
Browse latest View live

“የዘረኝነት ስድብ ሲሰድቡኝ እና “ኤቦላ”ሲሉኝ እራሴን ለመከላከል ያደረኩት ነው”- የብሔራዊ ቡድናችን አጥቂ ራምኬል ሎክ ዶንግ በፖሊስ ከተወሰደ በኋላ

$
0
0

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን እና የመብራት ሀይሉ ተስፋ የተጣለበት አጥቂ ራምኬል ሎክ ዶንግ ትላንት በተለያዮ ድህረገፆች ስሙ ከፍርድ ቤት እና በፖሊስ ተይዞ መቅረቡ ተከትሎ በረካታ አስተያየቶች እየተሰጡ ነው።
ramkelኢትዮ-ኪክ ወደ ዋሊያዎቹ ካምፕ ኢንተርኮንቲኔንታል ሆቴል በመደወል ከጋምቤላ ምርጥ ፍሬ እና የዋሊያዎቹ አጥቂ ራምኬል ጋር ያደረገውን ቆይታ እንድታነቡል ብሎም እውነታውን እንድትገነዘቡ ለማድረግ ሞክረናል።
ኢትዮኪክ:- ለቃለምልልሱ ፍቃደኛ በመሆንህ ራምኬሎ ሎክ በአንባባዎቼ ስም እናመስግናለን።
ራምኬሎ:- ኧረ ምንም ችግር የለውም!
ኢትዮኪክ:- ትላንት ምንድነው የተፈጠረው?
አሁንስ ያለኸው የት ነው?
ራምኬሎ:- ጉዳዮ ትላናንት ሳይሆን ከሳምንታት በፊት የፕሪምየር ሊጉን ጨዋታ ከመከላከያ ጋር ከማድረጋችን ከሶስት ቀን በፊት አካባቢ ኤልፖ ካምፖችን በር ላይ ቆሜ የቤተሰብ ጉዳይ እየተነጋገርኩ ሳለ የማላቃቸው ሶስት ሰዎች የዘረኝነት ስድብ እንዲሁም ‘ኤቦላ’ ብለው ሰደቡኝ ከዛ በኃላ ነው ነገሩ የተከሰተው። አሁን ያለሁት ከብሔራዊ ቡድን ጋር ሆቴል።
ኢትዮኪክ:-ጉደዮ የተፈጠረው ቀን ላይ ነው?
ራምኬሎ:- አይደለም ፤ምሽት ለሶስት እሩብ ጉዳይ አካባቢ ነው።
ኢትዮኪክ:- በዛ ሰአት ካምፕ በሩ ላይ ምን እያረክ ነበር?
ራምኬሎ:-ከአንድ ጓደኛዮ ጋር ሹፌር ነው ፤የቤተሰብ ጉዳይ እያዋራውት ነበር። ታናሽ ወንድሜ ታሞ ስለነበር ይሄ ሹፌር በዛኑ ምሽት ወደ ጋንቤላ ስለሚሄድ ለወንድሜ መታከሚያ ገንዘብ ይዞልኝ እንዲሄድ ኤልፖ በር ላይ ቀጥሬው ከእርሱ ጋር እያወራን ባለበት ሰአት ነው ይሄ ነገር የተከሰተው።
ኢትዮኪክ:- ሰዎቹ ስንት ናቸው? ታውቃቸዋለህ?
ራምኬሎ:- እነሱ ሶስት ናቸው። እንደውም አንዱ ከመሀከላቸው የፀጥታ አስከባሪ ልብስ የለበሰ ነው። ሁለቱ መጀመሪያ ‘ኤቦላ ‘ከዛም ዘረኝነት ስድብ ሲሳደቡ አጠገባቸው ያለውን የፀጥታ አስከባሪ ጓደኛቸው የተማመኑ ይመስላል። ከዛ በኃላ ሁለቱ ከእኔ ጋር ድበድብ ጀመሩ አንዱ ደግሞ አብሮኝ የነበረውን ጓደኛዮን ጋር መደባደብ ጀመረ ፣ እነሱ ሶስት ናቸው እኛ ሁለት። በዛ ላይ የፀጥታ አስከባሪ ፀጥታ ማስከበሩን ትቶ ሲሳደቡ እና ሲደባደቡ እኔም እራሴን ለመከላከል ያደረኩት የመልስ ምት ነው።
ኢትዮኪክ:- ምንድነው የደረሰው ጉዳት?
ራምኬሎ:- በድብድቡ ሰአት አንዱ ጥርሱ ወልቄዋለው መሰለኝ፣ አይኑም ሳያብጥ አይቀርም።ሲጀመር እኔ አልደረስኩባቸውም ፣ ሰውም ላይ የምደርስ አይነት ባህሪ የለኝም። እራሳቸው ተሳድበው ሲያበቁ ለመደባደብ ሲመጡ እራሴን ተከላክያለው።
ኢትዮኪክ:- ከእግር ኳስ ውጭ ራምኬሎ ቦክስ ያዘወትራለህ እንዴ?
ራምኬሎ:- [በፈገግታ] ኧሯ ቦክስ እንኳን አላዘወትርም….
ኢትዮኪክ:- ትላንት ፖሊሶች መጥው ሲወስዱህ ደንግጠህ ነበር?
ራምኬሎ:- No! ምንም የሚያስደነግጥ ነገር አልነበረውም።ጉዳዮን ሰምቼ ነበር፤ ከትላንት በስቲያ ሆቴል መጥተው ከቡድን መሪያችን ጋር ተነጋግረው እኔም እሮብ ፍርድ ቤት ቀጠሮ እንዳለኝ ስለተነከገረኝ አልደነገጥኩም። በዛ ላይ እነዚህ የከሰሱኝ ሰዎች ክለቤ በር ላይ ነው የተከሰተው ፤ እኔን መክሰስ ከፈለጉ የት እንደምጫወት ያውቃሉ። እስከዛሬ ቆይተው ብሄራዊ ቡድን ስመረጥ ጠብቀው መክሰሳቸው ሌላ ተልህኮ እንዳላቸው ያሳያል።
ኢትዮኪክ:- እጅህን በሰንሰለት ታስረህ ነበር እንዴ ወደ ህግ ቦታ ስትሄድ?
ራምኬሎ:- ኧሯ የምን ሰንሰለት ፤ እጄን ኬሴ ውስጥ ነበር [ፈገግታ]
ኢትዮኪክ:- አሁን ክሱ በምን ሁኔታ ላይ?
ራምኬሎ:- ከአልጄሪያ ጨዋታ በኃላ እንደገና የፍርድ ቤት ቀጠሮ አለኝ።
ኢትዮኪክ:- እንዴት ነው ይህ ሁኔታ የፈጠረብህ ስሜት ?
ራምኬሎ:- ኧረ ምንም ነገር አልተሰማኝም፤ እኔ ትኩረቴ ብሔራዊ ቡድኑ ነው። ከእኔ የሚፈለገውን ማደረግ ነው ለብሔራዊ ቡድናችን ማገልገል።
ኢትዮኪክ:- ዛሬ ምሽት ወደ አልጄሪያ ትጓዛላችሁ ፤ ራምኬሎ በአልጄሪያ ጨዋታ ምን ያስባል?
ራምኬሎ:- እኔ እንግድህ ብሔራዊ ቡድኑ ከተጠራው ጀምሮ ሀሳቤ አንድ ነው፤ በተቻለኝ አቅም ብሔራዊ ቡድናችን የአልጄሪያ ጨዋታ አሸንፈን መምጣት ነው የማስብው።
ኢትዮኪክ:- ስለነበረን ቆይታ ራምኬሎን ከልብ አድርገን እናመሰግናል።

ምንጭ: ኢትዮኪክ


ቤተክርስቲያን እንዳይፈርስ የተቃወሙት ዜጎች ታፍሰው የት እንደደረሱ አልታወቀም; “ይህ ሁሉ የሆነው የእምነቱን ተከታዮች በመናቅ ነው”

$
0
0

(ነገረ ኢትዮጵያ) ትናንት ህዳር 3/2007 ዓ.ም ከቀኑ 5 ሰዓት ጀምሮ በቦሌ ክፍለ ከተማ የማሪያም ቤተ ክርስቲያን እንዳይፈርስ በመቃወማቸው የታፈኑት ዜጎች የት እንደደረሱ አልታወቀም ሲሉ በወቅቱ ጉዳዩን ሲከታተሉ የነበሩ የአካባቢው ነዋሪዎችና የእምነቱ ተከታዮች ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡
news
በወቅቱ 600 ያህል ዜጎች ተገኝተው ቤተ ክርስቲያኗ እንዳትፈርስ ሲቃወሙ እንደተመለከቱ የገለጹት የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች የቤተ ክርስቲያኗን መፍረስ የተቃወሙትን ጨምሮ ሌሎች በአካባቢው የተገኙ ዜጎችም በፖሊስ መታፈሳቸውን ገልጸዋል፡፡ ነዋሪዎቹ ‹‹ህዝቡ በሰንደቅ አላማ አምላክ አታፍርሱብን እያለ ቢለምንም እነሱ ግን ጥይት ወደላይ በመተኩስ ህዝቡን ከማሸበራቸውም በላይ ያገኙትን እየደበደቡ በ9 የድንጋይ መጫኛ መኪና አስገድደው በመጫን ወዳልታወቀ ቦታ ውስደዋቸዋል፡፡ አድማ በታኝ ፖሊስ ቄስ፣ አዛውንት፣ ህጻንና ሴት ሳይል ያገኘውም አፍሶ ወስዷል፡፡ የኮብል ስቶን ጠራቢዎች ሳይቀሩ በአካባቢው በመገኘታቸው ታፍሰው ታስረዋል፡፡ አሁን የት እንዳሉ አይታወቅም፡፡›› ሲሉ ገልጸዋል፡፡

ቤተ ክርስቲያኗ ከተሰራች ከሁለት አመት በላይ እንደሆነ የገለጹት አንድ የአካባቢው ነዋሪ ‹‹ቤተ ክርስቲያኗ ከተሰራችበት ጊዜ ጀምሮ እንድትፈርስ ጥያቄ እንደቀረበ ተገልጾልን አያውውም፡፡ አሁን ነው ደርሰው ያፈረሱት፡፡ የቤተ ክርስቲያኗን አገልጋዮች ጨምሮ በጣም ብዙ ሰው በዱላ ተደብድቧል፡፡ ይህ ሁሉ የሆነው የእምነቱን ተከታዮች በመናቅ ነው፡፡›› ሲሉ ቅሬታቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
የአካባቢው ነዋሪዎችና አማኞች ከቀኑ 5 ሰዓት ጀምሮ እስከ 9 ሰዓት ቤተ ክርስትያኗ እንዳትፈርስ እንደተቃወሙ፣ አድማ በታኝ ፖሊስ በአካባቢው ያገኘውን ሰው ካፈሰ በኋላ ቤተ ክርስቲያኗን በማፍረስ ቆርቆሮውን በመኪና ጭኖ እንደሄደ የአይን እማኞች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

ልማታዊው ጭፍጨፋ በአፋር ክልል በ ግንቦት 2003 ዓ.ም

$
0
0

አኩ ኢብን አፋር

ምን ጊዜውም በአፋር ህዝብ ዘንድ የማይረሳ ቀን ነው!!
የተፈጸመው በአፋር ክልል በዱብቲ ወረዳ ነው።

police afar
በ2003 ዓ.ም አንድ አሊ ኡመር የተባለ የ10ኛ ክፊል ተማሪ የሆነው ወጣት ሌሊት በሱኳር ፋብሪካ ዘበኛ ሁኖ ሰለሚስራ ጧት ደግሞ የጦር መሰራውን እቤት አስቀምጦ ወደ ትምህርት ቤቱ የሄዳል።
እንደተለመደው ተማሪ አሊ ኡመር ከአንድ ጓደኛው ጋር የጦር መሳሪያውን ይዞ ከተኛበት የስራ ቦታ ወደ ቤቱ በመሄድ ላይ ሳለ ሁለት የፈደራል ፖሊሶች በመንገድ ላይ ያገኙዋቸዋል። መሳሪያውን አስረክብ አሉት!

ልጁ ደግሞ ማንነቱን በሚገባ ካስረዳቸው በኃላ መሳሪያውን ህጋዊ መሆኑንና እሱ በሱኳር ፋብሪካ ዘበኛ እንደሆነ ነገራቸው።

አሁንም መሳሪያውን አስረክብ አሉት እሱም እኔም ህጋዊ ዘበኛ ነኝ መሳሪዬም ህጋዊ ነው እንጂ አላሰረከብም አላቸው።

ከዛ ከፖሊሶቹ አንደኛው ለምን ብዙ ትከራከረዋለህ በማለት ጭንቅላቱን መቶ ገደለው አብሮት የነበረው ልጅም ወሰዱት እየደበደቡት ከዋሉ በኃላ ማታ ለቀቁት።
ይሁን እንጅ ችግሩ ተባብሶ ቀጠለ። የማቹ ቤተሰቦች ፖሊሱን ለህግ እንድቀርብ ደጋግሞው ቢጠይቁም ሰሚ አላገኙም።
ሁለት የማቹ ቤተሰብ የሆኑት ወጣቶች ልጁን ገድሎ ለህግ ያልቀረበ ፖሊሱን ፈለገው ገደሉት እነዚህ ሁለት ወጣቶች በጊዜው በአፋር ክልላዊ ፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን ወንጃለቻው ተጣርቶ ለፊርድ ቤት መቅረብ የነበረባቸው ቢሆንም በአቶ እስማእል አሊ ሲሮ የስልክ ትዕዛዝ መሰረት በሚሌ ካንፖ ለሚገኘው ፈደራል ፖሊስ አሳልፈው ሰጡዋቸው ፈዳራል ፖሊስም እነዚህ ወጣቶች ልክ ሚሌ እንደወሰዷቸው ገደሉዋቸው።
ይህን ተከትሎ የማቹ ጎሳ መሪን ጨምሮ ቤተሰቦቹ ሁሉም ታሰሩ።
ያለ ፊርድ ለ3 አመታት በሚሌ በፈደራል ፖሊሶች ከተሰቃዩ በኃላ ባለፉት ሦስት ወራት ውስጥ ተለቀዋል ከነዚህ ውስጥ በመጀመሪያ በፖሊስ የተገደለው አሊ ኡመር ወንድም አለ።

እነርሱም
1 ናስሪ አሊ ሀማድ
2 ሓቴ ዑመር ( የማቹ ወንድም )
3 ዳውድ ዑማር
4 ካዲር አስከር
5 አሊ ሓማድ ስሆኑ ከ3 አመታት በላይ በደብደባ፣ሙቀት፣ በረሃብ አንዲሁም በውኃ ጥም እያሰቃዩዋቸው እንደነበሩ ለምንጮችን ተናገሯል።
አሁንም ከዚህ ጉዳይ ጋር በተያያዘ እስር ላይ የሚገኙ እንዳሉ ተጠቀመዋል።
1 ዑመር የተባለ ለጊዜው የአባቱ ስም አልታወቀም
2 አሊ ሩዔ
3 መሐመድ ማያባሄ እነዚህ ግለሰቦች እስካሁን በግፍ ታስረው በመሰቃየት ላይ መሆናቸው ተገልፇል።
ባለፈው ሳምንት በሰመራ ከተማ የፅጥታ ጉዳይን በተመለከተ ስብሰባ እንደነበረና አብዴፓዎች ስለዚህ ጉዳይ ከምረጫ በፊት በፍታ ቤሄር እንድጨርሱ ከህወሀት ትዕዛዝ መተላለፉን የሰመራ ምንጮች ለአኩ ኢብን አፋር ዘግቧል።

አቶ ማሙሸት አማረ :- አዲሱ የመኢአድ ፕሬዝዳንት ተስፋና ተግዳሮት

$
0
0

“የቱ ይቀድማል?:-

aeupበዲክራሲያዊ መርህ ላይ የቆመ ሀገር ወይስ ዲሞክራሲን ሊሸከም የሚችል ባህል ላይ የቆመ ማህበረሰብ ?” በሚለዉ ጽሁፌ
የፖለቲካ ፓርቲዎቻችን የዉይይትና የክርክር ባህል አለመዳበርን በማስመልከት የተወሰኑ ፓርቲዎችን እያነሳሁ ወቅሼአቸዉ ነበር:: ፓርቲዎች ዉስጥ በግለሰብ ወይም በቡድን ደረጃ የሀሳብ ክፍፍል ሲነሳ ፓርቲዎች በሀሳብ የመሸናነፍ ባህል እንዳላዳበሩ ምሳሌ አድርጌ ካቀረብኩት ፓርቲ አንዱ የመላዉ ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ነበር:: እንዲህም ስል ፓርቲዉን በሀሳብ ሸንቆጥ አድርጌዉ ነበር:-

[ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]

አለማወቅ እንደልብ ያደርጋል! ማተብ እንቆርጣለን ያሰኛል! (ተክሌ የሻው)

$
0
0

ተክሌ የሻው
አለማወቅ እንደልብ ያናግራል። አላዋቂ ሰዎች ሲገሩ ካፋቸው የሚወጣው ቃል በማኅበረሰቡ ባህል፣ ወግ፣ አኗኗር፣ ሰላምና አጠቃላይ ማኅበራዊ ግንኙነት ውስጥ ሊያስከትል የሚችለውን ጥቅምና ጉዳት አያመዛዝኑም። ከአንደበታቸው የሚወጣው ቃል በትውልድ ላይ ጥሎት ሊያልፍ የሚችለውን መጥፎም ሆነ መልካም አሻራ አይመዝኑም። በመሆኑም ንግግራቸው አንደበታቸው ያቀበላቸውን እንደወረደ ወደ አድማጫቸው ስለሚለቁት የሰዎችን አዕምሮ ያቆስላል፤ የማኅበረሰቡን ባሕልና ወግ ይንዳል። ከሁሉም በላይ አላዋቂነት በፖለቲካ ሥልጣን ሲታጀብ ማን አህሎኝነት ስለሚጨመርበት የሚናገሩት ንግግር ልጓም አልባ ስለሚሆን ንግግራቸው ከጥቅሙ ጉዳቱ በእጅጉ ይበላጣል። ይህም ለአገርና ለትውልድ የነገር፣ የቂምና የጥላቻን ቁርሾ ጥሎ ስለሚያልፍ የሰላምና የአንድነት ፀር ይሆናል። ባጭር አገላለጽ « አላዋቂ ሳሚ ንፍጥ ይለቀልቃል» ዓይነት ነው።

ለዚህ አባባል ሰሞኑን የኢትዮጵያው የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ነኝ የሚለው ዶ/ር ሽፈራው ተክለማርያም የተባለው ማተብን አስመልክቶ የተናገረው ጥሩ ያላዋቂነት ምሳሌ ነው። ሰውየው «ማተብ የክርስትና ሃይማኖት መለያና ምልክት ከሆነ እንቆርጣለን» ሲል፣አፉን ሞልቶ በማን አለብኝነት የተናገረው ፣«ጨዋታ ሲደራ እናቴ ባርያ ናት» ያሰኛል እንደሚባለው፣አባባሉ ሊያስከትል የሚችለውን ሁኔታ፣ በማኅበረሰቡ አጠቃላይ ግንኙነት ሊፈጥር የሚችለውን እንደምታ አለማወቅ ወይም ማመዛዘን አለመቻል የወለደው እብሪት እና ድንቁርና ነው።

በአንፃሩ ዐዋቂዎች የሚናገሩትን በማስረጃ ስለሚያስደግፉ የሰሚዎቻቸውን አዕምሮ እና ኅሊና ይስባሉ። አድማጫቸውን ያስደስታሉ፣ ያሳውቃሉ፣ ያዝናናሉ። የዘሩት መብቀል ብቻ ሳይሆን ያፈራል ። ሰዎችን አያስከፉም፤ የሌሎችን መብት አይፃረሩም፤ የማኅበረሰቡን ባሕልና ወግ ያከብራሉ፤ ይጠብቃሉ፤ የነርሱን መልካም ነገር በመጨመር ያለፈውን በመልካም ጎኑ እንዲዳብር ያደርጋሉ። የንንግግራቸው መቋጫ አንድነትና ሰላም ነው።

እንዳው ወደማተብ ቆረጣው ይሳካል፣ አይሳካም፣ ወደሚለው ከመግባታችን በፊት የማተብን ምንነት፣ በኢትዮጵያ ኅብረተሰብ ውስጥ ያለውን ባሕላዊ፣ ሃይማኖታዊ ፋይዳና የያዘውን ዕሴት እንመልከት።

በኢትዮጵያውያን የቆየ መልካም ባሕል ውስጥ ማተብ ልዩ ቦታና ትርጉም ያለው የሐቅና የዕውነት ማስረገጫ፣ የተገቢና የትክክለኛ ነገር መግለጫ ነው። አዋ እገሌ፣ እሜቴ እገሊት ማተበ ጥኑ ናቸው፤ አቶ እገሌ፣ ወ/ሮ እገሊት ባለማተብ ናቸው፤ የሚባሉት አባባሎች አደራ ተቀባዮችን፣አደራ አስቀማጮችንና የታማኝ ሰዎችን ሥብዕና የሚንገልጽበት ኃይለ ቃል ነው። « የተናገሩት ከሚጠፋ የወለዱት ይጥፍ» ብለው ለቃላቸው የሚቆሙትን፣ ሃይማኖት አክባሪ፣ እግዚአብሔን ፈሪ የሆኑ ሰዎችን ከሌሎቹ ለይተን የምንጠራበት ውብ የሐቅ መገለጫ ቃል ነው። ቃሉ የራሳቸውን ለመለገስ እንጂ፣የሌሎችን ቤሳ ቤስቲ የማይፈልጉትን፣ አጠቃላይ ሕይዎታቸውና ኑሮአቸው ሐቅን፤ ዕውነትን መሠረት አድርገው የሚንቀሳቀሱ ሰዎች ማንነት መገላጫ የሆነ ቃል ነው። ይህ ቃል ከቃልነት አልፎ የሐቅ መገለጫ ለመሆን የበቃ ስለሆነ ባህል ነው። የዕውነት መገለጫ ነው።

በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ተከታዮች ዘንድ ማተብ የሥላሴዎች አንድነትና ሦስትነት የሚገለጽበት ረቂቅ ሚስጥር የያዘ ነው። በማቲዎስ ወንጌል ምዕራፍ 28 ከቁጥር 18 እስከ 20 እንዲህ ይላል። « ኢየሱስም ቀረበና እንዲህ ብሎ ተናገራቸው፣ ሥልጣን ሁሉ በሰማይና በምድር ተሰጠኝ። እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው፣ ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፤ እነሆ እኔ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተጋር ነኝ።» ሲል አምላካችንና ፈጣሪያችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለደቀ መዛሙርቱ በሰጠው ትዕዛዝ መሠረት የሚፈጸም ተጠማቂው ከመንፈስ ቅዱስ የመወለዱ ምልክት ነው። አጥማቂው ካህን «በአብ ስም አጠምቅሃለሁ፤ በወልድ ስም አጠምቅሃለሁ፣ በመንፈስ ቅዱስ ስም አጠምቅሃለሁ፤» ካለ በኋላ ለመጠመቁ ምልክት ይሆን ዘንድ ፣ሦስት ጥቁር፣ቀይና ብጫ ቀለም ያላቸውን ክሮችን ባንድነት ገምደው (ሸርበው) በአንገቱ ላይ ያስራሉ። የክሮቹ ሦስትነት የአብ ወልድ እና መንፈስ ቅዱስ ምሳሌ ሲሆን፣ ተገምደው አንድ መሆናቸው የሥላሶችን ሦስትነትና አንድነት ምሳሌ ነው።

የቀለሞቹ ትርጉምም ቀዩ የሰማዕትነት፣ ጥቁሩ መሰቀሉንና መከራ የመቀበሉ፣ብጫው የመንግሥተ ሰማየት ተስፋ ምልክቶች ናቸው። ጥምቀት ወንድ በተወለደ በ40 ቀኑ፣ ሴት በ80 ቀኗ የሚከናወን ፣ተጠማቂዎቹ ከመንፈስ ቅዱስ የመወለዳቸው መረጋገጫ ነው። ሁለት ልደት የምንለውም ሰው በአካል ከወላጆቹ የመወለዱ አንዱ ሲሆን፣ሁለተኛው በመጠመቁ ከመንፈስ ቅዱስ የመወለዱ ሚስጢር ነው።

ማንም የኢትዮጵያን ኦርቶዶክ ተዋሕዶ ሃይማኖት ቀኖና፣ዶግማ፣ ሥርዓትና ታሪክ ጠንቅቆ ለሚያውቅ ሰው የመጀመሪያዋ ብቸኛ የመንግሥትና የሕዝብ ሃይማኖት ሆና በአብርሃና በአጽብሃ ዘመን የታወጀች ሃይማኖት መሆኗን አይዘነጋም። ቤተክርስቲያኒቱ በዚህ ዕድሜ ጠገብ በሆነ ረጅም ታሪኳ ለኢትዮጵያና ለዓለም ሕዝብ እጅግ ብርቅና ድንቅ የሆኑ ዘመን የማይሽራቸው የቋንቋ፣ የሥዕል፣ የሥነ ሕንፃ፣ የመድኃኒት ቅመማ፣ የሥነፍጥረት፣ የቀን አቆጣጠር ቀመርን ያበረከተች ናት። ዛሬ የአገሪቱ የውጭ ምንዛሬ ማፍሪያ ከሆኑት አንዱ የሆነው የቱሪስት መስኅቦች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ውጤቶች ናቸው። የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያኖች፣ ጣና ሐይቅ ውስጥ የሚገኙ አድባራትና ገዳማት፣ መሰቅል (ደመራ)፣ ጥምቀት፣ የያሬድ ዝማሬና መሰሎቹ የቤተክርስቲያኑቱ አንጡራ ሀብቶች ናቸው።

ለግዕዝና ለአማርኛ ቋንቋ ድምፅ የሚወክሉ ፊደሎችን ከነሥርዓታቸው ቀርጻው ቋንቋውን የቃል ብቻ ሳይሆን፣ በጽሑፍም እንዲገለጽ ያደረገች ናት። ሌጦን ፍቀውና አለስልሰው ብራና ሠርተው መጽሐፍን ደጉሰው ታሪክ ለትውልድ እንዲተላለፍ ያደረገች ናት። ከመቃ ብዕር ሠርታ ጽሕፈትን ያስተማረች ናት። ሊቃውንቶቿ፣ሥራሥሩን ምሰው፣ ቅጠላቅጠሉን በጥሰው ቀጥቅጠውና ጨምቀው የሠሩት ቀለም እስካሁን በውበቱም ሆነ በጥራቱ ተወዳዳሪ ያልተገኘለትን ቀለም ያበረከተች ናት። ይህም በመሆኑ የሃይማኖቷ ሥርዓት ከሃይማኖትነት አልፎ የሕዝቡ ባሕልና የኢትዮጵያዊነት መልካም መታወቂ ለመሆን የበቃ ነው።

ቤተክርስቲያኗ እንደዛሬው ሕዝቡ ወንጀለኞችን የሚዳኝበት የወንጀለኛ መቅጫ እና የፍትሐብሔር ሕግ ሳይኖር፣ ፍትሐ-ነገሥትን ከዓለማዊና ከመንፈሣዊ ሕይዎት ጋር አጣጥማ ሕዝቡ ፍትሕን እንዲያገኝ የሕግን ሥርዓት በተጨባጭ ያሳየችና ያስተማረች ናት።

በሌላ በኩል የኦርቶዶክስ ሃይማኖት «አትግደል፣ አታመንዝር፤ አትስረቅ፣ አትዋሽ፣ በውሸት አትመስክር ፣ወዘተ» የሚለውን አምላካዊ ቃል አጥብቃ ስለምትከተል አማኟ ሰብአዊነትን፣ ሕጋዊነትን፣ ሰው አክባሪነትን፣ ሐቀኝነትን፣ ባህሉ እንዲሆን( ይህ ዘመናዊነት የተባለው አመለካከት ገብቶ ክሕደትና ቅጥፈት በአገሪቱ ሕዝብ ሥነልቦና ውስጥ ሁነኛ ቦታ እስኪይዝ ) ከፍተኛ ሚና የተጫዎተች ናት። ሕዝቡ መልካሙንና መጥፎውን፣ ደጉንና ክፉውን፣ ዓለማዊውንና መንፈሣዊውን ለይቶ እንዲያውቅ ያስተማረች ወንጌልን የሰበከችና ያስፋፋች በመሆኗ የአገርና የሕዝብ ባለውለታ ናት። ይህም ብቻ አይደለም፤ አገርን የሚወር፣ ሃይማኖትን የሚያስክድ፣ ነፃነትን የሚገፍ፣ ወራሪ ኃይል ሲነሣ፣ ሕዝቡን አስተባብራ በወራሪዎች ላይ ክንዱን በማንሳት ነፃነቱን እንዲጠብቅ፣ ሃይማኖቱን እንዲያጠና፣ የአገሩን አንድነት እንዲያስከብር የግንባር ቀደምትነት ሚና ስትጫዎት የኖረች ናት፤ ፍትሕ ሲጓደል፣ድሐ ሲበደል ነገሥታቱን የምትገስጽ፣ እንዲያም ሲል እንደዛሬው ሳይሆን፣ሕዝቡን አስተባብራ በክፉዎችና ባረመኔዎች ላይ የምታስነሳ የፍትሕ ተቋም ናት።

ይህን ሁሉ አጣምረን ስናይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክ ተዋህዶ ሃይማኖት ከእምነት አልፎ ባሕልና የመልካም ሥርዓት መሠረት ለመሆን የበቃ ነው። የሃይማኖቱ ሥርዓት እንግዳ መቀበልና ማክበርን፣ ባይተዋርን መርዳትና መንከባከብን፣ ለተራቡ መመገብን፣ ለታረዙ ማልበስን ለተጠሙ ማጠጣትን፣ ለታሰሩ ማስፈታትን የጽድቅና የመልካም ሥራ አርኣያ አድርጎ ስለሚወስድ የተለያዩ ሃይማኖቶች ወደ አገሪቱ ሲገቡ የተቃውሞ ድምፅ አልተሰማም። ለዚህም ነው የነበዩ መሐመድ ቤተሰቦች በቁራይሾች ሲሳደዱ፣ ነቢዩ «ወደ ኢትዮጵያ ሂዱ፣ከዚያ መልካም የክርስቲያን መንግሥት አለ» ብለው የላኩዋቸውና ከጥፋት ለመዳን የበቁት። ለዚህም ነቢዩ መሐመድ ባለማተብ (ሀቀኛ) ስለነበሩ፣ውለታን አዋቂ በመሆናቸው ማነኛውም የእስልምና ተከታይ ኢትዮጵያን እንዳይነካ ነቢያዊ ቃል የሰጡት። እስልምናም ሆነ ሌሎች ሃይማኖቶች በአገሪቱ ውስጥ በእንግድነት ሲገቡ ፣የአገሪቱና የሕዝቡ ሃይማኖት የሆነው የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት በማናቸውም ሃይማኖት ላይ ጥላቻ ሳያሳድር ጎን ለጎን መኖር የተቻለው፤ሃይማኖቱ እንግዳ ተቀባይ፣ የተቸገረ ረጅ፣ ላጣ መጽዋች ከመሆኑ የመነጨ ነው። ዕውነተኛው ታሪክ ይህ መሆኑ በግልጽ እየታየና እየታወቀ፣ በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት ተጽዕኖ ደርሶብናል፣ በአክራሪ ኦርቶዶክሶች ተበድለናል የሚሉ ወገኖች ፣ዛሬ ከሃይማኖት አልፎ የሕዝቡና የኢትዮጵያዊነት መታወቂያ፣ የሐቅ መግለጫ የሆነውን ማተብ እንቆርጣለን ሲሉ መደመጣቸው በማተቡና በሕዝቡ ባሕል፣ በማተቡና በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት መካከል ያለውን ቁርኝትና አንድነት በቅጡ ካለማወቅ ወይም «ሊበሏት ያሰቧትን አሞራ ጅግራናት ይሏታል» እንዲሉ፣ በዚህ አመካኝተው ይህኑ ከኦርቶዶክስ ሃይማኖት ጋር ቁርኝት አለው የሚባለውን የዐማራ ነገድ ነጥሎ ለመምታት የተሸረበ ታላቅ ሤራ መኖሩን የሚጠቁም እንደሆነ መገንዘብ አይገድም።

ሕዝቡ፣ በተለይም የኦርቶዶክስ ሃማኖት አማኙ፣ ማወቅ ያለበት፣ ባንዲራ ያንዲት አገር መለያ፣ መታወቂ እንደሆነ ሁሉ፣ ማተብም የኦርቶቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ተከታይ መለያ፣ ከመንፈስ ቅዱስ ስለመወለድ ማረጋገጫ የሆነ ነው። ማተብ ካንገት መበጠስ የሚቻለው ኦርቶዶክሳውያንን በፍፁም ማጥፋት ሲቻል ብቻ ነው። ይህ እንዳይሆን ኦርቶዶክሳውያን ሃይማኖታዊ ሥርዓታቸው በሚያዘው መሠረት ሃይማኖተ ጥኑ፣ ለዕውነት ሟችና ተሟጋች ሆነው መቆም ይጠበቅባቸዋል።

ሌላው መታወቅ ያለበት የክርስትና ሃይማኖት ተከታይ ሰው አከረረ ወይም አክራሪ ነው የሚባለው፣ ይህን ዓለም ትቶ፣ለማያልፈውና ለወዲያኛው ዓለም ቤቱን ለመሥራት በፀሎትና በስግደት ተወስኖ ለመኖር ገዳም ሲገባነው። ሃይማኖቱ አትግደል ስለሚል፣መግደል ታላቅ ሐጢያት በመሆኑ፣ ክርስቲያን በመግደል አክራሪ ሊሆን አይችልም። ክርስቲያን የሆነ በአክራሪ ሃማኖተኛ ስም ሌሎችን መግደል ከጀመረ ያሰው ክርስቲያን ሳይሆን ሰይጣንና ዳቢሎስ የሰፈሩበት ወንጀለኛ እንጂ፤ ክርስቲያን ተብሎ ሊጠራ የማይችል ነው። ምክንያቱም መግደል በሃይማኖቱ የተከለከለ የዳቢሎስ ሥራ በመሆኑ ነው።

አክራሪነትን የምናየው ገድሎ ሃይማኖቱን በግድ ለሚያስፋፋውና ይህን በማድረጉ «በጀነት 73 ልጃገረዶች ይጠብቁሃል» እየተባለ፣ ከጠላቶቻቸው ባላይ ራሳቸውን እየጠሉ የአጥፍቶ መጥፋት ወንጀል የሚፈጽሙት ናቸው። ይህ ዛሬ በምንኖርበት የምሥራቁ ዓለም የተለመደ ክስተት ከመሆን አልፎ ፣ባህልም እየሆነ መጥቷል። ይህ ዓይነቱ ተግባር በኦርቶዶክስ ሃይማኖት ብቻ ሳይሆን፣ በሌሎችም የክርስትና ሃይማኖቶች የተወገዘና የተከለከለ ከመሆን ዘሎ፣ ወደ መንግሥተ ሰማያት በር የማያስገባ የዳቢሎስ ሥራ እንደሆነ በየጊዜው የሚሰበክ ነው።

ዛሬ በኢትዮጵያ ሕዝብ ጫንቃ ላይ ተንፈራጠው የተቀመጡ ዘመነኞች፣ ይህችን የታሪክ፣ የባህል፣የቋንቋ፣ የሥ-ነምግባር ፣ የፍትሕ፣ የአስተዳደር የሥነ-ሥዕል፣ የሥነ-ሕንፃ ጥበብ ባለቤትና አውራሽ የሆነችን ጥንታዊ ሃይማኖት ለማጥፋት የሚያደርጉት ዙሪያ ገብ አፍራሽ ጥረት ሃይማኖቱን ብቻ ሳይሆን፣ መልካም ባሕላችንም ጭምር ለማጥፋት ታጥቀው የተነሱ መሆኑን ስለሚያረጋግጥ፣ ከሁሉ በፊት የኦርቶዶክስ ሃይማኖት አማኙ ሃይማኖቴ ወይም ሞቴ ብሎ እምነቱን ለማስከበር አንድነቱን ማጠንከር ይጠበቅበታል። በሁለተኛ ደረጃ ሃይማኖቱ ከእምነት አልፎ ባህል ስለሆነ፣ የእኛነት መገለጫ ስለሆነ፣ ኢትዮጵያዊው ለማንነቱ መከበርና መጠበቅ በአንድነት እንዲሰለፍ ግድ ይለዋል። በዚህ ሂደት የቤተርስቲያኗ አባቶች የአቡነ ጴጥሮስንና የአቡነ ሚካኤልን አርኣያነት በመከተል ሕዝቡን ከነጣቂ ተኩላዎች መጠበቅ፣ ሃይማኖቷን ሊያጎድፍ የተዘጋጀውን ኃይል ሕዝቡ ተባብሮ እምነቱን እንዲጠብቅ ሳያሰልሱ ማስተማር ይጠበቅባቸዋል።

በሌላ በኩል ማተብ ይበጠስ የሚሉ ሰዎች ሐቅ ይጥፋ፣ ውሸት ይንገሥ፣ መታመን የፋራ ነው፣ አለመታመን ብልጥነት ነው(አራዳነት ነው)፣ ለዕውነት መቆም ኋላቀርነት ነው፣ ከሐሰት ጋር ማበር አዋቂነት ነው እያሉን መሆኑን ልብ ልንል ይገባል። አዎ !በሥልጣን ላይ ያሉት ሰዎች እከሌ ከእከሌ ሳይባል፣መሠረተ ባንዳ የባንዳ ልጆች ስለሆኑ ለነርሱ ሐቅ፣ዕውነት ምናቸውም አይደለም። የአገሪቱን የረጅም ጊዜ ታሪክ በመቶ ዓመት የገደቡት፣ የኢትዮጵያን ሕዝብ አንድነት የካዱት፣ ባንዲራችን ጨርቅ፣ ያሉት ዕውነትን የማያምኑ፣ ሐቅን የማይቀበሉ ከሐዲዎችና ሐሰተኞች ከመሆናቸው የመነጨ ነው። ማተብ ሲበጠስ ሃይማኖት የሚበጠስ ሳይሆን፤ቀድሞ ሊበጥስ የተነሳውን ብቻ ሳይሆን፣ያሰበውን የሚበጥስ ኃይል ከሕዝቡ ጋር ያለ መሆኑን ከጌታቸው ከዳቢሎሱ መለስ ዜናዊ እና ከአባ ጳውሎስ ሕልፈተ ሞት ትምህርት ሊወስዱ በተገባቸው ነበር። ዳሩ «ያደቆነ ሰይጣን ሳያቀስስ አይለቅም» ሆኖ ባቸው፣ የሃይማኖታችንና የእኛነታችን መገለጫ የሆነውን ማተባችን ሊቆርጡ አሰቡ። ሽፈራው በመቶ ሽዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ደም ከተጨማለቁት ሰዎች አንዱ ነው። ይህንም ማተብ የማስቆረጥ ምኞት መቃጣት እንጂ መማታት አይደለም ብለን ልንተረጉመው ፈጽሞ አይገባም። መቃጣት በራሱ ወንጀል ነው። ይህም ከወያኔ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን እስከ ወዲያኛው ለማጥፋት ለተያያዘው የጥፋት ዘመቻ አንዱ አካል መሆን አውቀን ጥፋቱ ዕውን ከመሆኑ በፊት ስለኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት የሚጮኸው ወገን ከወዲሁ መላ ማለት ይጠበቅበታል። የእጅን ለቆ መሟገት ሰማይን መቧጠጥ ነውና ማተባችን ከወዲሁ ጠበቅ ለማድረግ እንዘጋጅ!

ETHREp

 

ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ የ20 ሺህ ብር ዋስትና ገንዘብ ባለማስያዙ በእስር ላይ ነው

$
0
0

ኀዳር (አራት) ቀን ፳፻፯ / ኢሳት ዜና :- የፌዴራሉ ዐቃቤ ሕግ የዕንቁ መፅሔት አዘጋጅ በነበረው ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ ላይ የተሳሳተ መረጃን በመስጠት፣ ማነሳሳትና ግዙፍ በሆነ ማሰናዳት ወንጀል የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 2ኛ ወንጀል አራዳ ምድብ ችሎት ህዳር 2 ቀን 2007 ዓ.ም ክስ

ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ

ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ

የመሠረተበት ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ የተጠየቀውን የ20ሺህ ብር ዋስትና ማቅረብ ባለመቻሉ በቂሊንጦ በእስር ላይ መሆኑ ታውቆአል፡፡ የጋዜጠኛውን ዋስትና በመዋጮ ለመሸፈን የቅርብ ጉዋደኞቹ የባንክ አካውንት በመክፈት በዛሬው ዕለት ዕርዳታ ማሰባሰብ ጀምረዋል፡፡

የዐቃቤ ሕግ የክስ ዝርዝር እንደሚያስረዳው የቀድሞ የዕንቁ መጽሔት ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ፤ አቶ አምሳሉ ገ/ኪዳን በተባሉ ፀሐፊ “የተገነቡትና በመገንባት ላይ ያሉት ሀውልቶች የነማን እና ለነማንስ ናቸው?”

በሚል ርዕስ ባቀረበው ፅሁፍ መነሻነት፤ ባሳለፍነው ዓመት በጅማ ዩኒቨርስቲ በሚገኙ ተማሪዎች መካከል ግጭት እንዲቀሰቀስ መንስዔ መሆኑንና በግጭቱም 30ሺህ ብር የሚገመት ንብረት መውደሙን ይጠቅሳል።

ጋዜጠና ኤልያስ ማክሰኞ ዕለት ክሱን ለመስማት ፍ/ቤት በተገኘበት ወቅት የ20 ሺ ብር ዋስትና አቅርቦ እንዲለቀቅ ፍ/ቤቱ ብይን የሰጠ ቢሆንም ጋዜጠኛው ለጊዜው የሚያሲይዘው ገንዘብ በማጣቱ ቀጨኔ መድሃኒያለም አካባቢ በሚገኝ አንድ ፖሊስ ጣቢያ እንዲያድር ከተደረገ በኃላ ወደ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት መዛወሩ ታውቆአል፡፡

የጋዜጠኛው የቅርብ ጉዋደኞችና ወዳጆች ጋዜጠኛውን ከእስር ለማስፈታት የባንክ አካውንት በመክፈት ዕርዳታ ማሰባሰብ መጀመራቸውንና የአካውንቱ ቁጥርም

የኢትዮጽያ ንግድ ባንክ የሂሳብ ቁጥር 1000097440655

Swift Code:- CBETETAA መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

ፍ/ቤቱ የጋዜጠኛውን ጉዳይ ለማየት ለታህሳስ 4 ቀን 2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠቱ አይዘነጋም፡፡

Source:: Ethsat

የመለስ “ትሩፋቶች” (ባለቤት አልባ ከተማ) ደራሲ፤ ኤርምያስ ለገሰ ቅኝት፤ መስፍን ማሞ ተሰማ

$
0
0

meles bookዘምረው ዝም አላሉም። ዘምረው አመፁ። አብዮት አፈነዱ፤ የእንስሳት አብዮት። በሚኖሩበት ሀገር – በእነሱ አጠራር፤ የእርሻ ጣቢያ – ለዘመናት በጭቆና ቀንበር ረግጦ ሲገዛቸውና ሲመዘብራቸው በኖረው የሰው ዘር ገዢያቸውና ግብረ አበሮቹ ላይ ሆ! ብለው ተነሱ። ቀንበር በቃን። ባርነት በቃን። ብዝበዛ በቃን። … ነፃነት እንጂ። -–[ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]—

ስልጣኔን የለቀኩት በአንዳንድ ብልጣብልጦች እና የሴራና አድማ አካሄድ በሚችሉ ሰዎች ፓርቲው ስለተጠለፈ ነው

$
0
0

“ስልጣኔን የለቀኩት በአንዳንድ ብልጣብልጦች እና የሴራና አድማ አካሄድ በሚችሉ ሰዎች ፓርቲው ስለተጠለፈ ነው::’ – አቶ አበባው መሓሪ የመኢአድ ፕሬዚዳንት

“ፓርቲው ወደፊት ለመራመድ የማይችልበት ወደፊትም የማይሻሻልበት ደረጃ ላይ ደርሷል::”አቶ አበባው
Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)
Abebawየመኢአድ ፕረዚዳንት የነበሩት አቶ አበባው መሓሪ ስልጣናቸውን ሊለቁ የቻሉት በገጠማቸው አስገዳጅ የድርጅታዊ የውስጥ ጉዳይ መሆኑን ተናግረዋል እንደ አቶ አበባው ደብዳቤ በአብዛኛው የመኢአድ አባላት ከፍተኛ የድምጽ ድጋፍ ከተመረጥኩበት የፕሬዚዳንትነት ቦታ ላይ ድርጅቱ ወደፊት እንዳይራመድ የሚያደርጉ እና ከዚህ በፊት ተሳስረውና ተቆላልፈው በመጡ የውስጥ ችግሮች ለሃገራቸው መስራት አለመቻላቸውን በመጥቀስ ፓርቲው ወደፊት የማይራመድበት አጣብቂኝ ውስጥ መሆኑን ለጠቅላላው ጉባዬ ገልጸዋል::የመኢአድ የውስጥ ችግር በመጪው የኢትዮጵያ ሕዝብ ትግል ላይ ውሃ የቸለሰ ነው ያሉት አቶ አበባው ኢትዮጵያውያን አቤት የሚልላቸው አካል እየጎደለ መሄዱን ጠቁመው በመኢአድ ውስጥ ያለው ችግር ከአቅም በላይ የሆነ ስለሆነ ፍርዱን እና መዝገቡን ለታሪክ በመተው ስልጣናቸውን እንደለቀቁት ከአቅም በላይም እንደሆነ አስረድተዋል::

ከአቅም በላይ ያሉትን ጉዳይ ሲገልጹ … ለየኢትዮጵያውያን ምሁራን ከትግሉ መሸሽ ምክንያቱ የትግሉ መስመር በአንዳንድ ብልጣ ብልጦች እና የሴራ እና የአድማ አካሄድን በሚችሉ ግለሰቦች ስለሚተለፍ መሆኑን መኢአድ ውስጥ ከተከሰተው ችግር እንደተገነዘቡ በደብዳቤያቸው ገልጸዋል::

የአቶ አበባው መሃሪ ፊርማ የሰፈረበትን ሙሉ ደብዳቤውን ከታች ያንብቡት :

10806462_875292445814912_7187866189333442964_n
Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)

– See more at: http://satenaw.com/amharic/?p=2462#sthash.hzTc9P9Y.dpuf


በድሬዳዋ ዩኒቪርሲቲ የሚማሩ የአፋር ተማሪዎችን ባህላዊ ወይም ሃይማኖታዊ ልብስ እንዳይለብሱ ተከለከሉ

$
0
0

አኩ ኢብን አፋር ለዘ-ሐበሻ እንደዘገበው

ተማሪዎቹ እንደሚሉት ከሆነ በመመገቢያ ሬስቶራንትና ላይብረሪን ጨምሮ የባህል ልብስ ማለትም ሽሪጥና የመሳሰሉትን የባህል ልብስ መልበስ አትችሉም እንደሚባሉ በምሬት ገልፀዋል።

afar womenበኢትዮጵያ ህገ መንግስት የባህል፣የሃይማኖትና የብሄር እኩልነት አረጋግጠናል ይላል ግን ወያኔ የሚመራው የኢህአዴግ ፓርቲ በተግባር ላይ ማሳየት አልቻለም ይላሉ።

ከሁሉም በላይ ግን ይላሉ ተማሪዎች ያሳሰበን የሃይማኖት ጉዳይ ነው።

ሶላት ልንሰግድ የሚፈቅድልን ሃይማኖታችን በሚፈቅደው መልክ ሳይሆን ኢህአዴግ በሚፈልገው መልክ ነው።

ሶላት የምንሰግድበት ሰዓት ላይ ያስተምሩናል።

ሶላት እንደ ሃይማኖት አያዩትም አስፈቅደህ ሰግደህ ልትመለስ የማይታሰብ ነው።

ብንሰግድም በጀማኣ ወይም ተሰብስበን አብረን መስገድ አንችልም።

ስለዚህ አባቶቻችን በዲን (ሃይማኖት)ና በባህል መደራደር ሰላልስተማሩን ጉዳዩ በጣም አሳስቦናል ብሏል።
የአፋር ሙስሊም ተማሪዎች ቁጥር መጨመር ያልወደደው የወያኔ መንግስት በዩኒቨርስቲዎች ላይ ከፍተኛ እንግልት እያደረሰባቸው ይገኛል።

“ከዚህ በፊት ከባህርዳር ዩኒቨርስቲ ብዙ የሙስሊም ተማሪዎች መባረራቸው የሚታወስ ሲሆን ከተባረሩት ውስጥ ብዙዎቹ የአፋር ተማሪዎች መሆናቸው ይታወቃል። በተለያዪ ዩኒቨርስቲዎች የአፋር ሙስሊም ተማሪዎችን ለማስፈራራትና ለማሸማቀቅ የተለያዩ ስልቶችን እየተጠቀሙ ይገኛሉ። ሰሞኑን በድሬ ዳዋ ዩኒቨርስቲ ውስጥ የባህልና ሃይማኖታዊ ልብስ እንዳይለብሱ መከልከል መጀመሩ የዚሁ ሴራ አካል ነው ። በአሁኑ ሰዓት በድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ 59 የአፋር ተማሪዎች እየተማሩ ይገኛሉ የሚሉ” የፖለቲካ ታዛቢዎች አሉ::

ፍልፍሉ አሜሪካ እንዳይገባ ተከለከለ

$
0
0

በምነው ሸዋ ኢንተርቴይመንት በኩል ወደ ሰሜን አሜሪካ መጥቶ የነበረውና በተለያዩ ስቴቶች የኮሜዲ ሥራዎችን ቢያቀርብም ብዙም ተቀባይነት ሳያገኝ ወደ ሀገር ቤት የተመለሰው ኮሜዲያን ፍልፍሉ ተመልሶ ወደ አሜሪካ ለመምጣት ፈቃድ ቢጠይቅም በአሜሪካ ኤምባሲ በኩል መከለክሉ ታወቀ::
filfilu
ኮሜዲያኑ ወደ ሃገር ቤት እመለስበታለሁ ብሎ ለኢምባሲው ከተናገረበት ቀን በጣም አሳልፎ ወደ ሃገር ቤት በመመለሱ የተነሳ አሁን በድጋሚ ወደ አሜሪካ የመግቢያ ፈቃድ ሲጠይቅ ተከልክሏል:: ፍልፍሉ በስሜን አሜሪካ በተዘዋወረባቸው ከተሞች በኮሜዲ ዝግጅቶቹ ላይ የተጠበቀው ያህል ሰው ያልተገኘ ሲሆን በርካታ ፕሮሞተሮችም ለኪሳራ መዳረጋቸውን በተለያዩ አጋጣሚዎች ሲገልጹ ይሰማል::

ፍልፍሉ ለመድረክ ስራዎች ሳይሆን ለተቀረጹ ስራዎች ብቻ የሚሆን ኮሜዲያን ነው የሚሉት ለሙያው ቀረብ ያሉ ሰዎች ያልፈጠረበትን ስታንዳፕ ኮሜዲ አቀርባለሁ ብሎ ለትዝብት መውደቁን ይናገራሉ::

ኮሜዲያን ፍልፍሉ የባለስልጣን ልጅ አግብቼ ቤተሰቦቿ ኢትዮጵያ ውስጥ ሊገሉኝ ይፈልጋሉ እያለ በሰሜን አሜሪካ ቆይታው ሲናገር የቆየ ሲሆን ሃገር ቤት እንደገባም በዱሪዬዎች መደብደቡ አይዘነጋም::

ኮሜዲያን ፍልፍሉ ወይም በረከት በቀለ የአሜሪካ መግቢያ ፈቃድ ከተከለከለ በኋላ በየሚዲያው በመቅረብና በሄደበት ቦታ ሁሉ አሜሪካንን በማጥላላት ላይ እንደሚገኝም ጨምሮ የደረሰን መረጃ ያመለክታል::

አዲሱ የመኢአድ አመራር ከሌሎች ፓርቲዎች ጋር የተጀመረው ግንኙነት እንደሚያስቀጥል አስታወቀ

$
0
0

• የፓርቲውን ማህተም ተሰርቄያለሁ ብሏል

aeupዛሬ ህዳር 4/2007 ዓ.ም በፓርቲው ዋና ጽፈት ቤት መግለጫ የሰጠው የመኢአድ አዲሱ አመራር ከመኢአድ ጋር ተመሳሳይ ፕሮግራም ካላቸውና ከሌሎቹም የፖለቲካ ድርጅቶች ጋር ከአሁን ቀደም አብሮ ለመስራት የተጀመረውን እንቅስቃሴ እንደሚያስቀጥል አስታውቋል፡፡

በ2003 ዓ.ም ከታህሳስ 15-17 ድረስ አይቤክ ሆቴል ጠቅላላ ጉባኤ ከተካሄደ በኋላ በፓርቲው አመራሮች መካከል ችግር እንደነበር የገለጸው አዲሱ አመራር ከዛ በኋላ አቶ አበባው መሃሪ ፕሬዝደንት የሆኑበት አካሄድ ትክክል እንዳልነበር፤ለአራት አመት ያህል በሁለቱ ቡድን መካከል የነበረው አለመግባባት በእርቅ እንደተቋጨና አቶ አበባው ኃላፊነታቸውን በፈቃዳቸው እንደለቀቁ የጻፉትን ደብዳቤ ዋቢ አድርጎ ገልጾአል፡፡ በመሆኑም የፓርቲው አባላትና ደጋፊዎች ያለ ምንም ገደብ ወደ መኢአድ ጽ/ቤት መምጣት ይችላሉ ሲል ጥሪውን አስተላልፏል፡፡

በአንጻሩ አዲሱ አመራር በህገ ወጥ መንገድ ነው ወደ ስልጣን የመጣው በሚል ቅር የተሰኙ የፓርቲው አመራሮችና አባላት ዛሬ ከሰዓት መግለጫ እንደሚሰጡ ተሰምቷል፡፡ ጉዳዩን ለማጣራት አቶ አበባው መሃሪ ጋር በተደጋጋሚ ብንደውልም የእጅ ስልካቸውን ሊያነሱ ባለመቻላቸው ሀሳባቸውን ማጠቃለል አልቻልንም፡፡

በሌላ በኩል አዲስ አመራር ማህተሙ አዲሱ አመራር ከመምጣቱ በፊት ፓርቲው ውስጥ በነበሩትና በአዲሱ አመራር ጋር ባልተስማሙ አካላት እንደተሰረቀ አስታውቋል፡፡ ‹‹ማህተሙ ከዚህ ቤት በነበሩ ሰዎች ተሰርቋል፡፡ ይህን ጉዳይ በወቅቱ ለፖሊስ አመልክተናል፡፡ በፓርቲው ማህተም እኛ የማናምንበትና ህገ ወጥ ነገር ቢሰራበት ተጠያቂ የሚሆኑት እነሱ ናቸው፡፡›› ሲሉ አዲሱ የፓርቲው ፕሬዝደንት አቶ ማሙሸት አማረ ገልጸዋል፡፡

ብርቱካን በሊባኖስ ተረፈች ፣ አልማዝ በኦማን የአካል ጉዳተኛ ሆና ቀረች ! የተረፈችው የእህት ብርቱካን ጉዳይ …(ነቢዩ ሲራክ)

$
0
0

birtukan

የማለዳ ወግ …
ብርቱካን በሊባኖስ ተረፈች ፣
አልማዝ በኦማን የአካል ጉዳተኛ ሆና ቀረች !

የተረፈችው የእህት ብርቱካን ጉዳይ …

በሃገረ ሊባኖሰ ቤሩት  ከ4ኛ ፎቅ ወድቃ የተረፈችው እህት ብርቱካን  ጤንነት የተስተካከለና ከድካም ህመሟ ሙሉ በሙሉ እያገገመች መሆኑን መረጃዎች ማምሻውን ደርሰውኛል ። የቆንስል ሃላፊዎች አልማዝን ሲያነጋግሯት በሊባኖስ ቆይታ ስራ መስራት እንጅ ወደ ሀገር ቤት መመለስ እንደማትፈልግ እንደገለጸችላቸው አምባሳደር ሐሊማ ሙሃመድ አጫውተውኛል። በቀጣይ ቀናትም ህክምና እየወሰደች ያለችበትን መካስድ ሆስፒታልን ለቃ እንደምትወጣ ፣ በቤሩት የቆንስል መጠለያ ሆና ህክምናና ጉዳይዋን እንደምትከታተል ተረድቻለሁ !

ተስፋ የቆረጡት ኢትዮጵያውያን አስተያየት …

    በብርቱካን ጉዳይ ዙሪያ ያነጋገርኳቸው ብዙ ነዋሪዎች የቆንስል ተዋካዮች ላይ እምነት እንደሌላቸው ይገልጻሉ ። እንደ አማራጭም የብርቱካንን ጉዳይ በጠበቃ አስይዘው ለመከራከር የሚቻልበትን ንገድ ለማፈላለግ ስራ መሰራት አለበት ሲሉ  ” የቆንስል ሃላፊዎችን ዲስኩር ማመን ትቶ የተለመደው የነዋሪውን ትብብር ማስተባበር ያሻል ” ይላሉ።  ለምን በመንግስት ተወካዮቻችን እምነት አጣችሁ?  ማለቴ አልቀረም ፣ ምላሻቸው ዘርዘር ያለ መረጃና ማስረጃ ያለው እውነት ይመስላል። አንድ ያሉኝን ብቻ ላንሳው  … በሃገራ ባንዴራ ስር ፣ በቆንስሏ በር በጥጋበኛ “ጀብራሬ” አረብ  እየተጎተተች ስትደበደብ የቆንስል ሀላፊዎች ምንም አለማድረጋቸው ፣  ከዚያም  ሃኪም ቤት በገባች በቀናት ልዩነት ” ራሷን በራሷ ገደለች !” መርዶ ነጋሪና ሬሳ ተቀባይና ላኪ ከመሆን ያለፈ ስራ የመብት ማስጠበቅ ስራ በቆንስል መስሪያ ቤቱ አለመሰራቱን ያጣቅሳሉ።  ከዚሁ ጋር በተዛማጅ ከአንድ ወር በፊት እዚያው ሊባኖስ “የአሰሪዋን ህጻን ልጅ አፍና ገድላለች! ” በሚል በፍርድ ውሳኔ ያልተሰጠው ጉዳይ በመገናኛ ብዙሃን ቀርቦ ነበር። በቀረበው መረጃ ስማችን ጎደፈ ። ዳሩ ግን የቀረበው መረጃ ኢትዮጵያዊቷ ወንጀለኛ አለመሆኗ ፍንጭ ሰጠ ፣ የራሳቸው ዜጎች ከሳሽ ባቀረበው መረጃና ማስረጃ ተመርኩዘው የተገላቢጦሹን አሳዩት ። ይህ ሁሉ ሲሆን የመንግስት ተወካዮቻችን ከሳሽን ወደ ተከሳሽነት የሚያሸጋግረውን መረጃ እንኳ ይዘው ታሳሪዋ ኢትዮጵያዊት እህት በዋስ መብቷ  ተጠብቆ በውጭ ሆና  እንድትከራከር አለማድረጋቸው በቆንስሉ የብርቱካን ክትትል ላይ የረባ ውጤት የማምጣት አቅም እንደሌላቸው ማሳያ ነው በማለት የሰላ ሂስና ወቀሳ ያቀርባሉ ።

የተስፈኞቹ ኢትዮጵያውያን አስተያየት …

    ” በቤሩት የቆንስል መ/ቤት ከበፊቱ የተሻለ ለውጥ ይታያል! ”  ያሉኝ ወገኖች ፣ ለውጥ ለመምጣቱና ለመታየቱ የሚያቀርቧቸው ጥቃቅን የቆንስል ግልጋሎት አሰጣጥ መረጃዎች ናቸው ።  ያም ሆኖ የመስራት አቅሙ የላቸውም ያሉኝ  የሚያነሱትን ” …የከዚህ በፊቱን የአለም ደቻሳና ሌላው ሌላው አሳዛኝ የመብት ጥበቃ ጉድለት “ያለፈው አለፈ ፣ ይሁን !”  ቢባል አሁን ድረስ እንዳልተሻሻሉ ብዙ ማሳያ አለ። ከወር በፊት  በነፍስ ግድያ ወንጀል ያለ ተጨባጭ መረጃ የታሰረችውን እህት ቆንስሉ አያማክሯትም ። ለዋስ መብቷን አላስጠበቁላትም።  ” በማለት “የቀረበውን የሰላ ሂስ ” ለውጥ አለ! ” ባዮች በተጨበጠ መከራከሪያ መላሽ ለመስጠት አልተቻላቸውም ።  ብቻ የቀረበውን ወቀሳ ሳያስተባብሉ ” በለውጥ ተስፋ ከማድረግ የተሻለ ነገር የለም! ”  በማለት የቆንሰል መ/ቤቱ የብርቱካንን ጉዳይ በቅርብ ተካታትሎ ውል እንደሚያስይዘው ያላቸውን ተስፋ አጋርተውኛል  !  …ቀጣዩ ምን ሊሆን እንደሚችል መገመት ቢቸግርም ዛሬ የእህት ብርቱካንን በአሰቃቂ ሁኔታ መውደቅና ከከፋ አደጋ መትረፏ በሊባኖስ ቤሩት ካሉት ባለፈ በአለም ዙሪያ ሆነን ጉዳዩን በቅርብ ለተከታተልን ሁሉ እፎይታ ሆኗል  … ተመስገን ነው !  እናም ” ያገባናል ” ባዮች በእህት ብርቱካን ሰናይ ዜና ተደስተን ፊታችን ወደ ሌላዋ ግፉዕ ማዞር ግድ ብሎን  ወደ አልማዝን እንርዳ ” ዘመቻችን ፊታችን መዞራችን እውነት ነው!

የአካል ጉዳተኛዋ የአልማዝ ጉዳይ  …

   ህዳር 2 ቀን 2007 ምሽት በሊባኖስ  የብርቱካንን ከፎቅ መውደቅ አሳዛኝ ዜና ስሰማ በሌላኛው አረብ ሀገር በኦማን የመኪና አደጋ ደርሶባት የአካል ጉዳተኛ በሆነችው በእህት አልማዝ ጉዳይ ተወጥሬ ነበር።  ከተለያዩ አረብ ሃገራት እና በሃገር ቤት በማህበራዊ መገናኛዎች ተገናኝተን የተውጣጣን ወደ ስድስት የምንደርስ ወንድምና እህቶች  ባንድ እየመከርን ነው። አላማችን ከመረጃ ልውውጡ ባለፈ የወገናችን እንባ በተግባር መጥረጉም “ያገባናል !” ብለን ነው። የእህት አልማዝን እርዳታ ለማሳካት ማድረግ ስላለብን ጉዳይ እየመከርን ባለበት ወቅት ከቤሩት የብርቱካን አደጋና  “አትተርፍም!” የተባለ መረጃ ደረሰኝ … ሌላዋን የአረብ ሃገር ኦማን ጉስቁል እህት አልማዝን አሰብኳት …

    እህት አልማዝ የአረብ ሃገሩ ስደት ሲነሳ ከመንግስት ጀምሮ እስከ ግለሰብ የእኛ ቀጥተኛና ቀጥተኛ ያልሆነ ድጋፍ እህቶቻችን አደጋ ላይ ጥሏቸዋል።በህግ ሽፋን ተሰጥቷቸው በሚንቀሳቀሱ ወሮበላ ህግ ይጣሳል ፣  ለህዝብ ቆመናል በሚሉ የመንግስት ተቋማት ህግ ይጣሳል ፣  በመልካም አስተዳደር እጦት ፣ በሙስና  ህይወታችን ከፍቷል ፣ በተለያያየ መንገድ በአረበወ ሃገራት ለገነነው “ዘመናዊ ባርነት ” ድጋፍ እያደረግን እያበረታታን ነው ። ይህን ማለቴ ያለነገር አይደለም ፣ በአረቡ ሃገር በኦማን አካሏ ተሰናክሎ  የእኛን እርዳታ ጠባቂ የሆነችውን እህት አልማዝ አበሳ አስታውሼ ብዙውን አውጥቸ አወረድኩት …

    …አልማዝ አንድ ፍሬ ጉብል ሳለች ካላቻ ጋብቻ   ትዳርን ሳታውቀው መስርታ ልጅ ወልዳ ነበር ፣ ብዙም ሳይቆይ ጉብሏ እናት ሆነች ፣  ኑሮ አልሞላ አልሳካ ብሏት ወደ አረብ ሀገር ወደ ኦማን ተሰደደች … ሙሉ አካሏን ይዛ ለስራ ብላ በራ ከሄደችበት ኦማን ሞስካት ብዙም ሳትቆይ ለመኪና አደጋ ተጋለጠች ፣  ሆስፒታል ገባች ፣ ለወራት በህክምና ስትረዳ ብትቆይም አዕምሮዋ ፣ እግሯና እጇ ብሎም መላ አካሏ የከፋ ጉዳት ደረሰባቸው ፣ አይሆኑ ሆነች: (  ከሃገር ቤት ጀምሮ በአረብ ሀገራት ብርቱ መረብ ያላቸው ደላሎች እህት አልማዝ ሆስፒታል ከገባች በኋላም በጉዳቷ ለመጠቀም መስገብገባቸውን ጠልቆ መረጃ መሰብሰብ አሞኛል ፣ ዛሬ ወደ ክፉዎች ባለ ጊዜ ደላላ ባለጸጎች መሰሪ ምግባር ዳሰሳ አልገባም !  … እህት አልማዝ በተስፋ አቢሲኒያ በጎ አድራጊ ቡድን  አባላት ፣ በተለይም በመስራቹ ብርቱ ወንድም በወዳጀ በመሳይ አክሊሉ ( በኑቢያ ኩሽ ቀዳማዊ  ) እና በወዳጆቹ ብርታት  በአሳር በመከራ ሃገር ቤት ገብታለች ። መቄዶንያ የአረጋውያን ደጋፊ በጎ አድራጊ ቡድን ትብብርም መጠለያም ተሰጥቷታል ።  … እህት አልማዝ እዚህ ላይ ደርሳለች …  ይህም ተመስገን ነው!

   ይህም ሁሉ ሆኖ የአልጋ ቁራኛ የሆነችው አልማዝ ” ከህመም ጉዳቷ የምታገግምበት ተስፋ አለ ” በመባሉ የእርዳታ ስራ ተጀምሯል ፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ በተጀመረው እርዳታ እዚህ ሳውዲ አረቢያ ውስጥ ያለውን እርዳታ ለማስተባበር ሃላፊነት ከወሰድኩ ቀናት ወዲህ ወገኖች አልማዝን ለመርዳት ያሳዪት መነቃቃት እጅግ በጣም አበረታች ሆኖ ቀጥሏል። በኮንትራት ስራ በየአረቡ ቤት የሚሰሩ እህቶቸ የ “ነግ በኔ ” ብለው በሰብአዊነት እያደረጉት ያለው መተባበር ውስጥን ስሜት የሚያረካ ለመሆኑ እማኝ ለመሆን ታድያለሁ  !  የቤት ቆሻሻ ለመጣል መውጫ ቀዳዳውን ፈልገው ያላቸውን ለአልማዝ ለማካፈል ያሳዩት ቅንነት ፍጹም በቃላት ልገለጽ የማይቻለኝን ኩራት፣ በእህቶቼ እንድጎናጸፈው ዘንድ  ምክንያት ሆኖኛል  ! ድምጻዊ  ጆሲ እንደ ሀውስ ያን ሰሞን እርዳታ ለማሰባሰብ ሲሞክር በገጠመውና በሆነው በግኖ ይመስለኛል   ” ለመስጠት መሰጠት ያስፈልጋል! ”  ማለቱ በእኔም ላይ ደርሶ  እውነት ነው ብያለሁ  ! ለእኔ እርዳታ ማድረግ ትርጉሙ ገንዘብ መስጠት ብቻ አይደለም ፣ ቀና ማሰብ ፣ መረጃ መለዋወጥ ፣ ሌላ ተዛማች ተጎጅውን የሚደግፍ ስራ መስራት ፣ የሚረዳን አለመቃወም ፣ ገንዘብ  ከመስጠት ባለፈ ለተጎጅው ወገን ወገናዊ አብሮነት  ፍቅር መግለጫ ነው… ባይ ነኝ  !

    ለማንኛውም ብርቱካን በሊባኖስ ተረፈች ፣ እሰየው ነው!   እህት አልማዝ በኦማን ተሰናክላ እንዳትቀር ወገናዊ ትብብራችን ትሻለችና እናስብበት !  በዚህ የበጎነት መንገድ በመጓዝ በጠና የተጎዱ ወገኖቻችን  በመደገፍ ልንታደጋቸው ካልቻልን ከንፈር መምጠጡ ብቻ እንዳላዋጣን ከእኛ በላይ የሚያውቀው የለም ! እናም የዜጎቹን መብት እንዲያስከብር መንግስትን ስንወተውት የዝሆን ጀሮ ሰጥቶ አልሰማን ቢልም ጩኸት በደላችን እስኪሰማ እየጮህንም ቢሆን በመደጋገፉ የተጎዱትን እየነቀስን በማውጣት የቻልነውን መስራት የዜግነት ውዴታ ግዴታ ነው ባይ ነኝ  !

ሁሉም ለበጎ ነው  !

ነቢዩ ሲራክ
ህዳር 5 ቀን 2007 ዓም

ኢትዮጵያ፡ “መፍትሔው ፍቺ ነው (ጌታቸው ኃይሌ)

$
0
0

Ethiopian Flagስለ ኢትዮጵያ ለማወቅ ፈልጎ መጻሕፍት የሚያገላብጥ ባይተዋር መጀመሪያ የሚታየው የሀገሪቷ ጥንታዊነትና ውበቷ፥ የነዋሪዎቿ መልከ መልካምነትና በብዙ ጎሳዎችና ነገዶች መኖሪያነቷ ሲሆን፥ እነዚህ መልካካም ኢትዮጵያውያን በፖለቲካው ረገድ ዕድለ ቢሶች መሆናቸው ነው። የፖለቲካ ለውጥ ለማምጣት፥ በተለይ በኛ ዘመን፥ ከፍ ያለ እንቅስቃሴ ተካሂዷል፤ ብዙ ሕይወትም አልፏል። ግን እንቅስቃሴውን መርተው መንግሥት ለመገልበጥ የቻሉ ሁሉ፥ “ካስወገድነው አገዛዝ የኛ አገዛዝ ይሻልሃል፤ እነ እገሌን አደኽይተን አነ እገሌን አናበለጽጋለን፤ በረዢም ዘመን ትግል ካስወገድነው እስር-ቤት መሰል አገዛዝ የኛ እስር-ቤት መሰል አገዛዝ ይሻላል” የሚሉ እንጂ ሕዝቡን ከአገዛዝ ነፃ የሚያወጡ አልሆኑም። እንዲያውም ያቋቋሙት አገዛዝ “ከድጡ ወደ ማጡ”” የሚባል አገዛዝ ነው። አይፈረድባቸውም፤ እነሱ የሚያውቁት ምን እንደሚፈልጉ እንጂ ሕዝቡ ምን እንደሚፈልጉ አያውቁም። ከየት አግኝተው ይወቁት? የሚያውቁት አያገባቸው ገብተው መፈትፈትና መጕረስ ነው። “ኢትዮጵያን ከአገዛዝ ነፃ አውጥቶ ዴሞክራሲን አጎናጸፋት” የሚል የታሪክ ክብር የሚቀዳጅ ጀግና ማን ይሆን? ለጊዜው የሚታየኝ እንከን የለሽ ንጹሕ ምርጫ የሚፈቅድ ባለሥልጣን ወይም የምርጫውን ሕግ የሚያስከብር የፖሊስ አዛዥ ነው። --[ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]——-

ፌደራል ፖሊሶች ለሚፈጽሟቸው ግድያዎች ተጠያቂው ማን ነው? (ከዳዊት ሰለሞን)

$
0
0

dawit

ከዳዊት ሰለሞን

ይህ ጥያቄ በቀጥታ በመንግስት ትዕዛዝ የተፈጸሙ ግድያዎችን አይመለከትም፡፡እንደውም በፓርላማ ከቀረበው ረቂቅ አዋጅ አንዱ ‹‹በግዳጅ ላይ ያለ የመንግስት ታጣቂ ለሚፈጽመው ጥፋት ተጠያቂ እንዳይሆን ››የሚሞግት ነው፡፡
ፓርላማው 446 ለ 1 የሚመራ በመሆኑም ገዢው ፓርቲ የፈለገውን አዋጅ የማውጣት መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡በዚህ ገጽ ግን ለማንሳት የወደድኩት ታጣቂዎች ከስራ ገበታቸው ውጪ እየፈጸሟቸው የሚገኙ ግድያዎች ሀላፊ ማን ይሆናል የሚለውን ነው፡፡
ንፋስ ስልክ አካባቢ የመንግስት የሰላም አስከባሪ አባል የነበረ አንድ መቶ አለቃ ጎረቤቶቹን በ35 የክላሽ ጥይት መግደሉና ህጻናቱን ያለ ወላጅ ማስቀረቱ አይዘነጋም፡፡
መቶ አለቃው ከታሰረ በኋላ በልዩ እንክብካቤ ተይዞ ወላጆቻቸውን ባጡ ህጻናት ላይ ይዘት እንደነበርና በኋላም አመለጠ ተባለ፡፡መቶ አለቃው መጨረሻ ላይ ስለመያዙ ተነገረ፡፡

ባህርዳር የተፈጸመውን አሰቃቂ ግድያ አንዘነጋውም፡፡አፍቅሪያታለሁ ያለ ፌደራል ፖሊስ የ18 ሰዎችን ህይወት ቀጥፎ ወንዝ ውስጥ ገብቶ ሞተ የሚል ወሬ ተናፈሰ፡፡

ቂርቆስ መንደር በምትገኝ የሴተኛ አዳሪዎች ሰፈር እንዲሁ የእኔ የሚላትን ሴተኛ አዳሪ ከሌላ ወንድ ጋር ተኝታ በማግኘቱ ፌደራሉ በሁለት ጥይት ደረቷን መትቶ ለህልፈት ዳረጋት ፣ከሴትየዋ ጋር የነበረው ጎልማሳም እግሩን በጥይት ለመቆረጥ በቅቷል፡፡
ይህ ፎቶ ግራፍም በተመሳሳይ መንገድ በፌደራል ፖሊስ ህይወቱን በግፍ ስለ ተነጠቀ ወጣት የሚጮህ ነው፡፡
ጅማን በእንባ፣በድንጋጤና በተቃውሞ የሞላ ክስተት የተስተናገደው በፌደራል ፖሊስ ነው፡፡በምሽት ሰው ቤት ሰብሮ የገባው ፖሊሱ አንዲት አይነ ስውር እናትና ልጃቸውን ቀጥፏል፡፡

ግለሰቡ ስለ መያዙም ተነግሯል፡፡ግን ይህ ነገር በገዳዮቹ መያዝ ብቻ የሚያበቃ መሆን የለበትም፡፡ተጠያቂነቱ ወደ ላይም መውጣት አለበት፡፡መሳሪያ መያዝ የማይገባቸው፣ሰብዓዊነት ምን ማለት እንደሆነ የማይረዱ፣ግደሉ ሲባሉ ከመግደል የማያመነቱ፣መሳሪያ ሲጨብጡ ጭንቅላታቸውን ቃታው ጋር የሚያደርጉ ሰዎችን መለዮ እያለበሱ ስልጣናቸውን ለማራዘም እስከጠቀሟቸው ድረስ ስለሚፈጽሙት ዘግናኝ ድርጊት ደንታ የሌላቸው አካላትም መጠየቅ ግድ ይላቸዋል፡፡

የሟቾቹ ደምም በተኳሾቹ ላይ ብቻ ሳይሆን ነፍጥ ባሸከሟቸው ሀይሎች ላይም ይጮሃል፡፡

የማለዳ ወግ …እኔ ፣ እነሱ እና “ቁንጽል ”የሚሉት መረጃ … (ነቢዩ ሲራክ)

$
0
0

የማለዳ ወግ …
እኔ ፣ እነሱ እና “ቁንጽል ” የሚሉት መረጃ …
* ደረቁ የካልድ እንባ
*  ” ለዚህማ ነፍስህንስ ብትሰጥ ምን አለበት! ” እናቴ …

Nebiyu Sirak ሳውዲ ውስጥ በገፋሁት ሁለት አስርት አመታት ከተለያዩ ወገኖቸ ከውስጥም ከውጭም ስደተኛውን በሚመለከት ተጨባጭ መረጃዎች ይደርሱኛል። የሚያመውን ምስል የያዙ መረጃዎችን ከሙያ አንጻር ብቻ ሳይሆን መረጃውን የሚመለከቱትን ወገኖቸን ስሜት እንዳልጎዳ በሚል በጽሁፍ ከመግለጽ ውጭ አልለጥፋቸውም ። መረጃዎችን ይዠ በቅርቤ ወዳለው የጅዳ ቆንስል ሃላፊዎች ቀርቤ አሳይቻቸውም አውቃለሁ ። በመብት ጥበቃ አልተጋችሁምና ትጉ ስላቸው ምክሬን አይቀበሉትም።  ይባስ ብለው በአይነ ቁራኛ ያዩኛል ፣ ካንድም ሁለት ሶስቴ ከቆንስሉ ግቢ እንዳትደርስ ተብየም አውቃለሁ !  ነጻ ከሚባለው ኮሚኒቲ ድረስ ዘልቀው የአባልነት መታወቂያየ እንዳይታደስ አድርገው ያውቃሉ ! ” ሃገር ቤት አይገባትም ” የሚባለው ተራና የወረደ ማስፈራሪያ የተለመደ ቢሆንም ሃገር ቤት ስገባ ግን ችግር ገጥሞኝ አያውቅም … ቂም ተቋጥሮብኛልና ዛሬ በተፈታ ድራማ የመንግስ ተወካዮች ለሁለት ወራት ከከባድ ወንጀለኞች ማጎሪያ ወህኒ ስወረወር እንደ ዜጋ መብቴን ለማስከበር ቀርቶ ” የት ነው? “ብለው አልጡቁኝም  … ! ልብ በሉ የማወራው ላይ ላዩን ነው!

ያን ሰሞን በጠራራ ጸሃይ ሜዳ ላይ የወደቀች እህት ወደ መጠለያ አስገቧት ለማለት ወደ ተጠባባቂው የጅዳ ቆንስል ጀኔራል አቶ ሸሪፍ ከይሩ ቢሮ ጎራ ብየ መረጃ ሳቀብላቸው አጠር ያለች ውይይት አድርገን ነበር ፣ ብዙ ከተወያየን በኋላ በተደጋጋሚ ስደውልላቸው ለምን ስልኬን እንደማያነሱ ጠይቄያቸው ” ሁሉን የምታውቅ ይመስልሃል ፣ ግን አታውቅም…ቁንጽል መረጃ ይዘህ ፣ ጉዳዩን ፖለቲሳይዝ እንደምታደርግ ስለምናውቅ አንተባበርህም! ” ሲሉ እንቅጩን ነግረውኝ አዝኛለሁ !  በዋናነት ለዜጎች መብት ማከበር የመንግስቱ ከፍተኛ ሃላፊነትን ተሸክመው ከተቀመጡት ሃላፊ መስማቴን ይህች ሃገር የማናት ? አላልኩም ፣ ሃገሩም ህዝቡም የእኔ መሆኑን ጠንቅቄ አውቃለሁ !   ያም ሆኖ አሁን አሁን ሃገሯ የእኔም ጭምር ሆና የምወዳቸውን ልጆቸን ይዠ እንደ ኩሩ ዜጋ እረፍቴን በሃገሬ ለማድረግ አልታደልኩም! ” የምሰማው ጥሩ አይደለም ፣ ከመጣህ እረግምሃለሁ ፣ ለልጆችህ ኑርላቸው !” የምትለኝ መነኩሴ እናቴ ቃልና ምክሯን ለማክበር ግድ ብሎኝ ሃገር ቤት መሄዱን ሳልወድ በግድ ደጋግሜ ሰርዥዋለሁ! ቀዳሚውን ፈጣሪ ቢያውቀውም ለመሰረዝ ውሳኔ ያደረሰኝ የምሰማውን ማድፈራሪያ ግፊቱን ፈርቸ ሳይሆን  የምወዳት እናቴ በመጨረሻዋ የህይዎት ዘመኗ ላሳዝናት ስለማልሻ እንጅ ” የቆስል ስራውን በማደናቀፍ! ” አለያም “ሽብርተኛ ደጋፊ “የሚል ክስ ተለጥፎብኝ  መታሰር መገረፉን የሚፈራ ልብ ኑሮኝ አይደለም  !  በማምንበት የአረብ ሃገር ስደተኛ ዜጎች መብት ይከበር ተዛማጅ መረጃና ሂስ በመሰንዘሬ  የሚመጣውን ለመቀበል ነፍሴ በጸጋ ልትቀበል ከቆረጠች አመታት አልፈዋል …

ይህን ሁሉ ማለቴ ያለ ነገር አይደለም ፣ ምሽት ላይ ሁለት ተቃራኒ ክስተትን አስተናግጃለሁና ነው ። አንዱ የቤሩቷን ብርቱላንና በኦማን የአልማዝን አበሳ ባቀረብኩበትየመረጃ ግብአቴ የተበሳጨ ወንድም ” … ደላላ ፣ ቆንስል ፣ መንግስት ምንቴስ እያልክ ፣ ቁንጽል መረጃ ይዘህ መንግስትን ታጋልጣለህ ፣ ገጽታ ታበላሻለህ ” የሚል ሰብዕናን መሰረት አድርጎ መወያየት የማይሻ ፣ ሲያስረዱት የማይገባው ጨካኝ  አጋጥሞኝ ነው …ሌላው ክስተት ደግሞ የዚህ ተቃራኒ መረጃ ሲሆን ” የሳውዲውን ትተህ ለምን ወደ ኦማንና ሊባኖስ ትሔዳለህ ?” ያለኝን አድራሻው የጠፋብኝን ወንድም አግኝቸው ፣ ከዚህ ቀደም የማወረቀውን መረጃ ልኮልኝ በአሳዛኙ ታሪክ ተረባብሻለሁ ! የሃገሬን ገጽታ እንደማላከፋ ፣  ቁንጽል መረጃ እንደማላውቅ ለዛሬው ሞጋቸና ለቆንስል ሸሪፍ ከይሩ ለትናንት ምሽቱ ሞጋቸ ምላሽ ይሆነኝ ዘንድ ሁለተኛውን ክስተት “ጉዳይ  እንዲህ ነው ” ብየ ልጀምረውና በቀጣይ ቀን ዝርዝር መረጃውን ላሳያችሁ ቆርጫለሁ  ! ጀሮ ያለው ይስማ  !

ወጣቱ ካልድ በከዛን ሆስፒታል …
ነገሩ እንዲህ ነው ፣ በሁለት አመት በፊት ገደማ በቀረበ የመረጃ ቅበላየ ” አንዲት እህትና አንድ ወንድም በየመን ሳውዲ የጠረፍ ከተሞች የመኪና አደጋ ደርሶባቸዋል ፣ ከተቻለ በፍርድ ቤት የኢንሹራንሱን ጉዳይ ተከታትላችሁ ጨርሱ ፣ አለያም ወደ ሃገር የሚገቡበትን መንገድ ፍጠሩ! ” ብየ ከሰላ ሂስ ጋር ጽፊ ነበር ። … ያን ጽሁፍ ካቀረብኩ በኋላ አልፎ አልፎ ስለጉዳዩ መረጃ የሚያቀብለኝ ወዳጀ ተጎጅዎች ወደ ሃገር በመላኩ ረገድ የጅዳ ቆንስል መስሪያ ቤት ምንም የሰራው ስራ አለመኖሩን አጫወተኝ ፣ ምንም ማድረግ ስለማይቻለኝ እኔና እርሱ የሚቻለንን ማድረጋችን ከህሊና ጸጸት ድነናል በሚል ብቻ አስረዳሁት ። ከዚያ በኋላ በግል ወደ ጅዳ ቆንስል ሃላፊዎች ዘንድ በአካል ሳይቀር ቀርቤ ለማስረዳት ሞከሬ  ” ጉዳዩ በፍርድ ቤት ተይዟል።፣ እኛ ምንም ማድረግ አንችልም  ” ማለታቸውን አስታውሳለሁ  ! ይህ ከሆነ ታዲታ ቆይቷል …

የጀዛኑ ወዳጀ አድራሻ በመቀየሩ ስለ ወጣት ካልድ የማገኘው መረጃ ተቋረጠ ። ያም ሆኖ ከስድስት ወር በፊት አንደ ሌላ ወንደም ካልድ እስካሁም በሆስፒታል የመኖሩን ፣ ሴቷ እህት ግን ከወራት በፊት ወደ ሃገር ቤት በአሳር በመከራ መግባቷን የጻፍኩትን የተከታተለ የጀዛን ነዋሪ በህዝብ ስልክ ደውሎ ” ማንነቴን አልነግርህም ፣ ካልድ በስቃይ ላይ ነው ፣ ወይ ሃገር ቤት አልገባ ወይ … ” እንዳለ ንግግሩን ሳይቀጥል የሳግ ድምጽ ተከትሎ ስልኩ ተዘጋ  ! ከቦታው የደረሰኝ የዚህ ሌላ መረጃ ባለቤት ስሜት መጎዳቱ ገብቶኛልና ውስጤን አወከው …ደነገጥኩ  ! ያ ሰው ግን ከዚያ ወዲህ ደውሎልኝ አያውቅም ፣ ከዚያ ጊዜ በኋላ በኩባንያ ስራ ምክንያት በተደጋጋሚ ወደ ጀዛን ብሔድም ከስራ ጫና የተነሳ ወደ  ሆስፒታሉ መሄድ ገደደኝ …እናም በቃ የሚወተውት የሚያስታውሰኝ ወዳጀ ርቋልና ካልድን ረሳሁት …

ዛሬ እኩለ ሌሊት ካልድን በሚመለከት አንድ አስገራሚ መረጃ ደረሰኝ ፣ ያ ወዳጀ በኦማን ለአካል ጉዳት ተዳርጋ ሀገር ቤት ለገባችወደ ለአልማዝ እርዳታ ከተሰራጨ የስልክ ቁጥሬን አግኝቶ መደወሉን አጫወተኝና ወደ ጉዳያችን ማወረጋት ጀመርን … ካልድ ስላለበት ሁኔታ ይነግረኝ ገባ ፣ አላመንኩም ፣ ለክፉ ለደጉ በሚል መረጃ አፍቃሬ መሆኔን ያውቃልና ” ተመልከተው!” ብሎ ካልድ ያለበትን ሁኔታ የሚያሳየውን መረጃ ላከልኝ … ተደመምኩ ፣!  የደረሰኝ መረጃ ለ”ቁንጽል መረጃው ” ውንጀላቸው ምላሽ ከመሆን ባለፈ መንግስት በዜጎቹ መብት ጥበቃ ዙሪያ ስለማይተጉ ሃላፊዎችና ጽንፈኛ ደጋፊዎቹ የተንሸዋረረ መረጃ ትቶ እውነቱን ይረዳ ዘንድ ይህ መረጃ ማሳያ ከሆነው ላቀርበው ወደድኩ ! መንግስት እንደ ቀደመው  ማየት ፣ መስማት ካልቻለ ደግሞ እየሆነ ያለውን እስኪያይ፣ እስኪሰማና  እስኪገባው የሚያገባን እንጮሃለን  !  በቃ ! ይህን ነው የምለው  ! …

ምናልባት እናቴ የወጣት ካልድን አሳዛኝ ታሪክ ከተንቀቀሳቃሽ ምስሉ ጋር እያሳየሁ ባጫውታት አሁን አሁን የሚነገራትን እየሰማች  ” ወደ ሃገር አትምጣ ፣ ጊዜው ለልጆችህ ስትል ኑርላቸው !” ! የምትለኝን አትደግምልኝም!  ሰብእናን እንዳስቀድም ኮትኩታ ያሳደገችኝ የእናት ስስት ምክሯን ትታ   ” ለዚህማ ነፍስህንስ ብትሰጥ ምን አለበት!  ” ብላ ተዘጋጅቶም ከሆነ ወደ ገሃነምም ቢሆን መርቃ እንደምትሸኘኝ ባለ ሙሉ ተስፋ ነኝ  …

አዎ  ! የወጣቱን ታሪክ በግርድፍ ከደረሰኝ የወዳጀ መረጃ ተንተርሸ በቀጣይ የማለዳ ወጌ የምናወራው ይሆናል …
Dry tears of Khalid Nebiyu Sirak: http://youtu.be/H5N4KyeWPNo
እስኪ በቃችሁ ይበለን  !

ነቢዩ ሲራክ
ህዳር 6 ቀን 2007 ዓም


በኢትዮጵያችን በጥርስና በጥፍር የሚደረግ ትግል እንዴት ይቁም? (ግርማ ሠይፉ ማሩ)

$
0
0

ግርማ ሠይፉ ማሩ

girmaseifu32@yahoo.com

girmaseifu.blogspots.com

(ግርማ ሰይፉ)

(ግርማ ሰይፉ)

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ/አንድነት አሳዛኙን የ2002 ምርጫ ውጤት ተከትሎ ፍራሽ አንጥፎ ኢህአዴግን ምርጫ ዘረፈ ከሚል መደበኛ ለቅሶ መውጣት አለብኝ ብሎ ቁርጠኛ ውሳኔ በመወሰን ውስጣችንን መፈተሸ ተገቢ አቅጣጫ ነው ብሎ በማመን በእኛ በኩልስ የነበረው ችግር ምንድነው? የሚለውን ጥያቄ አንስቶ ለመመለስ ከፍተኛ ጥረት አድርጎዋል፡፡ ይህ ነገሮች ወደ ውጭ ከማላከክ በዘለለ ሙሉ ቁጥጥር ባለን በራሳቸን ላይ የውስጥ ፍተሻ ማድረግ ጠቃሚና ተገቢ ነው ከሚል እምነት የመነጨ ነበር፡፡ ይህ ማለት ግን የውጭ ጫናዎች በተለይም የኢህአዴግ አፈና የነበራቸውን ተፅዕኖ አሳንሶ ማየት እና የኢህዴግን አፋኝነትን ዝቅ አድርጎ መመልከት አድርገው የሚውስዱ ሰዎች አይጠፉም፡፡ ዋናው ጉዳይ እና ቅድሚያ መሰጠት ያለበት የውሰጥ ጥንካሬና ድክመትን ማወቁ ነው የሚለው ነበር፡፡ በዚህም መነሻ አንድነት በተቃዋሚ ፓርቲዎች ታሪክ የመጀመሪያ የሆነውን የአምስት ዓመት ሰትራቴጂና ዕቅድ አዘጋጅቶ ለህዝብ ይፋ አድርጓል፡፡ ይህም ሆኖ ግን ሪፖርተርን የመሰሉ ጋዜጦች ተቃዋሚዎችን በጅምላ የሚመሩበት አቅጣጫ የሌላቸው አድርገው መፈረጃቸወን አላቆሙም፡፡ ሌሎችም ቢሆኑ ይህን ተከትለው ከማሰተጋባትና ተቃዋሚዎችን በጅምላ ከመክሰስ ወደኋላ አላሉም፡፡ ለማነኛውም ፍረጃው እንደተጠበቀ ሆኖ አንድነት ያለፉትን አራት ዓመታት ጎዞዉን ባስቀመጠው ሰትራቴጅና አምስት ዓመት ዕቅድ መሰረት አድርጎ ቀጥሏል፡፡ የእቅዱ ማጠቃለያ ዘመንም ከምርጫ ሁለት ሺ ሰባት ምርጫ ጋር የሚገጣጠም ነው፡፡

ይህ የአምስት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ ወደፊት እንደሚካሄድ ታሳቢ ተደርጎ የመጨረሻው ዓመት ሊኖረን የሚገባው ዋነኛ ሰራ ምርጫን መሰረት ያደረገ እንደሚሆን ይታወቃል፡፡ ከዚህ አንፃር ገዢው ፓርቲ በጥርሱም በጥፍሩም ምርጫን ለማሸነፍ እየተንቀሳቀሰ ሲሆን እግረ መንገዱን ደግሞ የተቃዋሚዎችን በተለይም ደግም የአንድነትን ጥርስ ማውለቅና ጥፍር ማዶልደሙን ተያይዞታል፡፡ የጫወታው ህግ በጥርስም በጥፍርም መጫወት የሚፈቅድ ከሆነ ተወዳደሪዎች በተመጣጣኝ ጥርስም ጥፍርም ሊኖራቸው ይገባል፡፡ በቦክስ ጫወታ ደረጃ የሚወጣው በኪሎ ነው፡፡  አጫዋቹም/ዳኛውም ጫወታው ከመጀመሩ በፊት ቅድሚያ ሰጥቶ ማረጋገጥ ያለበት ይህን ጉዳይ ሁሉም ተወዳዳሪዎች ማሟላታቸውን ነው፡፡

 

አንድነት በዚህ ዓይነት የጥርስና የጥፍር ጫወታ ውስጥ ገዢው ፓርቲ ለማድረግ እንደሚፈልገው የተወዳደሪን ጥርስ ማርገፍና ጥፍር ማዶልዶም ተመጣጣኝ ምላሹ የገዢውን ፓርቲ ኢህአዴግ ጥርስ ማርገፍና ጥፍር ማዶልዶም መፍትሔ ይሆናል ብሎ አያምንም፡፡ ለውድድሩ ጥርስም ጥፍርም አስፈላጊ ከሆነ የአንድነት ፓርቲ ጥርስና ጥፍር እንዳይጎዳ መጠበቅ ቅድሚያ ይሰጠው ነው፡፡ ይህ ነው በቁጥጥራችን ስር የሚገኘው እና ዋና ትኩረታችን ሊወስድ የሚገባ እንዲሁም ተገቢ ጊዜ መስጠት አለብን የምንለው፡፡ የገዢውን ፓርቲ ጥርስ ለማርገፍና ጥፍርሩን ለማዶልዶም የምናባክነው ጊዜ የራሳችን በመጠበቅ ብሎም በቁርጠኝነት ባለማስደፈር ቢሆን የበለጠ አዋጭ ነው ብለን እናምናለን፡፡

በገዢው ፓርቲ መንገድ የምንሄድ ከሆነ ግን ወደፊት ለሚደረግ ውድድር በሁለቱም ወገን የሚኖሩ ተወዳደሪዎች በድድ እና በዱልዱም ጥፍር የሚወዳደሩ ይሆናሉ ማለት ነው፡፡ ይህ ደግሞ የጫወታውን ህግ መለወጥ የሚጠይቅ ይሆናል፡፡ በዛሬው የጥርስና ጥፍር ተምሳሌት ዋነኛ ወካይ ባህሪዎች በሁለቱም ጎራ የተሰለፉ ኢትዮጵያዊያን መሆናቸውን ነው፡፡ ኢህአዴግ የተቃዋሚዎችን በተለይ የአንድነትን ጥርስና ጥፍር ላይ አደጋ አደረሰ ማለት በየደረጃው ያሉ የአንድነት አባላትና ደጋፊዎች ላይ የሚወስዳቸው ቅጥ ያጡ ህገወጥ እርምጃዎች ማለታቸን ነው፡፡ በአፀፋው አንድነት ይህን ያድርግ ሲባል ደግሞ በኢህአዴግ አባላትና ደጋፊዎች ላይ ቅጥ ያጡ ሕገ ወጥ እርምጃዎች እንውሰድ ማለት ነው፡፡ የእነዚህ ድምር ውጤት ኢትዮጵያዊያንን በፖለቲካ አቋማቸው ከመጉዳት የሚተናነስ አይደለም፡፡ በዚህ ሁኔታ በተጎዳ ህዝብ ውስጥ ወደፊትም ቢሆን የተሸለ እና የሰለጠነ አማራጭ ይዞ በፖለቲካ መወዳደር ይቻላል የሚል እምነት አይኖርም፡፡ ለዚህም ነው ጉልበታችንን የኢህአዴግ አባላትን ለመጉዳት ወይም ለመበቀል ሳይሆን የአንድነት አባላትና ደጋፊዎችን አቅም በማሳደግ የአይደፈሬነት ሰነልቦና ማዳበር መሆን ይኖርበታል የምንለው፡፡

በአንድነት በኩል የአባላቶቻችንን አቅም እናሳድጋለን ብለን ስንነሳ በዋነኝነት በፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል የሚደረግ ውድድር የሚመነጨው አንዱ ሀገር ወዳድ ሌላው ጠላት ነው ከሚል መንፈስ፣ ወይም በግል በደረሰብን በደል በቁጭትና ለበቀል መሆን እንደሌለበት በማሰተማር ነው፡፡ የፖለቲካ ፓርቲዎች የሚለያዩት በሚመርጡት የርዕዮተ ዓለም፣ ይህን ለመተግበር በሚያወጡት ፖሊሲና የማስፈፀሚያ ስትራቴጂዎች መሆኑን በማስረዳት በማስከተለም እነዚህ ልዩነቶች ሀገርን ሊጎዱ እንደሚችሉ ለህዝብ በማሰየት ህዝብ ለሚሰጠው ብይን ተገዢ ለመሆን ዝግጁ ሲኮን ነው፡፡ ይህን ልዩነታችንን ከጠባብ ቡድናዊ/የፓርቲ ወይም ሌላ ስብስብ ፍላጎት ከመነሳት “ሀገር ወዳድ እና የሀገር ጠላት” በሚል እንድንፈራረጅ ምክንያት ከሆነ የጋራ ሀገር እንዲኖረን እየሰራን ነው ማለት አይቻልም፡፡ ኢትዮጵያ ሀገራችን ለሁሉም ፓርቲዎች የጋራ መኖሪያ ከመሆን በዘለለ የሁሉም ፓርቲዎች አባላት የሚኖሩባት ብቻ ሳትሆን ለልጅ ልጆች በተሻለ ደረጃ ልናስተላልፋት ትልቅ ራዕይ ሰንቀን የምንቀሳቀስ መሆኑ በሁሉም ዘንድ መታወቅ አለበት፡፡ ኢትዮጵያችን እንድትኖር እኛም በእርሷ እንድንኮራ በሁሉም ጎራ የተሰለፍን ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ከፍተኛ ሀገራዊ ኃላፊነት እንዳለብን አውቀን መንቀሳቀስ ይኖርብናል፡፡

በኢህአዴግ በኩል የሚገኙ አባላት ብሎም ከፍተኛ አመራሮች ጭምር የተቃዋሚ ፓርቲዎችን “ኪራይ ሰብሳቢ” ከሚል ቅጥ አንባሩ ከጠፋው ፍረጃ በላይ ግልፅ ሆኖ በወጣ መልኩ በተቃዋሚ ጎራ የተሰለፍን ዜጎች በፍፁም ለሀገር ደንታ የሌለን አድርገው መሳል የተለመደና አስልቺ ፕሮፓጋንዳ ከሆነ ቆይቶዋል፡፡ ይህ በእውነቱ የኢህአዴግ በጥርስም በጥፍርም ለመጫወታ እንዲመቸው የሌላውን ጥርስ ማርገፍና ጥፍር ማዶልዶሚያ ስትራቴጂው ነው፡፡ ይህ መንገድ ግን ብዙ ርቀት የማያስኬድ ብቻ ሳይሆን ለሀገራችን ዘላቂ ሰላም የሚበጅ ነው የሚል እምነት የለንም፡፡

በተቃዋሚ መስመር የተሰለፍን ሰዎች መካከልም ኢህአዴግን መሳደብ እንደ ዋና የትግል ሰልት የተያዘ እስኪመስ ድረስ ጥግ እንደምንሄድ አምኖ መቀበል ስህተታችንን ለማረም ጉልዕ ድርሻ አለው፡፡ አንዳንዴም የሃሳብ ልዩነትን በሰለጠነ መንገድ ከመግለፅ ይልቅ ሰነምግባር በጎደለው ሁኔታ በተለይ የግለሰቦችን ስብዕና የሚነኩ አላስፈላጊ የቃላት ጫወታዎች እንዳሉ እንረዳለን፡፡ “ቅኔው ሲጣፋበት ቀረርቶ ሞላበት” የሚለው አባባል በሁለቱም ጎራ የመከራከሪያ ሃሰብ ድርቀት ምልክት ሊሆን ይቻላል፡፡ ይህንን ከመሰረቱ ለመቅረፍ ከላይ እንደተገለፀው አባላትን በስነምግባር መኮትኮት እና ዋነኛው የፓርቲዎች ልዩነት መሰረት መሆን የሚገባው የፖሊሲና የስትራቴጂ ጉዳዮች ላይ እንዲያተኩሩ ማድረግ ነው፡፡ ይህ ሲሆን በከፍተኛ ሀገራዊ መግባባት ሰሜት መንቀሳቀስ ይቻላል የሚል ፅኑ እምነት ይዳብራል፡፡

 

“አንድነት የአዲሱ ትውልድ ፓርቲ ሆኗል” (አቶ አስራት አብርሃም)

$
0
0
Asrat-Abereha2

አቶ አስራት አብርሃም

አቶ አስራት አብርሃም በእስር ላይ የሚገኘው የአቶ ሃብታሙ አያሌው የስራ ኃላፊነት ተክቶ የአንድነት ፓርቲ ተጠባባቂ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ሆኖ በመስራት ላይ ይገኛል፡፡ ስለ ፓርቲው ወቅታዊ ሁኔታና የወደፊት አቅጣጫ በተመለከተ ከአቶ አስራት ጋር ተወያይተናል፡፡ ፍቱን፡-በዚህ ወቅት መንግሥት በያዘው አቋም እና ተቃዋሚዎች ባላቸው ደካማ አደረጃጀት እና ምላሽ ምክንያት ፓርቲዎቹ እንኳን የህዝቡን መብት ከጥቃት ሊከላከሉ ለራሣቸው መሆን አቅቷቸዋል፣ የፓርቲዎች መኖር ጉዳት እንጂ ጥቅሙ አልገባንም የሚሉ ድምጾች በዝተዋል?

አስራት፡-ባለው ነባራዊ ሁኔታ ነው የሚወስነው ፣ በእርግጥ እዚህ አገር ችግር አለ:: ተቃዋሚዎች በውጪያዊ ተጽዕኖና በውስጣዊ ችግር እንደተፈለገው ተጠናክረው ሊወጡ አልቻሉም:: እየተከፋፈሉ፣ እየፈረሱ፣ እየተገነቡ ነው ያሉት:: በዚህ ምክንያት የአቅመቢስ ሆነዋል:: ይህ ሂደት መቀየር አለበት ብለን ነው የምናስበው:: ከዚህ ጋር ተያይዞ በአንድነት ውስጥ ፖለቲካውን በተሻለ አቅምና ራዕይ መምራት ያስፈልጋል፣ አዲስ አመራር መምጣት አለበት የሚል አቋም አምጥተዋል:: ያንን የለውጥ ፍላጐት ተከትሎ ፕሬዝዳንቱ ስልጣናቸውን ለቀው ለውጡ መጥቷል:: በዚህም ምክንያት ፓርቲውን ለሚያጠናክር አንዳንድ ሥራዎች እየሠራን ነው:: ፓርቲው የህዝብ ፓርቲ የሚሆንበትን መንገድ እየፈለግን ነው:

:በእርግጥም ፓርቲዎች ካልተጠናከሩ በስተቀር ብቅ የሚሉትን የፖለቲካ አመራሮች ለእስር እየዳረጉ፣ ፓርቲ እየተጐዳ፣ የህዝብ ሞራል እየተዳከመ የሚሄድበት ሁኔታ ሊቀጥል ይችላል::

[ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]

አማራ፣ ኦሮሞ፣ ስብአዊ መብቶችና ድርጅቶቻቸው፣ ተጠንቀቅ አማራ! ከቦጋለ ካሳዬ

$
0
0

አማራ፣ ኦሮሞ፣ ስብአዊ መብቶችና ድርጅቶቻቸው

amaraየደላቸው… የሰው ልጅ ይቅር፤ ማንኛውም ህመም ሊሰማው የሚችል ፍጡር አይጠቃ! አይገደል! ብለው እሪ! እሪ! ይላሉ። ያነባሉ። እንቅልፍ አይወስዳቸውም። የሌሎች ስቃዮች እነርሱንም ያስቃያቸዋል።
አንዴ ተማሪ እያለን የደብረ-ብርሃንን የብርድ ልብስ ፋብሪካ ልንጎበኝ ሄድን። አስተማሪያችን ፕሮፌሰር ፓንዲታ የሚባል ህንድ ነበር። ለምሳችን ስጋ ያለበት ሳንዱውች ተዘጋጅቶአል። የደብረብርሃን ብርድ ለጠኔ ዳርጎን ነበርና ሰፍ ብለን ሳንዱቻችንን መግመጥ ጀመርን። አስተማሪያችን ግን ከንፈሩ ደርቆ አይን አይናችንን ያየናል። ለመብላት ፈልጎአል። “ለምን አትበላም?” ብለን ብንጠይቀው፤ “ስጋ አልበላም። እምነቴ ማንኛውንም ፍጡር አትግደል ይላል።” ብሎን እርፍ!
በሆላንድ የእንሳስት መብት ተሙዋጋች የፖለቲካ ፓርቲ አለ። አሁን ዳች ፓርላማ ውስጥ ሁለት መቀመጫ አለው። ፓርቲው መሬት ማንኛውንም የሰው ልጆች ፍላጎቶች ለማሙዋላት ትችላለች። ይሁን እንጂ የሰዎች ስግብግብነትን ለማሙዋላት አትችልም ብሎ ያምናል። እንደ ፓርቲው ከሆነ ለምሳሌ የእንስሳትና እንስሳት ተዋጽኦ እንዱስትሪ፤ 30% በተፈጥሮ ይገኙ የነበሩ የእንሥሣትና የእጽዋት ዘሮችን በማጥፋት ተጠያቂ ነው። ከብቶችንም ለማደለብም ሆነ የወተት ጎርፍ ለማምረት መኖ በገፍ ስለሚያስፈልገው፤ በዚህም ሳቢያ መሬት ከድሃ ገበሬዎች ስለሚቀማ፤ የአለም ርሃብ እየተባባሰ የመጣበት አንዱ ዋናው ምክንያት ከእንስሳትና እንስሳ ተዋጾእኦ እንዱስትሪ ተግባር ጋር የተያያዘ መሆኑን ያረጋግጣል። በተጨማሪም የእርድ እንሳሳት ሲታረዱ ህመም እንዳይሰማቸው ይደረግ ይላል። አንዳንድ እንስሳት በተለይ አሳማዎች ለእርድ ሲቀርቡ ያለቅሳሉ! አንጀት ይበላል ነገሩ።
አሜሪካውያት ሴቶች የምጥን ህመም ስለሚፈሩ ማደንዘዣ ይወጋሉ ይባላል። በአውሮፓ ግን ሴቶቹ ማማጡ በተፈጥሮ ያለ ነገር ስለሆነ፤ እናምጣለን! የምን ማደንዘዣ ነው… እቴ! ብለው የምጡን ህመም ጥርሳቸውን ነክሰው ይጋፈጡታል።
የሰው ልጅ የቆየ እምነትም ይሁን ዛሬ በሰለጠነው አለም እንደምናየው እንስሳትም ይሁን ሰዎች እንዳይሰቃዩ የሚደረጉትን ጥረቶች ጨረፍ ካደረግን ወደ ዋናው ጉዳያችን እንግባ።
በኢትዮጵያ መገዳደል አዲስ ነገር አይደለም። በታሪካችን ግዛት በማስፋፋት፣ የተለያዩ ጭቆናዎችን በመቃወም፣ በሃይማኖት ሳቢያ የደረሱ እልቂቶች አሉ። ቀይና ነጭ ሽብር ትልቅ ጠባሳ የጣሉቡን እልቂቶች ናቸው።
አይኖችቻን ይጥፉ! እምቢ አናይም ካላልን፤ በህወሃት አገዛዝ በአማራ ላይ አላባራ ያለው ግድያ ግን ለየት ያለ ነው።
1. በኢትዮጵያ የአማራ(ሸዋ) ገዢ መደብ እየተባለ የሚጠራውን(ክላፋም እንደጻፈው፤ 48% ኦሮሞ ነው፣32% አማራ፣ትግሬዎችና ሌሎች ናቸው) እንደጠላት መፈረጅ የጀመሩት የብሄር-ብሄረሰብ ጥያቄ ያነሱ ሰዎችና ድርጅቶች ናቸው። በወገኖቻችን በኩል የጉዳዩ አነሳስ ለእኩልነት ተብሎ የታሰበና አማራን ለጥቃት ኢላማ ለመዳረግ ሆን ተብሎ የተደረገ አልነበረም ብሎ ማሰብ ይቻላል። በተጨማሪም በአገራችን የመናገር፣ የመጻፉና የመወያየት ነጻነት ስለሌለ እንደዚህ ያለው ፖለቲካ ወደሁዋላ ይዞ የሚመጣውን መዘዝ አስቀድሞ ማየት ዛሬ ላይ ተቀምጦ ያለፈውን እንደመተቸት ቀላል ነገር እንዳልሆነ እንገነዘባለን።
1.2 ይሁን እንጂ ዶ/ር መራር ጉዲናም እንደታዘበው፤ በተለይ ለእኩልነት አማሮች ከማንኛው የበለጠ ትልቅ ዋጋ ቢከፍሉም ዛሬ ግን ተክድዋል። በሁሉም በሚለው ነገር መስማማት ባይቻልም መራራ ህሊና ያለው ሰው ነው። እንደ አፈንዲ ሙተኪ አግላይ፣ ስድና እሥስት አይደለም።
2. እ.አ.አ በ1995 ዴፕሎማሲ በሚል ሄንሬ ኬሲንጀር በጻፉት መጽሃፍ ውስጥ ፤ አሜሪካ የአንደኛው ዓለም ጦርነት እንዳለቀ(1919) ፤ ዳግም በአውሮፓ ጦርነት እንዳይነሳ አውሮፓውያንን አንዱ አገር አንዱን እጠቀልላለሁ በሚል የሚደረግ የሃይል ግንባታ ፍክክር እንዲያቆሙና፤ ከእንግዲህ ብሄሮች የራሳቸውን እድል በራሳቸው መወሰን አለባቸው የሚለውን መርህ እንዲከተሉ ማስጠንቀቁዋን እናነባለን። ይህ የአሜሪካ አለምን በብሄር የማደራጀቱ ፓሊሲ በክሊንተን አስተዳደርም ዮግዝላቪያን በማፍረስ በጉልህ መከሰቱን አይተናል። በኢትዮጵያም ጊዜውን ጠብቆ ይቀር ይሆን?
3. የተቀረው የአፍሪካም ፍዳ ይኼው ነው። ምንም እንኩዋን አህጉሩ (ከኢትዮጵያ በስተቀር) በአውሮፓውያን ተቀራጭቶ የዛሬዎቹ አገሮች ቢፈጠሩም፤ ሰላም እንዲሰፍን በሚል ሽፋን የአፍሪካን ሃብት ለማራቆት በጎሳ ላይ የተመሰረቱ አገሮች እንዲመሰርቱ የሚያቀነቅኑ አሉ። አንዱ አቀንቃኝ የመለስ ዜናዊ አማካሪ የነበረ “ተራማጅ” የሚባል ሶሻል ዴሞክራት ነው። ቻይና ሳይታሰብ መጣና ጫወታውን ለውጠው እንጂ።
4. ወደ ኢትዮጵያ ስንመለስ፤ ጨቁዋኙ አማራ፤ ተጨቁዋኝ ሊሎቹ ተብሎ ህወሃትን፣ ኦነግንና ኦብነግን በሚደግፉ የውጭ ኃይሎች ሆን ተብሎ ድርሰት ተደርሶአል። በጉዳይ ላይ ብዙ መጻህፍት ተጽፈዋል። ብዙ ፒ.ኢች.ዲዎች ተመርቀውበታል። ይህቺን ማስታወሻ ዛሬ ቅዳሜ በምጽፍበት ሰዓት እንኩዋን የኢትዮጵያ ማህበር በሆላንድ ሁለት በዚሁ ድርሰት ዶ/ር የተባሉ ቀንደኛ የአማራ ጠላቶች ጠርቶ ስለ ኢትዮጵያ የወደፊት ፖለቲካ አቅጣጫ እንድንወያይ ጋብዞናል። እኔ ጠላቶቼን ቀደም ብዬ ስላማውቃቸው ከእነርሱ ጋር ስለ አገሬ አቅጣጫ መፍትሄ ለመፈለግ አልሂድም። የውይይት መብታቸውን ግን አከብራለሁ።
5. የውጭ ኃይሎች እነዚህ ብሄረተኛ ድርጅቶችን የሚደግፉበት ምክንያት ምንድን ነው? ህወሃትን የሚደግፉበት ምክንያቶች ግልጽ ናቸው። መሬት አግኝተዋል። ሽብርን ለመዋጋት በሚል ሰበብ ለሞት የሚማገድ የሰው ሃይል በቀላሉ ያገኛሉ። የህወሃት የጎሳ ፖለቲካም የኢትዮጵያን አገራዊ ስሜት ለማደብዘዝ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል። ከመሬቱም፣ከወታደር መማገዱም ሆነ እርስ በእርስ ከማናከሱ ፖለቲካ ህወሃት ተጠቃሚ ነው። ፕሮፌሰር ዓለማየሁ በሚገባ እንዳስቀመጡት፤ ህወሃት በምጽዋት የሚኖር የለማኞች አገዛዝ ነው።
6. ኦብነግን በመደገፍ የሚገኝም ነገር አለ። ጋዝ ወይም ነዳጅ ነው። እ.አ.አ በ2009 በጄኔቫ አንድን የእንግሊዝ ኢምባሲ ሹመኛ ከሰዎች ጋር ሆነን አንገጋግረን ነበር። ኤርትራም ተሹሞ የሰራ ሰውና ስለ አካባቢው እውቀት ያለው ነው። ስለ ስብአዊ መብቶች ጉዳይ በኢትዮጵያ ገለጻ አደረግንለት። አላማችን በየአራት አመቱ አባል አገሮችን ስለ ስብአዊ መብቶች መሻሻልና ችግሮች በሚገመግመው የተባበሩት መንግስታት ጉባኤ ላይ (ዩኒቨርሳል ፕሮዴክ ሪቪው) የኢትዮጵያን የሰብአዊ መብቶች ጥሰት ትኩረት እንዲያገኝ ለማድረግ ነበር። በጉባኤው ላይ አስተያየት ሰጭ አገሮች ከ5 ደቂቃ በላይ አይሰጣቸውም። ታዲያ እንግሊዙ የትኛውን የሰብአዊ ጥሰት አነሳ? በኦጋዴን ብቻ የተከሰተውን። በቃ። ሌላ ጥሰት ለወሬ ነጋሪም አልተሰማ። ቅዱስ ቫቲካን፣ሲዊዘርላንድ፣ሲውዴን፣ አውስትራሊያና ብራዚል በሚገባ በኢትዮጵያ ያለውን ችግር ለጉባኤው አስረድተዋል። የአሜሪካው ግን በጣም የተለየ ነበር። ኦባማ ገና በስልጣን የመጣበት ወቅት ስለነበር ለዴሞክራሲ መስፋፋት ተስፋ አልጨለመም ነበር። የአሜሪካው አምባሳደር የህወሃትን የጎሳ የበላይነት በጉባኤው ላይ ፍርጥ በማድረጉ፤ ሆዳሙ ፍሰሃ ገዳ ውሸት ነው ብሎ ቡራ ከረዩ ያለበት ትያትር ነበር ያየነው። ትእቢተኛው መለስ ዜናዊም ቀብጦ አምባሳደሩን ባለጌ ማለቱን አስታውሳለሁ።
7. ኦነግን በመደገፍና ኦሮሚያን በማስገንጠል ኦሮሞም ሆነ የውጭ ኃይሎች ምንም! ወላ ሃንቲ! የኢኮኖሚ ጥቅም አያገኙም። ባእዳን ዛሬ ካጋበሱት መሬት የበለጠ ኦነግ ኦሮሚያን መስርቶ ቢኮፈስ የበለጠ ጥቅም ሊያገኙ ይችላሉ? አይችሉም። ኦሮሞም እንደ አማራ አብሮ በደሙና በአጥንቱ በገነባት ኢትዮጵያ ሁሉ መብቱ ተከብሮ ነው መኖር የሚፈልገውም፤ የሚሻለውም።
7.1 ከተቀረው የኢትዮጵያ ህዝብ እየለዩ፤ ኦሮሞዎች ትናትም ሆነ ዛሬ ተጨቁኑዋል እየተባለ ጎልቶ በስብአዊ ድርጅቶች ሆነ በአለም አቀፍ ድርጅቶች የሚነገረው፤ የኦሮሞ ተቆርቁዋሪነቱ(ብሄረተኝነቱ) ገኖ ኢትዮጵያዊነቱ ተሙዋጥጦ ይጠፋል ከሚል ምኞት ነው። አቤ ቶኪቻው ይኼን ወዲያው ተገንዝቦ ማለፊያ አስተያየቱን እንዲህ ሲል ስንዝሮአል፤..”ስንቅ ያቀበሉ ኦሮሞ ያልሆኑም ታስረው እየማቀቁ ይገኛሉ።” የኦሮሞ ጥያቄ የሚባለው በተጨማሪም እንዲገን የሚደረገው አማራና ኦሮሞ እንዳይቀራረቡ ለማድረግና የወያኔን የግዛት ዘመን አደጋ እንዳይገጥመው ለመከላከል ነው። አማራና ኦሮሞ ተቀራርበው እንደ አምስቱ የአርበኞች ትግል(ጉራጌዎችም አሉበት) መዋጋት ከጀመሩ ህወሃት በግድ ይጠፋል። ይኼን እየተገነዘቡ፤ ብዙዎቹ የኦነግ ብሄረተኞች በአማራ ጥላቻ ስላበዱ አውቀውም ይሁን ሳያውቁ ለአድነታችን ጠላቶች መሳሪያ ሁነዋል። እነ ተስፋዬ ገ/አብና አንድናቂዎቻቸው አፈንዲ ሙተኪም የሚሰሩት ይኽንኑ ስራ መሆኑን አንብበናል። በጆራችን ስምተናል፡፡
7.2 ኢሳያስም ቢሆን እንዲህ እየባለገ በስልጣን ላይ እንዲቆይ የሚፈለገው፤ ኢትዮጵያን በማፍረሰ ቀመር ውስጥ ሊጠቅም ስለሚችል ነው። ዴምሄት 45 ሺህ የታጠቀ የትግሬ ጦር ነው። አቶ ጌታቸው ረዳ በትግርኛ ቁውንቁዋ ከተገኙ ምንጮች ሰሞኑን እንዳስነበበን፤ ትግርኝ ትግሪኝን ለመሰረት ኢሳያስ ያዋቀረው ጦር ነው። ሴቪ አድና ግን ከመሃከላችን ሆኖ ዴምሂት ወያኔን ለመጣል የሚታገል ጦር ነው ይለናል። የሚገርመው ሴቪ አድና አስብ የትግራይ ነው ሲል ጽፎኣል። ለነገሩ አስብ የአፋር ነው፡፡ የሚቀርበውም ለወሎ ነው። ትግራይ ትግርኝ ግን ግን አማራጩ ፕላን ወይም ፕላን ቢ ነው። ይቅናችሁ።
8. እንደመደምደሚያ፤ የሰው ልጅ የሚያመዛዝን አእምሮ ስላለው፤ እንኩዋን ለራሱ ለሰው ለእንሳስት ነፍስ ሲሳሳ አይተናል። ህወሃት ሰው በነገዱ አማራ ነህ እያለ መገደል የጀመረው በወልቃይት ጸገዴ ነው። እኛ ግን በስፋት የሰማነው መጀመሪያ በአርባጉጉ ነው። በአርባጉጉ አራጆቹ እርጉዝ ሴቶችን በሳንጃ ከመግደላቸው በፊት በጽንሱ ጾታ ፤ አማራ ወንድ? ወይስ ሴት? በማለት ይወራረዱ እንደነበርና ጡት ቆርጠው እስከማስበላት እንደደረሱ ራሳቸው ኦሮሞዎቹ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ጽፈው ከሰጡት ደብዳቤ መረዳት ይቻላል።
8.1 አማራ ተገደለ! ራስህን ተከላከል እያልን የምንጮኸው በዘር ቆጠራ ተለክፈን አይደለም። እጅግ ስብአዊነት ስለሚሰማን እንጂ። እንሆ 23 አመታት ተቆጠሩ፤ ፕሮፌሰር ዓስራት ወልደየስ እንዳሉት ጠላቶቹ አማራ የሚሉትን ፈልገው ሲያጡት አናይም። ስንት አማራ እየጠፋ አምነስቲ ምን አለ? ምንም። የፕሮፈሰር መስፍን አማራ የለም ነገር፤ አማራን ከጥቃት ለመከላከል አላስቻለም።
8.2 ስብአዊ መብቶች ብዙ ናቸው። ዓማራ ተብሎ በተለያዩ መንገዶች ሲጠፋ፤ ጠፋ! ተፍናቀለ! ተገደለ ብለን ስንጮኽ የጎሳን ፖለቲካ ማራመድ ነው የሚሉን ስለሰብአዊነት የጠለቀ ግንዛቤ የሌላቸው ናቸው። ለነገሩ እውቀት እንደ አባት ስም አይወረሰም። ጥናትና ጥረት ያስፈልግዋል። አንዳንዶቹ ከተለያዩ ጎሳዎች በመወለዳቸው አማራ አምሮ ከተነሳ የትኛውን እንመርጣለን ብለውም የሚጨነቁ ቅይጥ-ጎሰኞች አሉ። እነዚህ ሰዎች ስብአዊነትን ከሁሉም በላይ መሆኑን የዘነጉ ናቸው። ለነገሩ በኢትዮጵያ ዳርቻ ካሉ ጎሳዎች በስተቀር ያልተቀላቀለ የለም። ስለዚህ በኢትዮጵያ የጎሳ ፖለቲካ አገርን ለመበዝበዝና ካልሆነም ለመበተን የሚካሄድ ስልታዊ ሃሳብ/አይዶሎጂ እንጂ በትውልድ ሃረግ የሚመዘን ጉዳይ አይደለም። እኛ አማራ ንጽህ ዘር ነው፤ የራሱን መንግስት ያቁም አላልንም። በአማራነቱ የሚደርሰበት ጥቃት በአገዛዙ እቅድ የሚደረግ ስለሆነ ራሱን ከጥፋት ያድን ነው የምንለው። ምንም እንኩዋን በቅርቡ ባሳተመው መጽሃፉ ስለ አማራ እልቂት አንድም ነገር ያልተነፈሰው ብርሃኑ እንክዋን በደረሰበት ትችትና፤ ይኼንኑ ጉዳይ በመገንዘብ ባለፈው መስከረም የኢትዮጵያ አዲስ አመት ምክንያት በማድረግ በአደረገው ንግግር አማራው በተለይ የጥቃት ኢላማ መደረጉን አምኖአል። ከአክሱም የተገኘው ጌታቸው ረዳ

የሰማያዊ ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ታሰሩ

$
0
0

ነገረ ኢትዮጵያ

በተለያዩ የአዲስ አበባ ክፍሎች ለእሁዱ የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ ቅስቀሳ ሲያደርጉ የታሰቱትን የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና አመራሮች ለመጠየቅ ወደ ፖሊስ ጣቢያ የሄዱት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ታሰሩ፡፡

በቅስቀሳ ወቅት የነበሩት የሰማያዊ አባላትና አመራሮች መያዛቸውን ተከትሎ የእሁዱን የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ ለስበስባና ሰላማዊ ሰልፍ ማሳወቂያ ክፍል ያሳወቁበትን ህጋዊ ደብዳቤ በመያዝ የአባላቱና አመራሩ እስራት ህገ ወጥ መሆኑን ለማስረዳትና አባላቱን ለመጠየቅ ወደ አራዳ መምሪያ ፖሊስ ጣቢያ ያቀኑት የሰማያዊ ፓርቲ የፋይንስ ጉዳይ ኃላፊ አቶ ወሮታው ዋሴ እና የአደረጃጀት ጉዳይ ኃላፊው አቶ ብርሃኑ ተ/ያሬድ በፖሊስ ተይዘው ታስረዋል፡፡

1920593_613309012128094_4439816027396922242_n

በቅስቀሳ ላይ የሚገኙት የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና አመራሮች እየታሰሩ ነው

የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር እሁድ ህዳር 7/2007 ዓ.ም ለሚያደርገው የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ ቅስቀሳ ላይ የነበሩ የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና አመራሮች ታሰሩ፡፡

የብሄራዊ ምክር ቤት አባል የሆነው አቶ ዮሴፍ ተሻገር እንዲሁም የአዲስ አበባ ምክር ቤት አባል የሆነው ሲሳይ በዳኔ መገናኛ አካባቢ ቅስቀሳ ላይ በነበሩበት ወቅት ታስረዋል፡፡

በተመሳሳይ የምርጫ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ አባል አቶ ሳምሶን ግዛቸው እንዲሁም የአዲስ አበባ ዞን ምክትል ሰብሳቢና ህዝብ ግንኙነት አቶ ማቲያስ መኩሪያ በአራዳ ክፍለ ከተማ ቅስቀሳ ላይ በነበሩበት ወቅት በፖሊስ ተይዘው አራዳ ፖሊስ መምሪያ ታስረዋል፡፡

በሌሎች የአዲስ አበባ ክፍሎች ቅስቀሳ ላይ የሚገኙ የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና አመራሮች በፖሊስ ወከባ እየደረሰባቸው መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ህዳር 7/2007 ዓ.ም ቤልየር ሜዳ ላይ የሚደረገው የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ ሰማያዊ ፓርቲ የሚያስተብብረው ሲሆን በአንድ ወር የሚደረጉትን ሌሎቹን መርሃ ግብሮች 9ኙ ፓርቲዎች በየተራ እንደሚያሰተብብሩ መስማማታቸው ይታወቃል፡፡

10173740_613277408797921_4625849180036064757_n

ሊቀ ጳጳሱ ከስራና ወደ ውጭ አገር እንዳይወጡ ታገዱ (የዕግዱን ደብዳቤ ይዘናል)

$
0
0

Abune Yacob
የምስራቅ ኣፍሪካ ሃገረ ስብከት ሊቀጳጳስና መቀመጫቸውን በደቡብ ኣፍሪካ ኣድርገው የነበሩት ብጹእ ኣቡነ ያዕቆብ ከሃገር አንዳይወጡና ከስራቸው መታገዳቸውን ለዘሐበሻ የደረሰው መረጃ ኣመለከተ፥፥ የዘሐበሻ ታማኝ ምንጮች ከነ ደብዳበው የላኩት መረጃ የሚከተለው ነው፥፥ ዝርዝሩን ይዘን አንመለሳለን፥፥
aba yakob
aba yakob 3

Viewing all 8745 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>