1ኛ/ በሚከተሉት ሃቆች ላይ እንስማማ? ሕዝብ በግዲያ እያለቀ ነዉ። የተረፈዉ በመቶ ሺዎችና በሚሊዮኖች እየተፈናቀለ ይገኛል። ጭፍጨፋዉ በአብዛኛዉ ዘርና ኃይማኖትን እየመረጠ ነዉ፤ ከፍተኛ ሰለባዎች አማራዎችና ኦርቶዶክሶች ናቸዉ። አጣዬ እንዳለች ፈረሰች። የቀረዉ ሰሜን ሸዋ በተመሳሳይ ችግር ዉስጥ ወድቋል። የወለጋዉና የመተከል ዕለታዊ እልቂቶች ለጆሮ የሚሰቀጥጡ ናቸዉ፤ በተለይ የምስኪን እናቶች፤ ነፍሰጡሮች፤ አባቶች፤ ሕፃናትና ወጣቶች እጅግ አስከፊ ሰቆቃዎች። በነዚህ ምክንያቶች ሕዝቡ በነቂስ በሚሊዮኖች እየወጣ ብሶቱን እያሰማ ይገኛል። ጥያቄያቸዉ ቀላል ነዉ፤ አትግደሉን፤አታፈናቅሉን ነዉ የሚሉት። የብሶት መግለጫ እንጂ ተራ ጩሄት አይደለም። በትግራይ የንፁሐን ዜጎች ሰቆቃ እየተባባሰ ይገኛል። በደቡብ ሰላም የለም። በአፋርና በሶማሌ አካባቢዎች ግጭቶች እየተባባሱ ይገኛሉ። የዉስጥ ሰላምና አንድነት ሲናጋ ለዉጪ ታሪካዊ ጠላቶቻችን ያመቻል። በሰሜን ምዕራብ ድንበራችን
↧