የትንሣኤ በዓል ሲከበር በተለያዩ ምክንያቶች የተፈናቀሉ ወገኖችን በማሰብና በመደገፍ መሆን እንዳለበት የሃይማኖት መሪዎች አሳሰቡ፡፡ ባሕር ዳር፡ ሚያዚያ 22/2013 ዓ.ም (አሚኮ) የትንሣኤ በዓል ሲከበር በሰላም እጦት ከቤት ንብረታቸው የተፈናቀሉ ወገኖችን በማሰብና በመደገፍ ሊከብር እንደሚገባ ነው የሃይማኖት መሪዎች ጥሪ ያቀረቡት። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሊቀ-ጳጳስ ብፁዕ ካርዲናል ብርሃነ ኢየሱስ ሱራፌል እና የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት ጠቅላይ ጸሐፊ ቄስ ደረጀ ጀምበሩ የትንሣኤ በዓልን አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ብፁዕ ወቅዱስ አቡነማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት
↧