Quantcast
Channel: ዘ-ሐበሻ – Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 8745 articles
Browse latest View live

የወላድ መካን በጐንቻው!


ሰላም ምንድነው? ታደሰ ብሩ

Sport: መሠረት ደፋር የ5ሺህ ማጣሪያ ያሸነፈችበት ቪድዮ

Art: አማኑኤል ይልማ –ከታዋቂ ድምፃዊያን ጀርባ ያለ ታላቅ የሙዚቃ ሰው

$
0
0

amanuel & Aster
ዘርፈ ብዙ የኪነ ጥበብ ባለሙያ ነው፡፡ የሙዚቃ አቀናባሪ፣ የግጥምና ዜማ ደራሲ፣ የሙዚቃ ፕሮዲውሰር፣ የቪዲዮ ክሊፕ ፕሮዲውሰርና የፊልም ተዋናይ! አማኑኤል ይልማ፡፡
ለጌዲዮን ዳንኤል፣ ኃይልዬ ታደሰ፣ ሸዋንዳኝ ኃይሉ፣ አለማየሁ ሂርጶ፣ አረጋኸኝ ወራሽ፣ ጎሳዬ ተስፋዬ፣ ማዲንጎ አፈወርቅ፣ ብርሃኑ ተዘራ፣ ጸሐይ ዮሐንስ፣ ኤፍሬም ታምሩ፣ ማቲያስ ተፈራ፣ ጥበቡ ወርቅዬ፣ ግርማ ተፈራ፣ አቦነሽ አድነው፣ ፋሲል ደመወዜና ሌሎችም በርካታ ድምፃዊያን በአልበማቸው ውስጥ በግጥም፣ በዜማና በቅንብር ተሳትፎ አለው፡፡ እንዲሁም የተለያዩ ድምፃዊያንን ሙሉ አልበም አቀናብሮ ፕሮዲውስ አድርጓል፡፡ በቅርቡ ‹‹ዜማ አማን›› በሚል ኃይለየሱስን፣ ትዕግስትን፣ ህብስትን፣ ብዙአየሁን፣ ግርማ ተፈራን፣ ገረመውንና ፀጋዘአብን ያካተተ ኮሌክሽን አልበምም በፕሮዲውሰርነት አቅርቧል፡፡ በሚዲያዎች ራሱን ለማስተዋወቅ እንብዛም ግድ የሌለውን አማኑኤል ይልማን አነጋግረነዋል፡፡
ዘ-ሃበሻ፡- በኢትዮጵያ ሚሊኒየም ጊዜ የነበረውን በአል ለማክበር ከ50 በላይ ድምፃዊያን የተለያዩ ሙዚቃዎችን አውጥተው ነበር፡፡ ነገር ግን ከሁሉም ጎልተው የወጡት አንተ ያቀናበርካቸው የቴዲ አፍሮ ‹‹ጊዜ ለኩሉ›› እና የብርሃኑና ማዲንጎ ‹‹አንበሳው አገሳ›› ነበሩ፡፡ ያ እንዴት ሊሆን ቻለ?
አማኑኤል፡- እንዳልከው የ2000 በአልን ለማክበር ህዝቡን ለማንቀሳቀስ ብዙዎች ዘፈኖችን ሰርተዋል፡፡ በዚያ አጋጣሚ አንዱ ሆኜ እንደዜማ ደራሲና እንደ አቀናባሪ ተሳትፌ ነበር፡፡ ዕድለኛ ያደረገኝ እኔ የሰራሁት ዘፈን ህዝቡ የተቀበለው ሆነ፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ የቴዲ አፍሮ ‹‹ጊዜ ለኩሉ›› ወይም ‹‹አበባ አየህ ወይ›› የሚለው ዘፈን ሲሆን፣ ከዛ በመቀጠል ‹‹አንበሳው አገሳ›› የሚለው በብርሃኑ ተዘራና ማዲንጎ አፈወርቅ የተዜመው ነው፡፡ በጊዜው በታዋቂ ድምፃዊያን ጭምር የተሰሩ ብዙ ዘፈኖች ውድድሩ ውስጥ ነበሩ፡፡ ከእነዛ ውስጥ ግን በተለይ ‹‹አበባአየህ ወይ›› በአንድ ጊዜ ሒት ሆኖ ወጥቷል፡፡ በዚህ አጋጣሚ የምነግርህ ያኔ ከቴዲ ጋር ብዙ አብረን ስንጓጓዝ ‹‹ቴዲ አትዘፍንም ወይ?›› እያሉ ይጠይቁት ነበርና በጣም የተጨነቀበት ወቅት ነበር፡፡ ምን ይዤ ልምጣ? ብሎ በተጨናነቀበት ወቅት ሌሎች ስራዎችን ስንሰራ ቆይተን አበባአየህ ወይን ከሌሊቱ ዘጠኝ ሰዓት ነበር የጀመርነው፡፡ ወደ 11፡00 ሰዓት ላይ ጨረስነው፡፡ ከዚያ በኋላ ምንም ግጥም አልጨመረም፡፡ ድጋሚም አልዘፈነውም፡፡ አንዴ ስቱዲዮ ውስጥ የተሰራ ስራ ነው፡፡ ዜማና ግጥሙ የቴዲ አፍሮ ነው፡፡ ቅንብሩ ከእነሚክሲንጉና ማስተሪንጉ የእኔ ነው፡፡ ከዛ በኋላ የብርሃኑና የማዲንጎ ‹‹አንበሳው አገሳ›› ወጣ፡፡ (ዜማው የህዝብ፣ ግጥሙ የመሰለ ጌታሁን ሲሆን ቅንብሩ ሙሉ በሙሉ የእኔ ነው) ሁለቱም ላይ የሰቀሉ ዘፈኖች ነበሩ፡፡ እኔን የሚሊኒየሙ ዕድለኛ ያደረገኝ ሁለቱም ዘፈኖች ዓመት በዓል በመጣ ቁጥር የምንሰማቸው ማለትም ድሮ ከነበሩት ከእነጥላሁን ገሠሠ፣ ከእነ ብዙነሽ በቀለ የአመት በአል ዘፈኖች ጋር በማይተናነስ መልኩ እየተሰሙ ዘመን ተሻጋሪነታቸውን በማስመስከራቸው ነው፡፡
ዘ-ሃበሻ፡- በተለይ የቴዲ አፍሮን ‹‹ጊዜ ለኩሉ›› ቢዮንሴ አዲስ አበባ መጥታ በሰራችው ኮንሰርት መድረክ ላይ ተጫውተው ደንሳበታለች፡፡ ያ እንዴት ሊሆን እንደቻለ ብታጫውተኝ?
አማኑኤል፡- በወቅቱ እኔም እዚያው ሚሌኒየም አዳራሽ ነበርኩ፡፡ እና ሰርፕራይዝ ያደረገች ጊዜ እንደማንኛውም አድማጭ ደንግጫለሁ፡፡ በጣም አሪፍ ነበር፡፡ ሙዚቃውን የመረጠችው ሳውንድ ማኗ ናት የሚል ነገር በኋላ ሰምቻለሁ፡፡ እርግጥም በዚያን ጊዜ የሳውንዱ ግሩቭ (Groove) በጣም ሒት ነበረ፡፡ ብዙ ጊዜ እንደ አጋጣሚ ሆኖ እንደዚያ አይነት ሚክሲንግ አልተሰራም ነበር፡፡ በመሆኑም ሳውንድ ማኗ ወደደችው፡፡ በሳውንድ በኩል በጣም ብዙ የሚጠበቅብን ነገር ያለ ቢሆንም በወቅቱ ግን ያ ሳውንድ በቂ እንደነበረ አምናለሁ፡፡ በተጨማሪም ያን ጊዜ በመላው ኢትዮጵያ ይለቀቅ የነበረው ይህ ዘፈን ነበር፡፡ ህዝቡ ያብድበት የነበረ በመሆኑ የቴዲ አዘፋፈንም ምርጥ ስለነበረ መርጠውታል፡፡ በአጠቃላይ በዚያ የሚሌኒየም ወቅት ለቢዮንሴ ይመጥን የነበረ ሙዚቃ ስለሆነ ነው ብለን ብንወስደው ደስ ይለኛል፡፡
amanuel & ephrem Tamru
ዘ-ሃበሻ፡- ብዙ ጊዜ በግጥምና ዜማ ስራዎችህ ላይ እውነተኛ ታሪኮችን ወደ ሙዚቃ እየቀየርክ እንደምታቀርብ ይሰማል፡፡ ይህን ስታይል የመረጥከው ለምንድን ነው?
አማኑኤል፡- ይሄን ጥያቄ ለመመለስ ትንሽ ወደኋላ መለስ ብዬ ልጀምርልህ፡፡ ከያሬድ ሙዚቃ ት/ቤት የተመረቅኩበት መሳሪያ ደብል ቤዝ ይባላል፡፡ ፒያኖ ማይነሬ ሲሆን፣ በባህል መሳሪያ ማሲንቆን ተጫውቻለሁ፡፡ ማሲንቆ በጣም ዜመኛ ያደርጋል፡፡ ከዚያ ውጭ ደግሞ የአዝማሪ ግጥሞችን መስማት በጣም ደስ ይለኛል፡፡ ረጅም ጊዜ እየሄድኩኝ የእነሱን ስራዎች እከታተላለሁ፡፡ አንድ የአዝማሪ ስራንም ፕሮዲውስ አድርጌያለሁ፡፡ እንደነዚህ አይነት በድሮ ጊዜ የሚሰሩ ነገሮች ሪያሊቲ አላቸው፡፡ ለምሳሌ ከድሮ ድምፃዊያን የማደንቀው የጋሽ ባህሩ ቀኜ ግጥሞችን ነው፡፡ በዚህ ዘመን ‹‹አንጣላ›› ብሎ የሚዘፍን የለም፡፡
ልቤን ጅብ በበላው ባወጣው አጥንቱ፣
ተጣልቶ መታረቅ አይሆን እንደ ጥንቱ፡፡
የመሳሰሉ ግጥሞች ያለውን ነባራዊ ሁኔታ ቀድመው የሚነግሩህ ናቸው፡፡ እንደዚህ አይነት ፍልስፍና ውስጥ ስትገባና ይህን እያዳበርከው ስትሄድ፣ ላይፍን ወደ ሙዚቃ አምጥተህ የሰውን ታሪክ ስትፅፍ ከዛ የበለጠ ቀድመህ ሁሉ መድሃኒት ታዘጋጃለህ፡፡ እኔ ደግሞ ፊት ለፊት ያሉኝን ችግሮች ወደ እውነተኛ ታሪክ ማድረግ እፈልጋለሁ፡፡ ለምሳሌ በአንድ ዘመን እሰራቸው የነበሩት ስራዎች በአብዛኛው አፍቅሮ የተጎዳ ሰው ላይ ያመዝን ነበር፡፡ የተወሰኑትን ብጠቅስልህ ‹‹እንዳረከኝ አድርገኝ፣ ሳታመሀኝ ብላ፣ ኋላ እንዳይቆጭሽ፣ በአይኔ ላይ ዋልሽሳ በአይኔ፣ የማታ ማታ…›› ሌሎችም አሉ፡፡ በሴት ደግሞ የነፃነት አየለ ‹‹ላያገባኝ›› አለ፡፡ ማለትም እንዴት ይሄ ሁሉ ጊዜ አልፎና ዛሬ ከእኛ አልፎ ለሰው ተርፎ፣
ለካ ይሄን ሁሉ ጊዜ እያለፋኝ ነበረ ለካ
ሳያገባኝ እያለች የምትጫወተው ማለት ነው፡፡
ይህም አንዲት ሴት ረጅም ዓመት አንድ ወንድ ይዟት ሄዶ ጊዜዋን ሁሉ ገድሎ በመጨረሻ ሳያገባት ሲተዋት ያመላክታል፡፡ የብዙ ሴቶችን፣ ችግር ያሳየሁበት ነው፡፡
ዘ-ሃበሻ፡- በጎሳዬ ተስፋዬ የተዘፈነውን ‹‹ሳታመሀኝ ብላ›› ግጥም የፃፍከው ከእውነተኛ በምታውቀው ሰው ላይ ከደረሰ አጋጣሚ ተነስተህ መሆኑም ይነገራል፡፡
አማኑኤል፡- ልክ ነህ፡፡ ‹‹ሳታመሀኝ ብላ›› ትልቅ ታሪክ ነው፡፡ በአንድ የቅርብ ጓደኛዬ የደረሰ ታሪክ ነው፡፡ አንድ ሰው የሚወደውን ጓደኛውን በምን መንገድ እንደሚያጣው፣ ሚስቱን ደግሞ በጓደኛው እንዴት እንደሚያጣ የሚገልፅ ነው፡፡ የክሊፑ አለመሰራት ዘፈኑን በውስጥ ደረጃ አስቀረው እንጂ ትልቅ ታሪክ ያለው ነው፡፡
የሚገርምህ ከዚህ ዘፈን ጋር በተያያዘ ብዙ ገጠመኝ አለኝ፡፡ ለምሳሌ ‹‹እንዴት ሰውን ጅብ ትላለህ?›› ያሉኝ ሰዎች ነበሩ፡፡ እኔ ግን ‹‹ጅብ›› ስል በልመናና በጨዋነት ነበረ የገለፅኩት፡፡
አንቺም ትዳሬ ነሽ እሱም ጓደኛዬ፣
ጥፋቱ የማን ይሆን ስሄድ አንችን ጥዬ፣
አወይ ክፉ ዘመን ልቤ አዘነብሽ
እሱም ተሳሳተ የእኔ እናት አንቺም አልታመንሽ
ታማኝ ያንቺ ገላ ያለኔም አያውቅም
ምነው ደከመሳ አነሰው ወይ አቅም
ስደተኛ ታርገኝ ደሞ ብላ ብላ
ጅብ ረሃብ አይችልም ብለህ ወንድሜ ሳታመሀኝ ብላ
አየህ ‹‹ወንድሜ›› ነው ያልኩት፡፡ ጭካኔ የለውም፣ ግን መልዕክቱ ሃያል ነው፡፡ በጓደኛዬ ላይ የደረሰው ህመም ነው ያንን እንድፅፈው ያደረገኝ፡፡ ብዙዎች ይህ የእኔ ስራ መሆኑን ሲያውቁ የኔ ታሪክ መስሏቸው ደውለው ሀዘናቸውን የገለፁልኝ አሉ፡፡ ሌሎች ደግሞ ‹‹የእኔን ታሪክ ነው የሰራህልኝ›› ያሉኝም አሉ፡፡
amanuelዘ-ሃበሻ፡- አንተ በጥሞና ዜማውን የሰራኸውና ኤፍሬም ታምሩ የተጫወተው ‹‹ኋላ እንዳይቆጭሽ›› ሙዚቃም እውነተኛ ታሪክ ነው አይደል?
አማኑኤል፡- ኋላ እንዳይቆጭሽ እውነተኛ ታሪክ ነው፡፡ በአንድ ጊዜ የሰራሁት ስራ ነው፡፡ ታሪኩን በዝርዝር ባልነግርህም የዚያን ጊዜ የተፈጠሩት ‹‹ኋላ እንዳይቆጭሽ››፣ የጌዲዮን ዳንኤል ‹‹እንዳደረግከኝ አድርገኝ››፣ የፀሐዬ ዮሐንስ ‹‹ፍቅርሽ እንደ ጥላ፣ አንድ በይኝ…›› ወዘተ እውነተኛ ታሪክን መሰረት ያደረጉ ናቸው፡፡
ዘ-ሃበሻ፡- አማን አንተ ሌላ የምትታወቅበት ‹‹ለታናሿ ልስጋ›› በሚለው የሙዚቃ ቪዲዮ ነው፡፡ ይህንን ቪዲዮ ግጥምና ዜማ ሰርተህ ከማቀናበርህም በላይ ራስህ ፕሮዲውስና ዳይሬክት አድርገህ ያቀረብከው መሆኑን አውቃለሁ፡፡ ለመሆኑ ይህን ስራ ለማቅረብ እንዴት ተነሳሳህ? ከአድማጭ ያገኘኸው ምላሽስ?
አማኑኤል፡- የምር ለመናገር ደራሲ ስትሆን፣ በሰው ችግር ውስጥ ማለፍ ስትጀምር፣ ዘፈኖችን ወደ ሪያሊቲ ስታመጣና ወደ እውነተኛው በሄድክ ቁጥር አርቱም ይሳካልሃል፡፡ የምትፅፈው ነገር ይሳካል፡፡ ዳይሬክት የምታደርገው ነገር ሁሉም ወደ እውነት ይቀርብልሃል፡፡ ከቅንነት ከተነሳህ ማለት ነው፡፡ እና የሚገርምህ ነገር በቡና ቤት ሴቶች ላይ፣ በጎዳና ተዳዳሪዎች ላይ፣ በአላቻ ጋብቻ ላይ እንደዚህ አይነት ነገሮችን ለመስራት እያሰብኩ ባለሁበት ሰዓት ወደ ገጠር ውስጥ እየሄድኩ፣ በቀንም በማታም ያለውን ሁሉ እያየሁ እየቀረብኩ እፅፍ ነበር፡፡ እና በዚህን ወቅት አንዲት ልጅ በጣም አዝና አየሁኝ፡፡ ያቺ ልጅ በሀዘን አገጯን የያዘች፣ ከንፈሯ የሚንቀጠቀጥ፣ እንባ ያቀረረችና ደንግጣ የተቀመጠች ነበረች፡፡ እኔም የፃፍኩት ያንኑ ነው፡፡ ግጥሙንም ስፅፈው፤-
እንባ አዝሎብኝ አይኖቿ፣
መዳፏ አልፎ ከጉንጮቿ
እንባዋ ይፈሳል ሳያባራ
ብቻውን ያወራል ከንፈሯ
እያልኩ ጀመርኩት፡፡ ከዚያ ይህችን ህፃን ሊድሯት፣ ቤተሰቦቿም ፈረዱባት፣ እያልኩ ዘፈኑን እየሰራሁት ይህን ዘፈን በደንብ ሊጫወተው የሚችለው ማነው? የሚለው ውሳኔ የኔ ነበር፡፡ ጎሳዬን መረጥኩት፡፡ እንደውም ለጎሳዬ ክፍያ ስከፍለው ‹‹እንዴት እንደዚህ አይነት አይዲያ?›› ሲለኝ ግድየለህም ብዬ አስጀመርኩት፡፡ ከዚያ ቡሬ አንድ ጥጃ አጠገቧ ስለነበረች ‹‹ቡሬ ቡሬ ቀናችን አይደለም እኔና አንቺ ዛሬ፣ አለጊዜው ታርደሽ አለጊዜው ተድሬ›› የሚለው በመስታወት አራጋው ተቀረፀ፡፡ ታገል ሰይፉም ገባበት፡፡ በእንደዚህ አይነት ተቀረፀ፡፡ ዘፈኑን ከቀረፅን በኋላ የዚህን እውነተኛ ታሪክ ሰው ጭፈራ ይመስለዋል፡፡ ምክንያቱም ሲሰማው እንደዘፈን የሚያደምጠው ነው፡፡ ስለዚህ ክሊፑን በመስራት መልዕክቱን ህዝቡ እንዲረዳው ማድረግ ያስፈልግ ነበር፡፡ የዚህንም ሪስክ ወስጄ ወደ 50 ሺ ብር በማውጣት ክሊፑን አሰርቼዋለሁ፡፡ እዛ ውስጥ ያለ ሁሉ ድምፃዊ፣ አንባቢ ተከፍሎታል፡፡ ይሄ ሁሉ አልፎ እስካሁን ከሰራኋቸው በርካታ ስራዎችና ሙዚቃዎች በላይ በየሄድኩበት ዓለም ሁሉ ‹‹ለታናሿ ልስጋ›› ነው የሚሉኝ፡፡ ምክንያቱም በህዝብ ዘንድ ትልቅ ተቀባይነት ያገኘሁበት በዚህ ስራ ነው፡፡ እንደምታውቀው የአላቻ ጋብቻን በተመለከተ ብዙ ወረቀቶች፣ ብዙ ወርክሾፖች፣ ብዙ ስብሰባዎች ተደርገዋል፡፡ ግን በሰባት ደቂቃ አንድ የሙዚቃ ክሊፕ ብዙ ለውጥ ሊያመጣ የሚችል መሆኑን ብዙዎች መስክረውለታል፡፡ ሰውን እያዝናና ለቀጣዩዋ ለታናሿ ደግሞ ይታሰብበት በሚል መንገድ የቀረበ በመሆኑ ኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ ሳይሆን በአውሮፓም፣ በአሜሪካም፣ በካናዳም አውስትራሊያም፣ አረብ አገር ጭምር ያሉት የወደዱትና እንዲዘፈን ደጋግመው ያዩት ክሊፕ ሊሆን ችሏል፡፡
ዘ-ሃበሻ፡- በቅርቡም ሌላ ይህን መሰል ክሊፕም ሰርተሃል? ይህኛውስ?
አማኑኤል፡- አዎ፣ በቅርብ ጊዜ ድጋሚ ከጎሳዬ ጋር ሰርቻለሁ፡፡ ያቀናበረው አበጋዝ ነው፡፡ ግን ዜማውም ግጥሙም የእኔ ነው፡፡ ‹‹ፍጥረትን እንደቀላል›› የሚል ነው፡፡ ይህኛው ደግሞ ህፃናቶችን ብዙ ጊዜ ከገጠር እያመጡ ዘመድ ጋ ይቀመጡ በሚልና በተለያየ መንገድ በማምጣት ትልልቅ ስራ ከአቅማቸው በላይ ያሰሯቸዋል፡፡ እኔም የሰራሁት ያንን በመቃወም ነው፡፡ ይህም ስራ አስተማሪ፣ ትልቅ ተቀባይነት ያገኘና ማህበረሰቡን የሚነካ፣ ለውጥና ዕድገትን የሚያመጣ የህፃናትን ኃላፊነት እኛ መውሰድ እንዳለብን የሚያስገንዘብ ሆኗል፡፡ እንደ አጋጣሚ ይህን ያሰራኝ አንድ ድርጅት ነው፡፡ ለታናሿ ልስጋን አይተው በዚያ መንገድ እንዲሰራላቸው ፈልገው ጠይቀውኝ ቦታው ድረስ ሄጄ፣ እንዴት ሽመና እንደሚያሸምኗቸው እህል እንዴት እንደሚያስፈጯቸው ከባባድ ስራ ሲያሰሯቸው አይቼ በጣምም እንዳይከፉ አድርጌ ቀለል አድርጌ የሰራሁት ነው፡፡ ግን ያለው ሁኔታ በዚህ መንገድ ብቻ የሚገለፅ ሳይሆን ሁለትና ሶስት እጥፍ የበለጠ መገለፅ የሚችል ነው፡፡ እኔ ግን የማምነው ማንኛውንም አይነት ችግር ነገሮችን በማቅለል ማህበረሰቡ በሚረዳበት መንገድ ማስተማርና ማዝናናት እንዳለብን ነው፡፡ በመሆኑም ያቀረብኩት በዚህ ሁኔታ ነው፡፡ ከሁለቱ ስራዎቼ በተጨማሪ በቀጣይነት እንደዚህ አይነት ስራዎችን ማለትም ማህበረሰቡ ውስጥ ያለውን ችግር እየፈለፈልኩ የማውጣት አቋም አለኝ፡፡
ዘ-ሃበሻ፡- እስቲ ስለዜማ ላሰታስ ባንድስ እናውራ፡፡ እንዴት ተቋቋመ? እንዴትስ ሊፈርስ ቻለ?
አማኑኤል፡- እኔ ዜማ ላስታስ ባንድ ለሙዚቃ ዕድገት አንድ መሰረት ነው ብዬ የማምንበት ነው፡፡ ከያሬድ ሙዚቃ ት/ቤት የተመረቅን ልጆች ማለትም ኤልያስ መልካ፣ ሁንአንተ ሙሉ፣ ሚካኤል መላኩ፣ ምስጋናውና እኔ ሆነን ያቋቋምነው ሲሆን፣ ስንጀምር ድምፃዊዎች ትዕግስት በቀለ፣ ሚካኤል በላይነህ፣ እዮብ መኮንን፣ ኃይሌ ሩትስ ባንዱ ውስጥ ነበሩ፡፡ ባንዱ ትልቅ የሳውንድ ለውጥ ይዞ የመጣና አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ነበር፡፡ ባንዱ ሊፈርስበት የቻለው ዋንኛ ምክንያት ሁላችንም ወደየስራችን ስቱዲዮ መበታተናችን ነው፡፡ መጀመሪያ ኤልያስ መልካ፣ ቀድሞን የራሱን ስቱዲዮ ሲከፍት ሁንአንተ ተከተለው፡፡ ከዚያ እኔም ወደ ስቱዲዮ ገባሁ፡፡ ከዚያ የየራሳችንን የስቱዲዮ ስራ ስንሰራ ወደ ባንዱ ለመስራት ስላልቻልን ሊፈርስ ችሏል፡፡ ይሁንና ባንዱ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የዓለማየሁ እሸቴ፣ የባህት ገ/ህይወት፣ የፍቅር አዲስና የመሳሰሉትን የድሮ ሙዚቃዎች አምጥተን በጥሩ ሁኔታ ቀርፀን ሰው በሚገርም ሁኔታ ተቀብሎታል፡፡ በዚያ ሳውንድም ባንዱ በጣም አሪፍ ከሚባሉት ባንዶች ስሙን አስቀምጦ ለማለፍ ችሏል፡፡
amanuel teddy afro and maritu legesse ዘ-ሃበሻ፡- አንተ በሙዚቃ ስራ በተለያዩ የዓለማችን ክፍሎች ለመዞር የቻልክ ነህ፡፡ የአቡጊዳ ባንድ ውስጥ ተካተህም ከቴዲ አፍሮ ጋር ብዙ መድረኮች ላይ መስራትህን አውቃለሁ፡፡ የሙዚቃ ጉዞህን በተመለከተ እናውራ?
አማኑኤል፡- የሚገርምህ ከታዋቂ ድምፃዊያን ጋር ወደ ውጭ አገራት ከመሄዴ በፊት ከያሬድ ት/ቤት እንደተመርቅኩኝ አንድ ‹‹ፎርኤቨር ያንግ›› የሚል የባህል ቡድን አቋቁሜ ነበር፡፡ ከዚያ ቡድን ጋር ሀኖቨር የባህል ኤክስፖ በተዘጋጀበት ወቅት ከዛሬ 13 ዓመት በፊት በመሄድ ጀምረን በተከታታይ ለአንድ 6 ዓመታት የተለያዩ ቦታዎች ሰርተናል፡፡ ከዚያ ስቱዲዮ ከመግባቴ በፊት ከእነፍቅር አዲስ፣ ኃይልዬ፣ ይርዳው፣ ህብስት ቴዲ አፍሮን ጨምሮ ራሴ ፕሮሞተር እየሆንኩኝ ከአገር ውስጥ እስከ አረብ አገሮች እሰራ ነበር፡፡ የመጨረሻ ጉዞዬን ያደረግኩት ደግሞ ከቴዲ አፍሮ አቡጊዳ ባንድ ጋር በመቀላቀል ነው፡፡ ከአቡጊዳ ጋር ከ24 ሾው በላይ ሰርቻለሁ፡፡ ይህም በመላ አውሮፓ፣ አረብ አገራት፣ እንዲሁም አሜሪካና ካናዳ ዞሬያለሁ፡፡
ዘ-ሃበሻ፡- ምንም አልበም ሳይኖረው በመላው ዓለም ታዋቂ ለመሆን የበቃው ጃኪ ጎሲ (ጎሳዬ ቀለሙ) ከዚህ ቀደም በዚሁ ዘ-ሃበሻ ጋዜጣ ቃለ ምልልስ ሲያደርግ አንተን አመስግኗል፡፡ ከስኬቱ በስተጀርባ ያለህ ቁልፍ ሰው መሆንህንም ተናግሯል፡፡ ለመሆኑ ከጃኪ ጋር የነበራችሁ የስራ ግንኙነት ምን ይመስላል?
አማኑኤል፡- ጃክ ከጥቂት ዓመታት በፊት እኔ ጋር ሊሰራ በአጋጣሚ ወደ ስቱዲዮ መጥቶ ነበር፡፡ ይዞት የመጣው ስታይልም ትንሽ ወጣ የሚል ነው፡፡ ማለት ከአማርኛ ሙዚቃዎች ወጣ ያለና እንደ ሒፕ ሆፕ አይነት ነገር ነበር፡፡ እና የሒፕ ሆፕ ስታይሉን በሚያሰማኝ ጊዜ ልጁ አንድ ቃናና በጣም የሚገርም ድምፅ እንዳለው ተረዳሁ፡፡ ይሄን ድምፁን ደግሞ በእርግጠኝነት የሌላ ዜማ ስታይል ቢሰራበት ጥሩ ይሆናል በሚል ትንሽ ደቂቃ ተነጋገርን፡፡ ልጁም ጥሩና ቅን ስለሆነ ወዲያው ተመለሰ፡፡ ምክንያቱም የዜማ ደራሲ ስትሆን የመጀመሪያው ነገርህ ሰው መፍጠር ነው፡፡ አንድን ድምፃዊ አምጥቶ መስራት እንደማለት ነው፡፡ እንደፊልም ለዚህ ተዋናይ ይህን ካራክተር ብሰጠው ይዋጣለታል ብሎ መቅረፅ ነው፡፡ ስለዚህ በዚያ መንገድ የመጀመሪያውን ‹‹ጭራሽ›› የሚለውን ሰራሁለትና ይዞት ወደ አገሩ ሄደ፡፡ እዛ ከለቀቀ በኋላ አቀባበሉ የሚገርም ሆነ፡፡ እኔ መልዕክቱንም ስፅፈው ውጭ አገር ስላሉ ሰዎች በመለያየትና በመነፋፈቅ ውስጥ እንዴት እንደሚተሳሰቡ በሚያደርግ ስሜት ነበር፡፡ በመሆኑም ውጭ አገር ያሉ ሰዎች በጠቅላላ ወደዱት፡፡ ከዚያ ከስድስት ወር በኋላ ደወለልኝና ‹‹ዘፈኑ በጣም ቡም ብሏል›› አለኝ፡፡ አላመንኩም፡፡ ‹‹እውነትህን ነው?›› አልኩና ዩቲዩብ ላይ ሳየው ደነገጥኩኝ፡፡ የሚገርምህ ወደ 2 ሚሊዮን 800 ሺ ህዝብ አይቶለታል፡፡ በደወለልኝ ጊዜ ሌላ ዘፈን እንዳዘጋጅለት በጠየቀኝ መሰረት ‹‹ደሞ አፌን›› ሰራሁለት፡፡ የመጀመሪያው የባህል ዘመናዊ ሲሆን ይህ ግን ችክችካ አይነት ለመድረክ የሚሆን ነው፡፡ ከዚያ፣ በየኮንሰርቶች ተመራጭ ለመሆንና ለመስቀል ቻለ፡፡ ቀጥሎ ‹‹ሰላ በይ›› የሚለውን በሌላ ስቱዲዮ መጥቶ ሰራው፡፡ እሱም ውጤታማ ሆነለት፡፡ ይሄ ልጅ የተሾመ አሰግድን ‹‹የእኔ አካል›› የሚለውን ድጋሚ በመዝፈን አንድ ዘፈን ጨምሮ በአራት ዘፈን በዓለም ላይ እየተዘዋወረ በመስራት ላይ ይገኛል፡፡
እኔ ለጃክ የመጀመሪያውን ሙዚቃ ግጥምም ዜማም ቅንብርም ስለሰራሁለት ሊያመሰግነኝ ቢችልም፣ እኔ ደግሞ በጣም ብልህ ልጅ እንደሆነ ይሰማኛል፡፡ ለምን ብትል በደራሲ ያምናል፡፡ የድሮዎቹን ትልቅ ደረጃ የደረሱት እነ ኤፍሬም ታምሩን ብትመለከት ለረጅም ጊዜ የሰሩት ደራሲዎችን ይዘው በመምጣታቸው ነው፡፡ ልጁ በዚሁ ከቀጠለ ታዋቂዎቹ የደረሱበት ቦታ የማይደርስበት መንገድ የለም፡፡
ዘ-ሃበሻ፡- ብዙውን ጊዜ የድሮ ድምፃዊያንን በተለያዩ መንገዶች ታነሳለህ፡፡ ለምንድን ነው?
አማኑኤል፡- ያለጥርጥር እኔ የድሮዎቹ ድምፃዊያን አድናቂ ነኝ፡፡ ከ50ዎቹ ጀምሮ የነበሩት በተለይ ባህሩ ቀኜ፣ አሰፋ አባተ፣ ወደዚህ ስትመጣ ጋሽ ይርጋ ዱባለ በጣም ድምፃዊ ናቸው፡፡ በዚያን ጊዜ የሚያገኙት ግጥምም ሆነ ዜማ ያስገርመኝ ነበር፡፡ በተለይ ጋሽ ባህሩ የሚፈጥረው ዜማና ግጥም በጣም ለኢትዮጵያ ሙዚቃ መሰረት የነበረና ለረጅም ዓመት የተደመጠ ነው፡፡ ወደዚህ ስንመጣ ደግሞ የእነ ጥላሁን፣ የእነ ብዙነሽ፣ የእነ ሒሩት ዘመን አለ፡፡ ሲቀጥል ሮሀ ባንድ፣ በ70ዎቹ እነ ኤፍሬም ታምሩ፣ ሙሉቀን መለሰ፣ ቴዎድሮስ ታደሰ፣ አስቴር አወቀ እያልን መዘርዘር እንችላለን፡፡ እነዚህ ሰዎች ሙዚቃን ለ40 እና 30 ዓመታት ያሻገሩ ናቸው፡፡ ስለዚህ እንደቀላል አይታዩም፡፡ አሁን የእኛ አገር ሙዚቃዎች ለሶስትና ለአራት ወር ተሰምተው ሲቆዩ እንደትልቅ ነገር የምናይበት ጊዜ ላይ ደርሰናል፡፡ ስለዚህ እኔ የዚያን ጊዜ ሰዎች በምን መንገድ ቢሰሩት ነው ቴክኖሎጂ በሌለበት ሰዓት፣ በአናሎግ ሲስተም እየቀዱ፣ ኮምፒውተር ሳያግዛቸው፣ ላይቭ እየቀዱ፣ ወጣቱ በእነሱ ዘፈን እየተማረከ እኛ እንዴት እንደነሱ መስራት አቃተን? የሚሉ ጥያቄዎች ስላሉኝ ያኛው ትውልድ ይበልጥብኛል፡፡ ይሄ የእኔ ብቻ ሳይሆን፣ የአድማጭ፣ የህዝብና የአርቲስቱ ጥያቄ ይመስለኛል፡፡
ዘ-ሃበሻ፡- የዚህ መፍትሄው ምንድን ነው ትላለህ?
አማኑኤል፡- አንደኛው ነገር ራሳችንን እየሆንን አይደለንም፡፡ ራሳችንን መሆን መቻል አለብን፡፡ ሁሉም በየፊናው የተለያየውን ዓለም ሙዚቃ ይሰራል፡፡ አይስራ አልምም፡፡ በስታይሉ ውስጥ ደግሞ ስራውን በማቅለል ደረጃ በአንድ ሞኖ ስቱዲዮ (ሆም ስቱዲዮ) ውስጥ በመሰራቱ አንድ ሰው ሙዚቃውን እንደፈለገው ማድረግ ጀመረ፡፡ ድምፃዊያኑም ስለቀለለው ገባ፡፡ መአት ድምፃዊያን ተፈጠሩ፡፡ ግን ከዚያ ውስጥ ምን ያህሉ ድምፃዊ ነው? ብለህ ብታስብ ሁሉም አይደሉም፡፡ ስለዚህ ህዝቡንም አሰለቸነው፡፡
እኛ የእኛነት የምትለው ነገር የለም፡፡ ሬጌው ምን ያህል በኢትዮጵያ ሄዷል? ብትል የለም ገና መጀመሩ ነው፡፡ ሒፕ ሆፕ አለ ወይ? ብትል ሒፕ ሆፕ የሚባል ሙዚቃ የት አለ? ሌላው ዓለም መጥቶ ሲሰማን በጣም ያዝንብናል፡፡ በየስቱዲዮው ነጮቹ ጥቁሮቹ መጥተው አይተው የተሰማቸውን ስሜት አውቃለሁ፡፡ ስለዚህ በዚህ ትውልድም እንደድሮው የራሳቸውን ቀለም ይዘው መስራት እንዳለባቸው ይሰማኛል፡፡ ኢንዱስትሪው እንዲያድግና አድማጭ እንዲሰማን ከፈለግን ጥሩ ዜማ፣ ለግጥሙም መጨነቅ፣ ለአሬንጅመንቱም መጨነቅና ጥሩ ድምፃዊም መስራት ያስፈልገናል፡፡
ዘ-ሃበሻ፡- የሙዚቃ አቀናባሪ፣ የግጥምና ዜማ ደራሲ፣ የሙዚቃ ቪዲዮ ክሊፕ ዳይሬክተር ፕሮዲውሰር ስለመሆንህ እስካሁን በነበረን ቆይታችን ስናወራ ቆይተናል፡፡ አሁን ደግሞ በፊልሙ ዓለም ስላለህ ተሳትፎ እናውራ፡፡ እንችላለን?
አማኑኤል፡- ይቻላል፡፡ ስለፊልም ካነሳን የመጀመሪያው ‹‹የማያልቀው መንገድ›› ነው፡፡ እንኳን እኔ ኢትዮጵያ ውስጥም ፊልም ገና እየገባ በነበረበት ከዛሬ 10 ዓመት በፊት ነበረ፡፡ የያኔው ከነበረው ሁኔታ አንፃር ጥሩ ነው፡፡ ወደ አሁኑ ዘመን ስንመጣ ‹‹ፔንዱለም›› እና ‹‹ከመጠን በላይ›› የሚሉ ፊልሞች ላይ ሰርቻለሁ፡፡
የፔንዱለም ፕሮዲውሰር ቶማስ ጠርቶ ሲፈትነኝ ሌሎች ዳይሬክተሮችም ይዞ ነበር፡፡ ከተፈተንኩ በኋላ የተቀረፅኩትን በቪዲዮ ስመለከተው እውነቴን ነው የምልህ ጠላሁት፡፡ እናም ‹‹እኔ መግባት የለብኝም፡፡ እኔ አልሆናችሁም›› አልኳቸው፡፡ ግን ዳይሬክተሩ ለዚህ ቦታ አማን ይሆናል ብሎ ከወሰነ ሪስኩን ይወስዳል፡፡ ስለዚህም ‹‹ይህን ልጅ እለውጠዋለሁ፣ በዚህ አይነት ፎርም አመጣዋለሁ›› ብሎ ስላሰበ ዳይሬክተሩንም አምኜ ገባሁበት፡፡ እውር አሞራ እንደማለት ነው የማታውቀው ነገር ውስጥ መግባት፡፡ በዚህ መንገድ ሰራሁ፡፡ ፊልሙ እስኪያልቅ ድረስ ስቱዲዮ ዘግቼ ነው የሰራሁት፡፡
ዘ-ሃበሻ፡- የፔንዱለም ፊልም ምርቃት ከተማውን ሁሉ በነቀነቀ ሁኔታ ነበር የተከናወነው፡፡ በዚህ ረገድ የአንተም ወሳኝ ድርሻ እንደነበረበት ሰምቻለሁ፡፡ እውነት ነው?
አማኑኤል፡- ፊልሙ ከተጠናቀቀ በኋላ በአንዳንድ ቦታዎች ማስታወቂያውን ሰማሁ፡፡ ያኔ ለፕሮዲውሰሩ ቶም ደወልኩለትና መተዋወቅ ያለበት በዚህ አይነት መንገድ አይደለም አልኩት፡፡ ምክንያቱም እንደ አበባዮሽ አይነት እን ደጃኪ አይነት ስዎች ጎልተው ሲወጡ ደስ ይለኛል፡፡ ዘፈን ከተሰራ ጎልቶ መውጣት አለበት፡፡ ፊልምም ቢሆን እንደዚያው ነው፡፡ ስለዚህ የሚዲያውን ስራ ሁሉ ጠቅልዬ ያዝኩት፡፡ እንደውም የማልረሳው ለሳውንድ ትራኩ ብዙአየሁ ብዙ ብር ጠየቀ፡፡ እኔ ‹‹በቃ ራሴ እገዘዋለሁ›› ብዬ አሰራሁትና ጨርሼ ቶምን ሰራሁት፡፡ ቶምም ሲሰማው ዘፈኑን ሳላጋንን ከ30 ጊዜ በላይ ቆሞ ሰማው፡፡ ፊልሙን ግልፅ አድርጎ የሚያሳይ በመሆኑ ዘፈን ይሄን ያህል ፓወር አለው ወይ? ብሎ ደነገጠ፡፡ ከዚያ ተጀመረ፡፡ ቶም ሁሉንም ወጪ አወጣለሁ በማለቱ ወደ ሚዲያ መጥተን ሬዲዮኑን ተቆጣጠርነው፣ ጋዜጦችን ተቆጣጠርን፡፡ ቀጥሎ የሚሊኒየም አዳራሽ ሀሳብ መጣ፡፡ ቀይ ምንጣፍ ታሰበ፡፡ እኔ ወደ ባንድ መጣሁኝ፡፡ ሔለን በርሄ ገባች፡፡ በዚህ ጊዜ ሰዎችን ሳማክር ‹‹እናንተ እብድ ናችሁ ወይ፤ እንዴት ዘፈንና ፊልም አንድ ላይ ይታያል? በዚያ ላይ ሚሊኒየም አዳራሽ›› ብለው አልተቀበሉኝም ነበር፡፡ ግን ነገሮችን ትልቅም ትንሽም የምታደርገው አንተ ነህና በውጥናችን ገፍተንበት በስተመጨረሻ 14 ሺ ሰው መጥቶ ፊልሙን ሊያየው ችሏል፡፡
ዘ-ሃበሻ፡- ለዚሁ ፊልም ማጀቢያነት ሔለን በርሔ የተጫወተችውን ሙዚቃ በግጥምም በዜማም በማቀናበርም ሰርተሀል፡፡ ይሄ ሙዚቃዋ ደግሞ ከፊልሙም በኋላ በተለያዩ ሚዲያዎች ሲደመጥ ይታያል፡፡ ሙዚቃውን ስታዘጋጅላት ከፊልሙም ውጭ ይደመጣል ብለህ አስበህ ነበር?
አማኑኤል፡- ይኸውልህ አንድ ምሳሌ ልንገርህ፡፡ ‹‹ለካ ለካ ያንተ ዓለም፣ ወዲህ ወዲያ ፔንዱለም›› የምትለዋ የዘፈኑ ግጥም ኤዲት ሲደረግ ነበርኩኝ፡፡ እና ያኔ ‹‹በናታችሁ ልብስ ስለካ እዚህች ቦታ አስገቡኝ›› አልኩ፡፡ ፊልሙ ላይ የምሰራው ልብስ ሰፊ ሆኜ ነው፡፡ እና ለካ፣ ለካ ማለት ልብሱን ለካ እንደማለት ነው፡፡ በፊልሙ ላይ ግን ዝም ብለህ ፊልሙን ባታየውም ደግሞ ‹‹ለካ ከእኔ ጋር አልነበርክም›› የሚል ትርጉም ይሰጥሃል፡፡ የውጪዎቹን ስራዎች እያደነቅንና የእነሱን ተሞክሮ እየቀሰምን መሄድ ያለብን ይመስለኛል፡፡ ታይታኒክ ፊልም ለእኔ ምርጥ ፊልም ነው፡፡ የፊልሙን ማጀቢያ ሙዚቃ የሰራችው ሴሊንዲዮን ናት፡፡ ይህ ማጀቢያ ሲሰራ ስሎው ነው፡፡ ከፊልሙ ጋር ልክክ ብሎ ገብቶ እንዳትወጣ አድርጎ ዘፈኑን በሰማህ ቁጥር ብዙ የፍቅር ትውስታ እንዲኖርህ ያስችላል፡፡ ይሄ ዘፈን ቴክኖና ሐውስ ሆኖ ወጥቷል፡፡ ወደ ጭፈራ ዘይቤ ሆኖ ቀርቧል፡፡ እኔ የሄለን በርሔንም ሙዚቃ እኔ አንዳንዴ ሲጨፍሩበት አያለሁ፡፡ ጥሩ ነው፡፡ ይሄ ከፊልም ማጀቢያ ሙዚቃ ልዩ ትኩረት እንዲሰጠው መነሳሳትን የሚፈጥር ይመስለኛል፡፡
ዘ-ሃበሻ፡- ከሰሞኑ ‹‹ዜማ አማን›› በሚል ርዕስ አዲስ አልበም በፕሮዲውሰርነት አቅርበሃል፡፡ በዚህ አልበምህ ካመጣኸው ድምፃዊያን ኃይለየሱስ አንዱ ነው፡፡ ኃይለየሱስ ከሙዚቃው አካባቢ ጠፍቶ ነበርና የት አገኘኸው?
አማኑኤል፡- የኃይለየሱስ ነገር እንደማንኛውም አድማጭ እኔንም ይቆጨኝ ነበር፡፡ ተማሪ ሆኜ ያሬድ ሙዚቃ ት/ቤት እያለሁ እሱን ለማየት ለመስማት ስል ኤግዚቢሽን ማዕከል ድረስ እሄድ ነበር፡፡ ከዚያ በኋላ ያንን የመሰለ ድምፅ ይዞ ጠፋ፡፡
‹‹ይለፍ ዕድሜ፣ አንችን ስል ቆሜ›› የሚለው ወረድ ብሎ ጀምሮ በኋላ ላይ በጣም ከፍ የሚል ነው፡፡ ሀይለየሱስን ውስጤ ሁሌም ስለሚያስበው በቀጥታ እሱ ነው ይህን የሚዘፍነው ብዬ ወስኜ ደወልኩለት፡፡ እሱም ለረጅም ጊዜ ይፈልገኝ ነበርና ተነጋገርን፡፡ ዘፈኑን ሰጠሁት፡፡ በአጭር ጊዜ ይዞት ሰራው፡፡ አድማጭም በጣም የእሱን ዘፈን ወዶታል፡፡ ኃይለየሱስ የሚገርም ድምፃዊ ሲሆን፣ አብሬው በመስራቴ ደስተኛ ነኝ፡፡
ዘ-ሃበሻ፡- በአልበምህ የተካተቱት ድምፃዊያን በአሜሪካና በኢትዮጵያ የሚኖሩ ናቸውና እነሱን ማሰባሰቡና መጠበቁ አላስቸገረህም?
አማኑኤል፡- በጣም ተስፋ የሚያስቆርጥ ደረጃ ያደርሳል፡፡ አንዳንዴ ምን ውስጥ ነው የገባሁት? እስከማለት ደርሼ ነበር፡፡ ሙዚቃ ግን ከገባህበት አይለቅህም፡፡ አንዳንዴ ፈተና ቢበዛብ ህም በእልህ ተስፋን ሰንቄ ለአድማጭ ላበቃው ችያለሁ፡፡ ወደ አምስት ዓመት ያህል የፈጀብኝም ለዚህ ነበር፡፡S

Health: በትዳር መካከል ጸብ ሲነሳ እንዴት መፍታት ይቻላል?

$
0
0

ከሊሊ ሞገስ

ትዳር በባህር ወይም ውቅያኖስ ውስጥ ያለችን ትልቅ መርከብ ይመስላል፡፡ መርከቧ ረጅም ርቀት እንደመጓዟ ለተለያዩ አየር ፀባይ ለውጦች መጋለጧ አይቀሬ ነው፡፡ ፀጥታና ሰላም የሰፈነበት ጉዞ እንደምታደርግ ሁሉ አንዳንዴ ማዕበልና ሞገድ ለበዛበት ነፋስ፣ ለተተናኳሽ ሻርኮች፣ ከበረዶ ክምር ጋር ለግጭት፣ ቀደም ብለው ሳይፈተሹ ላለፉት የቴክኒክ ብልሽቶችና በቅርብ ጊዜ ደግሞ ለባህር ላይ ወንበዴዎች ስትጋለጥ እየሰማን ነው፡፡ ታዲያ ከዚህ ሰው ሰራሽና ተፈጥሯዊ ከሆነው አደጋ ለመውጣት ወይንም ቀድሞውኑ ላለመጋለጥ ካፒቴኑ፣ ረዳቶቹና ቴክኒሺያኖቹ የበኩላቸውን ጥረት ያደርጋሉ፡፡ የሚጠበቅባቸውን ጥንቃቄ ካላደረጉ ደግሞ ለመዘረፍ፤ እንደ ታይታኒክም ለመስመጥ፣ ከዚያም ባለፈ ለሞት ይዳረጋሉ፡፡
ትዳርም እንዲሁ ነው፡፡ የዕድሜ ልክ ኃላፊነት የምንወስድበት፣ ከተለመደው የግንኙነት አካሄድ በዘለለ ራሳችንን ለገባንበት ትስስር መስዋዕት የምናደርግበት፣ መልካምና አሳዛኝ የሆኑ ክስተቶችን የምናስተናግድበት ረጅም የህይወት ጎዳና ነው፡፡ ታዲያ እነዚህ ገጠመኞች ለምን ተፈጠሩ? ብለን ብቻ አንቆዝምም፤ ጠዋትና ማታም እያብሰለሰልን ዕድሜያችንን አንገፋም፡፡ ለችግራችን መሰረታዊ የሆነውን መንስኤውን ማወቅ፣ ለገጠመን ጉዳይ እንዴት መመለስ እንደሚገባን ማተኮር ያስፈልገናል፡፡ ይህን ዕውን ለማድረግ ደግሞ ሁለቱ ባለትዳሮች የሚወስዷቸው እርምጃዎች ወሳኞች ናቸው፡፡ ስለዚህ ጥንዶች ትዳራቸውን ሊያወፍሩት፣ ሊያቀጭጩት፣ መልካምና አስደሳች አሊያም በሰቆቃ የተሞላ ሊያደርጉት ይችላሉ፡፡
Marrage and facebook
የዛሬው እንግዳችን ጌታቸው የሰላሳ ስድስት ዓመት ጎልማሳ ነው፡፡ ቆንጅዬ ሚስትና የአምስት ዓመት ሴት ህፃን ልጅ አለው፡፡ በሃያዎቹ አጋማሽ ዕድሜው አካባቢ በነበረው የቅድመ ጋብቻ የወሲብ ልምምድ ከቀድሞዋ ጓደኛው የአስር ዓመት ወንድ ልጅ አድርሷል፡፡ ልጁ የሚኖረው ከአያቶቹ ማለትም ከእናቱ ወገኖች ጋር ነው፡፡ ‹‹ባለቤቴ ይህን ከመጋባታችን በፊት ታውቃለች፣ እኔም በተወሰነ ጊዜ እየሄኩ እጠይቀዋለሁ›› ይለናል፡፡
‹‹ይሁንና ባለቤቴ ለሴት ልጃችን በቂ ክብካቤ ሳላደርግ ለወንድ ልጄ ብዙ ትኩረት እንደምሰጥና የተለያዩ ነገሮችን እንድምገዛለት ነገረችኝ፡፡ በትንሽ ነገር ከኔ ጋር መጠላት ጀምራለች፤ አለመግባባት ሲፈጠርም የወንድ ልጄን ጉዳይ ሁሌ ታነሳለች፡፡ የርሱን ጉዳይ ትታው የራሳችንን ህይወት እንድንመራ ብነግራትም ትዳራችን አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ እየገባ ነው ያለው፡፡ በጣም ተጨንቄያለሁ፡፡ ከርሷ ምንድነው ማድረግ ያለብኝ?›› በማለት ጌታቸው ጠይቆናል፡፡
ወጣትነት ብርታትና ጥንካሬ የሞላበት፣ ብዙ ሰዎች ሊመለሱ ቢናፍቁት የማያገኙት፣ ራሳቸውን ለመለወጥ ቢሞክሩ መሆን የማይችሉበት ብዙ ውጣ ውረዶች ያሉበት በህይወት ዘመናችን የምናሳልፈው ጊዜ ነው፡፡ ወጣትነት ከነችግሮቹ በዕውነት ደስ የሚል የህይወታችን አንዱ ክፍል ነው፡፡ አንዳንዶች በእርግጥም ይህን ዘመን በትኩስ ሃይላቸው ይጠቀሙበታል፤ ሌሎችንም ያገለግሉበታል፤ ራዕያቸውንም እውን ለማድረግ የወደፊቱን መሰረት በማስያዝ የተቻላቸውን ያደርጉበታል፡፡ ሌላው ደግሞ በተባለው እየተመራ፤ መኖር የተፈቀደው ለዛሬ ብቻ ይመስላል፡፡ ነገን ሳይመለከት እንዲሁ በዋል ፈሰስ ወርቃማ ጊዜውን ያባክነዋል፡፡
እንግዲህ ከወንድማችን ጥያቄ መረዳት እንደምንችለው በአንድ ወቅት በነበረው የቅድመ ጋብቻ የወሲብ ልምምድ ልጅ ወለደ፡፡ መልካም አደረገ ባንለውም በወቅቱ ለፈፀመው ወይም ለገጠመው ነገር ምንም ሊያደርግና ሊመልሰው የማይችለው ነገር እንደሆነ ሁላችንም እንረዳለን፡፡ ያ ያለፈው ታሪኩ ነው፤ አንፍቀውም፡፡ ልንፍቀው እንሞክር ብንልም መላጥ፣ ማድማትና ማቁሰል ነው የሚሆንብን፡፡ ስለዚህ… ከሄድን ሁል ጊዜም ቢሆን ሊፈጠር ወይም ሊከሰት የሚችል ነገር እንዳለ ቀድሞውኑ ማሰብ ነው፡፡ አያችሁ በድርጊታችን ልጅ ሳይፈለግ ወደዚህ ምድር ይመጣል፤ ለኤች.አይ.ቪና ሌሎች የአባላዘር በሽታዎች መዳረግ አለ፤ ባልና ሚስት… ከገጽ 8 የዞረ
ከቤተሰብና ጓደኛ መገለል፤ እግዚአብሔርን ማሳዘን ይመጣል፣ ለተለያዩ ማህበራዊና ስነ ልቦና ችግሮች መጋለጥ ይኖራል፡፡ አያችሁ በወጣትነት ዘመን ሁሌ ቸበርቻቻ የለም፤ አንዳንዴ የሚጎረብጡ ሁኔታዎችንም ማሳለፍ አለ፡፡ አካሄዳችንን ካላስተካከልን፤ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድም ካላደረግን ደግሞ ዘወትር ልንረሳው የማንችለውን ጠባሳ ነው የምንሸከመው፡፡ ስለዚህ በዚህ አጋጣሚ የምንመክረው ከጋብቻ በፊት ያለ ማንኛውም ግንኙነት ለቀጣይ ህይወታችን መሰረት የምንገነባበት ጊዜና ወሳኝ ቢሆንም የወሲብ ልምምድ ማድረግ ግን አይጠበቅብንም፤ አይጠቅምም፡፡ ብዙዎቻችን አድርገን አልፈን ይሆናል፤ ግን ገንቢ አልነበሩም፡፡ ለጊዜው ተደስተንባቸው ይሆናል፤ መጨረሻቸው ግን አያምርም፡፡ ሐጢያት ከመሆኑም ባሻገር ዘርፈ ብዙ ለሆኑ ችግሮችና ጭንቀቶች ይዳርጉናል፡፡ ልምምዱን ከጋብቻ በኋላ ለጋብቻና ለትዳር ብቻ ማድረግ ነው፡፡
በጣም የሚገርመው ነገር ያልተፈለገ እርግዝና በሁለቱ ሰዎች ላይ ከሚደርሰው የስሜት ችግርና ማህበራዊ ጫና ባሻገር በተወለደው ልጅ ላይ የሚገጥመው ሚዛናዊ ያልሆነ አስተዳደግ በወደፊት ስብዕናው ላይ ከፍተኛ ችግር ማስከተሉ ነው፡፡ ሰዎች ብዙውን ጊዜ የሚያስቡት የራሳቸውን ጊዜያዊ ችግር ከመቅረፍ እንጂ ሳይፈልግ ወደዚች ምድር በሚያመጡት ልጅ ላይ ሊደርስ የሚችለውን ችግር አያስተውሉትም፡፡ ይህን በምን መንገድ እንደፈቱት ሊፈቱት እንደሞከሩ ባናውቅም አንድ እውነታ አለ፡፡ ተለያይተው ነው የሚኖሩት፡፡ አባት ሌላ ትዳር መስርቶ በሌላ ዓለም ውስጥ ሲመላለስ ልጅ ደግሞ ከእናቱና ቤተሰቧ ጋር ሌላ ህይወት ይገፋሉ፡፡ ከዚህ የሚከፋው ደግሞ አሁን ባለ ው አዲስ ህይወት ላይ በፊት የተፈጠረው ችግር ከአሁኑ ላይ ሌ ላ ችግርን እየወለደ ትዳርን መበጥበጡ ነው፡፡ እየተረዳችሁን ነው?
ከላይ ያነሳናቸውን መነሻዎች ከግምት ውስጥ በማስገባት በወንድማችን ትዳር እያንዣበበ ያለውን ችግር ለመቅረፍ ይበጃሉ የምንላቸው ምክሮች ካነበብናቸውና በህይወታችን ተሞክሮ ካየናቸው ነገሮች በመነሳት የሚከተሉትን አቅርበናል፡፡ (ይሁንና እነዚህ እውነታዎች በሌሎች የባልና ሚስት ጭቅጭቅ ችግሮች ውስጥ መፍትሄ ሊሆኑ እንደሚችሉ መረዳት ያስፈልጋል)
- የችግሩን መንስኤ ማወቅ
በእርግጥ ላለመግባባታችሁ ምክንያት የሆነው የወንድ ልጅህ ጉዳይ ነው ብለህ ታስባለህን? መሸፈኛ ላለመሆኑ ምን ያህል እርግጠኛ ነህ? ተፈጠረ ለምትለውስ ችግርና አለመግባባት ባለቤትህ ሳትሆን አንተ ለችግሩ ያበረከትከውን ነገር እንዳለስ አስበህ ታውቃለህ? አየህ መጀመሪያ እነዚህን መለየትና መሰል ጥያቄዎችን መመለስ የመጀመሪያ ጉዳይህ ሊሆን ነው የሚገባ ህ፡፡ ለዚህ ደግሞ መፍትሄ ሊመጣ የሚችለው መጀመሪያ ከራስህ በኩል ያለውን ስታስተካክልና ስታፀዳ ነው፡፡ ሁሉም ቤቱን ቢያፀዳ አካባቢም ንፁህ ይሆናል እንደሚባለው ነው፡፡
የኛ ችግር ምን መሰለህ? ብዙውን ጊዜ ለችግሮቻችን ሌላው ላይ መቀሰርና ሁኔታዎች ላይ ማላከክ እንጂ የለመድነው ወደራሳችን መልሰን መመልከቱን አናስብም፡፡ እንዲህ አደረጉብ ኝ፤ ይህን ሰጡኝ እንጂ ጉዳዩ ለመከሰቱ የኛ እጅ አለበት፤ የስራ ዬን አገኘሁ አንልም፡፡ በእጃችን ያለውን መፍትሄ ሳንጠቀም ሌላ አዲስ ነገር እንፈልጋለን፡፡ ባለን ሳናመሰግን የሌለንን እንናፍ ቃለን፡፡ ስለዚህ የመጀመሪያው ምክራችን የሚሆነው ከርሷ ጋር ምን ላድርግ ሳይሆን ከኔ በኩል ምን ላድርግ ብለህ ራስህን እንድትጠይቅና ለችግሩ ትክክለኛውን መንስኤ እንድታውቅ ነው፡፡ መቼም ወደህና ፈቅደህ ያለህበትንና ያሳለፍከውን ሁኔታ ተረድታ ነው ያገባችህ የሚል እምነት አለን፡፡
ቃል ኪዳናችሁን አክብሩ
በየትኛውም ስርዓት ተጋቡ ብቻ በሰርጋችሁ ዕለት አንዳችሁ ለሌላኛው ቃል መግባታችሁ አይቀርም፡፡ በተለይ ደግሞ መንፈሳዊ ጋብቻ ሲሆን በእግዚአብር በጉባኤ መካከል የገባችሁትን ቃል ማስታወስ ነው፡፡ ጋብቻ ውስጥ መጎርበጥ ቢኖርም፣ መውደቅ መነሳት ቢፈጠርም ቃል ኪዳናችሁን ማሰብ ተገቢ ይመስለናል፡፡ ስለዚህ ከመጋባታችሁ በፊት ስለልጁ ጉዳይ ከተነጋገራችሁ እንዴት ልታሳድጉት ነበር ያሰባችሁት? ልትረዱትስ ተነጋግራችኋል? የተባባላችሁትን እናንተው ስለምታውቁ ያንን ኃላፊነት በተሰማው መንገድ መጠበቅ ነው፡፡
ልጅህን በፊት አልረዳውም፤ ምንም አላደርግለትም ብለህ ነግረኻት ከሆነና አያቶቹና እናቱ ይበቁታል ብለህ ወደ ትዳር ከገባህ ያንን ማክበር ነው፡፡ እርሷም ምንም ችግር የለም፤ ዋናው ፍቅሩ ነው በውጪ ሆኖ ልትረዳው ትችላለህ ብላህ ከነበረ ቃሏን መጠበቅ ይኖርባታል፡፡ ጠቅልለህ ቤትህ ካስገባሃት ወይም ጠቅላላ ቤት ከገባች በኋላ ባህሪያችሁንና የገባችሁትን ቃል አጥፋችሁ ከሆነ አግባብ ይመሰለንም፡፡
ደግማችሁ በግልፅ ተነጋገሩ
ከላይ የጠቀስነው ነገር ሊሰራ መስሎ ካልታያችሁና፣ ቃላችሁን ማጠፍ ከጀመራችሁ ማድረግ የሚገባችሁ ነገር በጉዳዩ ላይ መነጋገር ነው፡፡ በስሜት ተገፋፍታችሁና የነበራችሁበት ወቅታዊ ፍቅር አርቃችሁ እንዳትመለከቱ ካደረጋችሁ ደግማችሁ በጉዳዩ ላይ በግልፅ መወያየት ነው፡፡ መቼም እንደ ባለአዕምሮ ሰው አትርዳው አትልህም፤ አንተም እርሷ እንዳለችው ከሴት ልጅህ በማስበለጥ እየረዳኸው ካለ አግባብ ነው ለማለት አንደፍርም፡፡ ሁለቱም ልጆችህ ቢሆኑም በአንድ አይነት ማየት አለብኝ ብለህ መሰብ ግን የዋህነት ነው የሚመስለን፡፡ ለዚህም የአብርሃምን ታሪክ ማስታወሱ የምንልህ የበለጠ ይገባሃል የሚል እምነት አለን፡፡
አብርሃም ሚስቱ ሳራ መውለድ ባልቻለችበት ወቅት አገልጋይ ከሆነቻት አጋር ጋር እንዲተኛ ፈቀደችለት፡፡ ኢስማኤል የተባለ ልጅም አገኘ፡፡ ሳራም በእግዚአብሔር ዘንድ መጎብኘትዋ በደረሰ ጊዜ ፀነሰች፣ ይስሃቅንም ወለደች፡፡ ይሁንና ኢስማኤል ከይስሃቅ ጋር እኩል በአባቱ ቤት ያድግ ዘንድና ያለውንም ይካፈል ዘንድ ሳራ ደስተኛ አለነበረችም፡፡ አጋርን ከነልጁ ያሰናብታቸው ዘንድ ጠየቀችው፡፡ አብርሃምም የተባለውን አደረገ፡፡ አብርሃም ልጁን ኢስማኤልን ጠልቶት ይመስልሃል ከአጋር ጋር እንዲሄድ ያደረገው? ከቃልኪዳን ሚስቱ ከሳራ ሀሳብ ጋር በመተባበር አይመስልህምን? የተስፋውን ልጅ ይስሃቅን የመረጠው ዝም ብሎ ይመስልሃልን? አየህ በቃል ኪዳን የተገኘ ለጅና በመወስለት የመጣ አንድ አይደለም፡፡ ከዚህ የምንማረው ነገር ያለ ይመስለናል፡፡
ባለቤትህን አማክር
ሌላው ስለትዳር ሲታሰብ ሁሌ መዘንጋት የሌለብህ ነገር ከጋብቻ በኋላ የኔ የሚባል ነገር የለም፡፡ የእኛ የሚባል አጀንዳ ነው የሚመጣው፡፡ ያንተ ጉዳይ የርሷ ነው፤ የርሷም ደግሞ የአንተ ነው፡፡ ለልጅህ የምታወጣውን ጊዜና ገንዘብ ከባለቤትህ ጋር በመመካከር ሊሆን ይገባል፡፡ አንድ ነገር ማሰብ ያለብህ ልጅህን መርዳትህ ወንጀል ባይሆንም፤ ሄደህ መጎብኘትህንም ማንም ባይጠላውም መርሳት የሌለብህ ነገር ልህንን ልታይ ስትሄድ የቀድሞ ጓደኛህንም የማግኘቱ አጋጣሚ የሰፋ መሆኑ ነው፡፡ ይህ ደግሞ ከባለቤትህ ፈቃድና እውቅና ውጪ ሲዘወተር ሌላ ነገር እንድትጠረጥር ያደርጋታል፡፡ ሰው ነችና ደግሞ ቢሰማት ሊገርምህ አይገባም፡፡ በትዳራችሁ ላይ የወንድ ልጃችሁ ጉዳይ እስከገባ ድረስ የርሱን ነገር ተይው ልትላት አይገባም፡፡ ልጁ እኮ እያነጋገራችሁ ነው? ልጁ እኮ ላለመግባባታችሁ መንስኤ እየሆነ ነው፡፡ የራሳችሁን ኑሮ ለመኖር ከፈለጋችሁ በጋራ ጉዳያችሁ ብቻ ነው ልታተኩሩ የሚገባው፡፡ ግን እውነታውን እንይ ካልን አይደለም ከአብራካችን ስለወጡት ልጆች ከሌላውም ጋር ቢሆን መገናኘታችን፣ መነካካታችን የግድ ይላል፡፡ ደሴት ሆነን ልንኖር አልተጠራንም፡፡ ስለዚህ የርሱን ነገር ትተሽ የራሳችንን ኑሮ ብቻ እንኑር አትበላት፡፡ አማክራት፡፡ ነገሩን በመሸሽ ዘላቂ የሆነ መፍትሄ ልናመጣ አንችልም፡፡ ነገሩን አዳፍነነው በአፈር ሸፋፍነነው ላሁኑ በዚሁ ብናልፍ ዝናብ ሲዘንብበትና ነፋስ ሲመጣበት አግጦ መውጣቱ አይቀርም፡፡
- የእግዚአብሔርን ቃል አጥኑ
ከላይ ያነሳናቸው ጠቃሚ ምክሮች ቢረዷችሁም በትዳራችሁ ዘላቂ የሆነ ውጤት እንድታመጡ ግን ከናፈቃችሁ ሁልጊዜ የእግዚአብሔርን ቃል ማሰብ ነው፡፡ ክርስቲያን እንደመሆናችሁ ለማሰብ ከዛም ባለፈ የሚታየ ለውጥ በህይወታችሁ ለማምጣት ቃሉን ማጥናት መልካም ነው እንላለን፡፡ ቃሉ ህይወት አለው፤ መዳን በርሱ በኩል ብቻ እንደሆነ ነው የሚናገረው፡፡ አየህ ቃሉ ውስጥህ ሲገባ ተመሳሳይ ስሜት አይኖርህም፡፡ ስታጠፋ ይወቅስሃል፤ ስታዝን ያፅናናሃል፤ ስትደክም ያበረታሃል፤ ከመንገድ ወጣ ትስትልም ወደ ቀናው ጎዳና ይመልስሃል፡፡
ስለዚህ ይህን ማድረግ በህይወታችሁ ስትለማመዱ እናንተ ስላላችሁ ወይም ልጆቻችሁን ስለተንከባከባችሁ ብቻ በስርዓት ያድጋሉ ማለት እንዳልሆነ ትረዳላችሁ፡፡ አብርሃም ልጁን ከአጋር ጋር ሲሰድ እግዚአብሔር ዝም አላላቸውም፡፡ በሚያስፈልጋቸው ነገር ሁሉ ይረዳቸው ነበር፡፡ ስለዚህ ቃሉ ሲገባችሁ ልጅህ የመከራከሪያ አጀንዳ፤ ላለመግባባታችሁ መንስኤ አይሆንም፡፡ ያላችሁን ነገር ለአምላካችሁ አሳልፋችሁ መስጠት ትጀምራላችሁ፡፡ የሰጣችሁትንም ይጠብቅና ያሳድግ ዘንድ እርሱ ታማኝ ስለሆነ ቃሉን ዕለት ዕለት ለማጥናት ሞክሩ፡፡
እንግዲህ ይበጃችኋል ብለን ያሰብነውን በተለያየ አቅጣጫ ለመጠቆም ሞከርን፡፡ ለውጥና ፍተሻ ከራስ ነውና የሚጀምረው ስራህን በራስህ እንድትጀምር፤ እንድትመካከሩ፤ በግልፅ እንድትወያዩ ቃል ኪዳናችሁንም በማክበር የአምላካችሁን ቃል ተግባራዊ እንድታደርጉ አውግተናል፡፡ እኛ እንግዲህ መጠቆምና አቅጣጫ ማሳየት እንጂ ተሳታፊዎቹ እናንተው የችግሩ ባለቤቶች ስለሆናችሁ ከዚህ በላይ ልንሄድ አንችልም፡፡ ሁሉን የሚችለው አንድዬ እርሱው ይርዳችሁ፡፡ ለዛሬ አበቃን፡፡ ቸር እንሰንብት!

መንግስት በአዲስ አበባ ኤርፖርት ሁለት ተቀጣጣይ ሲሊንደሮች አገኘሁ አለ

$
0
0

addis ababa airport
(ዘ-ሐበሻ) የኢትዮጵያ መንግስት የደህነነት መስሪያ ቤት ባለፈው እሁድ ኦገስት 11 ቀን 2013 በአዲስ አበባ በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሁለት ተቀጣጣይ ባዕድ እቃ የያዙ ሁለት ሲሊንደሮች መገኘታቸውን አስታወቀ። የኢትዮጵያ መንግስት የብሔራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎትና የፌዴራል ፖሊስ የጋራ የፀረ ሽብር ግብረ ሃይል በመንግስት ሚዲያዎች ላይ ባሰራጩት ዜና እንደገለጹት ሲሊንደሮቹ በአውሮፕላን ማረፊያው የመንገደኞች መነሻ አከባቢ እንደሚገኙ ጥቆማ ያደረሱት የፅዳት ሰራተኞች ናቸው ብሏል።

የመንግስት ሚድያዎች እንደዘገቡት የፈንጂ አምካኝ ባለሙያዎች ሲሊንደሮቹ ተቀጣጣይና በቀላሉ በእሳት በመያያዝ ጉዳት ማድረስ የሚችሉ መሆናቸውን መረጋገጡን እና ሲሊንደሮቹ የያዙት ተቀጣጣይ ንጥረ ነገር ባህሪም እየተጣራ ነው።

መንግስት ይህን ተቀጣጣይ ሲሊንደር በአዲስ አበባ ኤርፖርት ማን እንዳስቀመጠው ባይገልጽም አንዳንድ የፖለቲካ ተንታኞች ግን መንግስት ከዚህ ቀደም ካለው ባህሪ አኳያ ራሱ ሲሊንደሩን አስቀመጦ በአንድ ድርጅት ላይ ለማላከክ ነው ይላሉ። አስተያየት ሰጪዎቹ ጨምረውም ከዚህ ቀደም መንግስት ኦነግን ለማስጠላት የትግራይ ሆቴልን ጨምሮ የተለያዩ ቦታዎችን በማፈንዳት ኦነግን በአሸባሪነት መፈረጁን፣ ይህን ሆቴል አፈነዱ ተብለው በቴሌቭዥን የቀረቡት ሰዎች ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ በሌላ ጊዜ ደቡብ አፍሪካ ውስጥ መታየቸውን፤ በቅንጅት ላይ በኋላም በግንቦት 7 ላይም አኬልዳማ ድራማን ለመሥራት የጠቀመውን በማስታወስ አሁን በአዲስ አበባ ኤርፖርት ተቀመጠ የተባለውን ተቀጣጣይ ሲሊንደር ከመንግስት ውጭ ሌላ ሰው ያደርገዋል የሚል እምነት እንደሌላቸው አስታወቀዋል።

ሌሎች አስተያየት ሰጪዎችም ይህን ዜና የመንግስት ድራማ ያደርጉታል። መንግስት በሃገር ቤት ተቃውሞ ሲበዛበት እንዲህ ያሉ ተልካሻ ምክንያቶችን በማቅረብ ሰዎችን በሽብርተኝነት ለመክሰስ የሚጠቀምበት ዘዴ ነው ሲሉ መንግስት የበተነውን የተቀጣጣይ ሲሊንደር በአዲስ አበባ ቦሌ አየር መረፊያ የመገኘቱን ዜና ያጣጥሉታል።

“ኢሕአዴግ ፖለቲካውን የሚመራው በዕዝ ነው እንጂ በሃሳብ የበላይነት አይደለም”–አቶ ሃብታሙ አያሌው

$
0
0

አቶ ሃብታሙ አያሌው የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ብሄራዊ ምክር ቤት አባልና ምክትል የህዝብ ግኑኝነት ሃላፊ ነው፡፡ወደ ፖለቲካው ዓለም የገባው በኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤት በማስተማር አገልግሎት ተጠምዶ ሳለ አንድ ችግር ይነሳና ቤተክርስቲያኑ በሚገኝበት ቀበሌ በአስተዳደሩ ይጠራል፡፡በቀበሌው የተገኘው ሃብታሙ የተፈጠረውን ችግር ያብራራበት መንገድ በአሁኑ ሰዓት ከፍተኛ የኢህአዴግ ባለስልጣን የሆኑ ግለሰብን ይማርካል፡፡ግለሰቡ ከስብሰባው በኋላ ሃብታሙን በመቅረብ በቅርቡ የሚመሰረት አንድ ነጻ የወጣት ማህበር ስላለ በዚያ የምስረታ በዓል ላይ እንዲገኝ ያግባባዋል፡፡መንፈሳዊው ሃብታሙም በህይወቱ ለመጀመሪያ ጊዜ አጀንዳውን መንፈሳዊ ህይወት ባላደረገ ማህበር ምስረታ ላይ ይታደማል፣በዚያው ዕለትም ስሙ ተጠቁሞ ይመረጣል፡፡ ዳዊት ሰለሞን ከገዢው ፓርቲ ጋር በቅርበት በመስራት በአሁኑ ሰዓት ገዢውን ፓርቲ እየታገለ የሚገኘውን ሃብታሙን በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዩች አነጋግሮታል፡፡
habtamu
ላይፍ — አምላክን ከማገልገል ህይወት ወደ ፖለቲካ የመምጣት ውሳኔን ማሳለፍ ምን ያህል አስቸጋሪ ነበር ?
ሃብታሙ—ፖለቲካ እውቀት ብቻ ሳይሆን ስብዕናን ይፈልጋል፡፡ፖለቲካን ከሃይማኖት የሚለየው ምድራዊ መሆኑ ነው፡፡ሃይማኖት ለመንፈሳዊ በረከት የምትሰራበት ከሞት በኋላ ስላለ ህይወት በአብዛኛው የምትኖረው ነው፡፡ሃይማኖት የሚፈልገው ስብዕና ይህ ስብዕና ውሸትን መጠየፍ፣እውነትን መከተልና ለተበደለው መጮህን የሚይዝ ነው፡፡ፖለቲካውም ይህንን ይፈልጋል፡፡እርግጥ ነው ፖለቲካው ከስብዕና በተጨማሪ እውቀትን ይፈልጋል፡፡ነገር ግን ይህንን ክፍተት መሙላት ይቻላል፡፡በሃይማኖት ቤቶች ፖለቲካውን የአለማዊ ሰው መገለጫ በማድረግ የመመልከት አዝማሚያ አለ ይህ ግን መለወጥ መቻል አለበት፡፡ፈሪሃ እግዚአብሄር ያላቸው ሰዎች ወደ ፖለቲካው መምጣት እንደሚገባቸው አምናለሁ፡፡
ላይፍ — ወደ ማህበሩ ከመጣህና በአመራርነት ከተመረጥክ በኋላ ምን ተፈጠረ ?
ሃብታሙ — የአዲስ አበባ ፎረም ሲመሰረት የሄድኩት ከአንድ ጓደኞዬ ጋር ነበር፡፡አንድ የማላውቀው ሰው ስሜን ጠርቶ በአመራርነት እንድመረጥ ጠቆመኝ፡፡እኔ ግን ምንም ልምድ እንደሌለኝ በመግለጽ ጥቆማውን ለመቃውም ሞከርኩ፡፡መጀመሪያ የጠቆመኝን ሰው ከአመታት በኋላ አግኝቼው ካድሬዎች እኔን እንዲጠቁም ስላዘዙት እንደጠቆመኝ ነግሮኛል፡፡ጥቆማውን እንድቀበል በዚያ የነበሩ ሰዎች ግፊት ስላሳደሩብኝም ተመረጥኩ፡፡ከዚያም የማህበሩ የክፍለ ከተማው ምክትል ሰብሳቢ ሆኚ ተመረጥኩ ብዙም ሳይቆይ የአዲስ አበባ የፎረም ሰብሳቢ ተደረግኩ፡፡በመለጠቅም ዘጠኝ አደረጃጀቶች ማለትም የአዲስ አበባ ወጣት ፎረም፣የኢህአዴግ ሊግና ሌሎች ማህበራት የመሰረቱት ፌደሬሽን ፕሬዘዳንት ሆኜ ተመረጥኩ፡፡ከመንግስት በደረሰኝ ደብዳቤም የሕዝብ ግኑኝነት ሆኜ እንድሰራ ተደረግኩ፡፡ነገር ግን በዚህ መንገድ ከሁለት አመት በላይ መቀጠል አልቻልኩም፡፡
ላይፍ — ምንድን ነው በዚህ መንገድ እንዳትቀጥል ያደረገህ?
ሃብታሙ — ፌደሬሽኑም ሆነ የወጣቶች ፎረም ሲመሰረት ኢህአዴግ በነጻነታቸው ዙሪያ ምንም ጥያቄ አላነሳም፡፡ነገር ግን ቀስ በቀስ ማህበራቱን በካድሬ ትዕዛዝ ለመምራት መንቀሳቀስ ተጀመረ፡፡በዚህ ላይ ማህበራቱ መቶ በመቶ በጀታቸውን የሚያኙት በመንግሰት መሆኑም በነጻነታቸው ዙሪያ ጥያቄ ያስነሳል፡፡የሲቪክ ማህበራት በነጻነት እንዲንቀሳቀሱ የሚያደርጋቸው የህግ ድንጋጌ ቢኖርም መሬት ላይ ያለው እውነታ ግን ከዚህ ወጣ ያለ ነው፡፡እኔም ሆንኩ ሌሎች ወጣቶች አንዲህ መሆኑን በግልጽ ስንቃወም ቆይተናል፡፡በመጨረሻ ግን የነበረውን ነገር በውስጥ ትግል መለወጥ እንደማይቻል ስገነዘብ ለቅቄ ወጥቻለሁ፡፡
ላይፍ — በፎረምና በፌደሬሽኑ ውስጥ የነበረህን ከፍተኛ ሃላፊነት ከለቀቅክ በኋላ ባለ ራዕይ ወጣቶች ማህበርን መስርተሃል፡፡ማህበሩን ለመመስረት መነሻ የሆነ ምክንያት ምንድን ነው?
ሃብታሙ — አንድ ነገር ማስታወስ እፈልጋለሁ በሃላፊነት በነበርኩባቸው ወቅቶች ዘወትር ይነሱ የነበሩ ክርክሮች ‹‹አንተ ከኢህአዴግ ጋር እየሰራህ እንዴት ማህበራት ነጻ መሆን አለባቸው ትላለህ? ይህንን የምትለው በኢህአዴግ ስለማታምን ነው ይሉኝ ነበር፡፡ሃሳቤን ለማስለወጥም ብዙዎች ሽምግልና እስከመቀመጥ ደርሰው ነበር፡፡ባለ ራዕይ ማህበርን ለመመስረት ያበቃን በኢትዩጵያ ውስጥ ለማንም ወገንተኛ ያልሆነ ሲቪክ ማህበር መኖር አለበት የሚል አቋም ያለን ወጣቶች በተለያዩ አጋጣሚዎች መገናኘት በመቻላችን ነው፡፡
ላይፍ — ከገዢው ፓርቲ በመለየትና ታገኘው የነበረን ጥቅማ ጥቅም በመተው ‹‹በቃኝ ››የሚል ውሳኔን መሳለፍ ከባድ ምርጫ አልነበረም ?
ሃብታሙ — ኢህአዴግ ቤት እያለሁ ወፍራም ደሞዝ ነበረኝ ፣መኪና ተመድቦልኝ የተለያዩ አበሎች ይከፈሉኝ ነበር፡፡ስልጣን በራሱ የሚፈጥረው ወዳጅም አለ፡፡በሆድ ለሚያስብ ሰው እኔ ከነበርኩበት ሁኔታ መውጣት አስቸጋሪ ነው፡፡እኔ ግን ህሊናዬ ላልፈቀደው ነገር በሆዴ እየተደለልኩ መኖር የምችል ሰው ባለመሆኔ የምመራውን ህይወት በህሊና ለመለወጥ አልተቸገርኩም፡፡ በርካታ ዜጎች በችግር እየተቆራመዱ ለስደት ሲጋለጡ እያየሁ እኔን ተመችቶኛልና ስለ ሌላው ምንም አያገባኝም ለማለት አልደፈርኩም፡፡ኢህአዴግ ለተቃዋሚዎች ምን እንደሚያስብም አውቃለሁ ነገር ግን ያንን ኢህአዴግ ለተቃዋሚዎቹ ያዘጋጀውን ጽዋ መጠጣት ለእኔ ክብር እንደሆነ በማሰቤም በቃኝ ለማለት እንዳልቸገር አድርጎኛል፡፡
ላይፍ — ወደ ተቃዋሚው ጎራ ስትመጣ በዚያ ያሉ ሰዎች ከኢህአዴግ ጋር የነበረኝን ቆይታ ስለሚያውቁ ሊያምኑኝ አይችሉም የሚል ስጋት አላደረብህም ?
ሃብታሙ — በእርግጥ የአገራችን የፖለቲካ አስተሳሰብ የሚገኝበት ደረጃ በጣም ዝቅተኛ በመሆኑ ነገሮች አስቸጋሪ ይሆናሉ፡፡ከገዢው ፓርቲም ሆነ ከተቃዋሚነት ወደ ኢህአዴግነት ለሚሄዱ ሰዎች ሁኔታዎች ቀላል አይሆኑም፡፡በሁሉም ወገን በጥርጣሬ የመታየት ዕድል ሰፊ ነው፡፡በእኛ አገር የአንድ ፓርቲ አባል ከሆንክ እስከ ዕለተ ሞትህ የዛ ፓርቲ ወይም አስተሳሰብ አካል እንደሆንክ እንደምትቀጥል ይጠበቃል፡፡ለምሳሌ ኢህአዴግ ቤት ሃሳብ በመሸጥ መቀጠል አይቻልም፡፡በኢህአዴግ ውስጥ ኢህአዴግን በሃሳብ መታገል አይቻልም፡፡ፖለቲካውን የሚመራው በዕዝ ነው እንጂ በሃሳብ የበላይነት አይደለም፡፡በእንዲህ አይነት በዕዝ ሰንሰለት በሚመራ ድርጅት ውስጥ መቆየት ደግሞ የማይታሰብ በመሆኑ የተቃውሞውን ጎራ ለመቀላቀል አብቅቶኛል፡፡
ላይፍ — ኢህአዴግ ቤት በነበርክባቸው ወቅቶች ያፈራሃቸው ጓደኞች አሁን የቀድሞውን መስመር ስትቃወም ሲመለከቱ ምን ይሉሃል?
ሃብታሙ — እኔ ወደ ህዝብ የምሄደው እኔን ብቻ አድምጠኝ ለማለት አይደለም፡፡በግሌ በፊትም ይሁን በቀጣይ የሚኖሩኝ ወይም የነበሩኝ ጓደኞች አቋም እንዳለው ሰው እንዲያስቡኝ እፈልጋለሁ፡፡እስካሁንም ያለው ነገር ይህ ነው፡፡ኢህአዴግን የተውኩትና አንድነትን የተቀላቀልኩትም የአቋም ልዩነት ነው፡፡በአንድነት ውስጥ ዲሞክራሲያዊ ሃይሎችን በማግኘቴ ለውጥ እናመጣለን የሚል እምነት በመሰነቄ እየታገል እገኛለሁ፡፡
ላይፍ — ተቃዋሚዎችን በመቀላቀልህና ኢህአዴግን በመታገልህ የደረሰብህ ችግር የለም?
ሃብታሙ — እውነቱን ለመናገር ችግር የለም ማለት አይቻልም፡፡ችግር ብቻ ሳይሆን የተከተልኩት መስመር የህይወት መስዋዕትነትን ጭምር የሚጠይቅ መሆኑን አውቃለሁ፡፡ገዢው ፓርቲ የምበላውን አጥቼ እንድንበረከክ በመፈለግ ያሸነፍኳቸውን ጨረታዎች እንኳን እንዳላገኝና በዜግነቴ ሰርቼ እንዳልኖር እያደረገ ይገኛል፡፡ይህንን የሚያደርገው ግን ኢትዩጵያዊያንን ካለማወቅ በመሆኑ አልገረምም፡፡ኢትዩጵያዊ ክብሩን የሚጠብቅና ለፍርፋሬ ሲል ማተቡን የማይበጥስ ነው፡፡
ላይፍ — ወደ ፓርቲው ህዝባዊ ንቅናቄ እንምጣ ፣አንድነት እያደረገው የሚገኘው ሰላማዊ ሰልፍና ህዝባዊ ስብሰባ ሌላ ፓርቲ በቅርቡ ማድረጉን ተከትሎ በኩረጃ መልክ እየተደረገ የሚገኝ ነው ወይስ በጥናት ነው?
ሃብታሙ — ማንንም አልኮረጅንም ፣እያደረግነው የምንገኘው እንቅስቃሴ በስትራቴጂክ መጽሀፋችን ቀደም ብሎ የሰፈረ ነው፡፡ስለዚህ እየሰራን የምንገኘው በእቅዳችን መሰረት ነው፡፡ዞሮ ዞሮ ማንም አደረገው ማን የተደረገው ነገር የአገሪቱን ፖለቲካ አንድ እርምጃ ከገፋው ጥቅሙ የሁላችን በመሆኑ ጀማሪው እከሌ ነው አይደለም የሚለው ነገር አስጨናቂ አይሆንም፡፡አንድነት በዚህች አገር ለውጥ እንዲመጣ ያቅማቸውን ላበረከቱና እያበረከቱ ለሚገኙ ሁሉ እውቅና ይሰጣል፡፡በደፈናው ባለፉት አርባ አመታት ምንም አስተዋእጾ አልተበረከተም የሚል ድምዳሜ ላይ ፓርቲያችን አይደርስም፡፡እነ ፕሮፌሰር አስራትን ጨምሮ በዙ ሺህዎች ለዚህች አገር የህይወት መስዋዕትነትን ከፍለዋል፡፡ለዚህ እውቅና መቸር ይገባናል፡፡እውንት ለመናገር ሰላማዊ ሰልፍ በማድረግ የህዝብን አይን የገፈፉት በታዲዩስ ታንቱ የሚመራው የአገር ወዳድ ኢትዩጵያዊያን ማህበር ነው፡፡ለግራዚያኒ ሃውልት እንዲቆምለት መወሰኑን በመቃወም ሰልፍ እንዲጠራ ያነሳሱት እን ታዲዩስ ናቸው፡፡ለዚህ ተገቢውን አክብሮት ሊቸራቸው የሚገባ ቢሆንም ሌሎች መድረኩን በመቆጣጠር የማይገባቸውን ውዳሴ ለመሸመት ተንቀሳቅሰውበታል፡፡በሃይል በተቀለበሰው ሰላማዊ ሰልፍ ከአርባ በላይ አባላቶቹ የታሰሩበት ባለ ራዕይ ማህበርም ከሰላማዊ ሰልፉ አዘጋጆች አንዱ ነበር፡፡
ላይፍ — መስከረም አምስት አንድነት በአዲስ አበባ ለማድረግ ያቀደውን ሰልፍ የአንድ ፓርቲ ሊቀመንበር‹‹አንድነት ይህንን ሰልፍ የጠራው እነ አንዷለም የታሰሩበትን ቀን ለማክበር ነው፣እኛ ግን ሰልፍ የምንወጣው እነ አንዷለም እንዲፈቱ ነው ››ብለዋል፡፡እስኪ የሰልፉን አላማ ንገረኝ?
ሃብታሙ — (ረዥም ሳቅ)ፖለቲካ እንግዲህ እንደተርጓሚው ነው፡፡ይህ አስተሳሰብ ተገቢ ባይሆንም አስተሳሰቡ ግን የመደመጥ ዕድል ማግኘት እንደሚገባው ይሰማኛል፡፡ግለሰቡ እንዲህ የሚያስቡ ከሆነ ማድረግ የሚጠበቅብን አስተሳሰባቸውን እንዲያሳድጉ መርዳት ነው፡፡ለኢትዩጵያ ፖለቲካ የሚጠቅም አስተሳሰብ ባለመሆኑም የራስን ገጽታ ለመገንባት የሌሎችን መልክ ማቆሸሽ ቅንነት የጎደለው ድርጊት ነው፡፡በግሌ ይህንን የተናገሩት አቶይልቃል አንድ ሰልፍ በመጥራት ስማቸው በየቦታው መነሳት በመጀመሩ ስካር ውስጥ የገቡ ይመስለኛል፡፡ኢትዩጵያ ውስጥ ፓርቲ አለ ብዬ አላምንም ማለትና በመድረክና በአንድነት ውስጥ ለጊዜው ተፈጠረ የተባለውን ልዮነት በማራገብ እየተባሉ ነው ማለት እንዴት አይነት ፖለቲካ እንደሆነ አይገባኝም፡፡እዚህ አገር ፓርቲ የለም ብሎ የሚያምን ፓርቲ በምን ስሌት ከሰላሳ ሶስት ፓርቲዎች ጋር በትብብር ለመስራት መፈራረሙ አስገራሚ ነው፡፡የሉም ካሉ እንዴት አብረው ሊሰሩ ፈረሙ፡፡ኢህአዴግም እኮ የሚለው ይህንኑ ነው አኔ ከሌለው ይህች አገር ትጠፋለች የሚለው ፓርቲዎች አሉ በማለት ስለማያምን ነው፡፡ይህንን ጥያቄ ስላነሳህው ልመልሰው እንጂ ዝሆን የሚያባርር ለወፍ ድንጋይ አይወረውርም፡፡እኛን እንቅልፍ የሚነሳን የአገራችን ጉዳይ ነው፡፡እንዴት ይህንን አምባገነን ስርዓት እንለውጣለን የሚለው ያስጨንቀናል እንጂ የቃላት እሰጥ ገባ ውስጥ በመግባት ጊዜ ማባከን አንፈልግም፡፡የኢትዮጵያ ህዝብ ግን ፍርዱን እንደሚሰጥ በግሌ አምናለሁ፡፡
ላይፍ –ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ በቅርቡ አንዳንድ የፖለቲካ ድርጅቶች በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ በመግባት ርካሽ የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት እየተሯሯጡ ነው፡፡እነዚህ የፖለቲካ ሃይሎች ከዚህ ድርጊታቸው ካልተቆጠቡ እርምጃ እንወስዳለን በማለት ዝተዋል፡፡ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስም ባይጠሩም ይህ ማስጠንቀቂያ በዋናነት አንድነትን የሚመለከት አይመስልህም?
ሃብታሙ –ኢህአዴግ ሲጨነቅ የሚናገራቸው ነገሮች ፍጹም የማይገናኙ ናቸው፡፡አቶ ሃይለማርያም በምንና እንዴት መታገል እንደሚገባን ሊያዙን ወይም የምንታገልባቸውን ነገሮች እየቆነጠሩ ሊሰጡን አይችሉም፡፡እኛንና እሳቸውን የሚዳኘን የአገሪቱ ህግ ነው፡፡ስልጣን ስለያዙ ለህገ መንግስቱ ቅርብ ናቸው አያስብልም፡፡እኛም የህገ መንግስት ጥሰት እየተፈጸመ ነው በማለት እየከሰስን ነው፡፡ነጻ የፍትህ ስርዓት ቢኖር ማን ህጉን እንደጣሰም በግልጽ ይታይ ነበር፡፡ለማንኛውም ግን ሙስሊም ወገኖቻችን ያነሱት ጥያቄ የሃይል ሳይሆን ስልጡን ምላሽ እንዲሰጠው ከመጠየቅ ወደ ኋላ አንልም፡፡በማስፈራሪያው በመሸማቀቅ ለወገኖቻችን አጋርነታችንን ከማሳየት እንደማንቦዝንም መታወቅ አለበት፡፡

ሰላም ምንድነው? (ታደሰ ብሩ)

$
0
0

Ethiopian Flag
ከታደሰ ብሩ

1. መንደርደሪያ

የወያኔ ሰዎች ጋር የፓለቲካ ሙግት መሰል ነገር ከገጠማቸው ውይይቱን ያለ ጥርጥር የሚረቱበት ወደሚመስላቸው ወደ “ሰላም” ጉዳይ ይስቡታል። ከዚያም አገራችን ለዘመናት ሰላም የራቃት የነበረ መሆኑን ያስቷውሷችሁና “እድሜ ለኢሕአዴግ ይኸው የሰላም አየር እየተነፈስን ነው” ይሏችኋል። ንግግራቸውን የመቀጠል እድል ካገኙ መረር ብለው “ነገር ግን ፀረ-ሰላም ኃይሎች አልተኙልንም። በሰሜን፣ በምሥራቅ፣ በአገር ውስጥ፣ በዲያስፓራ ….” እያሉ የፀረ-ሰላም ኃይሎች ረዥም ዝርዝር ያቀርቡላችኋል።

የእርስዎ ጭንቅላት “ድልድይ እያፈረሰ አዲስ አበባ የገባ ድርጅት ስለ ሰላም ለመስበክና ሌሎቹን በአሸባሪነት ለመክሰስ እንዴት ልብ አገኘ?” በሚል ጥያቄ ተጠምዶ ሊሆን ይችላል።

ወያኔ ወዳጅዎ ግን እርቆ ሄዷል “አንተም የፀረ-ሰላም ኃይሎች መጠቀሚያ ሆነሃል፤ ከዚህ ተግባርህ ብትታቀብ ይሻልሃል። ዓለም ዓቀፍ መስፈርት ያሟላ የማያፈናፍን የፀረ-ሽብር ሕግ አለን” …. እያለ ይቀጥላል። በሰላም ስም ሰላምዎን አድፍርሶት ይውላል።

በወያኔ ቴሌቪዥንና ራድዮ የሚተላለፉ ቃላት ብዛት ስታትስቲክስ ቢኖር ኖሮ “ሰላማችን” አንደኛ ይወጣ ነበር ይሆናል። ምናልባት አንደኝነት ካጣ ደግሞ “በልማታችን” ተበልጦ ሁለተኛ ይወጣ ነበር።

በሰላም ስም ማጭበርበር የተጀመረው ዛሬ አይደለም። አዶልፍ ሂትለር የቼክ ሪፑብሊክን ከመውረሩ በፊት አስገራሚ የሰላም ጥሪ አድርጎ ነበር፤ ሩሲያን ከመወረሩ በፊት ደግሞ የሰላም ውል ተፈራርሞ ነበር። በአንድ ወቅት የሶማሊያው ዚያድ ባሬ መቋድሾ ውስጥ ታላቅ የሰላም ሰልፍ መርቷል። ከዩጋንዳው ማርሻል ኢዲአሚን ዳዳ በርካታ ኒሻኖች አንዱ “የእንግሊዝ የሰላም ኒሻን” የሚባለው ነው። ሆኖም ግን ከላይ የተጠቀሱ ሰዎች የሚታወቁት በሰላምተኝነታቸው አይደለም። ልክ እንደእነሱ ሁሉ የኛዎቹም ወያኔዎች ለሰላም ከእኔ ወዲያ ላሳር ቢሉ አይግረመን።

ለመሆኑ “ሰላም” ምንድነው?

እኔ ይህን ይህንን ጥያቄ ለራሴ ካነሳሁ ከሀያ ዓመታት በላይ ተቆጥረዋል። የዛሬ 23 ዓመታት ገደማ ከፃፍኩት የተማሪነት ጊዜዬ ረዥም ግጥም ውስጥ ሶስት አንጓዎችን ብቻ ልጋብዝዎት።

ሰላም

ሰላም !!!!!

አንዱ ለፀሎተ ውዳሴው

ሌላው ለፍሬከርስኪ ጉባዬው

ደሞ ሌላው … ለነገር ማጣፈጫ

ለፈራጅ አዕምሮ ማቀጨጫ

ለአምባ-ገነን ሥልጣን መጨበጫ

ስንቱ ለከንቱ በከንቱ ያነሳሻል

አንስቶ …. ክቦ … ክቦ … ይጥልሻል

ከልጅነቴ ጀምሮ የምሰማት

ልጅ፣ ሽማግሌው የሚወዳት

የማትለወጥ ጣፋጭ ቃል

“ሰላም” የምትባል

ትርጉሟ ጠፍቶብኛል

እባካችሁ የገባችሁ አስረዱኝ

ሰላም ምንድን ናት ንገሩኝ።

በኢራን፣ በኢራቅ፣ በጋዛ ሠርጥ፣ ካምፑቺያ

ኒኳራጓ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ናምቢያ

በሰሜን ሕንድ ፣ በአፍጋኒስታን፣ በኢትዮጵያ

ያለሽ እናት፣ ያለህ ወገን

ያለህ ሕፃን

ሰላም ምን ማለት ነው ንገረኝ

ዋጋዋ ምን ያህል ነው አስረዳኝ

አንተም የአውሮፓው ሰው ንገረኝ

ስንት ነብስ፤ ስንት ሀብት፤ ስንት ጥይት ነው

ሰላምን ገዝቶ ለማቆየት ‘ሚከፈለው?

ሕዳር 1982

2. ሰላም ምን ማለት ነው?

ከላይ ቅንጫቢውን ብቻ ያቀረብኩት ረዥም መራር ግጥም ከፃፍኩ 23 ዓመታት ተቆጥረዋል። ከዚያ ወዲህ የፓለቲካ ሥርዓት ተቀይሯልጥያቄው ግን ከያኔው ይበልጥ ዛሬ አንገብጋቢ ሆኗል።

እውን ሰላም ምን ማለት ነው?

በጣም አጭርና ግልጽ የሆነ ትርጓሜ በመስጠት ልጀምር፤

ሰላም ማለት የሁከት (violence) አለመኖር ማለት ነው።

ይህ ትርጓሜ ትክክል ቢሆንም እዚህ ላይ መቆም ግን ነገር ማድበስበስ ነው።

የሚከተሉትን ሁለት ምሳሌዎችን ያጢኗቸው።

1. ማጅራት መቺዎች የበዙበት መንደር ውስጥ ሁከት እንጂ ሰላም የለም። ቶሎሳ ማጅራት መቺዎች የበዙበት መንደር ነዋሪ ነው፤ እናም በሰላም እጦት ኑሮውን በስጋትና በሰቀቀን እንዲያሳልፍ ተገዷል። ቶሎሳ ብቻ ሳይሆን ሌሎችም የመንደሩ ነዋሪዎች ሰላማቸው ተናግቷል።

2. “ረዥሞ” የተባለው ሰፈር አብዛኛዎቹ ነዋሪዎች ረዣዥሞች ሲሆኑ አጭር ሰው አይወዱም። ሆኖም ግን ተፈጥሮ “ጠማባቸው” አጭር አድርጋ የፈጠረቻቸው ጥቂት ሰዎች ረዥሞ ሰፈር ውስጥ ይኖራሉ። እነዚህ ሰዎች በሚደርስባቸው መድልዖ፣ ማንጓጠጥና ማግለል ምክንያት ሰላማቸው ተናግቶ ኑሮዓቸውን በምሬት፣ በስጋትና በሰቀቀን እንዲያሳልፉ ተገደዋል። ጠንክር ይህንን የስጋትና የሰቀቀን ኑሮ በረዥሞ መንደር የሚገፋ ቁመተ አጭር ሰው ነው።

ቶሎሳና ጠንክር ሰላም የራቃቸው ሰዎች ናቸው። የሁለቱ የሰላም እጦት ምክንያት ግን ለየቅል ነው። የቶሎሳው ቀጥታና ግልጽ ጥቃት ሲሆን የጠንክር ግን ውስብስና መዋቅራዊ ነው። መፍትሔዎቻቸውም ለየቅል ናቸው። የቶሎሳን ችግር ዘበኛ ወይም ጠባቂ በመቅጠር መወጣት ይቻላል። የጠንክርን ችግር ለመፍታት ግን የሥርዓትና የአስተሳሰብ ለውጥ ይፈልጋል።

ሰዎች በማጅራት መቺዎች በሚዘረፉበት ከተማ ውስጥ ሰላም የሌለ መሆኑን ማሳመን ቀላል ነው። ሰዎች በመንግሥት በሚዘረፉበት ከተማ ውስጥ ሰላም የሌለ መሆኑ ማሳመን ግን የዚያን ያህል ቀላል ላይሆን ይችላል። የመንግሥት ዘረፋ እንደ ግለሰብ ዘረፋ ቀጥተኛና ግልጽ አይደለም። መንግሥት ሲዘርፍ ማጅራት መቺዎችን ማሠማራት ላያስፈልገው ይችላል። መንግሥት ኢፍትሃዊ ታክስ በመጫን ዘረፋውን ሕጋዊ ሊያደርገው ይችላል። የመንግሥት ዘረፋ በግልጽ ላይታይ ይችላል፤ ቀስ እያለ እየተብላላ ቆይቶ ሲፈነዳ ግን ውጤቱ አንድ ወይም ሁለት ማጅራት መቺዎችን ለፍርድ ከማቅረብ ጋር የሚመሳሰል አይደለም።

ከላይ ከቀረቡት ምሳሌዎች ሁለት ዓይነት ሰላሞች መኖራቸውን መገንዘብ እንችላለን። እነዚህ ሁለት ዓይነት ሰላሞች አሉታዊ ሰላም እና አዎንታዊ ሰላም ተብለው ይጠራሉ።

1. አሉታዊ ሰላም (Negative Peace) – አሉታዊ ሰላም በግለሰብ ወይም በቤተሰብ ላይ ግልጽ ሁከት (Direct Violence) ያለመኖር ውጤት ነው።

በሰዎች ሕይወት ወይም ንብረት ላይ ቀጥተኛ ጥቃት ሲፈፀም ግልጽ ሁከት ተፈፀመ ይባላል። ለምሳሌ፣ ጦርነት በሰውም በንብረትም ላይ ቀጥተኛ ጥቃት የሚያደርስ በመሆኑ ግልጽ ሁከት ነው። ዝርፊያና ቅሚያም ግልጽ ሁከቶች ናቸው። ግልጽ ሁከት ከሌለ ዘራፊዎች፣ ኪስ አውላቂዎች፣ ወመኔዎች፣ ልጃገረዶችን የሚደፍሩ ምግባረ ብልሹዎች የሉም ማለት ነውና ሰዎች በሰላም ወጥተው በሰላም ወደ ቤታቸው ይመለሳሉ።

በግልጽ ሁከት መወገድ ሳቢያ የሚገኘው ሰላም “አሉታዊ ሰላም” ይባላል። አሉታዊ ሰላም ሲኖር “ሁሉ አማን” የሆነ ሊመስል ይችላል ሆኖም ሁከቱን እንጂ የሁከቱን ሥረ ምክንያት ስለማያስቀረው ወደፊት ሁከት የመነሳት እድሉ ከፍተኛ ነው።

2. አዎንታዊ ሰላም (Positive Peace) – አዎንታዊ ሰላም የመዋቅራዊ ሁከት[1] (structural vilolence) ያለመኖር ውጤት ነው።

መዋቅራዊ ሁከት በአድሎዓዊ ሥርዓት ሳቢያ የሚደረግ ተቋማዊ ጥቃትን ይመለከታል። ዘረኛ ፓሊሲ ለምሳሌ አንዱ ዘር ሌሎቹን እንዲያጠቃ መንገድ የሚያመቻች በመሆኑ ተቋማዊ ሁከትን ይፈጥራል። ወንዶች በሴቶች ላይ የበላይነት እንዲኖራቸው ሥርዓቱ የሚፈቅድ ከሆነ ውጤቱ በሴቶች ላይ የሚደርስ ተቋማዊ ጥቃት ነው። በተዛባ የሀብት ክፍፍል ሳቢያ የሚመጣ ድህነት የመዋቅራዊ ሁከት ውጤት ነው። የፍትህ መዛባት፣ ግዙፍ ሙስናዎች (Grand Corruption)፣ በሥልጣን መባለጎች የመዋቅራዊ ሁከት ውጤቶች ናቸው። ማይምነትም ቢሆን በአብዛኛው የመዋቅራዊ ሁከት ውጤት ነው።

በመዋቅራዊ ሁከት መወገድ ምክንያት የሚገኝ ሰላም “አዎንታዊ ሰላም” ይባላል። በሌላ አነጋገር አዎንታዊ ሰላም የሚሰፍነው ማኅበራዊ ፍትህ ሲሰፍን ነው። አዎንታዊ ሰላም ሲኖር ሰዎች ችግሮቻቸውን በድርድር ይፈታሉ። አዎንታዊ ሰላም በማኅበራዊ ቡድኖች መካከል ቀና የሆነ መስተጋብር መኖሩ አመልካች ነው።

3. አሉታዊ ሰላም እና አምባ-ገነን አገዛዞች

በአንድ አገር ውስጥ አዎንታዊ ሰላም አለ ማለት በዜጎች መካከል መዋቅራዊ መድልዎ አይደረግም ማለት ነው። አዎንታዊ ሰላም የሰፈነበት አገር ሕዝብ ከራሱ ጋር የታረቀ ነው። በዚህ አገር ውስጥ ለዘላቂ ሰላም አስተማማኝ መሠረት ተጥሏል ብለን አፋችንን ሞልተን መናገር እንችላለን። ይህ ማለት ግን አንድ ሰካራም ሌላውን የሚፈነክትበት አጋጣሚ የለም ማለት አይደለም። ፈጽሞ ግጭቶች አይነሱም ማለትም አይደለም። እንዲያውም በየጊዜው ሰልፎችና ተቃዉሞዎች በአደባባይ የሚሰሙበት ግርግር የበዛበት አገር ሊሆን ይችላል። ሆኖም ግን አለመግባባቶች ቢነሱ መፍትሔ የሚያገኙበት አሠራር አለ። አዎንታዊ ሰላም ችግሮች ሲፈጠሩ መፍትሔ እየፈለገላቸው ራሱን ጠብቆ የሚያቆይ ሰላም ነው። የአዎንታዊ ሰላም መኖር ለዘላቂ ሰላም ዋስትና ነው።

በአንፃሩ አዎንታዊ ሰላም ሳይኖር አሉታዊ ሰላም ሊኖር ይችላል። ማኅበራዊ ችግሮች ሳይነኩ ግልጽ ሁከቶችን ብቻ በማስወገድ ወይን በማፈን አሉታዊ ሰላምን ማስፈን ይቻላል።

አምባገነን መንግሥታት የአሉታዊ ሰላም አፍቃሪዎች ናቸው። የመንደር ሌቦችን፣ ማጅራት መቺዎችን፣ ወመኔዎችን እያደኑ አይቀጡ ጥቃት ይቀጣሉ። በዚህም ዓይነቱ ሥራቸው “የሰላም አባት” የተባሉ አምባገነኖች ብዙ ናቸው። ታድያ ግን ተቃዋሚዎቻቸውንም ከሌቦችና ዘራፊዎች ጋር ደብልቀው ይቀጣሉ። በውጤቱም ብዙዎች አምባገነን መንግሥታት የሚኩራሩበትን “ሰላም” ያሰፍናሉ። ይህ ዓይነቱ አሉታዊ ሰላም “አደገኛ ሰላም” ብለን መጥራት እንችላለን።

ታሪክን ገረፍ እናድርግ። በጆሴፍ ስታሊን “ቆራጥ አመራር” ሳቢያ ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ማብቂያ እስከ ሚካኤል ጎርባቾች አመራር ድረስ ለአርባ ዓመታት ያህል የዘለቀ አደገኛ አሉታዊ ሰላም በመላው የሶቭየት ኅብረት ግዛት ውስጥ ሰፍኖ ነበር። ምሥራቅ ጀርመንን 1949 እስከ 1990 እአአ ለ 41 ዓመታት ሉዓላዊት አገር አድርጎ ያቆያት ሕዝብን በክርን በመደቆስ በተገኘ አሉታዊ ሰላም ነው። አልባኒያም ከ30 ዓመታት በላይ በጡንቻ “የሰላም ደሴት” ሆና ኖራለች። ሊቢያ በኮሎኔል ሞአመር ጋዳፊ ብርቱ “ሕዝባዊ ክንድ” እና በአረንጓዴው መጽሐፍ አረንጓዴ መመሪያ ለ30 ዓመታት ኮሽታ የማይሰማባት ሁለመናዋ አረንጓዴ የሆነች አገር ሆና ነበር። ሙባረክ እስራኤልን የመሰለ የጎረቤት ባላንጣ እያለበት እንኳም ግብጽን ለ30 ዓመታት “በሰላም” ገዝቷል። አውሮፓ ውስጥ አሉታዊ ሰላም ለተራዘመ ጊዜ ከቆየባቸው አገሮች ግንባር ቀደሟ ዩጎዝላቢያ ናት። እአአ 1929 እስከ 1991 ለ68 ዓመታት ጉልበት ያፈረጠው አሉታዊ ሰላም ዩጎዝላቪያን ሰብስቦ አቆያት።

ከላይ ከተዘረዘሩት ምሳሌዎች በቀላሉ መረዳት እንደሚቻለው አደገኛ የሆነው አሉታዊ ሰላም ለተወሰነ ጊዜ መልካም ቢመስልም ከረዥም ጊዜ ውጤቶቹ አንዱ ውድመት መሆኑ ነው። ሶብየት ኅብረት ተበታትና ከካርታ ጠፋች። ምሥራቅ ጀርመን በምዕራብ ጀርመን ተውጣ ከካርታ ጠፋች። ዮጎዝላቢያ እጅግ አሳዛኝ በሆነ መንገድ ተበታትና ከካርታ ጠፋች። አልባኒና አዲስ አገር እንደና ተዋቀረች። ሊቢያ አረንጓዴ ሰንደቅ ዓላማዋን ጥላ ከአርባ ዓመታት በፊት ወደነበረው ማንነቷ ለመመለስ እየጣረች ነው። ግብጽ ገና ራሷን ፈልጋ ማግኘት አልቻለችም። አብዛኛውም ጊዜ አሉታዊ ሰላሞች ሲደፈርሱ የቆሙበትን ሥርዓት ይዘው ነው የሚጠፉት።

ወደ ራሳችን ጉዳይ እንመለስ። ወያኔ ነጋ ጠባ “ሰላማችን፤ ሰላማችን” የሚለው የትኛውን ዓይነት ሰላም ፈጥሮ ነው?

ዘረኝነት የፓለቲካ ሥርዓቱ መታወቂያ ሆኖ እያለ፤
ኢፍትሃዊ የሀብትና የሥልጣን ክፍፍል እና ሙስና የሥርዓቱ መለያ ሆነው እያለ፤
ፍትህ ተዋርዳ ፍርድ ቤቶች ገዢዎች የሰጡት ቅጣት ማሳወቂያ በሆኑበት፤
በዘርና በፓለቲካ ወገንተኝነት የተዋቀሩት የጦር ሠራዊት፣ የፓሊስና የስለላ ተቋማት ኢትዮጵያዊያንን ማጥቂያ ሆነው እያለ፤
በፓለቲካ እምነታቸውና በሀይማኖቻቸው ምክንያት ታስረው ሰቆቃ እየተፈፀማቸው ያሉ ወገኖቻችን ብዛት በአስደጋጭ ፍጥነት እየጨመረ ባለበት ሁኔታ፤
ሚሊዮኖች ድሀ ገበሬዎች ከይዞታቸው እየተፈናቀሉ በገዛ አገራቸው ስደተኛ የሆኑበት ሁኔታ እየተባባሰ መምጣቱን እያየን፤
ኢትዮጵያዊያን ገበሬዎች ቤተሰቦቻቸውን የሚመግቡት ቁራጭ መሬት አጥተው እያለ ሰፋፊ ለም መሬቶች ለውጭ ባለሀብቶች በገፍ እየተሸጠ ባለበት ሁኔታ፤
የወያኔ ሹማምንት በሀብት ላይ ሀብት እየጨመሩ ከተሞችን በሕንፃዎች ሲያሽቆጠቆጡ ዛንጋባ እንኳን አጥተው በረንዳ ላይ የሚያድሩ ዜጎች ቁጥር በከፍተኛ ፍጥነት እየጨመረ መሆኑን በገዛ ዓይኖቻችን እያየን፤
ከፍተኛ ትምህርታቸው ያጠናቀቁ ወጣቶች ለሚጠብቃቸው የሥራ እድል ባይማሩ ኖሮ ይበልጥ ተመራጭ ይሆኑ የነበረ የመሆኑ አሳዛኝ ሐቅ እያየን፤
ወጣቶች በተስፋ እጦት ከአገር ሲሰደዱ በባህር ሰጥመው አሊያም በበረሃ ንዳድ ተቃጥለው እያለቁ ባሉበት በአሁኑ ሰዓት፤
አብዛኛው ሰው ቁርስ፣ ምሳና ራቱን ደርቦ “ቁምራ” እየበላ ስለ ተከታታይ ዓመታት 11.6 % ዓመታዊ የኢኮኖሚ እድገት መስማት ግዴታ የሆነበት የጉድ አገር ሆኖ እያለ፤
የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የአፍሪቃና የአረብ አገራት እስር ቤቶች በኢትዮጵያዊያን ወንዶችና ሴቶች ተሞልተው እያለ፤ እና
ወያኔ የሚያደርሰው ግፍ ሞልቶ በፈሰሰበት በአሁኑ ወቅት “ሰላማችን፣ ሰላማችን” እያለ ሲነዘንዘን መስማት ልብን ያቆስላል።
ይኸ ሁሉ ኢፍትሃዊነት ባለበት ሊኖር የሚችለው ሰላም አሉታዊ ሰላም ያውም ተቃውሞን በጉልበት በመደፍጠጥ የሚገኘው አደገኛ አሉታዊ ሰላም ብቻ ነው። ለዚህም ነው ወያኔ ሕገወጥነትን ሕጋዊ የሚደርጉ አዋጆችን የሚያወጣው።

በጉልበት የሚመጣ አሉታዊ ሰላም ለአገራችን አይበጃትምና የወያኔን ሰላም መቃወም ተገቢ ነው። ከብዙ አገሮች ልምድ እንዳየነው አደገኛው አሉታዊ ሰላም ከመኖሩ አለመኖሩ ይሻላል። የወያኔ ሰላምም ለኢትዮጵያችን የሚበጅ አይደለም።

4. ሰላምተኛነት ሁሌ ትክክል ነውን?

በዚህ ንዑስ አርዕስት ሥር ለማለት የፈለግሁትን ሁሉ ሁለት ትላልቅ ስም ያላቸው ሰዎች ስላሉልኝ ለእነሱ ቦታ እለቃለሁ።

ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ

ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ታህሳስ 4 ቀን 2002 ዓ. ም. (December 10, 2009) የኖቤል የሰላም ሽልማት ሲቀበሉ ያደረጉት ንግግር ሙሉው መሰማት (ወይም መነበብ) ያለበት ቢሆንም አንባቢዎቼን ላለማሰልቸት አለፍ አለፍ ብዬ ልጥቀስ[2]።

እውነቱን በመቀበል እንጀምር − ብጥብጥ ያለበት ቅራኔን በእኛ እድሜ ማስቀረት አንችልም። ለወደፊቱም ሕዝቦች − በግልም ሆነ በጋራ − ኃይልን መጠቀም አስፈላጊ ብቻ ሳይሆን ከሞራል አንፃርም ተገቢ የሚሆንበት ሁኔታ ይኖራል።

አንሳሳት! ክፋት በዓለም ላይ አለ። በሰላማዊ ትግል ሂትለርን መግታት አይቻልም ነበር። ድርድር የአልቃይዳን መሪዎች መሣሪያዎቻቸውን እንዲጥሉ አያደርግም። አንዳንዴ ጉልበት መጠቀም ያስፈልጋል ማለት ከሃቅ የራቀ ምፀት አይደለም፤ ይልቁንስ ታሪክን በቅጡ መረዳት፤ የሰውን ልጅ ድክመቶችን ማወቅ እና የምክንያታዊነት ውስንነትን መገንዘብ ነው።

ሲቪል ዜጎች በገዛ መንግሥታቸው የሚታረዱበት ሁኔታ፤ የእርስ በርስ ጦርነቶች ወይም አንድን የዓለም አካባቢ ሊያምሱ የሚችሉ ብጥብጦችና ሰቆቃዎችን ለመከላከል ኃይልን የመጠቀም አማራጭ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል።

ሰላም ተመራጭ መሆኑ መታመኑ ብቻውን ሰላምን ለማስገኘት አይበቃም። ሰላም ኃላፊነት መቀበል ይጠይቃል። ሰላም መስዋዕትነትን ይጠይቃል።

ሰላም የሚታይ ብጥብጥ አለመኖር ማለት አይደለም። ፍትሃዊ ሰላም ዘላቂነት የሚኖረው በእያንዳንዱ ግለሰብ ተፈጥሮዓዊ መብቶችና ክብር ላይ የተገነባ ሲሆን ነው።

ዜጎች የመናገር፣ የማምለክ፣ መሪዎቻቸውን የመምረጥ ወይም ያለፍርሃት የመሰብሰብ ነፃነታቸው በተገፈፉ ጊዜ ዘላቂ ሰላም አይኖርም። …. እንደምናውቀው አውሮፓም ሰላም ያገኘችው ነፃ ስትሆን ነው።

ፕሬዚዳንት ኦባማ ኢትዮጵያዊ ሁነው ይህንን ንግግር አዲስ አበባ ውስጥ ተናግረውት ቢሆን ኖሮ ሕገወጥነትን ሕጋዊ ያደረጉ አንቀጾች ተጠቅሰውባቸው ንግግራቸው ለአሸባሪነታቸው የማያሻማ ማስረጃ ሆኖ እድሜ ልክ ያስፈርድባቸው ነበር። እሳቸው ግን ኦስሎ ውስጥ በበርካታ ካሜራዎች ፊት ለፊት የሰላም የኖቤል ሽልማት ለመቀበል ይህንን ተናገሩ።

የሰላም የኖቤል ሽልማት ተሸላሚው ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ “አንሳሳት! ክፋት በዓለም ላይ አለ። በሰላማዊ ትግል ሂትለርን መግታት አይቻልም ነበር” አሉ። ቀጥለውም “ሲቪል ዜጎች በገዛ መንግሥታቸው የሚታረዱበት ሁኔታ፤ የእርስ በርስ ጦርነቶች ወይም አንድን የዓለም አካባቢ ሊያምሱ የሚችሉ ብጥብጦችና ሰቆቃዎችን ለመከላከል ኃይልን የመጠቀም አማራጭ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል” አሉ።

ማርቲን ሉተርን ኪንግ

የማርቲን ሉተርን ኪንግን “ፍቅር፣ ሕግ እና ሕዝባዊ እምቢተኝነት[3]” ሙሉውን ማንበብ ይጠቅማል። ለአሁኑ ግን አንዲት ትንሽ ጥቅስ ብቻ ልውሰድ፡

ሰላም ማለት ፍትህ፣ ቀና ፍላጎትና ወንድማማችነትን የመሳሰሉ አዎንታዊ ነገሮች መገኘት ጭምር እንጂ ጭንቀት፣ ውዥንብር ወይም ጦርነት የመሳሰሉ አሉታዊ ነገሮች አለመኖር ማለት ብቻ አይደለም። ኢየሱስ “ሰይፍን እንጂ ሰላምን ለማምጣት አልመጣሁም” ሲል …… እኔ እንደሚመስለኝ ለማለት የፈለገው የሚከተለውን ነው። …. ውጥረትም ሆነ ቅራኔ የሌለበት የድሮዉን አሉታዊ ሰላም አይደለም ይዤላችሁ የመጣሁት። እኔ ይዤላችሁ የመጣሁት በብርሀንናና በጨለማ፣ በፍትህና ኢፍትሃዊነት መካከል ባለ ፍትጊያ የሚንቀለቀለውን አዎንታዊውን ሰላምን ነው።

….

5. ማጠቃለያ

የወያኔ ካድሬዎች፣ ራድዮና ቴሌቪዥናቸው ስለ ሰላም አውርተው አይጠግቡም። “ሰላማችንን አደጋ ላይ ሊጥሉብን ሞከሩ” በሚል ሰበብ በርካታ ወገኖቻችን በእስር ቤቶች እየማቀቁ ነው።

ሰላም አንድ አይነት ስታንዳርድ የወጣለት የፋብሪካ ሸቀጥ አይደለም። ጥሩ ሰላም አለ፤ መጥፎ ሰላምም አለ። እናም ወያኔዎች የሚዘፍኑለት የሚያቅራሩለት ሰላም ምን ዓይነት ሰላም እንደሆነ መርምረን ማወቅ የራሳችን ኃላፊነት ነው።

ሕዝብ በማፈንና በመርገጥ የሚመጣ ሰላም በረዥም ጊዜ አገርን የከፋ አደጋ ላይ ይጥላልና አንፈልገውም። አደገኛውን አሉታዊ ሰላምን መቃወም ሕዝብን፣ ነፃነቱንና አገሩን ከሚወድ ዜጋ ሁሉ የሚጠበቅ ተግባር ነው። በሰላም ስም ሲያታልሉን ልንታለልላቸው አይገባም።

ሰዎች በሰላም ውለው መግባታቸው ብቻውን የዘላቂ ሰላም ምልክት አይደለም። የዘላቂ ሰላም ዋስትና ማኅበራዊ ፍትህን ማስፈን ነው፤ ይህ ደግሞ ወያኔ ሥልጣን ላይ ሆኖ የሚሆን ነገር አይደለም።

አስተያየት መስጠት ከፈለጉ: tkersmo@gmail.com

[1]. በማኅበራዊ ሣይንስ በስፋት የሚታወቁ የሁከት (Violence) ዓይነቶች ሦስት ናቸው። ሦስተኛውና በዚህ ጽሁፍ ያልተጠቀሰው “የባህል ሁከት (Cultural Violence)” በመባል የሚታወሰው በባህል ላይ የሚደረግን ጥቃት የሚመለከተውን ነው።

[2] http://www.youtube.com/watch?v=AORo-YEXxNQ

[3] Martin Luther King Jr “Love, Law, and Civil Disobedience,” in “A Testament of Hope: The Essential Writings and Speeches of Martin Luther King Jr.,” pp. 6, 50-51. .


Sport: የተጨዋቾች ዝውውር ዋጋ ንረት ምክንያቱ ምን ይሆን?

$
0
0

arsenalየተጨዋቾች የዝውውር ሂሳብ እየናረ ከመጣ ከራርሟል፡፡ በእርግጥ ጭማሬ ማሳየቱ የማይቀር ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት ለዝውውር እየወጣ ያለው ሂሳብ እጅግ ከፍተኛ መሆኑ ግን እንቆቅልሽ ነው፡፡ በክረምቱ የዝውውር ገበያ እስካሁን ለራዳሜል ፋልካኦ፤ ኤዲንሰን ካቫኒ፣ ኔይማር፣ ፈርናንዲንሆ፣ ማሪዮ ጎትዘ፣ ጀምስ ሮድሪጌዝ፣ አሲደር ኢላራሜንዲና ጎንዛሎ ሂጓይን ግዢዎች በአጠቃላይ 325 ሚሊዮን ፓውንድ ወጥቷል፡፡ በአማካይ ለአንድ ተጨዋች 40 ሚሊዮን ፓውንድ ማለት ነው፡፡ እነዚህ ግዢዎች የተፈፀሙት የክረምቱ የዝውውር መስኮት ከተከፈተ ገና አጋማሽ ላይ እንኳ ሳይደርስ መሆኑን ልብ ይሏል፡፡ ሁሉም ተጨዋቾች አስደናቂዎች ናቸው፡፡ ነገር ግን ምርጡ ተጨዋች ከ30 ሚሊዮን ፓውንድ በላይ እንዲሁም ኮከብ የሆነ ተጨዋች 50 ሚሊዮን ፓውንድና ከዚያ በላይ ሊከፈልለት ይገባል የሚል የተፃፈ ህግ የለም፡፡ ይህ ሂሳብ እጅግ ከፍተኛ ነው፡፡ በዚህ ላይ የተጨዋቾቹ የደመወዝ መጠንም አልተካተተበትም፡፡
የታሪክ መዛግብትን መለስ ብሎ ለቃኘ የዝውውር ሂሳብ በምን ያህል ፍጥነት መጨመሩን ይመለከታል፡፡ ጂያንሎዊጂ ቤንቲኒ በ1992 በ12 ሚሊዮን ፓውንድ ሲዘዋወር የወቅቱን የሽያጭ ሪከርድ በመስበር የራሱ አድርጎት ነበር፡፡ የሌንቲኒ ዝውውር ከተፈፀመ ከ14 ዓመታት በኋላ ክሪስቲያኖ ሮናልዶ ሪከርዱን 80 ሚሊዮን ፓውንድ አድርሶታል፡፡ በአጠቃላይ የዝውውር ሂሳብ ከፍተኛ ንረት ታይቷል፡፡ የዓለም አቀፉ ኢኮኖሚ በተንኮታኮተበት ወቅት ከፍተኛ ጭማሪ ማሳየቱ ግን የበለጠ ያስገርማል፡፡

የዦን ማርክ ቦስማን ወይም በአጭሩ የቦስማን ህግ መጽደቁ የዝውውር ገጽታውን በአጠቃላይ ቀይሮታል፡፡ የቦስማን ህግ በዝውውር ጉዳይ የበለጠውን ኃይል ለተጨዋቾችና ወኪሎቻቸው አጎናፅፏል፡፡ የተሻለ ኮንትራትና ክፍያ ለማግኘት በሚያደርጉት ድርድር የአንበሳውን ድርሻ እንዲይዙ ያደርጋቸዋል፡፡ ይህ አካሄድ የተጨዋች የዝውውር ሂሳብና ደመወዝ በከፍተኛ ፍጥነት እንዲያድግ የበኩሉን አስተዋፅኦ አበርክቷል፡፡ የዩሮ መገበያያ ገንዘብ በ1999 ስራ ላይ ከዋለ ወዲህ 54 ተጨዋቾች በ35 ሚሊዮን ዩሮ ወይም በላይ በሆነ ሂሳብ ተዘዋውረዋል፡፡ ይህ ቁጥር የክረምቱ የዝውውር መስኮት ከመዘጋቱ በፊት ሊያሻቅብ ይችላል፡፡ ቤል፣ ዌይን ሩኒ እና ሉዊስ ሱአሬዝ የመሳሰሉት ተጨዋቾች በከፍተኛ ሂሳብ ሊዘዋወሩ እንደሚችሉ መዘገብ ከተጀመረ ሰንበትበት ብሏል፡፡

ለተጨዋቾች ግዢ የሚወጣው ገንዘብ ለማሻቀቡ ምክንያት የቦስማን ህግ ብቻ አይደለም፡፡ እግርኳሱ እያገኘ ያለው ያልተቋረጠ የሚዲያ ሽፋን ሌላው ምክንያት ነው፡፡ ከቴሌቪዥን ስርጭት የሚገኘው ዳጎስ ያለ የገንዘብ ስምምነት ለስፖርቱ የበለጠ አቅም ሰጥቶታል፡፡ የፕሪሚየር ሊጉን ጨዋታዎች ለማስተላለፍ ስካይና ሲቲ የተሰኙት ድርጅቶች ለሶስት ዓመታት ኮንትራት 5.5 ቢሊዮን ፓውንድ ይከፍላሉ፡፡ ይህን መሰሉ ስምምነት ሌሎች ስፖንሰሮችም ይስባሉ፡፡ ክለቦች ከማሊያና ቁሳቁሶች ንግድ እንዲሁም ከስፖንሰሮች በሚሊዮን የሚገመት ገቢ ያገኛሉ፡፡ ይህ ግዙፍ የሆነ ገቢ ለዝውውር የበለጠ ገንዘብ እንዲያወጡ መንገድ ይከፍትላቸዋል፡፡
በዘመናዊው እግር በስፋት የሚሳተፉትን የራሺያ ቢሊየነሮችም ይጠቀሳሉ፡፡ በእርግጥ በርካታ ክለቦች ቱጃር ባለሀብቶች የተያዙ ናቸው፡፡ በሮማን አብራሞቪች፣ ሼህ መንሱር አልናህያን እና የካታር ኢንቨስትመንት ግሩፕ ሚሊዮኖችን በክለቦች ላይ ማፍሰሳቸው ሌሎችም ወደ እግርኳሱ ተግተልትለው እንዲመጡ አድርጓል፡፡ የእነዚህ ባለሀብቶች ለዝውውር የሚጠየቀውን ሂሳብ መክፈላቸው ወይም ትንንሽ ክለቦች ከሽያጩ ጥሩ ገንዘብ ለማግኘት ሲሉ ክለቦች ከሽያጩ ጥሩ ገንዘብ ለማግኘት ሲሉ ውሳኔያቸውን ግትር በማድረግ ብዙ ተጨዋቾች በማይገባቸው ሂሳብ እንዲዘዋወሩ ያደርጋሉ፡፡

የክለቦች ዓለማ ዋንጫዎችን ማሸነፍ ነው፡፡ እነዚህ ድሎች ደግሞ ጠቀም ያለ ሽልማት ያስገኛሉ፡፡ ደጋፊዎችና ተጨዋቾች ዋንጫዎችን ማንሳት ቢወዱም የክለብ ባለቤቶች ግን ብዙ ገንዘብ ያስገኝላቸዋል፡፡ ከዋንጫ አሸናፊነት የሚገነው ገንዘብ ብቻ ሳይሆን የክለቡ እውቅናም ይናኛል፡፡ አምና ባርን ሙኒክ የቻምፒየንስ ሊጉ አሸናፊ በመሆኑ 36 ሚሊዮን ዩሮ አግኝቷል፡፡ እነዚህ የተለያዩ ምክንያቶችን ስንመለከት በእግርኳሱ ላይ ገንዘብ ወሳኝነቱ መላቁን እንረዳለን፡፡ ባየርን ከቻምፒየንስ ሊጉ ድል ያገኘውን ሂሳብ ብቻ ለጎትዘ ዝውውር አውሏል፡፡ ባቫሪያኑ ወጣቱን በስኳዱ ውስጥ ማካተታቸው በመጪው የውድድር ዘመን ለስኬት ያላቸውን እድል የበለጠ ያሰፋዋል፡፡ ዋንጫ በድጋሚ ካነሱ ደግሞ የበለጠ ገቢ ያገኛሉ፡፡ በአንድ ዓመት ውስጥ 100 ሚሊዮን ፓውንድ የሚያገኝ ክለብ ለተጨዋች ዝውውር 10 ሚሊዮን ፓውንድ ፓውንድ ከሚያወጣው ጋር ልዩነት የለውም፡፡

ከስፖርቱ ውጪ ያለውን ዓለም በአንፃራዊነት ስንመለከት ለአንድ ተጨዋች ዝውውር 40 ሚሊዮን ፓውንድና 250 ሺ ፓውንድ ሳምንታዊ ደመወዝ መክፈል ተገቢ አለመሆኑ ይታያል፡፡ ይህ ከፍተኛ ገንዘብ ድህነትን ማስወገድና አደጋዎችን መከላከልን በመሳሰሉት መስኮች ላይ ፈሰስ ተደርጎ ቢሆን ኖሮ የበርካቶች ፍላጎት ነበር፡፡ ሆኖም በእግርኳሱ መጠኑ ከልክ ያለፈ ገንዘብ ይንሸራሸራል፡፡ ገደብ እስከሚበጅለት ድረስ ወጪው እየናረ መሄዱን አያቋርጥም፡፡ የአውሮፓ እግርኳስ ማህበር የፋይናንስ ጨዋነት ደንብ ወጪው ገደብ እንዲኖረው ተብሎ የተቀረፀ ነበር፡፡

ክለቦች ስኬታማ ለመሆን የገዘፈ ወጪ ማውጣት አለባቸው? ለሚለው ጥያቄ መልሱ አዎ የሚል ነው፡፡ ምክንያቱም በአብዛኞቹ ሀገራት ሊግ የበላይነት ያላቸው ጥቂት ቡድኖች ብቻ አልያም በቢሊዮኖች ታግዘው የሚመጡት መሆናቸው በቂ ማረጋገጫ ነው፡፡ ሆኖም በአነስተኛ ሂሳብ ውጤታማ የሆኑ ውስን ቡድኖችም ይገኛሉ፡፡ በአሁኑ ወቅት ለመመልከት የሚያስደስተው የዶርትሙንድ ቡድን አጠቃላይ ወጪ ግን ያነሰ ነው፡፡ በተጠናቀቀው የውድድር ዘመን የቻምፒየንስ ሊግ ፍፃሜ ላይ የተሰለፉት የዶርትሙንድ ቋሚ 11 ተጨዋቾች የተገዙበት ድምር ዋጋ ከ38 ሚሊዮን ፓውንድ ያነሰ ነበር፡፡ ከእነርሱም ውስጥ 15 ሚሊዮን ፓውንዱ የማርኮ ሩስ ግዢ መሆኑ ሲታሰብ ቁጥሩ የበለጠ ያንሳል፡፡ ይህ ወጪ ጎትዘን አለመካተቱ ልብ ይሏል፡፡ በጀርመን ሱፐር ካፕ ዶርትሙንድ የፔፕ ጋርዲዮላን ባየርን 4-2 ሲረታም የተጫዋቾቹ የተገዙበት ዋጋ ተመሳሳይ ነው፡፡

fabrigasአርሰናልና ባርሴሎና በአነስተኛ ወጪ ስኬታማ በመሆን ሌሎቹ ምሳሌዎች ናቸው፡፡ የሰሜን ለንደኑ ቡድን ባለፉት ጥቂት ዓመታት ዋንጫ ማንሳት ባይችልም በመደበኛነት በሊጉ እስከ አራተኛ በመውጣትና በቻምፒየንስ ሊጉ ጥሎ ማለፉ ደረጃ መድረስ ችሏል፡፡ አርሰን ቬንገር ለዝውውር ከፍተኛ ሂሳብ አለማውጣታቸው የመድፈኞቹን ደጋፊዎች ባያስደስትም ያመጡት ስኬት ግን የሚደነቅ ነው፡፡ ባርሳ በቀደመው ጊዜ ለዝውውር ከፍተኛ ገንዘብ ቢያፈስም ባለፉት ጥቂት ዓመታት ላስመዘገበው ስኬት መሰረቶች የላ ማሲያ ውጤቶች ናቸው፡፡ ቪክቶር ቫልዴዝ፣ ካርሎስ ፑዩል፣ ዤራርድ ፒኬ፣ ዣቪ ሄርናንዴዝ፣ አንድሬስ ኢኒዬሽታ፣ ሰርጂዮ ቡስኬትስ፣ ፔድሮ ሮድሪጌዝና ሊዮኔል ሜሲ የቡድኑ ምሰሶዎች ሲሆኑ ሁሉም የተመረቁት ከላ ማሲያ ነበር፡፡ ከዚሁ አካዳሚ ተገኝተው ለሌሎች ክለቦች በመጫወት ላይ የነበሩትን ሴስክ ፋብሪጋዝና ዮርዲ አልባን ወደ ቀድሞ ቤታቸው ለመመለስ ግን ከፍ ያለ ሂሳብ ተከፍሎባቸዋል፡፡
እነዚህ የተጠቀሱት ምሳሌዎች በወጣቶች ላይ ኢንቨስት ማድረግ ጠቃሚነቱ ያሳየናል፡፡ የጀርመን እግርኳስ በወጣቶች እንዴት ስኬታማ እንደሚሆን አሳይቷል፡፡ ሀገሪቱ ለወጣት አካዳሚዎች ስርነቀል ለውጥ በማድረጓ አሁን ፍሬውን እያጨደች ትገኛለች፡፡ ስፔንም ብትሆን በየዓመቱ ወጣት ከዋክብት ማውጣቷን እንደቀጠለች ነው፡፡ ይህን ማሳካት ግን እንደሚታሰበው ቀላል አይደለም፡፡

በክለብ ውስጥ ያለው አለመረጋጋት ግን በሂደቱ እንደ መሰናክል ይታያል፡፡ ገንዘብ ለእግርኳሱ ኃይል በመጨመሩ አሰልጣኞች በወጣቶች ስብስብ ቡድን ለመገንባት በቂ ጊዜ አይሰጣቸውም፡፡ ደጋፊዎችና ባለቤቶችም ፈጣን ስኬት መመኘታቸው ሌላው የአሰልጣኞች ፈተና ነው፡፡ አሰልጣኞች ስራቸውን በፍጥነት ማጣታቸው ተለመደ ሆኗል፡፡ አዲስ የሚሾመው አሰልጣኝ ደግሞ የተለየ ፍልስፍና ይዞ ስለሚመጣ ቡድኑ ቀጣይነት እንዳይኖረው ይደረጋል፡፡ በዝውውርና ደመወዝ ላይ ብዙ ገንዘብ የሚፈስ በመሆኑ በርካቶች ቅሬታቸውን ያሰማሉ፡፡ ሌሎች በአንፃሩ ለዝውውር የተመደበው ሂሳብ ወጪ ባለመደረጉ ያማርራሉ፡፡

ጁነዲን ሳዶ ተገደሉ የሚለው ዜና ሃሰት ነው ተባለ

$
0
0

junedin(ዘ-ሐበሻ) ፌስቡክን ጨምሮ በተለያዩ የማህበራዊ ድረገጾች ላይ በሰፊው እየተወራ የሚገኘው የአቶ ጁነዲን ሳዶ በወያኔ ተገደሉ የሚለው ዜና ሃሰት መሆኑን ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ሰዎች እየገለጹ ነው። እነዚህ ለአቶ ጁነዲን ቅርብ ነን ያሉ ወገኖች “የወሬው ምንጭ ሁሌም ሕዝብን በወሬ ማራበሽ የሚወደው የወያኔ መንግስት ነው” ይላሉ።
ወጣቱ የፖለቲካ ተንታኝ ጃዋር መሀመድ በፌስቡክ ገጹ “ጁነዲን ተገደሉ የሚለው ዜና ሃሰት ነው” ሲል በተለይ በአያንቱ ድረገጽ ላይ የወጣውን ዜና አስተባብሏል። አያንቱ ድረ ገጽ Gurmessaa Beekamaa የተባሉ ሰው በፌስቡክ የለጠፉትን ዜና “ይህ ዜና ከነፃ ምንጮች አልተረጋገጠም” በሚል በማቅረብ ዜናው እንዲቀጣጠል ያደረገ ቢሆንም፤ ድረገጹ ከሰዓታት በኋላ ደግሞ ጁነዲን በሕይወት ስለመኖራቸውና ስላለመኖራቸው የተምታታ መረጃዎች እየደረሰን ነው በሚል ጉዳዩን እያጣራ እንደሚገኝና የዜናው ምንጭ ናቸው የተባሉት ግለሰብም ስለጁነዲን ተጨባጭ ማስረጃቸውን እንዲያቀርቡ ጠይቋል።
የወያኔ ሚዲያ እንደሆነ የሚነገርለት ኢትዮቻናል የተባለውና በሃገር ቤት የሚታተመው ጋዜጣ ከዚህ ቀደም ጁነዲን ሳዶ ወደ ኬንያ ጠፍተዋል በሚል ሃሰተኛ ዜና ማሰራጨቱ የሚዘነጋ አይደለም ያሉት እነዚሁ የጁነዲንን ሞት የሚያስተባብሉ ወገኖች አሁንም ተገደሉ ብሎ የሚያወራው ራሱ ወያኔ፤ የሕዝቡን የአስተሳሰብ አቅጣጫ ለመቀየር ነው ይላሉ። በተለይ በነፃው ፕሬስ ላይ ለረዥም ዓመታት የሰሩ አንድ አንጋፋ ጋዜጠኛ ለዘ-ሐበሻ እንደገለጹት “የወያኔ መንግስት ሃሰተኛ ዜናዎችን በመፈብረክ ሚዲያዎች ተአማኒነት እንዲያጡ ለማድረግ ሲጥር ይህ የመጀመሪያው አይደለም። በነፃ ጋዜጦች ስም የራሱን ጋዜጦች በማሳተም ሃሰተኛ ዜናዎችን እያቀረበ በራሱ ቴሌቭዥን ደግሞ ‘ነፃ ጋዜጠኛ የሚባሉት እንዲህ እያሉ የውሸት ዜና እየጻፉ ነው’ የሚል ፕሮፓጋንዳ በመሥራት ራሱ በከፈተው ነፃ ጋዜጣ ሌላውን ነፃ ጋዜጣ ሲያሰደብና ተአማኒነት እንዲያጡ በማድረግ ቆይቷል። አሁን ደግሞ እንዲህ ያለው ዜና፣ ባለፈው ዓመት መንግስቱ ኃይለማርያም በዙምባብዌ ሞቱ የሚሉት ዜናዎች በራሱ በወያኔ ተዘጋጅቶ በፌስቡክ የሚለጠፈው ፌስቡክ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ለውጥ እንደሚያመጡ ስለሚያውቅ መንግስት ሕዝቡ ፌስቡክ ላይ የሚጻፉ መረጃዎችን እንዳያምን ለማድረግ ነው የተዘጋጀ ድራማ ነው” ይላሉ።
የጁነዲን ሳዶ ባለቤት በወያኔ መንግስት ሽብርተኛ ተብለው የታሰሩ ሲሆን ይህን ተከትሎም ከሲቪል ሰርቪስ ሚኒስትርነታቸው መነሳታቸው ይታወሳል። ጁነዲን የሕወሓት ተለጣፊ ከሆነው ኦሕዴድ ጋር በሚሰሩበት ወቅት በአውስትራሊያ እና በሚኒሶታ ከፍተኛ ተቃውሞ አጋጥሟቸው እንደነበር መዘገቡ ይታወሳል።

ለአቡነ ጳውሎስ የመቃብር የነሐስ ሐውልት የተመደበው 1.5 ሚልዮን ብር ነው

$
0
0

የአቡነ ጳውሎስ ሙት ዓመት ትናንት ታስቦ ውሏል። ይህን ተከትሎ በወጡ መረጃዎች የሟቹን ፓትርያርክ የመቃብር ሐውልት በነሐስ ለማሠራት 1.5 ሚልዮን ብር የተመደበ መሆኑ ታውቋል። የሐራ ሙሉ ዘገባ እንደወረደ ይኸው፦
ለሐውልቱ ሥራ የተዋዋለው ተቋራጭ አድራሻውን አጥፍቶ ጀርመን ከረመ
በውሉ መሠረት ከነሐስ የሚሠራውን ሐውልት በ186 ቀን ሠርቶ ማስረከብ ነበረበት
ለጥቅምት ፲፪ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም ‹‹ዝክረ አበው›› እንዲያደርስ ታዝዟል

ነሐሴ ፲ ቀን ፳፻፬ ዓ.ም ሌሊት ከዚህ ዓለም በሞተ ሥጋ የተለዩት የአምስተኛው ፓትርያሪክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ኅልፈት አንደኛ ዓመት መታሰቢያ ሥነ ሥርዐት በዛሬው ዕለት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በማሕሌት፣ በጸሎተ ፍትሐትና በቅዳሴ ታስቦ ውሏል፡፡

abunapauolos(1)በቤተ ክርስቲያናችን የሙታን መታሰቢያ ቀኖና መሠረት በዐጸደ ነፍስ ያሉትን ዕጣን፣ ጧፍ እና መሥዋዕት በማቅረብ ተዝካረ ጸሎት ማድረግ ሥርዐት መኾኑን ከመጽሐፈ ግንዘት እና መጽሐፈ ሢራክ በመጥቀስ ያስረዱት ብፁዕ አቡነ ገሪማ፣ የአቡነ ጳውሎስ ዕረፍት አንደኛ ዓመት መታሰቢያ የሚካሄደው ‹‹ቅዱስነታቸው በሁሉም አቅጣጫ ያስመዘገቧቸውን የሥራ ውጤቶች በማዘከር›› መኾኑን ገልጸዋል፡፡

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ከዐሥራ አንድ ያህል ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ጋራ የሙት ዓመት መታሰቢያ ሥነ ሥርዐቱን መርተዋል፤ ንግግራቸውም ‹‹ነፍሰ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ወፓትርያሪክ አባ ጳውሎስን ከማኅበረ መላእክት፣ ከማኅበረ ጻድቃን እንድትደምርልን እንለምንሃለን›› በሚል የተወሰነና የተጠቃለለ ነበር፡፡

ጸሎተ ፍትሐቱ በተከናወነበት የካቴድራሉ ዐጸድ ውስጥ የሚገኘውና ሥራው ያልተጠናቀቀው መካነ መቃብራቸው በእብነ በረድ ተዘግቷል፤ በቆርቆሮ የታጠረው ዐጸድ ዙሪያው ጒንጒን አበባ ተደርጎበት የቀድሞውን ፓትርያሪክ ግዙፍ ምስል በያዘ ባነር ተሸፍኗል፤ ‹‹መልካሙን ገድል ተጋድያለኹ. . .›› የሚለው የቅዱስ ጳውሎስ ጥቅስ በታላላቅ ፊደላት ሰፍሮበታል፡፡ የመታሰቢያ ሥነ ሥርዐቱ ተካፋዮች ከጸሎተ ፍትሐቱ በኋላ ወደተቀጸረው የመካነ መቃብሩ ዐጸድ ቢዘልቁም ከዚህ በቀር የሚያዩት ነገር አልነበረም፡፡

የመቃብር ሐውልቱ ሥራ ስለመዘግየቱ የተመለከቱ ጥያቄዎችና ቅሬታዎች ለመንበረ ፓትርያሪክ ጠቅላይ ቤተ ክህነቱ መድረሳቸውን የገለጹት የጽ/ቤቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ፣ ሐውልቱ ከነሐስ እንዲሠራ ተወስኖ ሥራውን ለማስፈጸም የተቋቋመው ኮሚቴ ለክንውኑ በተመደበው ገንዘብ መሠረት ጨረታ አውጥቶ ለአሸናፊው ተቋራጭ ውል ተሰጥቶ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡

‹‹በጨረታው ውል መሠረት ተቋራጩ ሥራውን በ186 ቀን ጨርሶ ማስረከብ ነበረበት፤ ባለማጠናቀቁ ለመንፈቅ እንዲያደርስ ተራዘመለት፤ አላደረሰም›› ያሉት ብፁዕነታቸው፣ ‹‹ስልኩንም አጥፍቶ ነሐሴ 6 ቀን ብቅ ብሎ ጀርመን ነበርኹ ብሎ አረዳን›› ሲሉ እርሱ እየተጠበቀ ሥራው ከውሉ ውጭ እስከ ሙት ዓመት ድረስ መዘግየቱን አስረድተዋል፡፡

ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ ለሐውልቱ ሥራ የተመደበው ገንዘብ [1.5 ሚልዮን ብር መኾኑ ተዘግቧል] በባንክ ተጠብቆ እንዳለ መኾኑን ገልጠው÷ ‹‹እብነ በረዱ ተስተካክሎ ተቀምጧል፤ ተቋራጩም ነሐሱን [ከነሐስ የተሠራ ምስላቸውን] አምጥቼ ማቆም ብቻ ነው የሚቀረው ብሎናል፤ በተገባው ውል መሠረት ለጥቅምት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ባሉበት ይመረቃል፤ የዘገየው በእኛ ምክንያት አይደለም፤ ይህን እንድትረዱልን ነው፤›› ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

በቀድሞው ዘመነ ፕትርክና ይኹን አሁን የፓትርያሪኩ ልዩ ጽ/ቤት ሓላፊ የኾኑት ብፁዕ አቡነ ገሪማ በንባብ ባሰሙት ዝክረ ፓትርያሪክ አቡነ ጳውሎስ፣ ‹‹በዘመናቸው 49 ኤጲስ ቆጶሳትን አስገኝተዋል›› ብለዋል፡፡ ለአንደኛ ዓመት መታሰቢያ በብፁዕነታቸው ተዘጋጅቶ በሥነ ሥርዐቱ ላይ የተሠራጨውና የፓትርያሪኩን ዜና ሕይወትና ሥራዎች የያዘው ኅትመትም የአቡነ ጳውሎስን ኅልፈት አስመልክቶ የሚከተለውን አስፍሯል፤

ይኹንና ‹‹መኑ ሰብእ ዘየሐዩ ወኢይሬእያ ለሞት፤ ሕያው ሁኖ የሚኖር ሞትንስ የማያይ ሰው ማን ነው?›› /መዝ.88÷48/ ተብሎ በነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት በተነገረው መሠረት ቅዱስ ፓትርያርካችን በጾመ ፍልሰታ ለማርያም በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ቤተ ክርስቲያን በመቀደስና ሐዋርያዊ ተልእኮ በመፈጸም አንደኛውን ሱባኤ ካጠናቀቁ በኋላ ነሐሴ 8 ቀን 2004 ዓ.ም በዐሥራ አንድ ሰዓት አካባቢ ለምርመራ ወደ ሆስፒታል ሄደው በመታከም ላይ እንዳሉ ነሐሴ 10 ቀን 2004 ዓ.ም ከንጋቱ 11፡00 በተወለዱ በ76 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞተ ሥጋ ተለይተዋል፡፡

ለረጅም ጊዜ የአቡነ ጳውሎስ መጋቤ ሥርዐት ኾነው ያገለገሉት ፕሮቶኮል ሹማቸው ሙሉጌታ በቀለ ስለ ጤንነት ይዞታቸውና ድንገተኛ ኅልፈታቸው ነሐሴ ፲፪ ቀን ፳፻፬ ዓ.ም በፓትርያሪኩ የቀብር ሥነ ሥርዐት አፈጻጸም ሂደት ላይ ተወያይቶ መርሐ ግብር ለማውጣት ተሰብስቦ በነበረው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ፊት ቀርበው እንደሰጡት የተነገረው የቃል አስረጅ ደግሞ ፓትርያሪኩ ከተባለው ሰዓት ቀደም ብለው ስለማረፋቸው የሚጠቁም ነው፤

ማክሰኞ [ነሐሴ 8 ቀን] በቅድስት ማርያም አስቀድሰው ነበር፤ ከቅዳሴ ከወጡ በኋላ ከተወሰኑ አባቶችና እንግዶች ጋራ ምሳ በሉ፤ እኔም ወደ ቤቴ ሄድኩ፤ ማምሻውን አመማቸው ተባለና ተጠርቼ መጣኹ፤ ጤንነታቸውን በግል የሚከታተለው ዶ/ር ተጠርቶ መጣና አያቸው፤ ለክፉ የሚሰጥ አይደለም ብሎ ሄደ፤ ነገር ግን ሕመም ስለጠናባቸው ብዙ ጊዜ ወደሚታከሙበት ባልቻ ሆስፒታል ይዣቸው ሄድኹ፤ ሐኪሞቹ ሲመረምሯቸው ሳምባቸው ውኃ ቋጥሯል፤ ፈቃድዎ ከኾነ ውኃውን እንቅዳው ብለዋቸው ኦፕሬሽን ክፍል ገብተው ተቀዱ፤ ረቡዕ ተሽሏቸው ሰውም ሲያናግሩ ውለው ነበር፤ እኩለ ሌሊት ገደማ ግን ተጫጫነኝ ሲሉኝ ተረኛ ዶክተሮችን ጠርቼ አዩዋቸው፤ ዕረፍት እንዲያደርጉ አዘዟቸው፤ እኔም ከጎን ወደነበረ ማረፊያ ክፍል ሄድኩ፤ ንጋት ላይ ወደ ክፍላቸው ስመለስ ዐርፈው አገኘኋቸው፡፡

በወቅቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ የነበሩት ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል ለአሜሪካ ድምፅ ሬዲዮ የአማርኛ ቋንቋ አገልግሎት ሲናገሩ፣ ‹‹አብረን አስቀድሰን ቢሮም አብረን ቆይተን ነበር፤ ፓትርያሪኩ በስኳር ሕመም ይታወቁ ነበር፤ ጾሙም ሕመማቸውን ሳያከፋው አልቀረም፤ ብቻ ታመው አቅኑኝ ሳይሉ ፃዕር ጋዕር ሳይበዛባቸው ቅዳሴውን ሳያቋርጡ ከቤተ ክርስቲያን ወደ ቤተ ክርስቲያን ነው የሄዱት፤›› ብለው ነበር፡፡

ሌሎች ምንጮች በበኩላቸው የፓትርያሪኩን ሕመም ያከፋው÷ በወቅቱ ይፋ ያልተደረገውን የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ኅልፈት ሲረዱ በደረሰባቸው ከፍተኛ ድንጋጤና ይህን ተከትሎ ይወስዷቸው የነበሩትን መድኃኒቶች አወሳሰድ ማስተጓጎላቸው ያስከተለባቸው ‘multiple organ failure’ እንደነበረ ሲናገሩ ቆይተዋል፡፡

የፓትርያሪክ አቡነ ጳውሎስ ቤተ ዘመዶች ‹‹የአቡነ ጳውሎስ ፋውንዴሽን›› ለማቋቋም መንቀሳቀስ መጀመራቸው ከመንበረ ፓትርያሪኩ ምንጮች ተሰምቷል፡፡ ይህ ፋውንዴሽን በፓትርያሪኩ ፳ኛ ዓመት በዓለ ሢመት በሼራተን አዲስ በተከበረበት ወቅት ራእይ ለትውልድ የተሰኘው አካል በስማቸው ‹‹የካንሰር፣ቲቢና ኤድስ የሕክምናና ማገገሚያ ማእከል›› በ200 ሚልዮን ብር ለመገንባት ካቀደበት የበዓለ ሢመት ስጦታ ጋራ ግንኙነት ይኖረው እንደኾነ አልታወቀም፡፡

የፓትርያሪኩ ኅልፈት በተሰማበት ዕለት ረፋድ መኖርያ ቤታቸው፣ በስጦታ ያገኟቸው አይከኖች፣ መስቀሎች፣ አልባሳትና ሽልማቶች የሚገኙበት ሙዝየም ፖሊስና የጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ጠቅላላ አገልግሎት በተገኘበት መታሸጉ ተገልጦ የነበረ ቢኾንም ከአሮጌ አልጋና ካገለገሉ አልባሳት በቀር የተገኘ ነገር አለመኖሩ ተጠቁሟል፤ በምትኩ ፓትርያሪኩ በሽልማት ያገኟቸው አራት መኪኖች የይገባናል ጥያቄ እንደቀረበባቸውና ለዚህም ክሥ እንደሚመሠረት ተሰምቷል፡፡

ቢያንስ ቅዱስ ሲኖዶስ በግንቦት ፳፻፭ ዓ.ም የርክበ ካህናት ምልአተ ጉባኤው በቀድሞው ፓትርያሪክ ንብረት ላይ ለመወሰን የያዘው አጀንዳም በቂ ውይይት እንዳልተካሄደበትና ውሳኔም እንዳልተሰጠበት ነው ለመረዳት የተቻለው፡፡ በ፲፱፻፺፩ ዓ.ም ሕገ ቤተ ክርስቲያን አንቀጽ ፵፭ ንኡስ አንቀጽ (፩) እና (፪) ‹‹ስለ ቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ሀብትና ንብረት›› ግን የሚከተለው ተደንግጓል፤

አንድ የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ከዚህ ዓለም በሞት በሚለይበት ጊዜ የግል የኾነ ገንዘብ ቢኖረው ይረዳቸው ለነበሩ ዕጓለሙታንና ችግረኞች ይሰጣል፡፡ (አብጥሊስ ፴፱)
ኤጲስ ቆጶሱ መንፈሳዊ አገልግሎቱን ሲያከናውንባቸው የቆዩ መጻሕፍት፣ አልባሳት፣ አርዌ ብርት፣ መስቀሎች፣ መቋሚያዎችና የመሳሰሉት ሁሉ በቤተ ክርስቲያኒቱ ንብረትነት በስሙ ተመዝግበው በሀገረ ስብከቱ በሙዝየም ይቀመጣሉ፡፡
ነገር ግን እንደ ሕጉ አልኾነም፤ እንዲኾንም ተከታትሎ የሚጠይቅና የሚያስፈጽም አካል ያለ አይመስልም፡፡ እንዲያውም የታዛቢዎች አስተያየት የሚያስረዳው የቀድሞው ፓትርያሪክ ዜና ኅልፈት ከተሰማበት ዕለትና ከዚያም በኋላ የአንዳንድ ጉዳዮች አያያዝ፣ ‹‹ሲደከምበትና በብርቱ ሲፈለግ የቆየው የአቡነ ጳውሎስ ኅልፈት ብቻ እንደነበረና ሁሉም ነገር ከኅልፈታቸው ጋራ አብሮ ያከተመ የሚያስመስል ነው፡፡››

ዓባይ ሊያለማን ወይስ ሊያጠፋን? –የሕዳሴው ግድብና ዐባይ፣ የሚሊኒየሙ ዐባይ ተጋቦት

$
0
0

አዘጋጅ ለኢትዮጵያ ፍቅር ከቃሊቲ

የዐባይ ሥረ_መሠረትና የሕዳሴው ግድብ ማነጣጠሪያ እነሆ!
ጥናቱ የተፈጸመው ሚያዚያ 2003 (2011 እ ኤ አ) ነው። አቅርቦት የፀሐፊው ትክክለኛ ቅጂ (በአቀራረባዊ ጥንቅር) መነሻ የጊዜው የኢትዮጵያ ጉዳይ ሆኖ የቀጠለውና ሕዝቡም የጠየቁትን እያደረገ ያለበት የሚሌኒየሙ ታላቅ የዐባይ ግድብ እንደተነገረው፤ የሚገደበው ከሱዳን ድንበር 17 (አሥራ ሰባት) ኪሎሜትር ባለ ቀረቤታ በዐባይ ወንዝ ላይ ነው። ግድቡ ወደ 62 ቢሊዮን ሜትር ኩብ ውኃ የመያዝ አቅም አለው። የውኃው መጠን የጣና ሐይቅ ከሚይዘው ውኃ እጥፍ ይሆናል።
በሚታቆረው ውኃ 6ሺ (ስድስት ሺ) ሜጋ ዋት የኤሌትሪክ ኃይል ሊመረት ታቅዷል። የሚመረተው የኤሌክትሪክ ኃይል ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለሱዳንና ለግብፅም ሊሸጥ ታስቧል። ይህ ግንባታ 80
ቢሊዮን ብር ይፈልጋል።
Blue Nile
ገንዘቡ በግብፅ ተፅዕኖ ሳቢያ የውጭ ብድር ወይም ዕርዳታ እንዳያገኝ ስለተደረገ፤ በኢትዮጵያ ሕዝብ የመዋጮና ቦንድ ሺያጭ ሊሸፈን ተወስኗል።ለሕዝቡም ታሪካዊ ተዐምር ሊሠራ እንደሆነና የልማት
ሁሉ አንጋፋ እንደሆነ ተነግሮት የቻለውንና ያልቻለውንም ከማድረጉ በላይ ለሃገር የሚበጅ ልማታዊ ድንቅ እንደተፈጠረ ተበስሮለታል። ባለፈው ሚያዚያ (April) 2013 እ ኤ አ
ወር ማብቃያ አካባቢ በወጣው ዜና ደግሞ (ይህ ጥንቅር ከቀረበ ከሁለት ዓመት በኋላ መሆኑ ነው። ቻይና ለሚሌኒየሙ ግድብ ግንባታ 1.5 ቢሊዮን ዶላር ልታበድር ነው ተብሏል።
ታዲያ ግብፅና ሱዳን ምነው ዝም አሉ?
እኮ ቢጠቅማቸውማ ነው ዝምታቸው፤ የዐባይ ልጅ ይህ እንዴት ያየዋል? አባይ (ናይል)እየተባለ የሚጠራው በዓለም ረዥሙ ወንዝ፣6671 ኪሎ ሜትር እርዝማት ሲኖረው፣ከዘጠኝ አገሮች ይመነጫል።ግብፅ ምንም የምታመነጨው የውኃ አስተዋፆ የላትም። ሆኖም በናይል ውኃ በከፍተኛ ደረጃ ተጠቃሚ አገር ናት። ግብፅ 100% የሰሐራ በረሃ አካል በመሆኗ በሜዲቴሪንያን አካባቢ ጥቂት ዝናብ ጠብ ከማለቱ ሌላ ከዓመት ዓመት ዝናብ አይጥልም።
በሌላ በኩል ደግሞ ከሁሉም የናይል ተፋሰስ አገሮች ይበልጥ የ80% በመቶ ከአባይና ከሌሎች የኢትዮጵያ ወንዞች የሚገኘው ውኃ አባይን ይገልጸዋል። በጠቅላላው የናይል ወንዝ 74 ቢሊዮን
ሜትር ኩብ ውኃ በዓመት ሲሰጥ ከዚህ ውስጥ ከኢትዮጵያ የሚገኘው የውኃ ድርሻ መጠን 54 ቢሊዮን ሜትር ኩብ ውኃ ነው። የዚህ ሁሉ ውኃ ምንጭ ኢትዮጵያ ስትሆን፤እንደ ሱዳንና ግብፅ እምነት ጥቂት ውኃ እንኳን ለመጠቀም መብት የላትም።ሌሎቹንም የናይል ውኃ አመንጪና ባለቤት የራስጌ አገሮችን በማግለል መብታቸውን ገፍፈው ሱዳንና ግብፅ ተከፋፍለውታል።
እ ኤ አ 1959 ዓ ም በተፈራረሙት ስምምነት መሠረት ግብፅ 55.5 ቢሊዮን ሜትር ኩብ ፤ሱዳን ደግሞ 18.5 ቢሊዮን ሜትር ኩብ ውኃ ይወስዳሉ።በተለይ ግብፅ የውኃው ዋና ባለቤት እራሷን አድርጋ በመቁጠር አመንጪዎቹን የራስጌ አገሮች ለአነስተኛ የውኃ ጠቀሜታ እንኳን ፈቃጅ መሆን አለብኝ ባይ ናት። ለዚህም ኢትዮጵያን ማዳከም ወይንም ማጥፋት ተልዕኮዋ ሆኗል።
የአባይ ጠቀሜታ
ግብፅና ሱዳን ፍፁም ተጠቃሚዎች ሲሆኑ፤ በተቃራኒው የውኃ መነሻ የሆነችው ኢትዮጵያ ተጠቃሚ አልሆነችም። ግብፅ 3.0 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በመስኖ ታለማለች። ሱዳን 1.8 ሚሊዮን ሄክታር እንደዚሁ በናይል መስኖ ታለማለች። ኢትዮጵያ አትጠቀምም በመስኖ አለማችም። የግብፅ በረሃ በናይል ውኃ በሺ ዓመታት የሚቆጠር የመስኖ እርሻ ልምድ ለምቶ እራሳቸውን ከመመገብ አልፈው የዳበረ ኢኮኖሚ ገንብተውበታል። አባይን ወደ ምዕራብ የግብፅ በረሃ ቀይሰው በመውሰድ ተጨማሪ 1.2 ሚሊዮን ሄክታር በረሃ ለማልማት መንቀሳቀስ ከጀመሩ ቆይተዋል።በዚህ ምዕራባዊ ከተማ ከአንድ ሚሊዮን ሕዝብ በላይ የሚኖርበት ዘመናዊ ከተማ እየተገነባ ነው። የሲናይንም በረሃ ለማልማት በዓመት 4.5 ቢሊዮን ሜትር ኩብ የአባይ ውኃ የሚያስተላልፍ ቧንቧ ዘርግተዋል። የመስኖ ሥራቸውን ለማካሄድ ያስቻላቸውም ታላቁ የአሳዋን ግድብ ነው።ግድቡ 162 ቢሊዮን ሜትር ኩብ ውኃ የማከማቸት አቅም አለው። በክረምት ወራት ከኢትዮጵያ የሚፈሰውን ውኃ አጠራቅመው በመያዝ በሰከንድ 1500 ቶን ውኃ እየለቀቀ በረሃውን ያለማል። ይህም ሆኖ በግብፆች ዕቅድ ተጨማሪ በረሃ ለማልማት 15ቢሊዮን ሜትር ኩብ ውኃ ተጨማሪ ያስፈልገዋል። ለዚህም የተለያዩ
ፕሮጀክቶች አስጠንተዋል። ጥናቱ ተጠናቆ ግንባታውም ተጀምሮ የነበረው አንዱ ፕሮጀክት በደቡብ ሱዳን ክልል ያለው የጀንገሌ ካናል ፕሮጀክት ነበር። የናይል ወንዝ በደቡብ ሱዳን ሱድ እየተባለ
የሚጠራውን ረባዳና ረግረግ ሰፊ መሬት አቋርጦ ያልፍል።ወንዙ በክረምት ከአፍ እስከ ገደብ ሲሞላ ግደቡን ጥሶ ለጥ ወዳለው ሜዳ መፍሰስ ይጀምራል።ግድቡን አልፎ የተንጣለለው ውኃ ተመልሶ ወደ ወንዙ ሊገባ ስለማይችል፤እንደተንጣለለ ይደርቃል።ይህም በፀሐይ ሙቀት እየተነነ ይጠፋል። ታዲያ ግብፃውያን የጀንግሌ ካናልን ፕሮጀክት ያጠኑትና ሥራውንም የጀመሩት በትነት የሚባክነውን ውኃ
በማግኘት የናይልን ውኃ መጠን 10% ከፍ ለማድረግ ነበር።
1ኛ የጀንግሌ ካናሉ ግንባታ የተጀመረው የደቡብ ሱዳን ነፃ አውጪ ድርጅት የነፃነት እንቅስቃሴ በጀመረበት ወቅት ስለነበር ፕሮጀክቱ ሳይገፋ አገራችን ይደርቃል፣ ኢኮሎጂውም ይለወጣል፣ በማለት
ኤስ .ፒ .ኤል. ኤም ፕሮጀክቱ ላይ ጥቃት በመሰንዘር አጨናገፈው።
2ኛ ተጨማሪ ውኃ ለማግኘት ያስችላል ተብሎ የተጠናው ሌላው ፕሮጀክት ደግሞ በኢትዮጵያ ትልልቅ ግድቦች መገንባትና የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ነው። ግብፅ በረሃማ አገር በመሆኗ የፀሐይ
ሙቀት ያጠቃታል፤በዚያ የተነሣ በአገራቸው ከተገነባው ቃላቁ የአስዋን ግድብ በፀሐይ ሙቀት ብቻ በትነት ከተከማቸው ውኃ 12% ይባክናል።ይህ በጣም የሚያሳስባቸው ጉዳይ ነው። ብዙ ውኃ ሊይዝ የሚችል ሌላ ትልቅ ግድብ ለመገንባት የሚቻለበት ቦታ ስለሌላቸው ተጨማሪ ውኃ በሃገራቸው ውስጥ ለማከማቸት ያላቸው ዕድል በጣም የመነመነ መሆኑን ተረዱት። በዚህ የተነሣ ጥረታቸውን በኢትዮጵያ ላይ አድርገዋል።በደጋው ኢትዮጵያ ትላልቅ ግድቦች ለገነቡባቸው የሚችሉበት ቦታዎች በርካታ ናቸው። በሚገደቡት ግድቦች የሚከማቸው ውኃ በትነት የመባከን አደጋ አያጋጥመውም።ውኃው ሳይባክን ለብዙ ጊዜ ተጠብቆ የመቆየት ዕድል አለው።ኤሌክትሪክ ለማምረት እየተባለ ከሚገነቡት ግድቦች ከሚለቀቀው ውኃ ምን ያህል ተጨማሪ ውኃ ሊገኝ እንደሚችል ግብፃውያን አስጠንተው ውቀውታል።
በጥናቱ መሠረት በኢትዮጵያ 23 ትላልቅ ግድቦችን በአባይ መጋቢ ወንዞች ላይ መገንባት የሚቻልባቸው ቦታዎች ተለይተው ታውቀዋል፤መነሻ ጥናት ተካሄዶባቸዋል፤እንደጥናቱ በእነዚህ ቦቻዎች በሚገነቡ ግድቦች ብዙ ቢሊዮን ሜትር ኩብ መጠን ያለው ውኃ ይከማቻል።ከዚያም በያንዳንዱ ግድብ የሚተከሉት የኤሌክትሪክ ማመንጫ ተርባይን ለማሽከርከር ውኃ ይለቀቃል።የአባይ ወንዝ በሚሞላበት ወቅት የአገራችንን ድንበር አልፎ ሱዳን ሲገባ የሚያፈሰው የውኃ መጠን 400 ሜትር ኩብ ውኃ በሰኮንድ ሲሆን አባይ ደረቀ በሚባልበት በበጋው ወቅት ደግሞ 4 ሜትር ኩብ ውኃ በሰኮንድ ይፈሳል።
ልዩነቱን አጢኑት በበጋው የሚፈሰው በአንድ መቶ ጊዜ ይቀንሳል።ከዚህ ሁኔታ መገንዘብ የሚቻለው በሱዳንም ሆነ በግብፅ በክረምት ወራት ከኢትዮጵያ የሚፈስላቸውን ውኃ ገድበው በመያዝ በበጋ ወራት እየለቀቁ መጠነኛ የእርሻ ሥራ ከማካሄድ ውጭ የመስኖ እርሻ እንቅስቃሴ አያካሄዱም ማለት ነው። በኢትዮጵያ ግድቦች ተገንብተው ውኃ እየለቀቁ ተርባይኖችን ማሽከርከር ሰንጀምር ግን ይህ
ሁኔታ ሙሉ በሙሉ ይለወጣል። ከተጠኑት 23 የግድብ ሥፍራዎች ውስጥ አነስተኛ ውኃ የማከማቸት አቅም ያላቸው አራት ግድቦች ቢገነቡና በየአንዳንዱ ግድብ ኤሌክትሪክ ለማመንጨት፤ አራት አራት
ተርባይኖች ቢተከሉና እነዚህን ተርባይኖች ለማሽከርከር 20 ሜትር ኩብ ውኃ በሰኮንድ ቢለቀቅ ሱዳንና ግብፅን አባይ ሲደርቅ 80 ሜትር ኩብ ውኃ በሰኮንድ ያገኛሉ ማለት ነው።
ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ብቻ ለማምረት ፈልጋ ግድብ ከገደበችና ተርባይኖችን ለማሽከርከር አንድ ጊዜ ውኃ መልቀቅ ከጀመረች በኋላ ውኃውን በከፊል ወይም በሙሉ ለመስኖ እርሻ ልማት መጠቀም
ብትሞክር የሱዳንና የግብፅን ሕዝቦች በረሃብ ፈጀች፤ የአባይን አቅጣጫ ቀየረች፤ በሚል ሰበብ ለጦርነት መነሳታቸው አይቀርም። በዓለም አቀፍ ደረጃም እንድትወገዝ ፓለቲካዊና ኤኮኖሚያዊ ጫና
እንዲወድቅባት ያደርጋሉ።
በዚህ ምክንያት በአባይ ወይም በአባይ ገባር ወንዞች ላይ ግድብ ገንብተን የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ከመጀመራችን በፊት ውሎ አድሮ ኢትዮጵያን የሚጎዳ ሁኔታ አለመፍጠሩን ከብዙ አቅጣጫዎች መመርመር አለብን። እንደሚታወቀው የኤሌክትሪክ ኃይል ለማንኛውም አገር ዕድገትና ሥልጣኔ ወሳኝ ኃይል ነው። ኃይል እንደመሆኑ ሁሉ ኢትዮጵያም የኢሌክትሪክ ኃይል በከፍተኛ ደረጃ ያስፈልጋታል። በቀላል መንገድ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማግኘት ደግሞ ያላትን የውኃ ኃይል መጠቀም ይኖርባታል። በውኃው ኃይል ኤሌክትሪክ ስናመርት ግን ተርባይኖቹን የሚያሽከረክረው ውኃ ተለቆ የሚሄድ ሳይሆን ለመስኖ ልማት ላይ መዋል ይኖርበታል።ግድብ ፣ገድበን ኤሌክትሪክ ለማመንጨት ስናስብ፣ የሚለቀቀው ውኃ እታች ወርዶ ማሳውን እንዲያጠጣ ተደርጎ መታቀድ ይኖርበታል።በዚህ አኳኋን ካልታቀደ በከፍተኛ ወጪ ያጠራቀምነውን ውኃ ያለምንም ክፍያ ለሱዳንና ለግብፅ አሳለፈን ሰጠን ማለት ነው። ከዚህ ግንዛቤ በመነሣት በደርግ ጊዜ የመልካ ዋከና የኤሌክትሪክ ማመንጫ ጣቢያ ሲገነባ በተጓዳኝ በኡጋዴን ጎዴ አካባቢ ተርባይኑን ለማሽከርከር የሚለቀቀው ውኃ ተጠልፎ እስከ 50ሺ ሄክታር የመስኖ እርሻ እንዲያጠጣ ታቅዶ ኤሌክትሪክ ማመንጨት ሥራ እንደጀመረ የ20ሺ ሄክታር ማሳ እንዲያለማ ተደርጎ ነበር።
በሌላ በኩል ከልማት ጋር ሣይያያዝ የተገነባው የፊንጫ ኤሌክትሪክ ማመንጫ ጣቢያ የሚለቀቀው ውኃ ያለጥቅም መፍሰሱን በመመልክት ለስኳር ፋብሪካ ጥሬ ዕቃ የሚሆን ሸንኮራ አገዳ በ10ሺ ሄክታር ማሳ እንዲያለማ ታቅዶ ሥራው ተጀምሮ ነበር።የጣናን ሃይቅ በማሳደግ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት ሲወሰን በተመሳሳይ መንገድ የሚለቀቀውን ውኃ በመጠቀም በበለስ ሸለቆ እስከ 100ሺ
ሄክታር የመስኖ እርሻ ለማት ለማካሄድ እንቅስቃሴው ተጀምሮ ነበር።በሌሎች አካባቢዎችም የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት በሚታሰብበት ጊዜ የሚለቀቀው ውኃ ጥቅም ላይ ውሎ የአገራችንን ኤኮኖሚ ለማሳደግና በምግብም ራሳችንን እንድንችል እንዲረዳ ጎን ለጎን መታቀድ ነበረበት።
ከመስኖ ልማት ጋር ሳይያያዝ ግድብ መገንባትና ኤሌክትሪክ ማመንጨት የግብፅን ፍላጎት በፍቃደኝነት ማሟላት ማለት ነው።ግብፅ ሙሉ ወጪውን በመሸፈን በኢትዮጵያ ትላልቅ ግድቦችን ለመገንባት የኤሌክትሪክ ኃይል በማመንጨት የሚለቀቀውን ውኃ ሳይቀናነስ እንድትወስድ ማረጋገጫ ቢሰጣት ያለ ማቅማማት እንደምትስማማ በእርግጠኛነት መናገር ይቻላል።ግብፅ ውኃውን ከምንም ነገር አስበልጣ ስለምትፈልገው በኢትዮጵያ ግድቦች ቢገነቡና ኤሌክትሪክ በቻ እንዲመረት ቢደረግ ምንም ዓይነት ተቃውሞ አታሰማም።ለማስረጃ ያህል በጣና ሃይቅ የአባይ ወንዝ መውጪያ ላይ የተወሰነ ግድብ ተገንበቶ የጣና ውኃ መጠን እንዲጨምር ከተደረገ በኋላ በምዕራብ አቅጣጫ ጣና ተሸነቁሮ ውኃውን ቁልቁል በመልቀቅ ተርባይን እንዲያሽከረከር ተደርጎ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ከተጀመረ
ቆየት ብሏል፤ የተከዜ ወንዝ ተገድቦ የተጠራቀመው ውኃ እየተለቀቀ ኤሌክትሪክ ማምረት ከተጀመረ ዓመታት ተቆጥረዋል።ታዲያንስ ግብፅች የተጠራቀመ ውኃ በጣም በሚያስፈልጋቸው በድርቅ ጊዜ
ሳይቋረጥ የሚያገኙት መሆናቸውን ስለሚያውቁ ለምን በጣና ሃይቅ ኤሌክትሪክ ይመረታል፣በተከዜ ወንዝ ላይ ግድብ ተገንብቶ ኤሌክትሪክ ማመንጨት ለምን ተጀመረ ጥቅማችንን ይጎዳል ብለው አልተናገሩም ፤ ተቃውምም አላሰሙም፤ ምክንያቱ ተጠቃሚዎቹ እነሱ ናቸውና።
አባይን አስመልክቶ ይህን ያህል ከተነጋገርን ስለ’’ ታላቁ የሚሊኒዮም ግድብ’’ አንዳንድ ነገር ብናነሳ መልካም ይመስለኛል።እንደተነገረን ግድቡ የሚገነባው በቤኒሻንጉል ክልል ከሱዳን ድንበር 17 ኪሎሜትር ርቀት በሚገኝ ቦታ ላይ ነው። ግድቡ 62 ቢሊዮን ሜትር ኩብ ውኃ ይይዛል።የግንባታው ወጪ 80 ቢሊዮን ብር ሲሆን በኢትዮጵያ ሕዝብ መዋጮ ይሸፈናል ተብሏል።በግድቡ ውኃ ከ6ሺ በላይ ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ይመነጫል።እንግዲህ ከግድቡ ኢትዮጵያ የምታገኘው ጥቅም የኤሌክትሪክ ኃይል ብቻ መሆኑ ነው።ግብፅና ሱዳን ግን ተጨማሪ ውኃ ያገኛሉ። ኤሌክትሪክ ኃይል ለማምረት ምን ያህል ተርባይኖች እንደሚተከሉ አይታወቅም።
6000ኪሎ ዋት ኤሌክትሪክ ለማምረት አንዱ ተርባይን 50 ሜጋ ዋት የሚያመነጭ ቢሆን እንኳን ከ 100 ተርባይኖች በላይ መተከል ይኖርባቸዋል።አንዱን ተርባይን ለማሽከርከር 5 ሜትር ኩብ ውኃ በሰኮንድ መልቀቅ ያስፈልጋል ቢባል እንኳን 100 ተርባይኖችን ለማሽከርከር 500 ሜትር ኩብ ውኃ በሰኮንድ መልቀቅ ያስፈልጋል ማለት ነው። አባይ ሲሞላ በክረምት ወራት ከተጠራቀመው ውኃ
ተርባይኖችን ለማሽከርከር መልቀቅ አስፈላጊ አይሆንም። ወንዙ በግድቡ ላይ ሰለሚያልፍ እግር መንገዱን ተርባይኖቹን እያሽከረከረ ያልፋል።በግድቡ የተከማቸውን ውኃ መልቀቅ የሚያስፈልገው በበጋ ወራት አባይ ሲደርቅ ነው።ተርባይኖች ከዓመት ዓመት መሽከርከር ሰለአለባቸው ከግድብ እየተለቀቀ የሚወርደው ውኃ በቋሚነት ያስፈልጋል። በዚህ አሠራር በክረምት ወራት አባይ ሲሞላ ከሚገኘው
የውኃ መጠን የበለጠ ግብፅና ሱዳን በበጋ ወራት ያገኛሉ ማለት ነው።ይህ መጠን በተፈጥሮ ከሚያገኙት በእጅጉ ይበልጣል።በተፈጥሮ የሚያገኙት ውኃ እየቆጨን እያለ እያንዳንዱ እትዮጵያዊ
እየተመጠጠ በተሰበሰበው ገንዘብ ትልቅ ግድብ ገድበን ውኃ አጠራቅመን በተጨማሪ መስጠታችን እንደሆነ የኢትዮጵያ ሕዝብ የተረዳው ወይም የተገነዘበው አይመስልም።ሕዝቡ የሚመስለው ወንዙ ተገድቦ ለልማት ውሎ ከረሃብ እንደሚወጣ ነው።
በጥቅሉ አባይ ሊገደብ ነው እየተባለ ይነገረዋል።በሚገደበው ግድብ ከሚከማቸው ውኃ አንድ ሄክታር መሬት እንኳን በመስኖ እንደማይለማ አይነገረውም። ከታላቁ ግድብ ጋር ምንም የመስኖ ልማት ፕሮግራም አልተያዘም። ወደፊት ውኃውን ለልማት እናውለዋለን እንዳይባል ከግድቡ በታች ለእርሻ የሚሆን መሬት የለም። በርባራ አካባቢ ነው፤ ከዚያም ቢሆን ውኃው ተለቆ ተርባይን ከአሽከረከረ በኋላ በቀጥታ ሱዳን ውስጥ ይገባል።ምክንያቱም በሱዳን ጠረፍና በግድቡ መሐል 17 ኪሎ ሜትር ብቻ እርቀት ነው ያለው።የውኃ ጉዳይ ለግብፅ የመኖር ወይም ያለመኖር ጥያቄ ነው። ከኢትዮጵያ
የምትወጣዋን ውኃ ትቆጣጠራለች። ይህ አዲሱ ግድብ ሥራው ተጠናቆ ኤሌክትሪክ ለማመንጨት ውኃ መልቀቅ ከጀመረ በኋላ ውኃውን ማቆም አይቻልም።ምክንያቱም ከዓመት ዓመት የሚፈሰው ውኃ እየተለካ ይመዘገባል።
ኤሌክትሪክ ማምረት አቆማለሁ ብላ ኢትዮጵያ ብታቆም ጦርነት እንደማወጅ ተቆጥሮ በግብፅና ከሱዳን ጋር ውጊያ መግጠምን ያስከትላል።በመሆኑም ዛሬ የሐገር ፍቅር ስሜታችንን ቀስቅሰው በሚገባ ግልፅ ሳይሆንልን የግድቡን ሥራ መደገፋችን ገንዘብ ማውጣታችን ወደፊት መዘዝ ያስከትልብናል። ‘አባይ ሊያለማን ወይስ ሊያጠፋን’ ብለን መጠየቅም ይኖርብናል። ግድቡ የመስኖ ልማት
ጋር ቢያያዝ ከረሃብ ከድህነት ልንወጣ ስለምንችል ማንኛውንም ዓይነት መስዋዕትነት ሕዝብ ቢከፍል ተገቢ በሆነ ነበር፤ ከሕዝብ ጎን ጋር ያልተዛመደ ግዙፍ ሥራ መወጠኑ በኋላ አሁን ለሚደረገው የሚያስጠይቅ ሊሆን ይችላል።
የሚገርመው ደግሞ ከዚህ ድንቅ ከተባለው ግድብ የሚገኘው የኤሌክትሪክ ኃይል ለሱዳንና ለግብፅ ይሸጣል መባሉ ነው።የሚሸጠውም በጣም በአነስተኛ ዋጋ ነው።በአሁኑ ጊዜ ለሱዳን አንድ ኪሎዋት የሚሸጠው በስድስት ሳንቲም የአሜሪካን ሲሆን፣ሱዳን በሃገሯ እስከአሁን የምትሸጠው ሃያ ስድስት ሳንቲም የአሜሪካ ነው።በዚህ ዓይነት የ ሃያ ሳንቲም ትርፍ ታገኛለች ማለት ነው። ሱዳንና ግብፅ በውኃችን የተነሣ ጠላት አድርገውን ብዙ ጎድተውናል።ወደፊትም ይጎዱናል። ሃገራችንን ለመከፋፈልና ለመገነጠል ለተሰለፉት ዛሬ ኤርትራን ገንጥለው ለሚያስዳድሩትና የኢትዮጵያን ሕዝብ በዘር በጎሣ ከፋፍለው ለሚመሩት ቡድኖች አጋር ሆነው ቆይተዋል።’አንዳንዴ የአባይ ግድብ ለነዚህ ሃገሮች ወሮታ ይሆን’ ብለው የሚጠይቁ ሃገር ወዳዶች አሉ። ታዲያ በዚህ የጠላትነት መንፈስ እየተመለከቱን እያሉ ኤሌክትሪክን ያህል የልማት ኃይል አቅራቢ ሆነን እንዲያድጉና እንዲበለጽጉ በወታደራዊ ቴክኒክና ቴክኖሎጂ እንዲዳብሩ መርዳታችን እንደሆነ መገንዘብ አልቻልንም።
ኤሌክትሪክ ለጎረቤት አገሮች የመሸጥ ሐሣብ በደርግ ዘመን ተነስቶ ነበር።የጦር መሣሪያ ከማስታጠቅ አይተናነስም ተብሎ ሐሣቡ ውድቅ ተደርጎ ነበር።ኢትዮጵያ የሚያስፈልጋትን የኤሌክትሪክ ኃይል ሌሎች ወንዞች ማመንጨት ይቻላል ተብሎ፤በግልገል ግቤ በርካታ ግድቦች ተገድበው በቂ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚመረትበት ቦታ የሌለ ይመስል ታላቁ ግድብ ኤሌክትሪክ በኤሌክትሪክ ያደርገናል ችግራችን በሙሉ ይወገዳል፤እየተባለ የሚካሄደው አዳናጋሪ ፕሮፓጋንዳ ወደፊት ሃቁ መታወቁ አይቀርም።እኔ እንደምገምተው ከግብፅ ጋር ስምምነት አድርገው በጋራ የነደፉት ፕሮጀክት
ይመስለኛል።በጥናቱም ላይ የግብፅ እጅ ይኖርበታል የሚል ግምት አለኝ።የዚህ ግድብ ሥራ ግብፅን የሚጎዳ ቢሆን ኖሮ በዓለም ከፍተኛ ጩህትና የፖለቲካ ትረምስ ይሰማ ነበር። ግብፅ ያለችው ነገር ቢኖር ቴክኒካል ወረቀቶቹን ስጡኝ ነው፤ይህም ለማለት ያህል እንጂ ቴክኒካል ጥናቱ ቀድሞ በእጇ ይገኛል።
አሁን ለግብፅና ለሱዳን የሚጠቅም ሥራ ኢትዮጵያ በማንቀሳቀሷ ከዚህ በፊት በአባይ ጉዳይ ላይ አልነጋገርም፤ ስምምነትም በአዲስ መልክ አላደርግም ሲሉ የነበሩ ሁለቱ አገሮች በጉዳዩ ላይ ንደራደራለን የሚል አቋም ይዘዋል።የኢትዮጵያ ሕዝብ ገንዘብ ማውጣቱን እንዲቀጥል ብቻ አለፍ አለፍ እያሉ በለሆሳስ የግድቡ ሥራ አሳስቦናል ይላሉ። ዘለዓለማዊ የሃገር መታደግና ዕድገት ሳይሆን ዘለዓለማዊ ጠንቅ እንዳይተከልባት ለምን? ለማን? እንዴት? የሚለው የሃገር ጥቅም መለኪያ፣ሊተኮርበት ይገባል።ከራስ እያወለቁ ጠላትን እያስታጠቁ ግንባታ ስንኩል ስለሆነ አባይ መዘዝ ሳይሆን ሕዝብ አገዝ እንዲሆን ሁሉም ዕድሉ አሁን መሆኑን መገንዘብ ይገባዋል።

የመንግስቱ ኃይለማርያም አጃቢ “የሌ/ኮ መንግስቱ ያልተነገሩ ሚስጢሮች”የተሰኘ መጽሐፍ አሳትመው በተኑ

$
0
0

mengistu haile mariam(ዘ-ሐበሻ) ዙምባብዌ በስደት የሚገኙት የቀድሞው ፕሬዚዳንት መንግስቱ ኃይለማርያም በስማቸው የሚወጣው መጽሐፍ ቁጥር በ10ሮች የሚቆጠሩ ሲሆኑ እርሳቸው ግን አንድ መጽሐፍ ብቻ አውጥተዋል። “የመንግስቱ ትዝታዎች”። ዛሬ ደግሞ በአዲስ አበባና በመላው ኢትዮጵያ የፕሬዚዳንቱ የቀድሞ አጃቢ ያሳተመውና “የሌ/ኮ መንግስቱ ምስጢሮች” የተሰኘ መጽሐፍ መሰራጨቱን የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች አስታውቀዋል።
በቀድሞ የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት መንግስቱ ሃይለማርያም የቤተመንግስትና የሥራ ህይወት ዙሪያ እንደተጻፈ የሚነገርለት ይኸው “የሌ/ኮ መንግስቱ ያልተነገሩ ሚስጥሮች” የተሰኘው መፅሀፍ የተጻፈው የቀድሞው ልዩ ኃይል አባል እና የፕሬዝዳንት መንግስቱ አጃቢ በነበሩት እሸቱ ወንድሙ ወልደስላሴ እንደሆነ ታውቋል። ይህ መጽሐፍ ባለ 120 ገፅ እንደሆነ የገለጹት የዘሐበሻ ዘጋቢዎች የመጽሐፉ ደራሲ ለ14 ዓመታት በልዩ ጥበቃነት መስራታቸውን አስታውቀዋል። እኚሁ የቀድሞው የመንግስቱ ኃይለማርያም አጃቢ ካሁን ቀደም “ህይወት በመንግስቱ ቤተመንግስት” በሚል ርዕስ ሁለት ቅፅ መጻሕፍትን ያሳተሙ መሆኑ ይታወሳል።

የፀረ ሽብርተኝነት ህጉ ለምን አያስፈራ? (በግርማ ሠይፈ ማሩ)

መሲ ባንቺም ኮራን –ከነብዩ ሲራክ


ቅዱስ ጊዮርጊስ በቱኒዚያው ክለብ 3 ለ 1 ተሸነፈ

$
0
0

St George
(ዘ-ሐበሻ) በአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ እየተካፈለ የሚገኘው የቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብ በደጋፊው ፊት በቱኒዚያዊ ክለብ ሲ ኤስ ሰፋክሲን 3ለ1 ተሸነፈ። በውድድሩ በከቱኒዚያና ማሊ ክለቦች ጋር ተድልድሎ በመጫወት ላይ የሚገኘው ቅዱስ ጊዮርጊስ ዛሬ ኦገስት 18፣ 2013 በምድቡ መሪ ሲ ኤስ ሰፋክሲን 3ለ1 በመሸነፍ ደጋፊውን አንገቱን አስደፍቷል።

ሲ ኤስ ሰፋክሲን በምድቡ ያደረጋቸውን ሶስት ጨዋታዎች በማሸነፍ 9 ነጥብ እየመራ የሚገኝ ሲሆን ቅዱስ ጊዮርጊስ ስታዲ ማሊን አሸንፎና በኢቶልዲ ሳህልና ሲ ኤስ ሰፋክሲ ተሸንፎ በ3 ነጥብ ይዟል፡፡ በደጋፊው ፊት የቱኒዚያውን ሲ ኤስ ሰፋክሲን የገጠመው ጊዮርጊስ ጨዋታው ከባድ እንደሚሆንበት የስፖርት ተንታኞች ይናገራሉ።

የ ዶክቶር ገመቹ ከእውነታው የራቀ የተሳሳተ መረጃ

የድምጻዊ ኢዮብ መኮንን ቃለ ምልልስ ቪድዮ –ለትውስታ

$
0
0

ይህን ቃለ ምልልስ ያደረገው የቀድሞው የማህደር ጋዜጣ ዋና አዘጋጅና አሳታሚ ወርቅአፈራው አሰፋ ነው። ስለኢዮብ ግንዛቤ ሊሰጣችሁ ይችላልና ይመልከቱት።

“የሚያንጽ ካልሆነ በስተቀር ኔጊቲቭ የሆነ ዘፈን መዝፈን አልፈልግም”

ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬና ዘሪሁን ገ/እግዚአብሔር ሊፈቱ ይሆን?

$
0
0

እስር ቤት የምትገኘው ጋዜጠኛ ሒሩት ክፍሌ

እስር ቤት የምትገኘው ጋዜጠኛ ሒሩት ክፍሌ

ዘጋቢ ጋዜጠኛ ስለሺ ሐጎስ

በእነ ኤልያስ ክፍሌ መዝገብ በሽብርተኝነት ክስ ተፈርዶባቸው በማረሚያ ቤት ከሚገኙት አራቱ ኢትዮጵያውያን መሀከል ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ፣ ወ/ሮ ሂሩት ክፍሌና አቶ ዘሪሁን ገ/እግዚአብሄር በ2004 ዓ.ም ይቅርታ የጠየቁ ሲሆን ምላሽ ሳያገኙ ለረዥም ጊዜ መቆየታቸው ሲያነጋግር ሰንብቷል፡፡ በተለይ ሲውዲናውያኑ ጋዜጠኞች ከኢትዮጵያውያኑ ጋር በተመሳሳይ ወቅት ይቅርታ ጠይቀው አፋጣኝ ምላሽ ማግኘታቸውና በአንጻሩ የእነውብሸት ይቅርታ ከአመት በላይ መዘግየቱ ተገቢ አለመሆኑ ሲገለጽ ቆይቷል፡፡

ከአንድ አመት በላይ ቆይታ በኋላ ሐምሌ 25 2005 ዓ.ም የይቅርታ ቦርድ ጽ/ቤት ማህተም አርፎበት ለወ/ሮ ሂሩት ክፍሌ በተላከ ደብዳቤ የይቅርታ ጥያቄያቸው ለፕሬዝዳንቱ ቀርቦ ውድቅ መደረጉ ተገልጾላቸዋል፡፡ ወ/ሮ ሂሩት ከእነ ውብሸት ጋር ባንድ መዝገብ ተከሰው 19 አመት የተፈረደባቸው ሲሆን የይቅርታ ጥያቄውንም ያቀረቡት በተመሳሳይ ወቅት ነው፡፡ ይሁን እንጂ ወደ ህትመት እስከገባንበት ጊዜ ድረስ ለጋዜጠኛ ውብሸት ታዬና ለአቶ ዘሪሁን ገ/እግዚአብሔር የደረሳቸው ደብዳቤ አለመኖሩን አረጋግጠናል፡፡

የወ/ሮ ሂሩት ይቅርታ በፕሬዝዳንቱ ውድቅ መደረጉን አስመልክቶ ልጃቸው ፍጹም መሰለ እናቱ ከተፈረደባቸው በኋላ ይግባኝ ከማለት ይልቅ ይቅርታ መጠየቅ የወሰኑበት ምክኒያት የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ በፓርላማ ቀርበው “እንኳን ሀገር ውስጥ ያሉት ውጪ ያሉትም ቢሆኑ ዛሬ ይቅርታ ከጠየቁ ከነገ ጀምሮ ነጻ ናቸው” የሚል ቃል መግባታቸው እንደሆነ ገልጾ ይግባኝ የምንልበት አማራጭም አልፎ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከገቡት ቃል በተቃራኒ ይቅርታው ውድቅ ተደርጓል መባሉ እንዳሳዘነው ተናግሯል፡፡ ፍጹም አክሎም “ለሲውዲናውያን የተሰጠው ዕድል ለኢትዮጵያውያን ጨርሶ ይከለከላል የሚል ዕምነት ስለሌለን የይቅርታ ጥያቄውን በድጋሚ በሽማግሌዎች በኩል እናቀርባለን” ብሏል፡፡

የአቶ መለስ ዜናዊን ሙታመት አስመልክቶ በርካታ እስረኞችን ለመፍታት መንግስት በእንቅስቃሴ ላይ እንደሚገኝ ያረጋገጡት ምንጮቻችን ጋዜጠኛ ውብሸትና አቶ ዘሪሁን ደብዳቤ ያልደረሳቸው ከሚፈተቱት እስረኞች ዝርዝር ውስጥ ገብተው ሳይሆን እንደማይቀር ግምታቸውን አስቀምጠዋል፡፡

Health: ተፈጥሯዊ –ብጉር ማጥፊያዎች

$
0
0

ከሊሊ ሞገስ
እዚህ ሚኒሶታ አንዳንድ ሴቶች የሞንግ ወይም የቻይና ገበያ በመሄድ የፊት ሳሙናዎችን እና ቅባቶችን በመግዛት ቡግራችንን እናጠፋለን፤ መልካችንን እናቀላለን በሚል ካለ ሃኪም ትዕዛዝ ይህን ሳሙናና ቅባት በመጠቀም ፊታቸውን ሲያበላሹ አስተውለናል። አንዳንድ ሴቶችም ወደ ዘ-ሐበሻ በመደወል “ሳሙናውና ቅባቱ ፊታችንን አበላሸው፣ አዥጎረጎረን፣ ቡግር አወጣብን” ሲሉ በ እኛ የደረሰው እንዳይደርስ ምክራችንን አስተላልፉልን ብለውናል። የዘ-ሐበሻ የጤና አምድ ሁልጊዜም ሰዎች ሳሙናም ሆነ ፊት የሚያጠራ ቅባት ከመቀባት በፊት ከቆዳ ሃኪም ጋር መነጋገር እንደሚያስፈልግ ስትመክር ቆይታለች። የኤሲያኖች ቆዳ እና የሃበሾች ቆዳ አንድ አይነት አይደለም። እነርሱን ስለጠቀማቸው ሃበሾችን ይጠቅማል ማለት አይደለም። በመሆኑም የዚህ ችግር ስለባዎች ወደ ሃኪም እንዲሄዱ በመምከር ተፈጥሯዊ የቡግር ማጥፊያዎችን እንጠቁማለን። ይህንን ያዘጋጀነውም ለግንዛቤዎ እንዲጠቅም እንጂ ሁልጊዜም ቢሆን አንድ ነገር ከማድረግ በፊት ሃኪምዎን ማማከርዎን አይርሱ።
health
ቅባታማ ምርቶችን ያስወግዱ፡- ከፍተኛ የቅባትነት ይዘት ያላቸውን የፀጉር ቅባቶች ጨምሮ የፊት ማውዣዎች (moisturizers) እና ዘይታማ ማጽጃዎችን አይጠቀሙ፡፡
የፊትዎን ንፅህና ይጠብቁ፡- ፊትዎን የእጅዎ መዳፍ ላይ በፍፁም ማሳረፍ አሊያም በተደጋጋሚ ፊትዎን መዳሰስ አይኖርብዎትም፡፡ ፀጉርዎን አዘውትረው በሻምፖ ይታጠቡ፣ ነገር ግን ፊትዎን መንካት የለቦትም፡፡
የአካል እንቅስቃሴ ያዘውትሩ፡- በመካከለኛ ደረጃ የአካል እንቅስቃሴ ማዘውተርዎ የደም ዝውውርን ከማቀለጣጠፉም በላይ መርዛማ ንጥረ ነገሮች ከሰውነትዎ እንዲወገዱ ለማድረግ ይረዳል፡፡
ከጭንቀት ነፃ ይሁኑ፡- በርካታ ጥናቶች ጭንቀት ብጉርን ከማባባሱም በላይ የቆዳ ጤንነት ችግር ላይ እንዲወድቅ ያደርጋል ይላሉ፡፡ ጭንቀት ሲያድርብዎ ከወዳጆችዎ ጋር ይማከሩ፣ የሚወዱትን ሙዚቃ ያዳምጡ፣ አሊያም ዘና ለማለት ይሞክሩ፡፡ የእግር ጉዞ ማድረግዎ ዘና እንዲሉ ያደርጋል፡፡ እነዚህን ጨምሮ ሌሎች ከጭንቀት ነፃ እንዲሆኑ የሚረዱም ነገሮችንም ይከውኑ፡፡
በቂ የፀሐይ ብርሃንና ኦክስጅን፡- የሐይ ብርሃን ቫይታሚን ዲን ለሰውነታችን ይሰጣል፡፡ ይህ ቫይታሚን ለቆዳ ጤንነት በጣም አስፈላጊ ነው፡፡ ንፁህ አየርና የፀሐይ ሙቀት ጭንቀትን በመቀነስ በቆዳ ውስጥ የኦክስጅን መጠን እንዲጨምር ያደርጋሉ፡፡ ይሁን እንጂ ፀሐይ ላይ ለረጅም ጊዜ በመቆየት ቆዳዎ እንዲቆጣ ማድረግ አይኖርብዎትም፡፡
ብጉርን ለመቀነስና ለማጥፋት ይረዳሉ ተብለው የሚመረቱ ዘመናዊ ባህላዊ ቅባቶችና ዘይቶች በርካታ ናቸው፡፡ ብዙዎቹ ለጊዜው ችግሩን ያጠፉ ቢመስሉም ቅባቱ ካለቀ በኋላ ግን ብጉሩ ተባብሶ ሊቀጥል የሚችልበት ዕድል ሰፊ ነው፡፡ ከባህላዊም ሆነ ዘመናዊ ህክምናዎች ባልተናነሰ ተፈጥሯዊ የሚባሉት ዘዴዎች ከፍተኛ የሆነ ጠቀሜታ ይሰጣሉ፡፡ ጥቂቶቹ የሚከተሉት ናቸው፡፡
ብጉሮችን በጣትዎ አይነካኩ፡- ፊትዎ ላይ የሚታዩትን ብጉሮች በጣትዎችዎ መጫን ወይም ማሸት አይገባም፡፡ እንዲህ በሚያደርጉበት ጊዜ የፈሳሹን (sebum ይሰኛል) መጠን እንዲጨምር ከማድረግዎም በላይ ከቆዳዎ ስር ያለው አካል (membrane) እንዲቀደድ ያደርጋሉ፡፡ ኢንፌክሽኑና ፈሳሹ በቆዳዎ ስር በመዛመት ሌሎች ብጉሮች እንዲፈጠሩም ምክንያት ይሆናል፡፡ ከሁሉም በላይ በፊትዎ ላይ የማይጠፉ ጠባሳዎች የመከሰት ዕድልን እንዲጨምር ሊያደርጉ ስለሚችሉ ፊትዎን በጣትዎችዎ ማሸትን ያስወግዱ፡፡
ፊትዎን በቀን ሁለት ጊዜ በሳሙና ይታጠቡ፡- ፊታቸው ላይ ብጉር የሚታይባቸው ሰዎች ከሰልፈር (sulfur) የተሰሩ ሳሙናዎችን እንዲጠቀሙ ይመከራል፡፡ ቆዳዎ በተፈጥሮው ባለ ወዝ (oily) ከሆነ benzoyl peroxide የተካተተበት ሳሙና ይጠቀሙ፡፡ ፊትዎን በስፖንጅና በሌሎችም ሻካራ ጨርቆችና ብሩሾች እየሞዠቁ እንዳያጥቡ፡፡
- ብጉሩን ያብሰዋል እንጂ አያጠፋውም፡፡
ፊትዎን ከሁለት ጊዜ በላይ ደጋግመው በማጠብ እንዳያደርቁት መጠንቀቅ ይኖርብዎታል፡፡ የቆዳ ዕጢዎች ፊትዎ የደረቀ ከመሰላቸው ብዙ sebum እንዲመረት በማድረግ ብጉሩ እንዲስፋፋ ምክንያት ይሆናሉ፡፡
ምግብና ብጉር፡- ለበርካታ ሰዎች የምግብ አለርጂ ለረጅም ጊዜ የማይጠፋ ብጉር እንዲፈጠርባቸው ሊያደርግ ይችላል፡፡ ብጉር ፊታቸው ላይ የሚታይባቸው ሰዎች ቅባትና ቅመማ ቅመም የበዛባቸው ምግቦች አብዝተው እንዲወስዱ ይመከራል፡፡ የቅርብ ጊዜ ጥናቶች በወተት ውስጥ የሚገኙ ሆርሞኖችና በባህር ምግቦች ውስጥ የሚገኘው ከፍተኛ የአዮዲን መጠን ብጉርን እንደሚያባብሱ ተደርሶበታል ይላሉ፡፡ ከተቻለ እነዚህ ምግቦች አይወሰዱ፡፡ ከእነዚህ በተጨማሪ ስኳር፣ የወተት ተዋፅኦዎች፣ ለረጅም ሰዓት ሲጠበሱ የቆዩ ምግቦች፣ ስጋ፣ የኦቾሎኒ ቅቤ እና የመሳሰሉት ቅባታማና ዘይታማ ምግቦችን ያስወግዱ፡፡ ከዚህ በተቃራኒው አረንጓዴ ተክሎች፣ የአትክልት ጭማቂና በዚንክ የበለፀጉ ምግቦች ብጉርን ለመቀነስ ይረዳሉ፡፡
ውሃ ይጠጡ፡- ሲባል በመጠኑ በርከት ያለ መሆን ይኖርበታል፡፡ ጄኒፈር ቶደን የተባሉ የብጉር ኤክስፐርት በቀን ስምንት ብርጭቆ ውሃ በመጠጣት ብጉርን መከላከል እንደሚቻል ይመክራሉ፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ውሃ ቆሻሻን ከሰውነታችን ሲስተም ማስወገድ ስለሚችል ነው፡፡ ይህ ደግሞ ሰውነታችን ብጉርን እንዲከላከልና እንዲያድን ይረዳዋል፡፡
ሜክአፖችን አይጠቀሙ፡- የተለያዩ የሜክአፕ ምርቶች ብጉርን ሊያስከትሉ ስለሚችሉ በተቻለ መጠን ባይጠቀሟቸው ይመከራል፡፡ እነዚህ መኳኳያዎች ብጉር እንዲስፋፋ ያደርጋሉ፡፡ የግድ መጠቀም አለብኝ ካሉ ደግሞ መሰረታቸው ውሃ የሆነ (water based) ሜክአፖችን ምርጫዎ ያድርጉ፡፡ የሜክአፕ ብሩሾችዎን በቋሚነት ያጽዱ፤ እንዲሁም ወደ መኝታዎ ከመሄድዎ በፊት ፊትዎንና ሜክአፕ የነካውን አካል ይታጠቡ፡፡
የወይራ ዘይት
- የጓሮ አትክልት መንከባከቢያ ቁሳቁሶችን በቀላሉ ለማጽዳት ያስችላል፡፡
- የቤትና የቢሮ ፈርኒቸር ያሳምራል፡፡
- በቀላሉ ከዓይን ላይ ሜክአፕ ለማስለቀቅ ይረዳል፡፡
- ከማይዝግ ብረት የተሰሩ (stainless steel) ቁሶች እንዲያንፀባርቁ ያደርጋል፡፡
- የካጄት አሊያም የሱሪዎ ዚፕ ተቀርቅሮ አልንቀሳቀስ ካለ የወይራ ዘይት ጠብ ያድርጉበት፡፡
- የቆዳዎን ልስላሴ ይጠብቃል፡፡
- ማንኳራፋትን ያስወግዳል፡፡
- የኩራዝ መብራት ሆኖ ማገልግል ይችላል፡፡
- አንዳንድ ስቲከሮች የተዉትን ማጣበቂያ ያስወግዳል፡፡
- ለጉሮሮ ህመም ፈውስ ይሰጣል፡፡
- የጆሮ ህመምን ያስታግሳል፡፡
- ጺምዎን ከተላጩት በኋላ ጥቂት የወይራ ዘይት ይቀቡት፡፡ ልስላሴው ያስደስትዎታል፡፡
- ጫማዎን ቢጠርጉበት ያሳምርልዎታል፡፡
- ጥሩ የፀጉር ቶኒክ ነው፡፡
- ገላዎን ገንዳ ውስጥ የሚለቃለቁ ከሆነ የወይራ ዘይት ጠብ ያድርጉበት፡፡ S

Viewing all 8745 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>